ሜዲካል ቱሪዝም
***************
ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ከሐገራቸው በመውጣት የሕክምና አገልግሎትን እንዲገኙ ሊገደዱ ይችላሉ፡፡ ይህ እንቅስቃሴ ሜዲካል ቱሪዝም በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ኢንዱስትሪ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየገዘፈና በጤናው ዘርፍ የተሸለ ደረጃ ላይ የደረሱት ሐገራትንም ከቀን ወደቀን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ቁጥራቸው የበዛ ሐገራት እና ፖሊሲ አውጪዎቻቸውም በዘርፉ ላይ አይናቸውን ከጣሉ ሰነባብተዋል፡፡
ሜዲካል ቱሪዝም ከረጅም ጊዜያት አንስቶ ሲተገበር የቆየ የህክምናው ኢንዱስትሪ አካል ነው፡፡ በተወሰኑ ሐገራት ያሉት ፈዋሽ ፍል ውሃዎች ቀዳሚዎቹ የሜዲካል ቱሪዝም አስጀማሪዎች ነበሩ፡፡ ታድያ ከጥቂት አስርት ዓመታት ወዲህ በተወሰኑ የህክምና አገልግሎቶች ብቻ ሳይወሰን ከፍተኛ የዘርፍ ዕድገትን እያስመዘገበ ይገኛል፡፡ ለዚህ የቁጥጥር ስርዓቶች፣ የቴክኖሎጂ ዕድገት፣ የባለ ዝቅተኛ ታሪፍ አየር መንገዶች መስፋፋት፣ በባህል ዙሪያ እየተቀየረ ያለው አመለካከት እና ሌሎችም በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የደቡብ ምስርቅ እሲያ፣ አውሮፓ እና ላቲን አሜሪካ ሐገራት ቀዳሚዎቹ የሜዲካል ቱሪዝም መዳረሻ በመሆን ገበያውን ይመራሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ እንደ ህንድ፣ ማሌዢያ፣ ታይላንድ፣ ሲንጋፖር፣ ብራዚል፣ ኩባ፣ ሜክሲኮ እና ኮስታ ቀዳሚ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከነዚህ ክልሎች ወጣ ብለው በተቀመጡት ደቡብ አፍሪካ እና የተባበሩት አረብ ኢምሬቶችም የሜዲካል ቱሪዝም እንቅስቃሴ ጎልቶ በመታየት ላይ ነው፡፡ ለነዚህ ሐገራት ጎልቶ መውጣት የተለያዩ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ፡- አንፃራዊ የዋጋ ልዩነት፣ የሐገራቱ ትስስር፣ የህክምናው ዓይነት፣ መልከዓ ምድራዊ ቅርበት እንዲሁም የጤና መሰረተ ልማት፡፡ ከነዚህ መካከል በህክምው ዓይነት ላይ የተመሰረቱትን ያየን እንደሆን በላቲን አሜሪካን ያሉ ሐገራት በጥርስ፣ ውፍረት ቅነሳ፣ ውበት እና ፕላስቲክ ቀዶ ህክምናዎች የጠነከረ ስምን ለመገንባት ችለዋል፡፡ ህንድን ጨምሮ እነደ ማሌዢያ፣ ሲንጋፖር እና ታይላንድ ያሉ የደቡብ ምስራቅ እሲያ ሐገራት ደግሞ በልብ እንዲሁም አጥንትና ጡንቻ ህክምናዎች ዝናን አግኝተዋል፡፡ ሌላው በዋጋ ረገድ ሐገራት ያላቸው ተመራጭነት ነው፡፡ በዚህ ረገድ የደቡብ ምስራቅ እሲያ ሐገራት ባላቸው አንፃራዊ የዋጋ ቅናሽ ከበለፀጉት ሐገራት ጭምር ታካሚዎችን ለመሳብ ችለዋል፡፡
ሆኖም እንደሌሎቹ ዘርፎች ሁሉ የሜዲካል ቱሪዝምም ከተግዳሮቶች አላመለጠም፡፡ በተለይ በህክምና እንዲሁም ስነ-ምግባር እና ሕግ ተኮር በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያሉ ስጋቶች ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ ለዚህ ሐገራት ያላቸው የተለያየ የህክምና ፍቃድ አሰጣጥ፣ አሰራር እና ሕግጋት እንዲሁም እነዚህን ተከትሎ የሚመጣው የህምና ተቋማት እና ባለሙያዎች ደረጃ መለያየት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡
ወደ ሐገራችን ስንመጣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ታካሚዎችን ወደ ውጪ ሐገራት በመስደድ ላይ እንገኛለን፡፡ ይህም ለሐገራችን ሌላ ምጣኔ-ሐብታዊና ማሕበራዊ ጫና ይዞልን መጥቷል፡፡ ይህን ሁናቴ የሚለውጡና ሐገራችንን ወደ ሌላ የሜዲካል ቱሪዝም መዳረሻነት ከፍ የሚያደርጉ እርምጃዎችን መውሰድ ከመንግስትም ሆነ የግል ባለሐብቶች ይጠበቃል፡፡ ታድያ ምንም እንኳን በዘርፉ መሪ ወደሆኑት ሀገራት ለመጠጋት ረጅም ጊዜን የሚፈጅ ቢሆንም ባለንበት አካባቢ እንኳን የስበት ማዕከል የሚያደርጉንን ስራዎች መስራት ይገባናል፡፡
ምንጭ፡- News Medical
***************
ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ከሐገራቸው በመውጣት የሕክምና አገልግሎትን እንዲገኙ ሊገደዱ ይችላሉ፡፡ ይህ እንቅስቃሴ ሜዲካል ቱሪዝም በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ኢንዱስትሪ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየገዘፈና በጤናው ዘርፍ የተሸለ ደረጃ ላይ የደረሱት ሐገራትንም ከቀን ወደቀን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ቁጥራቸው የበዛ ሐገራት እና ፖሊሲ አውጪዎቻቸውም በዘርፉ ላይ አይናቸውን ከጣሉ ሰነባብተዋል፡፡
ሜዲካል ቱሪዝም ከረጅም ጊዜያት አንስቶ ሲተገበር የቆየ የህክምናው ኢንዱስትሪ አካል ነው፡፡ በተወሰኑ ሐገራት ያሉት ፈዋሽ ፍል ውሃዎች ቀዳሚዎቹ የሜዲካል ቱሪዝም አስጀማሪዎች ነበሩ፡፡ ታድያ ከጥቂት አስርት ዓመታት ወዲህ በተወሰኑ የህክምና አገልግሎቶች ብቻ ሳይወሰን ከፍተኛ የዘርፍ ዕድገትን እያስመዘገበ ይገኛል፡፡ ለዚህ የቁጥጥር ስርዓቶች፣ የቴክኖሎጂ ዕድገት፣ የባለ ዝቅተኛ ታሪፍ አየር መንገዶች መስፋፋት፣ በባህል ዙሪያ እየተቀየረ ያለው አመለካከት እና ሌሎችም በገፊ ምክንያትነት ይጠቀሳሉ፡፡
በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የደቡብ ምስርቅ እሲያ፣ አውሮፓ እና ላቲን አሜሪካ ሐገራት ቀዳሚዎቹ የሜዲካል ቱሪዝም መዳረሻ በመሆን ገበያውን ይመራሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ እንደ ህንድ፣ ማሌዢያ፣ ታይላንድ፣ ሲንጋፖር፣ ብራዚል፣ ኩባ፣ ሜክሲኮ እና ኮስታ ቀዳሚ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ከነዚህ ክልሎች ወጣ ብለው በተቀመጡት ደቡብ አፍሪካ እና የተባበሩት አረብ ኢምሬቶችም የሜዲካል ቱሪዝም እንቅስቃሴ ጎልቶ በመታየት ላይ ነው፡፡ ለነዚህ ሐገራት ጎልቶ መውጣት የተለያዩ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ፡- አንፃራዊ የዋጋ ልዩነት፣ የሐገራቱ ትስስር፣ የህክምናው ዓይነት፣ መልከዓ ምድራዊ ቅርበት እንዲሁም የጤና መሰረተ ልማት፡፡ ከነዚህ መካከል በህክምው ዓይነት ላይ የተመሰረቱትን ያየን እንደሆን በላቲን አሜሪካን ያሉ ሐገራት በጥርስ፣ ውፍረት ቅነሳ፣ ውበት እና ፕላስቲክ ቀዶ ህክምናዎች የጠነከረ ስምን ለመገንባት ችለዋል፡፡ ህንድን ጨምሮ እነደ ማሌዢያ፣ ሲንጋፖር እና ታይላንድ ያሉ የደቡብ ምስራቅ እሲያ ሐገራት ደግሞ በልብ እንዲሁም አጥንትና ጡንቻ ህክምናዎች ዝናን አግኝተዋል፡፡ ሌላው በዋጋ ረገድ ሐገራት ያላቸው ተመራጭነት ነው፡፡ በዚህ ረገድ የደቡብ ምስራቅ እሲያ ሐገራት ባላቸው አንፃራዊ የዋጋ ቅናሽ ከበለፀጉት ሐገራት ጭምር ታካሚዎችን ለመሳብ ችለዋል፡፡
