ዛፍን መትከል እንደዋነኛ የመፍትሄ አማራጭ መውሰድ ይገባል፤ ጥናት። =======================
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም የዛፍ ተከላዎች በመረግ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን እንኳን ብናይ ከሁለት ዛፍ ለሁለት ሺህ አንስቶ እስከ አሁኑ የአራት ቢሊዮን ዕፅዋት ተከላ መርሀ ግብር ያለውን እንቅስቃሴ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ሆኖም በግቡ ውጤታማነት ላይ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆየተተዋል፡፡
ከቀናት በፊት የወጣው ጥናት ለዚህ በጎ ምላሽ የሚሰጥ ሆኗል፡፡ እንደጥናቱ ከሆነ ዕፅዋት በተገቢው አፈር ላይ ከተተከሉ 205 ጊጋ ቶን የሚሆን የሚሆን ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በሚቀጥሉት ከ40 እስከ መቶ ዓመታት ውስጥ መሰብሰብ ይችላሉ፡፡ ይህን አሀዝ ለንፅፅር ስናቀርበው የሰው ልጆች ከኢንዱስትሪ አብዮት መፈንዳት አንስቶ ካመነጨነው ሁለት ሶስተኛው ጋር የሚስተካከል ነው፡፡ በተጓዳኝም በእጅጉ እየተጎዳ የሚገኘውን የዓለማችን ስነ-ምህዳር ይጠገናል፡፡
ጥናቱ 80,000 የሳተላይት ምስሎችን በመሰብሰብ የመረመረ ሲሆን ምድራችን ምን ያህል ዕፅዋትን፤ በየትኛው ስፍራና የአየር እንዲሁም አፈር ሁኔታ ማቀበል እንደምትችልም ጭምር የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የተገለጸውን ውጤት ያስገኝ ዘንድ ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ቆዳ ስፋት ዘጠኝ እጥፍ በሚበልጥ መሬት ላይ ዕፅዋትን መትከል እንደሚቻልና እንደሚገባ አስቀምጧል፡፡ ሆኖም ተከላው ከወዲሁ መቀላጠፍ ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልሆነ እየጨመረ በሚመጣው የዓለም ሙቀት አማካኝነት የሚከሰቱት ድርቅ እና የዛፎች አተነፋፈስ ለውጥ የዛፎቹን ዕድገት ሊገታ ይችላል፡፡
ሆኖም መንገዶች አልጋ በአልጋ አይሆኑም፡፡ ወደፊት እንደሚያጋጥሚ ከሚጠበቁ ችግሮች ውስጥ አንዱ የዋጋው ጉዳይ ነው፡፡ ዛፎችን በዚህ መጠን መትከል በትንሹ 300 ቢሊዮን ዶላርን ይጠይቃል፤ ምንም እንኳን እንደቡድኑ ግምት ከሌሎች የካርበን መምጠጫ መንገዶች አንፃር ርካሽ እንደሆነ ቢነገርም፡፡
ታድያ እርስዎስ ስንት ዛፎችን በዚህ ክረምት ስንት ዛፎችን ተክለዋል፤ ስንረትስ ለመትከል ዕቅድ ይዘዋል፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
የአየር ንብረት ለውጥን ለመቆጣጠር ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም የዛፍ ተከላዎች በመረግ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን እንኳን ብናይ ከሁለት ዛፍ ለሁለት ሺህ አንስቶ እስከ አሁኑ የአራት ቢሊዮን ዕፅዋት ተከላ መርሀ ግብር ያለውን እንቅስቃሴ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ሆኖም በግቡ ውጤታማነት ላይ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆየተተዋል፡፡
ከቀናት በፊት የወጣው ጥናት ለዚህ በጎ ምላሽ የሚሰጥ ሆኗል፡፡ እንደጥናቱ ከሆነ ዕፅዋት በተገቢው አፈር ላይ ከተተከሉ 205 ጊጋ ቶን የሚሆን የሚሆን ካርቦን ዳይ ኦክሳይድን በሚቀጥሉት ከ40 እስከ መቶ ዓመታት ውስጥ መሰብሰብ ይችላሉ፡፡ ይህን አሀዝ ለንፅፅር ስናቀርበው የሰው ልጆች ከኢንዱስትሪ አብዮት መፈንዳት አንስቶ ካመነጨነው ሁለት ሶስተኛው ጋር የሚስተካከል ነው፡፡ በተጓዳኝም በእጅጉ እየተጎዳ የሚገኘውን የዓለማችን ስነ-ምህዳር ይጠገናል፡፡
ጥናቱ 80,000 የሳተላይት ምስሎችን በመሰብሰብ የመረመረ ሲሆን ምድራችን ምን ያህል ዕፅዋትን፤ በየትኛው ስፍራና የአየር እንዲሁም አፈር ሁኔታ ማቀበል እንደምትችልም ጭምር የሚያሳይ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የተገለጸውን ውጤት ያስገኝ ዘንድ ከኢትዮጵያ አጠቃላይ ቆዳ ስፋት ዘጠኝ እጥፍ በሚበልጥ መሬት ላይ ዕፅዋትን መትከል እንደሚቻልና እንደሚገባ አስቀምጧል፡፡ ሆኖም ተከላው ከወዲሁ መቀላጠፍ ይኖርበታል፡፡ ይህ ካልሆነ እየጨመረ በሚመጣው የዓለም ሙቀት አማካኝነት የሚከሰቱት ድርቅ እና የዛፎች አተነፋፈስ ለውጥ የዛፎቹን ዕድገት ሊገታ ይችላል፡፡
ሆኖም መንገዶች አልጋ በአልጋ አይሆኑም፡፡ ወደፊት እንደሚያጋጥሚ ከሚጠበቁ ችግሮች ውስጥ አንዱ የዋጋው ጉዳይ ነው፡፡ ዛፎችን በዚህ መጠን መትከል በትንሹ 300 ቢሊዮን ዶላርን ይጠይቃል፤ ምንም እንኳን እንደቡድኑ ግምት ከሌሎች የካርበን መምጠጫ መንገዶች አንፃር ርካሽ እንደሆነ ቢነገርም፡፡
ታድያ እርስዎስ ስንት ዛፎችን በዚህ ክረምት ስንት ዛፎችን ተክለዋል፤ ስንረትስ ለመትከል ዕቅድ ይዘዋል፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ
=================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በሥሩ በሚገኙት ሦስት ማዕከላት ላሉ የምርምር ዳይሬክቶሬቶች ከዚህ ቀጥሎ በተዘረዘሩት የስራ መስኮች ላይ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የሚያሟሉ ባለሙያዎች እንዲያመለክቱ ይጋብዛል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• ተወዳዳሪዎች ማሟላት ያለባቸው፡-
• ለሚወዳደሩበት የሥራ መደብ ማመልከቻ/Application Letter/፣ካሪኩለምቪቴ(CV)፣ የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ የThesis/Dissertation እና የሌሎች ሕትመቶች Abstract፣ አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤ በተጨማሪም ስልክ ቁጥር እና ኢሜይል በማመልከቻቸው ላይ መግለጽ ይኖርበታል፡፡
• የምዝገባ ሁኔታ በOnline http://www.techin.gov.et/am/web/sticsite/techin12
