እጅግ ፈጣን የጎግል ጎ መተግበሪያ ቀረበ
ጎግል ያለ በይነ መረብ መረጃን ለመላላክ የሚያስችለው ጎ መተግበሪያው ላይ ማሻሻያ ማድረጉ ተነግሯል። ጎግል ጎ የተባለውን መተግበሪያውን ባሳለፍነው ዓመት ያስተዋወቀ ሲሆን፥ መተግበሪያውም የአንድሮይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም በሚጠቀሙ ስልኮች ላይ ነው የሚሰራው።
መተግበሪያው በስልካችን ላይ ያሉንን መረጃዎች አስተካክለን ለመያዝ የሚረዳ ሲሆን፥ ያለ በይነ-መረብ ግንኙነትም በተወሰነ ክልል ውስጥ ላሉ ስልኮች የተለያዩ መረጃዎችን በፍጥነት ለመላላክ ያገለግላል።በተጨማሪም በስልካች ላይ ያሉ ፋይሎችን ከፋፍለን ለማስቀመጥ፣ ስልካችን በሚሞላት ጊዜ አላስፈላጊ ፋይሎችን ለማጥፋት፣ በስልካችን ውስጥ ካለው የመረጃ መያዣ ምን ያህሉን እንደተቀምንና እንደቀረን ለማወቅ፣ ተመሳሳይ ፋይሎችን ለማጥፋት፣ ፋይሎቻችን እንዳይጠፉብት ጎግል ድራይቭ ላይ ለማስቀመጥ እና የማንጠቀምባቸውን መተግበሪያዎች አን-ኢንስቶል ለማድረግ የሚረዳ ነው።
ይህ ማሻሻያ የተደረገለት አዲሱ የጎግል ጎ መተግበሪያ ላይ “ሼር (Share)” የሚል አማራጭ የምናገኝ ሲሆን፥ ይህንን በመንካትም እንደ ፎቶግራፍ፣ ተንቀሳቃሽ ምስል እና ሌሎችም በስልካችን ላይ ያሉ ፋይሎችን በፍጥነት መላላክ አንችላለን። መረጃን የሚያስተላልፍበት ፍጥነትም ከዚህ ቀደም ከነበረው በአራት እጥፍ ጨምሯል የተባለ ሲሆን፥ በተሻሻለው መሰረትም በሰከንድ 490 ሜጋ ባይት መረጃን ለመላላክ ያስችላል። ይህ ማለት ከፍተኛ ጥራት ያላቸው 100 ፎቶ ግራፎ ምስሎችን ከ5 ሴኮንድ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከአንድ ስልክ ወደ ሌላ ስልክ ያስተላልፋል። በሁለት ስልኮች መካከል መረጃ ለመለዋወጥም ስልኮቹን በ5 ሰከንዶች ውስጥ ማገናኘት እንደሚችል ተነግሮለታል።
መተግበሪያው በቅርቡ በጎግል ፒክስል ስልክ ላይ ተጭኖ ከተለቀቀው የአንድሮይድ መተግበሪያ ስሪት ጀምሮ እስክ አንድሮይድ 5.0 የሚጠቀሙ ማንኛውም ስልኮች ላይ በመጫን መጠቀም እንችላለን። አዲሱን የጎግል ጎ ከፈለጋችሁም ወደ ጎግል ፕላይ ስቶር ጎራ በማለት ማግኘት ይችላሉ።
ምንጭ፦ Techworm
ጎግል ያለ በይነ መረብ መረጃን ለመላላክ የሚያስችለው ጎ መተግበሪያው ላይ ማሻሻያ ማድረጉ ተነግሯል። ጎግል ጎ የተባለውን መተግበሪያውን ባሳለፍነው ዓመት ያስተዋወቀ ሲሆን፥ መተግበሪያውም የአንድሮይድ ኦፕሬቲንግ ሲስተም በሚጠቀሙ ስልኮች ላይ ነው የሚሰራው።
መተግበሪያው በስልካችን ላይ ያሉንን መረጃዎች አስተካክለን ለመያዝ የሚረዳ ሲሆን፥ ያለ በይነ-መረብ ግንኙነትም በተወሰነ ክልል ውስጥ ላሉ ስልኮች የተለያዩ መረጃዎችን በፍጥነት ለመላላክ ያገለግላል።በተጨማሪም በስልካች ላይ ያሉ ፋይሎችን ከፋፍለን ለማስቀመጥ፣ ስልካችን በሚሞላት ጊዜ አላስፈላጊ ፋይሎችን ለማጥፋት፣ በስልካችን ውስጥ ካለው የመረጃ መያዣ ምን ያህሉን እንደተቀምንና እንደቀረን ለማወቅ፣ ተመሳሳይ ፋይሎችን ለማጥፋት፣ ፋይሎቻችን እንዳይጠፉብት ጎግል ድራይቭ ላይ ለማስቀመጥ እና የማንጠቀምባቸውን መተግበሪያዎች አን-ኢንስቶል ለማድረግ የሚረዳ ነው።
ይህ ማሻሻያ የተደረገለት አዲሱ የጎግል ጎ መተግበሪያ ላይ “ሼር (Share)” የሚል አማራጭ የምናገኝ ሲሆን፥ ይህንን በመንካትም እንደ ፎቶግራፍ፣ ተንቀሳቃሽ ምስል እና ሌሎችም በስልካችን ላይ ያሉ ፋይሎችን በፍጥነት መላላክ አንችላለን። መረጃን የሚያስተላልፍበት ፍጥነትም ከዚህ ቀደም ከነበረው በአራት እጥፍ ጨምሯል የተባለ ሲሆን፥ በተሻሻለው መሰረትም በሰከንድ 490 ሜጋ ባይት መረጃን ለመላላክ ያስችላል። ይህ ማለት ከፍተኛ ጥራት ያላቸው 100 ፎቶ ግራፎ ምስሎችን ከ5 ሴኮንድ ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከአንድ ስልክ ወደ ሌላ ስልክ ያስተላልፋል። በሁለት ስልኮች መካከል መረጃ ለመለዋወጥም ስልኮቹን በ5 ሰከንዶች ውስጥ ማገናኘት እንደሚችል ተነግሮለታል።
መተግበሪያው በቅርቡ በጎግል ፒክስል ስልክ ላይ ተጭኖ ከተለቀቀው የአንድሮይድ መተግበሪያ ስሪት ጀምሮ እስክ አንድሮይድ 5.0 የሚጠቀሙ ማንኛውም ስልኮች ላይ በመጫን መጠቀም እንችላለን። አዲሱን የጎግል ጎ ከፈለጋችሁም ወደ ጎግል ፕላይ ስቶር ጎራ በማለት ማግኘት ይችላሉ።
ምንጭ፦ Techworm
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ለቀጨኔ ሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከል የኮምፒውተር ልገሳ አደረገ።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት አመራሮች የቀጨኔ ሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከልን ጎበኙ። በማእከሉ ውስጥ የሚገኘውን ቤተመጽሃፍት በኮምፒውተር ለማደራጀት የሚረዱ ከአንድ ሚልየን በላይ መጽሃፍት የተጫኑባቸው 15 ኮምፒውተሮችን ኢኒስቲትዩቱን በመወከል የኢኒስቱትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ለህጻናት ሴቶችና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ አስረክበዋል።
ክብርት ወይዘሮ አለሚቱ ኡመድ የህጻናት ሴቶችና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ የሴቶችና ህጻናትን ጥቃት ለመቅረፍና ብቁ ዜጋን ለማፍራት የሁሉም ዜጋ ያልተቋረጠ ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል። ህጻናት ክየትኛውም እገዛ በላይ የሚያስፈልጋቸው ፍቅር ነው ያሉት ሚኒስትር ድኤታዋ ከየትኛውም ቁሳዊ ልገሳ በላይ ኣንዲህ ጎብኝቷቸው ከጎናችሁ ነን የሚላቸው ቤተሰብ፣ አይዞን የሚል ዘመድ እና እኔን የሚል ወገን ህጻናት ይፈልጋሉ ብለው የኢኒስቲትዩቱን ጉብኝትና ድጋፍ አመስግነዋል።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ በበኩላቸው ኢኒስቲትዩቱ የሚያደርጋቸውን ማህበራዊ ተሳትፎዎቹ ሰፊ ሆነው ሳለ ይህን ብዙዎች ሊያውቁትና ሊደግፉት የሚገባ ሆኖ ሳለ በብዙሃን የተዘነጋውን የሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከል ለመመልከት እስካሁን በመዘግየታችን ተቆጭተናል ብለዋል። አስር ብር ለኣንድ ሰው መስጠት አስር ብርን ለአስር ሰው አከፋፍሎ ከመስጠት ይሻላል ያሉት ዋናው ዳይሬክተሩ፡ የምናደጋቸውን እገዛዎች በተበታተነና ባልተደራጀ መልኩ ከማድረግ ወጥተን ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ እገዛዎች ላይ ማተኮር ይገባል ብለዋል። በቀጣይም ለማእከሉ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የቀጨኔ ሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከል በ1944 በእቴጌ መነን ወላጅ ላጡ ሴት ህጻናት ማሳገደጊያነት የተቋቋመ ነው። በአሁኑ ወቅት ማእከሉ እድሜያቸው ከ6 አመት በላይ የሆኑ 187 ሴት ታዳጊዎችን እያሳደገ ያለ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 12 ልዩ እገዛ የሚሹና 8 የኣእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ሴት ታዳጊዎች ናቸው።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት አመራሮች የቀጨኔ ሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከልን ጎበኙ። በማእከሉ ውስጥ የሚገኘውን ቤተመጽሃፍት በኮምፒውተር ለማደራጀት የሚረዱ ከአንድ ሚልየን በላይ መጽሃፍት የተጫኑባቸው 15 ኮምፒውተሮችን ኢኒስቲትዩቱን በመወከል የኢኒስቱትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ለህጻናት ሴቶችና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ አስረክበዋል።
ክብርት ወይዘሮ አለሚቱ ኡመድ የህጻናት ሴቶችና ወጣቶች ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ የሴቶችና ህጻናትን ጥቃት ለመቅረፍና ብቁ ዜጋን ለማፍራት የሁሉም ዜጋ ያልተቋረጠ ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል። ህጻናት ክየትኛውም እገዛ በላይ የሚያስፈልጋቸው ፍቅር ነው ያሉት ሚኒስትር ድኤታዋ ከየትኛውም ቁሳዊ ልገሳ በላይ ኣንዲህ ጎብኝቷቸው ከጎናችሁ ነን የሚላቸው ቤተሰብ፣ አይዞን የሚል ዘመድ እና እኔን የሚል ወገን ህጻናት ይፈልጋሉ ብለው የኢኒስቲትዩቱን ጉብኝትና ድጋፍ አመስግነዋል።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ በበኩላቸው ኢኒስቲትዩቱ የሚያደርጋቸውን ማህበራዊ ተሳትፎዎቹ ሰፊ ሆነው ሳለ ይህን ብዙዎች ሊያውቁትና ሊደግፉት የሚገባ ሆኖ ሳለ በብዙሃን የተዘነጋውን የሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከል ለመመልከት እስካሁን በመዘግየታችን ተቆጭተናል ብለዋል። አስር ብር ለኣንድ ሰው መስጠት አስር ብርን ለአስር ሰው አከፋፍሎ ከመስጠት ይሻላል ያሉት ዋናው ዳይሬክተሩ፡ የምናደጋቸውን እገዛዎች በተበታተነና ባልተደራጀ መልኩ ከማድረግ ወጥተን ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ እገዛዎች ላይ ማተኮር ይገባል ብለዋል። በቀጣይም ለማእከሉ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የቀጨኔ ሴት ህጻናት ማሳደጊያና ማቆያ ማእከል በ1944 በእቴጌ መነን ወላጅ ላጡ ሴት ህጻናት ማሳገደጊያነት የተቋቋመ ነው። በአሁኑ ወቅት ማእከሉ እድሜያቸው ከ6 አመት በላይ የሆኑ 187 ሴት ታዳጊዎችን እያሳደገ ያለ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 12 ልዩ እገዛ የሚሹና 8 የኣእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ሴት ታዳጊዎች ናቸው።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በሳይንስ ጋዜጠኝነት እና ኮምዩኒኬሽን ላይ ያዘጋጀው ስልጠና ተጠናቀቀ።
ከታህሳስ 18 እስከ 19 2011 በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረው የሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚኒኬሽን ስልጠና በተለያዩ ዝግጅቶች ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዋናነት ስልጠናው የሚዲያ ባለሙያዎችን፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋማትን እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት መምህራንና ተማሪዎችን አሳትፏል፡፡ በአጠቃላይ ዝግጅቱ በአራት ዋና ዋና መርሃ ግብሮች ተከፋፍሎ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ብሎም ሳይንስ ጋዜጠኝነትን አብይ ጉዳይ በማድረግ በፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ፣ ዶክተር ጌታቸው ድንቁ፣ ዶክተር ጤናው ተረፈ እና ዶክተር ዮሃንስ ሽፈራው ስልጠና ሰጪነት እንዲሁም በታዳሚዎች ሀሳብ ሰንዛሪነት ተከናውኗል፡፡
ከስልጠናው ባሻገር ተሳታፊዎች ኢኒስቲትዩቱ ሰራተኞች ጋር በጋራ አዝናኝ የነበረ የቡና ጠጡ ዝግጅትን ታድመዋል።
በስተመጨረሻም የዝግጅቱን መዝጊያ ንግግር የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ሳህለ ማርያም ሲያደርጉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃን ለማህበረሰቡ የማድረስ ስራዎች በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት አቅም ብቻ ሊከወኑ ስለማይችሉ ሚዲያው የራሱን ድርሻ ወስዶ ሊሰራ እንደሚገባና ወርክሾፑም ይህን ማሳካት ያስችል ዘንድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ ለሰልጣኞችና አሰልጣኞች በምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
ከታህሳስ 18 እስከ 19 2011 በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረው የሳይንስ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኮሚኒኬሽን ስልጠና በተለያዩ ዝግጅቶች ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዋናነት ስልጠናው የሚዲያ ባለሙያዎችን፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋማትን እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት መምህራንና ተማሪዎችን አሳትፏል፡፡ በአጠቃላይ ዝግጅቱ በአራት ዋና ዋና መርሃ ግብሮች ተከፋፍሎ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ብሎም ሳይንስ ጋዜጠኝነትን አብይ ጉዳይ በማድረግ በፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ፣ ዶክተር ጌታቸው ድንቁ፣ ዶክተር ጤናው ተረፈ እና ዶክተር ዮሃንስ ሽፈራው ስልጠና ሰጪነት እንዲሁም በታዳሚዎች ሀሳብ ሰንዛሪነት ተከናውኗል፡፡
ከስልጠናው ባሻገር ተሳታፊዎች ኢኒስቲትዩቱ ሰራተኞች ጋር በጋራ አዝናኝ የነበረ የቡና ጠጡ ዝግጅትን ታድመዋል።
በስተመጨረሻም የዝግጅቱን መዝጊያ ንግግር የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ሳህለ ማርያም ሲያደርጉ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃን ለማህበረሰቡ የማድረስ ስራዎች በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት አቅም ብቻ ሊከወኑ ስለማይችሉ ሚዲያው የራሱን ድርሻ ወስዶ ሊሰራ እንደሚገባና ወርክሾፑም ይህን ማሳካት ያስችል ዘንድ ትልቅ ሚና እንደሚኖረው አፅዕኖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡ ለሰልጣኞችና አሰልጣኞች በምክትል ዋና ዳይሬክተሩ የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፡፡
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ላምባዲና ሶሻል ኮሚቴ የገናን በዓል አስመልክቶ የቡና ጠጡ ዝግጅት አካሄደ
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በዛሬው እለት የገናን በዓል እንዲሁም ተቋሙ የተመሰረተበትን አምስተኛ ዓመት በድምቀት አክብሯል፡፡ በዝግጅቱም ላይ የፋና ቴሌቪዥን ፋና ቀለማት የቤተሰብ ጥየቃ አዘጋጆች የታደሙበት ነበር፡፡ ከእነርሱም በተጨማሪ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚንስትርን ጨምሮ ልዩ ልዩ የመንግስት ከፍተኛ ሃላፊዎችና የተቋሙ የቀድሞ ባልደረባዎች ተገኝተው አክብረዋል፡፡ በዝግጅቱም አዝናኝ የሆኑ ልዩ ልዩ ውድድሮች የተካሄዱ ተካሂደዋል፡፡
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በዛሬው እለት የገናን በዓል እንዲሁም ተቋሙ የተመሰረተበትን አምስተኛ ዓመት በድምቀት አክብሯል፡፡ በዝግጅቱም ላይ የፋና ቴሌቪዥን ፋና ቀለማት የቤተሰብ ጥየቃ አዘጋጆች የታደሙበት ነበር፡፡ ከእነርሱም በተጨማሪ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚንስትርን ጨምሮ ልዩ ልዩ የመንግስት ከፍተኛ ሃላፊዎችና የተቋሙ የቀድሞ ባልደረባዎች ተገኝተው አክብረዋል፡፡ በዝግጅቱም አዝናኝ የሆኑ ልዩ ልዩ ውድድሮች የተካሄዱ ተካሂደዋል፡፡
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በቱሪዝም ዘርፉ ላይ የራሱን ሚና ለመወጣት ብሎም ዘርፉን ለማመንደግ የሚደረግ ሀገራዊ ጥረትን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የሚያስችለውን ስምምነት ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር ተፈራርሟል።
የስምምነት ሰነዱን በቱሪዝም ኢትዮጵያ በኩል ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን የቱሪዝም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ የፈረሙ ሲሆን በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በኩል ደግሞ የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ፈርመዋል።
ይህ በቱሪዝም ኢትዮጵያና በቴክኖሊጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት መካከል የተደረሰው መግባቢያ ብዙ የጋራ የሆኑ አንኳር ስራዎች የተካተቱበት ሲሆን በመጀመሪያ ምእራፍ ላይም የቱሪዝም ሳተላይት አካውንትን ለማስተዋወቅና በኢትዮጵያ ደረጃም በራስ አቅም አዳብሮና ኣልምቶ ስራላይ ለማዋል የሚደረግ ጥረትን ለመደገፍ የተደረሰ ስምምነት ነው።
የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት በአለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ የቱሪዝም እንቅስቃሴዎችና መዳረሻዎችን ጨምሮ ሌሎችም ቱሪዝም ነክ መረጃዎች የተካተቱበት ስርአት ሲሆን ኢትዮጵያም ይህን ስርአት መተግበሯ በቱሪዝም ዘርፉ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ፋይዳ እንደሚኖረው በፊርማ ስነስረአቱ ላይ ተገልጿል።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በቱሪዝም ዘርፉ ላይ የራሱን ሚና ለመወጣት ብሎም ዘርፉን ለማመንደግ የሚደረግ ሀገራዊ ጥረትን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የሚያስችለውን ስምምነት ከቱሪዝም ኢትዮጵያ ጋር ተፈራርሟል።
የስምምነት ሰነዱን በቱሪዝም ኢትዮጵያ በኩል ወይዘሪት ሌንሳ መኮንን የቱሪዝም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስኪያጅ የፈረሙ ሲሆን በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በኩል ደግሞ የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሳንዶካን ደበበ ፈርመዋል።
ይህ በቱሪዝም ኢትዮጵያና በቴክኖሊጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት መካከል የተደረሰው መግባቢያ ብዙ የጋራ የሆኑ አንኳር ስራዎች የተካተቱበት ሲሆን በመጀመሪያ ምእራፍ ላይም የቱሪዝም ሳተላይት አካውንትን ለማስተዋወቅና በኢትዮጵያ ደረጃም በራስ አቅም አዳብሮና ኣልምቶ ስራላይ ለማዋል የሚደረግ ጥረትን ለመደገፍ የተደረሰ ስምምነት ነው።
የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት በአለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙ የቱሪዝም እንቅስቃሴዎችና መዳረሻዎችን ጨምሮ ሌሎችም ቱሪዝም ነክ መረጃዎች የተካተቱበት ስርአት ሲሆን ኢትዮጵያም ይህን ስርአት መተግበሯ በቱሪዝም ዘርፉ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ፋይዳ እንደሚኖረው በፊርማ ስነስረአቱ ላይ ተገልጿል።
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን አስተዳደር እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያተኮረ ሴሚናር ተካሄደ።
በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን አስተዳደር እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን ሴሚናር ተከናውኗል፡፡ ኢኒስቲትዩቱ ያዘጋጀው ይህ ሴሚናር ላይ በደቡብ አፍሪካው ሽዋኔ ዩኒቨርሲቴ ኦፍ ቴክኖሎጂ ውስጥ በተመራማሪነት እያገለገሉ የሚገኙት ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ እንዲሁም መቀመጫውን በሃገረ አሜሪካን ካሊፎርኒያ ውስጥ ያደረገው የኤ ኤስ ሲ ኢንጂነሪንግ መስራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢንጂነር በሃይሉ አሰፋ ለተሳታፊዎች ገለጻዎች አድርገዋል፡፡
ዝግጅቱን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ተሾመ ሳህለማርያም በዓለም ሃገራት መካከል ያለው የሃብት ክፍፍል ምጣኔ በቴክኖሎጂ ባለቤትነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ታድያ ይህን ልዩነት ማጥበብና የሃገራትን እድገት ማረጋገጥ የሚቻለውም ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽንን እንደ ዋና መሳሪያ በመገልገል እንደሆነና፤ ኢኒስቲትዩቱም በዚህ ረገድ የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ አክለው አስታውቀዋል፡፡
በሴሚናሩ የጠዋት ክፍለ ጊዜ ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ Economic Development and Innovation፣ Components Making System of Innovation እና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተው አብራርተዋል፡፡ ቀጣዩን ክፍለ ጊዜም ኢንጂነር በሃይሉ አሰፋ በኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ በተለይም ተቋማቸው ኤ ኤስ ሲ ኢንጂነሪንግ በሃገራችን እያከናወነ ያለውን የፀሃይ እና ነፋስ ሃይል ማመንጫ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ ተግዳሮቶችና ተስፋዎች ላይ ለታዳሚዎቹ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን አስተዳደር እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢነርጂ ዘርፍ ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን ሴሚናር ተከናውኗል፡፡ ኢኒስቲትዩቱ ያዘጋጀው ይህ ሴሚናር ላይ በደቡብ አፍሪካው ሽዋኔ ዩኒቨርሲቴ ኦፍ ቴክኖሎጂ ውስጥ በተመራማሪነት እያገለገሉ የሚገኙት ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ እንዲሁም መቀመጫውን በሃገረ አሜሪካን ካሊፎርኒያ ውስጥ ያደረገው የኤ ኤስ ሲ ኢንጂነሪንግ መስራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ኢንጂነር በሃይሉ አሰፋ ለተሳታፊዎች ገለጻዎች አድርገዋል፡፡
ዝግጅቱን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ተሾመ ሳህለማርያም በዓለም ሃገራት መካከል ያለው የሃብት ክፍፍል ምጣኔ በቴክኖሎጂ ባለቤትነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ታድያ ይህን ልዩነት ማጥበብና የሃገራትን እድገት ማረጋገጥ የሚቻለውም ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽንን እንደ ዋና መሳሪያ በመገልገል እንደሆነና፤ ኢኒስቲትዩቱም በዚህ ረገድ የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ አክለው አስታውቀዋል፡፡
በሴሚናሩ የጠዋት ክፍለ ጊዜ ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ Economic Development and Innovation፣ Components Making System of Innovation እና ሌሎች ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተው አብራርተዋል፡፡ ቀጣዩን ክፍለ ጊዜም ኢንጂነር በሃይሉ አሰፋ በኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ በተለይም ተቋማቸው ኤ ኤስ ሲ ኢንጂነሪንግ በሃገራችን እያከናወነ ያለውን የፀሃይ እና ነፋስ ሃይል ማመንጫ መሰረተ ልማቶች ዝርጋታ ተግዳሮቶችና ተስፋዎች ላይ ለታዳሚዎቹ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
ስለ ፎሊክ አሲድ ምን ያህል ያውቃሉ ?
****************************
ሴቶች ከእርግዝና በፊትና በእርግዝና ወቅት የሚያደርጉት ጥንቃቄ ለራሳቸውም ሆነ ለሚወለደው ልጅ ጤንነት የራሱ የሆነ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ በተለይም በእርግዝና ወራት የሚያደርጓቸው ነገሮች ለልጁ ጤንነት ወሳኝ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከእነዚህ ነገሮች ውስጥ አንዱ ደግሞ ፎሊክ አሲድን በእንክብል መውሰድ ነው፡፡
ፎሊክ አሲድ ለጽንስ ዕድገት እጅግ አስፈላጊ የሆነና ከእርግዝና በፊት ለመጀመሪያዎቹ 12 ሳምንታት የሚወሰድ ንጥረ ነገር ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሁሉም ሴቶች ለማርገዝ ሲያስቡና በእርግዝና ወቅት ፎሊክ አሲድን መውሰድ እንዲሚገባቸው ይታመናል፤ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፎሊክ አሲድን መውሰድ ለሁሉም ሴቶች ጠቃሚ ይሆናል የሚለው ሀሳብ እንደማይሰራ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡ አንዳንድ ሴቶች ሰውነታቸው ውስጥ ያለው ጂን ለፎሊክ አሲድ ተስማሚ ላይሆን ስለሚችል ከፎሊክ አሲድ የተሻለ አማራጭ በመጠቀም ከፎሊክ አሲድ የሚገኘውን ጥቅም ማግኘት ይችላሉ፡፡
ፎሊክ አሲድና ፎሌት የሚሉት ቃላት ተቀራራቢ ትርጉም ያላቸው ሲሆኑ ሁለቱም የሚገልጹት ቫይታሚን ቢ9ን ነው፡፡ ፎሌት የተፈጥሮ ቫይታሚን ቢ9 ሲሆን እንደ ብሮኮሊ (አበባ ጎመን) እና ስፒናች ዓይነት ያሉ አረንጓዴ አትክልት ውስጥና ደረቅ ባቄላ መሳይ የቅባት እህል ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡ ፎሊክ አሲድ ግን በፋብሪካ ሂደት ውስጥ አልፈው በሚታሸጉ ምግቦች ውስጥ ሰው ሰራሽ ሆኖ የሚገኝ ቫይታሚን ቢ9 ነው፡፡
ከፍተኛ የፎሌት መጠን ያላቸውን ምግቦች ዘወትር በመመገብ በቀን 200 ማይክሮ ግራም ፎሌት ማግኘት ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን ለአንዳንድ ሰዎች ከዚህ የበለጠ የፎሌት መጠን አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ ፎሌት ወይም ፎሊክ አሲድ ጤናማ ለሆነ የጽንስ ዕድገት አስፈላጊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ለዚህም ነው ነፍሰጡር የሆኑ ሴቶች ከመደበኛው መጠን ዕጥፍ /400 ማይክሮ ግራም ፎሊክ አሲድ/ፎሌት መውሰድ እንዳለባቸው የሚነገረው፡፡ ይህን በማድረግም በጽንስ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን በማስወገድ ጤናማ የሆነ ልጅ መውለድ ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን ይህን ያህል ፎሌት አሲድ በተፈጥሮ ምግብ ውስጥ ማግኘት ከባድ በመሆኑ በተጨማሪነት በሕክምና የሚመረተውን እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡
ምንጭ፡ medical news today
****************************
ሴቶች ከእርግዝና በፊትና በእርግዝና ወቅት የሚያደርጉት ጥንቃቄ ለራሳቸውም ሆነ ለሚወለደው ልጅ ጤንነት የራሱ የሆነ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ በተለይም በእርግዝና ወራት የሚያደርጓቸው ነገሮች ለልጁ ጤንነት ወሳኝ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ከእነዚህ ነገሮች ውስጥ አንዱ ደግሞ ፎሊክ አሲድን በእንክብል መውሰድ ነው፡፡
ፎሊክ አሲድ ለጽንስ ዕድገት እጅግ አስፈላጊ የሆነና ከእርግዝና በፊት ለመጀመሪያዎቹ 12 ሳምንታት የሚወሰድ ንጥረ ነገር ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሁሉም ሴቶች ለማርገዝ ሲያስቡና በእርግዝና ወቅት ፎሊክ አሲድን መውሰድ እንዲሚገባቸው ይታመናል፤ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፎሊክ አሲድን መውሰድ ለሁሉም ሴቶች ጠቃሚ ይሆናል የሚለው ሀሳብ እንደማይሰራ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡ አንዳንድ ሴቶች ሰውነታቸው ውስጥ ያለው ጂን ለፎሊክ አሲድ ተስማሚ ላይሆን ስለሚችል ከፎሊክ አሲድ የተሻለ አማራጭ በመጠቀም ከፎሊክ አሲድ የሚገኘውን ጥቅም ማግኘት ይችላሉ፡፡
ፎሊክ አሲድና ፎሌት የሚሉት ቃላት ተቀራራቢ ትርጉም ያላቸው ሲሆኑ ሁለቱም የሚገልጹት ቫይታሚን ቢ9ን ነው፡፡ ፎሌት የተፈጥሮ ቫይታሚን ቢ9 ሲሆን እንደ ብሮኮሊ (አበባ ጎመን) እና ስፒናች ዓይነት ያሉ አረንጓዴ አትክልት ውስጥና ደረቅ ባቄላ መሳይ የቅባት እህል ውስጥ የሚገኝ ነው፡፡ ፎሊክ አሲድ ግን በፋብሪካ ሂደት ውስጥ አልፈው በሚታሸጉ ምግቦች ውስጥ ሰው ሰራሽ ሆኖ የሚገኝ ቫይታሚን ቢ9 ነው፡፡
ከፍተኛ የፎሌት መጠን ያላቸውን ምግቦች ዘወትር በመመገብ በቀን 200 ማይክሮ ግራም ፎሌት ማግኘት ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን ለአንዳንድ ሰዎች ከዚህ የበለጠ የፎሌት መጠን አስፈላጊ ሊሆን ይችላል፡፡ ፎሌት ወይም ፎሊክ አሲድ ጤናማ ለሆነ የጽንስ ዕድገት አስፈላጊ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ለዚህም ነው ነፍሰጡር የሆኑ ሴቶች ከመደበኛው መጠን ዕጥፍ /400 ማይክሮ ግራም ፎሊክ አሲድ/ፎሌት መውሰድ እንዳለባቸው የሚነገረው፡፡ ይህን በማድረግም በጽንስ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን በማስወገድ ጤናማ የሆነ ልጅ መውለድ ይቻላል፡፡ ሆኖም ግን ይህን ያህል ፎሌት አሲድ በተፈጥሮ ምግብ ውስጥ ማግኘት ከባድ በመሆኑ በተጨማሪነት በሕክምና የሚመረተውን እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡
ምንጭ፡ medical news today
የኢንተርኔት አጠቃቀሞን/ቢዝነሶን ከደህንነት ስጋት ውጪ ማድረግ ይፈልጋሉ
*****************************************
*****************
እንግዲያውስ እንዚህን 5 ነጥቦች በሚገባ ይመልከቷቸው
በየትኛውም ሁኔታ ስራዎ ከኢንተርኔት ጋር ተያያዥነት ካለው እንደ ድረገፅ፣ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት እንዲሁም እንደ የኢሜል አድራሻ ያሉ የዲጂታል ሃብቶች ለስራዎ የጀርባ አጥንት መሆናቸው አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም እነዚህን የዲጂታል መሳሪያዎች በሚጠቀሙበት ወቅት መረጃዎ ከርሶዎ አልፎ ወደ ሌላ ሶስተኛ ወገን ወይም ሌሎች የመረጃ መንታፊዎች ጋር እንዳይደርስ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል፡፡
አንደሚታወቀው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ በኢንተርኔት አጠቃቀም ዙሪያ ያሉ የደህንነት ስጋቶች ከመቼውም በላይ እየጨመሩ መምጣታቸው ብዙዎችን የሚያስማማ ሃቅ ነው፡፡ በየቀኑ ከፍተኛ ጥፋት የሚያደርሱ እና በተለያዩ የሳይበር ወንጀሎች የሚሳተፉ አካለት እጅግ በረቀቁ ስልቶችና በአዳዲስ ቴክኒኮች በመታገዝ ትልቅ የሚባሉ ኮርፖሬተሮችን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ድረገፆችን በመበርበርና ጥቃት በማድረስ ላይ ይገኛሉ፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ እንዚህ ትልልቅ የቢዝነስ ተቋማት ከመሰል የሳይበር ጥቃት የማያመልጡና እንደዚህ አይነት ስጋት የተጋረጠባቸው ከሆነ በመካከለኛ እና በትንንሽ የኦንላይን ቢዝነስ የተሰማሩ አካለት እጅጉን የሰፋ የደህንነት ስጋት እንደሚኖርባቸው የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ በመሆኑም ከኢንተርኔት ጋር ተያያዥነት ያለው ቢዝነስ የሚያካሂዱ ሰዎች እንዚህን አምስት ነጥቦች በሚገባ ቢያያዋቸው ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
1. አውቶማቲክ ማሻሻያዎች (Automated Updates)
አብዛኛውን ጊዜ የኦላይን ቢዝነስ የሚያካሂዱ ሰዎች የሚዘነጉት ጉዳይ ቢኖር ሲስተምን ያለማሻሻል ወይም system updates ያለማድረግ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም በቀላሉ ሃከሮች ሲስተሙን እንዲያውቁትና የሚፈልጉትን ጥቃትም በቀላሉ እንዲፈፅሙ ያግዛቸዋል፡፡ በመሆኑም ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸውን እያንዳንዳቸውን ሴስተሞች ማለትም ኦፕሬቴንግ ሲስተምን (operating systems) ጨምሮ ሌሎች የአፕሊኬሽን ሴስተሞችን እና የድረገፅ ፕለጊኖችን (website plugins) በሚገባ እንዲሻሻሉ ማድረግ ያለባቸውን ሳንካ (bugs) እንዲያስወግዱና የዲጂታል ሃብቱም በሚገባ እንዲጠበቅ ይረዳል፡፡
2. ባለብዙ-ንብርብር ደህንነት (Multi-Layer Security)
የድረገፅ መቆጣጠሪያ ፓኔልን ለማግኘት መሞከር እና በቁጥጥር ውስጥ እንዲሆን ማድረግ ብዞዎቹ የሳይበር ጥቃት አድራሾች የሚተገብሩትና የሚጠቀሙበት መንገድ ነው፡፡ ስለሆነም የኦላይን ቢዝነስ የሚያካሂዱ ሰዎች በድረገፃቸው ላይ የሚያደርጉት ቁጥጥር እንድ ጊዜ ከእጃቸው ወቶ በሃከሮች ቁጥጥር ውስጥ ከገባ መልሶ ለማግኘት እጅግ አዳጋች በመሆኑ አጠቃላይ ቢዝነሳቸው ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ ስለዚህም ከምንም በላይ የድረገፅ አጠቃቀም ቁጥጥርን ወይም (access control)ን ማጥበቅ እጅግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ታዲያ ባለብዙ-ንብርብር ደህንነት ማከል እና የሚጠቀሙትን የይለፍ ቃል አይነት በማርዘምና እጅግ በተወሳሰቡ የቁጥርና የፊደላት ጥርቅም በማስገባት ለግምት እንዲከብድ ማድረግ፤ የደህንነት ስጋቱን በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል፡፡
3. የአንቲቫይረስ ፕሮግራሞች (Antivirus Programs)
ዘላቂነት ባለው ሁኔታ ኮምፒውተሮን ከተለያዩ አጥፊ መተግበሪያዎች (malwares) እና አላስፈላጊ የሆኑ መልእክቶችን ለብዙዎች የማላክ ሁኔታ (spam) በመጠበቅ የኦንላይን ቢዝነሶ ከየትኛውም የሳይበር ጥቃት ራሱን እንዲከላከል ማድረግ የአንቲቫይረስ ፕሮግራሞች ከሚሰጧቸው ጥቅሞች ውስጥ ቀዳሚው ነው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ፕሮግራሞች በሚጠቀሙበት ወቅት ከፍተኛ ትኩረት ለሚያስፈልጋቸው ብሮውዘሮች (browsers) እና መተግበሪዎች ቅድሚያ በመስጠት ኮምፒውተሮን ከማንኛውም ቫይረስ እንዲጠብቁ ያስፈልጋል፡፡
4. የኔትዎርክ ጥበቃ
አብዛኛውን ጊዜ የኢንተርኔት ግንኙነትን በጋራ ኔትወርክ ሲጠቀሙ የሚያስተዳድሩት መረጃ ኔትወርኩን በሚጋራ ሌላ ተጠቃሚ ሊገኝና ሊደረስበት ይችላል፡፡ በተለይም በግንኙነቱ ወቅት የጠነከረ የኢንክሪፕሽን ቴክኒክ የማይኖር ከሆነ መረጃው በማንኛውም ሁኔታ ለጥቃት የመጋለጥ እድሉ ሰፊ ነው፡፡ በዚህ ረገድ እንደ ፋየርዎል (Firewall) ያሉ የኔትዎርክ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችን በመጠቀም በኔትዎርክ ትራፊኩ ላይ የሚገቡና የሚወጡ አካለትን መቆጣጠር ይቻላል፡፡ በመሆኑም በኮንትሮል ፓኔል (Control Panel) ላይ የፋየርዎል ገፅታን በማከል የኔትዎርክ ጥበቃን ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡
5. አጠራጣሪና የማይታወቁ ኢሜሎችን አለመክፈት
ብዙዎቹ የሳይበር ጥቃት ወንጀሎች የሚፈፀሙት የማይታወቁ ኢሜሎች በተጠቃሚዎች ሲከፈት እና መልስ (reply) ሲላክባቸው ነው፡፡ ብዙዎቹ የኢሜል ዓባሪዎች (attachments) የተለያየ ይዘት ያላቸው ቫይረሶች እና Trojan horses ይሰራጭባቸዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ታዲያ እንደዚህ አይነት ኢሜሎችበአላስፈላጊ ማህደሮች (junk folders) ውስጥ የሚከማቹ ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ ግን በኢሜል ኢንቦክስ (inbox) ውስጥ ሊታዩ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ማናቸውንም አጠራጣሪ እና ማን እንደላካቸው የማይታወቁ ኢሜሎችን በቀጥታ ከመክፈት መቆጠብ ከመሰል አደጋ ራስን ያድናል፡፡
ምንጭ፡ HACK READ
*****************************************
*****************
እንግዲያውስ እንዚህን 5 ነጥቦች በሚገባ ይመልከቷቸው
በየትኛውም ሁኔታ ስራዎ ከኢንተርኔት ጋር ተያያዥነት ካለው እንደ ድረገፅ፣ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት እንዲሁም እንደ የኢሜል አድራሻ ያሉ የዲጂታል ሃብቶች ለስራዎ የጀርባ አጥንት መሆናቸው አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም እነዚህን የዲጂታል መሳሪያዎች በሚጠቀሙበት ወቅት መረጃዎ ከርሶዎ አልፎ ወደ ሌላ ሶስተኛ ወገን ወይም ሌሎች የመረጃ መንታፊዎች ጋር እንዳይደርስ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል፡፡
አንደሚታወቀው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ በኢንተርኔት አጠቃቀም ዙሪያ ያሉ የደህንነት ስጋቶች ከመቼውም በላይ እየጨመሩ መምጣታቸው ብዙዎችን የሚያስማማ ሃቅ ነው፡፡ በየቀኑ ከፍተኛ ጥፋት የሚያደርሱ እና በተለያዩ የሳይበር ወንጀሎች የሚሳተፉ አካለት እጅግ በረቀቁ ስልቶችና በአዳዲስ ቴክኒኮች በመታገዝ ትልቅ የሚባሉ ኮርፖሬተሮችን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት ድረገፆችን በመበርበርና ጥቃት በማድረስ ላይ ይገኛሉ፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ እንዚህ ትልልቅ የቢዝነስ ተቋማት ከመሰል የሳይበር ጥቃት የማያመልጡና እንደዚህ አይነት ስጋት የተጋረጠባቸው ከሆነ በመካከለኛ እና በትንንሽ የኦንላይን ቢዝነስ የተሰማሩ አካለት እጅጉን የሰፋ የደህንነት ስጋት እንደሚኖርባቸው የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ በመሆኑም ከኢንተርኔት ጋር ተያያዥነት ያለው ቢዝነስ የሚያካሂዱ ሰዎች እንዚህን አምስት ነጥቦች በሚገባ ቢያያዋቸው ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
1. አውቶማቲክ ማሻሻያዎች (Automated Updates)
አብዛኛውን ጊዜ የኦላይን ቢዝነስ የሚያካሂዱ ሰዎች የሚዘነጉት ጉዳይ ቢኖር ሲስተምን ያለማሻሻል ወይም system updates ያለማድረግ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም በቀላሉ ሃከሮች ሲስተሙን እንዲያውቁትና የሚፈልጉትን ጥቃትም በቀላሉ እንዲፈፅሙ ያግዛቸዋል፡፡ በመሆኑም ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸውን እያንዳንዳቸውን ሴስተሞች ማለትም ኦፕሬቴንግ ሲስተምን (operating systems) ጨምሮ ሌሎች የአፕሊኬሽን ሴስተሞችን እና የድረገፅ ፕለጊኖችን (website plugins) በሚገባ እንዲሻሻሉ ማድረግ ያለባቸውን ሳንካ (bugs) እንዲያስወግዱና የዲጂታል ሃብቱም በሚገባ እንዲጠበቅ ይረዳል፡፡
2. ባለብዙ-ንብርብር ደህንነት (Multi-Layer Security)
የድረገፅ መቆጣጠሪያ ፓኔልን ለማግኘት መሞከር እና በቁጥጥር ውስጥ እንዲሆን ማድረግ ብዞዎቹ የሳይበር ጥቃት አድራሾች የሚተገብሩትና የሚጠቀሙበት መንገድ ነው፡፡ ስለሆነም የኦላይን ቢዝነስ የሚያካሂዱ ሰዎች በድረገፃቸው ላይ የሚያደርጉት ቁጥጥር እንድ ጊዜ ከእጃቸው ወቶ በሃከሮች ቁጥጥር ውስጥ ከገባ መልሶ ለማግኘት እጅግ አዳጋች በመሆኑ አጠቃላይ ቢዝነሳቸው ለአደጋ ይጋለጣል፡፡ ስለዚህም ከምንም በላይ የድረገፅ አጠቃቀም ቁጥጥርን ወይም (access control)ን ማጥበቅ እጅግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ታዲያ ባለብዙ-ንብርብር ደህንነት ማከል እና የሚጠቀሙትን የይለፍ ቃል አይነት በማርዘምና እጅግ በተወሳሰቡ የቁጥርና የፊደላት ጥርቅም በማስገባት ለግምት እንዲከብድ ማድረግ፤ የደህንነት ስጋቱን በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሰዋል፡፡
3. የአንቲቫይረስ ፕሮግራሞች (Antivirus Programs)
ዘላቂነት ባለው ሁኔታ ኮምፒውተሮን ከተለያዩ አጥፊ መተግበሪያዎች (malwares) እና አላስፈላጊ የሆኑ መልእክቶችን ለብዙዎች የማላክ ሁኔታ (spam) በመጠበቅ የኦንላይን ቢዝነሶ ከየትኛውም የሳይበር ጥቃት ራሱን እንዲከላከል ማድረግ የአንቲቫይረስ ፕሮግራሞች ከሚሰጧቸው ጥቅሞች ውስጥ ቀዳሚው ነው፡፡ በመሆኑም እነዚህን ፕሮግራሞች በሚጠቀሙበት ወቅት ከፍተኛ ትኩረት ለሚያስፈልጋቸው ብሮውዘሮች (browsers) እና መተግበሪዎች ቅድሚያ በመስጠት ኮምፒውተሮን ከማንኛውም ቫይረስ እንዲጠብቁ ያስፈልጋል፡፡
4. የኔትዎርክ ጥበቃ
አብዛኛውን ጊዜ የኢንተርኔት ግንኙነትን በጋራ ኔትወርክ ሲጠቀሙ የሚያስተዳድሩት መረጃ ኔትወርኩን በሚጋራ ሌላ ተጠቃሚ ሊገኝና ሊደረስበት ይችላል፡፡ በተለይም በግንኙነቱ ወቅት የጠነከረ የኢንክሪፕሽን ቴክኒክ የማይኖር ከሆነ መረጃው በማንኛውም ሁኔታ ለጥቃት የመጋለጥ እድሉ ሰፊ ነው፡፡ በዚህ ረገድ እንደ ፋየርዎል (Firewall) ያሉ የኔትዎርክ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎችን በመጠቀም በኔትዎርክ ትራፊኩ ላይ የሚገቡና የሚወጡ አካለትን መቆጣጠር ይቻላል፡፡ በመሆኑም በኮንትሮል ፓኔል (Control Panel) ላይ የፋየርዎል ገፅታን በማከል የኔትዎርክ ጥበቃን ማጎልበት ያስፈልጋል፡፡
5. አጠራጣሪና የማይታወቁ ኢሜሎችን አለመክፈት
ብዙዎቹ የሳይበር ጥቃት ወንጀሎች የሚፈፀሙት የማይታወቁ ኢሜሎች በተጠቃሚዎች ሲከፈት እና መልስ (reply) ሲላክባቸው ነው፡፡ ብዙዎቹ የኢሜል ዓባሪዎች (attachments) የተለያየ ይዘት ያላቸው ቫይረሶች እና Trojan horses ይሰራጭባቸዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ ታዲያ እንደዚህ አይነት ኢሜሎችበአላስፈላጊ ማህደሮች (junk folders) ውስጥ የሚከማቹ ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ ግን በኢሜል ኢንቦክስ (inbox) ውስጥ ሊታዩ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ማናቸውንም አጠራጣሪ እና ማን እንደላካቸው የማይታወቁ ኢሜሎችን በቀጥታ ከመክፈት መቆጠብ ከመሰል አደጋ ራስን ያድናል፡፡
ምንጭ፡ HACK READ