ሆኖም እንደሌሎቹ ዘርፎች ሁሉ የሜዲካል ቱሪዝምም ከተግዳሮቶች አላመለጠም፡፡ በተለይ በህክምና እንዲሁም ስነ-ምግባር እና ሕግ ተኮር በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያሉ ስጋቶች ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ ለዚህ ሐገራት ያላቸው የተለያየ የህክምና ፍቃድ አሰጣጥ፣ አሰራር እና ሕግጋት እንዲሁም እነዚህን ተከትሎ የሚመጣው የህምና ተቋማት እና ባለሙያዎች ደረጃ መለያየት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡
ወደ ሐገራችን ስንመጣ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ታካሚዎችን ወደ ውጪ ሐገራት በመስደድ ላይ እንገኛለን፡፡ ይህም ለሐገራችን ሌላ ምጣኔ-ሐብታዊና ማሕበራዊ ጫና ይዞልን መጥቷል፡፡ ይህን ሁናቴ የሚለውጡና ሐገራችንን ወደ ሌላ የሜዲካል ቱሪዝም መዳረሻነት ከፍ የሚያደርጉ እርምጃዎችን መውሰድ ከመንግስትም ሆነ የግል ባለሐብቶች ይጠበቃል፡፡ ታድያ ምንም እንኳን በዘርፉ መሪ ወደሆኑት ሀገራት ለመጠጋት ረጅም ጊዜን የሚፈጅ ቢሆንም ባለንበት አካባቢ እንኳን የስበት ማዕከል የሚያደርጉንን ስራዎች መስራት ይገባናል፡፡
ምንጭ፡- News Medical
3ኛው ዓለም ዓቀፍ የICT ኤክስፖ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ
*************
ኢኖቬት ኢትዮጵያ በሚል መሪ ቃል ለአምስት ቀናት የሚከናወነው 3ኛው ዓለም አቀፍ የICT ኤክስፖ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ተጀምሯል፡፡
የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሐገራችን ለገባችበት የለውጥ ምህዋር ስኬት ሳይንስና ኢኖቬሽን ትልቅ ድርሻ እንዳለው አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ በተያያዘም የተለያዩ ዘርፎቻችን በቴክኖሎጂ በማገዝ ማበልፀግና ሐገራችንንም አሁን ካለችበት የቴክኖሎጂ ኋላ ቀርናት ማላቀቅ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴሩ ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ በበኩላቸው ዘርፉ ላይ በሚሰሩት ሐገሀራዊ እንዲሁም ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ያተኮረ ንግር ለታዳሚያኑ አድርገዋል፡፡ በሐገራችን የ25 ሺህ ኪ.ሜ ፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታ የተከናወነ መሆኑንና ከወረዳ አንስቶ ባሉት ልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሴኮንድ እስከ 1 ጊጋ ባይት ፍጥነት ያለው የፊክስድ ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎትም ዝርጋታ በአንድ ዓመት ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምር ገልፀዋል፡፡
በኤክስፖው ላይ በሐገር ውስጥ እና ዊጪ ሐገራት መሰረታቸውን ያደረጉ በርካታ የግል እንዲሁም የመንግስት ተቋማት ተሳታፊ የሚሆኑበት ሲሆን ቁጥሩ ከፍ ያለ ህብረተሰብም እንደሚጎበኘው ይጠበቃል፡፡
*************
ኢኖቬት ኢትዮጵያ በሚል መሪ ቃል ለአምስት ቀናት የሚከናወነው 3ኛው ዓለም አቀፍ የICT ኤክስፖ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ተጀምሯል፡፡
የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ሐገራችን ለገባችበት የለውጥ ምህዋር ስኬት ሳይንስና ኢኖቬሽን ትልቅ ድርሻ እንዳለው አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ በተያያዘም የተለያዩ ዘርፎቻችን በቴክኖሎጂ በማገዝ ማበልፀግና ሐገራችንንም አሁን ካለችበት የቴክኖሎጂ ኋላ ቀርናት ማላቀቅ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴሩ ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ በበኩላቸው ዘርፉ ላይ በሚሰሩት ሐገሀራዊ እንዲሁም ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ያተኮረ ንግር ለታዳሚያኑ አድርገዋል፡፡ በሐገራችን የ25 ሺህ ኪ.ሜ ፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታ የተከናወነ መሆኑንና ከወረዳ አንስቶ ባሉት ልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሴኮንድ እስከ 1 ጊጋ ባይት ፍጥነት ያለው የፊክስድ ብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎትም ዝርጋታ በአንድ ዓመት ውስጥ ተጠናቆ አገልግሎት እንደሚጀምር ገልፀዋል፡፡
በኤክስፖው ላይ በሐገር ውስጥ እና ዊጪ ሐገራት መሰረታቸውን ያደረጉ በርካታ የግል እንዲሁም የመንግስት ተቋማት ተሳታፊ የሚሆኑበት ሲሆን ቁጥሩ ከፍ ያለ ህብረተሰብም እንደሚጎበኘው ይጠበቃል፡፡
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሰራተኞች የዕፅዋት ተከላን አከናወኑ
******************
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስትቲውት ሰተራተኞች በዛሬው እለት የአዲስ አዳማ የፍጥነት መንገድ ላይ በመገኘት ዕፅዋትን ተክለዋል፡፡ ከኢትዮጵያ የክፍያ መንዶች ኢንተርፕራይዝ ጋራ በጋራ የተከወነው ይህ የዕፅዋት ተከላ በዓመቱ አራት ቢሊዮን ዕፅዋትን ለመትከል የተያዘው ሐገራዊ ዕቅድ አካል ነው፡፡
ይህን ተግባር በማስመልከት ቃለ መጠይቅ ያደረግንላቸው የኢንስትቲውታችን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ መሰል ክንውኖች ለተቋሙ አዲስ ሁነት እንዳልሆነና ከዚህ ቀደምም በተያዩ ጊዜያት ዕፅዋትን የመትከል ስነ ስራ እንደተሰራ ገልፀውልናል፡፡ አያይዘውም የተጀመረውን ሐገር ዓቀፍ እንቅስቃሴ በበጎ በመመልከት ሌሎች አካላትም እንዲሁ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
በዓመት ሰባት ሚሊዮን ህዝብ በአየር መበከል ምክንያት ለህልፈተ ህይወት ሲዳረግ 2.4 ሚሊዮን የሚሆኑትም ደግሞ የዓየር ንብረት መበከልን ተከትሎ በሚመጣ የልብ ህመም ህይወታቸውን ያጣሉ፡፡
******************
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስትቲውት ሰተራተኞች በዛሬው እለት የአዲስ አዳማ የፍጥነት መንገድ ላይ በመገኘት ዕፅዋትን ተክለዋል፡፡ ከኢትዮጵያ የክፍያ መንዶች ኢንተርፕራይዝ ጋራ በጋራ የተከወነው ይህ የዕፅዋት ተከላ በዓመቱ አራት ቢሊዮን ዕፅዋትን ለመትከል የተያዘው ሐገራዊ ዕቅድ አካል ነው፡፡
ይህን ተግባር በማስመልከት ቃለ መጠይቅ ያደረግንላቸው የኢንስትቲውታችን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ መሰል ክንውኖች ለተቋሙ አዲስ ሁነት እንዳልሆነና ከዚህ ቀደምም በተያዩ ጊዜያት ዕፅዋትን የመትከል ስነ ስራ እንደተሰራ ገልፀውልናል፡፡ አያይዘውም የተጀመረውን ሐገር ዓቀፍ እንቅስቃሴ በበጎ በመመልከት ሌሎች አካላትም እንዲሁ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
