የዝሆኔ በሽታን በሚከላከሉ ምርቶች ላይ የዘጠና ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ሊደረግ ነው
**********************************************መቀመጫውን አሜሪካን ያደረገው ፈርትል ክርኤቲቭ ላብስ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ከሼዲ ግሮቭ ግሩፕ አማካሪ ተቋም ጋር በሚሰሯቸው የዝሆኔ በሽታን (Mycetoma) ተከላካይ ጓንት እና ጫማዎች ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ውስጥ ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ እንዲሁም የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዱካን ደበበን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች የተሳተፉበት ሲሆን የፈርትል ክርኤቲቭ ላብስ እና ሼዲ ግሮቭ ገሩፕ ሃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሙሉጌታ አለምሰገድ እና ዶ/ር ደረጄ ተሰማ ተገኝተውበታል፡፡ ተቋሙ በኢትዮጵያ ለማምረት ስላቀዳቸው የዝሆኔ በሽታን መከላከያዎች በዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ሙሉጌታ አለምሰገድ አማካኝነት ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ስለ ተቋማቸው ምንነት፣ ስለሚያከናውኗቸው ተግባራት እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሊያመጡ ባቀዷቸው ትሩፋቶች ዙሪያ ለታዳሚዎቹ ገለፃ አቅርበዋል፡፡
ፕሮጀክቱ እነዚህን የመከላከያ ጓንት እና ጫማዎችን የዝሆኔ በሽታ በብዛት በሚታይባቸው አራት ዋና ዋና የዓለማችን ክፍሎች የሚያሰራጭ ሲሆን ኢትዮጵያም ከሌሎች የአፍሪካ ቀንድ ሃገራት ጋር በጋራ በመሆን ዞን አንድ ውስጥ ተካታለች፡፡ ታድያ የመከላከያዎቹ ቅድመ ምርት ስራዎቹ በሃገረ አሜሪካን የሚሰሩ ሲሆን የማምረት እና ማሰራጨት ተግባራቱ ግን እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ይከወናሉ፡፡ በዚህም ሳቢያ የዘጠና ሚሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ ኢትዮጵያ ውስጥ ለማድረግ ታቅዷል፡፡ ይህም 1,600 የፋብሪካ ውስጥ እና 2,400 ከምርት ሽያጭ ጋር ለተገናኙ የስራ ዕድሎች መፈጠር ምክንያት እንደሚሆን ታምኖበታል፡፡ ምርቱን ተግባራዊ ለማድረግ ከተለያዩ የሃገሪቱ የምርምር እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ዶ/ር ዮናታን በውይይቱ የገለፁ ሲሆን ከመንግስት አፋጣኝ የኢንቨስትመንት ፍቃድን ከማግኘት አንስቶ የተለያዩ ድጋፎች ይደረግላቸው ዘንድ ጥያቄን አቅርበዋል፡፡
ፈርትል ክርኤቲቭ ላብስ መቀመጫውን ሚሺጋን አሜሪካን ውስጥ በማድረግ የተመሰረተና እንደ ዓለም ጤና ድርጅት ካሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ የሚሰራ ኩባንያ ሲሆን በምርምር እና ስርፀት ላይ ትኩረቱን በማድረግ ይንቀሳቀሳል፡፡ ሳና ብሎ የሰየማቸው የዝሆኔ በሽታን መከላከያ ጫማና ጓንቶቹም በአይነታቸው የመጀመሪያ ናቸው፡፡ እነዚህ ምርቶች ፀረ-ባክቴሪያ እና ውሃን የማያሳልፉ ከመሆናቸውም ባሻገር ምቹና ሌሎች ገፅታዎችንም አቅፈው የያዙ ናቸው፡፡ የምርት ሂደታቸውም በዋነኝነት በ3ዲ ማተሚያ ማሽኖች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
**********************************************መቀመጫውን አሜሪካን ያደረገው ፈርትል ክርኤቲቭ ላብስ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ከሼዲ ግሮቭ ግሩፕ አማካሪ ተቋም ጋር በሚሰሯቸው የዝሆኔ በሽታን (Mycetoma) ተከላካይ ጓንት እና ጫማዎች ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ውስጥ ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶ/ር ጌታሁን መኩሪያ እንዲሁም የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዱካን ደበበን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች የተሳተፉበት ሲሆን የፈርትል ክርኤቲቭ ላብስ እና ሼዲ ግሮቭ ገሩፕ ሃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሙሉጌታ አለምሰገድ እና ዶ/ር ደረጄ ተሰማ ተገኝተውበታል፡፡ ተቋሙ በኢትዮጵያ ለማምረት ስላቀዳቸው የዝሆኔ በሽታን መከላከያዎች በዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ሙሉጌታ አለምሰገድ አማካኝነት ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ስለ ተቋማቸው ምንነት፣ ስለሚያከናውኗቸው ተግባራት እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሊያመጡ ባቀዷቸው ትሩፋቶች ዙሪያ ለታዳሚዎቹ ገለፃ አቅርበዋል፡፡
ፕሮጀክቱ እነዚህን የመከላከያ ጓንት እና ጫማዎችን የዝሆኔ በሽታ በብዛት በሚታይባቸው አራት ዋና ዋና የዓለማችን ክፍሎች የሚያሰራጭ ሲሆን ኢትዮጵያም ከሌሎች የአፍሪካ ቀንድ ሃገራት ጋር በጋራ በመሆን ዞን አንድ ውስጥ ተካታለች፡፡ ታድያ የመከላከያዎቹ ቅድመ ምርት ስራዎቹ በሃገረ አሜሪካን የሚሰሩ ሲሆን የማምረት እና ማሰራጨት ተግባራቱ ግን እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ይከወናሉ፡፡ በዚህም ሳቢያ የዘጠና ሚሊዮን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ፈሰስ ኢትዮጵያ ውስጥ ለማድረግ ታቅዷል፡፡ ይህም 1,600 የፋብሪካ ውስጥ እና 2,400 ከምርት ሽያጭ ጋር ለተገናኙ የስራ ዕድሎች መፈጠር ምክንያት እንደሚሆን ታምኖበታል፡፡ ምርቱን ተግባራዊ ለማድረግ ከተለያዩ የሃገሪቱ የምርምር እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ዶ/ር ዮናታን በውይይቱ የገለፁ ሲሆን ከመንግስት አፋጣኝ የኢንቨስትመንት ፍቃድን ከማግኘት አንስቶ የተለያዩ ድጋፎች ይደረግላቸው ዘንድ ጥያቄን አቅርበዋል፡፡
