ኤሌክትሪክን ለጦር መሳሪያነት በአሜሪካ
***************************
የአሜሪካ ጦር ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ውሎ የማያውቅ ጨረር አመንጪ የጦር መሳሪያ እየሰራ መሆኑ ተነገረ፡፡ መሳሪያው ለመምታት ባለመው ነገር ላይ ተከታታይ ጨረሮችን የሚለቅ ነው፡፡ ይህ ተጋክቲካል አልትራሾርት ፐልስድ የተባለ መሳሪያ በሳይንስ ፊክሽን ፊልሞች ላይ እንደሚታዩ መሳሪያዎች አይነት እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡
ይህም ከ250 እስከ 300 ኪሎዋት ተተኳሽ ያለው ሲሆን የአሜሪካ ባህር ሃይል ከታጠቀው መሳሪያ አስር እጥፍ ሀይል ያለውና የተተኮሰ ሚሳኤልን መደምሰስ የሚያስችል እንደሆነም ታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በምድር፣ በባህርና በአየር ሃይሉ የተለያየ ብቃት ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች የታጠቀው ጦሩ ይህኛውን ለየት የሚያደርገው በኤሌክትሪክ ሃይል ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም የኤሌክትሪክ ሃይል እስካልተቋረጠ ድረስ ሃይሉ የማይነጥፍ እንደሆነ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
አዲሱ መሳሪያም በተሸከርካሪ የሚጓጓዝ ሲሆን ተንቀሳቃሽ ጀኔሬተርና ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ ያስፈልገዋል፡፡ የመጀመሪያዎቹ አራት ተሸከርካሪዎች ከነሙሉ መሳሪያቸው ለ2024 እንደሚደርሱ ተነግሯል፡፡
ምንጭ New scientist
***************************
የአሜሪካ ጦር ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ውሎ የማያውቅ ጨረር አመንጪ የጦር መሳሪያ እየሰራ መሆኑ ተነገረ፡፡ መሳሪያው ለመምታት ባለመው ነገር ላይ ተከታታይ ጨረሮችን የሚለቅ ነው፡፡ ይህ ተጋክቲካል አልትራሾርት ፐልስድ የተባለ መሳሪያ በሳይንስ ፊክሽን ፊልሞች ላይ እንደሚታዩ መሳሪያዎች አይነት እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡
ይህም ከ250 እስከ 300 ኪሎዋት ተተኳሽ ያለው ሲሆን የአሜሪካ ባህር ሃይል ከታጠቀው መሳሪያ አስር እጥፍ ሀይል ያለውና የተተኮሰ ሚሳኤልን መደምሰስ የሚያስችል እንደሆነም ታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በምድር፣ በባህርና በአየር ሃይሉ የተለያየ ብቃት ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች የታጠቀው ጦሩ ይህኛውን ለየት የሚያደርገው በኤሌክትሪክ ሃይል ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም የኤሌክትሪክ ሃይል እስካልተቋረጠ ድረስ ሃይሉ የማይነጥፍ እንደሆነ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
አዲሱ መሳሪያም በተሸከርካሪ የሚጓጓዝ ሲሆን ተንቀሳቃሽ ጀኔሬተርና ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ ያስፈልገዋል፡፡ የመጀመሪያዎቹ አራት ተሸከርካሪዎች ከነሙሉ መሳሪያቸው ለ2024 እንደሚደርሱ ተነግሯል፡፡
ምንጭ New scientist
በ1 ዓመት የታጣው የ20 ሚሊዮን ዓመታት ህይወት ዘመን
========================
በኮሮና ቫይረስ ሳብያ በ81 ሀገራት ብቻ ከ20.5 ሚሊዮን ዓመታት የሚልቅ ቀሪ ዕድሜ መታጣቱን አዲስ ጥናት አመላከተ፡፡ ጥናቱ በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ባይሆንም እንኳን በቅርቡ መሞታቸው አይቀርም ነበር የሚለውን አስተሳሰብ አየር ላይ የሚዋልል መሰረተ ቢስ እንደሚያደርገውም ተነግሮለታል፡፡
የታጣው የመኖርያ ዘመን ሲባል ሟቾች በሞቱበት ጊዜ ባላቸው ዕድሜ እና ይኖሩበታል ተብሎ በሚታመነው የዕድሜ ጣርያ መካከል ያለው ልዩነት ነው፡፡ ጥናቱ የተሰራውም በ81 ሀገራት የተከሰቱ ከ1,279,866 በላይ የኮቪድ-19 ሞቶችን ብሎም የየሀገራቱን የተቀመጠ ዓማካኝ የህይወት ጣርያ ላይ በመመርኮዝ ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት በነዚህ 81 ሀገራት የነበሩ የሚሊዮኖች ህይወት ውስጥ ገና ወደፊት ሊኖር ይቻል የነበረ የ20,507,518 ወይም በእያንዳንዱ ሟች በአማካኝ የ16 ዓመታት ዕድሜ ታጥቷል ማለት ነው፡፡ ከነዚህ የታጡ ዓመታት ውስጥ 44.9 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ዓመት ባለው ውስጥ ይገኙ ከነበሩ ሰዎች ላይ፣ 30.2 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በታች ከሆኑት ላይ እንዲሁም 25 በመቶው ዕድሜያቸው ከ75 ዓመት በላይ ከሆኑት ላይ ነው፡፡
ሀገራትን በምሳሌነት ወስደን ካየነው በእንግሊዝ ውስጥ የ833,874 ዓመታት ህይወት የታጣ ሲሆን ይህም በአማካኝ የ11.4 ዓመት ህይወት ነው፡፡ በስፔን ደግሞ አጠቃላይ 572,567 ወይም በአማካኝ 11.24 ዓመት ሲታጣ ነገሩ የከፋባት ፔሩ በአጠቃላይ 764,856 ዓመት በአማካኝ ደግሞ የ20.2 ዓመት ዕድሜን ሟች ዜጎቿ አጥተዋል፡፡ ምንም እንኳን በተለይ በሀብታሞቹ ሀገራት ውስጥ የመሞት ዕድላቸው ከፍ የሚለው በእርጅና ዘመን ውስጥ ባሉት ዜጎች ላይ ቢሆንም አብዛኛው ሞት የተከሰተው ግን ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ባለው ክልል ውስጥ ያሉት ላይ ነው፡፡
እንዲህም ሆኖ ግን በሀብታም ሀገራት ውስጥ የታጡት ዓመታት በዋናነት ከነዚህ ዕድሜያቸው በአንፃራዊነት ከፍ ካሉት ላይ ቢሆንም መካከለኛና አነስተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ዘንድ ግን ብዙው ዓመት ዕድሜያቸው 55 እና ከዚያ በታች ከሆኑት ላይ የተቀነሰ ነው፡፡ በፆታም ወንዶች ከሴቶች በ44 በመቶ የበለጠ ዕድሜን አጥተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
========================
በኮሮና ቫይረስ ሳብያ በ81 ሀገራት ብቻ ከ20.5 ሚሊዮን ዓመታት የሚልቅ ቀሪ ዕድሜ መታጣቱን አዲስ ጥናት አመላከተ፡፡ ጥናቱ በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ባይሆንም እንኳን በቅርቡ መሞታቸው አይቀርም ነበር የሚለውን አስተሳሰብ አየር ላይ የሚዋልል መሰረተ ቢስ እንደሚያደርገውም ተነግሮለታል፡፡
የታጣው የመኖርያ ዘመን ሲባል ሟቾች በሞቱበት ጊዜ ባላቸው ዕድሜ እና ይኖሩበታል ተብሎ በሚታመነው የዕድሜ ጣርያ መካከል ያለው ልዩነት ነው፡፡ ጥናቱ የተሰራውም በ81 ሀገራት የተከሰቱ ከ1,279,866 በላይ የኮቪድ-19 ሞቶችን ብሎም የየሀገራቱን የተቀመጠ ዓማካኝ የህይወት ጣርያ ላይ በመመርኮዝ ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት በነዚህ 81 ሀገራት የነበሩ የሚሊዮኖች ህይወት ውስጥ ገና ወደፊት ሊኖር ይቻል የነበረ የ20,507,518 ወይም በእያንዳንዱ ሟች በአማካኝ የ16 ዓመታት ዕድሜ ታጥቷል ማለት ነው፡፡ ከነዚህ የታጡ ዓመታት ውስጥ 44.9 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ዓመት ባለው ውስጥ ይገኙ ከነበሩ ሰዎች ላይ፣ 30.2 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በታች ከሆኑት ላይ እንዲሁም 25 በመቶው ዕድሜያቸው ከ75 ዓመት በላይ ከሆኑት ላይ ነው፡፡
ሀገራትን በምሳሌነት ወስደን ካየነው በእንግሊዝ ውስጥ የ833,874 ዓመታት ህይወት የታጣ ሲሆን ይህም በአማካኝ የ11.4 ዓመት ህይወት ነው፡፡ በስፔን ደግሞ አጠቃላይ 572,567 ወይም በአማካኝ 11.24 ዓመት ሲታጣ ነገሩ የከፋባት ፔሩ በአጠቃላይ 764,856 ዓመት በአማካኝ ደግሞ የ20.2 ዓመት ዕድሜን ሟች ዜጎቿ አጥተዋል፡፡ ምንም እንኳን በተለይ በሀብታሞቹ ሀገራት ውስጥ የመሞት ዕድላቸው ከፍ የሚለው በእርጅና ዘመን ውስጥ ባሉት ዜጎች ላይ ቢሆንም አብዛኛው ሞት የተከሰተው ግን ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ባለው ክልል ውስጥ ያሉት ላይ ነው፡፡
እንዲህም ሆኖ ግን በሀብታም ሀገራት ውስጥ የታጡት ዓመታት በዋናነት ከነዚህ ዕድሜያቸው በአንፃራዊነት ከፍ ካሉት ላይ ቢሆንም መካከለኛና አነስተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ዘንድ ግን ብዙው ዓመት ዕድሜያቸው 55 እና ከዚያ በታች ከሆኑት ላይ የተቀነሰ ነው፡፡ በፆታም ወንዶች ከሴቶች በ44 በመቶ የበለጠ ዕድሜን አጥተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ቴክ-ሳይንስ ሪቪው ፪፤ ነገ 10 ሰዓት ይጠብቁን
=================
በነገው የቴክ ሳይንስ መሰናዶዋችን ላለፉት ተከታታይ ሳምንታት ወደ እናንተው ያደረስናቸው የአብይ ፕሮግራም እና ብላቴናት ዝግጅቶቻችንን በሪቪው መልሰን የምንቃኛቸው ይሆናል፡፡ በዚህም፤
በአብይ ፕሮግራማችን ላይ፤ ስለ ሚጥል በሽታ፣ ስለ ዲጂታል ላይብረሪ፣ የግብርና ምርምር ስራዎች መቼ ተጀመረ፣ ቀርከሀ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ አፍሪካ እና ቴክኖሎጂ እና መድሐኒታማና መዓዛማነት ያላቸው እጽዋቶች
ብላቴናት ደግሞ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዊልቸር፣ የድሮን ፈጠራ፣ የሴኩሪቲ ካሜራ፣ ዘመናዊ የሻይ ቡና ማፊያ፣ ሻማን በድጋሚ መጠቀም፣ ተሸከርካሪ የሰራው ተማሪ፣ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን ላይ የሰራናቸውን ዝግጅቶች መለስ ብለን እናስቃኛችኋለን፡፡
የዩትዩብ ቻናላችንን (https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg) ሰብስክራይብ ማድረጉን እንዳይረሱ፤ ከዓመታት በፊት ከተላለፈው የመጀመሪየው ክፍል አንስቶ ያሉትን ሁሉንም የቴክ-ሳይንስ ፕሮግራሞች አንድ በአንድ መመልከትና ለእርስዎም ሆነ ቤተሰብዎ ዕውቀትን መገብየት ይችሉበታልና፡፡
=================
በነገው የቴክ ሳይንስ መሰናዶዋችን ላለፉት ተከታታይ ሳምንታት ወደ እናንተው ያደረስናቸው የአብይ ፕሮግራም እና ብላቴናት ዝግጅቶቻችንን በሪቪው መልሰን የምንቃኛቸው ይሆናል፡፡ በዚህም፤
በአብይ ፕሮግራማችን ላይ፤ ስለ ሚጥል በሽታ፣ ስለ ዲጂታል ላይብረሪ፣ የግብርና ምርምር ስራዎች መቼ ተጀመረ፣ ቀርከሀ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ አፍሪካ እና ቴክኖሎጂ እና መድሐኒታማና መዓዛማነት ያላቸው እጽዋቶች
ብላቴናት ደግሞ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዊልቸር፣ የድሮን ፈጠራ፣ የሴኩሪቲ ካሜራ፣ ዘመናዊ የሻይ ቡና ማፊያ፣ ሻማን በድጋሚ መጠቀም፣ ተሸከርካሪ የሰራው ተማሪ፣ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን ላይ የሰራናቸውን ዝግጅቶች መለስ ብለን እናስቃኛችኋለን፡፡
የዩትዩብ ቻናላችንን (https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg) ሰብስክራይብ ማድረጉን እንዳይረሱ፤ ከዓመታት በፊት ከተላለፈው የመጀመሪየው ክፍል አንስቶ ያሉትን ሁሉንም የቴክ-ሳይንስ ፕሮግራሞች አንድ በአንድ መመልከትና ለእርስዎም ሆነ ቤተሰብዎ ዕውቀትን መገብየት ይችሉበታልና፡፡
ያለንበትን ቦታ በመከታተል ብቻ ወደ ገመናችን የሚመለከቱት የስልክ መተግበሪያዎቻችን ነገር
=========================
በየቦታው ከእጃችን የማንለያቸው ስልኮቻችን ላይ ያሉት መተግበሪያዎች በሌላ አካል እንዲታወቁብን የማንፈልጋቸው መረጃዎችን አሳልፈው እንደሚሰጡብን በተለያየ ጊዜ ሲነገር ቆይቷል፡፡ በቅርቡም እነዚህ በስልካችን ላይ ጭነን ያስቀመጥናቸው መተግበሪያዎች ያለንበትን ቦታ በመከታተል ብቻ ስለ እኛ ምን ያህል መረጃን እንደሚሰበስቡ ለማወቅ በማለም ከጣያልያኑ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቦሎኛ የመጣው ሚሮኮ ሙሴሌይሲ እና ከእንግሊዙ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን የመጣው ቤንጃሚን ባሮን ጥናትን አድርገዋል፤ ለዚህ እንዲረዳ ብለው ያዘጋጁትን መተግበሪያ በመጠቀም፡፡ በዚህም አጥኚዎቹ መተግበሪያው ምን አይነት የግል መረጃዎችን እንደሚወስድና በጥናቱ ተሳታፊዎች ዘንድ ያለውን ስሜታዊነትም (Sensitivity) መረዳት ችለዋል፡፡
ተጠቃሚዎች ስልካቸው ላይ ለሚጭኗቸው መተግበሪያዎች ፍቃድ ሲሰጧቸው ምን እንደሚያስከትልባቸው በብዛት እንደማያጤኑ የሚናገረው ሚሮኮ ሙሴሌይሲ መረጃዎቹ ተጠቃሚዎች የሚኖሩበትን፣ ልማዳቸውን፣ ፍላጎታቸውን፣ ስነ-ህዝባዊ ሁኔታቸውን (Demographics) እና ስብዕናቸው የሚያሳዩ እንደሆኑ ጠቅሷል፡፡
ይህ ጥናት አድራሻን ከመከታተል የሚገኘው ሰፊ ግላዊ መረጃ ላይ ምልከታን በመስጠት የመጀመሪያው ነው፡፡ በተለይም እነዚህ መረጃዎች የተጠቃሚዎችን የግለኝነት መብት የሚጥሱ ስለመሆናቸውም አሳይቷል፡፡ ይህን ለማስቆም ታድያ አጥኚዎቹ “ትራኪንግአድቫይዘር” የተሰኘ ያለማቋረጥ ከተጠቃሚዎች ያሉበትን ቦታ የሚከታተል መተግበሪያን ሰርተው መረጃዎችን እየሰበሰቡ መልሰው ወደ ተጠቃሚዎቹ በመውሰድ ስለ መረጃዎቹ ስሜታዊነት ያላቸውን እይታ ሲጠይቁ ቆይተዋል፡፡
በጥናቱ ላይ 69 ተጠቃሚዎች መተግበሪያውን ለሁለት ሳምንታት ስልካቸው ላይ አድርገው ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡ በዚህም ትራክአድቫይዘር የተሰኘ መተግበሪያው ከ200 ሺህ በላይ ቦታዎችን ተከታትሎ 2,500 ስፍራዎችን በመለየት ወደ 5ሺህ የሚጠጉ ስነ-ህዝብ እና ስብዕናን የተመለከቱ የግል መረጃዎችን መሰብሰብ ችሏል፡፡ ከተሰበሰቡት መረጃዎች ውስጥ ስለ ጤና፣ ማህበራዊ-ምጣኔ ሀብታዊ ሁናቴ፣ ዘር እና ኃይማኖት የሆኑትን ተጠቃሚዎቹ ስሜታዊ የግል መረጃዎቻችን ናቸው ሲሉ ለይተዋቸዋል፡፡
እንደ አጥኚዎቹ ከሆነ አሁን የተሰራውን አይነት ትንተናዎች ተጠቃሚውን ታላሚ ያደረጉና በተለይም ስሜታዊ የግል መረጃዎቻቸውን የሚጠብቁ የማስታወቂያ ስርዓቶችን በማምጣት ረገድ መንገድ ጠራጊ ናቸው፡፡ ለእንደዚህ አይነት ስርዓቶች ምስጋና ይግባና ተጠቃሚዎች ወደ ክሊኒክ እና ሆስፒታል ባመሩ ቁጥር ጤናቸውን የተመለከቱ መረጃዎችን እንዲጠብቁ የሚያደርግ ማሳሰቢያዎችን መላክ ይቻላል ሲል ሚሮኮ ሙሴሌይሲ ይናገራል፡፡ አክሎም ቀድሞ በተቀመጡ የግለኝነት ማስተካከያዎች አማካኝነት አስፈላጊ መረጃዎች በሦስተኛ አካል እንዳይሰበሰቡ ወደሚያደርጉ ስርዓች መበልፀግ ሊያመራን ይችላል ብሏል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
=========================
በየቦታው ከእጃችን የማንለያቸው ስልኮቻችን ላይ ያሉት መተግበሪያዎች በሌላ አካል እንዲታወቁብን የማንፈልጋቸው መረጃዎችን አሳልፈው እንደሚሰጡብን በተለያየ ጊዜ ሲነገር ቆይቷል፡፡ በቅርቡም እነዚህ በስልካችን ላይ ጭነን ያስቀመጥናቸው መተግበሪያዎች ያለንበትን ቦታ በመከታተል ብቻ ስለ እኛ ምን ያህል መረጃን እንደሚሰበስቡ ለማወቅ በማለም ከጣያልያኑ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቦሎኛ የመጣው ሚሮኮ ሙሴሌይሲ እና ከእንግሊዙ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን የመጣው ቤንጃሚን ባሮን ጥናትን አድርገዋል፤ ለዚህ እንዲረዳ ብለው ያዘጋጁትን መተግበሪያ በመጠቀም፡፡ በዚህም አጥኚዎቹ መተግበሪያው ምን አይነት የግል መረጃዎችን እንደሚወስድና በጥናቱ ተሳታፊዎች ዘንድ ያለውን ስሜታዊነትም (Sensitivity) መረዳት ችለዋል፡፡
ተጠቃሚዎች ስልካቸው ላይ ለሚጭኗቸው መተግበሪያዎች ፍቃድ ሲሰጧቸው ምን እንደሚያስከትልባቸው በብዛት እንደማያጤኑ የሚናገረው ሚሮኮ ሙሴሌይሲ መረጃዎቹ ተጠቃሚዎች የሚኖሩበትን፣ ልማዳቸውን፣ ፍላጎታቸውን፣ ስነ-ህዝባዊ ሁኔታቸውን (Demographics) እና ስብዕናቸው የሚያሳዩ እንደሆኑ ጠቅሷል፡፡
ይህ ጥናት አድራሻን ከመከታተል የሚገኘው ሰፊ ግላዊ መረጃ ላይ ምልከታን በመስጠት የመጀመሪያው ነው፡፡ በተለይም እነዚህ መረጃዎች የተጠቃሚዎችን የግለኝነት መብት የሚጥሱ ስለመሆናቸውም አሳይቷል፡፡ ይህን ለማስቆም ታድያ አጥኚዎቹ “ትራኪንግአድቫይዘር” የተሰኘ ያለማቋረጥ ከተጠቃሚዎች ያሉበትን ቦታ የሚከታተል መተግበሪያን ሰርተው መረጃዎችን እየሰበሰቡ መልሰው ወደ ተጠቃሚዎቹ በመውሰድ ስለ መረጃዎቹ ስሜታዊነት ያላቸውን እይታ ሲጠይቁ ቆይተዋል፡፡
በጥናቱ ላይ 69 ተጠቃሚዎች መተግበሪያውን ለሁለት ሳምንታት ስልካቸው ላይ አድርገው ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡ በዚህም ትራክአድቫይዘር የተሰኘ መተግበሪያው ከ200 ሺህ በላይ ቦታዎችን ተከታትሎ 2,500 ስፍራዎችን በመለየት ወደ 5ሺህ የሚጠጉ ስነ-ህዝብ እና ስብዕናን የተመለከቱ የግል መረጃዎችን መሰብሰብ ችሏል፡፡ ከተሰበሰቡት መረጃዎች ውስጥ ስለ ጤና፣ ማህበራዊ-ምጣኔ ሀብታዊ ሁናቴ፣ ዘር እና ኃይማኖት የሆኑትን ተጠቃሚዎቹ ስሜታዊ የግል መረጃዎቻችን ናቸው ሲሉ ለይተዋቸዋል፡፡
እንደ አጥኚዎቹ ከሆነ አሁን የተሰራውን አይነት ትንተናዎች ተጠቃሚውን ታላሚ ያደረጉና በተለይም ስሜታዊ የግል መረጃዎቻቸውን የሚጠብቁ የማስታወቂያ ስርዓቶችን በማምጣት ረገድ መንገድ ጠራጊ ናቸው፡፡ ለእንደዚህ አይነት ስርዓቶች ምስጋና ይግባና ተጠቃሚዎች ወደ ክሊኒክ እና ሆስፒታል ባመሩ ቁጥር ጤናቸውን የተመለከቱ መረጃዎችን እንዲጠብቁ የሚያደርግ ማሳሰቢያዎችን መላክ ይቻላል ሲል ሚሮኮ ሙሴሌይሲ ይናገራል፡፡ አክሎም ቀድሞ በተቀመጡ የግለኝነት ማስተካከያዎች አማካኝነት አስፈላጊ መረጃዎች በሦስተኛ አካል እንዳይሰበሰቡ ወደሚያደርጉ ስርዓች መበልፀግ ሊያመራን ይችላል ብሏል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
የቅዳሜውን አደጋ ተከትሎ ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ከበረራ እየታገዱ ናቸው
=======================
ቅዳሜ የተከሰተውንና የአውሮፕላኑ ስብርባሪዎች ከሰማይ እንዲወድቁ ያደረገው የሞተር ቃጠሎን ተከትሎ በአሜሪካን እና ጃፓን የሚገኙ ቁጥራቸው የበዛ ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ከበረራ እዲታገዱ ተደርጓል፡፡ አውሮፕላኑ በረራውን በማቋረጥ እንዲያርፍ ያስገደደውን ይህን አደጋ ተከትሎ ትናንት የአሜሪካን አቪዬሽን ቁጥጥር ባለስልጣን የፕራት እና ዊትኒ ፒደብልዩ4000 ሞተር የተገጠመላቸው የቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡
የበረራ ቁጥሩ 328 የሆነውና በዩናይትድ አየር መንገድ ንብረትነት የተመዘገበው አውሮፕላኑ ከትናንት ወድያ በረራውን ከጀመረ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነበር የሞተር ሽፋኖቹ በአቅራብያ በሚገኘው መኖርያ ሰፈር ላይ ቁልቁል መውደቅ እንደጀመሩ ወደ ዴንቨር ኤርፖርት በፍጥነት እንዲመለስ የተገደደው፡፡ አየር መንገዱ በራሱ ተነሳሽነት አሁን እየተገለገለባቸው የሚገኙትን 24 የቦይንግ 777 አውሮፕላኖች (የተጠቀሰው ሞተር የተገጠመላቸውን) ከበረራ እንዳገደና ከአቪዬሽን ተቆጣጣሪዎች ጋርም በትብብር እንደሚሰራ አስታውቋል፡፡ አሁን አገልግሎት እየሰጡ ካሉት በተጨማሪም 28 ተመሳሳይ አውሮፕላኖች በአየር መንገዱ ተቀምጠው ይገኛሉ፡፡
ቦይንግ በበኩሉ ነገሮችን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን እና ከአሜሪካንም ሆነ ጃፓን አቪዬሽን ተቆጣጣሪዎች ጋራ አንድ ላይ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል፡፡ እስካሁንም የ346 ሰዎችን ህይወት ከቀጠፉት ሁለቱ የ737 ማክስ አውሮፕላኖች አደጋ አመጣሽ ቀውስ ሙሉ በሙሉ ያልወጣው ቦይንግ የፕራት እና ዊትኒ ሞተር የተገጠመላቸው 777 ሞዴል አውሮፕላኖች ሙሉ በሙሉ ከበረራ እንዲታገዱ ምክሩን ለግሷል፡፡ የአሜሪካን አቪዬሽን ቁጥጥር ባለስልጣን ውስጥ በተቆጣጣሪነት የሚያገለግሉት ስቲቭ ዲኪንሰን እንደሚሉትም ተቋማቸው ከቦይንግም ሆነ ፕራት እና ዊትኒ ጋራ ስብሰባ ተቀምጦ የነበረ ሲሆን የቀረቡ መረጃዎች ላይ በመመስረት ይህን ሞተር የሚጠቀሙ ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች በረራቸውን እንዲያቆሙ በጋራ ወስነዋል፡፡
የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በወርሃ ታህሳስ የበረራ ቁጥሩ 904 የሆነው የጃፓን አየር መንገዱ ቦይንግ 777 አውሮፕላን ኦኪናዋ ካለው የናሃ ኤርፖርት ለቆ በረራ ከጀመረ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ባጋጠመው የሞተር ችግር ሳብያ ተመልሶ ወደ ኤርፖርቱ እንዲያርፍ መገደዱን ተከትሎ የሞተር ማሻሻያዎች እንዲደረጉለት ትዕዛዝ ሰጥቶ እንደነበር ተናግሯል፡፡ በጃፓን የፒደብልዩ4000 ሞተር የተገጠመላቸው 32 ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ተመዝግበው እንዳሉና 13 በጃፓን አየር መንገድ፤ 19ኙ ደግሞ በኦል ኒፖን አየር መንገድ እጅ ያሉ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
ምንጭ፡ Financial Times
=======================
ቅዳሜ የተከሰተውንና የአውሮፕላኑ ስብርባሪዎች ከሰማይ እንዲወድቁ ያደረገው የሞተር ቃጠሎን ተከትሎ በአሜሪካን እና ጃፓን የሚገኙ ቁጥራቸው የበዛ ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ከበረራ እዲታገዱ ተደርጓል፡፡ አውሮፕላኑ በረራውን በማቋረጥ እንዲያርፍ ያስገደደውን ይህን አደጋ ተከትሎ ትናንት የአሜሪካን አቪዬሽን ቁጥጥር ባለስልጣን የፕራት እና ዊትኒ ፒደብልዩ4000 ሞተር የተገጠመላቸው የቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር፡፡
የበረራ ቁጥሩ 328 የሆነውና በዩናይትድ አየር መንገድ ንብረትነት የተመዘገበው አውሮፕላኑ ከትናንት ወድያ በረራውን ከጀመረ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነበር የሞተር ሽፋኖቹ በአቅራብያ በሚገኘው መኖርያ ሰፈር ላይ ቁልቁል መውደቅ እንደጀመሩ ወደ ዴንቨር ኤርፖርት በፍጥነት እንዲመለስ የተገደደው፡፡ አየር መንገዱ በራሱ ተነሳሽነት አሁን እየተገለገለባቸው የሚገኙትን 24 የቦይንግ 777 አውሮፕላኖች (የተጠቀሰው ሞተር የተገጠመላቸውን) ከበረራ እንዳገደና ከአቪዬሽን ተቆጣጣሪዎች ጋርም በትብብር እንደሚሰራ አስታውቋል፡፡ አሁን አገልግሎት እየሰጡ ካሉት በተጨማሪም 28 ተመሳሳይ አውሮፕላኖች በአየር መንገዱ ተቀምጠው ይገኛሉ፡፡
ቦይንግ በበኩሉ ነገሮችን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን እና ከአሜሪካንም ሆነ ጃፓን አቪዬሽን ተቆጣጣሪዎች ጋራ አንድ ላይ ሆኖ እየሰራ መሆኑን ተናግሯል፡፡ እስካሁንም የ346 ሰዎችን ህይወት ከቀጠፉት ሁለቱ የ737 ማክስ አውሮፕላኖች አደጋ አመጣሽ ቀውስ ሙሉ በሙሉ ያልወጣው ቦይንግ የፕራት እና ዊትኒ ሞተር የተገጠመላቸው 777 ሞዴል አውሮፕላኖች ሙሉ በሙሉ ከበረራ እንዲታገዱ ምክሩን ለግሷል፡፡ የአሜሪካን አቪዬሽን ቁጥጥር ባለስልጣን ውስጥ በተቆጣጣሪነት የሚያገለግሉት ስቲቭ ዲኪንሰን እንደሚሉትም ተቋማቸው ከቦይንግም ሆነ ፕራት እና ዊትኒ ጋራ ስብሰባ ተቀምጦ የነበረ ሲሆን የቀረቡ መረጃዎች ላይ በመመስረት ይህን ሞተር የሚጠቀሙ ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች በረራቸውን እንዲያቆሙ በጋራ ወስነዋል፡፡
የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በወርሃ ታህሳስ የበረራ ቁጥሩ 904 የሆነው የጃፓን አየር መንገዱ ቦይንግ 777 አውሮፕላን ኦኪናዋ ካለው የናሃ ኤርፖርት ለቆ በረራ ከጀመረ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ባጋጠመው የሞተር ችግር ሳብያ ተመልሶ ወደ ኤርፖርቱ እንዲያርፍ መገደዱን ተከትሎ የሞተር ማሻሻያዎች እንዲደረጉለት ትዕዛዝ ሰጥቶ እንደነበር ተናግሯል፡፡ በጃፓን የፒደብልዩ4000 ሞተር የተገጠመላቸው 32 ቦይንግ 777 አውሮፕላኖች ተመዝግበው እንዳሉና 13 በጃፓን አየር መንገድ፤ 19ኙ ደግሞ በኦል ኒፖን አየር መንገድ እጅ ያሉ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
ምንጭ፡ Financial Times
በተለያዩ መተግበሪያዎች የሚሰራጩ የጤና መረጃዎችን ፌስቡክ አገደ
************************************
ፌስቡክ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በፕላትፎርሙ ላይ ጥብቅ ክትትል እያደረገ መሆኑን አመላካች ነገሮች እየታዩ ነው፡፡ ከእነዚህም ባሳለፍነው የፈረንጆቹ አመት በተካሄደው አወዛጋቢው የአሜሪካውያን ምርጫ ወቅት የተወሰዱ እርምጃዎች አንድ ማሳያ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ፌስቡክ ፕላተግፎርሙን ተጠቅመው የተለያዩ ጤና ነክ መረጃዎችን የሚያስተላልፉ ሶስተኛ ወገን መተግበሪያዎችን ማገዱን አሳውቋል፡፡ ጉዳዩን የተከታተሉት የኒዮርክ ባለስልጣናት እንዳሉት ከሆነ ፌስቡክ እርምጃውን የወሰደው የድረ-ገጹን ህጎች በመጣስ መረጃዎችን በሚያሰራጩ መተግበሪያዎች ላይ ነው፡፡
ከዚህ በፊት መተግበሪያ የሚያበለጽጉ ተቋማትን ጤና፣ ቢዝነስና ግላዊ መረጃዎች ላይ መሰረት ያደረጉ ሶስተኛ ወገን መረጃዎችን እንዳያበለጽጉ ማሳሰቢያ ሰጥቶ የነበረው ፌስቡክ እስካሁን ድረስ ነገሩን ይፋ ሳያደርገው ቆይቷል፡፡ እንደ ተቋሙ ሰዎች ገለጻ ከሆነ እርምጃው የደንበኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተወሰደ ነው፡፡
ፌስቡክ በፕላትፎርሙ የታገዱ የቃላት ዝርዝርን በመፍጠርና በመተንተን እንዲሁም መተግበሪያው ውስጥ ተቀባይነት የሌላቸውን ሚስጥራዊ መረጃዎችን በተሻለ ሁኔታ ለማጣራት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም በማጣራት ላይ ይገኛል ፡፡ ፖሊሲያችን የደንበኞቻችንን ደህንነት ሊጎዱ የሚችሉ ሴንሲቲቭ መረጃዎችን በፕላትፎርሙ እንዲንቀሳቀሱ አይፈቅድም ያሉት የፌስቡክ ቃል አቀባይ በአሁኑ ወቅት እንዲህ አይነት መረጃዎችን የመለየትና የማገድ ስራችንን አጠናክረን ቀጥለናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Tech Xplore
************************************
ፌስቡክ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በፕላትፎርሙ ላይ ጥብቅ ክትትል እያደረገ መሆኑን አመላካች ነገሮች እየታዩ ነው፡፡ ከእነዚህም ባሳለፍነው የፈረንጆቹ አመት በተካሄደው አወዛጋቢው የአሜሪካውያን ምርጫ ወቅት የተወሰዱ እርምጃዎች አንድ ማሳያ ነው፡፡ አሁን ደግሞ ፌስቡክ ፕላተግፎርሙን ተጠቅመው የተለያዩ ጤና ነክ መረጃዎችን የሚያስተላልፉ ሶስተኛ ወገን መተግበሪያዎችን ማገዱን አሳውቋል፡፡ ጉዳዩን የተከታተሉት የኒዮርክ ባለስልጣናት እንዳሉት ከሆነ ፌስቡክ እርምጃውን የወሰደው የድረ-ገጹን ህጎች በመጣስ መረጃዎችን በሚያሰራጩ መተግበሪያዎች ላይ ነው፡፡
ከዚህ በፊት መተግበሪያ የሚያበለጽጉ ተቋማትን ጤና፣ ቢዝነስና ግላዊ መረጃዎች ላይ መሰረት ያደረጉ ሶስተኛ ወገን መረጃዎችን እንዳያበለጽጉ ማሳሰቢያ ሰጥቶ የነበረው ፌስቡክ እስካሁን ድረስ ነገሩን ይፋ ሳያደርገው ቆይቷል፡፡ እንደ ተቋሙ ሰዎች ገለጻ ከሆነ እርምጃው የደንበኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተወሰደ ነው፡፡
ፌስቡክ በፕላትፎርሙ የታገዱ የቃላት ዝርዝርን በመፍጠርና በመተንተን እንዲሁም መተግበሪያው ውስጥ ተቀባይነት የሌላቸውን ሚስጥራዊ መረጃዎችን በተሻለ ሁኔታ ለማጣራት ሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም በማጣራት ላይ ይገኛል ፡፡ ፖሊሲያችን የደንበኞቻችንን ደህንነት ሊጎዱ የሚችሉ ሴንሲቲቭ መረጃዎችን በፕላትፎርሙ እንዲንቀሳቀሱ አይፈቅድም ያሉት የፌስቡክ ቃል አቀባይ በአሁኑ ወቅት እንዲህ አይነት መረጃዎችን የመለየትና የማገድ ስራችንን አጠናክረን ቀጥለናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Tech Xplore
ዲ ኤን ኤ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲንቀሳቀስ የሚያሳይ ምስል በተመራማሪዎች ይፋ ተደርጓል
======================
ዲ ኤን ኤ ወይም ዘረመል የምንለው የሞሎኪውል ስብስብ በህዋሶቻችን ውስጥ የሚያደርገውን የመተጣጠፍ ወይም ዳንስ መሰል እንቅስቃሴ የሚያሳይ የመጀመሪያ ምስል ከሰሞኑ በተመራማሪዎች ይፋ ተደርጓል፡፡ እንግሊዝ ውስጥ በሚገኙ ሶስት ዩኒቨርስቲዎች በጥምረት የተሰራው አዲሱ ምርምር ተመራማሪዎች ጥቅም ላይ ባዋሉት እጅግ የላቀ የአቶሚክ ኃይል ማይክሮስኮፕ እና ምስል ለመከሰት በሚያስችል የሱፐር ኮምፒውተር ሲሚዩሌሽን አማካኝነት የተሰራ ነው፡፡
ከፀጉር ቀለማችን አንስቶ እስከ እግር ጥፍራችን ድረስ በምን ልክ ሰውነታችን እንደሚያድግ የሚወስነው እና ትእዛዝ የሚሰጠው ይህ የሰው ልጅ የዘረመል ኮድ (DNA) አጠቃላይ ለመኖራችን ምከንያት የሆነውን ፕሮቲን በማበልፀግና በማምረትም ሰውነታችን በትክክል ስራውን እንዲሰራ የሚያደርግ ረቂቅ የተፈጥሮ ስራ ነው፡፡ እንደአውሮፓውያን አቆጣጠር በ1953 ጀምስ ዋትሰን እና ፍራንሲስ ክሪክ በተባሉ የስነ ህይወት ተመራማሪዎች የመጀመሪው የዲ ኤን ኤ ድርብ-ሄሊክስ መዋቅር (double-helix structure) ይፋ ከተደረገ በኋላ፤ እነዚህ ዘረመሎች በህዋሶቻችን ውስጥ የሚደርጉት የመተጣጠፍ እንቅስቃሴን ምን እንደሚመስል የሚያሳየው አዲሱ የተመራማሪዎች ምስል ከ70 አመታት በኋላ በዲ ኤን ኤ ዘሪያ የተገኝ ትልቅ የምርምር ውጤት ይሆናል፡፡
ተመራመሪዎች የማይታመነውን ባለነጠላ የዲ ኤን ኤ ሞለኪውል የምስል እንቅስቃሴ ለማበልፀግ በማይክሮስኮፑ የወሰዱት እጅግ ከፍተኛ ጥራት ያለው የምስል ቀረፃ በእጅጉ የረዳቸው ሲሆን ከዚህ በፊት በነበረው የቴክኖሎጂ አቅም የዲ ኤን ኤ ምስል መውሰድ ቢቻልም እንደአሁኑ ሲንቀሳቀስ የሚያሳይ ምስል ግን ማግኘት አልተቻለም ነበር፡፡
ይህ ተንቀሳቃሽ ምስል የዲ ኤን ኤ ድርብ-ሄሊክስ መዋቅር ውስጥ ያሉ እያንዳንዱን የአቶም አቀማመጥ በማሳየት ሁሉም ሞለኪውሎች በህዋሶቻችን ውስጥ የሚኖራቸውን የመዟዟር እና የመጠማዘዝ እንቅስቃሴ ለማብራራት ያግዛል፡፡ የዘረመሉን ተንቀሳቃሽ ምስል በማበልፀግ ሂደት ውስጥ ዋና ተሳታፊ የነበሩት ዶ/ር አሊስ ፓይን ይህ የምርምር ውጤት አጠቃላይ በዲ ኤን ኤ ዘሪያ የሚኖረንን የእውቀት አድማስ ለማስፋትና ሌሎች አደዲስ ግኝቶችን ለመጨምር ከማገዙም ባላይ አሁን ባለው ህክምና ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለማከል እንደሚረዳም ይናገራሉ፡፡
ምንጭ፡ Express እና Bigthink
======================
ዲ ኤን ኤ ወይም ዘረመል የምንለው የሞሎኪውል ስብስብ በህዋሶቻችን ውስጥ የሚያደርገውን የመተጣጠፍ ወይም ዳንስ መሰል እንቅስቃሴ የሚያሳይ የመጀመሪያ ምስል ከሰሞኑ በተመራማሪዎች ይፋ ተደርጓል፡፡ እንግሊዝ ውስጥ በሚገኙ ሶስት ዩኒቨርስቲዎች በጥምረት የተሰራው አዲሱ ምርምር ተመራማሪዎች ጥቅም ላይ ባዋሉት እጅግ የላቀ የአቶሚክ ኃይል ማይክሮስኮፕ እና ምስል ለመከሰት በሚያስችል የሱፐር ኮምፒውተር ሲሚዩሌሽን አማካኝነት የተሰራ ነው፡፡
ከፀጉር ቀለማችን አንስቶ እስከ እግር ጥፍራችን ድረስ በምን ልክ ሰውነታችን እንደሚያድግ የሚወስነው እና ትእዛዝ የሚሰጠው ይህ የሰው ልጅ የዘረመል ኮድ (DNA) አጠቃላይ ለመኖራችን ምከንያት የሆነውን ፕሮቲን በማበልፀግና በማምረትም ሰውነታችን በትክክል ስራውን እንዲሰራ የሚያደርግ ረቂቅ የተፈጥሮ ስራ ነው፡፡ እንደአውሮፓውያን አቆጣጠር በ1953 ጀምስ ዋትሰን እና ፍራንሲስ ክሪክ በተባሉ የስነ ህይወት ተመራማሪዎች የመጀመሪው የዲ ኤን ኤ ድርብ-ሄሊክስ መዋቅር (double-helix structure) ይፋ ከተደረገ በኋላ፤ እነዚህ ዘረመሎች በህዋሶቻችን ውስጥ የሚደርጉት የመተጣጠፍ እንቅስቃሴን ምን እንደሚመስል የሚያሳየው አዲሱ የተመራማሪዎች ምስል ከ70 አመታት በኋላ በዲ ኤን ኤ ዘሪያ የተገኝ ትልቅ የምርምር ውጤት ይሆናል፡፡
ተመራመሪዎች የማይታመነውን ባለነጠላ የዲ ኤን ኤ ሞለኪውል የምስል እንቅስቃሴ ለማበልፀግ በማይክሮስኮፑ የወሰዱት እጅግ ከፍተኛ ጥራት ያለው የምስል ቀረፃ በእጅጉ የረዳቸው ሲሆን ከዚህ በፊት በነበረው የቴክኖሎጂ አቅም የዲ ኤን ኤ ምስል መውሰድ ቢቻልም እንደአሁኑ ሲንቀሳቀስ የሚያሳይ ምስል ግን ማግኘት አልተቻለም ነበር፡፡
ይህ ተንቀሳቃሽ ምስል የዲ ኤን ኤ ድርብ-ሄሊክስ መዋቅር ውስጥ ያሉ እያንዳንዱን የአቶም አቀማመጥ በማሳየት ሁሉም ሞለኪውሎች በህዋሶቻችን ውስጥ የሚኖራቸውን የመዟዟር እና የመጠማዘዝ እንቅስቃሴ ለማብራራት ያግዛል፡፡ የዘረመሉን ተንቀሳቃሽ ምስል በማበልፀግ ሂደት ውስጥ ዋና ተሳታፊ የነበሩት ዶ/ር አሊስ ፓይን ይህ የምርምር ውጤት አጠቃላይ በዲ ኤን ኤ ዘሪያ የሚኖረንን የእውቀት አድማስ ለማስፋትና ሌሎች አደዲስ ግኝቶችን ለመጨምር ከማገዙም ባላይ አሁን ባለው ህክምና ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለማከል እንደሚረዳም ይናገራሉ፡፡
ምንጭ፡ Express እና Bigthink
የወጣቱ ፈጠራ በመንገድ ላይ ለሚሸጡ ሰዎች መልካም ነገር ይዞ መቷል
========================
በቶሎ የሚደርሱ ምግቦችን እና የተለያዩ መጠጦችን ሰዎች በሚበዙባቸው ቦታዎች በመዟዟር የሚሸጡ እና በዚህም ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ ብዙ አፍሪካውያን ዜጎች አሉ፡፡ ይህ እንቅስቃሴ በብዛት ከሚስተዋሉባት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ናይጄሪያ አንዷ ስትሆን በሃገሪቱ ሰሜናዊ ግዛት ይህ አንቅስቃሴ ይበልጥ ጎልቶ ይታያል፡፡ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ የሀገሪቱ ዜጎች በመንገድ ላይ ለሚያካሂዱት የምግብ ማቀነባበሪያ እና የሽያጭ ስራ መጠናቸው አነስ ያሉ ጄኔሪተሮች እጅግ አስፈላጊ ሲሆኑ ይህን ማሟላት ያልቻሉ ሰዎች ግን ስራውን በጊዜ ለማቆም ይገደዳሉ፡፡
ታዲያ ይህን ችግር የተመለከተው ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ ኡስማን በፀሃይ ኃይል የሚሰራ ግሩም ቴክኖሎጂን (kiosk) በማቅረብ ለወትሮ ያለጄኔረተር ንክች የማይደረገውን ይህን የማቀነባበር እና የሽያጭ ስራ ባቀረበው ቀላል መሳሪያ አማካኝነት ማንም ሰው እንዲሰራው አስችሏል፡፡ ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ በሚኖርበት የናይጀሪያ ሰሜን ግዛት ልዩ ስሟ ማኢ ሻዪ በተባለች አካባቢ ለሚኖሩ የሰፈሩ ሰዎች ያቀረበው ይህ የቴክኖሎጂ ውጤት ለማብሰል የሚያስችል ስቶቭ፣ ኢንቨርተር ባትሪ፣ ተንቀሳቃሽ ዴስክ እና ደንበኞች ያዘዙት ምግብ እስኪደርስ እንዲያዝናናቸው የተዘጋጀ ቴሌቪዥን ጭምር የተካተተበት ግሩም የቴክኖሎጀ ፈጠራ ነው፡፡ ወጣቱ ከእነዚህ ግብዓቶች በተጨማሪ ለምግብ ማስቀመጫ የሚያገለግል የፈጠራ አይነት በአዲሱ ቴክኖሎጂ ላይ ያካተተ ሲሆን፤ እነዚህ ሁሉ ግብዓቶች ከሶላር ፓኔል በሚያገኙት ሃይል መስራት የሚችሉ ናቸው፡፡
ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ iCart Solution ብሎ የሰየመው ይህ የቴክኖሎጂ ውጤት በቀላሉ መንቀሳቀስ የሚችል እና በቶሎ የሚደርሱ ምግቦችንና የተለያዩ መጠጦችን ሰዎች በሚበዙባቸው ቦታዎች በመዟዟር ለመሸጥ የሚያስችል ግሩም ቴክኖሎጂ ሲሆን ከዲዛይን ስራው ጀምሮ እስከ ምርት መጠናቀቂያው ድረስ ወጣቱ በሚያስተዳድረው ዳልስማን ቴክ በተባለ የቴክኖሎጂ ድርጅት የተከናወነ ነው፡፡ ይህን የቴክኖሎጂ ፈጠራ በፕሮቶታይፕ ደረጃ ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ቀን ብቻ እንደሚወስድበት የሚናገረው ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ ኡስማን በቀጣይ ጊዜያት ቴክኖሎጂውን በብዛት በማምረት ከሀገሩ አልፎ በሌሎች አፍሪካ ሀገራትም ምረቱን በስፋት ማቅረብ እንደሚፈልግ ይናገራል፡፡
ምንጭ፡ growingworld24
========================
በቶሎ የሚደርሱ ምግቦችን እና የተለያዩ መጠጦችን ሰዎች በሚበዙባቸው ቦታዎች በመዟዟር የሚሸጡ እና በዚህም ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ ብዙ አፍሪካውያን ዜጎች አሉ፡፡ ይህ እንቅስቃሴ በብዛት ከሚስተዋሉባት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ናይጄሪያ አንዷ ስትሆን በሃገሪቱ ሰሜናዊ ግዛት ይህ አንቅስቃሴ ይበልጥ ጎልቶ ይታያል፡፡ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ የሀገሪቱ ዜጎች በመንገድ ላይ ለሚያካሂዱት የምግብ ማቀነባበሪያ እና የሽያጭ ስራ መጠናቸው አነስ ያሉ ጄኔሪተሮች እጅግ አስፈላጊ ሲሆኑ ይህን ማሟላት ያልቻሉ ሰዎች ግን ስራውን በጊዜ ለማቆም ይገደዳሉ፡፡
ታዲያ ይህን ችግር የተመለከተው ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ ኡስማን በፀሃይ ኃይል የሚሰራ ግሩም ቴክኖሎጂን (kiosk) በማቅረብ ለወትሮ ያለጄኔረተር ንክች የማይደረገውን ይህን የማቀነባበር እና የሽያጭ ስራ ባቀረበው ቀላል መሳሪያ አማካኝነት ማንም ሰው እንዲሰራው አስችሏል፡፡ ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ በሚኖርበት የናይጀሪያ ሰሜን ግዛት ልዩ ስሟ ማኢ ሻዪ በተባለች አካባቢ ለሚኖሩ የሰፈሩ ሰዎች ያቀረበው ይህ የቴክኖሎጂ ውጤት ለማብሰል የሚያስችል ስቶቭ፣ ኢንቨርተር ባትሪ፣ ተንቀሳቃሽ ዴስክ እና ደንበኞች ያዘዙት ምግብ እስኪደርስ እንዲያዝናናቸው የተዘጋጀ ቴሌቪዥን ጭምር የተካተተበት ግሩም የቴክኖሎጀ ፈጠራ ነው፡፡ ወጣቱ ከእነዚህ ግብዓቶች በተጨማሪ ለምግብ ማስቀመጫ የሚያገለግል የፈጠራ አይነት በአዲሱ ቴክኖሎጂ ላይ ያካተተ ሲሆን፤ እነዚህ ሁሉ ግብዓቶች ከሶላር ፓኔል በሚያገኙት ሃይል መስራት የሚችሉ ናቸው፡፡
ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ iCart Solution ብሎ የሰየመው ይህ የቴክኖሎጂ ውጤት በቀላሉ መንቀሳቀስ የሚችል እና በቶሎ የሚደርሱ ምግቦችንና የተለያዩ መጠጦችን ሰዎች በሚበዙባቸው ቦታዎች በመዟዟር ለመሸጥ የሚያስችል ግሩም ቴክኖሎጂ ሲሆን ከዲዛይን ስራው ጀምሮ እስከ ምርት መጠናቀቂያው ድረስ ወጣቱ በሚያስተዳድረው ዳልስማን ቴክ በተባለ የቴክኖሎጂ ድርጅት የተከናወነ ነው፡፡ ይህን የቴክኖሎጂ ፈጠራ በፕሮቶታይፕ ደረጃ ሰርቶ ለማጠናቀቅ አምስት ቀን ብቻ እንደሚወስድበት የሚናገረው ወጣቱ የፈጠራ ባለሙያ ኡስማን በቀጣይ ጊዜያት ቴክኖሎጂውን በብዛት በማምረት ከሀገሩ አልፎ በሌሎች አፍሪካ ሀገራትም ምረቱን በስፋት ማቅረብ እንደሚፈልግ ይናገራል፡፡
ምንጭ፡ growingworld24
ከ87 ሺህ በላይ ከፍ ያለው የኮቪድ 19 ምርምር
*****************************
በአለም ዙሪያ ያሉ ተመራማሪዎች ኮቪድ 19 ከተከሰተ ጀምሮ በወረርሽኙ ዙሪያ ከ87 ሺህ በላይ የሚሆኑ በወረርሽኙ ዙሪያ የተሰሩ ጥናታዊ ጽሁፎችን እንዳሳተሙ ተነገረ፡፡ ይህ መረጃም እስካለፈው የፈረንጆቹ አመት ጥቅምት ወር ድረስ ያለው ነው፡፡ በዚህም ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ ተመራማሪዎች በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ይህን ያክል የምርምር ውጤት በመታተሙ እጅግ እንደተገረሙ ተናግረዋል፡፡
በኦሃዩ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ጆን ግሌን ቁጥሩ በጣም አስገራሚ እንደሆነና በሳይንስ ታሪክ ውስጥ ተደርጎ ያማያውቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ሁሉም በሚባል ደረጃ በአለማችን የሚገኙ የሳይንስ ማህበረሰብ አባላትና ተመራማሪዎች ትኩረታቸውን ወደ ወረርሽኙ ማዞራቸውን ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ በጉዳዩ ላይ መረጃ በሰበሰቡበት ወቅት ከተለያዩ ሳይንሳዊ የመረጃ ቋቶች ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የተሰሩ ጥናቶችን ለይተዋል፡፡ በዚህም ከጥር ግማሽ እስከ ሚያዚያ 2020 ድረስ 4875 የጥናት ውጤቶች ወይም አርቲክሎች የታተሙ ሲሆን ይህ ቁጥር እስከ ሀምሌ ግማሽ 2020 ድረስ ወደ 44 ሺህ 13 ከፍ ማለት ችሏል፡፡ በሚያስገርም መልኩ በአለም አቀፍ ደረጃ ተጠናክሮ የቀጠለው ይህ የምርምር ስራ በ2020ው የጥቅምት ወር መጀመሪያ ላይ 87 ሺህ 515 መድረሱን የተሰበሰበው መረጃ ያመለክታል፡፡
አጥኘዎቹ የኮሮና ወረርሽኝ ጥናትን በ1990ዎቹ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቶ ከነበረው የናኖ ስኬል ሳይንስ ጋር አወዳድረውታል፡፡ በናኖ ስኬል ዙሪያ የተሰሩ ጥናቶች ከ4000 ወደ 90 ሺህ ለማደግ 19 ዓመታት አስፈልጓል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ምርምሮች ግን እዚህ ቁጥር ላይ ለመድረስ አምስት ወራት ብቻ ፈጅቶባቸዋል፡፡ በዚህም ቁጥር ላይ የአሜሪካንና የቻይና አስተዋጽኦ ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ከአጠቃላዩ ቁጥር ቻይና 43 በመቶውን የሸፈነች ሲሆን የወረርሽኙ ስርጭት በቻይና እየቀነሰ ከመጣ ወዲህ የሚሰሩ ምርምሮችም ቁጥር እየቀነሰ መጥቷል፡፡ አሜሪካም ይህ ጥናት እስከተሰራበት ጊዜ ድረስ የ33 በመቶ ድርሻ ነበራት፡፡
ምንጭ: SciTechDaily
*****************************
በአለም ዙሪያ ያሉ ተመራማሪዎች ኮቪድ 19 ከተከሰተ ጀምሮ በወረርሽኙ ዙሪያ ከ87 ሺህ በላይ የሚሆኑ በወረርሽኙ ዙሪያ የተሰሩ ጥናታዊ ጽሁፎችን እንዳሳተሙ ተነገረ፡፡ ይህ መረጃም እስካለፈው የፈረንጆቹ አመት ጥቅምት ወር ድረስ ያለው ነው፡፡ በዚህም ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩ ተመራማሪዎች በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ይህን ያክል የምርምር ውጤት በመታተሙ እጅግ እንደተገረሙ ተናግረዋል፡፡
በኦሃዩ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ጆን ግሌን ቁጥሩ በጣም አስገራሚ እንደሆነና በሳይንስ ታሪክ ውስጥ ተደርጎ ያማያውቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ሁሉም በሚባል ደረጃ በአለማችን የሚገኙ የሳይንስ ማህበረሰብ አባላትና ተመራማሪዎች ትኩረታቸውን ወደ ወረርሽኙ ማዞራቸውን ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ በጉዳዩ ላይ መረጃ በሰበሰቡበት ወቅት ከተለያዩ ሳይንሳዊ የመረጃ ቋቶች ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የተሰሩ ጥናቶችን ለይተዋል፡፡ በዚህም ከጥር ግማሽ እስከ ሚያዚያ 2020 ድረስ 4875 የጥናት ውጤቶች ወይም አርቲክሎች የታተሙ ሲሆን ይህ ቁጥር እስከ ሀምሌ ግማሽ 2020 ድረስ ወደ 44 ሺህ 13 ከፍ ማለት ችሏል፡፡ በሚያስገርም መልኩ በአለም አቀፍ ደረጃ ተጠናክሮ የቀጠለው ይህ የምርምር ስራ በ2020ው የጥቅምት ወር መጀመሪያ ላይ 87 ሺህ 515 መድረሱን የተሰበሰበው መረጃ ያመለክታል፡፡
አጥኘዎቹ የኮሮና ወረርሽኝ ጥናትን በ1990ዎቹ ከፍተኛ ትኩረት አግኝቶ ከነበረው የናኖ ስኬል ሳይንስ ጋር አወዳድረውታል፡፡ በናኖ ስኬል ዙሪያ የተሰሩ ጥናቶች ከ4000 ወደ 90 ሺህ ለማደግ 19 ዓመታት አስፈልጓል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ምርምሮች ግን እዚህ ቁጥር ላይ ለመድረስ አምስት ወራት ብቻ ፈጅቶባቸዋል፡፡ በዚህም ቁጥር ላይ የአሜሪካንና የቻይና አስተዋጽኦ ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ከአጠቃላዩ ቁጥር ቻይና 43 በመቶውን የሸፈነች ሲሆን የወረርሽኙ ስርጭት በቻይና እየቀነሰ ከመጣ ወዲህ የሚሰሩ ምርምሮችም ቁጥር እየቀነሰ መጥቷል፡፡ አሜሪካም ይህ ጥናት እስከተሰራበት ጊዜ ድረስ የ33 በመቶ ድርሻ ነበራት፡፡
ምንጭ: SciTechDaily
ህልም ላይ ሆኖም የሒሳብ ጥያቄዎችን መፍታት እንደሚቻል ታወቀ
=========================
ሰዎችን በተኙበት ሰዓት ማዋራቱ ህልማቸው ላይ ተፅዕንዖ ያደርሳል፤ አንዳንዴም የተኛው ሰው ከእንቅልፉ ሳይነቃ ምላሾችን መስጠት ይችላል፡፡ ከአሜሪካኑ ኖርዝ ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ የሆኑት ኬን ፖለር እና ባልደረባዎቹ ሰዎች ህልም እያለሙ ባሉበት ሰዓት የሂሳብ ጥያቄዎችን ጭምር መፍታት እንደሚችሉ አረጋግጠዋል፡፡ ይህ የሚሆነው ያንቀላፋው ሰው ህልም ላይ መሆኑንና አንዳንዴም ሊቆጣጠረው በሚችለው ፈጣን የአይን እንቅስቃሴ (REM) ተብሎ በሚጠራ የእንቅልፋችን የመባቻ ደረጃ ላይ ነው፡፡
ከህልም አላሚው ጋራ ጥሩ ግንኙነት እያደረጉ መሆናቸውንና መልሱም በትክክል እንደተመለሰላቸው ለማረጋገጥ አጥኚዎቹ ትክክለኛው መልሶቻቸውን የሚያውቋቸውን ጥያቄዎች ለጥናቱ ተሳታፊዎች ሲጠይቁ እንደነበር ኬን ፓለር ተናግሯል፡፡ የጥናት ቡድኑ ተሳታፊዎቹን አዎ ወይም አይደለም የሚል ምላሽ የያዙ ጥያቄዎች ብሎም ቀላል የሂሳብ ስሌቶችን ሲጠይቋቸው የቆዩ ሲሆን መላሾቹ ወደ እንቅልፍ ከማምራታቸው በፊት ስለሚጠየቋቸው ጥያቄዎች መረጃ አልተሰጣቸውም፡፡ ህልም ውስጥ ያሉት የጥናቱ ተሳታፊዎች ታድያ ለተጠየቋቸው ጥያቄዎች 29 ጊዜ ትክክለኛ፣ አምስት ጊዜ የተሳሳተ እንዲሁም 28 ጊዜ የፊት ጡንቻቸውን ወይም አይናቸውን በማንቀሳቀስ አሻሚ የሆኑ ምላሾችን የሰጡ ሲሆን ለ96 ጊዜያት ደግሞ ምንም ምላሽ ሳይሰጡ አልፈዋል፡፡
ከእንቅልፋቸው ከነቁ በኋላ አንዳንድ ተሳታፊዎች እያለሙ ሳለ ከህልሙ ውጪ ጥያቄዎች ሲጠየቁ መስማታቸውን ሲናገሩ ሌሎቹ ደግሞ ጥያቄዎቹን ያዩት ህልም አካል አድርገው ገልፀዋቸዋል፡፡ አንድ መኪና እየነዳ እንደነበር ሆኖ ሲያልም የነበረ ተሳታፊ በበኩሉ መኪናውን በማሽከርከር ላይ ሳለ የሂሳብ ጥያቁዎች በራዲዮን ሲጠየቁ እንደነበር አድርጎ አድርጎ ጥያቄዎቹን ከህልሙ አስተሳስሯቸዋል፡፡
ጥናቱ አንድ ሰው ህልም እያየ ሳለ የህልሙ ይዘት ላይ ተፅዕንዖ ማድረስ እንደምንችል ያሳየ መሆኑን የገለፁት የእንግሊዙ ስዋንዚ ዩኒቨርሲቲ ምሁር ማርክ ብላግሮቭ “ቀጣዩ ጥያቄ አረፍተ ነገሮቹ በከፍተኛ ደረጃ ግላዊ ህይወት ላይ ያተኮሩና ስሜታዊ ቢሆኑ ምን ሊፈጠር ይችላል?” የሚለው እንደሆነ ይገልፃል፡፡ የሚያሰጋን ነገር ካለ ማለማችን እየታወቀን ባለው ህልም ላይ ነገሩን ብንሞክረው ከስጋታችን ልንላቀቅ እንደምንችልም ግምቱን ያስቀምጣል፡፡ በዚህም መሰረት ህልም ላይ ካለ ሰው ጋራ የሚደረግ ውይይት እንደ ጭንቀት፣ ስጋት እና መሰል የጤና ችግሮች ያሉበት ሰው የተሻለ እንቅልፍ እንዲተኛ ሊረዳው እንደሚችል ተስፋ አድርጓል፡፡
ምንጭ፡ New Scientist
ውድ የፔጃችን ቤተሰቦች አዳዲስ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ነክ መረጃዎችን በየቀኑ ለማግኝት የፔጃችን ተከታይ ይሁኑ፤
በሌሎች አማራጪች ሊያገኙን ከፈለጉም እነዚህን ይጠቀሙ
ድረ-ገፅ http://www.techin.gov.et/
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia
=========================
ሰዎችን በተኙበት ሰዓት ማዋራቱ ህልማቸው ላይ ተፅዕንዖ ያደርሳል፤ አንዳንዴም የተኛው ሰው ከእንቅልፉ ሳይነቃ ምላሾችን መስጠት ይችላል፡፡ ከአሜሪካኑ ኖርዝ ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ የሆኑት ኬን ፖለር እና ባልደረባዎቹ ሰዎች ህልም እያለሙ ባሉበት ሰዓት የሂሳብ ጥያቄዎችን ጭምር መፍታት እንደሚችሉ አረጋግጠዋል፡፡ ይህ የሚሆነው ያንቀላፋው ሰው ህልም ላይ መሆኑንና አንዳንዴም ሊቆጣጠረው በሚችለው ፈጣን የአይን እንቅስቃሴ (REM) ተብሎ በሚጠራ የእንቅልፋችን የመባቻ ደረጃ ላይ ነው፡፡
ከህልም አላሚው ጋራ ጥሩ ግንኙነት እያደረጉ መሆናቸውንና መልሱም በትክክል እንደተመለሰላቸው ለማረጋገጥ አጥኚዎቹ ትክክለኛው መልሶቻቸውን የሚያውቋቸውን ጥያቄዎች ለጥናቱ ተሳታፊዎች ሲጠይቁ እንደነበር ኬን ፓለር ተናግሯል፡፡ የጥናት ቡድኑ ተሳታፊዎቹን አዎ ወይም አይደለም የሚል ምላሽ የያዙ ጥያቄዎች ብሎም ቀላል የሂሳብ ስሌቶችን ሲጠይቋቸው የቆዩ ሲሆን መላሾቹ ወደ እንቅልፍ ከማምራታቸው በፊት ስለሚጠየቋቸው ጥያቄዎች መረጃ አልተሰጣቸውም፡፡ ህልም ውስጥ ያሉት የጥናቱ ተሳታፊዎች ታድያ ለተጠየቋቸው ጥያቄዎች 29 ጊዜ ትክክለኛ፣ አምስት ጊዜ የተሳሳተ እንዲሁም 28 ጊዜ የፊት ጡንቻቸውን ወይም አይናቸውን በማንቀሳቀስ አሻሚ የሆኑ ምላሾችን የሰጡ ሲሆን ለ96 ጊዜያት ደግሞ ምንም ምላሽ ሳይሰጡ አልፈዋል፡፡
ከእንቅልፋቸው ከነቁ በኋላ አንዳንድ ተሳታፊዎች እያለሙ ሳለ ከህልሙ ውጪ ጥያቄዎች ሲጠየቁ መስማታቸውን ሲናገሩ ሌሎቹ ደግሞ ጥያቄዎቹን ያዩት ህልም አካል አድርገው ገልፀዋቸዋል፡፡ አንድ መኪና እየነዳ እንደነበር ሆኖ ሲያልም የነበረ ተሳታፊ በበኩሉ መኪናውን በማሽከርከር ላይ ሳለ የሂሳብ ጥያቁዎች በራዲዮን ሲጠየቁ እንደነበር አድርጎ አድርጎ ጥያቄዎቹን ከህልሙ አስተሳስሯቸዋል፡፡
ጥናቱ አንድ ሰው ህልም እያየ ሳለ የህልሙ ይዘት ላይ ተፅዕንዖ ማድረስ እንደምንችል ያሳየ መሆኑን የገለፁት የእንግሊዙ ስዋንዚ ዩኒቨርሲቲ ምሁር ማርክ ብላግሮቭ “ቀጣዩ ጥያቄ አረፍተ ነገሮቹ በከፍተኛ ደረጃ ግላዊ ህይወት ላይ ያተኮሩና ስሜታዊ ቢሆኑ ምን ሊፈጠር ይችላል?” የሚለው እንደሆነ ይገልፃል፡፡ የሚያሰጋን ነገር ካለ ማለማችን እየታወቀን ባለው ህልም ላይ ነገሩን ብንሞክረው ከስጋታችን ልንላቀቅ እንደምንችልም ግምቱን ያስቀምጣል፡፡ በዚህም መሰረት ህልም ላይ ካለ ሰው ጋራ የሚደረግ ውይይት እንደ ጭንቀት፣ ስጋት እና መሰል የጤና ችግሮች ያሉበት ሰው የተሻለ እንቅልፍ እንዲተኛ ሊረዳው እንደሚችል ተስፋ አድርጓል፡፡
ምንጭ፡ New Scientist
ውድ የፔጃችን ቤተሰቦች አዳዲስ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ነክ መረጃዎችን በየቀኑ ለማግኝት የፔጃችን ተከታይ ይሁኑ፤
በሌሎች አማራጪች ሊያገኙን ከፈለጉም እነዚህን ይጠቀሙ
ድረ-ገፅ http://www.techin.gov.et/
ዩትዩብ youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg
ትዊተር twitter.com/TechinEthiopia