የፀሃያችንን ድንበር አልፈው የሄዱት ሁለቱ መንኮራኩሮች
*********************
የአሜሪካው የጠፈር ምርምር ተቋም ናሳ እንደግሪጎሪያኑ በ1977 በተለያየ ወር ልዩነት ያመጠቃቸው ቮዬጀር1 እና ቮዬጀር2 (Voyager 1&2) የተሰኙት አሳሽ መንኮራኩሮች ስለ ፕላኔት ጁፒተር፣ ሳተርን፣ ዩራኑስ እና ኔፕቱን ስሪት አጥንተው እንደጨረሱ ወደ በይነኮከባዊ ህዋ (interstellar space) መላካቸው የሚታወቅ ነው። እነዚህ መንኮራኩሮች ከ37 አመታት የህዋ ውስጥ ጉዞ በኋላ በጁላይ 2012 አካባቢ ሴንሰሮቻቸው የፀሀይ ነፋሳት ፍጥነት ቀንሶ የበይነኮከባዊ ነፋሳት ፍጥነት እንደጨመረ ማረጋገጥ ችለዋል። በመሆኑም ስርአተፀሀያችንን ለቀው ወደ በይነኮከባዊ ህዋ ጉዟቸውን እንዳደረጉ እርግጥ ሆኗል።
ስለ ስርአተፀሀያችን ድንበሮች ያለንን እውቀት በሙሉ ያስጨበጡን ቮዬጀሮች በጥቂት ወራት ተለያይተው የተላኩ ቢሆንም ስርአተፀሀያችንን ከቦ የሚገኝውን እና ከድንኩዋ ፕላኔት ፕሉቶ ምህዋር በእጅጉ ርቆ የሚገኝውን ኢነባራዊ ድንበር ሂልዮስፌር (Heliosphere) አልፈው መሄዳቸው በታሪክ በሰው ልጅ ከተሰሩ አሳሽ መንኮራኩሮች ውስጥ ቀዳሚ ያደርጋቸዋል። መንትያዎቹ አሳሽ መንኮራኩሮች የሚጉዋዙበት አቅጣጫ እንዲሁ የተለያየ ቢሆንም ሁለቱም ግን ስርአተፀሀያችንን ለቀው ወጥተዋል። ቮዬጀር2 አሁን ላይ 'ሳጁታርየስ' ወደተሰኘው ህብረከዋክብት (Constallation) አቅጣጫ በሰኮንድ 16ኪ.ሜ እየገሰገሰች ጉዞዋን ቀጥላለች። በዚህ ፍጥነት ከቀጠለች ከ 296,000 አመታት በሁዋላ ሰማያችን ላይ ደምቃ ከምትታየው 'ሲረስ' ከተሰኘቸው ኮከብ ልትደርስ ትችላለች ተብሎ ይታሰባል።
ይሁንና ሁለቱም መንኮራኩሮች መንቀሳቀሻ ሀይላቸው የሆነው 'ፕሉቶኒየም ተርሞኤሌክትሪክ ጀነሬተር' የተሰኘው ባትሪያቸው ከ5 አመታት በሁዋላ በ 2025 ሙሉ ለሙሉ ተሟጦ የሚያልቅ በመሆኑ መረጃቸውን መላክ ያቆማሉ። ይህ ማለት ግን ጉዟቸውን ያቋርጣሉ ማለት አይደለም። ከሁለቱ መንኮራኩሮች በፊት እንደመጠቀችው ፓዮኔር 10 አሳሽ መንኩራኩር ሁላ መንትዮቹም በውስጣቸው ምድራችንን የሚገልፅ እና መገኛ አቅጣጫዋን የሚጠቁም ካርታ ይዘዋል። እነዚህ አሳሽ መንኮራኩሮች ማረፊያቸው በውል አይታወቅምና ምናልባት ከኛ ውጭ ህይወት ያላቸው ፍጡራን እነዚህን መንኮራኩሮች ቢያገኟቸው ከየት እንደመጡ እና ስለመጡበት ፕላኔት በደምብ የሚያስረዳ ካርታ እና ስእላዊ መግለጫን ይዘው ይጓዛሉ።
አሁን ላይ ከቮዬጀሮች የተላክ መልእክት ምድራችን ለመደረስ ከ16 ሰአታት በላይ የሚፈጅበት ሲሆን አሁን ከደረሱበት የinterstellar medium (ISM) አንፃር መልክቱን ለማድረስ የሚፈጅባቸው ጊዜ በመጠኑም ቢሆን ለውጥ ያመጣል፡፡ መንትዮቹ መንኮራኩሮች ከላይ እንሰተጠቀሰው በ2012 በላኳቸው መረጃዎች የፀሀይ ነፋሳት ፍጥነት ቀንሶ የበይነኮከባዊ ነፋሳት ፍጥነት መጨመር ተከትሎ interstellar medium ላይ መድረሳቸው የሚጠቀስ ሲሆን በቅርቡም በተለይም ቮዬጀር2 የተባለቸው ሞንኮራኩር የላከቸው ሲግናል ስለጥልቁ ህዋ ያላወቅናቸውን እና ስለበይነኮከባዊ ህዋ ሰፊ መረጃን ትሰጣለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡Science Focus እና theguardian
*********************
የአሜሪካው የጠፈር ምርምር ተቋም ናሳ እንደግሪጎሪያኑ በ1977 በተለያየ ወር ልዩነት ያመጠቃቸው ቮዬጀር1 እና ቮዬጀር2 (Voyager 1&2) የተሰኙት አሳሽ መንኮራኩሮች ስለ ፕላኔት ጁፒተር፣ ሳተርን፣ ዩራኑስ እና ኔፕቱን ስሪት አጥንተው እንደጨረሱ ወደ በይነኮከባዊ ህዋ (interstellar space) መላካቸው የሚታወቅ ነው። እነዚህ መንኮራኩሮች ከ37 አመታት የህዋ ውስጥ ጉዞ በኋላ በጁላይ 2012 አካባቢ ሴንሰሮቻቸው የፀሀይ ነፋሳት ፍጥነት ቀንሶ የበይነኮከባዊ ነፋሳት ፍጥነት እንደጨመረ ማረጋገጥ ችለዋል። በመሆኑም ስርአተፀሀያችንን ለቀው ወደ በይነኮከባዊ ህዋ ጉዟቸውን እንዳደረጉ እርግጥ ሆኗል።