ብቻ ሲሆን አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን በኢሜል Vacancy@techin.gov.et አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤
• ሴት ተወዳዳሪዎች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ፤
• ለፈተና የሚቀርቡትን ተወዳዳሪዎች በአድራሻቸው የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን::
• ተቋሙን የተመለከቱ ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግ የፌሥቡክ አድራሻችን Technology and Innovation Institute, Ethiopia ወይም የኢንስቲትዩቱን ድረ-ገፅ
www.techin.gov.et በመጠቀም ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን::
=================
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በሥሩ በሚገኙት ሦስት ማዕከላት ላሉ የምርምር ዳይሬክቶሬቶች ከዚህ ቀጥሎ በተዘረዘሩት የስራ መስኮች ላይ ባለሙያዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የሚያሟሉ ባለሙያዎች እንዲያመለክቱ ይጋብዛል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• ተወዳዳሪዎች ማሟላት ያለባቸው፡-
• ለሚወዳደሩበት የሥራ መደብ ማመልከቻ/Application Letter/፣ካሪኩለምቪቴ(CV)፣ የተሟላ የትምህርትና የሥራ ልምድ የThesis/Dissertation እና የሌሎች ሕትመቶች Abstract፣ አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤ በተጨማሪም ስልክ ቁጥር እና ኢሜይል በማመልከቻቸው ላይ መግለጽ ይኖርበታል፡፡
• የምዝገባ ሁኔታ በOnline http://www.techin.gov.et/am/web/sticsite/techin12
ብቻ ሲሆን አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን በኢሜል Vacancy@techin.gov.et አያይዘው መላክ ይኖርባቸዋል፤
• ሴት ተወዳዳሪዎች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ፤
• ለፈተና የሚቀርቡትን ተወዳዳሪዎች በአድራሻቸው የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን::
• ተቋሙን የተመለከቱ ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግ የፌሥቡክ አድራሻችን Technology and Innovation Institute, Ethiopia ወይም የኢንስቲትዩቱን ድረ-ገፅ
www.techin.gov.et በመጠቀም ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን::
መልካም ተስፋ ለኢትዮጵያውያን አካል ጉዳተኞች
============================
ናትናኤል ታከለ ይባላል፤ ወጣት የፈጠራ ባለሙያ ሲሆን እጅግ ለአጠቃቀም ቀላል እና ዘርፈ ብዙ ጥቅምን የምትሰጥ የአካል ጉዳተኞች ተሽከርካሪን ሰርቶ ያቀረበ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ተሸርካሪዋን በራሱአቅም ሰርቶ ያቀረባት ሲሆን እስከ 80 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደትን ተሸክማ ከፀሐይ በምታገኘው ኃይል አማካኝነት ትንቀሳቀሳለች፡፡ በተለያየ አቅጣጫ ይመራት ዘንድ ጆይስቲኮች ተገጥመውላታል፡፡ እነዚህን ጆይስቲኮች ተጠቅመው መገልገል ለማይችሉም ቢሆን በብሉቱዝ አማካኝነት ካሉበት ቦታ ሆነው በስልካቸው ሊቆጣጠሯት ይችላሉ፡፡ የተሰራላት የአንድሮይድ መተግበሪያ (አፕ) ታድያ ይህን በማስተናበር ረገድ ትልቁን ሚና ይጫወታል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ተሸከርካሪዋ በሰዓት እስከ 20 ኪ.ሜ መጓዝንም ትችላለቸው፡፡ በህዝብ ጎዳናዎች ላይም ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ አሳፍራ ለመንቀሳቀስ በሚያስችሏት መሳሪያዎች የተሞላች ናት፡፡
ስለ ወጣቱ እና አስደናቂ ፈጠራው ሙሉውን ለማወቅ በመቅርጸ ምስላችን ካስቀረነው ተንቀሳቃሽ ምስል እንካችሁ ብለንዎታል፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=Oh-7QdiCEUQ&t=29s
============================
ናትናኤል ታከለ ይባላል፤ ወጣት የፈጠራ ባለሙያ ሲሆን እጅግ ለአጠቃቀም ቀላል እና ዘርፈ ብዙ ጥቅምን የምትሰጥ የአካል ጉዳተኞች ተሽከርካሪን ሰርቶ ያቀረበ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ተሸርካሪዋን በራሱአቅም ሰርቶ ያቀረባት ሲሆን እስከ 80 ኪሎ ግራም የሚደርስ ክብደትን ተሸክማ ከፀሐይ በምታገኘው ኃይል አማካኝነት ትንቀሳቀሳለች፡፡ በተለያየ አቅጣጫ ይመራት ዘንድ ጆይስቲኮች ተገጥመውላታል፡፡ እነዚህን ጆይስቲኮች ተጠቅመው መገልገል ለማይችሉም ቢሆን በብሉቱዝ አማካኝነት ካሉበት ቦታ ሆነው በስልካቸው ሊቆጣጠሯት ይችላሉ፡፡ የተሰራላት የአንድሮይድ መተግበሪያ (አፕ) ታድያ ይህን በማስተናበር ረገድ ትልቁን ሚና ይጫወታል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ ተሸከርካሪዋ በሰዓት እስከ 20 ኪ.ሜ መጓዝንም ትችላለቸው፡፡ በህዝብ ጎዳናዎች ላይም ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ አሳፍራ ለመንቀሳቀስ በሚያስችሏት መሳሪያዎች የተሞላች ናት፡፡
ስለ ወጣቱ እና አስደናቂ ፈጠራው ሙሉውን ለማወቅ በመቅርጸ ምስላችን ካስቀረነው ተንቀሳቃሽ ምስል እንካችሁ ብለንዎታል፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=Oh-7QdiCEUQ&t=29s
YouTube
በሀገር ልጅ ለሀገርልጅ የተሰራ
ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!!