ፈርትል ክርኤቲቭ ላብስ መቀመጫውን ሚሺጋን አሜሪካን ውስጥ በማድረግ የተመሰረተና እንደ ዓለም ጤና ድርጅት ካሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በጋራ የሚሰራ ኩባንያ ሲሆን በምርምር እና ስርፀት ላይ ትኩረቱን በማድረግ ይንቀሳቀሳል፡፡ ሳና ብሎ የሰየማቸው የዝሆኔ በሽታን መከላከያ ጫማና ጓንቶቹም በአይነታቸው የመጀመሪያ ናቸው፡፡ እነዚህ ምርቶች ፀረ-ባክቴሪያ እና ውሃን የማያሳልፉ ከመሆናቸውም ባሻገር ምቹና ሌሎች ገፅታዎችንም አቅፈው የያዙ ናቸው፡፡ የምርት ሂደታቸውም በዋነኝነት በ3ዲ ማተሚያ ማሽኖች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡
ከባድ አጫሾች ዓይናቸው ሊጠፋ ይችላል
***************************************
ምንም እንኳን ማጨስ በጤናችን ላይ የሚያስከትለውን ትልቅ አደጋ የሚያመላክቱ የተለያዩ ሳይንሳዊ እውነታዎችና ማረጋገጫዎች መውጣታቸውን የቀጠሉ ቢሆንም አሁንም ሰዎች ጆሮ ዳባ በሚመስል መልኩ ማጨሳቸውን ቀጥለዋል፡፡
እስካሁን ድረስ እንኳን በተረጋገጡ ጥናቶች መሰረት ማጨስ ከሚያመጣብን ከፍተኛ የጤና ጉዳት መካከል አስም፣ የሳምባ በሽታ፣ ስትሮክ እና ካንሰር በቀዳሚነት የሚጠቀሱ በሽታዎች ናቸው፡፡ ከዚህ ባለፈ ከልብ ችግር ጋር በተገናኘ በየቀኑ አንድ ሲጋራ የሚያጨስ ሰው ለልብ በሸታ የመጋለጥ እድሉ በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ታዲያ ሰሞኑን በወጣ አንድ ጥናት በከባድ ሁኔታ ሲጋራ ማጨስ ከላይ ከተጠቀሱት በሽታዎች ባሻገር ለእውርነት እንደሚዳርግ ተገልጿል፡፡ በአሜሪካ ሩትጀርስ ዩኒቨርስቲ በተከናወነው በዚህ ጥናት ተመራማሪዎች እንደገለፁት ከሆነ በቀን ውስጥ ከ20 በላይ ሲጋራዎችን የሚጨስ ሰው የዓይን መታወር ሊደርስበት እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
ጥናቱ ላይ ከ25 እስከ 45 የሚገመቱ 71 ሰዎች በጠቅላለው የተሳፉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም ትንሽ ቁጥር ያለቸው አልፎ አልፎ የሚያጨሱና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ደግሞ ከ20 በላይ ሲጋራዎችን በየቀኑ የሚያጨሱ እና ከሱሳቸው ማየል የተነሳ አንድም ጊዜ ለማቆም የልሞከሩ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት ተመራማሪዎቹ የተሳተፊዎቹን የቀለም ልየታና የዕይታ ንፅፅር ለመረዳት እንዲያስችላቸው 19-ኢንች ከሚሆን የካቶድ ሬይ መቆጣጠሪያ 59 ኢንች ርቀው አንዲቀመጡ ካደረጉ በኋላ ስቲሙሊው (stimuli) እንዲገለፅና ሁለቱም ዓይኖቻቸው እንዲመረመሩ ተደርጓል፡፡
በወጤቱም መሰረት አጥኘዎቹ እንደገለፁት በአጫሾቹ የቀለም ልየታ ላይ ሰፊ ለውጥ ማየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይም የጥናቱ ዋና መሪ ስቴቨን ሲልቨርስቲን እንደሚናገሩት በሲጋራ ውስጥ ለፍጆታ የሚውሉት የኒዩሮቶክሲክ ኬሚካሎች የአዕምሮን የዕይታ ማመዛዘኛ ሂደት በማሰተጓጎል ወይም እንቅስቃሴውን በመቀነስ አጠቃላይ የእይታ አቅምን አንደሚያዳክም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ተመራማሪው እንደሚገልፁት ከባድ አጫሾች የዕይታ ንፅፅር አቅማቸው ሳይቀር አልፎ አልፎ ከሚያጨሱት ተሳታፊዎች አንፃር በእጅጉ እንደሚቀንስ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Explorist
***************************************
ምንም እንኳን ማጨስ በጤናችን ላይ የሚያስከትለውን ትልቅ አደጋ የሚያመላክቱ የተለያዩ ሳይንሳዊ እውነታዎችና ማረጋገጫዎች መውጣታቸውን የቀጠሉ ቢሆንም አሁንም ሰዎች ጆሮ ዳባ በሚመስል መልኩ ማጨሳቸውን ቀጥለዋል፡፡
እስካሁን ድረስ እንኳን በተረጋገጡ ጥናቶች መሰረት ማጨስ ከሚያመጣብን ከፍተኛ የጤና ጉዳት መካከል አስም፣ የሳምባ በሽታ፣ ስትሮክ እና ካንሰር በቀዳሚነት የሚጠቀሱ በሽታዎች ናቸው፡፡ ከዚህ ባለፈ ከልብ ችግር ጋር በተገናኘ በየቀኑ አንድ ሲጋራ የሚያጨስ ሰው ለልብ በሸታ የመጋለጥ እድሉ በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ታዲያ ሰሞኑን በወጣ አንድ ጥናት በከባድ ሁኔታ ሲጋራ ማጨስ ከላይ ከተጠቀሱት በሽታዎች ባሻገር ለእውርነት እንደሚዳርግ ተገልጿል፡፡ በአሜሪካ ሩትጀርስ ዩኒቨርስቲ በተከናወነው በዚህ ጥናት ተመራማሪዎች እንደገለፁት ከሆነ በቀን ውስጥ ከ20 በላይ ሲጋራዎችን የሚጨስ ሰው የዓይን መታወር ሊደርስበት እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
ጥናቱ ላይ ከ25 እስከ 45 የሚገመቱ 71 ሰዎች በጠቅላለው የተሳፉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም ትንሽ ቁጥር ያለቸው አልፎ አልፎ የሚያጨሱና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ደግሞ ከ20 በላይ ሲጋራዎችን በየቀኑ የሚያጨሱ እና ከሱሳቸው ማየል የተነሳ አንድም ጊዜ ለማቆም የልሞከሩ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት ተመራማሪዎቹ የተሳተፊዎቹን የቀለም ልየታና የዕይታ ንፅፅር ለመረዳት እንዲያስችላቸው 19-ኢንች ከሚሆን የካቶድ ሬይ መቆጣጠሪያ 59 ኢንች ርቀው አንዲቀመጡ ካደረጉ በኋላ ስቲሙሊው (stimuli) እንዲገለፅና ሁለቱም ዓይኖቻቸው እንዲመረመሩ ተደርጓል፡፡
በወጤቱም መሰረት አጥኘዎቹ እንደገለፁት በአጫሾቹ የቀለም ልየታ ላይ ሰፊ ለውጥ ማየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይም የጥናቱ ዋና መሪ ስቴቨን ሲልቨርስቲን እንደሚናገሩት በሲጋራ ውስጥ ለፍጆታ የሚውሉት የኒዩሮቶክሲክ ኬሚካሎች የአዕምሮን የዕይታ ማመዛዘኛ ሂደት በማሰተጓጎል ወይም እንቅስቃሴውን በመቀነስ አጠቃላይ የእይታ አቅምን አንደሚያዳክም ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ተመራማሪው እንደሚገልፁት ከባድ አጫሾች የዕይታ ንፅፅር አቅማቸው ሳይቀር አልፎ አልፎ ከሚያጨሱት ተሳታፊዎች አንፃር በእጅጉ እንደሚቀንስ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Explorist
የዓለማችን ግዙፉ ንብ ዳግም ተገኘ
******************************
የዓለማችን ግዙፉ ንብ በዓለም ዓቀፍ አጥኚዎች አማካኝነት ገጠራማው የኢንዶኔዚያ ክፍል ውስጥ መገኘቱ ትናንት ይፋ ተደርጓል፡፡ ሜጋቺሊ ፕሉቶ ወይም በተለምዶው አጠራሩ የዋላስ ግዙፍ ንብ ተብሎ የሚጠራው ይህ የንብ ዝርያ የአራት ሴ.ሜ ርዝማኔ ሲኖረው የክንፎቹም ስፋት እስከ 7.5 ሴ.ሜ ይለካል፡፡ ለንፅፅር ብናቀርበው እንኳን ንቡ የሰውን ልጅ አውራ ጣት በሚስተካከል መጠን ላይ ይገኛል፡፡
በፕሪንስቶን ዩኒቨርሲቴ የኤቲሞሎጂ ምሁሩ ኤሊ ዋይማን ከሁለት ሳይንቲስት እና አንድ ፎቶ አንሺ ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን ከወር በፊት ነበር የሁለት ሳምንታት አሰሳውን የጀመሩት፡፡ አሰሳውም ንቡ ከዚህ በፊት እንደታየባቸው የሚነገርባቸውን ሶስት የኢንዶኔዢያ ደሴቶች ያካለለ ነው፡፡ በመጨረሻም ለሰላሳ ስምንት ዓመታት ከዓለም ዕይታ ተሰውሮ የቆየው ይህ ንብ ባሳለፍነው ወር ሞሉካስ በተሰኘው ደሴት ላይ ነበር ተመራማሪዎቹ ያገኙት፡፡
ይህ የንብ ዝርያ ዳግም ጠፍቶ ሲገኝ የአሁኑ የመጀመሪያው አልሆነም፡፡ በቀዳሚነት በእንግሊዛዊው ናቹራሊስት አልፍሬድ ሩሴል ዋላስ አማካኝነት ከተገኘበት እ.አ.አ 1858 አንስቶ በአሜሪካዊው ኤቲሞሎጂስት አዳም ሜሰር አማካኝነት ዳግም እስከተገኙበት 1981 ድረስ በሳይንሱ ዓለም እንደጠፋ ይቆጠር ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ ባለፉት ዓመታት ውስጥ ከዓይን ከመሰወሩ ባሻገር ግሎባል ዋይልድ ላይፍ ኮንሰርቬሽን በተሰኘው ተቋም አማካኝነት 25 እጅግ ከሚፈለጉ የነፍሳት ዝርያዎች ተመድቦ ቆይቷል፡፡
ምንጭ፡ Science News
******************************
የዓለማችን ግዙፉ ንብ በዓለም ዓቀፍ አጥኚዎች አማካኝነት ገጠራማው የኢንዶኔዚያ ክፍል ውስጥ መገኘቱ ትናንት ይፋ ተደርጓል፡፡ ሜጋቺሊ ፕሉቶ ወይም በተለምዶው አጠራሩ የዋላስ ግዙፍ ንብ ተብሎ የሚጠራው ይህ የንብ ዝርያ የአራት ሴ.ሜ ርዝማኔ ሲኖረው የክንፎቹም ስፋት እስከ 7.5 ሴ.ሜ ይለካል፡፡ ለንፅፅር ብናቀርበው እንኳን ንቡ የሰውን ልጅ አውራ ጣት በሚስተካከል መጠን ላይ ይገኛል፡፡
በፕሪንስቶን ዩኒቨርሲቴ የኤቲሞሎጂ ምሁሩ ኤሊ ዋይማን ከሁለት ሳይንቲስት እና አንድ ፎቶ አንሺ ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን ከወር በፊት ነበር የሁለት ሳምንታት አሰሳውን የጀመሩት፡፡ አሰሳውም ንቡ ከዚህ በፊት እንደታየባቸው የሚነገርባቸውን ሶስት የኢንዶኔዢያ ደሴቶች ያካለለ ነው፡፡ በመጨረሻም ለሰላሳ ስምንት ዓመታት ከዓለም ዕይታ ተሰውሮ የቆየው ይህ ንብ ባሳለፍነው ወር ሞሉካስ በተሰኘው ደሴት ላይ ነበር ተመራማሪዎቹ ያገኙት፡፡
ይህ የንብ ዝርያ ዳግም ጠፍቶ ሲገኝ የአሁኑ የመጀመሪያው አልሆነም፡፡ በቀዳሚነት በእንግሊዛዊው ናቹራሊስት አልፍሬድ ሩሴል ዋላስ አማካኝነት ከተገኘበት እ.አ.አ 1858 አንስቶ በአሜሪካዊው ኤቲሞሎጂስት አዳም ሜሰር አማካኝነት ዳግም እስከተገኙበት 1981 ድረስ በሳይንሱ ዓለም እንደጠፋ ይቆጠር ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ ባለፉት ዓመታት ውስጥ ከዓይን ከመሰወሩ ባሻገር ግሎባል ዋይልድ ላይፍ ኮንሰርቬሽን በተሰኘው ተቋም አማካኝነት 25 እጅግ ከሚፈለጉ የነፍሳት ዝርያዎች ተመድቦ ቆይቷል፡፡
ምንጭ፡ Science News
ለምን እናዛጋለን? ሳይንሳዊ ብያኔ
*******************************
ሰዎች ስለማዛጋት ሲሰሙም ሆነ ሲያነቡ ቀጥታ ሊያዛጉ እንደሚችሉ በጉዳዩ ላይ ምርምር ያካሄዱ ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ በዚህም የተነሳ ምናልበትም ይህን ፅሀፍ አያነበቡ ባሉበት ወቅት ከመቅፅበት አዛግተው ሊሆን ይችላል፡፡
ለመሆኑ ግን ማዛጋት የተለየ ሳይንሳዊ ምክንያት ይኖረው ይሆን? ሰዎችስ ተኝተው ከተነሱ በኋላ አልያም አንድን ስራ ጨርሰው ወደሌላ ለማለፍ በሚጥሩበት ወቅት ማዛጋት ተደጋግሞ የሚመጣው ለምን ይሆን? ለእነዚህ እና ሌሎች መሰል ጥያቂዎች ሳይንስ የሚሰጠውን ብያኔ እንመልከት፡፡
ሰዎች ከመኝታ በኋላ ሲነቁ፣ በስራ ሲደክሙ፣ ሲደብራቸው አልያም የሆነ አዲስ ነገር ለመጀመር ሲያስቡ ማዛጋት ከመቅፅበት ሊመጣባቸው ይችላል፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን በቅርባቸው ያለ ሰው ሲያዛጋ ከተመለከቱ በደቂቃ ልዩነት ውስጥ አነሱም ሊያዛጉ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ ማዛጋት የሚባለው ነገር አንዳች ተላላፊ (contagious) ባህሪ የያዘ ነው የሚል ብያኔ አንዲኖር አድርጓል፡፡
ከዚህ ባለፈ ግን በኒዎርክ ፖሊቴክኒክ ኢኒስቲትዩት የተደረገ አንድ የሳይንቲስቶች ጥናት የማዛጋት ምክንያትን ሲያስቀምጥ የአእምሮ ማቀዝቀዣ ዘዴ ወይም (brain cooling mechanism) ነው ብሎ ይበይናል፡፡ ይህንንም ሲያብራራ ሰዎች በሚያዛጉበት ወቅት መንጋጋቸውን በሰፊው ከፍተው አየር ወደ ውስጣቸው ከሳቡ በኋላ ከመቅፅበት ወደ ውጭ የሚተነፍሱበት ሂደት አለ፡፡ ይህ ደግሞ ወደ ራስ ቅል የሚሄደውን ከፍተኛ የደም ፍሰት በማፋጠን የሴሬብራል ቅዝቃዜን ይጨምረዋል፡፡ ስለዚህም በሰውነታችን ውስጥ ያለው የሙቀት መጠን ከፍተኛ ሲሆን የድካምና የእንቅልፍ ስሜት የሚሰማን በመሆኑ ይህን ስሜት ለመገደብ ማዛጋት አይነተኛው መንገድ እንደሆነ ያስቀምጣሉ፡፡
ይህም በሌላ አገላለፅ ዶክተር ጋለፕ እንደሚሉት አዕምሯችን የማዘዣ ጣቢያ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ዝግጁ ለማድረግና ለቀጣዩም አንቅስቃሴ ሌሎቹን የሰውነት ክፍሎቻችንን ለማዘጋጀት እንዲረዳው የሚደርገው የማንቃት እና የመቀስቀስ ድርጊት ነው ብለው ይገልፁታል፡፡
ይህ ብያኔ አስካሁን ብዙዎች የሚቀበሉት ቢሆንም ለሌላ ሳይንሳዊ አመክንዮች ክፍት መሆኑን የሚናገሩት ተመራማሪዎቹ በማዛጋት ዙሪያ ሁላችንም እርግጣኛ መሆን ያለብን ግን ስለማዛጋት ተላላፊነት (contagiousness) ነው ይላሉ፡፡
ምንጭ፡ The New York Times
*******************************
ሰዎች ስለማዛጋት ሲሰሙም ሆነ ሲያነቡ ቀጥታ ሊያዛጉ እንደሚችሉ በጉዳዩ ላይ ምርምር ያካሄዱ ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ በዚህም የተነሳ ምናልበትም ይህን ፅሀፍ አያነበቡ ባሉበት ወቅት ከመቅፅበት አዛግተው ሊሆን ይችላል፡፡
ለመሆኑ ግን ማዛጋት የተለየ ሳይንሳዊ ምክንያት ይኖረው ይሆን? ሰዎችስ ተኝተው ከተነሱ በኋላ አልያም አንድን ስራ ጨርሰው ወደሌላ ለማለፍ በሚጥሩበት ወቅት ማዛጋት ተደጋግሞ የሚመጣው ለምን ይሆን? ለእነዚህ እና ሌሎች መሰል ጥያቂዎች ሳይንስ የሚሰጠውን ብያኔ እንመልከት፡፡
ሰዎች ከመኝታ በኋላ ሲነቁ፣ በስራ ሲደክሙ፣ ሲደብራቸው አልያም የሆነ አዲስ ነገር ለመጀመር ሲያስቡ ማዛጋት ከመቅፅበት ሊመጣባቸው ይችላል፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን በቅርባቸው ያለ ሰው ሲያዛጋ ከተመለከቱ በደቂቃ ልዩነት ውስጥ አነሱም ሊያዛጉ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ ማዛጋት የሚባለው ነገር አንዳች ተላላፊ (contagious) ባህሪ የያዘ ነው የሚል ብያኔ አንዲኖር አድርጓል፡፡
ከዚህ ባለፈ ግን በኒዎርክ ፖሊቴክኒክ ኢኒስቲትዩት የተደረገ አንድ የሳይንቲስቶች ጥናት የማዛጋት ምክንያትን ሲያስቀምጥ የአእምሮ ማቀዝቀዣ ዘዴ ወይም (brain cooling mechanism) ነው ብሎ ይበይናል፡፡ ይህንንም ሲያብራራ ሰዎች በሚያዛጉበት ወቅት መንጋጋቸውን በሰፊው ከፍተው አየር ወደ ውስጣቸው ከሳቡ በኋላ ከመቅፅበት ወደ ውጭ የሚተነፍሱበት ሂደት አለ፡፡ ይህ ደግሞ ወደ ራስ ቅል የሚሄደውን ከፍተኛ የደም ፍሰት በማፋጠን የሴሬብራል ቅዝቃዜን ይጨምረዋል፡፡ ስለዚህም በሰውነታችን ውስጥ ያለው የሙቀት መጠን ከፍተኛ ሲሆን የድካምና የእንቅልፍ ስሜት የሚሰማን በመሆኑ ይህን ስሜት ለመገደብ ማዛጋት አይነተኛው መንገድ እንደሆነ ያስቀምጣሉ፡፡
ይህም በሌላ አገላለፅ ዶክተር ጋለፕ እንደሚሉት አዕምሯችን የማዘዣ ጣቢያ እንደመሆኑ መጠን ራሱን ዝግጁ ለማድረግና ለቀጣዩም አንቅስቃሴ ሌሎቹን የሰውነት ክፍሎቻችንን ለማዘጋጀት እንዲረዳው የሚደርገው የማንቃት እና የመቀስቀስ ድርጊት ነው ብለው ይገልፁታል፡፡
ይህ ብያኔ አስካሁን ብዙዎች የሚቀበሉት ቢሆንም ለሌላ ሳይንሳዊ አመክንዮች ክፍት መሆኑን የሚናገሩት ተመራማሪዎቹ በማዛጋት ዙሪያ ሁላችንም እርግጣኛ መሆን ያለብን ግን ስለማዛጋት ተላላፊነት (contagiousness) ነው ይላሉ፡፡
ምንጭ፡ The New York Times
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞች የደም ልገሳ አከናወኑ
የደም ልገሳ ለተቀባዩ ህይወት፤ ለለጋሹም የህሊና ሐሴት ብሎም ሰብዓዊ ሃላፊነት ነው፡፡ ይህን የተረዱት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞችም በትናንትናው ዕለት በኢኒስቲትዩቱ ቅጥር ውስጥ የደም ልገሳን በማከናወን ሰብዓዊ ሃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡ የደም ልግሳው “ላማባዲና” በተሰኘው የተቋሙ ሰራተኞች ሶሻል ኮሚቴ አዘጋጅነት የሚካሄድ ሲሆን በየሶስት ወራት ልዩነት ይደረጋል፡፡ የተቋሙ ሰራተኞች ይህን መሰል በጎ ተግባራትን በተለያዩ ወቅቶች ከውነው አልፈዋል፡፡ በደም ልገሳ ረገድም የአሁኑን ጨምሮ ለስምንት ጊዜያት ደም የመለገስ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በበጎ ፍቃድ የሚለገስ ደም በአደጋና ሌሎች ሁናቴዎች ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ ብቸኛው የደም ምንጭ እና ህይወትን ማስቀጠያ መንገድ ነው፡፡ በዓለም ላይ በዓመት እስከ 80 ሚሊዮን ዩኒት የሚሆን ደም ከበጎ ፍቃደኞች የሚሰበሰብ ቢሆንም የደም ልገሳ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት ውስጥ በዝቅተኛ ደረጃ ይከወነል፡፡ ለአብነት እንኳን ብናይ ከሰሃራ በታች ባሉ ሃገራት ያለው የደም ፍላጎት 18 ሚሊዮን ዩኒት ቢሆንም ከዚህ ውስጥ የሚሰበሰበው 15 በመቶ ያህሉ ብቻ ነው፡፡ በኢትዮጵያም ያለው የደም ፍላጎት ከ80 እስከ 120 ሺህ ዩኒት ሲሆን በዓመት የሚሰበሰበው ግን ከ43 በመቶ አይበልጥም፡፡
ታድያ ይህን መሰል በበጎ ፍቃደኝነት ደምን የመለገስ ተግባራት በተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት፣ ማህበራት እንዲሁም ሌሎች ማህበረሰቡን በሚያስተሳስሩ አደረጃጀቶች በዘላቂነት ቢከወኑ የሚሊዮን ወገኖችን ህይወት ማዳን ይቻላል፡፡
እርስዎስ ለስንት ጊዜ ደም ለግሰዋል?
የደም ልገሳ ለተቀባዩ ህይወት፤ ለለጋሹም የህሊና ሐሴት ብሎም ሰብዓዊ ሃላፊነት ነው፡፡ ይህን የተረዱት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ሰራተኞችም በትናንትናው ዕለት በኢኒስቲትዩቱ ቅጥር ውስጥ የደም ልገሳን በማከናወን ሰብዓዊ ሃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡ የደም ልግሳው “ላማባዲና” በተሰኘው የተቋሙ ሰራተኞች ሶሻል ኮሚቴ አዘጋጅነት የሚካሄድ ሲሆን በየሶስት ወራት ልዩነት ይደረጋል፡፡ የተቋሙ ሰራተኞች ይህን መሰል በጎ ተግባራትን በተለያዩ ወቅቶች ከውነው አልፈዋል፡፡ በደም ልገሳ ረገድም የአሁኑን ጨምሮ ለስምንት ጊዜያት ደም የመለገስ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል፡፡
በበጎ ፍቃድ የሚለገስ ደም በአደጋና ሌሎች ሁናቴዎች ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ሁሉ ብቸኛው የደም ምንጭ እና ህይወትን ማስቀጠያ መንገድ ነው፡፡ በዓለም ላይ በዓመት እስከ 80 ሚሊዮን ዩኒት የሚሆን ደም ከበጎ ፍቃደኞች የሚሰበሰብ ቢሆንም የደም ልገሳ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት ውስጥ በዝቅተኛ ደረጃ ይከወነል፡፡ ለአብነት እንኳን ብናይ ከሰሃራ በታች ባሉ ሃገራት ያለው የደም ፍላጎት 18 ሚሊዮን ዩኒት ቢሆንም ከዚህ ውስጥ የሚሰበሰበው 15 በመቶ ያህሉ ብቻ ነው፡፡ በኢትዮጵያም ያለው የደም ፍላጎት ከ80 እስከ 120 ሺህ ዩኒት ሲሆን በዓመት የሚሰበሰበው ግን ከ43 በመቶ አይበልጥም፡፡
ታድያ ይህን መሰል በበጎ ፍቃደኝነት ደምን የመለገስ ተግባራት በተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት፣ ማህበራት እንዲሁም ሌሎች ማህበረሰቡን በሚያስተሳስሩ አደረጃጀቶች በዘላቂነት ቢከወኑ የሚሊዮን ወገኖችን ህይወት ማዳን ይቻላል፡፡
እርስዎስ ለስንት ጊዜ ደም ለግሰዋል?