ስለ ስርአተፀሀያችን ድንበሮች ያለንን እውቀት በሙሉ ያስጨበጡን ቮዬጀሮች በጥቂት ወራት ተለያይተው የተላኩ ቢሆንም ስርአተፀሀያችንን ከቦ የሚገኝውን እና ከድንኩዋ ፕላኔት ፕሉቶ ምህዋር በእጅጉ ርቆ የሚገኝውን ኢነባራዊ ድንበር ሂልዮስፌር (Heliosphere) አልፈው መሄዳቸው በታሪክ በሰው ልጅ ከተሰሩ አሳሽ መንኮራኩሮች ውስጥ ቀዳሚ ያደርጋቸዋል። መንትያዎቹ አሳሽ መንኮራኩሮች የሚጉዋዙበት አቅጣጫ እንዲሁ የተለያየ ቢሆንም ሁለቱም ግን ስርአተፀሀያችንን ለቀው ወጥተዋል። ቮዬጀር2 አሁን ላይ 'ሳጁታርየስ' ወደተሰኘው ህብረከዋክብት (Constallation) አቅጣጫ በሰኮንድ 16ኪ.ሜ እየገሰገሰች ጉዞዋን ቀጥላለች። በዚህ ፍጥነት ከቀጠለች ከ 296,000 አመታት በሁዋላ ሰማያችን ላይ ደምቃ ከምትታየው 'ሲረስ' ከተሰኘቸው ኮከብ ልትደርስ ትችላለች ተብሎ ይታሰባል።
ይሁንና ሁለቱም መንኮራኩሮች መንቀሳቀሻ ሀይላቸው የሆነው 'ፕሉቶኒየም ተርሞኤሌክትሪክ ጀነሬተር' የተሰኘው ባትሪያቸው ከ5 አመታት በሁዋላ በ 2025 ሙሉ ለሙሉ ተሟጦ የሚያልቅ በመሆኑ መረጃቸውን መላክ ያቆማሉ። ይህ ማለት ግን ጉዟቸውን ያቋርጣሉ ማለት አይደለም። ከሁለቱ መንኮራኩሮች በፊት እንደመጠቀችው ፓዮኔር 10 አሳሽ መንኩራኩር ሁላ መንትዮቹም በውስጣቸው ምድራችንን የሚገልፅ እና መገኛ አቅጣጫዋን የሚጠቁም ካርታ ይዘዋል። እነዚህ አሳሽ መንኮራኩሮች ማረፊያቸው በውል አይታወቅምና ምናልባት ከኛ ውጭ ህይወት ያላቸው ፍጡራን እነዚህን መንኮራኩሮች ቢያገኟቸው ከየት እንደመጡ እና ስለመጡበት ፕላኔት በደምብ የሚያስረዳ ካርታ እና ስእላዊ መግለጫን ይዘው ይጓዛሉ።
አሁን ላይ ከቮዬጀሮች የተላክ መልእክት ምድራችን ለመደረስ ከ16 ሰአታት በላይ የሚፈጅበት ሲሆን አሁን ከደረሱበት የinterstellar medium (ISM) አንፃር መልክቱን ለማድረስ የሚፈጅባቸው ጊዜ በመጠኑም ቢሆን ለውጥ ያመጣል፡፡ መንትዮቹ መንኮራኩሮች ከላይ እንሰተጠቀሰው በ2012 በላኳቸው መረጃዎች የፀሀይ ነፋሳት ፍጥነት ቀንሶ የበይነኮከባዊ ነፋሳት ፍጥነት መጨመር ተከትሎ interstellar medium ላይ መድረሳቸው የሚጠቀስ ሲሆን በቅርቡም በተለይም ቮዬጀር2 የተባለቸው ሞንኮራኩር የላከቸው ሲግናል ስለጥልቁ ህዋ ያላወቅናቸውን እና ስለበይነኮከባዊ ህዋ ሰፊ መረጃን ትሰጣለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡Science Focus እና theguardian
Presentation 2.jpg
1.3 MB
techin weekly seminar
venue: techin hall
date and time nov 14, from 4:30
venue: techin hall
date and time nov 14, from 4:30
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ አዕምሮአዊ ንብረት ፅህፈት ቤት ጋራ በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
***************************
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ የአዕምሮ ንብረት ድርጅት እና የአውሮፓ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት ጋራ በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡ ኢንስቲትዩቱን ወክለው የመግባቢያ ስምምነቱነን የፈረሙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ሲሆኑ በኢትዮጵያ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት በኩል የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኤርሚያስ የማነብርሀን ነበሩ፡፡