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞች ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበርን ጎበኙ
***************************
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞች በዛሬው ዕለት ሽሮ ሜዳ በሚገኘው ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር በአካል በመገኘት ልዩ ልዩ ድጋፎችን አድርገዋል፡፡ የተቋሙ ሰራተኞች ይህን ድጋፍ ያደረጉት የማህበረሰብ አቀፍ ስራዎችን በሚያከናውነው የሶሻል ኮሚቴ አማካኘነት ሲሆን፤ ይህም ኮሚቴው ከሚሰራቸው መሰል ተግባራት ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው፡፡
የኢኒስቲትዩቱ ሰራተኞች ይህን ድጋፍ ባደረጉበት ወቅት የማህበሩ አባላት ስለጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር አንዳንድ ገለፃዎችን ያደረጉላቸው ሲሆን በድጋፍ ሂደቱም በአጠቃላይ ለዕለት ተዕለት ፍጆታ የሚውሉ የተለያዩ ቁሳ ቁሶችን ረድተዋል፡፡
ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ሕጋዊ ሰውነት ኖሮት ከ2003 ጀምሮ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በመስራት ላይ የሚገኘ ማህበር ሲሆን በስሩም እጅግ ብዛት ያላቸው የአእምሮ ህሙማን እንደሚረዱ ይታወቃል፡፡
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞች ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበርን ጎበኙ
***************************
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞች በዛሬው ዕለት ሽሮ ሜዳ በሚገኘው ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር በአካል በመገኘት ልዩ ልዩ ድጋፎችን አድርገዋል፡፡ የተቋሙ ሰራተኞች ይህን ድጋፍ ያደረጉት የማህበረሰብ አቀፍ ስራዎችን በሚያከናውነው የሶሻል ኮሚቴ አማካኘነት ሲሆን፤ ይህም ኮሚቴው ከሚሰራቸው መሰል ተግባራት ውስጥ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው፡፡
የኢኒስቲትዩቱ ሰራተኞች ይህን ድጋፍ ባደረጉበት ወቅት የማህበሩ አባላት ስለጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር አንዳንድ ገለፃዎችን ያደረጉላቸው ሲሆን በድጋፍ ሂደቱም በአጠቃላይ ለዕለት ተዕለት ፍጆታ የሚውሉ የተለያዩ ቁሳ ቁሶችን ረድተዋል፡፡
ጌርጌሴኖን የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ሕጋዊ ሰውነት ኖሮት ከ2003 ጀምሮ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን በመስራት ላይ የሚገኘ ማህበር ሲሆን በስሩም እጅግ ብዛት ያላቸው የአእምሮ ህሙማን እንደሚረዱ ይታወቃል፡፡
“ለሁሉም ጊዜውን ይጠብቅለታል
በማለት ሰለሞን ቀድሞ ተናግሮታል
ሳትደፈር ኖራ ጨረቃም እርቃ
በሰው ተፈተነች ጊዜዋን ጠብቃ”
======================
የትዝታው ንጉስ ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ ይህን ስንኝ ከአራት አስርት ዓመታት በፊት ባቀነቀነው ዘፈኑ ውስጥ አካቶ ተጫውቶት ነበር፡፡ ታድያ ይህ የጊዜን ሃያልነት የሚያወሳው የታላቁ ሰው ስራ ለአድማጭ ጆሮ ከመብቃቱ ጥቂት ዓመታትን አስቀድሞ የሰው ልጅ ሚሊኒየሞችን በሚዘልቀው የስልጣኔ ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃን በእግሮቹ ለመርገጥ ችሎ ነበር፡፡ አሜሪካዊያኑ የህዋ ተመራማሪዎች ኒል አርምስትሮንግ፣ ኤድዊን ኢ. አልድሪን ጁኒየር እና ሚካኤል ኮሊንስ በሚመሩት የአፖሎ 11 ተልዕኮ አማካኝነት የሆነ ነበር፡፡ አርምስትሮንግ ጨረቃን በእግሮቹ የረገጠው የመጀመሪው ሰው ለመሆን ሲበቃ ከእርሱ ሃያ ደቂቃን ዘግይቶ ከመጓጓዣቸው የወጣው አልድሪን ሁለተኛው ሰው ለመሆን በቅቷል፡፡ እንሆ ይህ በህዋ ሳይንስ ውስጥ እንደ ትልቅ እርምጃ የሚወሰድ ተግባር የተከናወነበትን 50ኛ ዓመት ከሁለት ቀናት በፊት ደፍኗል፡፡
የሃምሳኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሂውስተን፤ ቴክሳስ በሚገኘው የናሳ ጎብኚዎች ማዕከል የአዲስ ዓመት አቀባበል በሚመስል መልኩ በኮንሰርት ታጅቦ ሲከበር በዋሽንግተን መታሰቢያ ላይም የጨረቃን ምስል የሚያሳዩ ምስሎችን ለ16 ደቂቃዎች በማንፀባረቅ ተከብሯል፡፡ ሌሎች የአሜሪካን ከተሞችም በተመሳሳይ በድምቀት አክብረውት ሲያልፉ በተቀረው ዓለምም ከማክበር አልቦዘነም፡፡ ከነዚህ ውስጥ በፓሪሱ ግራንድ ፓላሲስ ጨረቃን የሚወክል ቅርፅ በማንጠልጠልና ሌሎች ትዕይንቶችን በማከናወን የተካሄደው አውደ ርዕይ ይጠቀሳል፡፡