የልብ በሽታ ከመከሰቱ ጥቂት ወራት በፊት ሰውነታችን የሚያሳየን 5 ምልክቶች
*******************************************
በዓለማችን ከ30 በመቶ በላይ ለሚሆነው የሰዎች ሞት የልብ በሽታ ዋነኛው መንስኤ ነው፡፡ ከዚህ የልብ በሽታ መንስኤ ውስጥ ደግሞ አብዛኛውን ሰው ለሞት የሚዳርገው ventricular fibrillation የተባለው የልብ ችግር ሲሆን ይህም ተጠቂው በበሽታው መያዙን ሳያውቅ ህይወቱን የሚያጣበት ሁኔታ ሲፈጠር ነው፡፡ ይህ በሽታ ምንም አንኳን ምልክቶቹን አይተን ጥሩ ህክምና የምናገኝበት ሁኔታ ሲፈጠር ከ90 በመቶ በላይ የመዳን እድል ቢሰጠንም ብዙ ሰዎች ግን ምልክቶቹን ባለማወቃቸው ምክንያት የህክምና እርዳታ ሳያገኙ ህይወታቸውን እንዲያጡ ይሆናል፡፡ በመሆኑም የልብ በሽታ ከመከሰቱ ጥቂት ወራት በፊት ሰውነታችን የሚሳየንን የማስጠንቀቂያ ምልክት ችላ ሳንል ተገቢውን የህክመና ሂደት መጀመር ያስፈልጋል፡፡
እጅግ በጣም ከፍተኛ የድካም ስሜት
ለቀናት፣ ለሳምንታትና ለወራት የቆየ ከፍተኛ የድካም ስሜት የሚሰማን ከሆነ የልብ በሽታ ሊከሰት መሆኑን የሚያሳየን የመጀመሪያው መንገድ ነው፡፡ ይህ የድካም ስሜት ምናልባት ከእንቅልፍ ማጣትና ከሌሎች በሽታዎች ጋር የተያያዘ የድካም ስሜት ሳይሆን ለብዙ ጊዜያት የሚቆይ እና በመጠኑም እጅግ በጣም ከፍተኛ ሊባል የሚችል የድካም ስሜት በመሆኑ በጥንቃቄ ማየት ያስፈልጋል፡፡
የትንፋሽ ማጠር
አንዳንድ ጊዜ ቀላል ሊባል የማይችል የአተነፋፈስ ችግር ሲያጋጥም ከሳምባ ጋር ማገናኘት የተለመደ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከልብ ጋር ተያይዞ በሚዘዋወረው ደማችን ውስጥ ያለው የኦክስጅን ማነስ ለትንፋሽ መቆራረጥና ማጠር ምክንያት ሊሆን ስለሚችል በጥንቃቄ ማየት ይበጃል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በአንድ ጥናት እንደተገለፀው በልብ በሽታ ከሚያዙ ሰዎች መካከል 40 በመቶ የሚሆኑት እስከ ስድስት ወር የሚዘልቅ የትንፋሽ ማጠር እንደሚታባቸው አስቀምጧል፡፡
ከፍተኛ መጠን ያለው ላብ እና የደረት ህመም
አብዛኛውን ጊዜ ሞቃታማ አየር ሲኖርና አድካሚ ስራ ስንሰራ ጤናማ የሆነ ላብ ሊያልበን ይችላል፡፡ ነገር ግን ምንም አይነት የሚያደክም ስራ ሳንሰራ ባልተለመደ ሁኔታ በደረታችን፣ በእጃችን፣ በአንገታችን እና በመንጋጋችን ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው ላብ ካየን እና በተለይም በደረታችን ላይ የህመም ስሜትና ምቾት ያለመሰማት ነገር ከተመለከትን የልብ በሽታ ምልክት ሊሆን ይችላልና የህክምና ሂደት መጀመሩ ጥሩ ነው፡፡
የእንቅልፍ ማጣት፣ ድብርትና የፀጉር መመለጥ
ከጭንቀትና ድብርት በመነጨ የሚመጣ የእንቅልፍ ማጣት በተለያየ መልኩ የኦክስጅን መጠንን በማውረድ ለልብ በሽታ የመጋለጥ እድልን እንደሚጨምር በተደጋገሚ የተሰራ ጥናት ያሳየል፡፡ ከዚህ ባለፈ የፀጉር መመለጥ በግልፅ የሚታይ በልብ በሽታ የመጋለጥ ምልክት ሲሆን በተለይም 50 ዓመት በሞላቸው ወንዶች ላይ እና አንዳንድ ሴቶች ላይ በግልፅ የመታየት እድሉ ሰፊ ነው፡፡
ያልተለመደ የልብ ምት
ብዙውን ጊዜ ለአንድና ለሁለት ደቂቃ የሚቆይ ያልተለመደ የልብ ምት ለመፍዘዝ እና ለድካም የሚዳርግ ሲሆን ፍጥነቱን ሳይቀንስ የሚቀጥልበት ሁኔታ ደግሞ በአጠቃላይ ላልተስተካከለ የልብ ምት (arrhythmia) እና ለከፍተኛ የልብ ምት (tachycardia) ይዳርጋል፡፡ በመሆኑም እነዚህን ምልክቶች ስንመለከት አዘውትረን የምናከናውነውን የአኗኗር ዘይቤ ከመፈተሽ ባለፈ የሃኪም ምርመራ የምናደርግበትን ሁኔታ መጀመር እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ምንጭ፡ My Science Academy እና Bright Side
*******************************************
በዓለማችን ከ30 በመቶ በላይ ለሚሆነው የሰዎች ሞት የልብ በሽታ ዋነኛው መንስኤ ነው፡፡ ከዚህ የልብ በሽታ መንስኤ ውስጥ ደግሞ አብዛኛውን ሰው ለሞት የሚዳርገው ventricular fibrillation የተባለው የልብ ችግር ሲሆን ይህም ተጠቂው በበሽታው መያዙን ሳያውቅ ህይወቱን የሚያጣበት ሁኔታ ሲፈጠር ነው፡፡ ይህ በሽታ ምንም አንኳን ምልክቶቹን አይተን ጥሩ ህክምና የምናገኝበት ሁኔታ ሲፈጠር ከ90 በመቶ በላይ የመዳን እድል ቢሰጠንም ብዙ ሰዎች ግን ምልክቶቹን ባለማወቃቸው ምክንያት የህክምና እርዳታ ሳያገኙ ህይወታቸውን እንዲያጡ ይሆናል፡፡ በመሆኑም የልብ በሽታ ከመከሰቱ ጥቂት ወራት በፊት ሰውነታችን የሚሳየንን የማስጠንቀቂያ ምልክት ችላ ሳንል ተገቢውን የህክመና ሂደት መጀመር ያስፈልጋል፡፡
እጅግ በጣም ከፍተኛ የድካም ስሜት
ለቀናት፣ ለሳምንታትና ለወራት የቆየ ከፍተኛ የድካም ስሜት የሚሰማን ከሆነ የልብ በሽታ ሊከሰት መሆኑን የሚያሳየን የመጀመሪያው መንገድ ነው፡፡ ይህ የድካም ስሜት ምናልባት ከእንቅልፍ ማጣትና ከሌሎች በሽታዎች ጋር የተያያዘ የድካም ስሜት ሳይሆን ለብዙ ጊዜያት የሚቆይ እና በመጠኑም እጅግ በጣም ከፍተኛ ሊባል የሚችል የድካም ስሜት በመሆኑ በጥንቃቄ ማየት ያስፈልጋል፡፡
የትንፋሽ ማጠር
አንዳንድ ጊዜ ቀላል ሊባል የማይችል የአተነፋፈስ ችግር ሲያጋጥም ከሳምባ ጋር ማገናኘት የተለመደ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከልብ ጋር ተያይዞ በሚዘዋወረው ደማችን ውስጥ ያለው የኦክስጅን ማነስ ለትንፋሽ መቆራረጥና ማጠር ምክንያት ሊሆን ስለሚችል በጥንቃቄ ማየት ይበጃል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በአንድ ጥናት እንደተገለፀው በልብ በሽታ ከሚያዙ ሰዎች መካከል 40 በመቶ የሚሆኑት እስከ ስድስት ወር የሚዘልቅ የትንፋሽ ማጠር እንደሚታባቸው አስቀምጧል፡፡
ከፍተኛ መጠን ያለው ላብ እና የደረት ህመም
