TechIn2
1.22K subscribers
1.47K photos
1 video
120 files
500 links
Technology & Innovation Institute (TechIn2), Ethiopia

የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት

ጠቃሚና ወቅታዊ የሆኑ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ፣ ጤና እና ሰብአዊ-ኣቅም ግንባታ(Human Development)መረጃዎችንና ምክሮችን በየእለቱ እናደርሶታለን።
Download Telegram
ኢትዮጵያዊያን ምቀኞች ነን?
==================
በTECHIN ቤተሰቦች ሁለተኛ ቀን የክህሎት ግንባታ ውሎ በትናንትናው ሎሬት የትነበርሽ ንጉሴን እና አንጋፋውን ምሁር ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላን ባሳተፈው መድረክ ሰፊ ሀሳቦች ተንሸራሽረውበት አልፏል፡፡
መድረኩን በቅድሚያ ተረክበው የቆዩት ሎሬት የትነበርሽ ንጉሴ ስለ ቡድን ስራ ኃያልነት አስመልክተው ከታዳሚያኑ ጋር ጥልቅ ውይይት ሲያከናውኑ እኛ ኢትዮጵያዊያን ምቀኞች አሊያም በጋራ መብላትን እንጂ መስራትን ያልታደልን መሆን አለመሆናችንን ጥያቄ ሰንዝረው ለሰፊ ውይይት ጋብዘው ነበር፡፡ በጉዳዩም ልዩ ልዩ ሐሳቦች ተንፀባርቀውበታል፡፡
ከእርሳቸው በማስከተል በሳይንስ፣ ሀገራዊ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ከሰፊው የህይወት መንገዳቸው የተቀዱ እጅግ ጠቃሚ ልምድ እና ምሁራዊ እይታቸው አካፍለዋል፡፡ ፕሮፌሰሩ በተለይም ሳይንስን ለሰፊው ሰህብረተሰብ በማዳረስ (አህዝቦተ ሳይንስ) ዙሪያ ባላቸው ተሞክሮ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
“እንደ እምነቱ የሚኖሩ አማኞች ጠፍተዋል”
=========================
“ትናንትን እያሰብን ዛሬን እየረሳን፤ ዛሬን እየረሳን ነገን እያጠፋን ነው”፣ “እንደ እምነቱ የሚኖሩ አማኞች ጠፍተዋል” እነዚህን ጠንካራ ቃላት የተናገሩት የአስተዳደር ወሰንና ማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ናቸው፡፡ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ባልደረቦች ክህሎት ግንባታ ላይ ተገኝተው የስብእና ግንባታ አስተምሮታቸውን በርእቱ አንደበት አዋዝተው ያቀረቡት መመህሩ በምድር ላይ እስካሉ ድረስ የእኔነትን ስሜት በማጥፋትና በእኛነት ስሜት በመታነፅ የየራሳቸውን አሻራ አስፍረው ሊያልፉ እንደሚገባም አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
ከኡስታዝ አቡበከር በተጨማሪ በዛሬው መርሀ ግብር የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ የሆኑት ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ (የህይወት ጉዞ /ከዳውሮ እስከ ኮሎራዶ)፣ የአይኮግ ላብስ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ጌትነት አሰፋ (በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ) እንዲሁም ገበያ በተሰኘው ተቋም የቴክኖሎጂ ኩባንያ ውስጥ እያገለገሉ ያሉ ባለሙያዎች (በግንኙነት መንገዶች፣ ዲጂታል ገንዘብ...)ልምድና አስተምሮታቸውን ብሎም የተቋማቸውን ገፅታ ለቤተሰቦቻችን አካፍለዋል፡፡
፬ኛው ውሎ፤ ከአዕምሮ እስከ አዕምሮ ንብረት
======================
አራተኛ ቀኑን በያዘው የቴክኢን ቤተሰቦች የክህሎት ማጎልበቻ ስልጠና ውሎ፤ በታዋቂው የህክምና ባለሙያ ዶክተር ብሩክ ላቢሶ "ሀ" ብሎ የጀመረው የዛሬው መርሀ ግብር ከህክምና እስከ አዕምሮአዊ ንብረት ጉዳዮች ተዳሰውበታል፡፡ ዶ/ር ብሩክ በህክምና ረገድ ያሉትን ተቀዳሚ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በጥልቀት ያብራሩ ሲሆን ልዩና ውስብስብ ስለሆነው የሰው ልጆች ስነ አዕምሮአዊ አፈጣጠር ብሎም ማናቸውም የሰው ልጆች መፍጠር ስለሚችሉት ተፅዕንዖ (the power of one man the power of one woman) የዳሰሱበት ክፍል ቀልብን የሳበ ነበር፡፡ ለየት ባለው አቀራረባቸውም ተርታው ማህበረሰብ የተውጣጡ ግለሰቦች በምሳሌነት ተዳሰውበታል፡፡