በዓመት ሰባት ሚሊዮን ህዝብ በአየር መበከል ምክንያት ለህልፈተ ህይወት ሲዳረግ 2.4 ሚሊዮን የሚሆኑትም ደግሞ የዓየር ንብረት መበከልን ተከትሎ በሚመጣ የልብ ህመም ህይወታቸውን ያጣሉ፡፡
የICT ኤክስፖ ላይ በመገኘት ይጎብኙን
ኢኖቬት ኢትዮጵያ በሚል መሪ ቃል ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲከናወን የቆየው 3ኛው ዓለም አቀፍ የICT ኤክስፖ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ፍፃሜውን ያደርጋል፡፡ በዚህ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ አስመጪዎች፣ አገልግሎት ሰጪ አካላት እና ሌሎች ሐገራዊ እንዲሁም ግዙፍ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡
ታድያ በዚህ አውደ ርዕይ ላይ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩትም እንደ አንድ የቴክኖሎጂ ተቋም እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ በዝግጅቱ ይዘን ከቀረብናቸው ስራዎቻችን መካከል የዲጂታል ቤተ-መፅሐፍት (ከአጠቃቀም ገለፃ ጋር)፣ በወረቀት ላይ የሰፈሩ ፅሁፎችን ወደ ኮምፒውተራችን ገልብጠን ማስተካከል የሚያስችለንን ቴክኖሎጂ እነዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ ስራዎቻችንን እናስዳስስዎታለን፡፡ በተጨማሪም ተቋማችን በየሶስት ወሩ የሚያሳትመውን የቴክ-ሳይንስ መፅሐፍት እና የሐገራችንን ጠሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽ ሁናቴ የሚቃኙ የዳሰሳ ጥናቶችን በነፃ ያገኛሉ፡፡
ይፍጠኑ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ በማምራት ይጎብኙን!!!
ኢኖቬት ኢትዮጵያ በሚል መሪ ቃል ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲከናወን የቆየው 3ኛው ዓለም አቀፍ የICT ኤክስፖ ዛሬ በሚሊኒየም አዳራሽ ፍፃሜውን ያደርጋል፡፡ በዚህ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ አስመጪዎች፣ አገልግሎት ሰጪ አካላት እና ሌሎች ሐገራዊ እንዲሁም ግዙፍ ዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡
ታድያ በዚህ አውደ ርዕይ ላይ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩትም እንደ አንድ የቴክኖሎጂ ተቋም እየተሳተፈ ይገኛል፡፡ በዝግጅቱ ይዘን ከቀረብናቸው ስራዎቻችን መካከል የዲጂታል ቤተ-መፅሐፍት (ከአጠቃቀም ገለፃ ጋር)፣ በወረቀት ላይ የሰፈሩ ፅሁፎችን ወደ ኮምፒውተራችን ገልብጠን ማስተካከል የሚያስችለንን ቴክኖሎጂ እነዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ ስራዎቻችንን እናስዳስስዎታለን፡፡ በተጨማሪም ተቋማችን በየሶስት ወሩ የሚያሳትመውን የቴክ-ሳይንስ መፅሐፍት እና የሐገራችንን ጠሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽ ሁናቴ የሚቃኙ የዳሰሳ ጥናቶችን በነፃ ያገኛሉ፡፡
ይፍጠኑ ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ በማምራት ይጎብኙን!!!
