አዲሱን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፖሊሲ ክለሳን አስመልክቶ የተደረገው ምክክር
=====================
ለአዲሱ ፖሊሲ ክለሳ ግብዓት ይሆን ዘንድ ዛሬ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተካሄደው ምክክሩ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የተውጣጡ ተሳታፊዎችን ተሳታፊ ያደረገ ነበር፡፡ በምክክሩ ላይ በሚኒስቴሩ የፖሊሲና ፊውቸር ፕላኒንግ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ደስታ አበራ ቀድሞ በስራ ላይ ስለነበረው እንዲሁም ክለሳ ተደጎበት በመጣው ፖሊሲ ላይ ዝርዝር ማብራርያ ለታዳሚያኑ አቅርበዋል፡፡ የቀድሞው ፖሊሲ ችግሮች ቢኖሩበትም ምጣኔ-ሐብታዊ ዕድገት ማስመዝቡን የገለፁት አቶ ደስታ አጋጠሙት የተባሉት ተግዳሮቶችን በዝርዝር አስቀምጠዋል፡፡ ለአዲሱ ፖሊሲ ክለሳ መነሻ ሁኔታዎች ሆነው የተቀመጡትን ጉዳዮች እንዲሁም ክለሳው ሲሰራ የተከተላቸው ፍልስፍናዎች በአቶ ደስታ ገለፃ ውስጥ ተካተው ቀርበዋል፡፡
የፖሊሲ ክለሳው ታድያ በዋናነት ተግባር ላይ የቆየውን ፖሊሲ ድክመቶች በማሻሻል ላይ ያተኮረ ነው፡፡ እኛም 2012 እና በያዝነው ዓመት ታትመው ለህዝብ በደረሱት 18 እና 19ኛ እትም የቴክ-ሳይንስ መፅሔቶቻችን ላይ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲውን በስፋት መቃኘታችን ይታወሳል፡፡ በሁለቱ ተከታታይ ፅሁፎች ዳሰሳ ከተደረገባቸው የፖሊሲው አቅጣጫና ስትራቴጂ፣ ትግበራ፣ አፈፃፀም እንዲሁም ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች በተጨማሪ አሉበት የሚባሉ ክፍተቶችም በስፋት ተዳሰውበት ነበር፡፡ እዚህ ላይ ከተጠቀሱት ክፍተቶች ውስጥ በዋናነት ፖሊሲው ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቶ ከማላመድ ባሻገር ለኢኖቬሽን የሚገባውን ትኩረት አለመስጠቱ፣ ሀገር በቀል ዕውቀት ላይ በተገቢ መልኩ አለመስራቱ እንዲሁም የፖሊሲው ዕቅድ እና አተገባበር እርስ በእርስ መጣጣም አለመቻላቸው ይጠቀሳል፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች ይፈታል የተባለለት አዲሱ የፖሊሲ ረቂቅ “በ2040 ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ለኢትዮጵያ ብልጽግና ዋነኛ መሣሪያ ሆኖ ማየት” የሚል ርዕይን አስቀምጦ ሲነሳ የሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሰው ሃብት ልማት፣ አካባቢዊ ማህበራዊና ባህላዊ ልማት፣ የኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልማት እንዲሁም አይ.ሲ.ቲ ልማት እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ጨምሮ በ12 ቁልፍ ናቸው ባላቸው ጉዳዮች ላይ ስትራቴጂዎችን የቀረፀ ነው፡፡
በዛሬው ምክክር ላይ ከገለፃው ባሻገር ከተጠሪ ተቋማት የመጡ ተሳታፊዎች በፖሊሲ ክለሳው ላይ ግብዓት የሚሆኑ አስተያየቶች የተሰጡበት ውይይትን አድርገዋል፡፡
=====================
ለአዲሱ ፖሊሲ ክለሳ ግብዓት ይሆን ዘንድ ዛሬ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተካሄደው ምክክሩ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የተውጣጡ ተሳታፊዎችን ተሳታፊ ያደረገ ነበር፡፡ በምክክሩ ላይ በሚኒስቴሩ የፖሊሲና ፊውቸር ፕላኒንግ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ደስታ አበራ ቀድሞ በስራ ላይ ስለነበረው እንዲሁም ክለሳ ተደጎበት በመጣው ፖሊሲ ላይ ዝርዝር ማብራርያ ለታዳሚያኑ አቅርበዋል፡፡ የቀድሞው ፖሊሲ ችግሮች ቢኖሩበትም ምጣኔ-ሐብታዊ ዕድገት ማስመዝቡን የገለፁት አቶ ደስታ አጋጠሙት የተባሉት ተግዳሮቶችን በዝርዝር አስቀምጠዋል፡፡ ለአዲሱ ፖሊሲ ክለሳ መነሻ ሁኔታዎች ሆነው የተቀመጡትን ጉዳዮች እንዲሁም ክለሳው ሲሰራ የተከተላቸው ፍልስፍናዎች በአቶ ደስታ ገለፃ ውስጥ ተካተው ቀርበዋል፡፡
የፖሊሲ ክለሳው ታድያ በዋናነት ተግባር ላይ የቆየውን ፖሊሲ ድክመቶች በማሻሻል ላይ ያተኮረ ነው፡፡ እኛም 2012 እና በያዝነው ዓመት ታትመው ለህዝብ በደረሱት 18 እና 19ኛ እትም የቴክ-ሳይንስ መፅሔቶቻችን ላይ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲውን በስፋት መቃኘታችን ይታወሳል፡፡ በሁለቱ ተከታታይ ፅሁፎች ዳሰሳ ከተደረገባቸው የፖሊሲው አቅጣጫና ስትራቴጂ፣ ትግበራ፣ አፈፃፀም እንዲሁም ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች በተጨማሪ አሉበት የሚባሉ ክፍተቶችም በስፋት ተዳሰውበት ነበር፡፡ እዚህ ላይ ከተጠቀሱት ክፍተቶች ውስጥ በዋናነት ፖሊሲው ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቶ ከማላመድ ባሻገር ለኢኖቬሽን የሚገባውን ትኩረት አለመስጠቱ፣ ሀገር በቀል ዕውቀት ላይ በተገቢ መልኩ አለመስራቱ እንዲሁም የፖሊሲው ዕቅድ እና አተገባበር እርስ በእርስ መጣጣም አለመቻላቸው ይጠቀሳል፡፡
ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮች ይፈታል የተባለለት አዲሱ የፖሊሲ ረቂቅ “በ2040 ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ለኢትዮጵያ ብልጽግና ዋነኛ መሣሪያ ሆኖ ማየት” የሚል ርዕይን አስቀምጦ ሲነሳ የሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ሰው ሃብት ልማት፣ አካባቢዊ ማህበራዊና ባህላዊ ልማት፣ የኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልማት እንዲሁም አይ.ሲ.ቲ ልማት እና ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ጨምሮ በ12 ቁልፍ ናቸው ባላቸው ጉዳዮች ላይ ስትራቴጂዎችን የቀረፀ ነው፡፡
በዛሬው ምክክር ላይ ከገለፃው ባሻገር ከተጠሪ ተቋማት የመጡ ተሳታፊዎች በፖሊሲ ክለሳው ላይ ግብዓት የሚሆኑ አስተያየቶች የተሰጡበት ውይይትን አድርገዋል፡፡
ወደ ማርስ የምታቀናው "ውሻዋ" ሮቦት
-----------------------------
እንደ ኪዩሪሲቲ ያሉ ቀደምት የማርስ ሮቨሮች (rovers) የፕላኔቷን ገፀ ምድር በሚገባ በማሳስ አስገራሚ ግኝቶችን ለተመራማሪዎች ያቀበሉ ቢሆንም በሚታሰበው ልክ በቶሎ የሚላመዱ እና ከፍተኛ ፍጥነት የተላበሱ ባለመሆናቸው ሳይንቲስቶች የሚፈልጉትን ተጨማሪ የምርምር ስራ እንዲያካሂዱ አላስቻላቸውም ነበር፡፡ ታዲያ ሌሎች አማራጮችን ሲፈልጉ የነበሩት ተመራማሪዎች ከአመታት በፊት ቦስተን ዳይናሚክ በተባለ የሮቦት ኩባንያ ስትተዋወቅ የነበረችውን ውሻ መሰል ሮቦት በተመሳሳይ መልኩ በመስራት ለዚህ የአሰሳ ተልዕኮ እንዲያጯት ሆኗል፡፡