አብዛኛውን ጊዜ ሞቃታማ አየር ሲኖርና አድካሚ ስራ ስንሰራ ጤናማ የሆነ ላብ ሊያልበን ይችላል፡፡ ነገር ግን ምንም አይነት የሚያደክም ስራ ሳንሰራ ባልተለመደ ሁኔታ በደረታችን፣ በእጃችን፣ በአንገታችን እና በመንጋጋችን ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው ላብ ካየን እና በተለይም በደረታችን ላይ የህመም ስሜትና ምቾት ያለመሰማት ነገር ከተመለከትን የልብ በሽታ ምልክት ሊሆን ይችላልና የህክምና ሂደት መጀመሩ ጥሩ ነው፡፡
የእንቅልፍ ማጣት፣ ድብርትና የፀጉር መመለጥ
ከጭንቀትና ድብርት በመነጨ የሚመጣ የእንቅልፍ ማጣት በተለያየ መልኩ የኦክስጅን መጠንን በማውረድ ለልብ በሽታ የመጋለጥ እድልን እንደሚጨምር በተደጋገሚ የተሰራ ጥናት ያሳየል፡፡ ከዚህ ባለፈ የፀጉር መመለጥ በግልፅ የሚታይ በልብ በሽታ የመጋለጥ ምልክት ሲሆን በተለይም 50 ዓመት በሞላቸው ወንዶች ላይ እና አንዳንድ ሴቶች ላይ በግልፅ የመታየት እድሉ ሰፊ ነው፡፡
ያልተለመደ የልብ ምት
ብዙውን ጊዜ ለአንድና ለሁለት ደቂቃ የሚቆይ ያልተለመደ የልብ ምት ለመፍዘዝ እና ለድካም የሚዳርግ ሲሆን ፍጥነቱን ሳይቀንስ የሚቀጥልበት ሁኔታ ደግሞ በአጠቃላይ ላልተስተካከለ የልብ ምት (arrhythmia) እና ለከፍተኛ የልብ ምት (tachycardia) ይዳርጋል፡፡ በመሆኑም እነዚህን ምልክቶች ስንመለከት አዘውትረን የምናከናውነውን የአኗኗር ዘይቤ ከመፈተሽ ባለፈ የሃኪም ምርመራ የምናደርግበትን ሁኔታ መጀመር እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ምንጭ፡ My Science Academy እና Bright Side
ተመራማሪዎች የብሬል ላፕቶፕ ሰሩ
*************************
በህንድ ደልሂ መቀመጫውን ባረገው የህንድ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት የሚገኙ ተመራማሪዎች ለአይነ ስውራን የሚሆን የብሬል ላፕቶፕ መስራታቸውን አስታውቀዋል። ረዘም ያለ ጊዜ በወሰደው በዚህ አዲስ ፈጠራ ተመራማሪዎቹ እንደገለፁት ከሆነ የተሰራው የብሬል ላፕቶፕ መሰረታዊ የሆኑትን የኢሜል እና የዌብ ብሮውዘር አገልግሎቶች ከመስጠት ባለፈ የሶስተኛ ወገን መተግበሪያዎች ሊጫኑበት እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
DotBook የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ የብሬል ላፕቶፕ ሁለት አይነት መልክ ኖሮት የተሰራ ሲሆን እነሱም 40Q እና 20P የሚል ስያሜ ተሰቷቸዋል፡፡ 40Q የተባለው የብሬል ላፕቶፕ አርባ ፊደሎችን ወይም (characters) በየመስመሩ የያዘ የብሬል ኪቦርድ ሲሆን 20P የተሰኘው ደግሞ ሃያ ፊደሎችን በየመስመሩ የሚይዝ ነው፡፡
እስካሁን ዋጋቸው እጅግ ውድ የሆኑ 40 የሚደርሱ የብሬል መሳሪያዎች መሰራታቸውን የገለፁት ተመራማሪዎቹ ይህ ችግርም አዲሱን የብሬል ላፕቶፕ ለመስራት እንዳነሳሳቸው ገልፀዋል፡፡ ላፕቶፑ ከህንድ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በተጨማሪ ኖኢዳ እና ክሪቲካል ሶሊዩሽን ከተባሉ የግል ድርጅቶች ጋር በትብብር የተሰራ ሲሆን በመጋቢት ወር መጨረሻም ለተጠቃሚዎች እንደሚቀርብ ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡ Tech Explorist
*************************
በህንድ ደልሂ መቀመጫውን ባረገው የህንድ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት የሚገኙ ተመራማሪዎች ለአይነ ስውራን የሚሆን የብሬል ላፕቶፕ መስራታቸውን አስታውቀዋል። ረዘም ያለ ጊዜ በወሰደው በዚህ አዲስ ፈጠራ ተመራማሪዎቹ እንደገለፁት ከሆነ የተሰራው የብሬል ላፕቶፕ መሰረታዊ የሆኑትን የኢሜል እና የዌብ ብሮውዘር አገልግሎቶች ከመስጠት ባለፈ የሶስተኛ ወገን መተግበሪያዎች ሊጫኑበት እንደሚችል ገልፀዋል፡፡
DotBook የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ የብሬል ላፕቶፕ ሁለት አይነት መልክ ኖሮት የተሰራ ሲሆን እነሱም 40Q እና 20P የሚል ስያሜ ተሰቷቸዋል፡፡ 40Q የተባለው የብሬል ላፕቶፕ አርባ ፊደሎችን ወይም (characters) በየመስመሩ የያዘ የብሬል ኪቦርድ ሲሆን 20P የተሰኘው ደግሞ ሃያ ፊደሎችን በየመስመሩ የሚይዝ ነው፡፡
እስካሁን ዋጋቸው እጅግ ውድ የሆኑ 40 የሚደርሱ የብሬል መሳሪያዎች መሰራታቸውን የገለፁት ተመራማሪዎቹ ይህ ችግርም አዲሱን የብሬል ላፕቶፕ ለመስራት እንዳነሳሳቸው ገልፀዋል፡፡ ላፕቶፑ ከህንድ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት በተጨማሪ ኖኢዳ እና ክሪቲካል ሶሊዩሽን ከተባሉ የግል ድርጅቶች ጋር በትብብር የተሰራ ሲሆን በመጋቢት ወር መጨረሻም ለተጠቃሚዎች እንደሚቀርብ ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡ Tech Explorist
ዓለምን የለወጡ ሴት ሳይንቲስቶች
************************
ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶች ቀን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ይህ በዓል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ እና ሊኖራቸው የሚገባውን የውሳኔ አቅም ለማጉላት ከመዋሉም ባለፈ በመላው ዓለም የሚገኙ ሴቶች ስለመብታቸው እንዲያውቁና እንዲያሳውቁም ትልቅ በር ይከፍታል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ዓለማችንን በመለወጥ በኩል እና ሴትነት በራሱ ይዞት የሚመጣውን ጫና ተቋቁመው ልይነት መፍጠር የቻሉ ብዙ ሴቶች ያሉ ሲሆን ከዚህ በታች የምትመለከቷቸውም ይህን ጀበድ የፈፀሙና ለመጪዎቹም መንገድ የጠረጉ ናቸው፡፡
1. ቫላንታይን ትረሽኮቫ
በህዋ ጥናት እና ምርምር እ.አ.አ በ1963 የሩሲያ “ቮስቶክ” የተባለች መንኮራኩርን ይዛ ወደ ህዋ በመብረር ያረፈች የመጀመሪያዋ ሴት ስነህዋ ተመራማሪ ለመሆን የበቃች ሲሆን ለዚህም ተግባር የወሰደባት ጊዜ ሶስት ቀናቶች ብቻ ነበሩ። የሷን ፈለግ በመከተል ከ20 አመት በሆላ ሴሊ ራይድ ወደ ህዋ በመጎዝ በአለም ሁለተኛዋ እና በአሜሪካ የመጀመሪያዎ ሴት የስነ-ህዋ ሳይንስ ተመራማሪ ለመሆን ችላለች።