9ኛው ሐገር አቀፍ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ሽልማት ተከናውኗል፡፡ በክብር እንግድነት ተገኝተው ሽልማቶችን ያበረከቱት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር ዓብይ አህመድ ተሸላሚዎቹ ስራዎቻቸው የረጅም ጉዞዋቸው ጅማሬ እንደሆኑና በሐገራችን ያለው የሐብትና ግብዓት እጥረት ሳይገታቸው ወደፊትም ለተሸለ ፈጠራ እንዲተጉ በማሳሰብ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ሐገራችን ፈጣሪ አዕምሮ ያላቸው ዜጎች እጥረት እንዳለባት ያመላከቱት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ ስራዎች መሰራት እንዳለባቸውና የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርም እነዚህን ባለ ብሩክ ተስፋዎች ከመሸለም ባለፈ ከኢንዱስትሪዎች የማስተሳሰር ስራን ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የሐገር ዓቀፉ የፈጠራ ሳምንት መዝጊያ ጭምር በነበረው በዚህ በስነ ስርዓት ላይ 177 ከአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ተማሪና መምህራን ብሎም በግላቸው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ተሸላሚ እንደሆኑበት የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ሚኒስትትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ ገልፀዋል፡፡ ሚኒስትሩ አያይዘውም ቴክኖሎጂን ያላማከሉ ማህበራዊም ሆነ ምጣኔ-ሐብታዊ እንቅስቃሴዎች ከስኬት ስለማይደርሱ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙትን ህፃናት ከቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የነገዎቹን ታላላቅ የፈጠራ ባለሙያዎች መፍጠር እንዳለብን አብራርተዋል፡፡
ከ2002 ዓ.ም አንስቶ ሲከናወን በቆየው በዚህ ሽልማት ከ1800 በላይ የፈጠራ ባለሙያዎች ተሸላሚ ሆነውበታል፡፡
የሐገር ዓቀፉ የፈጠራ ሳምንት መዝጊያ ጭምር በነበረው በዚህ በስነ ስርዓት ላይ 177 ከአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት እንዲሁም ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ተማሪና መምህራን ብሎም በግላቸው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ተሸላሚ እንደሆኑበት የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ሚኒስትትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ ገልፀዋል፡፡ ሚኒስትሩ አያይዘውም ቴክኖሎጂን ያላማከሉ ማህበራዊም ሆነ ምጣኔ-ሐብታዊ እንቅስቃሴዎች ከስኬት ስለማይደርሱ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙትን ህፃናት ከቴክኖሎጂ በማስተሳሰር የነገዎቹን ታላላቅ የፈጠራ ባለሙያዎች መፍጠር እንዳለብን አብራርተዋል፡፡
ከ2002 ዓ.ም አንስቶ ሲከናወን በቆየው በዚህ ሽልማት ከ1800 በላይ የፈጠራ ባለሙያዎች ተሸላሚ ሆነውበታል፡፡
የመጀመሪያው የክህሎት ውድድር ተጀመረ
************************************
የመጀመሪያው ሐገር ዓቀፍ የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድር በተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ስራዎች ታጅቦ ትናንት ተጀምሯል፡፡ በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኤጀንሲና በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኢንስትቲውት በጋራ የሚዘጋጀው ይህ ውድድር “በክህሎትና ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለሰላምና ልማታችን ዋስትና ናቸው” በሚል መሪ ቃል እስከ ሰኔ 11 የሚዘልቅ ይሆናል፡፡ በተሳታፊነትም የተለያዩ የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዝ ኦፕሬተሮች ተካፋይ ያደርጋል፡፡
