TechIn2
1.22K subscribers
1.47K photos
1 video
120 files
500 links
Technology & Innovation Institute (TechIn2), Ethiopia

የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት

ጠቃሚና ወቅታዊ የሆኑ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ፣ ጤና እና ሰብአዊ-ኣቅም ግንባታ(Human Development)መረጃዎችንና ምክሮችን በየእለቱ እናደርሶታለን።
Download Telegram
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከሜቴክ የተረከበውን የኳሊቲ ኢንጅነሪንግ ማዕከል በሙሉ አቅሙ ስራ ለማስጀመር ከምሁራን ጋር መከረ
========================
ምክክሩ የተካሄደው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትት የተውጣጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የተረከበውን የኳሊቲ ኢንጅነሪንግ ማዕከል ባስጎበኘበት ወቅት ነበር፡፡
የጋዝና ሌሎች ፈሳሾችን ፍሰት ከሚለካ አንስቶ እስከ 3D ማሽን ግብዓቶች ድረስ ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ የሚያከናውኑ ማሽኖች የተጎበኙ ሲሆን ለእያንዳንዳቸው እስከ 40 ሚሊዮን ብር ወጪ ወጥቶባቸው ወደ ሀገር ቢገቡም ላለፉት አምስት ዓመታት ጥቅም ላይ ሳይውሉ ቆይተዋል፡፡
የማሽኖቹ ሐገራዊ ጥቅም የላቀ እንደሆነ ለመምህራን እና ተመራማሪዎቹ የገለፁት አቶ ሳንዶካን እነዚህን ወደ ስራ በማስገባት ረገድ ትልቅ ድርሻ ሊወስዱ እነደሚገባ ለምሁራኑ አሳስበዋል፡፡ ምሁራኑም በበኩላቸው ችገሩን ለመፍታተ የሚያስችል ምክረ ሐሳብ ይዘው ለመምጣት ቃል ገብተዋል፡፡
ስልሳ ስምንት ሺህ ካሬ ላይ ለምርምር ስራ ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተገነባው ማዕከሉ በውስጡ የኤሌክትሪካል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ፣ የጂኦሜትሪካል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ እንዲሁም የተርማል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ ቤተ-ሙከራዎችን ይዟል፡፡
Crypto Currency
*****************************************
*****************
በሁለተኛ የዓለም ጦርነት ግንኙነቶችን ሚስጥራዊ ለማድረግ ታስቦ የተፈጠረው ስነ-መሰውር (Cryptography) (ክሪፕቶግራፊ) የተሰኘው የመግባቢያ ቃል ኡሁን ባለንበት የዲጂታል ዓለም የሂሳብ ንድፈ ሃሳቦችን እና የኮምፒዊተር ሳይንስ መሰረታዊ ባህሪያትን ተላብሶ ግንኙነትን፣ መረጃን እና የዲጂታል ገንዘብ ዝውውርን በደህንነት ቀጠና ውስጥ ለማስገባት የሚውል ልዩ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፅንሰ ሃሳብ ሁኗል፡፡
ይህም ኢንተርኔትን ተጠቅሞ ተነባቢ መረጃዎችን (legible information) ወደ ማይነበቡና ሊደረስባቸው የማይችል የሚስጥር ኮዶች (uncrackable code) በመቀየር ዲጂታል ግብይቱ ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ታዲያ cryptocurrency(ክሪፕቶ ከረንሲ) የሚለው ስያሜም ከዚህ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም እንደመገበያያ የሚያገልግል የዲጂታል ገንዘብ ወይም (virtual currency) ማለት ነው፡፡ ይህም በሌላ አገላለፅ ምናባዊ መገበያያ ማለት ሲሆን ሚስጥራዊ ስልቶችን (encryption techniques) ተጠቅሞ የሚፈፀሙ ግብይቶች ደህንነታቸው የተጠበቁ የሚያደርግ የዲጂታሉ ዓለም አማራጭ የክፍያ ስርዓት ነው፡፡
