የቢትኮይን ዋጋ ለመጀመሪያ ጊዜ 50,000 ዶላር ደርሷል
=======================
ባለፉት ሁለት እና ሶስት አመታት ዋጋው አሽቆልቁሎ የነበረው ቢትኮይን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከፍተኛ ሁኔታ ወጋው እየጨመረ መምጣቱ ተነግሯል፡፡ የፈረንጆቹ አዲስ አመት ከገባ ጀምሮ አንዱ የቢትኮይን ዋጋ 32,149 ዶላር ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ይህ ዋጋ በቀጣዮቹ ጊዜያት ይበልጥ ጨምሮ በትናትናው ዕለት ከ50,000 ዶላር በላይ በማውጣት እስከዛሬ ያልታየ ሪከርድ ሰብሯል፡፡
የቢትኮይን ዋጋ እንዲህ ለመጨመሩ ዋና ምክንያት ተደርጎ የተወሰደው እንደ ቴስላ፣ ማስተርካርድ እና ቢ ኤን ዋይ ሜሎን ያሉ ግዙፍ ኩባንያዎች ታዋቂውን ክሪፕቶከረንሲ በከፍተኛ ሁኔታ በመግዛታቸው እና ሌሎች ትልልቅ ድርጅቶችም የክፍያ ስርዓታቸውን ወደዚህ የቢትኮይን አሰራር እየቀየሩ በመምጣታቸው ነው ተብሏል፡፡ ለአብነት ኤለን መስክ የሚመራው ቴስላ በአክስዮን ገበያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ካላቸው ኩባንያዎች በቀዳሚነተ የሚቀመጥ ሲሆን ይህ ኩባንያ በቅርቡ 1.5 በሊዮን ቢትኮይን ከመግዛቱም ባለፈ አንዳንድ ምርቶቹን በዚህ የክሪፕቶከረንሲ ለመገበያየት ማቀዱ የቢትኮይንን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንደጨመረው ተገልጿል፡፡
ከዚህ በለፈም ቢ ኤን ዋይ ሜሎን እየተባለ የሚጠራው አንጋፋ የአሜሪካ ባንክ ለቢትኮይን የግብይት ስርዓት ከፍተኛ ይሁንታ እና ድጋፍ ማድረጉ ሌላው ተጨማሪ ምክንያት ሲሆን እንደ ማስተርካርድ እና ማይክሮ ስትራቴጂ ያሉ ግዙፍ የፋይናንስና የቢዝነት ተቋማት በቢትኮይን ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ማካሄደቸው ለክሪፕቶከረንሲው ዋጋ መጨመር ሌሎች ምክንያት ናቸው፡፡ በ2016 ከፍተኛ የዋጋ እድገት የታየበት ቢትኮይን በተያዘው የፈረንጆቹ 2021 አመትም የ 72% ከፍተኛ ጭማሪ እንደሚያስመዘግብ ተነግሯል፡፡
ቢትኮይን የስነ-መሰውር (cryptography) ቴክኖሎጂን የሚጠቅም አንዱ የክሪፕቶከረንሲ ክፍል ሲሆን የብሎክቼን ቴክኖሎጂ ለመጀመሪያ ጊዜ የተተገበረበት እና አዲስ አይነት የዲጂታል ገንዘብ አጠቃቀምን እንዲሁም አከፋፈል ስርዓትን የሚዘረጋ ነፃ ሶፍተዌር ነው፡፡ ቢትኮይን በሁለት ሰው መካከል የዲጅታል፣ የገንዘብና የክፍያ ልውውጥ የሚካሄድበት አቻ ለአቻ (peer-to-peer) አሰራር ሲሆን የክፍያ ስርዓቱ ያለገንዘብ ተቋም ጣልቃገብነት ሊፈፀም ይችላል፡፡
ቢትኮይን መገበያያ እንደሌሎች የክሬፕቶከረንሲ አይነቶች ከልማዳዊው የገንዘብ አሰራር የተለየ ይዘት ያለው ሲሆን በኮምፒውተራችን ላይ ይህ ዲጂታል ገንዘብ ነው ብለን የምንጠቀመው ፋይል ወይም መረጃ የለም፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት ዲጂታል ገንዘቡ በየትኛውም አገር ስላልተፈጠረና በማንኛውም አገራዊ ወይም ዓለም አቀፋዊ የመንግስት ቷቋም ስለማይተዳደር ነው፡፡ የዲጂታል ገንዘብ ልውውጥ ስርዓቱም የሚከናወንባቸው ኮምፒውተሮች በተለያየ የዓለም ክፍል በሚገኙ ግለሰቦች ንብረትነት የሚተዳደሩ ናቸው፡፡ ይሄ አሰራር “distributed computation” የሚባል ሲሆን ዋና ዓላማውና ጥቅሙም የመረጃ ልውውጡና አስተዳደሩ በአንድ ተቋም ስር ሳይወድቅ ለሳይበር ጥቃት የማይመች ማድረግ እና የመረጃ ትክክለኝነቱ “data integrity” ዋስትና እንዲጠበቅ ማድረግ ነው፡፡ የቢትኮይን መገበያያ ቀድመው ከተፈጠሩ የክሬፕቶከረንሲ አይነቶች የመጀመሪያውና ዝነኛው ቢሆንም ከሱ በኋላ ግን ከ1500 በላይ የሚሆኑ የክሬፕቶከረንሲ አይነቶች አንደተፈጠሩ ተረጋግጧል፡፡
ምንጭ፡ Reuters እና Republicworld
=======================
ባለፉት ሁለት እና ሶስት አመታት ዋጋው አሽቆልቁሎ የነበረው ቢትኮይን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በከፍተኛ ሁኔታ ወጋው እየጨመረ መምጣቱ ተነግሯል፡፡ የፈረንጆቹ አዲስ አመት ከገባ ጀምሮ አንዱ የቢትኮይን ዋጋ 32,149 ዶላር ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ይህ ዋጋ በቀጣዮቹ ጊዜያት ይበልጥ ጨምሮ በትናትናው ዕለት ከ50,000 ዶላር በላይ በማውጣት እስከዛሬ ያልታየ ሪከርድ ሰብሯል፡፡
የቢትኮይን ዋጋ እንዲህ ለመጨመሩ ዋና ምክንያት ተደርጎ የተወሰደው እንደ ቴስላ፣ ማስተርካርድ እና ቢ ኤን ዋይ ሜሎን ያሉ ግዙፍ ኩባንያዎች ታዋቂውን ክሪፕቶከረንሲ በከፍተኛ ሁኔታ በመግዛታቸው እና ሌሎች ትልልቅ ድርጅቶችም የክፍያ ስርዓታቸውን ወደዚህ የቢትኮይን አሰራር እየቀየሩ በመምጣታቸው ነው ተብሏል፡፡ ለአብነት ኤለን መስክ የሚመራው ቴስላ በአክስዮን ገበያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ካላቸው ኩባንያዎች በቀዳሚነተ የሚቀመጥ ሲሆን ይህ ኩባንያ በቅርቡ 1.5 በሊዮን ቢትኮይን ከመግዛቱም ባለፈ አንዳንድ ምርቶቹን በዚህ የክሪፕቶከረንሲ ለመገበያየት ማቀዱ የቢትኮይንን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንደጨመረው ተገልጿል፡፡
ከዚህ በለፈም ቢ ኤን ዋይ ሜሎን እየተባለ የሚጠራው አንጋፋ የአሜሪካ ባንክ ለቢትኮይን የግብይት ስርዓት ከፍተኛ ይሁንታ እና ድጋፍ ማድረጉ ሌላው ተጨማሪ ምክንያት ሲሆን እንደ ማስተርካርድ እና ማይክሮ ስትራቴጂ ያሉ ግዙፍ የፋይናንስና የቢዝነት ተቋማት በቢትኮይን ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ማካሄደቸው ለክሪፕቶከረንሲው ዋጋ መጨመር ሌሎች ምክንያት ናቸው፡፡ በ2016 ከፍተኛ የዋጋ እድገት የታየበት ቢትኮይን በተያዘው የፈረንጆቹ 2021 አመትም የ 72% ከፍተኛ ጭማሪ እንደሚያስመዘግብ ተነግሯል፡፡
ቢትኮይን የስነ-መሰውር (cryptography) ቴክኖሎጂን የሚጠቅም አንዱ የክሪፕቶከረንሲ ክፍል ሲሆን የብሎክቼን ቴክኖሎጂ ለመጀመሪያ ጊዜ የተተገበረበት እና አዲስ አይነት የዲጂታል ገንዘብ አጠቃቀምን እንዲሁም አከፋፈል ስርዓትን የሚዘረጋ ነፃ ሶፍተዌር ነው፡፡ ቢትኮይን በሁለት ሰው መካከል የዲጅታል፣ የገንዘብና የክፍያ ልውውጥ የሚካሄድበት አቻ ለአቻ (peer-to-peer) አሰራር ሲሆን የክፍያ ስርዓቱ ያለገንዘብ ተቋም ጣልቃገብነት ሊፈፀም ይችላል፡፡
ቢትኮይን መገበያያ እንደሌሎች የክሬፕቶከረንሲ አይነቶች ከልማዳዊው የገንዘብ አሰራር የተለየ ይዘት ያለው ሲሆን በኮምፒውተራችን ላይ ይህ ዲጂታል ገንዘብ ነው ብለን የምንጠቀመው ፋይል ወይም መረጃ የለም፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት ዲጂታል ገንዘቡ በየትኛውም አገር ስላልተፈጠረና በማንኛውም አገራዊ ወይም ዓለም አቀፋዊ የመንግስት ቷቋም ስለማይተዳደር ነው፡፡ የዲጂታል ገንዘብ ልውውጥ ስርዓቱም የሚከናወንባቸው ኮምፒውተሮች በተለያየ የዓለም ክፍል በሚገኙ ግለሰቦች ንብረትነት የሚተዳደሩ ናቸው፡፡ ይሄ አሰራር “distributed computation” የሚባል ሲሆን ዋና ዓላማውና ጥቅሙም የመረጃ ልውውጡና አስተዳደሩ በአንድ ተቋም ስር ሳይወድቅ ለሳይበር ጥቃት የማይመች ማድረግ እና የመረጃ ትክክለኝነቱ “data integrity” ዋስትና እንዲጠበቅ ማድረግ ነው፡፡ የቢትኮይን መገበያያ ቀድመው ከተፈጠሩ የክሬፕቶከረንሲ አይነቶች የመጀመሪያውና ዝነኛው ቢሆንም ከሱ በኋላ ግን ከ1500 በላይ የሚሆኑ የክሬፕቶከረንሲ አይነቶች አንደተፈጠሩ ተረጋግጧል፡፡
ምንጭ፡ Reuters እና Republicworld
የኮቪድ-19 ክትባትን ባንከተብስ? ምን ይመጣብናል?