2. ሜሪ ኩሪ
እ.አ.አ በ1903 “በራዴሽን” ዙሪያ ባደረገችው ጥናት እና ምርምር የመጀመሪያዋ ሴት የኖቭል ፕራይዝ ተሸላሚ ለመሆን ስትበቃ ፤ እ.አ.አ በ1911 በኬሚስትሪ ዘርፍ ባደረገችው ጥናት እና ምርምር “ራዲየም” እና “ፖሎኒየም” የተባሉ ሁለት ንጥረ-ነገሮችን በማግኘት የመጀመሪያዋ ሴት ባለሁለት ኖቭል ፕራይዝ ተሸላሚ ለመሆን በቅታለች። በሁለት የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሁለት የኖቭል ሽልማቶችን በማሸነፍ በአለማችን የመጀመሪያዋ ለመሆን ችላለች።
3. ኢኒጂነር ዳና አሊሪያ
እ.አ.አ 1961 የመጀመሪያዋ ሴት የናሳ ኢኒጂነር ዳና አሊሪያ ትምህርቷን የተከታተለችው በኮምፒውተር ሳይንስ ኢኒጂነሪንግ ነው። ስራዋን የጀመረችው በካርኒፎርኒያ “ጄት ፕሮፑሊሽን ላብራቶሪ” ቢሆንም በሆላላይ ግን የመጀመሪያዋ ሴት የናሳ ኢኒጂነር ለመሆን በቅታለች። ዳና አሊሪያ በናሳ ቆይታዋ የጠፈር ተመራማሪዎች ከጠፈር ወደ ምድር መረጃዎችን እና መልእክቶችን የሚያስተላልፉበት በየነ-መረብ ለመዘርጋት በቅታለች። በዚህም ስራዋ በአሜሪካን የወታደሮች ጥናት እና ምርምር ላብራቶሪ ውስጥ የመጀመሪያዋ ሴት ስራ አስኪያጅ ሆናለች።
4. አሚሊያ ኢርህርት
እንደ እ.አ.አ ከ1930 በፊት አንድ ሰው ለብቻው የአትላንቲክ ውቅያኖስን በኢሊኮፍተር ለማቋረጥ ብዙ ሙከራዎች ተደርገው ነበር። ነገር ግን ይህን ማሳካት የቻለው አንድ ሰው ብቻ ነው ። እንደ እ.አ.አ በ1932 አሚሊያ ኢርህርት የአትላንቲክ ውቅያኖስን በማቋረጥ በአለማችን ሁለተኛዋ እና የመጀመሪያዋ ሴት ለመሆን በቅታለች። ይሄንን ጉዞ ለማጠናቀቅ የፈጀባት 15 ሰዓት ብቻ ሲሆን ሰአቱም በወቅቱ ሪከርድ ሆኖ ተይዟል። እ.አ.አ በ1937 አለምን ለመዞር ባደረገችው በረራ ሙከራ እስካሁንም የደረሰችበት ሳይታወቅ ልትጠፋ ችላለች። እንደ እ.አ.አ በ1953 ጃኬሊን ኮችራን የሷን ፈለግ በመከተል የንፋስ እንቅፋችነትን በመቀነስ የጄት ፍጥነትን ከአስራአንድ አመት በኃላ በእጥፍ መጨመር ችላለች።
ምንጭ፡ ቴክ ሳይንስ
************************
ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶች ቀን በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ይህ በዓል የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ እና ሊኖራቸው የሚገባውን የውሳኔ አቅም ለማጉላት ከመዋሉም ባለፈ በመላው ዓለም የሚገኙ ሴቶች ስለመብታቸው እንዲያውቁና እንዲያሳውቁም ትልቅ በር ይከፍታል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ዓለማችንን በመለወጥ በኩል እና ሴትነት በራሱ ይዞት የሚመጣውን ጫና ተቋቁመው ልይነት መፍጠር የቻሉ ብዙ ሴቶች ያሉ ሲሆን ከዚህ በታች የምትመለከቷቸውም ይህን ጀበድ የፈፀሙና ለመጪዎቹም መንገድ የጠረጉ ናቸው፡፡
1. ቫላንታይን ትረሽኮቫ
በህዋ ጥናት እና ምርምር እ.አ.አ በ1963 የሩሲያ “ቮስቶክ” የተባለች መንኮራኩርን ይዛ ወደ ህዋ በመብረር ያረፈች የመጀመሪያዋ ሴት ስነህዋ ተመራማሪ ለመሆን የበቃች ሲሆን ለዚህም ተግባር የወሰደባት ጊዜ ሶስት ቀናቶች ብቻ ነበሩ። የሷን ፈለግ በመከተል ከ20 አመት በሆላ ሴሊ ራይድ ወደ ህዋ በመጎዝ በአለም ሁለተኛዋ እና በአሜሪካ የመጀመሪያዎ ሴት የስነ-ህዋ ሳይንስ ተመራማሪ ለመሆን ችላለች።
2. ሜሪ ኩሪ
እ.አ.አ በ1903 “በራዴሽን” ዙሪያ ባደረገችው ጥናት እና ምርምር የመጀመሪያዋ ሴት የኖቭል ፕራይዝ ተሸላሚ ለመሆን ስትበቃ ፤ እ.አ.አ በ1911 በኬሚስትሪ ዘርፍ ባደረገችው ጥናት እና ምርምር “ራዲየም” እና “ፖሎኒየም” የተባሉ ሁለት ንጥረ-ነገሮችን በማግኘት የመጀመሪያዋ ሴት ባለሁለት ኖቭል ፕራይዝ ተሸላሚ ለመሆን በቅታለች። በሁለት የተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ሁለት የኖቭል ሽልማቶችን በማሸነፍ በአለማችን የመጀመሪያዋ ለመሆን ችላለች።
3. ኢኒጂነር ዳና አሊሪያ
እ.አ.አ 1961 የመጀመሪያዋ ሴት የናሳ ኢኒጂነር ዳና አሊሪያ ትምህርቷን የተከታተለችው በኮምፒውተር ሳይንስ ኢኒጂነሪንግ ነው። ስራዋን የጀመረችው በካርኒፎርኒያ “ጄት ፕሮፑሊሽን ላብራቶሪ” ቢሆንም በሆላላይ ግን የመጀመሪያዋ ሴት የናሳ ኢኒጂነር ለመሆን በቅታለች። ዳና አሊሪያ በናሳ ቆይታዋ የጠፈር ተመራማሪዎች ከጠፈር ወደ ምድር መረጃዎችን እና መልእክቶችን የሚያስተላልፉበት በየነ-መረብ ለመዘርጋት በቅታለች። በዚህም ስራዋ በአሜሪካን የወታደሮች ጥናት እና ምርምር ላብራቶሪ ውስጥ የመጀመሪያዋ ሴት ስራ አስኪያጅ ሆናለች።
4. አሚሊያ ኢርህርት
እንደ እ.አ.አ ከ1930 በፊት አንድ ሰው ለብቻው የአትላንቲክ ውቅያኖስን በኢሊኮፍተር ለማቋረጥ ብዙ ሙከራዎች ተደርገው ነበር። ነገር ግን ይህን ማሳካት የቻለው አንድ ሰው ብቻ ነው ። እንደ እ.አ.አ በ1932 አሚሊያ ኢርህርት የአትላንቲክ ውቅያኖስን በማቋረጥ በአለማችን ሁለተኛዋ እና የመጀመሪያዋ ሴት ለመሆን በቅታለች። ይሄንን ጉዞ ለማጠናቀቅ የፈጀባት 15 ሰዓት ብቻ ሲሆን ሰአቱም በወቅቱ ሪከርድ ሆኖ ተይዟል። እ.አ.አ በ1937 አለምን ለመዞር ባደረገችው በረራ ሙከራ እስካሁንም የደረሰችበት ሳይታወቅ ልትጠፋ ችላለች። እንደ እ.አ.አ በ1953 ጃኬሊን ኮችራን የሷን ፈለግ በመከተል የንፋስ እንቅፋችነትን በመቀነስ የጄት ፍጥነትን ከአስራአንድ አመት በኃላ በእጥፍ መጨመር ችላለች።
ምንጭ፡ ቴክ ሳይንስ
ጊዜው ለምን ይሮጣል?
*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*
በምድራችን የሚገኙ ለፍፁምነት የቀረቡ ሰዓቶች በሶስት መቶ ዓመታት ውስጥ አንድ ሴኮንድን ብቻ የሚያጎሉ የጊዜ መለኪያዎች ናቸው፡፡ ሆኖም አዕምሮዓችን እነዚህን ውስን የጊዜ ልኬቶች ወስዶ የራሱን ዕይታ ያክልባቸዋል፡፡ ታድያ ለምን አዕምሮዓችን በትክክለኛው የጊዜ ልኬት መሰረት አይሄድም?፤ በደስታችን ወቅት ሰዓቱ ለምን ይሮጣል፤ በድብርትስ ለምን ይንቀራፈፋል?