ልክ እንደሌሎች የገንዘብ ዓይነቶች ማለትም እንደ ዶላር፣ ፓውንድ ወይም ዩሮ በመንግስት አካል፣ በባንክ ወይም በሌላ ማዕከላዊ የፋይናንስ ተቋም የሚተዳደር ሳይሆን በኔትዎርክ ውስጥ ያለ ማንኛውም ተጠቀሚ የሚያስተዳድረው፣ በአንድ ኮምፒዩተር ወይም ሰርቨር ላይ የማይወሰን እና የሶስተኛ ወገን ጣልቃ ገብንት ሳያስፈልገው ከአንድ አካል ወደ ሌላ አካል አቻ ለአቻ (Peer-to-Peer) በሆነ መንገድ የሚፈፀም የዲጂታል መገበያያ ነው፡፡ በክሪፕቶከረንሲ አሰራር ሁለት ሰዎች እርስ በዕርስ ሳይተዋወቁና እንደ ባንክ ያሉ ማዕከላዊ የገንዘብ ተቋማት ጣልቃ ሳይገቡ የገንዘብ ልውውጥ እና ግብይት ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡
ነገር ግን በግብይቱ ወቅት ትምምኑ ሊፈጸም የሚችለው እያንዳንዱን የግብይት ሂዲት መዝግቦ በሚያስቀምጠው የዲጂታል የሂሳብ መዝገብ (digital ledger) አማካኝነት ነው፡፡ ይህን ደግሞ የሚዘረጋው በብሎክቼን ቴክኖሎጂ ነው፡፡
ምንጭ፡ bitdegree.com
TECHIN weekly seminar
You are invited to join us today @TECHINhall
# TECHINtalk
# TECHIN #weeklyseminar
የተሳትፎ ጥሪ
=========
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ‘‘Digitizing Finance: Mobile Payment’’ በሚል ርዕስ ረቡህ ህዳር 24 2012 (Dec 4) የአንድ ቀን ወርክሾፕ በስብሰባ አዳራሻችን አዘጋጅቷል፡፡ ፡፡ በዚህ ወርክሾፕ መሳተፍ ለምትፈልጉ ሁሉ በተቀመጠው ሊንክ አማካኝነት እስከ ሰኞ ህዳር 22 ድረስ ብቻ መመዝገብ ትችላላችሁ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfYpO3jXQj8vTabRMdU0_sDcLk8-eanriLk0hJNR7y57VuKvA/viewform
ለተመራጭ ተሳታፊዎች ውጤቱን በኢሜይል የምናሳውቅ ሲሆን ተጨማሪ ጥያቄ ካልዎት በኢሜይል አድራሻችን conference@techin.gov.et ያድርሱን፡፡
ያለን ቦታ አነስተኛ ነውና ይፍጠኑ!!!
የመብረቅ ጥቃት መቼና የት እንደሚፈጠር መተንበይ ተቻለ
የመብረቅ ጥቃት መቼና የት እንደሚፈጠር በሰው ሰራሽ አስተውሎት መተንበይ ተቻለ!
ለመተንበየ ከሚያዳግቱ ተፈጥሯዊ ክስተቶች ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው መብረቅ መሆኑ ይታወቃል፡፡ መብረቅ በየወቅቱ ሰዎችንና አንስሳቶችን ይገድላል፤ ቤቶችንና ደኖችን እሳት በማያያዝ ያወድማል እንዲሁም ብዙ መሰል ውድመቶችን ያስከትላል፡፡
የ EPFL’s School of Engineering ተመራማሪዎች በ 30 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ከ 10 እስከ 30 ደቂቃዎች በኋላ ሊፈጠር የሚችል የመብረቅ ጥቃትን ለመተንበይ የሚያስችል ቀላልና ወጪ ቆጣቢ የሆነ አዲስ ዘዴ ፈጥረዋል፡፡ ዘዴው በአየር ንብረት ጣቢያዎች የሚገኙ መረጃዎችንና ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በጋራ በማጣመር ይጠቀማል፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው ዘዴ በጣም ውስብስብና ፍጥነት የሚጎድለው ሲሆን ከ ራዳር አና ከ ሳተላይት የሚገኙ መረጃዎችን መጠቀሙ ወጪውን ከፍተኛ ያደርገዋል፡፡ አዲሱ ዘዴ በአንፃሩ በማንኛውም የአየር ንብረት ጣቢያ የሚገኝ መረጃን መጠቀሙ ከራዳርና ሳተላይት ውጪ የሆኑና የተግባቦት አውታሮች የሌሉባቸውን የገጠር አከባቢዎችን ለማካተት ያስችላል፡፡
በተጨማሪም ወቅታዊ መረጃን በቀላሉ ማግኘት መቻሉ በፍጥነት ለመተንበይና አውሎነፋስ ወይም ማእበል ከመፈጠሩ በፊት አስቀድሞ የማስጠንቀቂያ ደውል ለማበጀት ያስችላል፡፡
የመረጃው ምንጭ scitechdaily ሲሆን የምርምር ስራውም November 8, 2019 Climate and Atmospheric Science, a Nature Partner Journal ላይ መታተሙ ተገልጿል፡፡
ሐሴትን ከበጎነት !!!