ስምምነቱን አስመልክተው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ባደረጉት ንግግር ስምምነቱ ከፊርማም ባለፈ በተቋማቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደላቀ ተቋማዊ ደረጃ እንደሚያሻግረውና ለወደፊት ስራዎችም መነሻ እንደሚሆናቸው ገልፀዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ በበኩላቸው ስምምነቱ የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከአውሮፓ የአዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት ጋራ እንዲሰራ እንደሚያደርገውና ፅህፈት ቤታቸውም በዚህ ትስስር የግንኙነት ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል ገልፀዋል፡፡ አክለውም ኢንስቲትዩቱ ፓተንቶችን ለህብረተሰቡ በማድረስ ረገድ የሄደባቸውን ርቀቶች አውስተው የአውሮፓ አዕምሮ ንብረት ቢሮ በዚህ እንቅስቃሴ ጉልህ እገዛ እንደሚያደርግ ያላቸውን ተስፋ አስረድተዋል፡፡
በስነ-ስርዓቱ ተሳታፊ የነበሩት በአውሮፓ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት የዓለም አቀፍ ትብብር ክፍል ፕሮጀክት ማናጀር የሆኑት አቶ ኒኮላስ ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናን ችረው ስምምነቶቹን ወደ ተግባር የሚለውጡ የጋራ ስራዎችን ከኢንስቲትዩቱ ጋራ እንደሚሰሩ አሳውቀዋል፡፡
***************************
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ የአዕምሮ ንብረት ድርጅት እና የአውሮፓ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት ጋራ በጋራ ለመስራት ተስማሙ፡፡ ኢንስቲትዩቱን ወክለው የመግባቢያ ስምምነቱነን የፈረሙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ሲሆኑ በኢትዮጵያ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት በኩል የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኤርሚያስ የማነብርሀን ነበሩ፡፡
ስምምነቱን አስመልክተው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ባደረጉት ንግግር ስምምነቱ ከፊርማም ባለፈ በተቋማቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ወደላቀ ተቋማዊ ደረጃ እንደሚያሻግረውና ለወደፊት ስራዎችም መነሻ እንደሚሆናቸው ገልፀዋል፡፡ አቶ ኤርሚያስ በበኩላቸው ስምምነቱ የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከአውሮፓ የአዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት ጋራ እንዲሰራ እንደሚያደርገውና ፅህፈት ቤታቸውም በዚህ ትስስር የግንኙነት ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል ገልፀዋል፡፡ አክለውም ኢንስቲትዩቱ ፓተንቶችን ለህብረተሰቡ በማድረስ ረገድ የሄደባቸውን ርቀቶች አውስተው የአውሮፓ አዕምሮ ንብረት ቢሮ በዚህ እንቅስቃሴ ጉልህ እገዛ እንደሚያደርግ ያላቸውን ተስፋ አስረድተዋል፡፡
በስነ-ስርዓቱ ተሳታፊ የነበሩት በአውሮፓ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት የዓለም አቀፍ ትብብር ክፍል ፕሮጀክት ማናጀር የሆኑት አቶ ኒኮላስ ለተደረገላቸው አቀባበል ምስጋናን ችረው ስምምነቶቹን ወደ ተግባር የሚለውጡ የጋራ ስራዎችን ከኢንስቲትዩቱ ጋራ እንደሚሰሩ አሳውቀዋል፡፡
በሂሳብ ትምህርት የሴቶች ውጤት ማሽቆልቆል ምክንያቱ ተፈጥሮ ወይስ…?