ይህ ዓለምን ለሃምሳ ዓመታት ያስደነቀ ሁነት ከሳይንስ ስኬትነቱ በተጨማሪ ለጥርጣሬዎችም መነሻ ከመሆን አልዳነም፡፡ ለዚህ ተጠቃሹ የተልዕኮውን ዕውነተኛነት የሚጠይቀው ነው፡፡ በዋናነት የጨረቃን ጉዞ በሐሰትነት በሚወነጅሉ ሰዎች የሚራመደው ይህ ሐሳብ ጅማሬውን ያደረገው የአሜሪካን አየር ኃይል ባልደረባ የነበረው ቢል ካይሲንግ “We Never Went to the Moon: America’s Thirty Billion Dollar Swindle” በሚል ስያሜ ከ33 ዓመታት በፊት ካሳተመው አወዛጋቢ መፅሐፍ በኋላ ነበር፡፡ የመፅሐፉ ማጠንጠኛ ናሳ ፕሬዘዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዴ የሰጡትን የሰው ልጅን እ.አ.አ በስልሳዎቹ መባቻ ጨረቃ ላይ የማሳረፍ ተልዕኮን ማሳካት ባለመቻሉ ሰዎችን ወደ ምድራችን ምህዋር ብቻ መላኩን እና ለዚህም የቅርብ ዕውቀት እንዳለው ነው፡፡ ይህን ተከትሎ የተነሳው ይህ ፅንሰ ሐሳብ የኋላ ኋላ የሐገሪቱ የስለላ ተቋማት ገብተውባቸው የነበሩትን የሐሰት ተግባራት በመንተራስ በመላው ዓለም ቁጥራቸው የበዛ ተከታዮችን ሊያፈራ በቅቷል፡፡
ውዝግቦችን ለጊዜው ወደጎን በመተው ተልዕኮውን የተመለከትን እንደሆነ ይህ ጉዞ በተለያዩ አስገራሚ ዕውነታዎች የተሞላ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፤
• አርምስትሮንግ ከመሬት ከተነሳበት ቅፅበት አንስቶ ጨረቃ ላይ ደርሶ ከመንኮራኩሯ በመውጣት የጨረቃን ምድር እስከረገጠባት ቅፅበት ድረስ 109 ሰዓታት ከ42 ደቂቃ ፈጅቶበታል፡፡ ከዚህ ውስጥ አብዛኛው በጉዞ የጠፋ ነው፡፡
• ከጨረቃ ወደ ምድር የተደረገው የመልስ ጉዞ በበኩሉ 195 ሰዓታት፣ 18 ደቂቃ እና 35 ሰኮንዶችን ወስዷል፡፡
• ተጓዥ ቡድኑ ከጨረቃ ወደ ምድር ጉዞውን ከመጀመሩ በፊት 106 የተለያዩ ቁሳቁሶችን እዚያው ጨረቃ ላይ ትቶ የነበረ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ጉዞውን የሚያከብሩ የ74 ሐገራት መሪዎችን መልዕክትን የያዘ የሲልከን ዲስክ፣ በወርቅ የተሰራች አነስተኛ የዘንባባ ቅጠል፣ ሁነቱን ለዓለም ያስተላለፉት ካሜራዎች፣ ሽንትና ሰገራ እንዲሁም ባንዲራ ይገኙበታል፡፡
• ሚካኤል ኮሊንስ ከሌሎቹ ተመራማሪዎች ጋራ አብሮ ወደጨረቃ ቢጓዝም ቅሉ ሁለቱ ባለደረቦቹ ጨረቃን ሲረግጡ እርሱ ግን ከላይ በመሆን እስከ ጥልቅ ክፍሏ ድረስ በጨረቃ ሰማይ ላይ በምህዋሯ እንዲሽከረከር ተገዶ ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለ45 ደቂቃዎች እዚሁ መሬት ላይ ከነበረው የናሳ መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንኙነቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ በዚህም የተነሳ የዓለማችን ብቸኛው ሰው የሚል ተቀፅላ ስምን ሸምቷል፡፡
• አፖሎ ጋይዳንስ ኮምፒውተር (AGC) በመባል የምትታወቀው እና በአፖሎ 11 ውስጥ ተገጥማ ጉዞውን ያስተናበረችው ኮምፒውተር የራም (Random Access Memory) አቅሟ አሁን ካሉት ስማርት ስልኮች ሲነፃፀር ከአንድ ሚሊዮን እጥፍ በላይ ያነሰ ሲሆን ይህን ንፅፅር ወደ ሮም (Read Only Memory) ያመጣነው እንደሆነ ወደ 4.4 ሚሊዮን እጥፍ ይጠጋል፡፡ በተጨማሪም የኮምፒውተሯን ፕሮሰሰር ከዘንድሮዎቹ ስማርት ስልኮች አንፃር ሲታይ 100,000 እጥፍ ያነሰ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
• ይህ ሁነት በመላው ዓለም በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት የተላለፈ ሲሆን ከ600 ሚሊዮን የላቁ ሰዎችም በቴሌቪዥን መስኮቶቻቸው በቀጥታ ተከታትለውታል፡፡
ምንጭ፡ bbc፣ የናሳ ድረ-ገፅ እና ሌሎችም
በማለት ሰለሞን ቀድሞ ተናግሮታል
ሳትደፈር ኖራ ጨረቃም እርቃ
በሰው ተፈተነች ጊዜዋን ጠብቃ”
======================
የትዝታው ንጉስ ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ ይህን ስንኝ ከአራት አስርት ዓመታት በፊት ባቀነቀነው ዘፈኑ ውስጥ አካቶ ተጫውቶት ነበር፡፡ ታድያ ይህ የጊዜን ሃያልነት የሚያወሳው የታላቁ ሰው ስራ ለአድማጭ ጆሮ ከመብቃቱ ጥቂት ዓመታትን አስቀድሞ የሰው ልጅ ሚሊኒየሞችን በሚዘልቀው የስልጣኔ ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃን በእግሮቹ ለመርገጥ ችሎ ነበር፡፡ አሜሪካዊያኑ የህዋ ተመራማሪዎች ኒል አርምስትሮንግ፣ ኤድዊን ኢ. አልድሪን ጁኒየር እና ሚካኤል ኮሊንስ በሚመሩት የአፖሎ 11 ተልዕኮ አማካኝነት የሆነ ነበር፡፡ አርምስትሮንግ ጨረቃን በእግሮቹ የረገጠው የመጀመሪው ሰው ለመሆን ሲበቃ ከእርሱ ሃያ ደቂቃን ዘግይቶ ከመጓጓዣቸው የወጣው አልድሪን ሁለተኛው ሰው ለመሆን በቅቷል፡፡ እንሆ ይህ በህዋ ሳይንስ ውስጥ እንደ ትልቅ እርምጃ የሚወሰድ ተግባር የተከናወነበትን 50ኛ ዓመት ከሁለት ቀናት በፊት ደፍኗል፡፡
የሃምሳኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሂውስተን፤ ቴክሳስ በሚገኘው የናሳ ጎብኚዎች ማዕከል የአዲስ ዓመት አቀባበል በሚመስል መልኩ በኮንሰርት ታጅቦ ሲከበር በዋሽንግተን መታሰቢያ ላይም የጨረቃን ምስል የሚያሳዩ ምስሎችን ለ16 ደቂቃዎች በማንፀባረቅ ተከብሯል፡፡ ሌሎች የአሜሪካን ከተሞችም በተመሳሳይ በድምቀት አክብረውት ሲያልፉ በተቀረው ዓለምም ከማክበር አልቦዘነም፡፡ ከነዚህ ውስጥ በፓሪሱ ግራንድ ፓላሲስ ጨረቃን የሚወክል ቅርፅ በማንጠልጠልና ሌሎች ትዕይንቶችን በማከናወን የተካሄደው አውደ ርዕይ ይጠቀሳል፡፡
ይህ ዓለምን ለሃምሳ ዓመታት ያስደነቀ ሁነት ከሳይንስ ስኬትነቱ በተጨማሪ ለጥርጣሬዎችም መነሻ ከመሆን አልዳነም፡፡ ለዚህ ተጠቃሹ የተልዕኮውን ዕውነተኛነት የሚጠይቀው ነው፡፡ በዋናነት የጨረቃን ጉዞ በሐሰትነት በሚወነጅሉ ሰዎች የሚራመደው ይህ ሐሳብ ጅማሬውን ያደረገው የአሜሪካን አየር ኃይል ባልደረባ የነበረው ቢል ካይሲንግ “We Never Went to the Moon: America’s Thirty Billion Dollar Swindle” በሚል ስያሜ ከ33 ዓመታት በፊት ካሳተመው አወዛጋቢ መፅሐፍ በኋላ ነበር፡፡ የመፅሐፉ ማጠንጠኛ ናሳ ፕሬዘዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዴ የሰጡትን የሰው ልጅን እ.አ.አ በስልሳዎቹ መባቻ ጨረቃ ላይ የማሳረፍ ተልዕኮን ማሳካት ባለመቻሉ ሰዎችን ወደ ምድራችን ምህዋር ብቻ መላኩን እና ለዚህም የቅርብ ዕውቀት እንዳለው ነው፡፡ ይህን ተከትሎ የተነሳው ይህ ፅንሰ ሐሳብ የኋላ ኋላ የሐገሪቱ የስለላ ተቋማት ገብተውባቸው የነበሩትን የሐሰት ተግባራት በመንተራስ በመላው ዓለም ቁጥራቸው የበዛ ተከታዮችን ሊያፈራ በቅቷል፡፡
ውዝግቦችን ለጊዜው ወደጎን በመተው ተልዕኮውን የተመለከትን እንደሆነ ይህ ጉዞ በተለያዩ አስገራሚ ዕውነታዎች የተሞላ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ከነዚህም ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፤
• አርምስትሮንግ ከመሬት ከተነሳበት ቅፅበት አንስቶ ጨረቃ ላይ ደርሶ ከመንኮራኩሯ በመውጣት የጨረቃን ምድር እስከረገጠባት ቅፅበት ድረስ 109 ሰዓታት ከ42 ደቂቃ ፈጅቶበታል፡፡ ከዚህ ውስጥ አብዛኛው በጉዞ የጠፋ ነው፡፡
• ከጨረቃ ወደ ምድር የተደረገው የመልስ ጉዞ በበኩሉ 195 ሰዓታት፣ 18 ደቂቃ እና 35 ሰኮንዶችን ወስዷል፡፡
• ተጓዥ ቡድኑ ከጨረቃ ወደ ምድር ጉዞውን ከመጀመሩ በፊት 106 የተለያዩ ቁሳቁሶችን እዚያው ጨረቃ ላይ ትቶ የነበረ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ጉዞውን የሚያከብሩ የ74 ሐገራት መሪዎችን መልዕክትን የያዘ የሲልከን ዲስክ፣ በወርቅ የተሰራች አነስተኛ የዘንባባ ቅጠል፣ ሁነቱን ለዓለም ያስተላለፉት ካሜራዎች፣ ሽንትና ሰገራ እንዲሁም ባንዲራ ይገኙበታል፡፡
• ሚካኤል ኮሊንስ ከሌሎቹ ተመራማሪዎች ጋራ አብሮ ወደጨረቃ ቢጓዝም ቅሉ ሁለቱ ባለደረቦቹ ጨረቃን ሲረግጡ እርሱ ግን ከላይ በመሆን እስከ ጥልቅ ክፍሏ ድረስ በጨረቃ ሰማይ ላይ በምህዋሯ እንዲሽከረከር ተገዶ ነበር፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለ45 ደቂቃዎች እዚሁ መሬት ላይ ከነበረው የናሳ መቆጣጠሪያ ማዕከል ግንኙነቱ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ በዚህም የተነሳ የዓለማችን ብቸኛው ሰው የሚል ተቀፅላ ስምን ሸምቷል፡፡
• አፖሎ ጋይዳንስ ኮምፒውተር (AGC) በመባል የምትታወቀው እና በአፖሎ 11 ውስጥ ተገጥማ ጉዞውን ያስተናበረችው ኮምፒውተር የራም (Random Access Memory) አቅሟ አሁን ካሉት ስማርት ስልኮች ሲነፃፀር ከአንድ ሚሊዮን እጥፍ በላይ ያነሰ ሲሆን ይህን ንፅፅር ወደ ሮም (Read Only Memory) ያመጣነው እንደሆነ ወደ 4.4 ሚሊዮን እጥፍ ይጠጋል፡፡ በተጨማሪም የኮምፒውተሯን ፕሮሰሰር ከዘንድሮዎቹ ስማርት ስልኮች አንፃር ሲታይ 100,000 እጥፍ ያነሰ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
• ይህ ሁነት በመላው ዓለም በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት የተላለፈ ሲሆን ከ600 ሚሊዮን የላቁ ሰዎችም በቴሌቪዥን መስኮቶቻቸው በቀጥታ ተከታትለውታል፡፡
ምንጭ፡ bbc፣ የናሳ ድረ-ገፅ እና ሌሎችም
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ ጋር በግዙፍ ዳታ ትንተና|Big Data Analytics| ዙሪያ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
**************************************************************
በግዙፍ የመረጃ ትንተና (big data analysis) እና የቴክኖሎጂ አቅም በመፍጠር ላይ አተኩሮ የሚሰራው አለምአቀፉ የዜናይሲስ (ZENYSIS) ቴክኖሎጂ ኩባንያ ከቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢነስቲትዩት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡
በዛሬው ዕለት የተካሄደው ይህ የፊርማ ስነ ስርዓት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢነስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ እና በዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ ሪጂናል ዳይሬክተር አቶ በርናርድ ሎሬንዶ መካከል የተፈፀመ ሲሆን፤ ስምምነቱም በመረጃ ሳይንስና በቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ላይ ሃገራችን እያደረገች ያለችውን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ለማገዝ እንደሚረዳ ታምኖበታል፡፡
በተካሄደው የፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ስለስምምነቱ አስፈላጊነትና አጠቃላይ የተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ገለፃ ያደረጉት የኢነስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዱካን ደበበ እንዳሉት አሁን ያለንበት የዲጂታል ዘመን የተደራጀና ጥራት ያለውን መረጃ በመያዝ እና ቀድሞ በማወቅ የሚከናወን በመሆኑ እንደ ቢግ ዳታ አናሊስስ ያሉ የልህቀት መሳሪያዎች እጅግ ወሳኝ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ ዳይሬክተሩ በተለይም እንዳነሱት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢነስቲትዩት የሃገሪቱን የቴክኖሎጂ አቅም በምርምር እና ስርፀት ከመደገፍ ባለፈ ሴክተሮችን የማዘመን እና አቅም የመፍጠር ስራዎችን ለማከናወን የተቋቋመ በመሆኑ እንደ ዜናይሲስ ካሉ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ጋር በትብብር መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል የዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ ሪጂናል ዳይሬክተር አቶ በርናርድ ትብብሩን አስመልክተው እንደተናገሩት ኢትዮጵያን ጨምሮ በሌሎች አፍሪካ ሃገራት መረጃን በጥራት ሰብስቦ እና አደራጅቶ ለፖሊሲ አውጪዎች ማቅረብ ላይ ካለው ክፍተት አኳያ አለም አቀፍ ተሞክሮ ያላቸውን መሰል የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ማሳተፍ እና ከእነሱ ጋርም በትብብር መስራት ጠቃሚ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ እ.ኤ.አ በ2015 ከጎግል፣ አማዞን እና ናሳ በተወጣጡ የመረጃ እና ሶፍትዌር መሃንዲሶች አማካኝነት የተቋቋመ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን፤ በግዙፍ የመረጃ ትንተና እና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ላይ እየሰራ የሚገኝ ነው፡፡ ኩባንያው ላለፉት ሶስት አመታት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአምስት አሀጉራት የተለያዩ የአቅም ግንባታ እና የቴክኖሎጂ አገልግሎቶችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም እጅግ ወሳኝ በሆኑ የጤና እና ግብርና ዘርፎች ላይ አተኩሮ ይሰራል፡፡
**************************************************************
በግዙፍ የመረጃ ትንተና (big data analysis) እና የቴክኖሎጂ አቅም በመፍጠር ላይ አተኩሮ የሚሰራው አለምአቀፉ የዜናይሲስ (ZENYSIS) ቴክኖሎጂ ኩባንያ ከቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢነስቲትዩት ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡
በዛሬው ዕለት የተካሄደው ይህ የፊርማ ስነ ስርዓት በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢነስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ እና በዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ ሪጂናል ዳይሬክተር አቶ በርናርድ ሎሬንዶ መካከል የተፈፀመ ሲሆን፤ ስምምነቱም በመረጃ ሳይንስና በቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ላይ ሃገራችን እያደረገች ያለችውን ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ ለማገዝ እንደሚረዳ ታምኖበታል፡፡
በተካሄደው የፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ስለስምምነቱ አስፈላጊነትና አጠቃላይ የተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ገለፃ ያደረጉት የኢነስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዱካን ደበበ እንዳሉት አሁን ያለንበት የዲጂታል ዘመን የተደራጀና ጥራት ያለውን መረጃ በመያዝ እና ቀድሞ በማወቅ የሚከናወን በመሆኑ እንደ ቢግ ዳታ አናሊስስ ያሉ የልህቀት መሳሪያዎች እጅግ ወሳኝ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ ዳይሬክተሩ በተለይም እንዳነሱት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢነስቲትዩት የሃገሪቱን የቴክኖሎጂ አቅም በምርምር እና ስርፀት ከመደገፍ ባለፈ ሴክተሮችን የማዘመን እና አቅም የመፍጠር ስራዎችን ለማከናወን የተቋቋመ በመሆኑ እንደ ዜናይሲስ ካሉ አለም አቀፍ የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ጋር በትብብር መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል የዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ ሪጂናል ዳይሬክተር አቶ በርናርድ ትብብሩን አስመልክተው እንደተናገሩት ኢትዮጵያን ጨምሮ በሌሎች አፍሪካ ሃገራት መረጃን በጥራት ሰብስቦ እና አደራጅቶ ለፖሊሲ አውጪዎች ማቅረብ ላይ ካለው ክፍተት አኳያ አለም አቀፍ ተሞክሮ ያላቸውን መሰል የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች ማሳተፍ እና ከእነሱ ጋርም በትብብር መስራት ጠቃሚ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የዜናይሲስ ቴክኖሎጂስ እ.ኤ.አ በ2015 ከጎግል፣ አማዞን እና ናሳ በተወጣጡ የመረጃ እና ሶፍትዌር መሃንዲሶች አማካኝነት የተቋቋመ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን፤ በግዙፍ የመረጃ ትንተና እና የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ላይ እየሰራ የሚገኝ ነው፡፡ ኩባንያው ላለፉት ሶስት አመታት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአምስት አሀጉራት የተለያዩ የአቅም ግንባታ እና የቴክኖሎጂ አገልግሎቶችን ሲያከናውን የቆየ ሲሆን፤ በኢትዮጵያም እጅግ ወሳኝ በሆኑ የጤና እና ግብርና ዘርፎች ላይ አተኩሮ ይሰራል፡፡
ችግኝን እንዴት መትከል እና መንከባከብ ዓለብን
============================
ሰኞ ሐምሌ ፳፪ በሐገር ዓቀፍ ደረጃ 200 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ሽር ጉድ ውስጥ እንገኛለን፡፡ ሆኖም ከመትከል ባለፈ ዘመቻው ውጤት ያመጣ ዘንድ ችግኞቹን በአግባቡ መትከል እና መንከባከብ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ይረዳ ዘንድ ተከታዮቹን ተግባራት በቅደም ተከተል ማከናወን አለብን፡፡
፩፡ በመጀመሪያ ችግኞቹን የምንተክልበት ጉድጓድ ውስጥ እንደ ድንጋይ እንጨት፣ ቅጠል እና ውሃ ያሉ ባዕድ ነገሮች ካሉ ማውጣት አለብን፤
፪፡ ከጉድጓዱ ተቆፍሮ የወጣውን አፈር ከችግኙ ስሮች ይጣጣም ዘንድ እስከ ጉድጓዱ አጋማሽ ድረስ መልሶ መሙላት ይገባል፤
፫፡ በመቀጠልም ችግኙ ላይ ያለውን ፕላስቴክ አፈሩ ሳይፈስብን በጥንቃቄ በመላጥ ችግኙን እስከ ግንዱ መጀመሪያ ድረስ በጉድጓዱ ማኖር፤
፬፡ ችግኞቹ ተጣመው እንዳይቆሙ በመጠንቀቅ ተቆፍሮ የወጣውን አፈር በፕላስቲክ ተሸፍኖ በነበረው አካል ዙሪያው ጠቅጥቆ መሙላት
፭፡ ከተተከለ በኋላ ውሃ በመጠኑ ማጠጣት (በተለይም አፈሩ ደረቅ ከሆነ)
፮፡ ችግኝ ተሸፍኖባቸው የቆዩትን ፕላስቲኮች በመሰብሰብ በተገቢ ሁኔታ ማስወገድ፡፡
በችግኝ ተከላ ወቅት የሚስተዋሉና መቅረፍ የሚገባን ተደጋጋሚ ስህተቶች
• ችግኝን ከነፕላስቲኩ መትከል፤
• የችግኙ ስር አንዲታይ አድርጎ መትከል፤
• የችግኙን ግንድና ቅጠል ጭምር በጉርጓዱ መቅበር፤
• አፈሩን በትክክል አለመሙላት እና አለመጠቅጠቅ፤
• ችግኙን ሳይተክሉ በጉድጓድ ውስጥ አስቀምጦ ብቻ መሄድ፤
• አጣሞ መትከል፤
• ከአንድ በላይ ችግኝ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ መትከል፤
• የችግኙን ስር አጣሞ መትከል፤
• በውሃ በተሞላ ጉድጓድ ውስጥ መትከል፡፡
ችግኞችንስ ዕንዴት እንንከባከብ?
እንደየ ዝርያ፣ የተተከሉበት አካባቢ እና ወቅት ቢለያይም ችግኞች እስከ ሶስት ዓመታት ድረስ ልዩ እንክብካቤን ይሻሉ፡፡ በዚህም መሰረት ተከታዮቹን መንገዶች ተጠቅመን እንክብካቤን ልንቸራቸው ይገባል፡፡
• ከተተከሉበት ዕለት አንስቶ ችግኞቹን ከሰውና እንስሳት ንክኪ መጠበቅ (ከተቻለ ማጠር)፣ በዙሪያቸው ያለውን አረም፣ ደረቅ ሳር ወዘተ…ማንሳትና ከእሳት መጠበቅ እንዲሁም ከተባይና ነፍሳት ጥቃት በመታደግ ጥበቃ ማድረግ፤
• ብርሃን፣ ውሃና ንጥረ ነገሮችን ስለሚሻሟቸውና ለተባይ መራቢያ ስለሚሆኑ በዙሪያቸው ያለውን አረም ችግኞቹ ከተተከሉ ከሁለተኛው ሳምንት ጀምሮ በተከታታይ ማንሳት፤
• የሞቱ ችግኞች ካሉ ለይቶ መተካት፤
• ከክረምቱ ማብቂያ አንስቶ መኮትኮት፤
• የተተከሉበት አፈር ለምነት የጎደለው ሊሆን ስለሚችል ጉዝጓዝ፣ ቀልዝ፣ ፍግ ወይም ማዳበሪያ ከበጋው ወቅት ጅማሮ አንስቶ ማድረግ፤
• በበጋው ወቅት ሲገባ ወይም የተተከሉት እርጥበት አጠር ቦታ ሲሆን ውሃ ማጠጣት፤
• መመልመልና ማሳሳት፡፡
መልካም የተከላ ጊዜ እንዲሆንልዎ ተመኘን!!!
============================
ሰኞ ሐምሌ ፳፪ በሐገር ዓቀፍ ደረጃ 200 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ ሽር ጉድ ውስጥ እንገኛለን፡፡ ሆኖም ከመትከል ባለፈ ዘመቻው ውጤት ያመጣ ዘንድ ችግኞቹን በአግባቡ መትከል እና መንከባከብ ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ይረዳ ዘንድ ተከታዮቹን ተግባራት በቅደም ተከተል ማከናወን አለብን፡፡
፩፡ በመጀመሪያ ችግኞቹን የምንተክልበት ጉድጓድ ውስጥ እንደ ድንጋይ እንጨት፣ ቅጠል እና ውሃ ያሉ ባዕድ ነገሮች ካሉ ማውጣት አለብን፤
፪፡ ከጉድጓዱ ተቆፍሮ የወጣውን አፈር ከችግኙ ስሮች ይጣጣም ዘንድ እስከ ጉድጓዱ አጋማሽ ድረስ መልሶ መሙላት ይገባል፤
፫፡ በመቀጠልም ችግኙ ላይ ያለውን ፕላስቴክ አፈሩ ሳይፈስብን በጥንቃቄ በመላጥ ችግኙን እስከ ግንዱ መጀመሪያ ድረስ በጉድጓዱ ማኖር፤
፬፡ ችግኞቹ ተጣመው እንዳይቆሙ በመጠንቀቅ ተቆፍሮ የወጣውን አፈር በፕላስቲክ ተሸፍኖ በነበረው አካል ዙሪያው ጠቅጥቆ መሙላት
፭፡ ከተተከለ በኋላ ውሃ በመጠኑ ማጠጣት (በተለይም አፈሩ ደረቅ ከሆነ)
፮፡ ችግኝ ተሸፍኖባቸው የቆዩትን ፕላስቲኮች በመሰብሰብ በተገቢ ሁኔታ ማስወገድ፡፡
በችግኝ ተከላ ወቅት የሚስተዋሉና መቅረፍ የሚገባን ተደጋጋሚ ስህተቶች
• ችግኝን ከነፕላስቲኩ መትከል፤
• የችግኙ ስር አንዲታይ አድርጎ መትከል፤
• የችግኙን ግንድና ቅጠል ጭምር በጉርጓዱ መቅበር፤
• አፈሩን በትክክል አለመሙላት እና አለመጠቅጠቅ፤
• ችግኙን ሳይተክሉ በጉድጓድ ውስጥ አስቀምጦ ብቻ መሄድ፤
• አጣሞ መትከል፤
• ከአንድ በላይ ችግኝ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ መትከል፤
• የችግኙን ስር አጣሞ መትከል፤
• በውሃ በተሞላ ጉድጓድ ውስጥ መትከል፡፡
ችግኞችንስ ዕንዴት እንንከባከብ?
እንደየ ዝርያ፣ የተተከሉበት አካባቢ እና ወቅት ቢለያይም ችግኞች እስከ ሶስት ዓመታት ድረስ ልዩ እንክብካቤን ይሻሉ፡፡ በዚህም መሰረት ተከታዮቹን መንገዶች ተጠቅመን እንክብካቤን ልንቸራቸው ይገባል፡፡
• ከተተከሉበት ዕለት አንስቶ ችግኞቹን ከሰውና እንስሳት ንክኪ መጠበቅ (ከተቻለ ማጠር)፣ በዙሪያቸው ያለውን አረም፣ ደረቅ ሳር ወዘተ…ማንሳትና ከእሳት መጠበቅ እንዲሁም ከተባይና ነፍሳት ጥቃት በመታደግ ጥበቃ ማድረግ፤
• ብርሃን፣ ውሃና ንጥረ ነገሮችን ስለሚሻሟቸውና ለተባይ መራቢያ ስለሚሆኑ በዙሪያቸው ያለውን አረም ችግኞቹ ከተተከሉ ከሁለተኛው ሳምንት ጀምሮ በተከታታይ ማንሳት፤
• የሞቱ ችግኞች ካሉ ለይቶ መተካት፤
• ከክረምቱ ማብቂያ አንስቶ መኮትኮት፤
• የተተከሉበት አፈር ለምነት የጎደለው ሊሆን ስለሚችል ጉዝጓዝ፣ ቀልዝ፣ ፍግ ወይም ማዳበሪያ ከበጋው ወቅት ጅማሮ አንስቶ ማድረግ፤
• በበጋው ወቅት ሲገባ ወይም የተተከሉት እርጥበት አጠር ቦታ ሲሆን ውሃ ማጠጣት፤
• መመልመልና ማሳሳት፡፡
መልካም የተከላ ጊዜ እንዲሆንልዎ ተመኘን!!!
ተልዕኮው ተሳካ፤ እኛም የድርሻችንን ተወጣን !!!
==============================
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢኒትቲትዩት ሰራተኞች የችግኝ ተከላን በጋራ አከናወነዋል፡፡ ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በስሩ የሚገኙ ሌሎች ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ጨምሮ በተሳተፉበት በዚህ ስነ-ስርዓት ከአዲስ አበባ 75 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው የአለልቱ ወረዳ በጠቅላላው 17887 ችግኞች ለመትከል ተችሏል፡፡
አግኝተን ያነጋገርናቸው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታው ዶ/ር ጀማል በሽር ይህ ሐገር ዓቀፍ የችግኝ ተከላተ በጋራ ከተሰራ በሐገር ላይ ዕድገትን ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ እንደሆነ ሲናገሪ የችግኝ ተከላው የተከናወነበት ስፍራም ከመሐል ከተማ መራቁ የገጠሩን ኑሮ ለመገንዘብ ድርብ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ችግኞቹን ከመትከልም ባለፈ የመንከባከብ ተጋባራት በቀጣይነት አንደሚከናወኑ ጠቁመው አልፈዋል፡፡
ይህ የችግኝ የመትከል ስነ-ስርዓት ከላይ ከተጠቀሱት ተቋማትም በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት እንዲሁም የተከበረው ምክር ቤታ ዓባላትም ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡
==============================
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢኒትቲትዩት ሰራተኞች የችግኝ ተከላን በጋራ አከናወነዋል፡፡ ከኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በስሩ የሚገኙ ሌሎች ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ጨምሮ በተሳተፉበት በዚህ ስነ-ስርዓት ከአዲስ አበባ 75 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው የአለልቱ ወረዳ በጠቅላላው 17887 ችግኞች ለመትከል ተችሏል፡፡
አግኝተን ያነጋገርናቸው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታው ዶ/ር ጀማል በሽር ይህ ሐገር ዓቀፍ የችግኝ ተከላተ በጋራ ከተሰራ በሐገር ላይ ዕድገትን ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ እንደሆነ ሲናገሪ የችግኝ ተከላው የተከናወነበት ስፍራም ከመሐል ከተማ መራቁ የገጠሩን ኑሮ ለመገንዘብ ድርብ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም ችግኞቹን ከመትከልም ባለፈ የመንከባከብ ተጋባራት በቀጣይነት አንደሚከናወኑ ጠቁመው አልፈዋል፡፡
ይህ የችግኝ የመትከል ስነ-ስርዓት ከላይ ከተጠቀሱት ተቋማትም በተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት እንዲሁም የተከበረው ምክር ቤታ ዓባላትም ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