የዕለቱ የክብር ዕንግዳ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አህመድ ሺዴ መንግስት ትምህርት እና ስልጠና ለሐገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት መሰረታዊ መሆኑን ተረድቶ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱን ገልፀዋል፡፡ ክቡር ሚንስትሩ “ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ዜጎችንም ያፈራል” ባሉት ቴክኒክ እና ሙያ ተቋም ላይ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን አመለካከት ለማሻሻል የአተያይና የግንዛቤ ስራዎች መስራት እንደሚገባ አስቀምጠዋል፡፡ በመጨረሻም ዘርፉን ለማጎልበት እና የህብረተሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ ስራዎችን በጥናትና ምርምር መደገፍ እንደሚገባ በማሳሰብ በውድድሩ ለተሳተፉ ሰልጣኝ፣ አሰልጣኞች እና እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በዝግጅቱ የእንኳን ደህና መጣችው ንግግሩን ያቀረቡት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ሚንስትር ደኤታው ዶክተር አብዲዋሳ አብዱላሂ ትምህርት ለአንድን ሐገር የልማት መሳሪያና የእድገት ፍትሐዊነት ማረጋገጫ እንደሆነ ሲገልፁ፤ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠናም የሰው ልጆችን ድህነትና ስራ አጥትን ለማስወገድ እንዲሁም ሰላምን ለማረገገጥ የቁልፎች ሁሉ ቁልፍ ነው ብለዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና አንዱ ተልዕኮ የቴክሎጂ አቅምን በመገንባት ኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪ ማድረግ ቢሆንም ባለው የቅንጅት አሰራር፣ የማበረታቻ ስርዓት፣ የእይታ መድረኮች እና ኢንዱስትሪዎች ላይ መተግበሪያ መንገዶች አለመኖር ሳቢያ ይህ ሚናቸውን በብቃት መወጣት እንዳልቻሉ የተናገሩት ዶክተር አብዲዋሳ እነዚህን ተግዳሮቶች በመፍታት እና መሰል የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድሮችን ከታች ከወረዳ አንስቶ እስከ ሐገር ዓቀፍ ድረስ ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡
ውድድሩ የተወዳዳሪዎቹን ስራዎች በዓውደ ርዕይ መልክ በማሳየት እና የዘርፉን አቋም የሚገመግሙ የፓናል ውይይቶች በማካሄድ የሚቀጥል ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላሳዩ 11 ተወዳዳሪዎችም የሚበረከትላቸው ይሆናል፡፡
************************************
የመጀመሪያው ሐገር ዓቀፍ የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድር በተለያዩ ኪነ ጥበባዊ ስራዎች ታጅቦ ትናንት ተጀምሯል፡፡ በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኤጀንሲና በፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ኢንስትቲውት በጋራ የሚዘጋጀው ይህ ውድድር “በክህሎትና ስነ ምግባር የታነፀ ትውልድ ለሰላምና ልማታችን ዋስትና ናቸው” በሚል መሪ ቃል እስከ ሰኔ 11 የሚዘልቅ ይሆናል፡፡ በተሳታፊነትም የተለያዩ የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞች እና ኢንተርፕራይዝ ኦፕሬተሮች ተካፋይ ያደርጋል፡፡
የዕለቱ የክብር ዕንግዳ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የፌደራል ቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ አህመድ ሺዴ መንግስት ትምህርት እና ስልጠና ለሐገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት መሰረታዊ መሆኑን ተረድቶ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት መንቀሳቀሱን ገልፀዋል፡፡ ክቡር ሚንስትሩ “ስራ ፈላጊ ብቻ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ ዜጎችንም ያፈራል” ባሉት ቴክኒክ እና ሙያ ተቋም ላይ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን አመለካከት ለማሻሻል የአተያይና የግንዛቤ ስራዎች መስራት እንደሚገባ አስቀምጠዋል፡፡ በመጨረሻም ዘርፉን ለማጎልበት እና የህብረተሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ ስራዎችን በጥናትና ምርምር መደገፍ እንደሚገባ በማሳሰብ በውድድሩ ለተሳተፉ ሰልጣኝ፣ አሰልጣኞች እና እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በዝግጅቱ የእንኳን ደህና መጣችው ንግግሩን