በዲሴምበር 14 2020 የአሜሪካን ጂዮፊዚካል ህብረት (AGU) ባዘጋጀው የቪዲዮ ኮንፈረንስ ላይ በተመራማሪዎች የተገለፀው የዚህች ሮቦት የመታጨት ዜና በናሳ የምርምር ተቋም ውስጥ አንድ አካል በሆነው JPL- ላብራቶሪ አስተባባሪነት የተከናወነ ነው፡፡ ተመራማሪዎች እንደሚያስረዱት ቀደም ብለው የተላኩት እንደ ስፕሪት፣ ኦፖርቹዩኒቲ እና ኪዩሪሲቲ ያሉ የማርስ ሮቨሮች አብዛኛውን ጊዜ ለጥ ባለ መሬት እንቅስቅሴያቸውን በማድረግ ልዩ ልዩ መረጃዎችን መሰብሰብ ቢችሉም ተመራማሪዎች የሚፈልጓቸው ወሳኝ መረጃዎች በኮረብታዎች፣ በዋሻዎች እና በሌሎች ከባድ ቦታዎች ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ይህን ማድረግ የሚችሉ ሮቦቶች እጅግ ወሳኝ ነበሩ፡፡ ታዲያ ይህች አስገራሚ ሮቦት የመንቀሳቀስ እና የመቋቋም ችሎታዋ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ የተመራማሪዎችን የምርምር ፍላጎት በሚገባ እንደምትመልስ የሚጠበቅ ነው፡፡
Au-Spot የሚል ስያሜ ያላት ይህች ሮቦት አሁን ካሉት ሮቨሮች 12 እጥፍ ቅለት ያላት ስትሆን ይህም በፍጥነት መጓዝ እንድትችል እና ይበልጥ ተጣጣፊነት እንዲኖራት የሚያስችላት ነው፡፡ 32 ኪሎ የምትመዝነው ውሻዋ ሮቦት በሰዓት አምስት ኪሎ ሜትሮችን በመጓዝ የምትንቀሳቀስ ሲሆን፤ ምናልባት ደጋግማ በምትወድቅበት ጊዜ በቶሎ መነሳት እንድትችል የሚያግዝ የማገገሚያ አልጎሪዝምም ተዘጋጅቶላታል፡፡ ሮቦቷ ራስ-ገዝ በሚባል ደረጃ ከሚያጋጥሟት የመንገድ አማራጮች የተሻለውን እንድትመርጥ የሚያስችል አቅም ያላት ሲሆን ከርቀት መጠቆም የሚያስችል ፕሮሰሰር ጨምሮ 3D ካርታ መፍጥር የሚያስችል የምስል፣ የሙቀት እና የእንቅስቃሴ ሴንሰሮችንም አቅፋ ይዛለች፡፡
CoSTAR በተባለ የሮቦት ምርምር ተቋም ውስጥ በሚሰሩ 60 ሳይንቲስቶች የተፈጠረችው ይህች ሮቦት በቅርብ ጊዜ ለምታደርገው የማርስ ጉዞ መሬት ላይ በሚገኙ ዋሻዎች እና ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ ከባድ ስልጠናዎችን እያካሄደች ሲሆን፤ ስልጠናዋን አጠናቃ ወደፕላኔቷ በምታመራበት ወቅት እስከዛሬ ያልተሰሙ አስገራሚ የምርምር ውጤቶችን ልታስገኝ እንደምትችልም በጉጉት ይጠበቃል፡፡ ምንጭ፡ Bigthink
-----------------------------
እንደ ኪዩሪሲቲ ያሉ ቀደምት የማርስ ሮቨሮች (rovers) የፕላኔቷን ገፀ ምድር በሚገባ በማሳስ አስገራሚ ግኝቶችን ለተመራማሪዎች ያቀበሉ ቢሆንም በሚታሰበው ልክ በቶሎ የሚላመዱ እና ከፍተኛ ፍጥነት የተላበሱ ባለመሆናቸው ሳይንቲስቶች የሚፈልጉትን ተጨማሪ የምርምር ስራ እንዲያካሂዱ አላስቻላቸውም ነበር፡፡ ታዲያ ሌሎች አማራጮችን ሲፈልጉ የነበሩት ተመራማሪዎች ከአመታት በፊት ቦስተን ዳይናሚክ በተባለ የሮቦት ኩባንያ ስትተዋወቅ የነበረችውን ውሻ መሰል ሮቦት በተመሳሳይ መልኩ በመስራት ለዚህ የአሰሳ ተልዕኮ እንዲያጯት ሆኗል፡፡
በዲሴምበር 14 2020 የአሜሪካን ጂዮፊዚካል ህብረት (AGU) ባዘጋጀው የቪዲዮ ኮንፈረንስ ላይ በተመራማሪዎች የተገለፀው የዚህች ሮቦት የመታጨት ዜና በናሳ የምርምር ተቋም ውስጥ አንድ አካል በሆነው JPL- ላብራቶሪ አስተባባሪነት የተከናወነ ነው፡፡ ተመራማሪዎች እንደሚያስረዱት ቀደም ብለው የተላኩት እንደ ስፕሪት፣ ኦፖርቹዩኒቲ እና ኪዩሪሲቲ ያሉ የማርስ ሮቨሮች አብዛኛውን ጊዜ ለጥ ባለ መሬት እንቅስቅሴያቸውን በማድረግ ልዩ ልዩ መረጃዎችን መሰብሰብ ቢችሉም ተመራማሪዎች የሚፈልጓቸው ወሳኝ መረጃዎች በኮረብታዎች፣ በዋሻዎች እና በሌሎች ከባድ ቦታዎች ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ይህን ማድረግ የሚችሉ ሮቦቶች እጅግ ወሳኝ ነበሩ፡፡ ታዲያ ይህች አስገራሚ ሮቦት የመንቀሳቀስ እና የመቋቋም ችሎታዋ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ የተመራማሪዎችን የምርምር ፍላጎት በሚገባ እንደምትመልስ የሚጠበቅ ነው፡፡
Au-Spot የሚል ስያሜ ያላት ይህች ሮቦት አሁን ካሉት ሮቨሮች 12 እጥፍ ቅለት ያላት ስትሆን ይህም በፍጥነት መጓዝ እንድትችል እና ይበልጥ ተጣጣፊነት እንዲኖራት የሚያስችላት ነው፡፡ 32 ኪሎ የምትመዝነው ውሻዋ ሮቦት በሰዓት አምስት ኪሎ ሜትሮችን በመጓዝ የምትንቀሳቀስ ሲሆን፤ ምናልባት ደጋግማ በምትወድቅበት ጊዜ በቶሎ መነሳት እንድትችል የሚያግዝ የማገገሚያ አልጎሪዝምም ተዘጋጅቶላታል፡፡ ሮቦቷ ራስ-ገዝ በሚባል ደረጃ ከሚያጋጥሟት የመንገድ አማራጮች የተሻለውን እንድትመርጥ የሚያስችል አቅም ያላት ሲሆን ከርቀት መጠቆም የሚያስችል ፕሮሰሰር ጨምሮ 3D ካርታ መፍጥር የሚያስችል የምስል፣ የሙቀት እና የእንቅስቃሴ ሴንሰሮችንም አቅፋ ይዛለች፡፡
CoSTAR በተባለ የሮቦት ምርምር ተቋም ውስጥ በሚሰሩ 60 ሳይንቲስቶች የተፈጠረችው ይህች ሮቦት በቅርብ ጊዜ ለምታደርገው የማርስ ጉዞ መሬት ላይ በሚገኙ ዋሻዎች እና ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ ከባድ ስልጠናዎችን እያካሄደች ሲሆን፤ ስልጠናዋን አጠናቃ ወደፕላኔቷ በምታመራበት ወቅት እስከዛሬ ያልተሰሙ አስገራሚ የምርምር ውጤቶችን ልታስገኝ እንደምትችልም በጉጉት ይጠበቃል፡፡ ምንጭ፡ Bigthink
ምድር እየሰመጠች ነው
===========
በ20 ዓመታት ውስጥ ብቻ በተለያዩ ቦታዎች የሚከሰተው የመሬት መስመጥ 19 በመቶ የሚሆነውን የምድራችን ነዋሪ ተፅዕኖ ውስጥ እንደሚከተው በዩኔስኮ ድጋፍ ሰጪነት የተደረገ አዲስ ጥናት አስታውቋል፡፡ አንድ ካልተባለ የሰው ልጆች ተግባራት፣ ከድርቅ እና የባህር ውሃ መጨመር ጋር በመተባበር ብዙ የባህር ዳርቻ ከተሞችን በከፍተኛ ጎርፍ እንደሚያጥለቀልቋቸውም ተነግሯል፡፡ ባለፈው አስር ዓመት ውስጥ የኢንዶኔዢያ መዲና የሆነችው ጃካርታ 2.5 ሜትር ወደታች በመስመጧ ሳብያ የሀገሬው መንግስት አዲስ መዲና ፍለጋ ወደ በቦርኔኦ ደሴት ለማምራት አቅዷል፡፡ በአውሮፓም 25 በመቶው የሆላንድ መሬት ከባህር ጠለል በታች መገኘት ምክንያቱ ይኸው የመሬት መስመጥ ነው፡፡
በጥናቱ ላይ በመሪ አጥኚነት የተሳተፉት ጌራርዶ ሄሬራ-ጋሪንቻ እንደሚሉት ዝናብ አጠር የሆኑና ህዝብ እጅጉን ታጭቆ የሚኖርባቸው ወይም የመስኖ እርሻ የተስፋፋባቸው አካባቢዎች የከርሰ ምድር ውሃን በስፋት አውጥተው በሚጠቀሙበት ጊዜ ውሃን በውስጡ የያዘው የድንጋይ ንጣፍ (Aquifer) ከሚያገኘው የሚሰጠው በመብለጡ እየሳሳ ይመጣል፡፡ በዚህም የሰው ብዛትና ውሃ ቅርምቱን በህግ መገደብ አለመቻሉ የመሬት መስመጡን በዋናነት እያስከተለ ይገኛል፡፡ ለምሳሌ ኢራን ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ሕዝቧ በእጥፍ ያደገ ቢሆንም የከርሰ ምድርን ውሃ ማውጣቱ ላይ ግን ተገቢው ቁጥጥር ሳታደርግ ቆይታለች፡፡ ታድያ አሁን ላይ የሀገሪቱ ከተሞች በየዓመቱ 25 ሴ.ሜ በመስመጥ ከዓለማችን ቀዳሚዎቹ ቁልቁል ተጓዦች መካከል ለመሆን በቅተዋል፡፡