==========================
በ1992 ቲን ቶክ ባርቢ በሚባል የልጆች መጫወቻ አሻንጉሊት የተካተተ ቅንጭብ ድምፅ የሂሳብ ትምህርት ከባድ ነው የሚል ነበር፡፡ ሴቶች በተፈጥሯቸው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ስኬታማ መሆን አይችሉም የሚል ሐሳብ ነገር ግን እውነትነቱ ያልተረጋገጠ አቋም በማስተላፉ ህዝባዊ ተቃዉሞ ገጥሞት ነበር፡፡
ጄኔስ የተባለችው የኒዉሮ ሳይንስ ተባባሪ ፕሮፌሰር በካርኔጊ ሜሎን ዩኒቨርሲቲ ስትመራው የነበረው የወጣት ወንዶችና ሴቶች ልጆችን የአንጎል እድገት በጥልቀት የሚመረምር ጥናት ታድያ በሂሳብ ችሎታ ውስጥ ምንም አይነት ጾታን መሰረት ያደረገ ልዩነት አለመኖሩን አመላክቷል፡፡ የምርምር ቡድኑ መሪ እንደተናገሩት፤ የምርምሩ ውጤት ወጣት ልጆች ጾታቸው ምንም ይሁን ምንም የአንጎል ተግባራቸው ተመሳሳይ በመሆኑ ህብረተሰቡ በሒሳብ ውጤታማነታቸው ያለውን አመለካከት እንደገና እንዲያስብበት ማድረግ ይቻላል ብላለች፡፡
ካንቶን እና የጥናቱ ቡድኗ የመጀመሪያዉን የኒዉሮኢሜጂንግ ጥናት በማካሄድና ቪድዮ እንዲሁም የተለያዩ የስታቲስቲክስ አነጻጻሪዎችን በመጠቀም ማረጋገጥ እንደቻሉት ከሆነ የአዕምሮአዊ ዕድገት ልዩነትን የሚያመላክት በወጣት ወንዶችና ሴቶች መካከል ምንም አይነት አዕምሯዊ የትግበራና እድገት ልዩነት አልተገኘም፡፡
እንደተመራማሪዎቹ ከሆነ ለሴቶች ተማሪዎች የሒሳብ፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢንጂነሪንግ ውጤት መድቀቅ ዋነኛው ምክንያት ወደነዚህ የትምህርት መስኮች እንዳይቀላቀሉ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚደርስባቸው ተፅዕንዖ ነው፡፡ ቀድሞ የተሰሩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ ቤተሰብ አብዛኛውን ትኩረት በወንድ ልጆቻቸው ላይ የሚያውሉ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ሃቅ ታዲያ በትምህርት ቤትም ቢሆን መገንዘብ ይቻላል፡፡ የውጤት ብልጫን እንደሚያመጡ በማሰብ የሂሳብ አስተማሪዎች ለወንድ ተማሪዎቻቸው ሰፊውን ትኩረት ይለግሳሉ፡፡
የተወሰኑ የሂሳብ መመዘኛዎችን በመጠቀም የታዳጊ ህፃናትን የዕድገት እምርታ ለመገምገም ታስቦ የተከናወነውን ይህን ጥናት ሌሎችን የሂሳብ ችሎታዎችንም ወደሚገመግም ጥናትነት ለማስፋት እንዳለሙ የጥናት ቡድኑ መሪ አስታውቀዋል፡፡
ምንጭ፡ Science Daily
==========================
በ1992 ቲን ቶክ ባርቢ በሚባል የልጆች መጫወቻ አሻንጉሊት የተካተተ ቅንጭብ ድምፅ የሂሳብ ትምህርት ከባድ ነው የሚል ነበር፡፡ ሴቶች በተፈጥሯቸው የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ስኬታማ መሆን አይችሉም የሚል ሐሳብ ነገር ግን እውነትነቱ ያልተረጋገጠ አቋም በማስተላፉ ህዝባዊ ተቃዉሞ ገጥሞት ነበር፡፡
ጄኔስ የተባለችው የኒዉሮ ሳይንስ ተባባሪ ፕሮፌሰር በካርኔጊ ሜሎን ዩኒቨርሲቲ ስትመራው የነበረው የወጣት ወንዶችና ሴቶች ልጆችን የአንጎል እድገት በጥልቀት የሚመረምር ጥናት ታድያ በሂሳብ ችሎታ ውስጥ ምንም አይነት ጾታን መሰረት ያደረገ ልዩነት አለመኖሩን አመላክቷል፡፡ የምርምር ቡድኑ መሪ እንደተናገሩት፤ የምርምሩ ውጤት ወጣት ልጆች ጾታቸው ምንም ይሁን ምንም የአንጎል ተግባራቸው ተመሳሳይ በመሆኑ ህብረተሰቡ በሒሳብ ውጤታማነታቸው ያለውን አመለካከት እንደገና እንዲያስብበት ማድረግ ይቻላል ብላለች፡፡
ካንቶን እና የጥናቱ ቡድኗ የመጀመሪያዉን የኒዉሮኢሜጂንግ ጥናት በማካሄድና ቪድዮ እንዲሁም የተለያዩ የስታቲስቲክስ አነጻጻሪዎችን በመጠቀም ማረጋገጥ እንደቻሉት ከሆነ የአዕምሮአዊ ዕድገት ልዩነትን የሚያመላክት በወጣት ወንዶችና ሴቶች መካከል ምንም አይነት አዕምሯዊ የትግበራና እድገት ልዩነት አልተገኘም፡፡
እንደተመራማሪዎቹ ከሆነ ለሴቶች ተማሪዎች የሒሳብ፣ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢንጂነሪንግ ውጤት መድቀቅ ዋነኛው ምክንያት ወደነዚህ የትምህርት መስኮች እንዳይቀላቀሉ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚደርስባቸው ተፅዕንዖ ነው፡፡ ቀድሞ የተሰሩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ ቤተሰብ አብዛኛውን ትኩረት በወንድ ልጆቻቸው ላይ የሚያውሉ መሆኑን ነው፡፡ ይህን ሃቅ ታዲያ በትምህርት ቤትም ቢሆን መገንዘብ ይቻላል፡፡ የውጤት ብልጫን እንደሚያመጡ በማሰብ የሂሳብ አስተማሪዎች ለወንድ ተማሪዎቻቸው ሰፊውን ትኩረት ይለግሳሉ፡፡