ያቀረቡት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ሚንስትር ደኤታው ዶክተር አብዲዋሳ አብዱላሂ ትምህርት ለአንድን ሐገር የልማት መሳሪያና የእድገት ፍትሐዊነት ማረጋገጫ እንደሆነ ሲገልፁ፤ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠናም የሰው ልጆችን ድህነትና ስራ አጥትን ለማስወገድ እንዲሁም ሰላምን ለማረገገጥ የቁልፎች ሁሉ ቁልፍ ነው ብለዋል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠና አንዱ ተልዕኮ የቴክሎጂ አቅምን በመገንባት ኢንዱስትሪዎችን ተወዳዳሪ ማድረግ ቢሆንም ባለው የቅንጅት አሰራር፣ የማበረታቻ ስርዓት፣ የእይታ መድረኮች እና ኢንዱስትሪዎች ላይ መተግበሪያ መንገዶች አለመኖር ሳቢያ ይህ ሚናቸውን በብቃት መወጣት እንዳልቻሉ የተናገሩት ዶክተር አብዲዋሳ እነዚህን ተግዳሮቶች በመፍታት እና መሰል የቴክኖሎጂ ክህሎት እና ተግባራዊ ምርምር ውድድሮችን ከታች ከወረዳ አንስቶ እስከ ሐገር ዓቀፍ ድረስ ማከናወን ይገባል ብለዋል፡፡
ውድድሩ የተወዳዳሪዎቹን ስራዎች በዓውደ ርዕይ መልክ በማሳየት እና የዘርፉን አቋም የሚገመግሙ የፓናል ውይይቶች በማካሄድ የሚቀጥል ሲሆን ከፍተኛ ውጤት ላሳዩ 11 ተወዳዳሪዎችም የሚበረከትላቸው ይሆናል፡፡
“ሐገር የምትገነባው ከታች ጀምሮ ነው !” ክብርት ፕሬዘዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
************************************
የኢፌድሪ ፕሬዘዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመጀመሪያው ሐገራዊ የክህሎት ውድድር መቋጫ ላይ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስኬቶችን ቢመዘገቡም ዘርፉ ላይ የሚታየውን ሰፊ ክፍተት ለመድፈን የሁሉም አካላት ተሳትፎን እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ ሐገር የምትገነባው ከታች ጀምሮ ነው ያሉት ክብርት ፕሬዘዳንቷ ህብረተሰቡ በቴክኒክ እና ሙያ ላይ ያለውን አመለካከት የሚለውጡ የተግባርና ግንዛቤ ስራዎች እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
Technology Installation እና Database Administration ጨምሮ በአስራ አንድ ምድቦች ተከፍለው ከተወዳደሩት የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኝ፣ አሰልጣን እና ኢንተርፕራይዞች መካከል በየምድባቸው ከአንድ እስከ ሶስተኛ ለወጡት ተወዳዳሪዎች እንደየ ደረጃቸው የሜዳሊያ፣ ገንዘብ እና ሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በዕለቱ ክብርት ፕሬዘዳንቷን ጨምሮ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ሚኒስትር ደኤታዎቹ ዶክተር ሂሩት እና ዶክተር አብዲዋሳ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ሲገኙ የተሳታፊዎቹን ስራንም ለመጎብኘት ችለዋል፡፡
************************************
የኢፌድሪ ፕሬዘዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመጀመሪያው ሐገራዊ የክህሎት ውድድር መቋጫ ላይ የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ስኬቶችን ቢመዘገቡም ዘርፉ ላይ የሚታየውን ሰፊ ክፍተት ለመድፈን የሁሉም አካላት ተሳትፎን እንደሚሻ ተናግረዋል፡፡ ሐገር የምትገነባው ከታች ጀምሮ ነው ያሉት ክብርት ፕሬዘዳንቷ ህብረተሰቡ በቴክኒክ እና ሙያ ላይ ያለውን አመለካከት የሚለውጡ የተግባርና ግንዛቤ ስራዎች እንደሚሰሩ ገልፀዋል፡፡
Technology Installation እና Database Administration ጨምሮ በአስራ አንድ ምድቦች ተከፍለው ከተወዳደሩት የቴክኒክ እና ሙያ ሰልጣኝ፣ አሰልጣን እና ኢንተርፕራይዞች መካከል በየምድባቸው ከአንድ እስከ ሶስተኛ ለወጡት ተወዳዳሪዎች እንደየ ደረጃቸው የሜዳሊያ፣ ገንዘብ እና ሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በዕለቱ ክብርት ፕሬዘዳንቷን ጨምሮ የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ሚኒስትር ደኤታዎቹ ዶክተር ሂሩት እና ዶክተር አብዲዋሳ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ት ፍሬህይወት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ሲገኙ የተሳታፊዎቹን ስራንም ለመጎብኘት ችለዋል፡፡