*=*=*=*=*=*=*
የሰው ልጅ በምድር ሲመላለስ ታላቅ የመንፈስ እርካታን ከሚያጎናፅፉት ተግባራት መካከል አንዱ ለተቸገረ መድህን፤ ለወገንም አለኝታ መሆን ሲችል እንደሆነ ብዙዎቻችንን ያስማማል፡፡ ከነዚህ በጎ ተግባራት መካከልም ብዙዎችን ከህልፈት የሚታደገው የደም ልገሳ ተግባር ይጠቀሳል፡፡
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሰራተኞች በ፳፻፲፪ የመጀመሪያቸው የሆነውን የደም ልገሳ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውነዋል፡፡ በመርሀግብሩ ላይም የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ ፲፰ የቤተሰብ አባላቶቻችን ተገኝተው ደማቸውን ለግሰዋል፡፡ ታድያ ለበጎ አድራጎት ተግባራት እንግዳ ያልሆኑት የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሰራተኞች መሰል የደም ልገሳ መርሀ-ግብር ሲያከናውኑ የዛሬው ለአስራ አንደኛ ጊዜ ነው፡፡
በቅርቡ ይህን መሰል የደም ልገሳዎች በሀገራችን ኢትዮጵያም ቀስ በቀስ እየተስፋፋ ይገኛል፡፡ ባሳለፍነው ወርሃ ጥቅምት አጋማሽ ሀገር ቀን ቆጥሮ ቀጠሮ ይዞ ካከናወነው የደም ልገሳ ዘመቻ በላይም ለዚህ ምስክር የሚሆነን አይገኝም፡፡ በዕለቱም በአርባ የሀገራችን ከተሞች ከአስራ አራት ሺህ በላይ ዜጎች ታላቁን ስጦታ ከአካላቸው ቀንሰው ለወገን አካፍለዋል፡፡
የዲጂታል ፋይናንስን ለማሳደግ የሁሉም ትብብር ወሳኝ አንደሚሆን ተገለፀ
***************************************
‘‘Digitizing Finance: Mobile Payment’’ በሚል የተሰናዳው ይህ የአንድ ቀን ወርክሾፕ አንደሃገር በዲጂታል ኢኮኖሚው ላይ ያለንበትን ደረጃ፤ ያሉ ችግሮች እና የሚታዩ መልካም እድሎች በማንሳት እንዴት እንምራው ወይም እናሳድገው በሚለው አጀንዳ ላይ ትኩረቱን አድርጎ ተካሂዷል፡፡
በወርክሾፑ የተለያዩ የባንክ ተቋማት፣ የዩኒቨርስቲ ሙሁራን እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ የተሰማሩ ድርጅቶች የተሳተፉ ሲሆን፤ በባለሙያዎች በቀረቡ ሰፊ ትንተናዎች እና የፓናል ውይይቶች ሰፊ ጊዜ በመስጠት ተካሂዷል፡፡ በመርሃግብሩ ጅማሬ ወርክሾፑን በንግግር የከፈቱት የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ የመድረኩ መዘጋጀት በዘርፉ ለሚንቀሳቀሱ ባለሙያዎችና ሌሎች የንግድ ተቋማት የሚፈጥረውን ወርቃማ እድል አንስተው የዲጂታል ዘርፉን ይበልጥ ለማሳደግ የሁሉም ትብብር እጅግ መሰረታዊ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ የኬኒያን የዲጂታል ፋይናንስ እንቅስቀሴ እንደተሞክሮ በመጥቀስ ኢትዮጵያም ከዚህ ትልቅ ትምህርት መውሰድ እንደሚገባት እና ኢኒስቲትዩቱም እንዲህ ያሉ የውውይት መድረኮችን በማዘጋጀት የፕሮጀክት ሃሳቦች የሚያድጉበትንና የግንዛቤ ስራዎች የሚስፋፉበትን ሁኔታ ለመፍጠር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
በዚህ ወርክሾፕ ሰፊ ትንተና ካቀረቡ ባለሙያዎች መካከል ከደቡብ አፍሪካ የመጡት ወ/ሪት አንቶኒያ ኢሰር አንዷ ሲሆኑ የዲጂታል ፋይናንስና ቴክኖሎጂ በአለም አቀፍ ደረጃ እየተራመዱ ያለበትን ሁኔታ እና ሃገራት በዚህ ዘርፍ ውጤት ለማምጣት እየሄዱበት ያለውን ርቀት በጥልቅት አስረድተዋል፡፡ ከሳቸው በማስቀጠል መድረኩን የተረከቡት የቴኪኢን የቀድሞ የስራ ባልደረባ አቶ ዮዳሂ ዘሚካኤል ነባሩ የፋይናንስ ስርዓት በፖሊሲና በመዋቅር ደረጃ በዲጂታል ዘርፉ ላይ የሚኖረውን ጫና በማስረዳት፤ መንግስት እየሄደባቸው ያሉትን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ አብራርተዋል፡፡ አቶ ዮዳሂ በተለይም በመሰራት ላይ የሚገኘውን የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ በምሳሌ በማንሳት ሀገሪቱ በዚህ ዘርፍ ላይ ሃብት ለመፍጠር የሚያስችል ጥሩ መሰራት እንደሚኖራት ገልፀዋል፡፡
ከዚህ በማስቀጠል መድረኩን የያዙት የቤልካሽ ቴክኖሎጂ ዋና መስራች አቶ አብርሃም ጉልላት ከድርጅታቸው ተሞክሮ በመነሳት በዲጂታል ፋይናንስ እና የሞባይል ክፍያ ዙሪያ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችንና መልካም እድሎችን አብራርተዋል፡፡ የውርክሾፑ መርሃ ግብር ከእነዚህ አቅርቦቶች በተጨማሪ እጅግ ፍሬያማ በሆኑ የፓናል ወይይቶች የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊ በኩልም ገንቢ አስተያየቶች እና የመፍትሄ ሃሳቦች ተንፀባርቀውበታል፡፡