የተወሰኑ የሂሳብ መመዘኛዎችን በመጠቀም የታዳጊ ህፃናትን የዕድገት እምርታ ለመገምገም ታስቦ የተከናወነውን ይህን ጥናት ሌሎችን የሂሳብ ችሎታዎችንም ወደሚገመግም ጥናትነት ለማስፋት እንዳለሙ የጥናት ቡድኑ መሪ አስታውቀዋል፡፡
ምንጭ፡ Science Daily
የእስራኤል ተመራማሪዎች አዲስ የስኳር በሽታ ህክምና ዘዴን አገኙ
==========================
የእስራኤል ተመራማሪዎች ሰሞኑን ይፋ ባደረጉት ጥናት የስኳር ሕመምን ለማከም የሚስችል አዲስ የሕክምና ዜዴ ማግኘታቸው አስታውቀዋል። እንደ ተመራማሪዎቹ ከሆነ ታማሚዎችን በቋሚነት በተቀመጠ የሰዓታት ልዩነት በየቀኑ ሶስት ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ እንዲመገቡ በማድረግ ብቻ የአይነት 2 ካንሰር ታማሚዎችን የኢንሱሊን ፍጆታ መቀነስ ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ይህ አዲስ የህክምና መንገድ የታማሚዎችን የክብደት መጠን ብሎም የምግብ ፍላጎት፣ ዕለታዊ የኢንሱሊን እና የሄሞግሎቢን A1C መጠንን እና በደማቸው ውስጥ ያለውን የስኳር መጠን መቆጣጠር ያስችላል።
በ12 ሳምንታት ቆይታ ሃያ ስምንት ከመጠን ያለፈ ውፍረት ባለቸው የስኳር ሕመምተኞች ላይ በተካሄደ ሙከራ ታማሚዎቹ ከላይ የተገለጸውን የአመጋገብ ስርዓት በመከተላቸው ክብደታቸው በአማካይ በ5 ኪሎ ሲቀንስ የሄሞግሎቢን A1C መጠንም በ1.2 በመቶ ሊወርድ ችሏል፡፡ በተጨማሪም በነዚህ ሕመምተኞች ውስጥ ያለው የግሉኮስ መጠን በጣም ቀንሶ ታይቷል፡፡ ይህም ከጠቅላላው የኢንሱሊን ፍጆታቸው በአማካኝ 26 ያህሉን መቀነስ አስችሏቸዋል፡፡ በሌላ በኩል በነዚህ ሕመምተኞች ላይ የረሃብና ለጣፋጭ ምግቦች ያላቸው ስሜት ቀንሶ ተስተውሏል፡፡ በአንጻሩ በቀን ስድስት ጊዜ እንዲመገቡ የተደረጉ የስኳር ሕመምተኞች እነዚህ መሻሻሎች ሳይታይባቸው ቀርቷል፡፡
ከዚህ ጥናት ግኝቶች በመነሳት የስኳር ሕመምተኞችን አመጋገብ መቆጣጠር የሚያስችል ስርዓት እየሰሩ እንደሆነ ተመራማሪዎቹ አስታውቀዋል፡፡
የስኳር ህመም የሚከሰተው ሰውነታችን ለኑሮም ሆነ ለእድገት የሚያስፈልገውን ስኳር በትክክል ለመጠቀም ሳይችል ሲቀር መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። አንድ ሰው ለስኳር ሕመም ተጠቂ ነው የምንለው በደም ውስጥ ያለው የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ከፍ ብሎ ሲገኝ ሲሆን፤ ይህም ሰውነታችን ኢንሱሊን የተሰኘውን ሆርሞን በበቂ ሁኔታ ወይም ጭራሹኑ እንዳያመነጭ ሲያደርገው ነው።
ምንጭ፡ Xinhua
==========================
የእስራኤል ተመራማሪዎች ሰሞኑን ይፋ ባደረጉት ጥናት የስኳር ሕመምን ለማከም የሚስችል አዲስ የሕክምና ዜዴ ማግኘታቸው አስታውቀዋል። እንደ ተመራማሪዎቹ ከሆነ ታማሚዎችን በቋሚነት በተቀመጠ የሰዓታት ልዩነት በየቀኑ ሶስት ጊዜ የተመጣጠነ ምግብ እንዲመገቡ በማድረግ ብቻ የአይነት 2 ካንሰር ታማሚዎችን የኢንሱሊን ፍጆታ መቀነስ ይቻላል፡፡ በተጨማሪም ይህ አዲስ የህክምና መንገድ የታማሚዎችን የክብደት መጠን ብሎም የምግብ ፍላጎት፣ ዕለታዊ የኢንሱሊን እና የሄሞግሎቢን A1C መጠንን እና በደማቸው ውስጥ ያለውን የስኳር መጠን መቆጣጠር ያስችላል።
በ12 ሳምንታት ቆይታ ሃያ ስምንት ከመጠን ያለፈ ውፍረት ባለቸው የስኳር ሕመምተኞች ላይ በተካሄደ ሙከራ ታማሚዎቹ ከላይ የተገለጸውን የአመጋገብ ስርዓት በመከተላቸው ክብደታቸው በአማካይ በ5 ኪሎ ሲቀንስ የሄሞግሎቢን A1C መጠንም በ1.2 በመቶ ሊወርድ ችሏል፡፡ በተጨማሪም በነዚህ ሕመምተኞች ውስጥ ያለው የግሉኮስ መጠን በጣም ቀንሶ ታይቷል፡፡ ይህም ከጠቅላላው የኢንሱሊን ፍጆታቸው በአማካኝ 26 ያህሉን መቀነስ አስችሏቸዋል፡፡ በሌላ በኩል በነዚህ ሕመምተኞች ላይ የረሃብና ለጣፋጭ ምግቦች ያላቸው ስሜት ቀንሶ ተስተውሏል፡፡ በአንጻሩ በቀን ስድስት ጊዜ እንዲመገቡ የተደረጉ የስኳር ሕመምተኞች እነዚህ መሻሻሎች ሳይታይባቸው ቀርቷል፡፡
ከዚህ ጥናት ግኝቶች በመነሳት የስኳር ሕመምተኞችን አመጋገብ መቆጣጠር የሚያስችል ስርዓት እየሰሩ እንደሆነ ተመራማሪዎቹ አስታውቀዋል፡፡
የስኳር ህመም የሚከሰተው ሰውነታችን ለኑሮም ሆነ ለእድገት የሚያስፈልገውን ስኳር በትክክል ለመጠቀም ሳይችል ሲቀር መሆኑን የሕክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። አንድ ሰው ለስኳር ሕመም ተጠቂ ነው የምንለው በደም ውስጥ ያለው የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ከፍ ብሎ ሲገኝ ሲሆን፤ ይህም ሰውነታችን ኢንሱሊን የተሰኘውን ሆርሞን በበቂ ሁኔታ ወይም ጭራሹኑ እንዳያመነጭ ሲያደርገው ነው።
ምንጭ፡ Xinhua
ስትጠበቅ የቆየችው የኢትዮጵያ ሳተላይት በጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ህዋ ታመራለች
==========================
ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያዋ የሆነውን ሳተላይት የፊታችን ታህሳስ 7 ከጠዋቱ 12፡21 ወደ ህዋ እንደምታመጥቅ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ጀነራል ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን በላይ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ፡፡ ከቻይና የጠፈር ምርምር ተቋም ጋራ በመተባበር የተሰራችው ይህች ሳተላይት ኢቲ.አር.ኤስ.ኤስ-1 (ERRSS-1) የሚል ስያሜ የተሰጣት ሲሆን ሳተላይቷን ለመቆጣጠር እና መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችል ጣቢያም በእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና ምርምር ማዕከል እንደተዘጋጀላት ተገልጿል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ እንደገለፁት ይህች ሳተላይት በ80 ዲግሪ ላቲቲውድ ላይ በመሆን ኢትዮጵያን ብሎም የምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ አካባቢን ትሸፍናለች፡፡ በዚህም በግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድን ልማት እና አካባቢ ጥበቃ ዙሪያ መረጃ የሚሰጡ ምልከታዎችን ለሀገራችን የምታቀርብ ይሆናል፡፡
ሳተላይት ማምጠቅ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ይገኛል፡፡ እስካሁን ድረስ ሁለት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን ጨምሮ ስምንት የአፍሪካ ሀገራት ሳተላይታቸውን በህዋ እያንሳፈፉ ሲሆን ኢትዮጵያም ዘጠነኛዋ በመሆን የምትቀላቀላቸው ይሆናል፡፡
==========================
ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያዋ የሆነውን ሳተላይት የፊታችን ታህሳስ 7 ከጠዋቱ 12፡21 ወደ ህዋ እንደምታመጥቅ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ጀነራል ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን በላይ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ፡፡ ከቻይና የጠፈር ምርምር ተቋም ጋራ በመተባበር የተሰራችው ይህች ሳተላይት ኢቲ.አር.ኤስ.ኤስ-1 (ERRSS-1) የሚል ስያሜ የተሰጣት ሲሆን ሳተላይቷን ለመቆጣጠር እና መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችል ጣቢያም በእንጦጦ ኦብዘርቫቶሪ እና ምርምር ማዕከል እንደተዘጋጀላት ተገልጿል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ እንደገለፁት ይህች ሳተላይት በ80 ዲግሪ ላቲቲውድ ላይ በመሆን ኢትዮጵያን ብሎም የምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ አካባቢን ትሸፍናለች፡፡ በዚህም በግብርና፣ ውሃ፣ ማዕድን ልማት እና አካባቢ ጥበቃ ዙሪያ መረጃ የሚሰጡ ምልከታዎችን ለሀገራችን የምታቀርብ ይሆናል፡፡
ሳተላይት ማምጠቅ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ይገኛል፡፡ እስካሁን ድረስ ሁለት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን ጨምሮ ስምንት የአፍሪካ ሀገራት ሳተላይታቸውን በህዋ እያንሳፈፉ ሲሆን ኢትዮጵያም ዘጠነኛዋ በመሆን የምትቀላቀላቸው ይሆናል፡፡
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከIBA ኢትዮጵያ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
****
ጀማሪ ፈጣሪ እና ቴክኖሎጂስቶችን በማብቃት ላይ የሚሰራው IBA ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በጋራ ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የፊርማ ስነ ስርዓት አከሂደዋል፡፡ ስምምነቱን የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ እና የIBA ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አያሌው ግዛው የተፈራረሙ ሲሆን፤ በወናነትም በፈጠራ ስራ፣ ጀማሪ የንግድ ዘርፎች እና የስታር ታፕ ፕሮግራሞች በሚበለፅጉበት ሁኔታ እና መሰል ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሚሆን ተጠቅሷል፡፡
በአርባ የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች የኢኖቬሽን ማዕከላትን በማቋቋምና ያሉትንም በመጠናከር ዙሪያ እየሰራ የሚገኘው IBA ኢትዮጵያ በዚህ ስምምነትም ከቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ በመሆን አዳዲስ የፈጠራ ሃሳቦች ወደ ንግድ የሚገቡበትን፣ የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ መዕከላት የሚስፋፉበትን እና በዘርፉ ላይ ያተኮሩ ወርክሾፕና ስልጠናዎች የሚደረጉበትን ሁኔታዎች ለማመቻቸት እንደሚሰሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
IBA ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂስቶች የሚሰሩ ልዩ ልዩ ፈጠራዎችን ወደ ገንዘብ ምንጭነት መቀየርን በዋና ግብነት ይዞ በሃገራችን እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን መቀመጫውን ካደረገበት ሃገረ ኖርዌይ ደግሞ በስፋት ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፡፡ ከሰራቸው ስራዎቹ ውስጥም በኖርዌይ ያሉትን ስደተኞች በስራ ፈጠራ ማብቃት ይጠቀሳል፡፡ ወደ ሀገራችን ከመጣበትም ጊዜ አንስቶ ከተለያዩ አካላት ጋራ ግንኙነትን በመመስረተ የትምህርት ዘርፉን ዲጂታላይዝ በማድረግ እንዲሁም African innovation week የተሰኘውን የፈጠራና ቴክኖሎጂ መድረክ በማዘጋጀት ረገድ የሰራቸው ስራዎች ይጠቀሳሉ፡፡
****
ጀማሪ ፈጣሪ እና ቴክኖሎጂስቶችን በማብቃት ላይ የሚሰራው IBA ኢትዮጵያ ከቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በጋራ ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የፊርማ ስነ ስርዓት አከሂደዋል፡፡ ስምምነቱን የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ እና የIBA ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አያሌው ግዛው የተፈራረሙ ሲሆን፤ በወናነትም በፈጠራ ስራ፣ ጀማሪ የንግድ ዘርፎች እና የስታር ታፕ ፕሮግራሞች በሚበለፅጉበት ሁኔታ እና መሰል ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደሚሆን ተጠቅሷል፡፡
በአርባ የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች የኢኖቬሽን ማዕከላትን በማቋቋምና ያሉትንም በመጠናከር ዙሪያ እየሰራ የሚገኘው IBA ኢትዮጵያ በዚህ ስምምነትም ከቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ በመሆን አዳዲስ የፈጠራ ሃሳቦች ወደ ንግድ የሚገቡበትን፣ የቴክኖሎጂ ማበልፀጊያ መዕከላት የሚስፋፉበትን እና በዘርፉ ላይ ያተኮሩ ወርክሾፕና ስልጠናዎች የሚደረጉበትን ሁኔታዎች ለማመቻቸት እንደሚሰሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
IBA ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂስቶች የሚሰሩ ልዩ ልዩ ፈጠራዎችን ወደ ገንዘብ ምንጭነት መቀየርን በዋና ግብነት ይዞ በሃገራችን እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን መቀመጫውን ካደረገበት ሃገረ ኖርዌይ ደግሞ በስፋት ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፡፡ ከሰራቸው ስራዎቹ ውስጥም በኖርዌይ ያሉትን ስደተኞች በስራ ፈጠራ ማብቃት ይጠቀሳል፡፡ ወደ ሀገራችን ከመጣበትም ጊዜ አንስቶ ከተለያዩ አካላት ጋራ ግንኙነትን በመመስረተ የትምህርት ዘርፉን ዲጂታላይዝ በማድረግ እንዲሁም African innovation week የተሰኘውን የፈጠራና ቴክኖሎጂ መድረክ በማዘጋጀት ረገድ የሰራቸው ስራዎች ይጠቀሳሉ፡፡
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከሜቴክ የተረከበውን የኳሊቲ ኢንጅነሪንግ ማዕከል በሙሉ አቅሙ ስራ ለማስጀመር ከምሁራን ጋር መከረ
========================
ምክክሩ የተካሄደው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትት የተውጣጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የተረከበውን የኳሊቲ ኢንጅነሪንግ ማዕከል ባስጎበኘበት ወቅት ነበር፡፡
የጋዝና ሌሎች ፈሳሾችን ፍሰት ከሚለካ አንስቶ እስከ 3D ማሽን ግብዓቶች ድረስ ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ የሚያከናውኑ ማሽኖች የተጎበኙ ሲሆን ለእያንዳንዳቸው እስከ 40 ሚሊዮን ብር ወጪ ወጥቶባቸው ወደ ሀገር ቢገቡም ላለፉት አምስት ዓመታት ጥቅም ላይ ሳይውሉ ቆይተዋል፡፡
የማሽኖቹ ሐገራዊ ጥቅም የላቀ እንደሆነ ለመምህራን እና ተመራማሪዎቹ የገለፁት አቶ ሳንዶካን እነዚህን ወደ ስራ በማስገባት ረገድ ትልቅ ድርሻ ሊወስዱ እነደሚገባ ለምሁራኑ አሳስበዋል፡፡ ምሁራኑም በበኩላቸው ችገሩን ለመፍታተ የሚያስችል ምክረ ሐሳብ ይዘው ለመምጣት ቃል ገብተዋል፡፡
ስልሳ ስምንት ሺህ ካሬ ላይ ለምርምር ስራ ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተገነባው ማዕከሉ በውስጡ የኤሌክትሪካል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ፣ የጂኦሜትሪካል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ እንዲሁም የተርማል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ ቤተ-ሙከራዎችን ይዟል፡፡
========================
ምክክሩ የተካሄደው ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትት የተውጣጡ ምሁራንና ተመራማሪዎች የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የተረከበውን የኳሊቲ ኢንጅነሪንግ ማዕከል ባስጎበኘበት ወቅት ነበር፡፡
የጋዝና ሌሎች ፈሳሾችን ፍሰት ከሚለካ አንስቶ እስከ 3D ማሽን ግብዓቶች ድረስ ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ የሚያከናውኑ ማሽኖች የተጎበኙ ሲሆን ለእያንዳንዳቸው እስከ 40 ሚሊዮን ብር ወጪ ወጥቶባቸው ወደ ሀገር ቢገቡም ላለፉት አምስት ዓመታት ጥቅም ላይ ሳይውሉ ቆይተዋል፡፡
የማሽኖቹ ሐገራዊ ጥቅም የላቀ እንደሆነ ለመምህራን እና ተመራማሪዎቹ የገለፁት አቶ ሳንዶካን እነዚህን ወደ ስራ በማስገባት ረገድ ትልቅ ድርሻ ሊወስዱ እነደሚገባ ለምሁራኑ አሳስበዋል፡፡ ምሁራኑም በበኩላቸው ችገሩን ለመፍታተ የሚያስችል ምክረ ሐሳብ ይዘው ለመምጣት ቃል ገብተዋል፡፡
ስልሳ ስምንት ሺህ ካሬ ላይ ለምርምር ስራ ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተገነባው ማዕከሉ በውስጡ የኤሌክትሪካል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ፣ የጂኦሜትሪካል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ እንዲሁም የተርማል ካሊብሬሽን እና ቴስቲንግ ቤተ-ሙከራዎችን ይዟል፡፡