====================
እንደ ታንዛኒያ እና ማዳጋስካር ያሉ ሀገራት ህዝባቸውን በኮቪድ-19 መከላከያ ክትባቶች የመከተብ ዕቅድ እንደሌላቸው አሳውቀዋል፡፡ በግለሰብ ደረጃም ክትባቱን መውሰድ የማይፈልጉ ሰዎች መኖራቸውን ሰምተን ይሆናል፡፡ ግን እንደዚህ አይነት እርምጃዎች ምን ሊያመጡ ይችላሉ?
ያን ያህል የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባትን ያልወሰዱ ዜጎች ባሉባት ሀገር ውስጥ የወረርሺኙ ቆይታ የመርዘሙ ዕድል የሰፋ ይሆናል፡፡ ቫይረሱ በዘላቂነት ማህበረሰቡን እያጠቃ የሚቆይበት ጊዜ በተራዘመ ቁጥር ደግሞ ቫይረሱም ይበልጥ እራሱን እየለወጠ ይመጣል፡፡ ይህ መለወጥ (mutation) ደግሞ ይበልጡን አደገኛ ለሆኑ የሳርስ-ኮቭ-2 አይነቶች ምቹ መፈልፈያን ሊፈጥር ይችላል፡፡ በበራሒ ኮዳቸው ላይ ለውጦችን አድርገው ብቅ የሚሉት አዳዲሶቹ የኮሮና ቫይረስ አይነቶች በበኩላቸው ቀድሞ ክትባቱን የወሰዱት ሰዎችን ጭምር የማጥቃት አቅምን የማዳበር ዕድል አላቸው፡፡ ክትባት አንድ የቫይረስ አይነትን ሰውነታችን እንዲያውቀው በማድረግ የበሽታ መከላከል ስርዓቱን እንዲቀሰቅስ ማድረጊያ ነውና ቫይረሱ ሲለወጥ ያለመታወቅ እድሉን ይጨምረዋል፡፡ በዚህ አኳሀን አብዛኛው ህዝብ የተከተበባቸው አካባቢዎች እንኳን ሌላ ቦታ ላይ አይነቱን በለወጠ ምናልባትም ከቀድሞው የበለጠ ተላላፊና ገዳይ በሆነ ቫይረስ ይጠቃሉ፡፡ ምድራችን ላይ ማንም ለብቻው ተከልሎ አለመገኘቱን ስናስብ ደግሞ ሁላችንም ክትባቱን ካላገኘን አንዳችንም ደህንነታችን በብቸኝነት ጠብቀን መኖር እንደማንችል እንረዳለን፡፡
ታድያ መፍትሄው ምንድነው?
ከዚህ ችግር ለመዳን መንግስታት ዜጎቻቸውን ከከተቡ በኋላ ድንበራቸውን ዘግቶ መቀመጡ ቀላል ነገር ስለማይሆን ከዚህ ይልቅ ክትባቶቹን በተቻለ ፍጥነት ለሁሉም ሀገራት ዜጎች ማዳረስ ቀዳሚው መፍትሄ ነው፡፡ አሁን ላይ በቫይረሱ የተያዘን ሰው የሚያድኑ ምንም አይነት መድሃኒቶች ስለሌሉም ክትባቱን የማዳረሱ እንቅስቃሴ በፍጥነት መከናወን ይኖርበታል፡፡ ይህን ቶሎ ማሳካት እንዲቻል መንግስታት ክትባቶቹን በማምረት እና ለሁሉም በማዳረስ ረገድ በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ ለክትባቶቹ አምራቾች የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍም ሊያድግና ተጨማሪ ሌሎች ማምረቻዎችም በማደግ ላይ ባሉት ሀገራት ጭምር ሊከፈቱ ይገባል፡፡ ይህም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ጭምር የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡
ታድያ በርካታ ሀገራት ክትባቶቹን ለማግኘት ገና እየተጠባበቁ በመሆናቸው ወረርሺኙ ከተነሳበት ጊዜ አንስቶ ሲተገበሩ የቆዩትን እንደ ማስክ ማድረግ እና አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ያሉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መከወኑ ቢያንስ በአንድ ማህበረሰብ ውስጥም ሆነ ከአንድ ማህበረሰብ ወደ ሌላ ማህበረሰብ የሚኖረውን የቫይረሱን የስርጭት ይቀንሰዋል፤ ወደ ሆስፒታል የሚያመራውን እና ህይወቱን የሚያጣውን ሰው ቁጥርንም ያወርደዋል፡፡ በተጨማሪም በአንድ አካባቢ ከፍ ያለ ስርጭት መኖሩን የሚያሳይ መረጃ ሲገኝ አካባቢው ላይ የእንቅስቃሴ ገደቦችን ማድረግ ይገባል፡፡
በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን የተጠቂ መጠን በምርመራ መለየቱና የቫይረሱን በራሒ በቤተ-ሙከራ እየመረመሩ መከታተሉ ቀዳሚው ነገሮችን መረዳት የሚያስችል መንገድ ነው፡፡
ምንጭ፡ The Conversation
====================
እንደ ታንዛኒያ እና ማዳጋስካር ያሉ ሀገራት ህዝባቸውን በኮቪድ-19 መከላከያ ክትባቶች የመከተብ ዕቅድ እንደሌላቸው አሳውቀዋል፡፡ በግለሰብ ደረጃም ክትባቱን መውሰድ የማይፈልጉ ሰዎች መኖራቸውን ሰምተን ይሆናል፡፡ ግን እንደዚህ አይነት እርምጃዎች ምን ሊያመጡ ይችላሉ?
ያን ያህል የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባትን ያልወሰዱ ዜጎች ባሉባት ሀገር ውስጥ የወረርሺኙ ቆይታ የመርዘሙ ዕድል የሰፋ ይሆናል፡፡ ቫይረሱ በዘላቂነት ማህበረሰቡን እያጠቃ የሚቆይበት ጊዜ በተራዘመ ቁጥር ደግሞ ቫይረሱም ይበልጥ እራሱን እየለወጠ ይመጣል፡፡ ይህ መለወጥ (mutation) ደግሞ ይበልጡን አደገኛ ለሆኑ የሳርስ-ኮቭ-2 አይነቶች ምቹ መፈልፈያን ሊፈጥር ይችላል፡፡ በበራሒ ኮዳቸው ላይ ለውጦችን አድርገው ብቅ የሚሉት አዳዲሶቹ የኮሮና ቫይረስ አይነቶች በበኩላቸው ቀድሞ ክትባቱን የወሰዱት ሰዎችን ጭምር የማጥቃት አቅምን የማዳበር ዕድል አላቸው፡፡ ክትባት አንድ የቫይረስ አይነትን ሰውነታችን እንዲያውቀው በማድረግ የበሽታ መከላከል ስርዓቱን እንዲቀሰቅስ ማድረጊያ ነውና ቫይረሱ ሲለወጥ ያለመታወቅ እድሉን ይጨምረዋል፡፡ በዚህ አኳሀን አብዛኛው ህዝብ የተከተበባቸው አካባቢዎች እንኳን ሌላ ቦታ ላይ አይነቱን በለወጠ ምናልባትም ከቀድሞው የበለጠ ተላላፊና ገዳይ በሆነ ቫይረስ ይጠቃሉ፡፡ ምድራችን ላይ ማንም ለብቻው ተከልሎ አለመገኘቱን ስናስብ ደግሞ ሁላችንም ክትባቱን ካላገኘን አንዳችንም ደህንነታችን በብቸኝነት ጠብቀን መኖር እንደማንችል እንረዳለን፡፡
ታድያ መፍትሄው ምንድነው?
ከዚህ ችግር ለመዳን መንግስታት ዜጎቻቸውን ከከተቡ በኋላ ድንበራቸውን ዘግቶ መቀመጡ ቀላል ነገር ስለማይሆን ከዚህ ይልቅ ክትባቶቹን በተቻለ ፍጥነት ለሁሉም ሀገራት ዜጎች ማዳረስ ቀዳሚው መፍትሄ ነው፡፡ አሁን ላይ በቫይረሱ የተያዘን ሰው የሚያድኑ ምንም አይነት መድሃኒቶች ስለሌሉም ክትባቱን የማዳረሱ እንቅስቃሴ በፍጥነት መከናወን ይኖርበታል፡፡ ይህን ቶሎ ማሳካት እንዲቻል መንግስታት ክትባቶቹን በማምረት እና ለሁሉም በማዳረስ ረገድ በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል፡፡ ለክትባቶቹ አምራቾች የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍም ሊያድግና ተጨማሪ ሌሎች ማምረቻዎችም በማደግ ላይ ባሉት ሀገራት ጭምር ሊከፈቱ ይገባል፡፡ ይህም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ጭምር የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡
ታድያ በርካታ ሀገራት ክትባቶቹን ለማግኘት ገና እየተጠባበቁ በመሆናቸው ወረርሺኙ ከተነሳበት ጊዜ አንስቶ ሲተገበሩ የቆዩትን እንደ ማስክ ማድረግ እና አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ያሉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መከወኑ ቢያንስ በአንድ ማህበረሰብ ውስጥም ሆነ ከአንድ ማህበረሰብ ወደ ሌላ ማህበረሰብ የሚኖረውን የቫይረሱን የስርጭት ይቀንሰዋል፤ ወደ ሆስፒታል የሚያመራውን እና ህይወቱን የሚያጣውን ሰው ቁጥርንም ያወርደዋል፡፡ በተጨማሪም በአንድ አካባቢ ከፍ ያለ ስርጭት መኖሩን የሚያሳይ መረጃ ሲገኝ አካባቢው ላይ የእንቅስቃሴ ገደቦችን ማድረግ ይገባል፡፡
በማህበረሰቡ ውስጥ ያለውን የተጠቂ መጠን በምርመራ መለየቱና የቫይረሱን በራሒ በቤተ-ሙከራ እየመረመሩ መከታተሉ ቀዳሚው ነገሮችን መረዳት የሚያስችል መንገድ ነው፡፡
ምንጭ፡ The Conversation
እናት የሁሉም ነገር መድሃኒት
*******************
በዓለማችን ላይ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ወረርሽኞች ተከስተው ጥቂት የማይባሉ ሰዎችን ቀጥፈዋል፡፡ ሞትና የተለየዩ ምክንያቶች የብዙ ፍጥረታትን ህልውና በተለያዩ ጊዜያት አደጋ ላይ ጥለዋል፡፡ ለዚህም ነው በአሁኑ ሰዓት ሊጠፉ የተቃረቡ የሚባሉ ፍጥረታት ያሉን፡፡ ከጥንት ጀምሮ የሰው ልጅን በጅምላም ሆነ በተናጥል ህይወቱን የሚቀጥፉ አጋጣሚዎች ቢፈጠሩም የሰዎች ቁጥር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይስተዋልም፡፡ ለዚህ ነው እናት ‹መውለድ› የሚባል የሞት መድሃኒት አላት የሚባለው፡፡
አለማችን አሁንም በወረርሽኝ ላይ በመሆኗ የተሻለ መድሃኒት ፍለጋ ላይ ናት፡፡ በብዙ ጥረቶች የተወሰኑ መድሃኒቶች ቢገኙም የፍትሀዊነት ጉዳይ ግን በጥያቄ ውስጥ ያለ ነው፡፡ ምርምሮች አሁንም እየተደረጉ ሲሆን አሁን ተገኘ የተባለው አዲስ መረጃ ግን ወደ ዘጠኝ ወር ቤታችን፣ የልጅነት ምግባችን እንዲሁም የእድሜ ዘመን ወዳጃችን ወደ ሆነችው ውዷ እናት የሚወስድ ሆኗል፡፡
በሮችስተር የህክምና ማዕከል የተሰራ አንድ ጥናት ጡት ማጥባት የኮቪድ ቫይረስን እንደማያስተላልፍና ይልቁንም ህጻናት ቫይረሱን መቋቋም የሚችሉበትን አቅም እንደሚሰጣቸው አመልክቷል፡፡ በጥናቱም ከ18 በኪቪድ የተያዙ እናቶች የተወሰደ 37 የጡት ወተት ናሙና ውስጥ በአንዱም ቫይረሱ እንዳልተገኘ እና ይልቁንም በተወሰኑ ናሙናዎች ለቫይረሱ የሚሆኑ አንቲ ቦዲ ተገኝቶባቸዋል፡፡
በዚህም በኮቪድ 19 የተጠቁ እናቶች ከጨቅላ ልጆቻቸው መለየት እንደሌለባቸው ጥናቱ አመላክቷል፡፡ ባሳለፍናቸው ወራቶች የተለያዩ የጤና ተቋማት በጉዳዩ ዙሪያ አሻሚ መረጃዎችን ሲሰጡ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ ለጥናቱም ቢልና ሚሊንዳ ጌትስ የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት 130 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ፈሰስ አድርጓል፡፡
ምንጭ Technology.org
*******************
በዓለማችን ላይ በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ወረርሽኞች ተከስተው ጥቂት የማይባሉ ሰዎችን ቀጥፈዋል፡፡ ሞትና የተለየዩ ምክንያቶች የብዙ ፍጥረታትን ህልውና በተለያዩ ጊዜያት አደጋ ላይ ጥለዋል፡፡ ለዚህም ነው በአሁኑ ሰዓት ሊጠፉ የተቃረቡ የሚባሉ ፍጥረታት ያሉን፡፡ ከጥንት ጀምሮ የሰው ልጅን በጅምላም ሆነ በተናጥል ህይወቱን የሚቀጥፉ አጋጣሚዎች ቢፈጠሩም የሰዎች ቁጥር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይስተዋልም፡፡ ለዚህ ነው እናት ‹መውለድ› የሚባል የሞት መድሃኒት አላት የሚባለው፡፡
አለማችን አሁንም በወረርሽኝ ላይ በመሆኗ የተሻለ መድሃኒት ፍለጋ ላይ ናት፡፡ በብዙ ጥረቶች የተወሰኑ መድሃኒቶች ቢገኙም የፍትሀዊነት ጉዳይ ግን በጥያቄ ውስጥ ያለ ነው፡፡ ምርምሮች አሁንም እየተደረጉ ሲሆን አሁን ተገኘ የተባለው አዲስ መረጃ ግን ወደ ዘጠኝ ወር ቤታችን፣ የልጅነት ምግባችን እንዲሁም የእድሜ ዘመን ወዳጃችን ወደ ሆነችው ውዷ እናት የሚወስድ ሆኗል፡፡
በሮችስተር የህክምና ማዕከል የተሰራ አንድ ጥናት ጡት ማጥባት የኮቪድ ቫይረስን እንደማያስተላልፍና ይልቁንም ህጻናት ቫይረሱን መቋቋም የሚችሉበትን አቅም እንደሚሰጣቸው አመልክቷል፡፡ በጥናቱም ከ18 በኪቪድ የተያዙ እናቶች የተወሰደ 37 የጡት ወተት ናሙና ውስጥ በአንዱም ቫይረሱ እንዳልተገኘ እና ይልቁንም በተወሰኑ ናሙናዎች ለቫይረሱ የሚሆኑ አንቲ ቦዲ ተገኝቶባቸዋል፡፡
በዚህም በኮቪድ 19 የተጠቁ እናቶች ከጨቅላ ልጆቻቸው መለየት እንደሌለባቸው ጥናቱ አመላክቷል፡፡ ባሳለፍናቸው ወራቶች የተለያዩ የጤና ተቋማት በጉዳዩ ዙሪያ አሻሚ መረጃዎችን ሲሰጡ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ ለጥናቱም ቢልና ሚሊንዳ ጌትስ የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት 130 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ፈሰስ አድርጓል፡፡
ምንጭ Technology.org
ኮካ ኮላ የመጀመሪያውን የወረቀት ማሸጊያ ሊሞክር ነው
====================
በአለማችን ላይ የተፈጥሮን ሚዛን በማዛባት ትልቅ ችግር ከሚፈጥሩ ምክንያቶች መካከል የፕላስቲክ ብክለት አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በዚህ አለም አቀፍ ችግር ከፍተኛ የፕላስቲክ ገብዓት ጥቅም ላይ በማዋል የፕላስቲክ ብክለቱ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨመር ከሚያደርጉ ግዙፍ ተቋማት ውስጥ ደግሞ የኮካ ኮላ ኩባንያ በቀዳሚነት የሚቀመጥ ነው፡፡ በቅርቡ Break Free From Plastic የተሰኘው አለም አቀፍ ንቅናቄ ባዘጋጀው አመታዊ የደሰሳ ጥናት ላይ የኮካ ኮላ ኩባንያ ከየትኛውም አለም አቀፍ ተቋም በላይ ለፕላስቲክ ብክለት የመጀመሪያውን ደረጃ እንደሚወስድ አስታውቆ ነበር፡፡
በተፈጥሮ ላይ ከፍተኛ አደጋን በሚጠራው በዚህ አለም አቀፍ ችግር ላይ ትልቅ ድርሻን የሚወስደው የኮካ ኮላ ኩባንያ ይህን አደጋ በሚቀንስ መልኩ ወደፊት ለሚኖረው የምርት ግብዓት የመጀመሪያውን የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙስ ለመሞከር በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ከሰሞኑ በኩባንያው ድረ-ገፅ ላይ እንደተገለፀው ድርጅቱ በተያዘው የፈረንጆች አመት 2,000 የሚጠጉ የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙሶችን በፕሮቶታይፕ ደረጃ በማዘጋጀት የንድፋቸውን ውጤታማነት ለመገምገም እንደሚሞክር ተጠቅሷል፡፡ ኩባንያው ይህን የፕሮቶታይብ ሙከራ በዴንማርክ መቀመጫውን ካደረገ ፓባኮ ከተባለ የምርምር ተቋም ጋር የሚካሂድ ሲሆን፤ በሚኖራቸው የሙከራ ሂደትም አዴዝ በተባለ የአትክልት ጭማቂ ላይ በሚሰራ ተቋም ጋር በጋራ በመሆን የተጠቃሚዎችን እርካታ የሚገመግምሙ ይሆናል፡፡
የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙስ ለአለማችን አዲስ የማሸጊያ (packaging) አመራጭ ነው የሚሉት በአውሮፓ የኮካ ኮላ ኢኖቬሽን ማናጀር ስቴን ፍራንሰን ይህን ለመተግበር የምናደርገው ጥረትም ለወደፊቱ የአለማችን የአከባቢ ጥበቃ መልካም ተፅዕኖ እንደሚኖረው እናምናለን ይላሉ፡፡ አሁን በሙከራ ላይ የሚገኘው የወረቀት ጠርሙስ በተወሰነ መልኩ የፕላስቲክ ግብዓት ቢኖረውም በዘላቂነት ግን እንደማንኛውም የወረቀት አይነት መልሶ ጥቅም ላይ የሚውል የወረቀት ማሸጊያ ሊሰራ እንደታሰበ የኩባንያው ማናጀር ስቴን ፍራንሰን ይናገራሉ፡፡
ባለሙያዎች እንደሚገለፁት ይህ የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙስ የመጠቀም እንቅሰቃሴ ለአለማችን የአካባቢ ጥበቃ መልካም ነግር ይዞ በሚጣም በቶሎ ለመተግበር ከባድ ከሚያደርጉት ምክንያቶች መካከል በካርቦን የተሞሉ ማንኛውም መጠቶች (carbonated beverage) በከፍተኛ ግፊት እንዲታሸጉ ከማስፈለጋቸው አንጻር በወረቀት ጠርሙስ የሚከናወነው ይህ የማሸግ ስራ ከባድ ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች የተነሳ በተጠቃሚዎች ጤና ላይ መጠነኛ ተፅዕኖ ሊኖረው ስለሚችልም በዘርፉ የሚደረገው ረዥም የምርምር ሂደት እጅግ ወሳኝ ነው፡፡ ኩባንያው ይህን የሙከራ እንቅሰቃሴ ሲጀምር ረዥም ጊዜ የሚወስድ የምርምር ሂደት እንደሚያከናውን ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ ምንጭ፡ CTV NEWS
====================
በአለማችን ላይ የተፈጥሮን ሚዛን በማዛባት ትልቅ ችግር ከሚፈጥሩ ምክንያቶች መካከል የፕላስቲክ ብክለት አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በዚህ አለም አቀፍ ችግር ከፍተኛ የፕላስቲክ ገብዓት ጥቅም ላይ በማዋል የፕላስቲክ ብክለቱ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨመር ከሚያደርጉ ግዙፍ ተቋማት ውስጥ ደግሞ የኮካ ኮላ ኩባንያ በቀዳሚነት የሚቀመጥ ነው፡፡ በቅርቡ Break Free From Plastic የተሰኘው አለም አቀፍ ንቅናቄ ባዘጋጀው አመታዊ የደሰሳ ጥናት ላይ የኮካ ኮላ ኩባንያ ከየትኛውም አለም አቀፍ ተቋም በላይ ለፕላስቲክ ብክለት የመጀመሪያውን ደረጃ እንደሚወስድ አስታውቆ ነበር፡፡
በተፈጥሮ ላይ ከፍተኛ አደጋን በሚጠራው በዚህ አለም አቀፍ ችግር ላይ ትልቅ ድርሻን የሚወስደው የኮካ ኮላ ኩባንያ ይህን አደጋ በሚቀንስ መልኩ ወደፊት ለሚኖረው የምርት ግብዓት የመጀመሪያውን የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙስ ለመሞከር በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ከሰሞኑ በኩባንያው ድረ-ገፅ ላይ እንደተገለፀው ድርጅቱ በተያዘው የፈረንጆች አመት 2,000 የሚጠጉ የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙሶችን በፕሮቶታይፕ ደረጃ በማዘጋጀት የንድፋቸውን ውጤታማነት ለመገምገም እንደሚሞክር ተጠቅሷል፡፡ ኩባንያው ይህን የፕሮቶታይብ ሙከራ በዴንማርክ መቀመጫውን ካደረገ ፓባኮ ከተባለ የምርምር ተቋም ጋር የሚካሂድ ሲሆን፤ በሚኖራቸው የሙከራ ሂደትም አዴዝ በተባለ የአትክልት ጭማቂ ላይ በሚሰራ ተቋም ጋር በጋራ በመሆን የተጠቃሚዎችን እርካታ የሚገመግምሙ ይሆናል፡፡
የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙስ ለአለማችን አዲስ የማሸጊያ (packaging) አመራጭ ነው የሚሉት በአውሮፓ የኮካ ኮላ ኢኖቬሽን ማናጀር ስቴን ፍራንሰን ይህን ለመተግበር የምናደርገው ጥረትም ለወደፊቱ የአለማችን የአከባቢ ጥበቃ መልካም ተፅዕኖ እንደሚኖረው እናምናለን ይላሉ፡፡ አሁን በሙከራ ላይ የሚገኘው የወረቀት ጠርሙስ በተወሰነ መልኩ የፕላስቲክ ግብዓት ቢኖረውም በዘላቂነት ግን እንደማንኛውም የወረቀት አይነት መልሶ ጥቅም ላይ የሚውል የወረቀት ማሸጊያ ሊሰራ እንደታሰበ የኩባንያው ማናጀር ስቴን ፍራንሰን ይናገራሉ፡፡
ባለሙያዎች እንደሚገለፁት ይህ የወረቀት ማሸጊያ ጠርሙስ የመጠቀም እንቅሰቃሴ ለአለማችን የአካባቢ ጥበቃ መልካም ነግር ይዞ በሚጣም በቶሎ ለመተግበር ከባድ ከሚያደርጉት ምክንያቶች መካከል በካርቦን የተሞሉ ማንኛውም መጠቶች (carbonated beverage) በከፍተኛ ግፊት እንዲታሸጉ ከማስፈለጋቸው አንጻር በወረቀት ጠርሙስ የሚከናወነው ይህ የማሸግ ስራ ከባድ ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች የተነሳ በተጠቃሚዎች ጤና ላይ መጠነኛ ተፅዕኖ ሊኖረው ስለሚችልም በዘርፉ የሚደረገው ረዥም የምርምር ሂደት እጅግ ወሳኝ ነው፡፡ ኩባንያው ይህን የሙከራ እንቅሰቃሴ ሲጀምር ረዥም ጊዜ የሚወስድ የምርምር ሂደት እንደሚያከናውን ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ ምንጭ፡ CTV NEWS
ፌስቡክ በአውስትራሊያ የጣለው የዜና ተደራሽነት እገዳ
****************************
ፌስቡክ አውስትራሊያውያን በፕላት ፎርሙ ዜናዎችን እንዳያገኙ ማገዱን አሳወቀ፡፡ እንደ ማህበራዊ ሚዲያው መረጃ ከሆነ እገዳው የተጣለው በሃገሪቱ ዲጂታል ማሰራጫዎች ለሚያሰራጩት መረጃ እንዲከፍሉ የሚጠይቅ ረቂቅ ህግ መውጣቱን ተከትሎ ነው፡፡ ድርጅቱ አክሎም በአውስትራሊያ የሚገኙ መረጃ አሰራጮች መረጃ ማውጣታቸው ያልተቋረጠ ሲሆን መረጃዎቻቸውና ሊንኮቻቸው በፌስቡክ አማካኝነት ለአውስትራሊያውያን ተደራሽ አይሆኑም ብሏል፡፡
በዚህ እገዳ ምክንያት በአውስትራሊያ የሚገኙ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች የሀገር ውስጥ ወይም አለማቀፍ መረጃዎችን የማያገኙ ሲሆን ከአውስትራሊያ ውጭ ያሉ ተጠቃሚዎች ደግሞ ምንጫቸውን በአውስትራሊያ ያደረጉ መረጃዎችን ማግኘት አይችሉም፡፡ የፌስቡክ አካባቢያዊ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆኑት ዊሊያም ኢስቶን ረቂቅ ህጉ በፌስቡክ እና ፕላትፎርሙን በሚጠቀሙ የዜና ማሰራጫዎች መካከል ያለውን ግንኙነት ያልተረዳ ነው ሲሉ ትችታቸውን አቅርበዋል፡፡ ዳይሩክተሩ አክለውም በዚህ ሁኔታውን ባልተረዳ ህግ ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡና የዜና ይዘት ያላቸውን መረጃዎች ላማገድ እንደተገደዱ ተናግረዋል፡፡
ይህ መረጃም የወጣው ፌስቡክና ጎግል ከአውስትራሊያ የሚዲያ ተቋማት ጋር ተስፋ ሰጭ ስምምነት ላይ እንደደረሱ ከተነገረ በኋላ ነው፡፡ ፌስቡክ አሁን አንዳንድ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሆነ ቢገልጽም የአውስትራሊያው ኮሚኒኬሽን ሚኒስቴር ፓውል ፍሌቸር ግን ከህግ ማስከበር ጋር በተያያዙ ጉዳዩች መንግስታቸው ወደኋላ እንደማይመለስ ተናግረዋል፡፡ ሚንስትሩ አክለውም ፌስቡክ ስራውን መልሶ ማግኘት ከፈለገ በፕላትፎርሙ ላይ በሚያወጣቸው ዜናዎች ዙሪያ ታማኝነቱን ማሳየት አለበት ብለዋል፡፡
በረቂቅ ህጉ ዙሪያ የአውስትራሊያ ፓርላማ እየመከረበት ሲሆን ሴኔቱም እንደሚመለከተው እየተጠበቀ ነው፡፡ በዚህ ረቂቅ ህግ አብሮ እየተከራከረ ያለው ጎግልም የመረጃ መፈለጊያ ፕላትፎርሙን ከአውስትራሊያ ሊያነሳ ይችላል ተብሏል፡፡
ምንጭ: Tech Xplore
****************************
ፌስቡክ አውስትራሊያውያን በፕላት ፎርሙ ዜናዎችን እንዳያገኙ ማገዱን አሳወቀ፡፡ እንደ ማህበራዊ ሚዲያው መረጃ ከሆነ እገዳው የተጣለው በሃገሪቱ ዲጂታል ማሰራጫዎች ለሚያሰራጩት መረጃ እንዲከፍሉ የሚጠይቅ ረቂቅ ህግ መውጣቱን ተከትሎ ነው፡፡ ድርጅቱ አክሎም በአውስትራሊያ የሚገኙ መረጃ አሰራጮች መረጃ ማውጣታቸው ያልተቋረጠ ሲሆን መረጃዎቻቸውና ሊንኮቻቸው በፌስቡክ አማካኝነት ለአውስትራሊያውያን ተደራሽ አይሆኑም ብሏል፡፡
በዚህ እገዳ ምክንያት በአውስትራሊያ የሚገኙ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች የሀገር ውስጥ ወይም አለማቀፍ መረጃዎችን የማያገኙ ሲሆን ከአውስትራሊያ ውጭ ያሉ ተጠቃሚዎች ደግሞ ምንጫቸውን በአውስትራሊያ ያደረጉ መረጃዎችን ማግኘት አይችሉም፡፡ የፌስቡክ አካባቢያዊ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆኑት ዊሊያም ኢስቶን ረቂቅ ህጉ በፌስቡክ እና ፕላትፎርሙን በሚጠቀሙ የዜና ማሰራጫዎች መካከል ያለውን ግንኙነት ያልተረዳ ነው ሲሉ ትችታቸውን አቅርበዋል፡፡ ዳይሩክተሩ አክለውም በዚህ ሁኔታውን ባልተረዳ ህግ ምክንያት አጣብቂኝ ውስጥ እንደገቡና የዜና ይዘት ያላቸውን መረጃዎች ላማገድ እንደተገደዱ ተናግረዋል፡፡
ይህ መረጃም የወጣው ፌስቡክና ጎግል ከአውስትራሊያ የሚዲያ ተቋማት ጋር ተስፋ ሰጭ ስምምነት ላይ እንደደረሱ ከተነገረ በኋላ ነው፡፡ ፌስቡክ አሁን አንዳንድ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሆነ ቢገልጽም የአውስትራሊያው ኮሚኒኬሽን ሚኒስቴር ፓውል ፍሌቸር ግን ከህግ ማስከበር ጋር በተያያዙ ጉዳዩች መንግስታቸው ወደኋላ እንደማይመለስ ተናግረዋል፡፡ ሚንስትሩ አክለውም ፌስቡክ ስራውን መልሶ ማግኘት ከፈለገ በፕላትፎርሙ ላይ በሚያወጣቸው ዜናዎች ዙሪያ ታማኝነቱን ማሳየት አለበት ብለዋል፡፡
በረቂቅ ህጉ ዙሪያ የአውስትራሊያ ፓርላማ እየመከረበት ሲሆን ሴኔቱም እንደሚመለከተው እየተጠበቀ ነው፡፡ በዚህ ረቂቅ ህግ አብሮ እየተከራከረ ያለው ጎግልም የመረጃ መፈለጊያ ፕላትፎርሙን ከአውስትራሊያ ሊያነሳ ይችላል ተብሏል፡፡
ምንጭ: Tech Xplore
የትንፋሻችን ድምፅ ስንተኛ ለምን ይጨምራል?
====================
አንዳንድ ሰዎች በእንቅልፍ ሰዓት የሌሎችን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ ያንኮራፋሉ፡፡ ሆኖም ሰዎች ባያንኮራፉም እንኳን ከፍ ባለ ድምፅ ሲተነፍሱ ይታያል፡፡ ይህ ለምን ይሆናል?
ተኝተንም ሆነ ሳንተኛ በትንፋሽ ወቅት የምናወጣው ድምፅ በአየር መዘዋወርያ ትቦዋችን ውስጥ በሚፈጠር መርገብገብ ሳብያ የሚከሰት መሆኑን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ወደ ውስጥ በምንተነፍስበት ጊዜ ከአፍ እስከ ማንቁርት ድረስ ተዘርግቶ ያለው የላይኛው የአተነፋፈስ ስርዓት ክፍላችን ውስጥ የሚፈጠረው ፈጣን የአየር እንቅስቃሴ በመላው የአተነፋፈስ ስርዓችን ውስጥ ያለውን ግፊት ይቀንሰዋል፡፡ ግፊቱ ይህን የላይኛውን ክፍል ስለሚያኮማትረው ትንፋሽን ሊገድበው ይችላል፡፡
ባልተኛንበት ሰዓት በዚህ ክፍል የሚኖረው እንቅስቃሴ ቱቦውንም ክፍት አሰድርጎ አየር በነፃነት እንደዚዘዋወር አድርጎ የሚያቆይ ይሆናል፡፡ ሆኖም ስንተኛ እንቅስቃሴው በቀድሞ ጥንካሬው ስለማይሆ ክፍሉ የሚኮማተርና የትንፋሻችን ድምፅም እያየለ የሚመጣ ይሆናል፡፡
በእንቅልፍ ሰዓት በትንፋሽ ቱቦው ዙርያ ያሉትን ጡንቻዎች ይላላሉ፡፡ ቱቦው እንዲፍታታ የሚያደርጉት የእነዚህ ጡንቻዎች መላላት ደግሞ ቱቦው እንዲጠብ ያደርገዋል፡፡ የአየር መተላለፊያው ሲጠብ በውስጡ የሚተላለፈው አየር ፍጥነቱ ይጨምራል፡፡ በዚህ ምክንያት አየሩ ይበልጥ ሲርገበገብ ደግሞ የበለጠ ድምፅ የሚፈጥር ይሆናል፡፡ ቱቦው ከዚህም የበለጠ እየጠበበ የሚሄድና ከስትሮ ትንሽ ሰፋ ባለ ጥበት ላይ ሲገኝ ደግሞ ማንኮራፋት ይጀምራል፡፡
በእንቅልፍ ሰዓታችን የትንፋሽ ቱቦው ከማንኮራፋቱ በላይም የሚጠብ ከሆነ መተንፈስን የማይቻል ስለሚያደርገው አየር ፍለጋ እንባንናለን፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ ዋናው መፍትሄ የሰውነት ክብደትን ቀንሶ በአየር መተላለፊያ ቱቦው ዙርያ ያሉትን ስቦች ማስወገድ ነው፡፡ በሌላ መልኩ አልኮልም ቱቦው ላይ ያሉትን ጡንቻዎች ስለሚያላላቸው ከዕንቅልፍ ሰዓት በፊት አልኮልን መውሰድ ማቆም ይገባል፡፡ ይህ ሁሉ መፍትሄን ካላመጣ ግን በእንቅልፍ ሰዓት የአየር ቱቦዎችን ክፍት የሚያደርግ መሳርያ መጠቀም ሊያስፈልግ ይችላል፡፡
የአየር ቱቦው በሚጠብበት ሰዓት ትንፋሻችንም ቶለ ቶሎ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው በአማካኝ በየደቂቃው ለ14 ጊዜያት የሚተነፍስ ሲሆን በሚተኛበት ሰዓት ይህ ቁጥር ወደ 15 እና 16 ያድጋል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
====================
አንዳንድ ሰዎች በእንቅልፍ ሰዓት የሌሎችን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ ያንኮራፋሉ፡፡ ሆኖም ሰዎች ባያንኮራፉም እንኳን ከፍ ባለ ድምፅ ሲተነፍሱ ይታያል፡፡ ይህ ለምን ይሆናል?
ተኝተንም ሆነ ሳንተኛ በትንፋሽ ወቅት የምናወጣው ድምፅ በአየር መዘዋወርያ ትቦዋችን ውስጥ በሚፈጠር መርገብገብ ሳብያ የሚከሰት መሆኑን ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ ወደ ውስጥ በምንተነፍስበት ጊዜ ከአፍ እስከ ማንቁርት ድረስ ተዘርግቶ ያለው የላይኛው የአተነፋፈስ ስርዓት ክፍላችን ውስጥ የሚፈጠረው ፈጣን የአየር እንቅስቃሴ በመላው የአተነፋፈስ ስርዓችን ውስጥ ያለውን ግፊት ይቀንሰዋል፡፡ ግፊቱ ይህን የላይኛውን ክፍል ስለሚያኮማትረው ትንፋሽን ሊገድበው ይችላል፡፡
ባልተኛንበት ሰዓት በዚህ ክፍል የሚኖረው እንቅስቃሴ ቱቦውንም ክፍት አሰድርጎ አየር በነፃነት እንደዚዘዋወር አድርጎ የሚያቆይ ይሆናል፡፡ ሆኖም ስንተኛ እንቅስቃሴው በቀድሞ ጥንካሬው ስለማይሆ ክፍሉ የሚኮማተርና የትንፋሻችን ድምፅም እያየለ የሚመጣ ይሆናል፡፡
በእንቅልፍ ሰዓት በትንፋሽ ቱቦው ዙርያ ያሉትን ጡንቻዎች ይላላሉ፡፡ ቱቦው እንዲፍታታ የሚያደርጉት የእነዚህ ጡንቻዎች መላላት ደግሞ ቱቦው እንዲጠብ ያደርገዋል፡፡ የአየር መተላለፊያው ሲጠብ በውስጡ የሚተላለፈው አየር ፍጥነቱ ይጨምራል፡፡ በዚህ ምክንያት አየሩ ይበልጥ ሲርገበገብ ደግሞ የበለጠ ድምፅ የሚፈጥር ይሆናል፡፡ ቱቦው ከዚህም የበለጠ እየጠበበ የሚሄድና ከስትሮ ትንሽ ሰፋ ባለ ጥበት ላይ ሲገኝ ደግሞ ማንኮራፋት ይጀምራል፡፡
በእንቅልፍ ሰዓታችን የትንፋሽ ቱቦው ከማንኮራፋቱ በላይም የሚጠብ ከሆነ መተንፈስን የማይቻል ስለሚያደርገው አየር ፍለጋ እንባንናለን፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ ዋናው መፍትሄ የሰውነት ክብደትን ቀንሶ በአየር መተላለፊያ ቱቦው ዙርያ ያሉትን ስቦች ማስወገድ ነው፡፡ በሌላ መልኩ አልኮልም ቱቦው ላይ ያሉትን ጡንቻዎች ስለሚያላላቸው ከዕንቅልፍ ሰዓት በፊት አልኮልን መውሰድ ማቆም ይገባል፡፡ ይህ ሁሉ መፍትሄን ካላመጣ ግን በእንቅልፍ ሰዓት የአየር ቱቦዎችን ክፍት የሚያደርግ መሳርያ መጠቀም ሊያስፈልግ ይችላል፡፡
የአየር ቱቦው በሚጠብበት ሰዓት ትንፋሻችንም ቶለ ቶሎ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው በአማካኝ በየደቂቃው ለ14 ጊዜያት የሚተነፍስ ሲሆን በሚተኛበት ሰዓት ይህ ቁጥር ወደ 15 እና 16 ያድጋል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
ቪዲዮ አይቶ መፅሐፍ የሚፅፈው አዲሱ ቴክኖሎጂ
======================
ቴክኖሎጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቀድሞ በሰዎች ይሰሩ የነበሩ ተግባራትን ወስዶ ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ አሁን ደግሞ ይህ የእንጀራ ነጠቃው ወደ ጥበብ ባለሙያዎችም ፊቱን ማዞር ጀምሯል፡፡ ከቻይናዎቹ የዳሊየን ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂ እና ሆንግ ኮንግ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ አጥኚዎች ቀድሞ ከፍተኛ ክህሎት ባላቸው የጥበብ ባለሙያዎች ዲዛይን ይደረጉ የነበሩ በምስል የተቀነባበሩ ወይም የኮሚክ መፅሐፍትን መስራት ችሏል፡፡ ቴክኖሎጂው መፅሐፍቱን የሚሰራው ፊልም፣ የቴሌቪዥን ድራማ፣ አኒሜሽን እና ሌሎች ቪዲዮዎችንም በመመልከት ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ የሰሩት ስልት የቪዲዮ ፍሬሞችን ወስዶ ለኮሚክ መፅሐፍት በሚመች መልኩ ካስተካከላቸው በኋላ አነዱ ገፅ ላይ ያለው ምስል ከሌላኛው የተከተለ እንዲሆን አድርጎ በተለያየ ገፅ ያስቀምጣቸዋል፡፡ በተጨማሪም ምስሎቹ ላይ ያሉት ሰዎች የሚናገሯቸውን ቃላት ማስቀመጫ የሆነው የፅሁፍ ሳጥን ብዙዎቹ የኮሚክ መፅሐፍት ላይ እንደሚደረገው በተመሳሳይ ቅርፅ ከማስቀመጥ ይልቅ የተናጋሪውን ስሜት በሚገልፁ የተለያየ ቅርፅ ባላቸው ሳጥኖች ውስጥ የሚያስቀምጣቸው ይሆናል፡፡ ይህንንም ለማድረግ የቪዲዮውን ድምፅ እና በፅሁፍ የሚቀርበውን ንግግር (ሰብታይትል) ተመልክቶ በተለያዩ ንግግሮች ውስጥ ያለውን የስሜት መንፀባረቅ በመረዳት ነው፡፡
ስልቱ የኮሚክ መፅሐፍቱን ለመስራት ከታይታኒክ፣ ዘ ሜሴጅ፣ ፍሬንድስ እና አፕ ኢን ዘ ኤር ከተሰኙት ፊልምና የቴሌቪዥን ድራማዎች የወሰዳቸው 16 የቪዲዮ ክሊፖችን ተጠቅሟል፡፡ ቪዲዮዎቹ ከሁለት እስከ ስድስት ደቂቃ ርዝማኔ ያላቸው ነበሩ፡፡
ተመራማሪዎቹ አዲሱ ስልታቸውን በተለያዩ ሙከራዎች ላይ የፈተኑት ሲሆን በተጨማሪም በባለሙያዎች አማካኝነት ከፊልም ወደ ኮሚክ መፅሐፍትነት ከሚቀየሩት ጋራ አነፃፅረዋቸዋል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ሰዎችን ሰብስበው በአዲሱ ስልታቸው አማካኝነት የሰሯቸውን ኮሚክ መፅሐፍት ጥራት በጥበብ ባለሙያዎች ከሚሰራው ጋራ እንዲያነፃፅሩ አደረጉ፡፡ በውጤቱም አብዛኛዎቹ ተሳታፊዎች ከባለሙያዎች ይልቅ በአዲሱ ስርዓት የተሰራውን መርጠዋል፡፡
ተመራማሪዎቹ አዲሱን ስልት በበቂ ሁኔታ ካሻሻሉት እና ከዚህም በበለጠ የስራውን ጥራት የሚጨምሩ ጥናቶችን ካከናወኑበት በኋላ ከተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ወይም ሌሎች ቪዲዮዎች ወስዶ ኮሚክ መፅሐፍትን ለመስራት ማገልገል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
======================
ቴክኖሎጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቀድሞ በሰዎች ይሰሩ የነበሩ ተግባራትን ወስዶ ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ አሁን ደግሞ ይህ የእንጀራ ነጠቃው ወደ ጥበብ ባለሙያዎችም ፊቱን ማዞር ጀምሯል፡፡ ከቻይናዎቹ የዳሊየን ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂ እና ሆንግ ኮንግ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ አጥኚዎች ቀድሞ ከፍተኛ ክህሎት ባላቸው የጥበብ ባለሙያዎች ዲዛይን ይደረጉ የነበሩ በምስል የተቀነባበሩ ወይም የኮሚክ መፅሐፍትን መስራት ችሏል፡፡ ቴክኖሎጂው መፅሐፍቱን የሚሰራው ፊልም፣ የቴሌቪዥን ድራማ፣ አኒሜሽን እና ሌሎች ቪዲዮዎችንም በመመልከት ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ የሰሩት ስልት የቪዲዮ ፍሬሞችን ወስዶ ለኮሚክ መፅሐፍት በሚመች መልኩ ካስተካከላቸው በኋላ አነዱ ገፅ ላይ ያለው ምስል ከሌላኛው የተከተለ እንዲሆን አድርጎ በተለያየ ገፅ ያስቀምጣቸዋል፡፡ በተጨማሪም ምስሎቹ ላይ ያሉት ሰዎች የሚናገሯቸውን ቃላት ማስቀመጫ የሆነው የፅሁፍ ሳጥን ብዙዎቹ የኮሚክ መፅሐፍት ላይ እንደሚደረገው በተመሳሳይ ቅርፅ ከማስቀመጥ ይልቅ የተናጋሪውን ስሜት በሚገልፁ የተለያየ ቅርፅ ባላቸው ሳጥኖች ውስጥ የሚያስቀምጣቸው ይሆናል፡፡ ይህንንም ለማድረግ የቪዲዮውን ድምፅ እና በፅሁፍ የሚቀርበውን ንግግር (ሰብታይትል) ተመልክቶ በተለያዩ ንግግሮች ውስጥ ያለውን የስሜት መንፀባረቅ በመረዳት ነው፡፡
ስልቱ የኮሚክ መፅሐፍቱን ለመስራት ከታይታኒክ፣ ዘ ሜሴጅ፣ ፍሬንድስ እና አፕ ኢን ዘ ኤር ከተሰኙት ፊልምና የቴሌቪዥን ድራማዎች የወሰዳቸው 16 የቪዲዮ ክሊፖችን ተጠቅሟል፡፡ ቪዲዮዎቹ ከሁለት እስከ ስድስት ደቂቃ ርዝማኔ ያላቸው ነበሩ፡፡
ተመራማሪዎቹ አዲሱ ስልታቸውን በተለያዩ ሙከራዎች ላይ የፈተኑት ሲሆን በተጨማሪም በባለሙያዎች አማካኝነት ከፊልም ወደ ኮሚክ መፅሐፍትነት ከሚቀየሩት ጋራ አነፃፅረዋቸዋል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ሰዎችን ሰብስበው በአዲሱ ስልታቸው አማካኝነት የሰሯቸውን ኮሚክ መፅሐፍት ጥራት በጥበብ ባለሙያዎች ከሚሰራው ጋራ እንዲያነፃፅሩ አደረጉ፡፡ በውጤቱም አብዛኛዎቹ ተሳታፊዎች ከባለሙያዎች ይልቅ በአዲሱ ስርዓት የተሰራውን መርጠዋል፡፡
ተመራማሪዎቹ አዲሱን ስልት በበቂ ሁኔታ ካሻሻሉት እና ከዚህም በበለጠ የስራውን ጥራት የሚጨምሩ ጥናቶችን ካከናወኑበት በኋላ ከተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ወይም ሌሎች ቪዲዮዎች ወስዶ ኮሚክ መፅሐፍትን ለመስራት ማገልገል እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
ኤሌክትሪክን ለጦር መሳሪያነት በአሜሪካ
***************************
የአሜሪካ ጦር ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ውሎ የማያውቅ ጨረር አመንጪ የጦር መሳሪያ እየሰራ መሆኑ ተነገረ፡፡ መሳሪያው ለመምታት ባለመው ነገር ላይ ተከታታይ ጨረሮችን የሚለቅ ነው፡፡ ይህ ተጋክቲካል አልትራሾርት ፐልስድ የተባለ መሳሪያ በሳይንስ ፊክሽን ፊልሞች ላይ እንደሚታዩ መሳሪያዎች አይነት እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡
ይህም ከ250 እስከ 300 ኪሎዋት ተተኳሽ ያለው ሲሆን የአሜሪካ ባህር ሃይል ከታጠቀው መሳሪያ አስር እጥፍ ሀይል ያለውና የተተኮሰ ሚሳኤልን መደምሰስ የሚያስችል እንደሆነም ታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በምድር፣ በባህርና በአየር ሃይሉ የተለያየ ብቃት ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች የታጠቀው ጦሩ ይህኛውን ለየት የሚያደርገው በኤሌክትሪክ ሃይል ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም የኤሌክትሪክ ሃይል እስካልተቋረጠ ድረስ ሃይሉ የማይነጥፍ እንደሆነ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
አዲሱ መሳሪያም በተሸከርካሪ የሚጓጓዝ ሲሆን ተንቀሳቃሽ ጀኔሬተርና ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ ያስፈልገዋል፡፡ የመጀመሪያዎቹ አራት ተሸከርካሪዎች ከነሙሉ መሳሪያቸው ለ2024 እንደሚደርሱ ተነግሯል፡፡
ምንጭ New scientist
***************************
የአሜሪካ ጦር ከዚህ በፊት ጥቅም ላይ ውሎ የማያውቅ ጨረር አመንጪ የጦር መሳሪያ እየሰራ መሆኑ ተነገረ፡፡ መሳሪያው ለመምታት ባለመው ነገር ላይ ተከታታይ ጨረሮችን የሚለቅ ነው፡፡ ይህ ተጋክቲካል አልትራሾርት ፐልስድ የተባለ መሳሪያ በሳይንስ ፊክሽን ፊልሞች ላይ እንደሚታዩ መሳሪያዎች አይነት እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡
ይህም ከ250 እስከ 300 ኪሎዋት ተተኳሽ ያለው ሲሆን የአሜሪካ ባህር ሃይል ከታጠቀው መሳሪያ አስር እጥፍ ሀይል ያለውና የተተኮሰ ሚሳኤልን መደምሰስ የሚያስችል እንደሆነም ታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በምድር፣ በባህርና በአየር ሃይሉ የተለያየ ብቃት ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች የታጠቀው ጦሩ ይህኛውን ለየት የሚያደርገው በኤሌክትሪክ ሃይል ላይ የተመሰረተ መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም የኤሌክትሪክ ሃይል እስካልተቋረጠ ድረስ ሃይሉ የማይነጥፍ እንደሆነ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
አዲሱ መሳሪያም በተሸከርካሪ የሚጓጓዝ ሲሆን ተንቀሳቃሽ ጀኔሬተርና ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ ያስፈልገዋል፡፡ የመጀመሪያዎቹ አራት ተሸከርካሪዎች ከነሙሉ መሳሪያቸው ለ2024 እንደሚደርሱ ተነግሯል፡፡
ምንጭ New scientist
በ1 ዓመት የታጣው የ20 ሚሊዮን ዓመታት ህይወት ዘመን
========================
በኮሮና ቫይረስ ሳብያ በ81 ሀገራት ብቻ ከ20.5 ሚሊዮን ዓመታት የሚልቅ ቀሪ ዕድሜ መታጣቱን አዲስ ጥናት አመላከተ፡፡ ጥናቱ በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ባይሆንም እንኳን በቅርቡ መሞታቸው አይቀርም ነበር የሚለውን አስተሳሰብ አየር ላይ የሚዋልል መሰረተ ቢስ እንደሚያደርገውም ተነግሮለታል፡፡
የታጣው የመኖርያ ዘመን ሲባል ሟቾች በሞቱበት ጊዜ ባላቸው ዕድሜ እና ይኖሩበታል ተብሎ በሚታመነው የዕድሜ ጣርያ መካከል ያለው ልዩነት ነው፡፡ ጥናቱ የተሰራውም በ81 ሀገራት የተከሰቱ ከ1,279,866 በላይ የኮቪድ-19 ሞቶችን ብሎም የየሀገራቱን የተቀመጠ ዓማካኝ የህይወት ጣርያ ላይ በመመርኮዝ ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት በነዚህ 81 ሀገራት የነበሩ የሚሊዮኖች ህይወት ውስጥ ገና ወደፊት ሊኖር ይቻል የነበረ የ20,507,518 ወይም በእያንዳንዱ ሟች በአማካኝ የ16 ዓመታት ዕድሜ ታጥቷል ማለት ነው፡፡ ከነዚህ የታጡ ዓመታት ውስጥ 44.9 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ዓመት ባለው ውስጥ ይገኙ ከነበሩ ሰዎች ላይ፣ 30.2 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በታች ከሆኑት ላይ እንዲሁም 25 በመቶው ዕድሜያቸው ከ75 ዓመት በላይ ከሆኑት ላይ ነው፡፡
ሀገራትን በምሳሌነት ወስደን ካየነው በእንግሊዝ ውስጥ የ833,874 ዓመታት ህይወት የታጣ ሲሆን ይህም በአማካኝ የ11.4 ዓመት ህይወት ነው፡፡ በስፔን ደግሞ አጠቃላይ 572,567 ወይም በአማካኝ 11.24 ዓመት ሲታጣ ነገሩ የከፋባት ፔሩ በአጠቃላይ 764,856 ዓመት በአማካኝ ደግሞ የ20.2 ዓመት ዕድሜን ሟች ዜጎቿ አጥተዋል፡፡ ምንም እንኳን በተለይ በሀብታሞቹ ሀገራት ውስጥ የመሞት ዕድላቸው ከፍ የሚለው በእርጅና ዘመን ውስጥ ባሉት ዜጎች ላይ ቢሆንም አብዛኛው ሞት የተከሰተው ግን ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ባለው ክልል ውስጥ ያሉት ላይ ነው፡፡
እንዲህም ሆኖ ግን በሀብታም ሀገራት ውስጥ የታጡት ዓመታት በዋናነት ከነዚህ ዕድሜያቸው በአንፃራዊነት ከፍ ካሉት ላይ ቢሆንም መካከለኛና አነስተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ዘንድ ግን ብዙው ዓመት ዕድሜያቸው 55 እና ከዚያ በታች ከሆኑት ላይ የተቀነሰ ነው፡፡ በፆታም ወንዶች ከሴቶች በ44 በመቶ የበለጠ ዕድሜን አጥተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
========================
በኮሮና ቫይረስ ሳብያ በ81 ሀገራት ብቻ ከ20.5 ሚሊዮን ዓመታት የሚልቅ ቀሪ ዕድሜ መታጣቱን አዲስ ጥናት አመላከተ፡፡ ጥናቱ በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ባይሆንም እንኳን በቅርቡ መሞታቸው አይቀርም ነበር የሚለውን አስተሳሰብ አየር ላይ የሚዋልል መሰረተ ቢስ እንደሚያደርገውም ተነግሮለታል፡፡
የታጣው የመኖርያ ዘመን ሲባል ሟቾች በሞቱበት ጊዜ ባላቸው ዕድሜ እና ይኖሩበታል ተብሎ በሚታመነው የዕድሜ ጣርያ መካከል ያለው ልዩነት ነው፡፡ ጥናቱ የተሰራውም በ81 ሀገራት የተከሰቱ ከ1,279,866 በላይ የኮቪድ-19 ሞቶችን ብሎም የየሀገራቱን የተቀመጠ ዓማካኝ የህይወት ጣርያ ላይ በመመርኮዝ ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት በነዚህ 81 ሀገራት የነበሩ የሚሊዮኖች ህይወት ውስጥ ገና ወደፊት ሊኖር ይቻል የነበረ የ20,507,518 ወይም በእያንዳንዱ ሟች በአማካኝ የ16 ዓመታት ዕድሜ ታጥቷል ማለት ነው፡፡ ከነዚህ የታጡ ዓመታት ውስጥ 44.9 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ዓመት ባለው ውስጥ ይገኙ ከነበሩ ሰዎች ላይ፣ 30.2 በመቶው ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በታች ከሆኑት ላይ እንዲሁም 25 በመቶው ዕድሜያቸው ከ75 ዓመት በላይ ከሆኑት ላይ ነው፡፡
ሀገራትን በምሳሌነት ወስደን ካየነው በእንግሊዝ ውስጥ የ833,874 ዓመታት ህይወት የታጣ ሲሆን ይህም በአማካኝ የ11.4 ዓመት ህይወት ነው፡፡ በስፔን ደግሞ አጠቃላይ 572,567 ወይም በአማካኝ 11.24 ዓመት ሲታጣ ነገሩ የከፋባት ፔሩ በአጠቃላይ 764,856 ዓመት በአማካኝ ደግሞ የ20.2 ዓመት ዕድሜን ሟች ዜጎቿ አጥተዋል፡፡ ምንም እንኳን በተለይ በሀብታሞቹ ሀገራት ውስጥ የመሞት ዕድላቸው ከፍ የሚለው በእርጅና ዘመን ውስጥ ባሉት ዜጎች ላይ ቢሆንም አብዛኛው ሞት የተከሰተው ግን ዕድሜያቸው ከ55 እስከ 75 ባለው ክልል ውስጥ ያሉት ላይ ነው፡፡
እንዲህም ሆኖ ግን በሀብታም ሀገራት ውስጥ የታጡት ዓመታት በዋናነት ከነዚህ ዕድሜያቸው በአንፃራዊነት ከፍ ካሉት ላይ ቢሆንም መካከለኛና አነስተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ዘንድ ግን ብዙው ዓመት ዕድሜያቸው 55 እና ከዚያ በታች ከሆኑት ላይ የተቀነሰ ነው፡፡ በፆታም ወንዶች ከሴቶች በ44 በመቶ የበለጠ ዕድሜን አጥተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ቴክ-ሳይንስ ሪቪው ፪፤ ነገ 10 ሰዓት ይጠብቁን
=================
በነገው የቴክ ሳይንስ መሰናዶዋችን ላለፉት ተከታታይ ሳምንታት ወደ እናንተው ያደረስናቸው የአብይ ፕሮግራም እና ብላቴናት ዝግጅቶቻችንን በሪቪው መልሰን የምንቃኛቸው ይሆናል፡፡ በዚህም፤
በአብይ ፕሮግራማችን ላይ፤ ስለ ሚጥል በሽታ፣ ስለ ዲጂታል ላይብረሪ፣ የግብርና ምርምር ስራዎች መቼ ተጀመረ፣ ቀርከሀ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ አፍሪካ እና ቴክኖሎጂ እና መድሐኒታማና መዓዛማነት ያላቸው እጽዋቶች
ብላቴናት ደግሞ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዊልቸር፣ የድሮን ፈጠራ፣ የሴኩሪቲ ካሜራ፣ ዘመናዊ የሻይ ቡና ማፊያ፣ ሻማን በድጋሚ መጠቀም፣ ተሸከርካሪ የሰራው ተማሪ፣ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን ላይ የሰራናቸውን ዝግጅቶች መለስ ብለን እናስቃኛችኋለን፡፡
የዩትዩብ ቻናላችንን (https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg) ሰብስክራይብ ማድረጉን እንዳይረሱ፤ ከዓመታት በፊት ከተላለፈው የመጀመሪየው ክፍል አንስቶ ያሉትን ሁሉንም የቴክ-ሳይንስ ፕሮግራሞች አንድ በአንድ መመልከትና ለእርስዎም ሆነ ቤተሰብዎ ዕውቀትን መገብየት ይችሉበታልና፡፡
=================
በነገው የቴክ ሳይንስ መሰናዶዋችን ላለፉት ተከታታይ ሳምንታት ወደ እናንተው ያደረስናቸው የአብይ ፕሮግራም እና ብላቴናት ዝግጅቶቻችንን በሪቪው መልሰን የምንቃኛቸው ይሆናል፡፡ በዚህም፤
በአብይ ፕሮግራማችን ላይ፤ ስለ ሚጥል በሽታ፣ ስለ ዲጂታል ላይብረሪ፣ የግብርና ምርምር ስራዎች መቼ ተጀመረ፣ ቀርከሀ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ አፍሪካ እና ቴክኖሎጂ እና መድሐኒታማና መዓዛማነት ያላቸው እጽዋቶች
ብላቴናት ደግሞ፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዊልቸር፣ የድሮን ፈጠራ፣ የሴኩሪቲ ካሜራ፣ ዘመናዊ የሻይ ቡና ማፊያ፣ ሻማን በድጋሚ መጠቀም፣ ተሸከርካሪ የሰራው ተማሪ፣ የእንጀራ መጋገሪያ ማሽን ላይ የሰራናቸውን ዝግጅቶች መለስ ብለን እናስቃኛችኋለን፡፡
የዩትዩብ ቻናላችንን (https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg) ሰብስክራይብ ማድረጉን እንዳይረሱ፤ ከዓመታት በፊት ከተላለፈው የመጀመሪየው ክፍል አንስቶ ያሉትን ሁሉንም የቴክ-ሳይንስ ፕሮግራሞች አንድ በአንድ መመልከትና ለእርስዎም ሆነ ቤተሰብዎ ዕውቀትን መገብየት ይችሉበታልና፡፡