ከእርሳቸው በማስከተል መድረኩን የተረከቡት የኢትዮጵያ አዕምሮ ንብረት ፅህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኤርሚያስ የማነብርሀን ናቸው፡፡ በዚህ ክፍለ ጊዜም የአዕምሮአዊ ንብረት ምንነት፣ አይነቶች እንዲሁም ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ ተቃኝቷል፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን ወቅታዊ የአዕምሮ ንብረት እና ፈጠራ እንቀረስቃሴ ዝቅተኛ ግን ተስፋ ሰጪ እንደሆነ የተናገሩት ዋና ዳይሬክተሩ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ መነቃቃቶች እንዳሉ አመላክተዋል፡፡
ሚዲያና ዕውነታ
===========
ሐሳብን ለሌሎች ተደራሽ ማድረግ ለአንድ ስራ ቀና ውጤት ትልቁን ሚና ይወጣል፡፡ ለዚህ ይረዳ ዘንድ የዛሬውን የቴክ-ኢን ቤተሰቦች የክሆሎት ግንባታ ውሎ በሳይንስ ግንኙነት (science Communication) ላይ በማድረግ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ስልጠናን ሰጥተዋል፡፡ በሀገራችን የጋዜጠኝነት እና ግንኙነት አስተምሮት ሰፊ ልምድ ያላቸው ዶ/ር ጌታቸው በመሰረታዊ የግንኙነት ምንነት፣ መንገዶቹ፣ ታሪካዊ ዳራውን ብሎም በእይታዎቹ ዙሪያ ሰፋ ያለ የግንዛቤ ማስጨበጥን አከናውነዋል፡፡ ካነሷቸው ሐሳቦች መካከል ግለሰቦች ከሰፊው ማህበረሰብ ጋር ባላቸው የግንባር ግንኙነት እንዴት ጥሩ ተናጋሪ መሆን እንደሚችል ሲሆን ሃሳቦቹን በአዝናኝ አቀራረብና አስተማሪ ምሳሌዎች አዋዝተው አቅርበዋል፡፡ በተጨማሪም ሚዲያው የህብረተሰብን አስተሳሰብ እና ድርጊት በማነፅ ደረጃ ያለውን ጉልበት እንዲሁም የአቀራረባቸውን እይታዊ እውነተኝነትና የዘገባ አድማስ ተዳሰውበታል፡፡
ሌላው በዛሬው መድረክ ስልጠኛ የተሰጠበት ደረጃዎችን (standard) እና አራተኛውን የኢንዱስትሪ አብዮት አስመልክቶ የተሰጠው ሲሆን ኢትዮጵያ ደረጃዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተሩ አቶ እንዳለው መኮንን ነበሩ፡፡ ከደረጃዎች ምንነት አንስቶ በውስጡ ምን ይይዛል፣ ዓለም አቀፍ ደረጃ መዳቢዎች ብሎም በኢትዮጵያ ያለው የደረጃዎች አሰጣጥ ሁኔታና የአሰጣጥ ሰንሰለት ምን ይመስላል የሚለው ተዳሷል፡፡
የtechin ቤተሰቦች ክህሎት ማዳበሪያ በአስገራሚነቱ ቀጥሏል
==========================
ሁለተኛ ሳምንቱን የያዘው የtechin ቤተሰቦች ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና በዛሬው ዕለት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ የዛሬውን ስልጠና ያቀረቡት የላይትሀውስ ስልጠናና ማማከር መስራች እና ዋና ዳይሬተር አቶ እስክንድር ካሳ ሲሆኑ በመርሀ ግብራቸውም በለውጥ አመራርአሳታፊ (change management) እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ሰፊውን ጊዜ በመስጠት በአዝናኝና እንቅስቃሴዎች አጅበው አካሂደዋል፡፡
በስልጠናቸው መካከል አስተማሪውን የሚፈጥረው ተማሪው ነው ያሉየለውጥ እስክንድር ለውጥን በመቀበል ረገድ ስላለው የሰዎች እይታ በዝርዝርእንደሆነና በማስረዳት 70 በመቶ የለውጥ እንቅስቃዎች ሳይሳኩ የሚቀሩት በራሳቸው በሰዎች አማካኝነት ይህንንም ለማስተካከል ይረዳ ዘንድ ቀድሞ እራስን ለለውጥ ዝግጁ ማድረግ እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡ የክህሎት ስልጠናው ከዚህ በተጨማሪ ነገሮችን በበጎ ተርጉሞ ስለመረዳት፣ ስለ ይቅር ባይነት እንዲሁም ችግር አፈታት የዳሰሰ ሲሆን በታዳሚዎቹም ላይ ላቅ ያለ ደስታና መነሳሳትን ፈጥሯል፡፡