አዕምሮ ሰዓትን የሚወስደው ግምቶቹን ተንተርሶ ነው፡፡ አዕምሮ ነገሮች ከመከሰታቸው አስቀድሞ ምን ሊመስሉ እንደሚችሉ የራሱን ግምት ይወስዳል፡፡ እያንዳንዱ ሃሳብ የራሱ የሆኑ ጥጎች (Horizons) አሉት፡፡ ለምሳሌ አንድን መፅሃፍ በምናነብበት ወቅት የሃሳብ ጥጋችን የመፅሃፉ ሽፋን፣ ቃላት፣ ቀጣዩ ዓረፍተ ነገር ወዘተ…. መቋጫ ላይ ይሆናል፡፡ ጊዜው የሚሄድልንም ለእነዚህ መቋጫዎች ባስቀመጥነው ግምት ላይ ተመስርቶ ነው፡፡ አንድን ነገር ለመገንዘብ በምንጥርበት ሰዓት አዕምሮዓችን ሰፊ ምስል በመስራት የቅርብ እና የሩቅ መቋጫዎችን ያስቀምጣል፡፡ በድብርት ሰዓታት ውስጥ የቅርቡን መቋጫ ማማተር እንጀምራለን፡፡ ለምሳሌ ከታሪኩ ይልቅ የአረፍተ ነገሩ ፍፃሜ ላይ፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ መቋጫዎቹ አንድ ላይ ሳይጣመሩ ሲቀሩ ሰዓቱም መጓተት ይጀምራል፡፡ ለዚህ አዕምሮአዊ የጊዜ አመለካከት ተጠያቂ የሆነ የአዕምሮአችን አካል ባይኖርም ስለ አንድ ጉዳይ ማሰብ እና ማሰላሰል ከተጀመረ ግን ይህ የጊዜ እይታ ሊከሰት ይችላል፡፡
አዕምሮአችን በጊዜ ላይ ያለው ግንዛቤ በዚህ መልኩ ለምን እንደሆነ ግልፅ ማብራሪያ መስጠት ባይቻልም ዝግመተ ለውጥ አመጣሽ ሊሆን እንደሚችል ግን በቻምፓላሞድ ፋውንዴሽን የኒሮን ተመራማሪ የሆኑት ጆ ፓቶን ያስረዳሉ፡፡ ጨምረውም ህይወት ብቆይ ወይስ ብሄድ ይሻለኛል መሰል ውሳኔዎችን በተከታታይ የምንሰጥባት እንደሆነችና ይህ ውስጣዊ የጊዜ እይታ በአንድ ቦታ ላይ እስከመቼ መቆየት እንዳለብን እንድንወስን እንደሚያደርገን ይናገራሉ፡፡ ሆኖም ነገሮችን የመረመርን እንደሆነ ሁናቴዎችን አስቀድሞ መገመት አዕምሮአችን ለማስታወስ እንደሚጠቅሙት እንረዳለን፡፡
አዳዲስ ትውስታዎችን የሚያስቀምጡት ኔሮኖች ትስስር እውነታን ከሚያስቀምጡት አንፃር ጥቅጥቅ ያሉ ናቸው፡፡ እነዚህ ጥቅጥቅ ትስስሮች ትውስታውን እንዲቆይ ያደርጉታል፡፡ ለምሳሌ ረዘም ላለ ሰዓት የአውሮፕላን በረራ የምናከናውን ከሆነና ረዘም ያሉ በረራዎችን በተደጋጋሚ ማከናወን ከለመድን አሁን የምናደርገውን በረራ አዕምሮአችን ብዙ ትውስታዎችን ባለማስቀመጡ ሳቢያ በረራውን አጠር ባለ ቆይታ ያጠናቀቅን ሊመስለን ይችላል፡፡
የሆነው ሆኖ ወደ እርጅና በቀረብን ቁጥር የጊዜ ፍጥነት እየጨመረብን ይመጣል፡፡ ሁሉም ነገር ልብ ወለድ የሚመስልባቸው የልጅነት ጊዜያት አዕምሮአችን ጥቅጥቅ ትስስሮችን ስለሚፈጥር ብዝሃውን ለማስታወስ ይቻለናል፡፡ ባደግን ቁጥር ግን ነገሮችን የማስታወስ ችሎታችን እየመነመነ በወጣትነት አሊያም ተከትለውት በሚመጡት ዘመናት ምን እየሰራን እንዳሳለፍን ግራ እስከሚገባን ድረስ ልንረሳቸው እንችላለን፡፡
ምንጭ፡ Live Science
*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*-*
በምድራችን የሚገኙ ለፍፁምነት የቀረቡ ሰዓቶች በሶስት መቶ ዓመታት ውስጥ አንድ ሴኮንድን ብቻ የሚያጎሉ የጊዜ መለኪያዎች ናቸው፡፡ ሆኖም አዕምሮዓችን እነዚህን ውስን የጊዜ ልኬቶች ወስዶ የራሱን ዕይታ ያክልባቸዋል፡፡ ታድያ ለምን አዕምሮዓችን በትክክለኛው የጊዜ ልኬት መሰረት አይሄድም?፤ በደስታችን ወቅት ሰዓቱ ለምን ይሮጣል፤ በድብርትስ ለምን ይንቀራፈፋል?
አዕምሮ ሰዓትን የሚወስደው ግምቶቹን ተንተርሶ ነው፡፡ አዕምሮ ነገሮች ከመከሰታቸው አስቀድሞ ምን ሊመስሉ እንደሚችሉ የራሱን ግምት ይወስዳል፡፡ እያንዳንዱ ሃሳብ የራሱ የሆኑ ጥጎች (Horizons) አሉት፡፡ ለምሳሌ አንድን መፅሃፍ በምናነብበት ወቅት የሃሳብ ጥጋችን የመፅሃፉ ሽፋን፣ ቃላት፣ ቀጣዩ ዓረፍተ ነገር ወዘተ…. መቋጫ ላይ ይሆናል፡፡ ጊዜው የሚሄድልንም ለእነዚህ መቋጫዎች ባስቀመጥነው ግምት ላይ ተመስርቶ ነው፡፡ አንድን ነገር ለመገንዘብ በምንጥርበት ሰዓት አዕምሮዓችን ሰፊ ምስል በመስራት የቅርብ እና የሩቅ መቋጫዎችን ያስቀምጣል፡፡ በድብርት ሰዓታት ውስጥ የቅርቡን መቋጫ ማማተር እንጀምራለን፡፡ ለምሳሌ ከታሪኩ ይልቅ የአረፍተ ነገሩ ፍፃሜ ላይ፡፡ በዚህ ሁኔታ ውስጥ መቋጫዎቹ አንድ ላይ ሳይጣመሩ ሲቀሩ ሰዓቱም መጓተት ይጀምራል፡፡ ለዚህ አዕምሮአዊ የጊዜ አመለካከት ተጠያቂ የሆነ የአዕምሮአችን አካል ባይኖርም ስለ አንድ ጉዳይ ማሰብ እና ማሰላሰል ከተጀመረ ግን ይህ የጊዜ እይታ ሊከሰት ይችላል፡፡
አዕምሮአችን በጊዜ ላይ ያለው ግንዛቤ በዚህ መልኩ ለምን እንደሆነ ግልፅ ማብራሪያ መስጠት ባይቻልም ዝግመተ ለውጥ አመጣሽ ሊሆን እንደሚችል ግን በቻምፓላሞድ ፋውንዴሽን የኒሮን ተመራማሪ የሆኑት ጆ ፓቶን ያስረዳሉ፡፡ ጨምረውም ህይወት ብቆይ ወይስ ብሄድ ይሻለኛል መሰል ውሳኔዎችን በተከታታይ የምንሰጥባት እንደሆነችና ይህ ውስጣዊ የጊዜ እይታ በአንድ ቦታ ላይ እስከመቼ መቆየት እንዳለብን እንድንወስን እንደሚያደርገን ይናገራሉ፡፡ ሆኖም ነገሮችን የመረመርን እንደሆነ ሁናቴዎችን አስቀድሞ መገመት አዕምሮአችን ለማስታወስ እንደሚጠቅሙት እንረዳለን፡፡
አዳዲስ ትውስታዎችን የሚያስቀምጡት ኔሮኖች ትስስር እውነታን ከሚያስቀምጡት አንፃር ጥቅጥቅ ያሉ ናቸው፡፡ እነዚህ ጥቅጥቅ ትስስሮች ትውስታውን እንዲቆይ ያደርጉታል፡፡ ለምሳሌ ረዘም ላለ ሰዓት የአውሮፕላን በረራ የምናከናውን ከሆነና ረዘም ያሉ በረራዎችን በተደጋጋሚ ማከናወን ከለመድን አሁን የምናደርገውን በረራ አዕምሮአችን ብዙ ትውስታዎችን ባለማስቀመጡ ሳቢያ በረራውን አጠር ባለ ቆይታ ያጠናቀቅን ሊመስለን ይችላል፡፡
የሆነው ሆኖ ወደ እርጅና በቀረብን ቁጥር የጊዜ ፍጥነት እየጨመረብን ይመጣል፡፡ ሁሉም ነገር ልብ ወለድ የሚመስልባቸው የልጅነት ጊዜያት አዕምሮአችን ጥቅጥቅ ትስስሮችን ስለሚፈጥር ብዝሃውን ለማስታወስ ይቻለናል፡፡ ባደግን ቁጥር ግን ነገሮችን የማስታወስ ችሎታችን እየመነመነ በወጣትነት አሊያም ተከትለውት በሚመጡት ዘመናት ምን እየሰራን እንዳሳለፍን ግራ እስከሚገባን ድረስ ልንረሳቸው እንችላለን፡፡
ምንጭ፡ Live Science