ምንም እንኳን የመሬት መስመጥ አዲስ ጉዳይ ባይሆንም በአብዛኛው ግን በአካባቢያዊ ጉዳይነት ተወስኖ ቆይቷል፡፡ በዓለም አቀፍ አጥኚዎች ቡድን የተዘጋጀው አዲሱ ጥናት ግን ቀድሞ የነበሩትን ጥናቶች የሚያጠናክር፤ ግን ደግሞ የትኛዎቹ የምድራችን ክፍሎች በከፍተኛ የመስመጥ አደጋ ውስጥ ይገኛሉ የሚለውን ለመላው ዓለም በሚሰራ መንገድ ያቀረበ ነው፡፡ ችግሩ ዋነኛ መነሻ ከማያዛልቅ ግብርና እና አየር ንብረት ለውጥ ጋር የተሳሰረው ዓለም አቀፍ ጉዳይ መሆኑን ያመላከተው ጥናቱ አሜሪካን፣ ቻይና እና ህንድ የምግብ ፍላጎትን ለማሳካት ሲሉ የሚያደርጉት የከርሰ ምድር ውሃ ብዝበዛ የኋላ ኋላ መላውን ዓለም ተፅዕንዖ ስር እንደሚከትም ማስቀመጡን ሄራርዶ ይናገራል፡፡
ነገሩን የከፋ ሚያደርገው አየር ንብረት ለውጥ ረጃጅም የድርቅ ወቅቶችን እንደሚያመጣ የሚጠበቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የከርሰ ምድር ውሃ ይበልጥ እንዲወጣ ዕድል መፍጠሩ ነው፡፡ የባህር ውሃም ቢሆን በቀጣዩ ክፍለ ዘመን ከፍታው እስከ አንድ ሜትር እንደሚጨምር መተንበዩን ተከትሎም ሌሎች የባህር ዳርቻ ከተሞችም የጃካርታ እጣ ፈንታ ሊገጥማቸው መቻሉን መገመት አያዳግትም፡፡ ሆኖም የመሬት መስመጥ ከአየር ንብረት ለውጥ ይልቅ ለመፍታት ቀላል ችግር መሆኑን ጌራርዶ ይናገራል ባለፈው ክፍለ ዘመን ጅማሮ ላይ ቶኪዮ ገጥሟት የነበረውን የመስመጥ አደጋ የከርሰ ምድር ውሃ አወጣጥን የሚቆጣጠሩ ደንቦችን በማውጣት መፍታት መቻሏን በመልካም ምሳሌነት እያስቀመጠ፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
===========
በ20 ዓመታት ውስጥ ብቻ በተለያዩ ቦታዎች የሚከሰተው የመሬት መስመጥ 19 በመቶ የሚሆነውን የምድራችን ነዋሪ ተፅዕኖ ውስጥ እንደሚከተው በዩኔስኮ ድጋፍ ሰጪነት የተደረገ አዲስ ጥናት አስታውቋል፡፡ አንድ ካልተባለ የሰው ልጆች ተግባራት፣ ከድርቅ እና የባህር ውሃ መጨመር ጋር በመተባበር ብዙ የባህር ዳርቻ ከተሞችን በከፍተኛ ጎርፍ እንደሚያጥለቀልቋቸውም ተነግሯል፡፡ ባለፈው አስር ዓመት ውስጥ የኢንዶኔዢያ መዲና የሆነችው ጃካርታ 2.5 ሜትር ወደታች በመስመጧ ሳብያ የሀገሬው መንግስት አዲስ መዲና ፍለጋ ወደ በቦርኔኦ ደሴት ለማምራት አቅዷል፡፡ በአውሮፓም 25 በመቶው የሆላንድ መሬት ከባህር ጠለል በታች መገኘት ምክንያቱ ይኸው የመሬት መስመጥ ነው፡፡
በጥናቱ ላይ በመሪ አጥኚነት የተሳተፉት ጌራርዶ ሄሬራ-ጋሪንቻ እንደሚሉት ዝናብ አጠር የሆኑና ህዝብ እጅጉን ታጭቆ የሚኖርባቸው ወይም የመስኖ እርሻ የተስፋፋባቸው አካባቢዎች የከርሰ ምድር ውሃን በስፋት አውጥተው በሚጠቀሙበት ጊዜ ውሃን በውስጡ የያዘው የድንጋይ ንጣፍ (Aquifer) ከሚያገኘው የሚሰጠው በመብለጡ እየሳሳ ይመጣል፡፡ በዚህም የሰው ብዛትና ውሃ ቅርምቱን በህግ መገደብ አለመቻሉ የመሬት መስመጡን በዋናነት እያስከተለ ይገኛል፡፡ ለምሳሌ ኢራን ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ሕዝቧ በእጥፍ ያደገ ቢሆንም የከርሰ ምድርን ውሃ ማውጣቱ ላይ ግን ተገቢው ቁጥጥር ሳታደርግ ቆይታለች፡፡ ታድያ አሁን ላይ የሀገሪቱ ከተሞች በየዓመቱ 25 ሴ.ሜ በመስመጥ ከዓለማችን ቀዳሚዎቹ ቁልቁል ተጓዦች መካከል ለመሆን በቅተዋል፡፡
ምንም እንኳን የመሬት መስመጥ አዲስ ጉዳይ ባይሆንም በአብዛኛው ግን በአካባቢያዊ ጉዳይነት ተወስኖ ቆይቷል፡፡ በዓለም አቀፍ አጥኚዎች ቡድን የተዘጋጀው አዲሱ ጥናት ግን ቀድሞ የነበሩትን ጥናቶች የሚያጠናክር፤ ግን ደግሞ የትኛዎቹ የምድራችን ክፍሎች በከፍተኛ የመስመጥ አደጋ ውስጥ ይገኛሉ የሚለውን ለመላው ዓለም በሚሰራ መንገድ ያቀረበ ነው፡፡ ችግሩ ዋነኛ መነሻ ከማያዛልቅ ግብርና እና አየር ንብረት ለውጥ ጋር የተሳሰረው ዓለም አቀፍ ጉዳይ መሆኑን ያመላከተው ጥናቱ አሜሪካን፣ ቻይና እና ህንድ የምግብ ፍላጎትን ለማሳካት ሲሉ የሚያደርጉት የከርሰ ምድር ውሃ ብዝበዛ የኋላ ኋላ መላውን ዓለም ተፅዕንዖ ስር እንደሚከትም ማስቀመጡን ሄራርዶ ይናገራል፡፡
ነገሩን የከፋ ሚያደርገው አየር ንብረት ለውጥ ረጃጅም የድርቅ ወቅቶችን እንደሚያመጣ የሚጠበቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የከርሰ ምድር ውሃ ይበልጥ እንዲወጣ ዕድል መፍጠሩ ነው፡፡ የባህር ውሃም ቢሆን በቀጣዩ ክፍለ ዘመን ከፍታው እስከ አንድ ሜትር እንደሚጨምር መተንበዩን ተከትሎም ሌሎች የባህር ዳርቻ ከተሞችም የጃካርታ እጣ ፈንታ ሊገጥማቸው መቻሉን መገመት አያዳግትም፡፡ ሆኖም የመሬት መስመጥ ከአየር ንብረት ለውጥ ይልቅ ለመፍታት ቀላል ችግር መሆኑን ጌራርዶ ይናገራል ባለፈው ክፍለ ዘመን ጅማሮ ላይ ቶኪዮ ገጥሟት የነበረውን የመስመጥ አደጋ የከርሰ ምድር ውሃ አወጣጥን የሚቆጣጠሩ ደንቦችን በማውጣት መፍታት መቻሏን በመልካም ምሳሌነት እያስቀመጠ፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
የዚንክ ባትሪዎችን ታዳሽ የማድረጊያ መንገድ ተገኘላቸው
********************************
ከቻይና፣ ጀርመንና አሜሪካ የተውጣጣ የተመራማሪዎች ቡድን የዚንክ ባትሪዎችን ታዳሽ ማድረግ የሚያስችልን መንገድ ማበልጸጉ ተሰማ፡፡ ከሶስቱ ሀገራት የተውጣጣው የምርምር ቡድን አልካላይን ያልሆኑ ኤሌክትሮላይቶችን በመጠቀም ከተለመደው ዲዛይን የተለየ የዚንክና የኦክስጅን ኤሌክትሮኖች ጥምረት የሆነ አዲስ ባትሪን ሰርቷል፡፡
በአሆኑ ወቅት በጣም የተለመዱት ባትሪዎች የአልካላን ባትሪዎች ሲሆኑ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ናቸው፡፡ እነዚህ ባትሪዎች ዚንክን በዋና ግብዓትነት የሚጠቀሙት ለአጠቃቀም ምቹ በመሆኑና ዋጋውም በጣም ቀላል በመሆኑ ነው፡፡ ሌላኛው ኤሌክትሮድ አየርን በመጠቀም የተሰራ ነው፡፡ ይህ ዲዛይን ዚንክን መሰረት ያደረጉ ባትሪዎች በከፍኛ መጠን እንዲመረቱ ያስችላል፡፡
በአዲሱ ግኝት ተመራማሪዎቹ የዚንክ ባትሪዎችን ታዳሽ የማድረጊያ መንገዶችን አስተዋውቀዋል፡፡ ይህንን አዲስ ባትሪ ለመስራት ተመራማሪዎቹ ትክክለኛውን አልካላይን ያልሆነ ኤሌክትሮላይት የመረጡ ሲሆን ዚንክ-ኦክስጅን-ዚንክ ፕርኦክሳይድ የሆነ የሁለት ኤሌክትሮኖች ጥምረትን የሚጠቀም ባትሪን ሰርተዋል፡፡ ይህም ከተለመደው ባትሪ የበለጠ በድጋሚ ጥቅም ላይ እንዲውል አስችሎታል፡፡ ተመራማሪዎቹ ኤሌክትሮላይቶቹን ውሃ እንዳያገኛቸው በማድረግ ውሃ ወደ ካቶዱ እንዳይጠጋ ማድረግ ችለዋል፡፡ አዲሱ ዲዛይን በተሞከረበት ወቅት በድጋሜ ጥቅም ላይ ሲውል ሀይልን ለ1600 ሰዓታት ያክል መያዝ እንደሚችል መረጋገጡን ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ መረጃውን ከTech Xplore አግኝተነዋል፡፡
********************************
ከቻይና፣ ጀርመንና አሜሪካ የተውጣጣ የተመራማሪዎች ቡድን የዚንክ ባትሪዎችን ታዳሽ ማድረግ የሚያስችልን መንገድ ማበልጸጉ ተሰማ፡፡ ከሶስቱ ሀገራት የተውጣጣው የምርምር ቡድን አልካላይን ያልሆኑ ኤሌክትሮላይቶችን በመጠቀም ከተለመደው ዲዛይን የተለየ የዚንክና የኦክስጅን ኤሌክትሮኖች ጥምረት የሆነ አዲስ ባትሪን ሰርቷል፡፡
በአሆኑ ወቅት በጣም የተለመዱት ባትሪዎች የአልካላን ባትሪዎች ሲሆኑ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ናቸው፡፡ እነዚህ ባትሪዎች ዚንክን በዋና ግብዓትነት የሚጠቀሙት ለአጠቃቀም ምቹ በመሆኑና ዋጋውም በጣም ቀላል በመሆኑ ነው፡፡ ሌላኛው ኤሌክትሮድ አየርን በመጠቀም የተሰራ ነው፡፡ ይህ ዲዛይን ዚንክን መሰረት ያደረጉ ባትሪዎች በከፍኛ መጠን እንዲመረቱ ያስችላል፡፡
በአዲሱ ግኝት ተመራማሪዎቹ የዚንክ ባትሪዎችን ታዳሽ የማድረጊያ መንገዶችን አስተዋውቀዋል፡፡ ይህንን አዲስ ባትሪ ለመስራት ተመራማሪዎቹ ትክክለኛውን አልካላይን ያልሆነ ኤሌክትሮላይት የመረጡ ሲሆን ዚንክ-ኦክስጅን-ዚንክ ፕርኦክሳይድ የሆነ የሁለት ኤሌክትሮኖች ጥምረትን የሚጠቀም ባትሪን ሰርተዋል፡፡ ይህም ከተለመደው ባትሪ የበለጠ በድጋሚ ጥቅም ላይ እንዲውል አስችሎታል፡፡ ተመራማሪዎቹ ኤሌክትሮላይቶቹን ውሃ እንዳያገኛቸው በማድረግ ውሃ ወደ ካቶዱ እንዳይጠጋ ማድረግ ችለዋል፡፡ አዲሱ ዲዛይን በተሞከረበት ወቅት በድጋሜ ጥቅም ላይ ሲውል ሀይልን ለ1600 ሰዓታት ያክል መያዝ እንደሚችል መረጋገጡን ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ መረጃውን ከTech Xplore አግኝተነዋል፡፡
ማንጎ የፊት ቆዳ መሸብሸብን ለመቀነስ
***********************
እንደሌሎቹ አትክልትና ፍራፍሬዎች ሁሉ የማንጎ ፍሬ የሰውነታችን ህዋሳት በቶሎ እንዳይሞቱ የሚያደርግ ኬሚካል በውስጡ ይዟል፡፡ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተሰራ አንድ አዲስ ጥናት ማንጎን መብላት አጠቃላይ ፍራፋፍሬን በመብላት ከሚገኝ ጥቅም በተጨማሪ በፊት ላይ የሚከሰትን የቆዳ መሸብሸብ እንደሚያስቀር አረጋግጧል፡፡
የወር አበባ ማየት ያቆሙ ሴቶች በሳምንት አራት ጊዜ ግማሽ የሻይ ብርጭቆ ጣፋጭ ማንጎ ቢበሉ በሁለት ወር ውስጥ 23 በመቶ የፊት ቆዳ መሸብሸብን መቀነስ ሲችሉ ከሌላ ሁለት ወር በኋላ ደግሞ ተጨማሪ 20 በመቶ መቀነስ ይችላሉ ሲሉ አጥኝዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ አንዳንድ የማንጎ ዝርያዎች በብዛት የምንመገባቸው ከሆነ የከፋ የፊት ቆዳ መሸብሸብ የሚያስከትሉ እንደሆኑና ይህም ባላቸው ከፍተኛ የሆነ የስኳር መጠን ሊሆን እንደሚችል ግምቶች አሉ፡፡ ኤታውለፎ እየተባለ የሚጠራው የማንጎ ዝርያ ግን ከሌሎቹ ዝርያዎች በተቃራኒው ለፊት ቆዳ መሸብሸብ መድሃኒት ሆኖ ብቅ ብሏል፡፡
በምርምሩ ወቅት 28 የእርግዝና ጊዜያቸውን የጨረሱ ሴቶች በሁለት ምድብ ተከፍለው ሙከራው የተሰራ ሲሆን ግማሾቹ ግማሽ የሻይ ብርጭቆ ማንጎ በሳምንት አራት ጊዜ ለተከታታይ አራት ወራት እንዲጠቀሙ ሲደረግ ግማሾቹ ደግሞ በተመሳሳይ ጊዜ አንድ ከግማሽ የሻይ ብርጭቆ ማንጎ እንዲጠቀሙ ተደርገዋል፡፡ የፊት ቆዳ መሸብሸብ ውጤቱም ከፍኛ ጥራት ባለው ካሜራ ክትትል ተደርጎበታል፡፡
በዚህም ከአራት ወር በኋላ ግማሽ የሻይ ብርጭቆ ማንጉ ሲጠቀሙ የነበሩ ሴቶች በፊታቸው ቆዳ ላይ ከፍተኛ የሆነ መሻሻል ማሳየት ችለዋል፡፡ ከዚህም በመነሳት በሳምንት ውስጥ የምንመገበውን የማንጎ መጠን በማስተካከል በፊታችን ላይ የሚደርስን የቆዳ መሸብሸብ መቀነስ እንችላለን የሚል ማረጋገጫን አጥኝዎቹ ሰጥተዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
***********************
እንደሌሎቹ አትክልትና ፍራፍሬዎች ሁሉ የማንጎ ፍሬ የሰውነታችን ህዋሳት በቶሎ እንዳይሞቱ የሚያደርግ ኬሚካል በውስጡ ይዟል፡፡ በካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የተሰራ አንድ አዲስ ጥናት ማንጎን መብላት አጠቃላይ ፍራፋፍሬን በመብላት ከሚገኝ ጥቅም በተጨማሪ በፊት ላይ የሚከሰትን የቆዳ መሸብሸብ እንደሚያስቀር አረጋግጧል፡፡
የወር አበባ ማየት ያቆሙ ሴቶች በሳምንት አራት ጊዜ ግማሽ የሻይ ብርጭቆ ጣፋጭ ማንጎ ቢበሉ በሁለት ወር ውስጥ 23 በመቶ የፊት ቆዳ መሸብሸብን መቀነስ ሲችሉ ከሌላ ሁለት ወር በኋላ ደግሞ ተጨማሪ 20 በመቶ መቀነስ ይችላሉ ሲሉ አጥኝዎቹ አረጋግጠዋል፡፡ አንዳንድ የማንጎ ዝርያዎች በብዛት የምንመገባቸው ከሆነ የከፋ የፊት ቆዳ መሸብሸብ የሚያስከትሉ እንደሆኑና ይህም ባላቸው ከፍተኛ የሆነ የስኳር መጠን ሊሆን እንደሚችል ግምቶች አሉ፡፡ ኤታውለፎ እየተባለ የሚጠራው የማንጎ ዝርያ ግን ከሌሎቹ ዝርያዎች በተቃራኒው ለፊት ቆዳ መሸብሸብ መድሃኒት ሆኖ ብቅ ብሏል፡፡
በምርምሩ ወቅት 28 የእርግዝና ጊዜያቸውን የጨረሱ ሴቶች በሁለት ምድብ ተከፍለው ሙከራው የተሰራ ሲሆን ግማሾቹ ግማሽ የሻይ ብርጭቆ ማንጎ በሳምንት አራት ጊዜ ለተከታታይ አራት ወራት እንዲጠቀሙ ሲደረግ ግማሾቹ ደግሞ በተመሳሳይ ጊዜ አንድ ከግማሽ የሻይ ብርጭቆ ማንጎ እንዲጠቀሙ ተደርገዋል፡፡ የፊት ቆዳ መሸብሸብ ውጤቱም ከፍኛ ጥራት ባለው ካሜራ ክትትል ተደርጎበታል፡፡
በዚህም ከአራት ወር በኋላ ግማሽ የሻይ ብርጭቆ ማንጉ ሲጠቀሙ የነበሩ ሴቶች በፊታቸው ቆዳ ላይ ከፍተኛ የሆነ መሻሻል ማሳየት ችለዋል፡፡ ከዚህም በመነሳት በሳምንት ውስጥ የምንመገበውን የማንጎ መጠን በማስተካከል በፊታችን ላይ የሚደርስን የቆዳ መሸብሸብ መቀነስ እንችላለን የሚል ማረጋገጫን አጥኝዎቹ ሰጥተዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
ዘንዶን መመገብ
በአሜሪካኗ የፍሎሪዳ ግዛት ዘንዶዎችን መመገብ ሊጀመር እንደሚችል ተነግሯል፡፡ የግዛቲቱ አስተዳደር ለአካባቢው መጤ የሆኑት የበርማ ዘንዶዎች ከቁጥጥር ውጪ ሆነው በመስፋፋታቸው ሳብያ ቁጥራቸውን ለመቀነስ ህዝቡ እንዲመገባቸው ሊያበረታታ ይችላል፡፡ አስቀድሞ ግን የዘንዶዎቹ ስጋ በሜርኩሪ አለመጠቃቱን ለማረጋገጥ የዱር ጥበቃ ኮሚሽኑ ከጤና ቢሮው ጋር በመሆን ምርመራን እያደረጉ ነው፡፡ ይህ ግን ለአንዳንዶች የዘገየባቸው ይመስላል፤ በደቡባዊ ፍሎሪዳ የውሃ አስተዳደር ውስጥ በዘንዶ አዳኝነት ተቀጥራ የምትሰራውና ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ቁጥራቸው የበዛ ዘንዶዎችን ማጣጣሟ የተዘገበላት ዶና ካሊል የዘንዶ ስጋ በጣም ጣፋጭ ሆኖ እንዳገኘችው ትናገራለች፡፡
የበርማ ዘንዶዎች ደቡባዊ ፍሎሪዳ ውስጥ በሚገኘው የኤቨርግሌድስ ብሄራዊ ፓርክ መስፋፋት የጀመሩት ከአውሮፓውያኑ 1990ዎቹ ጀምሮ ነበር፡፡ መጀመሪያ ላይ በቤት ውስጥ ከሚንከባከቧቸው አሳዳጊዎች አምልጠው እንደሆነ በሚገመት መልኩ ወደ አካባቢው የተሰራጩ ሲሆን ወደ ኋላ ስነ-ምህዳሩ ላይ ጥፋት ለማድረስ በቅተዋል (ከዚህ ቀደም ዘንዶዎቹን ለመቀነስ ታስቦ በግዛቲቱ የሚደረገውን የአደን ውድድር መዘገባችን ይታወሳል)፡፡ አሁን ላይ ዘንዶዎቹ በግዛቲቱ የሰሜን እና ምዕራባዊ ክፍሎች በመስፋፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ አካባቢው ላይ ኑሮዋቸውነ ያደረጉት የበርማ ዘንዶዎች በአማካኝ ከ1.8 እስከ 2.7 ሜትር ርዝመት ያላቸው ቢሆኑም እስከዛሬ ከተገኙት በርዝመት አቻ የለሽ ሆኖ የተመዘገበው 5.4 ሜትር ነው፡፡ ይህ ግዝፈታቸው በጣም የተወሰነ አዳኝ እንዲኖራቸውና በተቃራኒው ከበፊትም በአካባቢው የሚኖሩትን ከአዕዋፍ እስከ አርጃኖ ያሉ እንስሳትን እንዲመገቡ ያደረጋቸው ሲሆን ከታዳኝ እንስሳቱ ውስጥ የተወሰኑት የመጥት አደጋ የተጋረጠባቸው ብርቅዬ እንስሳት ናቸው፡፡
ይህ አይነት ወራሪ እንስሳትን ለምግብነት እንዲውሉ ማድረጉ በግዛቲቱ አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደምም ከርከሮ እና ሌሎች ወራሪ እንሽላሊት እንዲሁም የአሳ ዝርያዎች እንደልብ ተበልተዋል፡፡ ሆኖም ዘንዶዎችን ለየት የሚያደርገው ሰውነታቸው ለሜርኩሪ ብክለት በይበልጥ ተጋላጭ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡ እንደ ማዕድን ማውጣት ያሉ የሰው ልጅ እንቅስቃሴዎች በተፈጥሮ ከሚገኝበት የምድራችን ክፍል ወደ ከባቢ አየር እንዲለቀቅ የሆነው ሜርኩሪ ከዝናብ ጋር ተቀላቅሎ በመዝነብ ወደ ውሃ አካላት ይገባል፤ ኤቨርግሌድ በዚህ ረገድ ከፍተኛ ተጋላጭነት አለው፡፡ ሜርኩሪው ወደ ውሃ አካላት በሚገባበት ወቅት የተለያዩ ደቂቀ አካላት ሜቲልሜርኩሪ ወደተባለ መርዛማ ቅርፅ ይለውጡታል፡፡ ከዚህ በኋላ በዚህ የተበከለ እንስሳ በሌላው እየተበላ ብክለቱ ከፍ ወዳሉት አዳኝ እንስሳት ይደርሳል፡፡
የሚተነፍስ እና ሚንቀሰቀስ ነገርን ሁሉ በመብላት የማይታሙት ዘንዶዎች በሜርኩሪው የተበከሉ እንስሳትን ሁሉ ሲያግበሰብሱ እንደመኖራቸው የስጋቸውን የመበከል እድል ከፍተኛ ያደርገዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በአካባቢው የተያዙ አንዳንድ ዘንዶዎች ለሰው ልጅ ጤናማ ነው ከሚባለው የሜርኩሪ መጠን በእጥፍ የበለጠ ይዘው ተገኝተዋል፡፡ ይህ የሜርኩሪ ይዘት ታድያ በሰው ልጆች ላይ የነርቭ፣ አተነፋፈስ እና ሌሎች የጤና ጉዳቶችን የማድረስ አቅም አለው፡፡ አስተዳደሩም በእባቦቹ ላይ ያለውን የሜርኩሪ መጠን ለመመርመር ማሰቡ ለዚህ ነው፡፡ ታድያ እስከ ዛሬ ዘንዶዎቹን ስመገብ የኖረችው ካሊ ጤና ድንገት ካሳሰብዎት በዘንዶዎቹ ስጋ ውስጥ ያለውን የሜርኩሪ መጠን የሚለካ መሳርያ ስላላት ከጉዳቱ ያመለጠች ይመስላል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
በአሜሪካኗ የፍሎሪዳ ግዛት ዘንዶዎችን መመገብ ሊጀመር እንደሚችል ተነግሯል፡፡ የግዛቲቱ አስተዳደር ለአካባቢው መጤ የሆኑት የበርማ ዘንዶዎች ከቁጥጥር ውጪ ሆነው በመስፋፋታቸው ሳብያ ቁጥራቸውን ለመቀነስ ህዝቡ እንዲመገባቸው ሊያበረታታ ይችላል፡፡ አስቀድሞ ግን የዘንዶዎቹ ስጋ በሜርኩሪ አለመጠቃቱን ለማረጋገጥ የዱር ጥበቃ ኮሚሽኑ ከጤና ቢሮው ጋር በመሆን ምርመራን እያደረጉ ነው፡፡ ይህ ግን ለአንዳንዶች የዘገየባቸው ይመስላል፤ በደቡባዊ ፍሎሪዳ የውሃ አስተዳደር ውስጥ በዘንዶ አዳኝነት ተቀጥራ የምትሰራውና ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ቁጥራቸው የበዛ ዘንዶዎችን ማጣጣሟ የተዘገበላት ዶና ካሊል የዘንዶ ስጋ በጣም ጣፋጭ ሆኖ እንዳገኘችው ትናገራለች፡፡
የበርማ ዘንዶዎች ደቡባዊ ፍሎሪዳ ውስጥ በሚገኘው የኤቨርግሌድስ ብሄራዊ ፓርክ መስፋፋት የጀመሩት ከአውሮፓውያኑ 1990ዎቹ ጀምሮ ነበር፡፡ መጀመሪያ ላይ በቤት ውስጥ ከሚንከባከቧቸው አሳዳጊዎች አምልጠው እንደሆነ በሚገመት መልኩ ወደ አካባቢው የተሰራጩ ሲሆን ወደ ኋላ ስነ-ምህዳሩ ላይ ጥፋት ለማድረስ በቅተዋል (ከዚህ ቀደም ዘንዶዎቹን ለመቀነስ ታስቦ በግዛቲቱ የሚደረገውን የአደን ውድድር መዘገባችን ይታወሳል)፡፡ አሁን ላይ ዘንዶዎቹ በግዛቲቱ የሰሜን እና ምዕራባዊ ክፍሎች በመስፋፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ አካባቢው ላይ ኑሮዋቸውነ ያደረጉት የበርማ ዘንዶዎች በአማካኝ ከ1.8 እስከ 2.7 ሜትር ርዝመት ያላቸው ቢሆኑም እስከዛሬ ከተገኙት በርዝመት አቻ የለሽ ሆኖ የተመዘገበው 5.4 ሜትር ነው፡፡ ይህ ግዝፈታቸው በጣም የተወሰነ አዳኝ እንዲኖራቸውና በተቃራኒው ከበፊትም በአካባቢው የሚኖሩትን ከአዕዋፍ እስከ አርጃኖ ያሉ እንስሳትን እንዲመገቡ ያደረጋቸው ሲሆን ከታዳኝ እንስሳቱ ውስጥ የተወሰኑት የመጥት አደጋ የተጋረጠባቸው ብርቅዬ እንስሳት ናቸው፡፡
ይህ አይነት ወራሪ እንስሳትን ለምግብነት እንዲውሉ ማድረጉ በግዛቲቱ አዲስ ነገር አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደምም ከርከሮ እና ሌሎች ወራሪ እንሽላሊት እንዲሁም የአሳ ዝርያዎች እንደልብ ተበልተዋል፡፡ ሆኖም ዘንዶዎችን ለየት የሚያደርገው ሰውነታቸው ለሜርኩሪ ብክለት በይበልጥ ተጋላጭ ሆኖ መገኘቱ ነው፡፡ እንደ ማዕድን ማውጣት ያሉ የሰው ልጅ እንቅስቃሴዎች በተፈጥሮ ከሚገኝበት የምድራችን ክፍል ወደ ከባቢ አየር እንዲለቀቅ የሆነው ሜርኩሪ ከዝናብ ጋር ተቀላቅሎ በመዝነብ ወደ ውሃ አካላት ይገባል፤ ኤቨርግሌድ በዚህ ረገድ ከፍተኛ ተጋላጭነት አለው፡፡ ሜርኩሪው ወደ ውሃ አካላት በሚገባበት ወቅት የተለያዩ ደቂቀ አካላት ሜቲልሜርኩሪ ወደተባለ መርዛማ ቅርፅ ይለውጡታል፡፡ ከዚህ በኋላ በዚህ የተበከለ እንስሳ በሌላው እየተበላ ብክለቱ ከፍ ወዳሉት አዳኝ እንስሳት ይደርሳል፡፡
የሚተነፍስ እና ሚንቀሰቀስ ነገርን ሁሉ በመብላት የማይታሙት ዘንዶዎች በሜርኩሪው የተበከሉ እንስሳትን ሁሉ ሲያግበሰብሱ እንደመኖራቸው የስጋቸውን የመበከል እድል ከፍተኛ ያደርገዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በአካባቢው የተያዙ አንዳንድ ዘንዶዎች ለሰው ልጅ ጤናማ ነው ከሚባለው የሜርኩሪ መጠን በእጥፍ የበለጠ ይዘው ተገኝተዋል፡፡ ይህ የሜርኩሪ ይዘት ታድያ በሰው ልጆች ላይ የነርቭ፣ አተነፋፈስ እና ሌሎች የጤና ጉዳቶችን የማድረስ አቅም አለው፡፡ አስተዳደሩም በእባቦቹ ላይ ያለውን የሜርኩሪ መጠን ለመመርመር ማሰቡ ለዚህ ነው፡፡ ታድያ እስከ ዛሬ ዘንዶዎቹን ስመገብ የኖረችው ካሊ ጤና ድንገት ካሳሰብዎት በዘንዶዎቹ ስጋ ውስጥ ያለውን የሜርኩሪ መጠን የሚለካ መሳርያ ስላላት ከጉዳቱ ያመለጠች ይመስላል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
የውሃ መልክ ያለው የጸሐይ ሐይል መሰብሰቢያ ንጣፍ እንደ መስኮት
*******************************
በኮሪያ በሚገኝ ኢንኮን ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የተሰራ አንድ ምርምር ብርሃን መሉ ለሙሉ አስተላላፊ የሆነና ለመስኮት መስታወትነት ሊያገለግል የሚችል የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ ንጣፍ የሚሰራበትን መንገድ ማበልጸጉ ተሰማ፡፡ ይህ ቀለም አልባ አስተላላፊ ንጣፍ በቤት መስኮቶች ላይ ተገጥሞ ኤሌክትሪክ በማመንጨት የወደፊቱን የቤት ውስጥ የሀይል ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡
ፈጠራው ከመደበኛው የጸሐይ ሐይል መሰብሰቢያ ንጣፍ ብርሃን ሰብሳቢውን ክፍል ብቻ በመለየት ታይታኒየም ዳይኦክሳይድና ከፊል አስተላላፊ ከሆነ ኒኬል ኦክሳይድ ጋር በማቀናጀት የተሰራ እንደሆነ ተመራማሪዎቹ አሳውቀዋል፡፡ ከፓሪሱ የአየር ንብረት ስምምነት በኋላ አብዛናዎቹ የአለማችን ሀገራት ከካርቦን ነጻ አለምን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የየበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ እንደሆነ በስፋ እየተነገረ ነው፡፡
በአማራጭ ሀይል ረገድ ተስፋ ሰጭ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን በተለይ የጸሐይ ሐይል መሰብሰቢያ ንጣፎች ከዋጋቸው፣ ከመፈጸም ብቃታቸውና ከአካባቢ ጋር ካላቸው ተስማሚነት አንጻር እጅግ ተመራጭ እየሆኑ መጥተዋል፡፡ የሀይል ፍላጎትን ከማሟላት ጎን ለጎን ከእለት ተእለት መገልገያዎች ጋር ተቀናጅቶ ሲገኝ ደግሞ ተመራጭነቱ የበለጠ ይጨምራል፡፡
ለምሳሌ ያክል የዚህ የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ እንደ የቤት መስኮት፣ የህንጻ ጣሪያዎች እና የሞባይል ስልክ ስክሪኖች ሆኖ ቢመጣ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት በመያዝ ተመራጭነቱ ከፍያለ ይሆናል፡፡ ብርሃን አስተላላፊ የሆነ የጸሐይ ሐይል በሰብሰቢያ ንጣፍ በሀሳብ ደረጃ የታወቀ ቢሆንም አዲሱ ግኝት ሀሳቡ ወደ ተግባር እንዲለወጥ አድርጎታል፡፡
ምንጭ: SciTechDaily
*******************************
በኮሪያ በሚገኝ ኢንኮን ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የተሰራ አንድ ምርምር ብርሃን መሉ ለሙሉ አስተላላፊ የሆነና ለመስኮት መስታወትነት ሊያገለግል የሚችል የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ ንጣፍ የሚሰራበትን መንገድ ማበልጸጉ ተሰማ፡፡ ይህ ቀለም አልባ አስተላላፊ ንጣፍ በቤት መስኮቶች ላይ ተገጥሞ ኤሌክትሪክ በማመንጨት የወደፊቱን የቤት ውስጥ የሀይል ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡
ፈጠራው ከመደበኛው የጸሐይ ሐይል መሰብሰቢያ ንጣፍ ብርሃን ሰብሳቢውን ክፍል ብቻ በመለየት ታይታኒየም ዳይኦክሳይድና ከፊል አስተላላፊ ከሆነ ኒኬል ኦክሳይድ ጋር በማቀናጀት የተሰራ እንደሆነ ተመራማሪዎቹ አሳውቀዋል፡፡ ከፓሪሱ የአየር ንብረት ስምምነት በኋላ አብዛናዎቹ የአለማችን ሀገራት ከካርቦን ነጻ አለምን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የየበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ እንደሆነ በስፋ እየተነገረ ነው፡፡
በአማራጭ ሀይል ረገድ ተስፋ ሰጭ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን በተለይ የጸሐይ ሐይል መሰብሰቢያ ንጣፎች ከዋጋቸው፣ ከመፈጸም ብቃታቸውና ከአካባቢ ጋር ካላቸው ተስማሚነት አንጻር እጅግ ተመራጭ እየሆኑ መጥተዋል፡፡ የሀይል ፍላጎትን ከማሟላት ጎን ለጎን ከእለት ተእለት መገልገያዎች ጋር ተቀናጅቶ ሲገኝ ደግሞ ተመራጭነቱ የበለጠ ይጨምራል፡፡
ለምሳሌ ያክል የዚህ የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ እንደ የቤት መስኮት፣ የህንጻ ጣሪያዎች እና የሞባይል ስልክ ስክሪኖች ሆኖ ቢመጣ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት በመያዝ ተመራጭነቱ ከፍያለ ይሆናል፡፡ ብርሃን አስተላላፊ የሆነ የጸሐይ ሐይል በሰብሰቢያ ንጣፍ በሀሳብ ደረጃ የታወቀ ቢሆንም አዲሱ ግኝት ሀሳቡ ወደ ተግባር እንዲለወጥ አድርጎታል፡፡
ምንጭ: SciTechDaily
ሰብአ ሰገልን የመራችው ኮከብ፤ የትኛዋ ናት?
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ሦስት ጥበበኛ ሰዎች የተወለደውን ንጉስ ፍለጋ አሁን ላይ “የቤተልሄም ኮከብ” ተብላ የምትታወቀው ኮከብን ተከትለው ወደ እየሩሳሌም ማቅናታቸው ተነግሯል፡፡ ሄሮድስን በማማከርም የተወለደውን ህፃን በቤተልሄም ማግኘታቸውን ይህ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ያስነብባል፡፡ ይህ ሁነት በሀይማኖት ውስጥ ካለው ቦታ ባለፈ ግን ለተመራማሪዎች አጓጊ የሆነ ጥያቄን ያጭራል፤ የትኛዋ ናት የቤተልሄም ኮከብ? ጥያቄው ከሃይማኖት እና ታሪክ ውጪም ያሉ ምሁራንን ሲያጠያየይቅ የቆየ ነው፡፡ ይህን ጉዳይ ለማብራራት ያለሙ ልዩ ልዩ የሕዋ ምርምር ሀልዮቶች ሲነገሩ ቢቆዩም አሁን ላይ ግን ወደ መልሱ እየቀረብን መስሏል፡፡
የቤተልሄም ኮከብ ኮሜት ወይም የፈነዳች ኮከብ አልነበረችም
ሀሌይ ተብላ የምትታወቀው ኮሜት በ11 ዓመተ ዓለም ትታይ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ምድር በተሽከረከረች ቁጥር ቦታዋም እየተለወወጠ ስለሚመጣ የተጠቀሰችው ኮከብ የሀሌይ ኮሜት አትመስልም፡፡ ከዚህም ባሻገር በጥንት ጊዜ ኮሜቶች እንደ መጥፎና የጥፋት ምልክት ተደርገው ይታዩ ስለነበር ከሁነቱ ጋር ያላት ትስስር እጅጉን አጠራጣሪ ነው፡፡
ተመራማሪዎች በዚህ ወቅት የኮከብ ፍንዳታ ወይም ሱፕርኖቫ ስለመከሰቱ የሚያሳይ ማስረጃ አለማግኘታቸውም የኮከብ ፍንዳታን ከእጩነቱ ያገላል፡፡ በተጨማሪ ሰብአ ሰገል ይህን ተከትለው ቢሆን ኖሮ የተጓዙት በከዋክብቱ ባሕርይ ምክንያት ክብ እየዞሩ በቆዩ ነበር፡፡
ሌሎች ተመራማሪዎች እ.አ.አ 2005 ላይ የወጣን ጥናት ላይ ተመርኩዘው የሚሰጧቸው ሀልዮቶች ደግሞ በአንድሮሜዳ ጋላክሲ ውስጥ የተከሰተ የኮከ ፍንዳታን ለሁነቱ በምክንያትነት ያቀርባሉ፡፡ ሆኖም ምንም እንኳን ጋላክሲውን ያለ መሳርያ እርዳታ በአይናችን ልንመለከተው የምንችል ቢሆንም ኮከቡ ሲፈነዳ ግን በቴሌስኮፕ እርዳታ እንኳን የሚቻል አልነበረም፡፡
ኮከብ ሲባል ሰማዩ በከዋክብት መሞላቱን ለማመላከት ይሆን?
ይህ ወደ ሁለት ግምቶች ይመራናል፡፡ አንደኛው ሰብአ ሰገል ሰማዩን በኮከብ ቆጠራ አማካኝነት ተርጉመውት ነበር የሚለው ነው፡፡ በቦታው ሲደርሱ ሄሮድስን አቅጣጫ መጠየቃቸው ጉዞዋቸው እስከመጨረሻው ድረስ ሙሉ በሙሉ በኮከብ እየተመሩ ስላለማድረጋቸው ጥቁምታን ይሰጠናል፡፡ በጊዜው የኮከብ ቆጠራ በከፍተኛ ደረጃ ጥቅም ላይ ይውል የነበረ በመሆኑ ኮከቡን በምስራቅ አይተው የመጡት ሰብአ ሰገልም ኮከብ ቆጣሪዎች ይሆናሉ ተብሎ ይገመታል፡፡ በፕላኔቶች እና ከዋክብት መካከል ልዩ ቅንጅት እንደመኖሩ ሰብአ ሰገል በከዋክብቱ መካከል የሰፈረውን ምስጢራዊ መልዕክት አንብበው ከሄሮድስ ዘንድ ሄደው ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሳሌ የከዋክብት ቆጠራ ጁፒተርን ከነገስታት ጋራ እንደማስተሳሰሩ እና ጨረቃም በ17 እንዲሁም 6 ዓ.ዓ በኤሪስ ህብረ ኮከብ ውስጥ እንደማለፏ መጠን የጁፒተር ዕይታ በጉዳዩ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ሊኖረውና የክርስቶስን መወለድም አመላክቶ ይችላል፡፡
ኮከቧ የጥምረት ውጤት ብትሆንስ?
ሌላኛው የህዋ ምርምር ማብራርያ በፕላኔት እና ከዋክብት መካከል የተፈጠረ ጥምረትን ተከትሎ የመጣ አብሪ ነገር በሰማይ ታይቶ ነበር የሚለው ነው፡፡ ይህ አይነት ጥምረት ሁለት ወይም ከዚያ የበለጡ የህዋ አካላት በጨለማ ሰማይ ሲገናኙ ከምድራችን ሆኖ ማየት ሲቻል የሚፈጠር ነው፡፡ ይህ ሁነት በተመሳሳይ ቦታ ላይ ተኮኖ ለቀናት ከፍ ሲልም ለሳምንታት በዚህ አኳሀን ሊታዩ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ጥበበኛ ሰዎችም ጥምረቱን እየተከታተሉ የነበር ከሆነ ወደ አንድ ቦታ መርቷቸው ይሆናል፡፡ የህዋ ተመራማሪው ማይክል ሞልናርም “ዘ ስታር ኦፍ ቤተልሄም” በሚለውን መፅሐፉ ትክክለኛው ሀልዮት ይህ ሊሆን እንደሚችል ያስቀምጣል፡፡ 17 እና 6 ዓ.ዓ የተከሰተው የፀሐይ፣ ጁፒተር፣ ሳተርን፣ እና ጨረቃ በኤሪስ ህብረ ኮከብ ላይ ያሳዩት መጣመር በተወሰኑ ምክንያቶች በመፅሐፍ ቅዱስ ከሰፈረው ታሪክ ጋር ይገጥማል፡፡ በመጀመሪያ ይህ ጥምረት የተፈጠረው ወደ ንጋት ላይ መሆኑ መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ኮከቧ በንጋት ላይ እንደወጣች ተደርጋ ከመገለጿ ጋር ይገጥማል፡፡ ክርስቶስ ያለበት ቦታ ላይ ዳግም ከማየታቸው በፊትም ኮከቧ ከሰብዓ ሰገል ተሰውራ ነበር፡፡ ይህም ምድር ስትዞር አቅጣጫዋን መቀየሯንና ጁፒተርም የዕይታ አቅጣጫዋን በጨለማ ትታይበት የነበረውን ስፍራ መቀሯን ተከትሎ የመጣ ሊሆን የሚችል ነው፡፡
ሌሎች በተመሳሳይ ጊዜ የተከሰቱ ሁለት ጥምረቶችም ለጉዳዩ ቀረብ ብለው ተገኝተዋል፡፡ አንደኛው በሰኔ 17 2ኛው ዓ.ዓ ላይ የተከሰተው የጁፒተር፣ ቬኑስ እና ሬግዩለስ ኮከብ ግንኙነት ሲሆን ሁለቱ ፕላኔቶች ለየብቻቸው ይታዩ ከነበረው በላይ ደምቀው ያለ ምንም ቴሌስኮፕ እርዳታ በቅንጅት እንደ አንድ ኮከብ ሆነው ታይተው ነበር፡፡ ሌላኛው ጥምረት ስድስተኛው ዓ.ዓ ላይ በጁፒተር፣ ሳተርን እና ማርስ ፓይሲስ ህብረ ኮከብ ላይ የፈጠሩት ጥምረት ነው፡፡ ሆኖም ሁለቱም የተገለፁት ጥምረቶች መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ከተቀመጠው አኳሀን በማይገነኝ መልኩ የተፈጠሩ ናቸው፡፡
የማይፈታው ምስጢር
ተመራማሪዎች የቤተልሄም ኮከብን የሚያብራሩ ልዩ ልዩ ሀልዮቶችን ከስራ ውጪ ያደረጉ ቢሆንም ይህች ኮከብ የትኛዋ እንደነበረች ወይም ስለመፈጠሯ ሳይንስ ምላሽ ሳይሰጥ ሊቀር ይችላል፡፡ ሆኖም ጉዳዩ ዛሬም ሆነ ወደፊት የብዙ ተመራማሪዎችን የማወቅ ፍላጎት እየኮረኮረ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 2 ሦስት ጥበበኛ ሰዎች የተወለደውን ንጉስ ፍለጋ አሁን ላይ “የቤተልሄም ኮከብ” ተብላ የምትታወቀው ኮከብን ተከትለው ወደ እየሩሳሌም ማቅናታቸው ተነግሯል፡፡ ሄሮድስን በማማከርም የተወለደውን ህፃን በቤተልሄም ማግኘታቸውን ይህ የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ያስነብባል፡፡ ይህ ሁነት በሀይማኖት ውስጥ ካለው ቦታ ባለፈ ግን ለተመራማሪዎች አጓጊ የሆነ ጥያቄን ያጭራል፤ የትኛዋ ናት የቤተልሄም ኮከብ? ጥያቄው ከሃይማኖት እና ታሪክ ውጪም ያሉ ምሁራንን ሲያጠያየይቅ የቆየ ነው፡፡ ይህን ጉዳይ ለማብራራት ያለሙ ልዩ ልዩ የሕዋ ምርምር ሀልዮቶች ሲነገሩ ቢቆዩም አሁን ላይ ግን ወደ መልሱ እየቀረብን መስሏል፡፡
የቤተልሄም ኮከብ ኮሜት ወይም የፈነዳች ኮከብ አልነበረችም
ሀሌይ ተብላ የምትታወቀው ኮሜት በ11 ዓመተ ዓለም ትታይ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ምድር በተሽከረከረች ቁጥር ቦታዋም እየተለወወጠ ስለሚመጣ የተጠቀሰችው ኮከብ የሀሌይ ኮሜት አትመስልም፡፡ ከዚህም ባሻገር በጥንት ጊዜ ኮሜቶች እንደ መጥፎና የጥፋት ምልክት ተደርገው ይታዩ ስለነበር ከሁነቱ ጋር ያላት ትስስር እጅጉን አጠራጣሪ ነው፡፡
ተመራማሪዎች በዚህ ወቅት የኮከብ ፍንዳታ ወይም ሱፕርኖቫ ስለመከሰቱ የሚያሳይ ማስረጃ አለማግኘታቸውም የኮከብ ፍንዳታን ከእጩነቱ ያገላል፡፡ በተጨማሪ ሰብአ ሰገል ይህን ተከትለው ቢሆን ኖሮ የተጓዙት በከዋክብቱ ባሕርይ ምክንያት ክብ እየዞሩ በቆዩ ነበር፡፡
ሌሎች ተመራማሪዎች እ.አ.አ 2005 ላይ የወጣን ጥናት ላይ ተመርኩዘው የሚሰጧቸው ሀልዮቶች ደግሞ በአንድሮሜዳ ጋላክሲ ውስጥ የተከሰተ የኮከ ፍንዳታን ለሁነቱ በምክንያትነት ያቀርባሉ፡፡ ሆኖም ምንም እንኳን ጋላክሲውን ያለ መሳርያ እርዳታ በአይናችን ልንመለከተው የምንችል ቢሆንም ኮከቡ ሲፈነዳ ግን በቴሌስኮፕ እርዳታ እንኳን የሚቻል አልነበረም፡፡
ኮከብ ሲባል ሰማዩ በከዋክብት መሞላቱን ለማመላከት ይሆን?
ይህ ወደ ሁለት ግምቶች ይመራናል፡፡ አንደኛው ሰብአ ሰገል ሰማዩን በኮከብ ቆጠራ አማካኝነት ተርጉመውት ነበር የሚለው ነው፡፡ በቦታው ሲደርሱ ሄሮድስን አቅጣጫ መጠየቃቸው ጉዞዋቸው እስከመጨረሻው ድረስ ሙሉ በሙሉ በኮከብ እየተመሩ ስላለማድረጋቸው ጥቁምታን ይሰጠናል፡፡ በጊዜው የኮከብ ቆጠራ በከፍተኛ ደረጃ ጥቅም ላይ ይውል የነበረ በመሆኑ ኮከቡን በምስራቅ አይተው የመጡት ሰብአ ሰገልም ኮከብ ቆጣሪዎች ይሆናሉ ተብሎ ይገመታል፡፡ በፕላኔቶች እና ከዋክብት መካከል ልዩ ቅንጅት እንደመኖሩ ሰብአ ሰገል በከዋክብቱ መካከል የሰፈረውን ምስጢራዊ መልዕክት አንብበው ከሄሮድስ ዘንድ ሄደው ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሳሌ የከዋክብት ቆጠራ ጁፒተርን ከነገስታት ጋራ እንደማስተሳሰሩ እና ጨረቃም በ17 እንዲሁም 6 ዓ.ዓ በኤሪስ ህብረ ኮከብ ውስጥ እንደማለፏ መጠን የጁፒተር ዕይታ በጉዳዩ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ሊኖረውና የክርስቶስን መወለድም አመላክቶ ይችላል፡፡
ኮከቧ የጥምረት ውጤት ብትሆንስ?
ሌላኛው የህዋ ምርምር ማብራርያ በፕላኔት እና ከዋክብት መካከል የተፈጠረ ጥምረትን ተከትሎ የመጣ አብሪ ነገር በሰማይ ታይቶ ነበር የሚለው ነው፡፡ ይህ አይነት ጥምረት ሁለት ወይም ከዚያ የበለጡ የህዋ አካላት በጨለማ ሰማይ ሲገናኙ ከምድራችን ሆኖ ማየት ሲቻል የሚፈጠር ነው፡፡ ይህ ሁነት በተመሳሳይ ቦታ ላይ ተኮኖ ለቀናት ከፍ ሲልም ለሳምንታት በዚህ አኳሀን ሊታዩ ይችላሉ፡፡ እነዚህ ጥበበኛ ሰዎችም ጥምረቱን እየተከታተሉ የነበር ከሆነ ወደ አንድ ቦታ መርቷቸው ይሆናል፡፡ የህዋ ተመራማሪው ማይክል ሞልናርም “ዘ ስታር ኦፍ ቤተልሄም” በሚለውን መፅሐፉ ትክክለኛው ሀልዮት ይህ ሊሆን እንደሚችል ያስቀምጣል፡፡ 17 እና 6 ዓ.ዓ የተከሰተው የፀሐይ፣ ጁፒተር፣ ሳተርን፣ እና ጨረቃ በኤሪስ ህብረ ኮከብ ላይ ያሳዩት መጣመር በተወሰኑ ምክንያቶች በመፅሐፍ ቅዱስ ከሰፈረው ታሪክ ጋር ይገጥማል፡፡ በመጀመሪያ ይህ ጥምረት የተፈጠረው ወደ ንጋት ላይ መሆኑ መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ኮከቧ በንጋት ላይ እንደወጣች ተደርጋ ከመገለጿ ጋር ይገጥማል፡፡ ክርስቶስ ያለበት ቦታ ላይ ዳግም ከማየታቸው በፊትም ኮከቧ ከሰብዓ ሰገል ተሰውራ ነበር፡፡ ይህም ምድር ስትዞር አቅጣጫዋን መቀየሯንና ጁፒተርም የዕይታ አቅጣጫዋን በጨለማ ትታይበት የነበረውን ስፍራ መቀሯን ተከትሎ የመጣ ሊሆን የሚችል ነው፡፡
ሌሎች በተመሳሳይ ጊዜ የተከሰቱ ሁለት ጥምረቶችም ለጉዳዩ ቀረብ ብለው ተገኝተዋል፡፡ አንደኛው በሰኔ 17 2ኛው ዓ.ዓ ላይ የተከሰተው የጁፒተር፣ ቬኑስ እና ሬግዩለስ ኮከብ ግንኙነት ሲሆን ሁለቱ ፕላኔቶች ለየብቻቸው ይታዩ ከነበረው በላይ ደምቀው ያለ ምንም ቴሌስኮፕ እርዳታ በቅንጅት እንደ አንድ ኮከብ ሆነው ታይተው ነበር፡፡ ሌላኛው ጥምረት ስድስተኛው ዓ.ዓ ላይ በጁፒተር፣ ሳተርን እና ማርስ ፓይሲስ ህብረ ኮከብ ላይ የፈጠሩት ጥምረት ነው፡፡ ሆኖም ሁለቱም የተገለፁት ጥምረቶች መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ከተቀመጠው አኳሀን በማይገነኝ መልኩ የተፈጠሩ ናቸው፡፡
የማይፈታው ምስጢር
ተመራማሪዎች የቤተልሄም ኮከብን የሚያብራሩ ልዩ ልዩ ሀልዮቶችን ከስራ ውጪ ያደረጉ ቢሆንም ይህች ኮከብ የትኛዋ እንደነበረች ወይም ስለመፈጠሯ ሳይንስ ምላሽ ሳይሰጥ ሊቀር ይችላል፡፡ ሆኖም ጉዳዩ ዛሬም ሆነ ወደፊት የብዙ ተመራማሪዎችን የማወቅ ፍላጎት እየኮረኮረ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ Live Science
የሰዎችን የፊት ገጽ ፎቶ ወደ ስዕል የመቀየሪያ ስልት
*********************************
በህንድ በሚገኝ አንድ የሮቦቲክስ የምርምር ማእከል የሚሰሩ ተመራማሪዎች በቅርቡ የሰዎችን የፊት ገጽ ፎቶ ወደ ስእል መቀየር የሚያስችል የሰው ሰራሽ አስተውሎት መንገድ ማበልጸጋቸው ተሰምቷል፡፡ ይህ ስልትም ጆርዳን ከርቭ ከሚባለው የአሳሳል ስልት ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው፡፡ ግኝታቸውንም ኪትራካር ሲሉ ሰይመውታል፡፡ የቃሉ አቻ ፍችም ሰዓሊ እንደማለት ነው፡፡
ይህ ጆርዳን ከረፍቭ መነሻውና መድረሻው ተመሳሳይ የሆነ አንድን ስዕል ያለምም መቆራረጥ መሳል የሚያስችል ነጠላ መስመር ነው፡፡ ይህ ኪትራካር የተባለ ስልት የአንድን ፎቶ መሰረታዊና ጥቃቅን ነገሮች በመረዳት እና የተለያዩ ስዕላዊ ቴክኒኮችን በመጠቀም ስዕልን መስራት የሚያስችል ነው፡፡
እንደ ተመራማሪዎቹ ገለጻ ይህ አዲሱ ስልት በመሰረታዊነት የሚሰራው ስራ አንድን የፊት ገጽ ፎቶ ወደ ጆርዳን ከርቪንግ አሳሳል ስልት መቀየር ነው፡፡ ሮቦቱ የተለያየ ቀለምና ውፍረት ያላቸውን መሳያ እስክርቢቶዎች የሚጠቀም እንደሆነ ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡ አንድ ደንበኛ ሰዓሊ ማድረግ ከሚችለው በተሻለ የአንድን ሰው ፊት ጥንቅቅ አድጎ ከ30 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ መሳል እደሚችል ኪትራካር ስለተባለው በሮቦት የታገዘ የአሳሳል ስልት ተነግሮለታል፡፡
ለስራው በተለያዩ ሀገራት የአእምሮ ንብረት ማረጋገጫ እየተሰጠው እደሆነ የገለጹት ተመራማሪዎቹ በቅርቡም በስፋ አገልግሎት ላይ እንደሚውል ተናግረዋል፡፡ ይህንንም መንገድ በማስፋ በሰዎች በቀላሉ የማሰሩ የተለያዩ ሞዴሎችን ለመስራት ማቀዳቸውን ተመራማሪዎቹ አስረድተዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
*********************************
በህንድ በሚገኝ አንድ የሮቦቲክስ የምርምር ማእከል የሚሰሩ ተመራማሪዎች በቅርቡ የሰዎችን የፊት ገጽ ፎቶ ወደ ስእል መቀየር የሚያስችል የሰው ሰራሽ አስተውሎት መንገድ ማበልጸጋቸው ተሰምቷል፡፡ ይህ ስልትም ጆርዳን ከርቭ ከሚባለው የአሳሳል ስልት ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው፡፡ ግኝታቸውንም ኪትራካር ሲሉ ሰይመውታል፡፡ የቃሉ አቻ ፍችም ሰዓሊ እንደማለት ነው፡፡
ይህ ጆርዳን ከረፍቭ መነሻውና መድረሻው ተመሳሳይ የሆነ አንድን ስዕል ያለምም መቆራረጥ መሳል የሚያስችል ነጠላ መስመር ነው፡፡ ይህ ኪትራካር የተባለ ስልት የአንድን ፎቶ መሰረታዊና ጥቃቅን ነገሮች በመረዳት እና የተለያዩ ስዕላዊ ቴክኒኮችን በመጠቀም ስዕልን መስራት የሚያስችል ነው፡፡
እንደ ተመራማሪዎቹ ገለጻ ይህ አዲሱ ስልት በመሰረታዊነት የሚሰራው ስራ አንድን የፊት ገጽ ፎቶ ወደ ጆርዳን ከርቪንግ አሳሳል ስልት መቀየር ነው፡፡ ሮቦቱ የተለያየ ቀለምና ውፍረት ያላቸውን መሳያ እስክርቢቶዎች የሚጠቀም እንደሆነ ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡ አንድ ደንበኛ ሰዓሊ ማድረግ ከሚችለው በተሻለ የአንድን ሰው ፊት ጥንቅቅ አድጎ ከ30 ደቂቃ ባነሰ ጊዜ ውስጥ መሳል እደሚችል ኪትራካር ስለተባለው በሮቦት የታገዘ የአሳሳል ስልት ተነግሮለታል፡፡
ለስራው በተለያዩ ሀገራት የአእምሮ ንብረት ማረጋገጫ እየተሰጠው እደሆነ የገለጹት ተመራማሪዎቹ በቅርቡም በስፋ አገልግሎት ላይ እንደሚውል ተናግረዋል፡፡ ይህንንም መንገድ በማስፋ በሰዎች በቀላሉ የማሰሩ የተለያዩ ሞዴሎችን ለመስራት ማቀዳቸውን ተመራማሪዎቹ አስረድተዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
መላው ክርስትና እምነት ተከታይ ቤተሰቦቻችን በሙሉ፤ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ!!! ሁላችሁም ባላችሁበት መልካም በዓልን ታሳልፉ ዘንድ ምኞታችን ነው፡፡
ከቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት
ከቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት