ኢትዮጵያ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት እንቅስቃሴዎቿን የቃኘው የምክክር መድረክ
===================
ከትናንት አንስቶ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ሰው ሰራሽ አስተውሎት እንዲሁም ሮቦቲክስ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዛሬው መድረክም የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ገለፃዎች የቀረቡ ሲሆን እነርሱን መነሻ በማድረግም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
በዕለቱ ከቀረቡት ውስጥ ቀዳሚ የነበረው ከአይኮግ ላብስ የመጡት አቶ ህሩይ ፀጋዬ “Beware of Greeks Baring Gifts: Robotics in Ethiopia” በሚል ርዕስ ያቀረቡት ሮቦቲክስ ላይ ያተኮረ ገለፃ ነው፡፡ በገለፃቸው ስለ ሮቦቶች ምንነት፣ ከቀድሞ ጊዜያት አንስቶ የነበረ አረዳድን እንዲሁም ሀገራዊ እንቅስቃሴ ላይ ያለውን ድክመት እና ዕድል አብራርተዋል፡፡ ሮቦቲክስን በተመለከተ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ዕንቅስቃሴዎች እጅግ ውስን ከመሆናቸውም ባሻገር የተሰሩ አነስተኛ ስራዎችም በኢንዱስትሪው ሊሰጣቸው ከሚገባው ቦታ በላይ ተጋኖ እንደሚወራላቸው የተናገሩት አቶ ህሩይ ዘርፉን ለማሳደግ የትምህርት ተቋማትና እና ባለድርሻዎች ተገቢውን ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በተቋማቸው አይኮግ ላብ ውስጥ የተኬዱ ርቀቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችንም ለታዳሚው በምሳሌነት አቅርበዋል፡፡
የዕለቱን ሁለተኛ ገለፃ ያቀረቡት በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ውስጥ በተመራማሪነት እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ቃልኪዳነ ገዛኸኝ ሲሆኑ እርሳቸውም በበኩላቸው በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ኢ-ኮሜርስ ግንኙነት ላይ በማተኮር ዳሰሳቸውን አጋርተዋል፡፡ በገለፃቸው የኢ-ኮሜርስ አይነት ታሪክ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሊጫወትበት ስለሚችለው ሚና ከመጥቀስም ባሻገር በኢትዮጵያ ደረጃ ተግባራዊ መሆን ይችላሉ ያሏቸው የቴክኖሎጂው ገፅታዎችን አስቃኝተዋል፡፡ በአሁን ሰዓት 14 ያህል ኢ-ኮሜርስ ላይ አተኩረው የሚንቀሳቀሱ ተቋማት በኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ያሉት አቶ ቃልኪዳን በሀገራችን በቅርቡ እያቆጠቆጠ ላለው የኢ-ኮሜርስ እንቅስቃሴ የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ተከትሎ የመጣውን አካላዊ ግንኙነትን የመቀነስ ፍላጎትን ጨምሮ በጎ ዕድልን ፈጥረዋል ያሏቸውን ነጥቦች አስቀምጠዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ አይሲቲ ፓርክ፣ ሮቦ ሮቦቲክስ፣ መረጃና መረብ ደህንነት ኤጀንሲ፣ ኢትዮ-ቴኬኮምን ጨምሮ ከግልና መንግስት መስሪያ ቤቶችና ከፍተኛ የትምሀርት ተቋማት የተወከሉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡
===================
ከትናንት አንስቶ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ሰው ሰራሽ አስተውሎት እንዲሁም ሮቦቲክስ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዛሬው መድረክም የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ገለፃዎች የቀረቡ ሲሆን እነርሱን መነሻ በማድረግም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
በዕለቱ ከቀረቡት ውስጥ ቀዳሚ የነበረው ከአይኮግ ላብስ የመጡት አቶ ህሩይ ፀጋዬ “Beware of Greeks Baring Gifts: Robotics in Ethiopia” በሚል ርዕስ ያቀረቡት ሮቦቲክስ ላይ ያተኮረ ገለፃ ነው፡፡ በገለፃቸው ስለ ሮቦቶች ምንነት፣ ከቀድሞ ጊዜያት አንስቶ የነበረ አረዳድን እንዲሁም ሀገራዊ እንቅስቃሴ ላይ ያለውን ድክመት እና ዕድል አብራርተዋል፡፡ ሮቦቲክስን በተመለከተ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ዕንቅስቃሴዎች እጅግ ውስን ከመሆናቸውም ባሻገር የተሰሩ አነስተኛ ስራዎችም በኢንዱስትሪው ሊሰጣቸው ከሚገባው ቦታ በላይ ተጋኖ እንደሚወራላቸው የተናገሩት አቶ ህሩይ ዘርፉን ለማሳደግ የትምህርት ተቋማትና እና ባለድርሻዎች ተገቢውን ስራ ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በተቋማቸው አይኮግ ላብ ውስጥ የተኬዱ ርቀቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችንም ለታዳሚው በምሳሌነት አቅርበዋል፡፡
የዕለቱን ሁለተኛ ገለፃ ያቀረቡት በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ውስጥ በተመራማሪነት እያገለገሉ የሚገኙት አቶ ቃልኪዳነ ገዛኸኝ ሲሆኑ እርሳቸውም በበኩላቸው በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ኢ-ኮሜርስ ግንኙነት ላይ በማተኮር ዳሰሳቸውን አጋርተዋል፡፡ በገለፃቸው የኢ-ኮሜርስ አይነት ታሪክ እና ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሊጫወትበት ስለሚችለው ሚና ከመጥቀስም ባሻገር በኢትዮጵያ ደረጃ ተግባራዊ መሆን ይችላሉ ያሏቸው የቴክኖሎጂው ገፅታዎችን አስቃኝተዋል፡፡ በአሁን ሰዓት 14 ያህል ኢ-ኮሜርስ ላይ አተኩረው የሚንቀሳቀሱ ተቋማት በኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ያሉት አቶ ቃልኪዳን በሀገራችን በቅርቡ እያቆጠቆጠ ላለው የኢ-ኮሜርስ እንቅስቃሴ የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ተከትሎ የመጣውን አካላዊ ግንኙነትን የመቀነስ ፍላጎትን ጨምሮ በጎ ዕድልን ፈጥረዋል ያሏቸውን ነጥቦች አስቀምጠዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ አይሲቲ ፓርክ፣ ሮቦ ሮቦቲክስ፣ መረጃና መረብ ደህንነት ኤጀንሲ፣ ኢትዮ-ቴኬኮምን ጨምሮ ከግልና መንግስት መስሪያ ቤቶችና ከፍተኛ የትምሀርት ተቋማት የተወከሉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነውበታል፡፡
ጁፒተር መሳይዋ ደመና አልባ ፕላኔት
***********************
ተመራማሪዎች በስነ-ፈለክ ምርምር ውስጥ የመጀመሪያ የሆነ ጁፒተርን የሚመስል ደመና አልባ ፕላኔት ማግኘታቸውን አሳወቁ፡፡ ስለ ፕላኔቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍንጭ የተገኘው በ2012 ቢሆንም ከባቢ አየሩ ግን እስካሁን ድረስ ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡ ሞቃቱ ጁፒተር የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው በሳይንሳዊ መጠሪያው WASP-62b የሚባል ሲሆን በስርዓተ ፀሐይ ውስጥ ከሚገኘው ጁፒተር ግማሽ ያክል መጠን ሲኖረው በ575 የብርሃን ዓመት ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
ፕላኔቱ ፀሐይን ለመዞር 12 ዓመት ከሚወስድበት ከጁፒተር በተቃራኒው የራሱን ኮከብ ዞሮ ለመጨረስ አራት ቀን ተኩል ብቻ ይፈጅበታል፡፡ ለኮከቡ ባለው ቅርበት የተነሳ ከፍተኛ ሙቀት አለው፡፡ ለዚህም ነው ተመራማሪዎቹ ሞቃቱ ጁፒተር ሲሉ የሰየሙት፡፡
ለምርምሩ ሃብል የተባለው የህዋ ቴሌስኮፕ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በውስጡ የሚገኙ ንጥረ ነገሮችን ለመለየት ስፔስትሮስኮፒ የተባለ ስልትን እንደተጠቀመች ምርምሩን ያደረገችው ሙንዛ አላም ተናግራለች፡፡ ምንም እንኳን ፖታሺየም መኖርን የሚያመለክት ፍንጭ ባይኖርም ሶዲየም የተባለው ንጥረ ነገር ግን በግልጽ ይታያል ስትል አስረድታለች፡፡
ደመና አልባ ፕላኔቶችን የማግኘት እድል እጅግ ዝቅተኛ እንደሆነ የምትናገረው አላን እስካሁን ባለው ምርምር ግልጽ የሆነ ከባቢ አየር ያለው ኤግዞ ፕላኔት ሞቃቱ ሳተርን የተሰኘውና በ2018 የተገኘው WASP-96b ፕላኔት መሆኑን ገልጻለች፡፡ የስነ ፈለክ ተመራማሪዎች እንዲህ አይነት ግልጽ የሆነ ከባቢ አየር ያላቸውን ፕላኔቶች ማጥናት በፕላኔቶች አፈጣጠር ዙሪያ ለሚደረገው ምርምር አጋዥ ይሆናል ብለዋል፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
***********************
ተመራማሪዎች በስነ-ፈለክ ምርምር ውስጥ የመጀመሪያ የሆነ ጁፒተርን የሚመስል ደመና አልባ ፕላኔት ማግኘታቸውን አሳወቁ፡፡ ስለ ፕላኔቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ፍንጭ የተገኘው በ2012 ቢሆንም ከባቢ አየሩ ግን እስካሁን ድረስ ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡ ሞቃቱ ጁፒተር የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው በሳይንሳዊ መጠሪያው WASP-62b የሚባል ሲሆን በስርዓተ ፀሐይ ውስጥ ከሚገኘው ጁፒተር ግማሽ ያክል መጠን ሲኖረው በ575 የብርሃን ዓመት ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
ፕላኔቱ ፀሐይን ለመዞር 12 ዓመት ከሚወስድበት ከጁፒተር በተቃራኒው የራሱን ኮከብ ዞሮ ለመጨረስ አራት ቀን ተኩል ብቻ ይፈጅበታል፡፡ ለኮከቡ ባለው ቅርበት የተነሳ ከፍተኛ ሙቀት አለው፡፡ ለዚህም ነው ተመራማሪዎቹ ሞቃቱ ጁፒተር ሲሉ የሰየሙት፡፡
ለምርምሩ ሃብል የተባለው የህዋ ቴሌስኮፕ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በውስጡ የሚገኙ ንጥረ ነገሮችን ለመለየት ስፔስትሮስኮፒ የተባለ ስልትን እንደተጠቀመች ምርምሩን ያደረገችው ሙንዛ አላም ተናግራለች፡፡ ምንም እንኳን ፖታሺየም መኖርን የሚያመለክት ፍንጭ ባይኖርም ሶዲየም የተባለው ንጥረ ነገር ግን በግልጽ ይታያል ስትል አስረድታለች፡፡
ደመና አልባ ፕላኔቶችን የማግኘት እድል እጅግ ዝቅተኛ እንደሆነ የምትናገረው አላን እስካሁን ባለው ምርምር ግልጽ የሆነ ከባቢ አየር ያለው ኤግዞ ፕላኔት ሞቃቱ ሳተርን የተሰኘውና በ2018 የተገኘው WASP-96b ፕላኔት መሆኑን ገልጻለች፡፡ የስነ ፈለክ ተመራማሪዎች እንዲህ አይነት ግልጽ የሆነ ከባቢ አየር ያላቸውን ፕላኔቶች ማጥናት በፕላኔቶች አፈጣጠር ዙሪያ ለሚደረገው ምርምር አጋዥ ይሆናል ብለዋል፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
10 አስፈላጊና ነፃ የዊንዶውስ 10 መተግበሪያዎች
በ2021 ስራዎችን ይበልጥ ሊቀላጥፉ የሚችሉ እና አዳዲስ የዘመኑ ገፅታዎችን ያካተቱ የኮምፒውተር መተግበሪያዎች ሊያስፈልጉን ይችላሉ፡፡ ታዲያ ከዚህ በታች የምትመለከቷቸው 10 መተግበሪያዎች አዳዲስ ገፅታዎችን በማከል በአዲሱ የፈረንጆቹ አመት ብዙ ተጠቃሚ ያፈራሉ ተብለው የሚጠበቁ ናቸው፡፡ መረጃውን ያስነበበው ቴክራደር እነዚህ ጠቃሚ መተግበሪያዎችን እንደሚከተለው አስቀምጧል፡-
1 TestDisk
ሜካኒካል የሆነው የመረጃ ማከማቻ በተለያዩ ምከንያቶች ብልሽት በሚያጋጥመው ወቅት መረጃችንን ለማዳን የሚያስችሉ መተግበሪያዎች እጅግ ይጠቅሙናል፡፡ TestDisk ይህን መረጃ የማዳን እና የመመለስ ስራ በሚገባ ለመከውን የሚያስችል መተግበሪያ ሲሆን በ2021 በ open-source ከተመዘገቡ ጠቃሚ መተግበሪያዎች አንዱ ነው፡፡
2 Cobian Backup
ይህ መተግበሪያ ፋይሎቻችንን እንደመጠባበቂያ ለማስቀመጥ ከሚረዱ ከፍተኛ አቅም ካላቸው ነፃ የባካፕ ፓኬጅ (free backup packages) ውስጥ በቀዳሚነት የሚቀመጥ ሲሆን በ2021 ብዙ ተጠቃሚዎች ይኖሩታል ተብሎ የሚታሰብ ጠቃሚ መተግበሪያ ነው፡፡
3 Tablacus File managers
ይህ የፋይል ማስተዳደሪያ እንደ ዊንደዎስ ኤክስፕሎረር ባሉ የፋይል ማስተዳደሪያዎች ላይ የልተጨመሩ እንደ tabs ያሉ አዲስ ገፅታዎችን ያካተተ ከመሆኑም ባለፈ የፋይል ማህደሮችን በምንፈልገው መልኩ ስድሮ ለማስቀመጥ እና የማይፈለጉ ፋይሎችን ደግሞ ዲሴብል ለማድረግ የሚረዳ ነው፡፡
4 CCleaner
ኮምፒውተራችንን ሊያጨናንቁ የሚችሉ አላስፈላጊ መረጃዎች ለማፅዳት እና ተመሳሳይ ፋይሎችን ለይቶ ለማጥፋት CCleaner እጅግ ጠቃሚ መተግበሪያ ነው፡፡ ይህ መተግበሪያ ረጅም እና አድካሚ የማጽዳት ሥራዎችን በአንድ ቦታ ሊሰራለን ከመቻሉም ባለፈ በፈጣን የማጣሪያ ሥርዓት ኮምፒውተራችንን በፍጥነት አንዲጓዝ የሚያደርግልን ነው፡፡
5 LibreOffice
በ2010 የተመሰረተው ይህ የመፃፊያ ስርዓት በየጊዜው በሚጨመሩለት አዳዲስ ገፅታዎች ይበልጥ እየተሻሻለ የመጣ እና አሁን ላይ በጣም ፈጣን ለአሳሰራ ምቹ ከሚባሉ የመፃፊያ ስርዓቶች በቀዳሚነት የሚመደብ ነው፡፡ LibreOffice ምንም ከማይከፈልባቸው ጠቃሚ open-source መተግበሪዎች ውስጥ ቀዳሚው ሲሆን በቀጣዮቹ አመታትም ብዙ ተጠቃሚዎች እንደሚኖሩት የሚገመት ነው፡፡
6 Notepad++
የትኛውንም የኮዲንግ ቋንቋዎች ተጠቅመን ኮድ ለመፃፍ እና የተለያዩ ስራዎችን ለማከናወን የሚያግዘን ይህ መተግበሪያ ከማይክሮሶፍት ዊንዶውስ Notepad ጋር እንዳማራጭ ልንጠቀመው እና እጅግ የበዙ ኮንቴክስችዋል ፎርማቶችን (contextual formatting) ያቀፈ ጠቃሚ መተግበሪያ ነው፡፡
ከእነዚህ መተግበሪያዎች በተጨማሪ ለቪዲዮ፣ ለምስል እና ለድምፅ ማቀናበሪ የሚያግዙ እጅግ አስፈላጊ መተግበሪያዎች መረጃውን ባስነበበው ቴክራደር እንዲሁ የተቀመጡ ሲሆን እነሱም ለምስል ማስተካከያ (Polarr)፣ ለድምፅ ማቀናበሪያ (Audacity እና Cakewalk) እንዲሁም ለቪዲዮ መስሪያ (Shotcut) በተከታይነት ተቀምጠዋል፡፡
ምንጭ፡ Techradar
በ2021 ስራዎችን ይበልጥ ሊቀላጥፉ የሚችሉ እና አዳዲስ የዘመኑ ገፅታዎችን ያካተቱ የኮምፒውተር መተግበሪያዎች ሊያስፈልጉን ይችላሉ፡፡ ታዲያ ከዚህ በታች የምትመለከቷቸው 10 መተግበሪያዎች አዳዲስ ገፅታዎችን በማከል በአዲሱ የፈረንጆቹ አመት ብዙ ተጠቃሚ ያፈራሉ ተብለው የሚጠበቁ ናቸው፡፡ መረጃውን ያስነበበው ቴክራደር እነዚህ ጠቃሚ መተግበሪያዎችን እንደሚከተለው አስቀምጧል፡-
1 TestDisk
ሜካኒካል የሆነው የመረጃ ማከማቻ በተለያዩ ምከንያቶች ብልሽት በሚያጋጥመው ወቅት መረጃችንን ለማዳን የሚያስችሉ መተግበሪያዎች እጅግ ይጠቅሙናል፡፡ TestDisk ይህን መረጃ የማዳን እና የመመለስ ስራ በሚገባ ለመከውን የሚያስችል መተግበሪያ ሲሆን በ2021 በ open-source ከተመዘገቡ ጠቃሚ መተግበሪያዎች አንዱ ነው፡፡
2 Cobian Backup
ይህ መተግበሪያ ፋይሎቻችንን እንደመጠባበቂያ ለማስቀመጥ ከሚረዱ ከፍተኛ አቅም ካላቸው ነፃ የባካፕ ፓኬጅ (free backup packages) ውስጥ በቀዳሚነት የሚቀመጥ ሲሆን በ2021 ብዙ ተጠቃሚዎች ይኖሩታል ተብሎ የሚታሰብ ጠቃሚ መተግበሪያ ነው፡፡
3 Tablacus File managers
ይህ የፋይል ማስተዳደሪያ እንደ ዊንደዎስ ኤክስፕሎረር ባሉ የፋይል ማስተዳደሪያዎች ላይ የልተጨመሩ እንደ tabs ያሉ አዲስ ገፅታዎችን ያካተተ ከመሆኑም ባለፈ የፋይል ማህደሮችን በምንፈልገው መልኩ ስድሮ ለማስቀመጥ እና የማይፈለጉ ፋይሎችን ደግሞ ዲሴብል ለማድረግ የሚረዳ ነው፡፡
4 CCleaner
ኮምፒውተራችንን ሊያጨናንቁ የሚችሉ አላስፈላጊ መረጃዎች ለማፅዳት እና ተመሳሳይ ፋይሎችን ለይቶ ለማጥፋት CCleaner እጅግ ጠቃሚ መተግበሪያ ነው፡፡ ይህ መተግበሪያ ረጅም እና አድካሚ የማጽዳት ሥራዎችን በአንድ ቦታ ሊሰራለን ከመቻሉም ባለፈ በፈጣን የማጣሪያ ሥርዓት ኮምፒውተራችንን በፍጥነት አንዲጓዝ የሚያደርግልን ነው፡፡
5 LibreOffice
በ2010 የተመሰረተው ይህ የመፃፊያ ስርዓት በየጊዜው በሚጨመሩለት አዳዲስ ገፅታዎች ይበልጥ እየተሻሻለ የመጣ እና አሁን ላይ በጣም ፈጣን ለአሳሰራ ምቹ ከሚባሉ የመፃፊያ ስርዓቶች በቀዳሚነት የሚመደብ ነው፡፡ LibreOffice ምንም ከማይከፈልባቸው ጠቃሚ open-source መተግበሪዎች ውስጥ ቀዳሚው ሲሆን በቀጣዮቹ አመታትም ብዙ ተጠቃሚዎች እንደሚኖሩት የሚገመት ነው፡፡
6 Notepad++
የትኛውንም የኮዲንግ ቋንቋዎች ተጠቅመን ኮድ ለመፃፍ እና የተለያዩ ስራዎችን ለማከናወን የሚያግዘን ይህ መተግበሪያ ከማይክሮሶፍት ዊንዶውስ Notepad ጋር እንዳማራጭ ልንጠቀመው እና እጅግ የበዙ ኮንቴክስችዋል ፎርማቶችን (contextual formatting) ያቀፈ ጠቃሚ መተግበሪያ ነው፡፡
ከእነዚህ መተግበሪያዎች በተጨማሪ ለቪዲዮ፣ ለምስል እና ለድምፅ ማቀናበሪ የሚያግዙ እጅግ አስፈላጊ መተግበሪያዎች መረጃውን ባስነበበው ቴክራደር እንዲሁ የተቀመጡ ሲሆን እነሱም ለምስል ማስተካከያ (Polarr)፣ ለድምፅ ማቀናበሪያ (Audacity እና Cakewalk) እንዲሁም ለቪዲዮ መስሪያ (Shotcut) በተከታይነት ተቀምጠዋል፡፡
ምንጭ፡ Techradar
ሳኒታይዘሮች የህፃናት ዓይን ላይ አሳሳቢ ጉዳት እያደረሱ ነው
======================
ከአንድ አመት በፊት የኮቪድ-19 ወረርሺኝ መቀስቀሱን ተከትሎ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘሮችን መጠቀም ዕለታዊ ተግባራችን ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ እነዚህ ሳኒታይዘሮች እጃችንን ሲያደርቁትና ሽታቸውም በዓይናችን እንባ ሲያቀር ቢቆይም ያሳለፍነው ሐሙስ የወጣ ጥናት እንደሚያሳየው ግን እስከ አይነ ስውርነት ሊያደርስ በሚችል ሁኔታ አይናቸው ውስጥ ሳኒታይዘር የሚገኝባቸው ህፃናት ቁጥር እያደገ መጥቷል፡፡
በአውሮፓውያኑ 2019 ሳኒታይዘር ህፃናት ለኬሚካል ካላቸው ተጋላጭነት ውስጥ የ1.3 በመቶውን ድርሻ ብቻ ይወስድ ነበር፡፡ ይህ ቁጥር በፍጥነት አድጎ በ2020 መጨረሻ ላይ 9.9 በመቶ ሆኗል፡፡ ለምሳሌ አንድ ትንሽ ህፃን ብቻ በፈረንሳይ ዓይኑ ውስጥ በተገኘ ሳኒታይዘር ሳብያ በሆስፒታል ቆይቶ ህክምና ለመከታተል ተገዶ የነበረ ቢሆንም በ2020 ቁጥሩ ወደ 16 ከፍ ብሏል፡፡ በሌላ ጥናትም ህንድ ውስጥ በሳኒታይዘር ሳብያ ሁለት ትናንሽ ህፃናት ከፍተኛ የዓይን ጤና ችግር ውስጥ ገብተው ነበር፤ የኋላ ኋላ በተደረገላቸው ርብርብ ሙሉ ለሙሉ ቢያገግሙም፡፡
የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘሮች ከፍተኛ የአልኮል መጠን በተለይም በኢታኖል መልኩ ስለሚይዙ ኮርኒያ ተብሎ በሚታወቀው የአይናችን ክፍል ውስጥ ያሉትን አንዳንድ ሕዋሳት ሊገድሉ ይችላሉ፡፡ ትናንሽ ህፃናት ደግሞ ከቁመታቸው ማጠር የተነሳ ሳኒታይዘሩ ሲረጭ ቀጥታ ወደ አይናቸው ተፈናጥሮ የመግባት ዕድሉ ከፍ ስለሚል ለዚህ በተለየ ተጋላጭ ናቸው፡፡ አንዳንድ ህፃናት ደግሞ ይባስ ብሎ ሳኒታይዘሩ እጃቸው ላይ ከተደረገላቸው በኋላ ወዲያው አይናቸውን ይነካካሉ፡፡ ቀዳሚው ስጋት ግን በህዝብ መሰብሰቢያ አካባቢዎች ብዙን ጊዜ ሳኒታይዘር የሚረጨው የህፃናቱ አይን በሚገኝበት ቁመት ገደማ መሆኑ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ በወርሀ ግንቦት ፈረንሳይ ውስጥ ሳኒታይዘር በአይናቸው ከገባባቸው ህፃናት መካከል 16.4 በመቶው ብቻ በነዚህ ስፍራዎች ቢሆንም ነሀሴ ላይ ግን መጠኑ ወደ 52.4 ሊያድግ ችሏል፡፡
ታድያ ይህን ችግር ለመከላከል ከሳኒታይዘር ይልቅ በማፅዳት ረገድም የተሻለ የሆነውን እጅን በውሃና ሳሙና መታጠብ ቀዳሚ ምርጫ ሊሆንና ወላጆችም የእነርሱ መጠንቀቅ እንዳለ ሆኖ ልጆቻቸው እንዴት ሳኒታይዘር በትክክል መርጨት እንዳለባቸው ማስተማር እንደሚገባ ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡ ሆኖም ሳኒታይዘሩ የህፃናት አይን ውስጥ (ወይም አዋቂ ውስጥም ቢሆን) የሚገባ ከሆነ ተከታዮቹን እርምጃዎች በአስቸኳይ መውሰድ ይገባል፡-
፩. አይናቸውን እንዳያሻሹ ማድረግ (ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ ስለሚያባብሰው)፤
፪. ሳኒታይዘሩ የተረጨበትን አይን ትንሽ ሞቅ ባለ ውሃ ለአስር ደቂቃ ማጠብ፤
፫. ህመሙና ማቃጠሉ ከቀጠለ ወይም የማየት እክል ከገጠማቸው ግን ህፃናቱን በፍጥነት ወደ አይን ሀኪሞች ወይም ድንገተኛ ክፍል ውስጥ ማስገባት ይገባል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
======================
ከአንድ አመት በፊት የኮቪድ-19 ወረርሺኝ መቀስቀሱን ተከትሎ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘሮችን መጠቀም ዕለታዊ ተግባራችን ከሆነ ሰነባብቷል፡፡ እነዚህ ሳኒታይዘሮች እጃችንን ሲያደርቁትና ሽታቸውም በዓይናችን እንባ ሲያቀር ቢቆይም ያሳለፍነው ሐሙስ የወጣ ጥናት እንደሚያሳየው ግን እስከ አይነ ስውርነት ሊያደርስ በሚችል ሁኔታ አይናቸው ውስጥ ሳኒታይዘር የሚገኝባቸው ህፃናት ቁጥር እያደገ መጥቷል፡፡
በአውሮፓውያኑ 2019 ሳኒታይዘር ህፃናት ለኬሚካል ካላቸው ተጋላጭነት ውስጥ የ1.3 በመቶውን ድርሻ ብቻ ይወስድ ነበር፡፡ ይህ ቁጥር በፍጥነት አድጎ በ2020 መጨረሻ ላይ 9.9 በመቶ ሆኗል፡፡ ለምሳሌ አንድ ትንሽ ህፃን ብቻ በፈረንሳይ ዓይኑ ውስጥ በተገኘ ሳኒታይዘር ሳብያ በሆስፒታል ቆይቶ ህክምና ለመከታተል ተገዶ የነበረ ቢሆንም በ2020 ቁጥሩ ወደ 16 ከፍ ብሏል፡፡ በሌላ ጥናትም ህንድ ውስጥ በሳኒታይዘር ሳብያ ሁለት ትናንሽ ህፃናት ከፍተኛ የዓይን ጤና ችግር ውስጥ ገብተው ነበር፤ የኋላ ኋላ በተደረገላቸው ርብርብ ሙሉ ለሙሉ ቢያገግሙም፡፡
የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘሮች ከፍተኛ የአልኮል መጠን በተለይም በኢታኖል መልኩ ስለሚይዙ ኮርኒያ ተብሎ በሚታወቀው የአይናችን ክፍል ውስጥ ያሉትን አንዳንድ ሕዋሳት ሊገድሉ ይችላሉ፡፡ ትናንሽ ህፃናት ደግሞ ከቁመታቸው ማጠር የተነሳ ሳኒታይዘሩ ሲረጭ ቀጥታ ወደ አይናቸው ተፈናጥሮ የመግባት ዕድሉ ከፍ ስለሚል ለዚህ በተለየ ተጋላጭ ናቸው፡፡ አንዳንድ ህፃናት ደግሞ ይባስ ብሎ ሳኒታይዘሩ እጃቸው ላይ ከተደረገላቸው በኋላ ወዲያው አይናቸውን ይነካካሉ፡፡ ቀዳሚው ስጋት ግን በህዝብ መሰብሰቢያ አካባቢዎች ብዙን ጊዜ ሳኒታይዘር የሚረጨው የህፃናቱ አይን በሚገኝበት ቁመት ገደማ መሆኑ ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ በወርሀ ግንቦት ፈረንሳይ ውስጥ ሳኒታይዘር በአይናቸው ከገባባቸው ህፃናት መካከል 16.4 በመቶው ብቻ በነዚህ ስፍራዎች ቢሆንም ነሀሴ ላይ ግን መጠኑ ወደ 52.4 ሊያድግ ችሏል፡፡
ታድያ ይህን ችግር ለመከላከል ከሳኒታይዘር ይልቅ በማፅዳት ረገድም የተሻለ የሆነውን እጅን በውሃና ሳሙና መታጠብ ቀዳሚ ምርጫ ሊሆንና ወላጆችም የእነርሱ መጠንቀቅ እንዳለ ሆኖ ልጆቻቸው እንዴት ሳኒታይዘር በትክክል መርጨት እንዳለባቸው ማስተማር እንደሚገባ ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡ ሆኖም ሳኒታይዘሩ የህፃናት አይን ውስጥ (ወይም አዋቂ ውስጥም ቢሆን) የሚገባ ከሆነ ተከታዮቹን እርምጃዎች በአስቸኳይ መውሰድ ይገባል፡-
፩. አይናቸውን እንዳያሻሹ ማድረግ (ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ ስለሚያባብሰው)፤
፪. ሳኒታይዘሩ የተረጨበትን አይን ትንሽ ሞቅ ባለ ውሃ ለአስር ደቂቃ ማጠብ፤
፫. ህመሙና ማቃጠሉ ከቀጠለ ወይም የማየት እክል ከገጠማቸው ግን ህፃናቱን በፍጥነት ወደ አይን ሀኪሞች ወይም ድንገተኛ ክፍል ውስጥ ማስገባት ይገባል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
ሁዋዌ ሹፌር አልባ መኪናዎችን የሚያዋራ መንገድ ሰራ
========================
በቻይናዋ ጃንሱ ግዛት ውስጥ ባለቸው የዉሺ ከተማ የተዘረጋው ባለ 4 ኪ.ሜ መንገዱ አሽከርካሪ አልባ አውቶብሶች የሚመላለሱበት ሲሆን የተገጠሙለት የትራፊክ መብራት፣ የመንገድ ዳር ምልክቶች እና ሌሎችም እንደ ራዳር፣ ሴንሰር እና ካሜራ ያሉ ቴክኖሎጂዎቹን ተጠቅሞ ከአውቶብሶቹ በመነጋገር ፍጥነታቸውን እንዲጨምሩ፣ እንዲቀንሱ፣ እንዲቆሙ ብሎም መሰናክሎች ሲያጋጥሙ አቅጣጫን ቀይረው እንዲያልፉ ያስችላቸዋል፡፡ በግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሁዋዌ እና ሌሎች አጋሮች ጥቅም ላይ የሚውለው መንገዱ ተሽከርካሪዎቿን ብልህ እና የተሳሰሩ የማድረጉ የቻይና ሀገራዊ ውጥን አካል ነው፡፡ ታድያ ሀገሪቱም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፎችን ለመምታት አልማለች፤ የመንገድ ትራፊኩ ደህንነት እንዲጠበቅና ሁዋዌን የመሳሰሉ ኩባንያዎቿም በመሰረተ ልማት ግንባታው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል፡፡
ኤክስ-ባስ ተብሎ የዳቦ ስም የወጣላቸው አውቶብሶቹ በመንገዱ ላይ የሚፈጠሩትን ማናቸውንም ነገሮች ከሚመለከትና ውሳኔ ከሚሰጥ የትራፊክ ቁጥጥር ስርዓት ጋራ የተገናኙ ናቸው፡፡ ሆኖም መረጃ ከስርዓቱ ወደ አውቶብሶቹ የሚተላለፍ ብቻ ሳይሆን አውቶብሶቹም በየጊዜው መረጃን ወደ ስርዓቱ የሚልኩና ሰዓታችንን ጠብቀን ወደ ጉዞ መዳረሻችን እንድንደርስ ያስችለናል የሚሉት የትራፊክ መብራትንም ለመምረጥ ጥያቄ የሚያቀርቡ ይሆናል፡፡ ታድያ አውቶብሶቹ በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ ቢሆኑም እንደ አስፈላጊነቱ ሊሾፍራቸው የሚችል አሽከርካሪ አላቸው፡፡
አሜሪካን በሀገር ደህንነት ስጋትነት ከፈረጀችው ጊዜ አንስቶ ዓለም አቀፍ ግፊት ውስጥ የሰነበተው ሁዋዌ አዳዲስ መስኮች ላይ አይኑን ጥሎ እየሰራ ነው፡፡ እዚህም በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ ብልህ ተሽከርካሪዎችን ከመስራት ይልቅ የተሽከርካሪዎቹን አብዮትን ዕውን የሚያደርጉ ሶፍትዌሮችን እና የትስስር ግብዓቶችን ለማቅረብ ተነስቷል፡፡
እራስ ገዝ ተሸከርካሪዎች መንገዶችን ለመቆጣጠር ዓመታትን እንደሚፈጅባቸው ቢገመትም የተለያዩ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎችን እያሳዩን ነው፡፡ ለምሳሌ አማዞን እራስ ገዝ ተሸከርካሪዎቹን በህዝብ ጎዳናዎች ላይ እንዲሞክር ፍቃድ ሲሰጠው አፕልም መሰል መኪናዎችን እስከ አውሮፓውያኑ 2024 እንደሚሰራ ይፋ አውጥቷል፡፡ በቻይናም ባይዱ የቴክኖሎጂ ኩባንያ በቤጂንግ ዙርያ ራስ ገዝ ተሽከርካሪዎችን እየሞከረ ሲሆን የሀገሪቱ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችም መኪናዎችን ያለ አሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ የሚየስችሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮሰሰሮችን እና ቀመሮችን በመስራት ተጠምደዋል፡፡ የሁዋዌ ቴክኖሎጂም ትክክለኛ መረጃን ለተሽከርካሪ፣ እግረኛ እና ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎች ስለ መንገድ ትራፊኩ፣ አየር ፀባይ እና ሊከሰቱ ስለሚችሉ አደጋዎች ወዲያው ወዲያው መረጃን ይሰጣል፡፡
በየ ስምንት ደቂቃው ልዩነት አንድ ሰው በትራፊክ አደጋ የምታጣው ቻይና በዚህ ቴክኖሎጂ እና አስቻይ መሰረተ ልማቶቹ ላይ በማተኮር አደጋን ለመቀነስ ወጥና እየሰራች ናት፡፡
ምንጭ፡ Bloomberg
========================
በቻይናዋ ጃንሱ ግዛት ውስጥ ባለቸው የዉሺ ከተማ የተዘረጋው ባለ 4 ኪ.ሜ መንገዱ አሽከርካሪ አልባ አውቶብሶች የሚመላለሱበት ሲሆን የተገጠሙለት የትራፊክ መብራት፣ የመንገድ ዳር ምልክቶች እና ሌሎችም እንደ ራዳር፣ ሴንሰር እና ካሜራ ያሉ ቴክኖሎጂዎቹን ተጠቅሞ ከአውቶብሶቹ በመነጋገር ፍጥነታቸውን እንዲጨምሩ፣ እንዲቀንሱ፣ እንዲቆሙ ብሎም መሰናክሎች ሲያጋጥሙ አቅጣጫን ቀይረው እንዲያልፉ ያስችላቸዋል፡፡ በግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሁዋዌ እና ሌሎች አጋሮች ጥቅም ላይ የሚውለው መንገዱ ተሽከርካሪዎቿን ብልህ እና የተሳሰሩ የማድረጉ የቻይና ሀገራዊ ውጥን አካል ነው፡፡ ታድያ ሀገሪቱም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፎችን ለመምታት አልማለች፤ የመንገድ ትራፊኩ ደህንነት እንዲጠበቅና ሁዋዌን የመሳሰሉ ኩባንያዎቿም በመሰረተ ልማት ግንባታው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል፡፡
ኤክስ-ባስ ተብሎ የዳቦ ስም የወጣላቸው አውቶብሶቹ በመንገዱ ላይ የሚፈጠሩትን ማናቸውንም ነገሮች ከሚመለከትና ውሳኔ ከሚሰጥ የትራፊክ ቁጥጥር ስርዓት ጋራ የተገናኙ ናቸው፡፡ ሆኖም መረጃ ከስርዓቱ ወደ አውቶብሶቹ የሚተላለፍ ብቻ ሳይሆን አውቶብሶቹም በየጊዜው መረጃን ወደ ስርዓቱ የሚልኩና ሰዓታችንን ጠብቀን ወደ ጉዞ መዳረሻችን እንድንደርስ ያስችለናል የሚሉት የትራፊክ መብራትንም ለመምረጥ ጥያቄ የሚያቀርቡ ይሆናል፡፡ ታድያ አውቶብሶቹ በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ ቢሆኑም እንደ አስፈላጊነቱ ሊሾፍራቸው የሚችል አሽከርካሪ አላቸው፡፡
አሜሪካን በሀገር ደህንነት ስጋትነት ከፈረጀችው ጊዜ አንስቶ ዓለም አቀፍ ግፊት ውስጥ የሰነበተው ሁዋዌ አዳዲስ መስኮች ላይ አይኑን ጥሎ እየሰራ ነው፡፡ እዚህም በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ ብልህ ተሽከርካሪዎችን ከመስራት ይልቅ የተሽከርካሪዎቹን አብዮትን ዕውን የሚያደርጉ ሶፍትዌሮችን እና የትስስር ግብዓቶችን ለማቅረብ ተነስቷል፡፡
እራስ ገዝ ተሸከርካሪዎች መንገዶችን ለመቆጣጠር ዓመታትን እንደሚፈጅባቸው ቢገመትም የተለያዩ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎችን እያሳዩን ነው፡፡ ለምሳሌ አማዞን እራስ ገዝ ተሸከርካሪዎቹን በህዝብ ጎዳናዎች ላይ እንዲሞክር ፍቃድ ሲሰጠው አፕልም መሰል መኪናዎችን እስከ አውሮፓውያኑ 2024 እንደሚሰራ ይፋ አውጥቷል፡፡ በቻይናም ባይዱ የቴክኖሎጂ ኩባንያ በቤጂንግ ዙርያ ራስ ገዝ ተሽከርካሪዎችን እየሞከረ ሲሆን የሀገሪቱ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችም መኪናዎችን ያለ አሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ የሚየስችሉ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፕሮሰሰሮችን እና ቀመሮችን በመስራት ተጠምደዋል፡፡ የሁዋዌ ቴክኖሎጂም ትክክለኛ መረጃን ለተሽከርካሪ፣ እግረኛ እና ሌሎች የመንገድ ተጠቃሚዎች ስለ መንገድ ትራፊኩ፣ አየር ፀባይ እና ሊከሰቱ ስለሚችሉ አደጋዎች ወዲያው ወዲያው መረጃን ይሰጣል፡፡
በየ ስምንት ደቂቃው ልዩነት አንድ ሰው በትራፊክ አደጋ የምታጣው ቻይና በዚህ ቴክኖሎጂ እና አስቻይ መሰረተ ልማቶቹ ላይ በማተኮር አደጋን ለመቀነስ ወጥና እየሰራች ናት፡፡
ምንጭ፡ Bloomberg
በከፍተኛ መጠን እየቀለጠ ያለው የአለማችን በረዶ
********************************
አንድ አዲስ ጥናት በአለማችን ላይ ያለው በረዶ በከፍተኛ መጠን እየቀለጠ መሆኑን ይፋ አደረገ፡፡ በጥናቱም አለማችን ከ1994 እስከ 2017 ድረስ 28 ትሪሊዮን ቶን የበረዶ ግግርን እንዳጣች አሳውቋል፡፡ ይህ በሌላ አገላለጽ መቶ ሜትር ውፍረት ያለው ሙሉ እንግሊዝን ሊሸፍን የሚችል የበረዶ ንጣፍ ማለት ነው፡፡ ጥናቱም የሳተላይት መረጃን በመጠቀም የተሰራ እንደሆነ ተገልጧል፡፡
በሊድስ ዩኒቨርሲቲ አማካኝነት የሚመራው ጥናት ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ውስጥ በአለማችን ያለው የበረዶ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀለጠ እየጠፋ እንደሆነ የሚያሳይ መረጃን ይዞ ወጥቷል፡፡ የቅልጠት መጠኑም በ90ዎቹ በየአመቱ 0.8 ትሪሊዮን ቶን ያክል ሲሆን ከዚያ ወዲህ እስከ 2017 ደግሞ በ1.3 ትሪሊዮን ቶን በየአመቱ የተለካ ነው፡፡ ይህ የበረዶ መቅለጥ በአለማችን ውስጥ የሚገኘውን የባህር ጠለል ልክ ከፍ በማድረግ የጎርፍ አደጋ ስጋትን እየጨመረው ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ከፍተኛ የሆነ የተፈጥሮ ሀብት መጥፋትን እያስከተለ ይገኛል ሲል ጥናቱ አመልክቷል፡፡
በእንግሊዙ የተፈጥሮ ሀብት ምርምር ካውንስል እየተደገፈ የሚሰራው ምርምር ባለፉት 23 ዓመታት በተሰራ ተከታታይ ጥናት የበረዶ ቅልጠት መጠኑ በ65 በመቶ ከፍ ማለቱን አሳይቷል፡፡ በጥናቱ ውስጥ ከፍተኛ የበረዶ ክምችት የሚገኝባቸው የአለማችን ሀገራት የተካተቱ ቢሆንም የቅልጠት መጠኑ ከፍ ብሎ የታየው በአንታርቲካ እና በግሪን ላንድ ነው፡፡ የበረዶ ግግሩ የሚቀልጥባቸው ሁለት ምክንያቶች ሲኖሩ አንደኛው ከከባቢ አየር ጋር የተያያዘው atmospheric melting የሚባለው ሲሆን 68 በመቶ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ መሰረቱን በውቅያኖሶች ላይ ያደረገውና የ32 ድርሻ ያለው oceanic melting ነው፡፡
ከላይ በተገለጸው የቁጥር መረጃ እንደምረዳው የከባቢ አየር ሙቀት መጨመር በአለማችን ላለው የበረዶ ግግር መቅለጥ ከፍተኛውን ድርሻ እየወሰደ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በውቅያኖሶች ላይ ያለውን በረዶ እያቀለጠ የውቅያኖስ ውሃ ከፍተኛ የሆነ የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኝ ያደርገዋል፡፡ የውቅያኖስ ውሃ መሞቅ ደግሞ የአርክቲክ ሙቀት ከመቸውም ጊዜ በላይ እንዲጨምር አድጎታል፡፡ እስካሁን በተሰራው ጥናት በሰሜን ንፍቀ ክበብ የሚገኘው በረዶ ከጠቅላላው 58 በመቶውን ሲሸፍን ቀሪው 42 በመቶ ደግሞ በደቡብ ንፍቀ ክበብ የሚገኝ ነው፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
********************************
አንድ አዲስ ጥናት በአለማችን ላይ ያለው በረዶ በከፍተኛ መጠን እየቀለጠ መሆኑን ይፋ አደረገ፡፡ በጥናቱም አለማችን ከ1994 እስከ 2017 ድረስ 28 ትሪሊዮን ቶን የበረዶ ግግርን እንዳጣች አሳውቋል፡፡ ይህ በሌላ አገላለጽ መቶ ሜትር ውፍረት ያለው ሙሉ እንግሊዝን ሊሸፍን የሚችል የበረዶ ንጣፍ ማለት ነው፡፡ ጥናቱም የሳተላይት መረጃን በመጠቀም የተሰራ እንደሆነ ተገልጧል፡፡
በሊድስ ዩኒቨርሲቲ አማካኝነት የሚመራው ጥናት ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ውስጥ በአለማችን ያለው የበረዶ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀለጠ እየጠፋ እንደሆነ የሚያሳይ መረጃን ይዞ ወጥቷል፡፡ የቅልጠት መጠኑም በ90ዎቹ በየአመቱ 0.8 ትሪሊዮን ቶን ያክል ሲሆን ከዚያ ወዲህ እስከ 2017 ደግሞ በ1.3 ትሪሊዮን ቶን በየአመቱ የተለካ ነው፡፡ ይህ የበረዶ መቅለጥ በአለማችን ውስጥ የሚገኘውን የባህር ጠለል ልክ ከፍ በማድረግ የጎርፍ አደጋ ስጋትን እየጨመረው ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ከፍተኛ የሆነ የተፈጥሮ ሀብት መጥፋትን እያስከተለ ይገኛል ሲል ጥናቱ አመልክቷል፡፡
በእንግሊዙ የተፈጥሮ ሀብት ምርምር ካውንስል እየተደገፈ የሚሰራው ምርምር ባለፉት 23 ዓመታት በተሰራ ተከታታይ ጥናት የበረዶ ቅልጠት መጠኑ በ65 በመቶ ከፍ ማለቱን አሳይቷል፡፡ በጥናቱ ውስጥ ከፍተኛ የበረዶ ክምችት የሚገኝባቸው የአለማችን ሀገራት የተካተቱ ቢሆንም የቅልጠት መጠኑ ከፍ ብሎ የታየው በአንታርቲካ እና በግሪን ላንድ ነው፡፡ የበረዶ ግግሩ የሚቀልጥባቸው ሁለት ምክንያቶች ሲኖሩ አንደኛው ከከባቢ አየር ጋር የተያያዘው atmospheric melting የሚባለው ሲሆን 68 በመቶ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ መሰረቱን በውቅያኖሶች ላይ ያደረገውና የ32 ድርሻ ያለው oceanic melting ነው፡፡
ከላይ በተገለጸው የቁጥር መረጃ እንደምረዳው የከባቢ አየር ሙቀት መጨመር በአለማችን ላለው የበረዶ ግግር መቅለጥ ከፍተኛውን ድርሻ እየወሰደ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በውቅያኖሶች ላይ ያለውን በረዶ እያቀለጠ የውቅያኖስ ውሃ ከፍተኛ የሆነ የፀሐይ ብርሃን እንዲያገኝ ያደርገዋል፡፡ የውቅያኖስ ውሃ መሞቅ ደግሞ የአርክቲክ ሙቀት ከመቸውም ጊዜ በላይ እንዲጨምር አድጎታል፡፡ እስካሁን በተሰራው ጥናት በሰሜን ንፍቀ ክበብ የሚገኘው በረዶ ከጠቅላላው 58 በመቶውን ሲሸፍን ቀሪው 42 በመቶ ደግሞ በደቡብ ንፍቀ ክበብ የሚገኝ ነው፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
በምድር ላይ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ኢንተርኔት ከማግኘታቸው በፊት ጨረቃ የ4G ኢንተርኔት ይኖራት ይሆን
----------------------------------------
ከጥቂት ጊዜያት በፊት ኖኪያ የተባለ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ናሳ በጨረቃ ላይ ለሚያካሂደው የአርተሚስ ፕሮግራም (Artemis program) የ 4G LTE የበይነ መረብ ግንኙነት እንዲዘረጋ መታጨቱ ሲዘገብ ቆይቷል፡፡ በሁለቱ ኩባንያዎች የተደረሰው ስምምነት ለምድር ብቸኛ የተፈጥሮ ሳተላይት በሆነችው ጨረቃ ላይ የ 4G LTE የበይነ መረብ ግንኙነት ለመዘርጋት የሚያስችል የ14.1 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ውልም የተካተተበት ነው፡፡
እንደአውሮፓውያኑ በ2022 ይጠናቀቃል የተባለለት የሁለቱ ኩባንያዎች በጨረቃ ላይ የ 4G ግንኙነት የመዘርጋት ስራ በታቀደው መሰረት የሚካሄድ ከሆነ በጨረቃ ላይ ሊገነባ የሚችለው ይህ ፈጣን የአውተር-መረብ ግንኙነት በምድር ላይ የሚኖሩ 4.5 ቢሊዮን ሰዎች ይህን የመሰለ የበይነ መረብ ግንኙነት ከማግኘታቸው በፊት የሚዘረጋ ፈጣን የበይነ መረብ ግንኙነት ይሆናል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ በአይ ቲ እና በሳይበር ደህንነት መፍትሄዎች ላይ ላይ አዳዲስ መረጃዎችን የሚያወጣው Cisco በቅርቡ ይፋ እንዳደረገው ከአለም አጠቃላይ ህዝብ የበይነ መረብ ግንኙነት ሽፋን ያለው ህዝብ 56 በመቶው ወይም 4.1 ቢሊዮን የሚሆነው ህዝብ ሲሆን ይህ አሃዝ እስከ 2020 መጠናቀቂያ ድረስ ያለውን የሚያካትት ነው፡፡ እንደተቀቋሙ ትንበያ በ2023 የበይነ መረብ ግንኙነት ተደራሽ የሚሆንለት የአለም ህዝብ 5.3 ቢሊዮን የሚሆነው ሲሆን ይህም 2/3ኛውን የአለም ህዝብ ይሸፍናል፡፡
Cisco ብትንበያው ያስቀመጠው የበይነ መረብ ተደራሽነት እንደ 4G ያለ ጥራት ያለው የበይነ መረብ ግንኙነት ሳይሆን በ 2G እና 3G መካከል ያለ መደበኛ የበይነ መረብ ግንኙነት ነው፡፡ በአንፃሩ በ2022 ይጠናቀቃል የተባለለት የሁለቱ ተቋማት ተልዕኮ እጅግ ፈጣን ከሚባለው የ5G ስርዓት በአንድ ደረጃ ብቻ ዝቅ ያለውን ፈጣን የ4G ስርዓት የሚስተዋውቅ ሲሆን በጨረቃ ላይ ለሚካሄደው ፈጣን የመረጃ ልውውጥ ትልቅ መሰረት በመጣልም በምድር ላይ የሚኖሩ ብዙ ቢሊዮን ሰዎች ለግንኙነቱ ተደራሽ ከመሆናቸው በፊት ጨረቃን የ4G ባለቤት የሚያደርጋት ልዩ ተልዕኮ ይሆናል ፡፡
ይህ የበይነ መረብ ተደራሽነት ከአጠቃላዩ የአለም ክፍል በአፍሪካ እና በእስያ በዝቅተኛ ደረጃ መገኘቱ የሚታወቅ ሲሆን ዘርፉን ይበልጥ እንዲሰራራ ለማድረግም ከፖሊሲና ከህግ ማዕቀፎች አንስቶ አስፈላጊ የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴዎችን በማስፋፋት እና ሌሎች የማሻሻያ ስራዎችን በማካሄድ ዝርፉን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚቻል በብዙዎች ይገለጻል፡፡
ምንጭ፡ Truth theory
----------------------------------------
ከጥቂት ጊዜያት በፊት ኖኪያ የተባለ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ናሳ በጨረቃ ላይ ለሚያካሂደው የአርተሚስ ፕሮግራም (Artemis program) የ 4G LTE የበይነ መረብ ግንኙነት እንዲዘረጋ መታጨቱ ሲዘገብ ቆይቷል፡፡ በሁለቱ ኩባንያዎች የተደረሰው ስምምነት ለምድር ብቸኛ የተፈጥሮ ሳተላይት በሆነችው ጨረቃ ላይ የ 4G LTE የበይነ መረብ ግንኙነት ለመዘርጋት የሚያስችል የ14.1 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ውልም የተካተተበት ነው፡፡
እንደአውሮፓውያኑ በ2022 ይጠናቀቃል የተባለለት የሁለቱ ኩባንያዎች በጨረቃ ላይ የ 4G ግንኙነት የመዘርጋት ስራ በታቀደው መሰረት የሚካሄድ ከሆነ በጨረቃ ላይ ሊገነባ የሚችለው ይህ ፈጣን የአውተር-መረብ ግንኙነት በምድር ላይ የሚኖሩ 4.5 ቢሊዮን ሰዎች ይህን የመሰለ የበይነ መረብ ግንኙነት ከማግኘታቸው በፊት የሚዘረጋ ፈጣን የበይነ መረብ ግንኙነት ይሆናል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ በአይ ቲ እና በሳይበር ደህንነት መፍትሄዎች ላይ ላይ አዳዲስ መረጃዎችን የሚያወጣው Cisco በቅርቡ ይፋ እንዳደረገው ከአለም አጠቃላይ ህዝብ የበይነ መረብ ግንኙነት ሽፋን ያለው ህዝብ 56 በመቶው ወይም 4.1 ቢሊዮን የሚሆነው ህዝብ ሲሆን ይህ አሃዝ እስከ 2020 መጠናቀቂያ ድረስ ያለውን የሚያካትት ነው፡፡ እንደተቀቋሙ ትንበያ በ2023 የበይነ መረብ ግንኙነት ተደራሽ የሚሆንለት የአለም ህዝብ 5.3 ቢሊዮን የሚሆነው ሲሆን ይህም 2/3ኛውን የአለም ህዝብ ይሸፍናል፡፡
Cisco ብትንበያው ያስቀመጠው የበይነ መረብ ተደራሽነት እንደ 4G ያለ ጥራት ያለው የበይነ መረብ ግንኙነት ሳይሆን በ 2G እና 3G መካከል ያለ መደበኛ የበይነ መረብ ግንኙነት ነው፡፡ በአንፃሩ በ2022 ይጠናቀቃል የተባለለት የሁለቱ ተቋማት ተልዕኮ እጅግ ፈጣን ከሚባለው የ5G ስርዓት በአንድ ደረጃ ብቻ ዝቅ ያለውን ፈጣን የ4G ስርዓት የሚስተዋውቅ ሲሆን በጨረቃ ላይ ለሚካሄደው ፈጣን የመረጃ ልውውጥ ትልቅ መሰረት በመጣልም በምድር ላይ የሚኖሩ ብዙ ቢሊዮን ሰዎች ለግንኙነቱ ተደራሽ ከመሆናቸው በፊት ጨረቃን የ4G ባለቤት የሚያደርጋት ልዩ ተልዕኮ ይሆናል ፡፡
ይህ የበይነ መረብ ተደራሽነት ከአጠቃላዩ የአለም ክፍል በአፍሪካ እና በእስያ በዝቅተኛ ደረጃ መገኘቱ የሚታወቅ ሲሆን ዘርፉን ይበልጥ እንዲሰራራ ለማድረግም ከፖሊሲና ከህግ ማዕቀፎች አንስቶ አስፈላጊ የመሰረተ ልማት እንቅስቃሴዎችን በማስፋፋት እና ሌሎች የማሻሻያ ስራዎችን በማካሄድ ዝርፉን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚቻል በብዙዎች ይገለጻል፡፡
ምንጭ፡ Truth theory
የመስኖ ፕሮጀክቶቻችን ተደጋጋሚ ውድቀት
======================
ኢትዮጵያን ጨምሮ በ24 የሰሃራ በታች አፍሪካዊያን ሀገራት ባለፉት 60 ዓመታት ውስጥ የተተገበሩ ትላልቅ የመስኖ ልማት ስራዎች ቃል በተገባላቸው መሰረት ውጤታማ ለመሆን አለመቻላቸውን የኔቸር ጆርናል ላይ የወጣ አዲስ ጥናት አመላከተ፡፡ የእንግሊዙ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ማንቼስተር ምሁራን በአካባቢው ከአውሮፓውያኑ 1948 እስከ 2008 ድረስ ባሉት 60 ዓመታት ውስጥ የተተገበሩ 79 የመስኖ ፕሮጀክቶችን (አምስቱ ከኢትዮጵያ) ቀዳሚ ውጥን የሚያስቀምጥ መረጃ ያሰባሰቡ ሲሆን በመቀጠልም የሳተላይት መረጃን በመጠቀም የመስኖ ልማት ስራዎቹ ምን ያህል መሬትን ማልማት እንደቻሉ አመሳክረዋል፡፡
በውጤቱ ማረጋገጥ እንደቻሉት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶቹ አስከፊ ሊባል በሚችል መልኩ ቀድሞ ከተቀመጠላቸው ግብ እጅግ ያነሰ ውጤትን አሳይተዋል፡፡ በዚህም ፕሮጀክቶቹ ሲወጠኑ እንሸፍነዋለን ካሉት መሬት ውስጥ በአማካኝ ማልማት የቻሉት 16 በመቶ የሚሆነውን ብቻ ሲሆን ቀድሞ ካቀዱት መሬት ከ80 በመቶ በላዩን መሸፈን የቻሉት ፕሮጀክቶች ቁጥር ደግሞ ከ20 አይበልጥም፡፡ በተጨማሪም ከ79ኙ ፕሮጀክቶች 16ቱ ሙሉ ለሙሉ እንዲቋረጡ ሆኗል፡፡ ነገሩን አሳዛኝ የሚያደርገው በ60 ዓመታቱ ውስጥ ምንም አይነት የውጤት መሻሻል እየታየ አለመሄዱ ነው፡፡
ይህ ውድቀት ከፕሮጀክቶቹ ግዝፈት አልያም ከአካባቢው የአየር ንብረት ለውጥ ጋራ የተያዘ አይደለም፡፡ ከዚህ ይልቅ የሀገራቱ የፖለቲካ አለመረጋጋት ቀዳሚው መንስዔ መሆኑን የጥናት ቡድኑ ያምናል፡፡ የተረጋጋ አስተዳደር ያለባቸው ሀገራት የሚገኙ ፕሮጀክቶችም የውድቀት ዕድላቸው አነስ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በሌላ መልኩ ፕሮጀክቶቹ ሲወጠኑ የምግብ ደህንነትን ከማረጋገጥ በዘለለ ምጣኔ ሀብታዊ ዓላማን ባለማንገባቸው ዝቅተኛ የገበያ ዋጋ ያላቸው ምርቶችን በመስጠት ተገድበዋል፡፡ በተጨማሪም ፕሮጀክቶቹ ሲታቀዱ በተዛባ አውንታዊ አመለካከት የተሞሉ እና ፖለቲካውም በወረቀት ላይ ትርፍን የሚያሳዩትን በመሻቱ ሳብያ መሬት ላይ ያለውን ዕውነት የሚመለከቱ ካለመሆናቸው በተጨማሪ ስራዎች በዋናነት የሚመሩት ቴክኒካል ዕውቀት፣ ከባቢያዊ ግንዛቤ እና የገንዘብ አቅርቦት በሚያጥራቸው ማዕከላዊያን የመንግስት ሰራተኞች ነው፡፡
ሆኖም በአካባቢው አሁንም ተረጋግተው እንደሀገር መቆም በተሳናቸው ሀገራት ጭምር እነዚህ በሄክታር (የሚለማ መሬት) በአማካኝ 20 ሺህ ዶላር ወጪን የሚያስወጡ መሰል ፕሮጀክቶች በስፋት ተወጥነው እየተሰራባቸው ይገኛሉ፡፡ መንግስታት እና ዓለም አቀፍ ተቋማትም በአካባቢው ትላልቅ የመስኖ ስራዎች ላይ ገንዘብ ፈገሰስ በማድረግ እንደ ውሃ ማስተላለፍያና ግድብ ያሉትንም እየሰሩ ናቸው፡፡ ይህንንም ተከትሎ ግዙፍ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ከፍተኛ የገንዘብ ወጪን የሚያስወጡና በአካባቢው ህዝብ ላይም ቀላል የማይባል ተፅዕንዖን የሚያደርሱ እንደመሆናቸው መጠን ፕሮጀክቶቹን ወጪ ቆጣቢና በዘላቂነት ከአከባቢያቸው የተስማሙ ለማድረግ ከዚህም በላይ ጥልቅ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ሲሉ የዚህ ጥናት ባለቤቶች ምክራቸውን መለገሳቸውን ጥናቱን አስመልክተው በኔቸር እና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ማንቼስተር የወጡት ዘገባዎች ያመላክታሉ፡፡ ሙሉ ጥናቱን በ nature መፅሄት ያገኛሉ
======================
ኢትዮጵያን ጨምሮ በ24 የሰሃራ በታች አፍሪካዊያን ሀገራት ባለፉት 60 ዓመታት ውስጥ የተተገበሩ ትላልቅ የመስኖ ልማት ስራዎች ቃል በተገባላቸው መሰረት ውጤታማ ለመሆን አለመቻላቸውን የኔቸር ጆርናል ላይ የወጣ አዲስ ጥናት አመላከተ፡፡ የእንግሊዙ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ማንቼስተር ምሁራን በአካባቢው ከአውሮፓውያኑ 1948 እስከ 2008 ድረስ ባሉት 60 ዓመታት ውስጥ የተተገበሩ 79 የመስኖ ፕሮጀክቶችን (አምስቱ ከኢትዮጵያ) ቀዳሚ ውጥን የሚያስቀምጥ መረጃ ያሰባሰቡ ሲሆን በመቀጠልም የሳተላይት መረጃን በመጠቀም የመስኖ ልማት ስራዎቹ ምን ያህል መሬትን ማልማት እንደቻሉ አመሳክረዋል፡፡
በውጤቱ ማረጋገጥ እንደቻሉት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶቹ አስከፊ ሊባል በሚችል መልኩ ቀድሞ ከተቀመጠላቸው ግብ እጅግ ያነሰ ውጤትን አሳይተዋል፡፡ በዚህም ፕሮጀክቶቹ ሲወጠኑ እንሸፍነዋለን ካሉት መሬት ውስጥ በአማካኝ ማልማት የቻሉት 16 በመቶ የሚሆነውን ብቻ ሲሆን ቀድሞ ካቀዱት መሬት ከ80 በመቶ በላዩን መሸፈን የቻሉት ፕሮጀክቶች ቁጥር ደግሞ ከ20 አይበልጥም፡፡ በተጨማሪም ከ79ኙ ፕሮጀክቶች 16ቱ ሙሉ ለሙሉ እንዲቋረጡ ሆኗል፡፡ ነገሩን አሳዛኝ የሚያደርገው በ60 ዓመታቱ ውስጥ ምንም አይነት የውጤት መሻሻል እየታየ አለመሄዱ ነው፡፡
ይህ ውድቀት ከፕሮጀክቶቹ ግዝፈት አልያም ከአካባቢው የአየር ንብረት ለውጥ ጋራ የተያዘ አይደለም፡፡ ከዚህ ይልቅ የሀገራቱ የፖለቲካ አለመረጋጋት ቀዳሚው መንስዔ መሆኑን የጥናት ቡድኑ ያምናል፡፡ የተረጋጋ አስተዳደር ያለባቸው ሀገራት የሚገኙ ፕሮጀክቶችም የውድቀት ዕድላቸው አነስ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በሌላ መልኩ ፕሮጀክቶቹ ሲወጠኑ የምግብ ደህንነትን ከማረጋገጥ በዘለለ ምጣኔ ሀብታዊ ዓላማን ባለማንገባቸው ዝቅተኛ የገበያ ዋጋ ያላቸው ምርቶችን በመስጠት ተገድበዋል፡፡ በተጨማሪም ፕሮጀክቶቹ ሲታቀዱ በተዛባ አውንታዊ አመለካከት የተሞሉ እና ፖለቲካውም በወረቀት ላይ ትርፍን የሚያሳዩትን በመሻቱ ሳብያ መሬት ላይ ያለውን ዕውነት የሚመለከቱ ካለመሆናቸው በተጨማሪ ስራዎች በዋናነት የሚመሩት ቴክኒካል ዕውቀት፣ ከባቢያዊ ግንዛቤ እና የገንዘብ አቅርቦት በሚያጥራቸው ማዕከላዊያን የመንግስት ሰራተኞች ነው፡፡
ሆኖም በአካባቢው አሁንም ተረጋግተው እንደሀገር መቆም በተሳናቸው ሀገራት ጭምር እነዚህ በሄክታር (የሚለማ መሬት) በአማካኝ 20 ሺህ ዶላር ወጪን የሚያስወጡ መሰል ፕሮጀክቶች በስፋት ተወጥነው እየተሰራባቸው ይገኛሉ፡፡ መንግስታት እና ዓለም አቀፍ ተቋማትም በአካባቢው ትላልቅ የመስኖ ስራዎች ላይ ገንዘብ ፈገሰስ በማድረግ እንደ ውሃ ማስተላለፍያና ግድብ ያሉትንም እየሰሩ ናቸው፡፡ ይህንንም ተከትሎ ግዙፍ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ከፍተኛ የገንዘብ ወጪን የሚያስወጡና በአካባቢው ህዝብ ላይም ቀላል የማይባል ተፅዕንዖን የሚያደርሱ እንደመሆናቸው መጠን ፕሮጀክቶቹን ወጪ ቆጣቢና በዘላቂነት ከአከባቢያቸው የተስማሙ ለማድረግ ከዚህም በላይ ጥልቅ ጥናቶች ያስፈልጋሉ ሲሉ የዚህ ጥናት ባለቤቶች ምክራቸውን መለገሳቸውን ጥናቱን አስመልክተው በኔቸር እና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ማንቼስተር የወጡት ዘገባዎች ያመላክታሉ፡፡ ሙሉ ጥናቱን በ nature መፅሄት ያገኛሉ
በሰው ሰራሽ ማዳቀል የተወለደው የአንበሳ ደቦል
***********************
በሲንጋፖር ሰው ሰራሽ የማዳቀል ዘዴን በመጠቀም የአንበሳ ደቦል መወለዱ ተነገረ፡፡ ሲንጋፖር ለከተማዋ የመጀመሪያ የተባለለትን ሲምባ የተሰኘ የአንበሳ ደቦል ወደ እንስሳት ማቆያዋ ተቀብላለች፡፡ ከዚህ በፊት በ2018 በደቡብ አፍሪካ ተመሳሳይ የማዳቀል ስራ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለት የአንበሳ ደቦሎች የተሞከረ ሲሆን ለአንበሳ ዝርያ የማዳቀል ስራ ብዙውን ጊዜ ያልተለመደ ነው፡፡
ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በአለማችን ያለው የአንበሶች ቁጥር በ40 በመቶ ያሽቆለቆለ ሲሆን እንደ አለማቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ህብረት መረጃ ከሆነ በአሁኑ ወቅት ከ23,000 እስከ 39,000 አንበሶች በምድራችን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ሲምባ የተሰኘው የሲንጋፖር የአንበሳ ግልገል ከአንድ እድሜ ጠገብ የአፍሪካ አንበሳ በተወሰደ ዘር የተዳቀለ ነው፡፡ የዚህ አንበሳ ስያሜ በዲዝኒ አኒሜሽን ፊልም (ዘ ላዮን ኪንግ) ካለው ዋና ገጸ-ባህሪ የተወሰደ ነው፡፡
በሚያሳዝን ሁኔታ የሲምባ አባት ሙሳፋ እጅግ ተዳክሞ የነበረ በመሆኑ የማዳቀል ስራውን እንዳልተቋቋመው የእንስሳት ጥበቃ ተቋሙ ተናግሯል፡፡ ሙሳፋ በተመሳሳይ ስሙን የወረሰው በእንስሳት ዙሪያ ከተሰራ የአኒሜሽን ፊልም ነው፡፡
ባሳለፍነው ጥቅምት ወር የተወለደው ሲምባ በእናቱ ካይላ እና በእንስሳት ጥበቃ ተቋሙ ሰራተኞች ጥበቃ እና እንክብካቤ እየተደረገለት ነው፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
***********************
በሲንጋፖር ሰው ሰራሽ የማዳቀል ዘዴን በመጠቀም የአንበሳ ደቦል መወለዱ ተነገረ፡፡ ሲንጋፖር ለከተማዋ የመጀመሪያ የተባለለትን ሲምባ የተሰኘ የአንበሳ ደቦል ወደ እንስሳት ማቆያዋ ተቀብላለች፡፡ ከዚህ በፊት በ2018 በደቡብ አፍሪካ ተመሳሳይ የማዳቀል ስራ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለት የአንበሳ ደቦሎች የተሞከረ ሲሆን ለአንበሳ ዝርያ የማዳቀል ስራ ብዙውን ጊዜ ያልተለመደ ነው፡፡
ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በአለማችን ያለው የአንበሶች ቁጥር በ40 በመቶ ያሽቆለቆለ ሲሆን እንደ አለማቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ህብረት መረጃ ከሆነ በአሁኑ ወቅት ከ23,000 እስከ 39,000 አንበሶች በምድራችን ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ሲምባ የተሰኘው የሲንጋፖር የአንበሳ ግልገል ከአንድ እድሜ ጠገብ የአፍሪካ አንበሳ በተወሰደ ዘር የተዳቀለ ነው፡፡ የዚህ አንበሳ ስያሜ በዲዝኒ አኒሜሽን ፊልም (ዘ ላዮን ኪንግ) ካለው ዋና ገጸ-ባህሪ የተወሰደ ነው፡፡
በሚያሳዝን ሁኔታ የሲምባ አባት ሙሳፋ እጅግ ተዳክሞ የነበረ በመሆኑ የማዳቀል ስራውን እንዳልተቋቋመው የእንስሳት ጥበቃ ተቋሙ ተናግሯል፡፡ ሙሳፋ በተመሳሳይ ስሙን የወረሰው በእንስሳት ዙሪያ ከተሰራ የአኒሜሽን ፊልም ነው፡፡
ባሳለፍነው ጥቅምት ወር የተወለደው ሲምባ በእናቱ ካይላ እና በእንስሳት ጥበቃ ተቋሙ ሰራተኞች ጥበቃ እና እንክብካቤ እየተደረገለት ነው፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
በስልክ ንግግር ወቅት አላስፈላጊ ድምፆችን የሚያስወግደው መተግበሪያ
--------------------------------------
ባለፈው አመት ኮቪድ-19 ይዞት በመጣው መዘዝ ምክንያት ብዙዎች ከቤታቸው ሆነው ስራዎችን እንዲያካሂዱ ተገደው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ከስራ ጋር የተያያዙ የመረጃ ልውውጦችን ለማካሄድ አንደ መደበኛ ስልክ፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ እና ሌሎች የመገናኛ ቴክኖሎጂዎች በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ታዲያ በዚህ የግንኙነት ሂደት ውስጥ ብዙዎች ሲቸገሩበት የነበረው ጉዳይ ባሉበት አካባቢ በሚሰሙ አላስፈላጊ ድምፆች ወይም (noises) የስልክ ግንኙነታቸው ተደጋግሞ መቋረጡ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ብዙዎቻችን መደበኛ ስልክ በምንጠቀምበት ወቅትም በተደጋጋሚ የሚያጋጥመን ችግር ሲሆን አዲሱ መተግበሪያም ቀላል መፍትሄን ያበጀ ይመስላል፡፡
the Krisp noise cancelling app በሚል የተሰየመው ይህ መተግበሪያ በመላው አለም ከሚገኙ ቴሌኮሚዩተሮች ጋር በጋራ ለመስራት በመቻሉ በቤታቸው ሆነው የሚሰሩ ሰዎች በመተግበሪያው የጠራ የድምፅ ሲስተም ወይም (crystal-clear audio) አማካኝነት ቤቶቻቸውን ፀጥ ወዳለ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለመቀየር ያስችላቸዋል፡፡ መተግበሪያው ከ800 በላይ በሚሆኑ አንደ ዙም፣ ስካይፒ እና ሚት ባሉ የመገናኛ መተግበሪያዎች ላይ መጠቀም የሚቻል ሲሆን በስልክ ንግግር ወቅት ከሁለቱም አካላት የሚሰሙ አዋኪ ድምፆችን ለይቶ ለማስወገድም የሚያስችል ነው፡፡
ይህ መተግበሪያ አላስፈላጊ ድምፆችን አጣርቶ ለማስወገድ የሚችለው በተገጠመለት ጥልቅ የነርቭ አውታረመረብ ወይም (Deep Neural Network) አማካኝነት ሲሆን ይህም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት ውስጥ ውስብስብ ከሚባሉት ቴክኖሎጂዎች አንዱ ነው፡፡ መተግበሪያውን የሰሩት ባለሙያዎች እንደሚያስረዱት አዲሱ መተግበሪያ ከሌሎች ተመሳሳይ ምርቶች የሚለይበት ዋና ምክንያት ከሚጠቀመው ውስብስብ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት በተጨማሪ 20 ሺህ ድምፆችን እና 50 ሺ ተናጋሪዎችን በአንድ ጊዜ ለመለየት በመቻሉ ነው ይላሉ፡፡ ይህ ደግሞ እስካሁን ከተሰሩት አላስፈላጊ ድምፅ ማስወገጃ (noise cancelling) ስርዓቶች በቀዳሚነት አንዲቀመጥ ያስቸላዋል፡፡
የመተግበሪያው የአሰራር ሂደት ለተጠቃሚዎች ብዙ አማራጮችን እንዲያገኙ የሚስችላቸው ሲሆን ከግላዊ ጥበቃ ጋር በተያያዘም ምንም አይነት ክፍትት እንዳይኖርበት ተደርጎ መሰራቱን ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡
ምንጭ፡ Futurism
--------------------------------------
ባለፈው አመት ኮቪድ-19 ይዞት በመጣው መዘዝ ምክንያት ብዙዎች ከቤታቸው ሆነው ስራዎችን እንዲያካሂዱ ተገደው ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ ከስራ ጋር የተያያዙ የመረጃ ልውውጦችን ለማካሄድ አንደ መደበኛ ስልክ፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ እና ሌሎች የመገናኛ ቴክኖሎጂዎች በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ታዲያ በዚህ የግንኙነት ሂደት ውስጥ ብዙዎች ሲቸገሩበት የነበረው ጉዳይ ባሉበት አካባቢ በሚሰሙ አላስፈላጊ ድምፆች ወይም (noises) የስልክ ግንኙነታቸው ተደጋግሞ መቋረጡ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ብዙዎቻችን መደበኛ ስልክ በምንጠቀምበት ወቅትም በተደጋጋሚ የሚያጋጥመን ችግር ሲሆን አዲሱ መተግበሪያም ቀላል መፍትሄን ያበጀ ይመስላል፡፡
the Krisp noise cancelling app በሚል የተሰየመው ይህ መተግበሪያ በመላው አለም ከሚገኙ ቴሌኮሚዩተሮች ጋር በጋራ ለመስራት በመቻሉ በቤታቸው ሆነው የሚሰሩ ሰዎች በመተግበሪያው የጠራ የድምፅ ሲስተም ወይም (crystal-clear audio) አማካኝነት ቤቶቻቸውን ፀጥ ወዳለ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለመቀየር ያስችላቸዋል፡፡ መተግበሪያው ከ800 በላይ በሚሆኑ አንደ ዙም፣ ስካይፒ እና ሚት ባሉ የመገናኛ መተግበሪያዎች ላይ መጠቀም የሚቻል ሲሆን በስልክ ንግግር ወቅት ከሁለቱም አካላት የሚሰሙ አዋኪ ድምፆችን ለይቶ ለማስወገድም የሚያስችል ነው፡፡
ይህ መተግበሪያ አላስፈላጊ ድምፆችን አጣርቶ ለማስወገድ የሚችለው በተገጠመለት ጥልቅ የነርቭ አውታረመረብ ወይም (Deep Neural Network) አማካኝነት ሲሆን ይህም በሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት ውስጥ ውስብስብ ከሚባሉት ቴክኖሎጂዎች አንዱ ነው፡፡ መተግበሪያውን የሰሩት ባለሙያዎች እንደሚያስረዱት አዲሱ መተግበሪያ ከሌሎች ተመሳሳይ ምርቶች የሚለይበት ዋና ምክንያት ከሚጠቀመው ውስብስብ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስርዓት በተጨማሪ 20 ሺህ ድምፆችን እና 50 ሺ ተናጋሪዎችን በአንድ ጊዜ ለመለየት በመቻሉ ነው ይላሉ፡፡ ይህ ደግሞ እስካሁን ከተሰሩት አላስፈላጊ ድምፅ ማስወገጃ (noise cancelling) ስርዓቶች በቀዳሚነት አንዲቀመጥ ያስቸላዋል፡፡
የመተግበሪያው የአሰራር ሂደት ለተጠቃሚዎች ብዙ አማራጮችን እንዲያገኙ የሚስችላቸው ሲሆን ከግላዊ ጥበቃ ጋር በተያያዘም ምንም አይነት ክፍትት እንዳይኖርበት ተደርጎ መሰራቱን ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡
ምንጭ፡ Futurism
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
============
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከዚህ በታች ለተገለፁት የስራ መደቦች ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡፡
የምዝገባ ቦታ፡- አራት ኪሎ ከፓርላማ ፊትለፊት ከሚገኘው የትራፊክ መብራት ወረድ ብሎ፣ አልያም በ http://recruit.techin.gov.et/ በመግባትና ቅድሚያ ሬጂስተር በማድረግ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
የመመዝገቢያ ቀን፡- ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 28 2013 ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ
በምዝገባ ወቅት መቅረብ የሚገባቸው ማስረጃዎች፡- ለሁሉም የስራ መደቦች የትምህርትና አግባብ ያለው የስራ ልምድ ማስረጃዎች ዋናውና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ
መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የተሰጡ የስራ ልምዶች ተቀባይነት የሚኖራው ተገቢውን የመንግስት ግብር መከፈሉን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ሲቀርቡ ብቻ ነው፡፡
ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ በ0118547758 ይጠቀሙ
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት
============
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከዚህ በታች ለተገለፁት የስራ መደቦች ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል፡፡
የምዝገባ ቦታ፡- አራት ኪሎ ከፓርላማ ፊትለፊት ከሚገኘው የትራፊክ መብራት ወረድ ብሎ፣ አልያም በ http://recruit.techin.gov.et/ በመግባትና ቅድሚያ ሬጂስተር በማድረግ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
የመመዝገቢያ ቀን፡- ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 28 2013 ድረስ ባሉት ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ
በምዝገባ ወቅት መቅረብ የሚገባቸው ማስረጃዎች፡- ለሁሉም የስራ መደቦች የትምህርትና አግባብ ያለው የስራ ልምድ ማስረጃዎች ዋናውና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ
መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የተሰጡ የስራ ልምዶች ተቀባይነት የሚኖራው ተገቢውን የመንግስት ግብር መከፈሉን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ሲቀርቡ ብቻ ነው፡፡
ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ በ0118547758 ይጠቀሙ
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት