አዲሱ የኮቪድ-19 አይነት እና ስጋቶቹ
*********************
ከሳምንት በፊት የብሪታንያ ባለስልጣናት ከሌሎቹ በ70 በመቶ በበለጠ መሰራጨት የሚችል አዲስ አይነት ሳርስ-ኮቭ-2 (ኮቪድ 19ኝ በሽታን የሚያመጣው ቫይረስ) መታየቱን የሚያሳይ መረጃ መውጣቱን ተከትሎ በለንደን እና ደቡባዊ አንግሊዝ አካባቢ ነዋሪዎች ከቤት እንዳይወጡ ክልከላን አስተላልፈው ነበር፡፡ በአሁኑ ሰዓት አዲሱ የቫይረሱ አይነት ቀድሞ የነበሩትን በሚያሰጋ ፍጥነት እየተካና ቀዳሚ እሆነ መምጣቱን ተከትሎ እስራኤል፣ ካናዳ፣ ቻይና እና ህንድን ጨምሮ ከ40 በላይ የዓለም ሀገራት ከወደ እንግሊዝ የሚነሳ በረራን አግደዋል፡፡
ይህን መሰል በቫይረሱ በራሒ ላይ በሚመጣ ለውጥ (Mutation) አማካኝነት አዲስ የቫይረሱ አይነት መከሰቱ ታድያ ብዙም አስገራሚ አይደለም፤ ተደጋግሞ የሚከሰት ነውና፡፡ ነገር ግን አዲሱ የቫይረሱ አይነት በፍጥነት ተሰራጭቶ ቀዳሚውን ስፍራ መያዙ ነው ለብዙዎች እራስ ምታት የሆነው፡፡ አዲሱ የቫይረስ ዓይነት ቅድሚያ የተገኘው ወርሀ መስከረም ላይ ነበር፡፡ ከሁለት ወራት በኋላ ግን በለንደን እንደ አዲስ ከሚያዙት ኮቪድ-19 ተጠቂዎች መካከል ሩብ ያህሉን፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ደግሞ የሁለት ሶስተኛውን ድርሻ ወስዷል፡፡
አዲሱ የቫይረሱ አይነት ቀድሞ ከነበረው ሲነፃፀር 17 ያህል የበራሒ ለውጦች ታይተውበታል፡፡ ከነኚህ ለውጦች መካከል ቫይረሱ ህዋሳችንን እንዲያጠቃ የሚያስችለው የፕሮቲን እሾሁ ይገኝበታል፡፡ እንደዚህ አይነት ለውጦች ታድያ ቫይረሱ ይበልጥ በፍጥነት እንዲስፋፋ የማድረግ እድል አላቸው፡፡ ለዓብነት ቫይረሱ ቅድሚያ በሰው ልጅ ህዋስ ላይ በሚያርፍበት ስፍራ (Receptor-Binding Domain) ላይ የሚኖረው ለውጥ ቫይረሱ ሕዋሶቹ ላይ በበለጠ መጣበቅ እንዲችል የማድረግ አቅም አለው፡፡
በተመሳሳይ 501.ቪ2 (501.V2) ተብሎ የሚጠራ ሌላ የቫይረሱ አይነት በደቡብ አፍሪካ የተገኘ ሲሆን ይህ በበኩሉ አዳዲስ ከሚያዙት ሰዎች መካከል የ80 እና 90 በመቶውን ድርሻ ይዟል፡፡ 501.ቪ2 ቫይረሱ በመጀመሪያው ማዕበል ሲሰራጭ ከነበረበትም በበለጠ ፍጥነት እተሰራጨ መሆኑን የደቡብ አፍሪካ የጤና ባሙያዎች እና ኃላፊዎች ተናግረዋል፡፡ በየቀኑ የሚያዘው ሰው መጠን ከሳምንታት በፊት ከነበረበት በሁለት እጥፍ ማደጉን ተከትሎ የሟቾች እና በሆስፒታል ቆይተው የሚታከሙ ሰዎችም ቀድሞ ከነበረበት ከፍተኛ ብልጫ እያሳየ ነው፡፡ የሀገሪቱ ተመራማሪዎች የኮቪድ-19 ክትባቶች አዲሱን የቫይረሱ አይነት መከላከል መቻላቸውን ለማረጋገጥ ሙከራዎችን እያደረጉ ሲሆን የእንቅስቃሴ እቀባዎችም ተላልፈዋል፡፡
ሆኖም እነዚህ ለውጦች አሁን እየተሰራጩ ያሉትን ክትባቶች ውጤታማ እንዳይሆኑ የማድረጋቸው እድል ቢያንስ ለአሁኑ ጠባብ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ለዚህ የሚሰጠው ምክንያት ቫይረሱ በአንድ በኩል ክትባቱን ማምለጥ ቢችል እንኳን በሌሎች ብዙ ጎኖቹ ግን ለክትባቱ እጅ ይሰጣል የሚለው ነው፡፡
ምንጭ፡ Associated Press፣ Live Science እና cnn
*********************
ከሳምንት በፊት የብሪታንያ ባለስልጣናት ከሌሎቹ በ70 በመቶ በበለጠ መሰራጨት የሚችል አዲስ አይነት ሳርስ-ኮቭ-2 (ኮቪድ 19ኝ በሽታን የሚያመጣው ቫይረስ) መታየቱን የሚያሳይ መረጃ መውጣቱን ተከትሎ በለንደን እና ደቡባዊ አንግሊዝ አካባቢ ነዋሪዎች ከቤት እንዳይወጡ ክልከላን አስተላልፈው ነበር፡፡ በአሁኑ ሰዓት አዲሱ የቫይረሱ አይነት ቀድሞ የነበሩትን በሚያሰጋ ፍጥነት እየተካና ቀዳሚ እሆነ መምጣቱን ተከትሎ እስራኤል፣ ካናዳ፣ ቻይና እና ህንድን ጨምሮ ከ40 በላይ የዓለም ሀገራት ከወደ እንግሊዝ የሚነሳ በረራን አግደዋል፡፡
ይህን መሰል በቫይረሱ በራሒ ላይ በሚመጣ ለውጥ (Mutation) አማካኝነት አዲስ የቫይረሱ አይነት መከሰቱ ታድያ ብዙም አስገራሚ አይደለም፤ ተደጋግሞ የሚከሰት ነውና፡፡ ነገር ግን አዲሱ የቫይረሱ አይነት በፍጥነት ተሰራጭቶ ቀዳሚውን ስፍራ መያዙ ነው ለብዙዎች እራስ ምታት የሆነው፡፡ አዲሱ የቫይረስ ዓይነት ቅድሚያ የተገኘው ወርሀ መስከረም ላይ ነበር፡፡ ከሁለት ወራት በኋላ ግን በለንደን እንደ አዲስ ከሚያዙት ኮቪድ-19 ተጠቂዎች መካከል ሩብ ያህሉን፤ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ደግሞ የሁለት ሶስተኛውን ድርሻ ወስዷል፡፡
አዲሱ የቫይረሱ አይነት ቀድሞ ከነበረው ሲነፃፀር 17 ያህል የበራሒ ለውጦች ታይተውበታል፡፡ ከነኚህ ለውጦች መካከል ቫይረሱ ህዋሳችንን እንዲያጠቃ የሚያስችለው የፕሮቲን እሾሁ ይገኝበታል፡፡ እንደዚህ አይነት ለውጦች ታድያ ቫይረሱ ይበልጥ በፍጥነት እንዲስፋፋ የማድረግ እድል አላቸው፡፡ ለዓብነት ቫይረሱ ቅድሚያ በሰው ልጅ ህዋስ ላይ በሚያርፍበት ስፍራ (Receptor-Binding Domain) ላይ የሚኖረው ለውጥ ቫይረሱ ሕዋሶቹ ላይ በበለጠ መጣበቅ እንዲችል የማድረግ አቅም አለው፡፡
በተመሳሳይ 501.ቪ2 (501.V2) ተብሎ የሚጠራ ሌላ የቫይረሱ አይነት በደቡብ አፍሪካ የተገኘ ሲሆን ይህ በበኩሉ አዳዲስ ከሚያዙት ሰዎች መካከል የ80 እና 90 በመቶውን ድርሻ ይዟል፡፡ 501.ቪ2 ቫይረሱ በመጀመሪያው ማዕበል ሲሰራጭ ከነበረበትም በበለጠ ፍጥነት እተሰራጨ መሆኑን የደቡብ አፍሪካ የጤና ባሙያዎች እና ኃላፊዎች ተናግረዋል፡፡ በየቀኑ የሚያዘው ሰው መጠን ከሳምንታት በፊት ከነበረበት በሁለት እጥፍ ማደጉን ተከትሎ የሟቾች እና በሆስፒታል ቆይተው የሚታከሙ ሰዎችም ቀድሞ ከነበረበት ከፍተኛ ብልጫ እያሳየ ነው፡፡ የሀገሪቱ ተመራማሪዎች የኮቪድ-19 ክትባቶች አዲሱን የቫይረሱ አይነት መከላከል መቻላቸውን ለማረጋገጥ ሙከራዎችን እያደረጉ ሲሆን የእንቅስቃሴ እቀባዎችም ተላልፈዋል፡፡
ሆኖም እነዚህ ለውጦች አሁን እየተሰራጩ ያሉትን ክትባቶች ውጤታማ እንዳይሆኑ የማድረጋቸው እድል ቢያንስ ለአሁኑ ጠባብ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ለዚህ የሚሰጠው ምክንያት ቫይረሱ በአንድ በኩል ክትባቱን ማምለጥ ቢችል እንኳን በሌሎች ብዙ ጎኖቹ ግን ለክትባቱ እጅ ይሰጣል የሚለው ነው፡፡
ምንጭ፡ Associated Press፣ Live Science እና cnn
"የኮሪያ አርቲፍሻል ፀሐይ" አዲስ ክብረ-ወሰን
******************************
የኮሪያ ሰው ሰራሽ ፀሐይ ለ20 ሴኮንዶች ያክል መቆየት የቻለ የ100 ሚሊዮን ዲግሪ ሙቀት በመያዝ የአለማችን አዲስ ክብረ-ወሰን አስመዝግቧል፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኝ አንድ የዘርፉ የምርምር ተቋም (KSTAR) የተሰራው ይህ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መቶ ሚሊዮን ዲግሪ ሴልሺየስ የደረሰ ከፍተኛ ሙቀት በመያዝ ለተመራማሪዎቹ ትልቅ ስኬትን አስገኝቷል፡፡
የምርምር ተቋሙ ከሴኡል ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲና ከአሜሪካው ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሰራው ይህ ምርምር ለተከታታይ 20 ሴኮንዶች ያክል የቆየ ሲሆን በኒውክሌር ፊውዥን ዙሪያ ለሚሰሩት ጥናት ምቹ ሁኔታ እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡ በ2019 በተደረገ ሙከራ የቆይታ ጊዜው ለ8 ሴኮንዶች ያክል ብቻ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የአሁኑ ሁለት እጥፍ ስኬትን ያስገኘ ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ አርቲፍሻል ፀሐይ ሲሉ የሰየሙት ከፍተኛ አስተላላፊ ቁስ የሀይድሮጅን አይሶቶፖችን የያዘ ሲሆን ይህ አዮኖችና ኤሌክትሮኖች የሚለያዩበትን የፕላዝማ ኩነት (state) እንዲፈጠር የሚያደርግ ነው፡፡ አዮኖቹ ከፍተኛ መጠን ባለው ሙቀት እንዲግሉ ይደረጋል፡፡
ምንም እንኳን ከ100 ሚሊዮን በላይ ከፍ ያለ ሙቀትን መያዝ የሚችሉ ሌሎች የፊውዥን ቁሶች ቢኖሩም እስካሁን ከ10 ሴኮንዶች በላይ ሙቀቱን ተቋቁመው መቆየት የቻሉ ግን አልነበሩም፡፡ ይህኛው ሙካራ ሊሳካ የቻለውም የምርምር ተቋሙ የውስጣዊ ግድግዳውን አቅም በማሻሻሉ ሲሆን ለዚህ ያበቃውም ባለፈው አመት የተሰራው ከፍተኛ ሙቀትን መቋቋም የሚችል ቁስ (plasma operation mode) መጠቀሙ ነው፡፡
እንደ ተመራማሪዎች ገለጻ ከሆነ የዚህ ምርምር ዋና አላማ እንከ 2025 ድረስ ከመቶ ሚሊዮን ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሙቀትን ለ300 ሴኮንዶች ያክል ማቆየት መቻል ነው፡፡ ፈጠራው ከፍተኛ ሙቀት መቋቋም የሚችል ቁስ በማግኘት የወደፊቱን የኒዩክሌር ማበልጸጊያ መሳሪያ ለማግኘት ያለመ ነው፡፡ መረጃውን ከPHYS.ORG አግኝተነዋል፡፡
******************************
የኮሪያ ሰው ሰራሽ ፀሐይ ለ20 ሴኮንዶች ያክል መቆየት የቻለ የ100 ሚሊዮን ዲግሪ ሙቀት በመያዝ የአለማችን አዲስ ክብረ-ወሰን አስመዝግቧል፡፡ በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኝ አንድ የዘርፉ የምርምር ተቋም (KSTAR) የተሰራው ይህ ሰው ሰራሽ ፀሐይ መቶ ሚሊዮን ዲግሪ ሴልሺየስ የደረሰ ከፍተኛ ሙቀት በመያዝ ለተመራማሪዎቹ ትልቅ ስኬትን አስገኝቷል፡፡
የምርምር ተቋሙ ከሴኡል ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲና ከአሜሪካው ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሰራው ይህ ምርምር ለተከታታይ 20 ሴኮንዶች ያክል የቆየ ሲሆን በኒውክሌር ፊውዥን ዙሪያ ለሚሰሩት ጥናት ምቹ ሁኔታ እንደሆነ ተነግሮለታል፡፡ በ2019 በተደረገ ሙከራ የቆይታ ጊዜው ለ8 ሴኮንዶች ያክል ብቻ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የአሁኑ ሁለት እጥፍ ስኬትን ያስገኘ ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ አርቲፍሻል ፀሐይ ሲሉ የሰየሙት ከፍተኛ አስተላላፊ ቁስ የሀይድሮጅን አይሶቶፖችን የያዘ ሲሆን ይህ አዮኖችና ኤሌክትሮኖች የሚለያዩበትን የፕላዝማ ኩነት (state) እንዲፈጠር የሚያደርግ ነው፡፡ አዮኖቹ ከፍተኛ መጠን ባለው ሙቀት እንዲግሉ ይደረጋል፡፡
ምንም እንኳን ከ100 ሚሊዮን በላይ ከፍ ያለ ሙቀትን መያዝ የሚችሉ ሌሎች የፊውዥን ቁሶች ቢኖሩም እስካሁን ከ10 ሴኮንዶች በላይ ሙቀቱን ተቋቁመው መቆየት የቻሉ ግን አልነበሩም፡፡ ይህኛው ሙካራ ሊሳካ የቻለውም የምርምር ተቋሙ የውስጣዊ ግድግዳውን አቅም በማሻሻሉ ሲሆን ለዚህ ያበቃውም ባለፈው አመት የተሰራው ከፍተኛ ሙቀትን መቋቋም የሚችል ቁስ (plasma operation mode) መጠቀሙ ነው፡፡
እንደ ተመራማሪዎች ገለጻ ከሆነ የዚህ ምርምር ዋና አላማ እንከ 2025 ድረስ ከመቶ ሚሊዮን ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሙቀትን ለ300 ሴኮንዶች ያክል ማቆየት መቻል ነው፡፡ ፈጠራው ከፍተኛ ሙቀት መቋቋም የሚችል ቁስ በማግኘት የወደፊቱን የኒዩክሌር ማበልጸጊያ መሳሪያ ለማግኘት ያለመ ነው፡፡ መረጃውን ከPHYS.ORG አግኝተነዋል፡፡
ቴክኖፖሊ
****
ቃሉ በዲጂታል አገልግሎቶች ላይ የጠቅላይነት ወይም ሞኖፖሊስቲክ ቁጥጥር ያላቸውን ግዙፎቹ ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ስብስብን የሚያመላክት ነው፡፡ 2020 የቴክኖሎጂ ዓለም ገበያ ላይ ያለው ድርሻ ባልተቋጨ የከፍታ ሂደት ውስጥ የቆበት ነበር፡፡ በእንደ ፌስቡክ፣ ግዙፎቹ ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የአሜሪካንን የአክሲዮን ገበያ ተቆጣጥረውት አሳልፈዋል፡፡ ይህ በተለይም ዓለማችን ያጋጠማት የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ተከትሎ ብዙ ነገሮች ወደ ዲጂታል መለወጣቸውን እና በመንግስታት የተወሰዱ የምጣኔ ሐብቱን የማረጋጋት እርምጃዎች (Monetary And Fiscal Stimulus) ዘርፉን በፍጥነት እንዲያድግ እና ተቋማቱ ለአክሲዮን ገበያ ሲቀርቡም የሚገዙበት የገንዘብ መጠን እ.አ.አ 1990ዎቹ መባቻ ላይ ከነበረውና ዶትኮም ቦም ወይም ዶትኮም በብል ተብሎ ከሚጠራው የበይነ-መረብ ተቋማት ዋጋ የናረበት ጊዜ በኋላ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ከፍ ያለበት ነበር፡፡
የነዚህ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋማት ዋጋ ማሻቀብን አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ ዕድገቱ እየተመዘገበ ያለው በዓለም ዙርያ ባሉ መንግስታዊ ተቆጣጣሪዎች ዓይነ ቁራኛ ክትትል ውስጥ በወደቁበት ሰዓት መሆኑ ነው፡፡ በአሜሪካን እንኳን ብናይ የሀገሪቱ ፍትህ ቢሮ እንዲሁም የፌደራሉ ንግድ ኮሚሽን በጉግል እና ፌስቡክ ላይ የክስ ጅራፍ አንስተውባቸዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረትም ሆነ እንግሊዝ በቅርቡ እነዚህን ተቋማት የሚቆጣጠር ጠንካራ ሕግ ወደፊት ሲያመጡ ቻይናም እንደ አሊባባ ያሉ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቿ ላይ ጥርስ መንከስ ጀምራለች፡፡
ሆኖም ይህ ሁሉ ጫና ባለበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እንኳን ዘርፉ እድገቱን እንደቀጠለ ነው፡፡ የኮቪድ-19 ወረርሺኝ እና ተከትሎት የሚፈጠረው ሁኔታ ስራዎች ከቢሮ ርቀው እንዲሰሩ እና ተቋማትም እንደ ሶፍትዌር፣ ፓተንት፣ የጥሬ ሀቅ ወይም ዳታ ትንተና እና ሌሎችም የአዕምሮ ንብረት አይነቶች ላይ ሀብታቸውን ማፍሰሳቸው እየጨመሩ መሆኑን ተከትሎ ሰው ልጆችን ሕይወት ቀድሞ ከነበረበትም በላይ ወደፊት ይበልጥ ዲጂታል እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡ ይህ ለእነዚህ ግዙፍ ተቋማት መልካም ዜናን ይዞ ቢመጣም እነዚህ የማይዳሰሱ ሀብቶች ላይ የሚደረገው የመዋለ ነዋይ ፈሰስ ግን ከስራ አጥነት ያልተላቀቀ ምጣኔ ሀብት መነቃቃት ጋራ በመያያዙ ለተቀጣሪ ሰራተኛው ቢያንስ ለአሁኑ ነገሮችን ጥሩ የሚያደርገው አይመስልም፡፡ ይህ ዘርፉ አሁንም በሀገራት ምጣኔ ሀብት ላይ ያለውን ቴክኖፖሊ በቀጣዮቹ ወራትና አመታት ውስጥ አስቀጥሎ ይዘልቃል ማለት ነው፡፡
ምንጭ፡ Financial Times
****
ቃሉ በዲጂታል አገልግሎቶች ላይ የጠቅላይነት ወይም ሞኖፖሊስቲክ ቁጥጥር ያላቸውን ግዙፎቹ ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ስብስብን የሚያመላክት ነው፡፡ 2020 የቴክኖሎጂ ዓለም ገበያ ላይ ያለው ድርሻ ባልተቋጨ የከፍታ ሂደት ውስጥ የቆበት ነበር፡፡ በእንደ ፌስቡክ፣ ግዙፎቹ ቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የአሜሪካንን የአክሲዮን ገበያ ተቆጣጥረውት አሳልፈዋል፡፡ ይህ በተለይም ዓለማችን ያጋጠማት የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ተከትሎ ብዙ ነገሮች ወደ ዲጂታል መለወጣቸውን እና በመንግስታት የተወሰዱ የምጣኔ ሐብቱን የማረጋጋት እርምጃዎች (Monetary And Fiscal Stimulus) ዘርፉን በፍጥነት እንዲያድግ እና ተቋማቱ ለአክሲዮን ገበያ ሲቀርቡም የሚገዙበት የገንዘብ መጠን እ.አ.አ 1990ዎቹ መባቻ ላይ ከነበረውና ዶትኮም ቦም ወይም ዶትኮም በብል ተብሎ ከሚጠራው የበይነ-መረብ ተቋማት ዋጋ የናረበት ጊዜ በኋላ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ከፍ ያለበት ነበር፡፡
የነዚህ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ተቋማት ዋጋ ማሻቀብን አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ ዕድገቱ እየተመዘገበ ያለው በዓለም ዙርያ ባሉ መንግስታዊ ተቆጣጣሪዎች ዓይነ ቁራኛ ክትትል ውስጥ በወደቁበት ሰዓት መሆኑ ነው፡፡ በአሜሪካን እንኳን ብናይ የሀገሪቱ ፍትህ ቢሮ እንዲሁም የፌደራሉ ንግድ ኮሚሽን በጉግል እና ፌስቡክ ላይ የክስ ጅራፍ አንስተውባቸዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረትም ሆነ እንግሊዝ በቅርቡ እነዚህን ተቋማት የሚቆጣጠር ጠንካራ ሕግ ወደፊት ሲያመጡ ቻይናም እንደ አሊባባ ያሉ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቿ ላይ ጥርስ መንከስ ጀምራለች፡፡
ሆኖም ይህ ሁሉ ጫና ባለበት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እንኳን ዘርፉ እድገቱን እንደቀጠለ ነው፡፡ የኮቪድ-19 ወረርሺኝ እና ተከትሎት የሚፈጠረው ሁኔታ ስራዎች ከቢሮ ርቀው እንዲሰሩ እና ተቋማትም እንደ ሶፍትዌር፣ ፓተንት፣ የጥሬ ሀቅ ወይም ዳታ ትንተና እና ሌሎችም የአዕምሮ ንብረት አይነቶች ላይ ሀብታቸውን ማፍሰሳቸው እየጨመሩ መሆኑን ተከትሎ ሰው ልጆችን ሕይወት ቀድሞ ከነበረበትም በላይ ወደፊት ይበልጥ ዲጂታል እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡ ይህ ለእነዚህ ግዙፍ ተቋማት መልካም ዜናን ይዞ ቢመጣም እነዚህ የማይዳሰሱ ሀብቶች ላይ የሚደረገው የመዋለ ነዋይ ፈሰስ ግን ከስራ አጥነት ያልተላቀቀ ምጣኔ ሀብት መነቃቃት ጋራ በመያያዙ ለተቀጣሪ ሰራተኛው ቢያንስ ለአሁኑ ነገሮችን ጥሩ የሚያደርገው አይመስልም፡፡ ይህ ዘርፉ አሁንም በሀገራት ምጣኔ ሀብት ላይ ያለውን ቴክኖፖሊ በቀጣዮቹ ወራትና አመታት ውስጥ አስቀጥሎ ይዘልቃል ማለት ነው፡፡
ምንጭ፡ Financial Times
ለካንሰር ህሙማን ተስፋ ሰጭ መድሀኒት
**************************
የካንሰር ሴሎችን እንዲዳብሩ እና እንዲስፋፉ የሚያደርገውን ክፍል በማጥቃት የህመሙን መስፋፋት መቀነስ የሚያስችል መድሀኒት መሰራቱ ተሰማ፡፡ መድሀኒቱ የካንሰር ሴሎችን እንዲዳከሙ የሚያደርገው የሀይል ምንጭ የሚሆናቸውን ማይቶኮነዶሪያ የተባለውን ክፍል በማጥቃት ነው፡፡ በስቶኮልም የሚገኝ አንድ የምርምር ተቋምና የጉተምበርግ ዩኒቨርሲቲ በሰሩት ምርምር መድሀኒቱን ለወደፊቱ የካንሰር ህሙማንን ለማከም ተስፋ ሰጭ ምልቶች መኖራቸውን ይፋ አድገዋል፡፡
ማይቶኮንዶሪያ ለህዋሳት ግንባታ የሚሆን ሀይልና የህዋሳት ክፍሎችን ለማዳበር የሚያገለግል ክፍል ነው፡፡ ለብዙ ጊዜያት ያክል የካንሰር ህዋስ እድገት ከማይቶኮንዶሪያ ተግባር ጋር የማይገናኝ ተደርጎ የሚታሰብ የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የሚወጡ መረጃዎች ግን እሳቤው ስህተት መሆኑን እያረጋገጡ ናቸው፡፡ በተለይም ለካንሰር ህመም ዋና የሚባሉ ህዋሳት ከማይቶኮንዶሪያ ተግባር ጋር ጥገኞች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ማይቶኮንዶሪያ ለመደበኛ የሰውነት ህዋሳት ባለው ጥቅም ምክንያት እሱን ለማጥቃት የሚሰጡ መድሀኒቶች ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትሉ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ካንሰርን ለማከም ማይቶኮንዶሪያን ማጥቃት አስቸጋሪ መሆኑ ታውቋል፡፡
ይህ የአሁኑ ምርምር ከላይ የተገለጸውን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ውጤት ይዞ እንደመጣ የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡ የምርምሩን ውጤት ካሳወቁት መካከል አንዷ የሆኑት ኒና ቦኔካምፕ በምርምሩ የከፋ ጉዳት የማያደርስና ጤነኛ ህዋሳትን የማያጠቃ መድሀኒት መሰራቱን በጽሁፋቸው አመልክተዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
**************************
የካንሰር ሴሎችን እንዲዳብሩ እና እንዲስፋፉ የሚያደርገውን ክፍል በማጥቃት የህመሙን መስፋፋት መቀነስ የሚያስችል መድሀኒት መሰራቱ ተሰማ፡፡ መድሀኒቱ የካንሰር ሴሎችን እንዲዳከሙ የሚያደርገው የሀይል ምንጭ የሚሆናቸውን ማይቶኮነዶሪያ የተባለውን ክፍል በማጥቃት ነው፡፡ በስቶኮልም የሚገኝ አንድ የምርምር ተቋምና የጉተምበርግ ዩኒቨርሲቲ በሰሩት ምርምር መድሀኒቱን ለወደፊቱ የካንሰር ህሙማንን ለማከም ተስፋ ሰጭ ምልቶች መኖራቸውን ይፋ አድገዋል፡፡
ማይቶኮንዶሪያ ለህዋሳት ግንባታ የሚሆን ሀይልና የህዋሳት ክፍሎችን ለማዳበር የሚያገለግል ክፍል ነው፡፡ ለብዙ ጊዜያት ያክል የካንሰር ህዋስ እድገት ከማይቶኮንዶሪያ ተግባር ጋር የማይገናኝ ተደርጎ የሚታሰብ የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የሚወጡ መረጃዎች ግን እሳቤው ስህተት መሆኑን እያረጋገጡ ናቸው፡፡ በተለይም ለካንሰር ህመም ዋና የሚባሉ ህዋሳት ከማይቶኮንዶሪያ ተግባር ጋር ጥገኞች ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ማይቶኮንዶሪያ ለመደበኛ የሰውነት ህዋሳት ባለው ጥቅም ምክንያት እሱን ለማጥቃት የሚሰጡ መድሀኒቶች ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትሉ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ካንሰርን ለማከም ማይቶኮንዶሪያን ማጥቃት አስቸጋሪ መሆኑ ታውቋል፡፡
ይህ የአሁኑ ምርምር ከላይ የተገለጸውን ችግር ለመቅረፍ የሚያስችል ውጤት ይዞ እንደመጣ የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡ የምርምሩን ውጤት ካሳወቁት መካከል አንዷ የሆኑት ኒና ቦኔካምፕ በምርምሩ የከፋ ጉዳት የማያደርስና ጤነኛ ህዋሳትን የማያጠቃ መድሀኒት መሰራቱን በጽሁፋቸው አመልክተዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
ሁለቱ የምርምር ተቋማት በጋራ ለመስራት ከስምምነት ደረሱ
=====================
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋራ በተቋማዊ የመረጃ አያያዝ ሲስተም ዝርጋታ፣ ዲታ-ቤዝ ወይም በመረጃ አያያዝ ስርአት ግንባታ ብሎም በፖሊሲ ትንተና እና ምርምር ዘዴን ጨምሮ በ12 አባይት ጉዳዮች ላይ በጋራ እንዲሰሩ የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከ6 እስከ 7 ቢሊዮን ዶላር በሚደርስ ወጪ ወረዳ ድረስ የዘለቀ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ብታከናውንም ስራ ላይ አለመዋሉን ያወሱት የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሁለቱ ተቋማትም ኢንፎርሜሽን እና ኮምዩኒኬሽን ላይ ማዕከል አድርገው በሰው ኃይል ማብቃት ላይ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በጥቂት ወራት ውስጥ የትግበራ እቅድ ተዘጋጅቶ በቀጥታ ወደ ስራ መገባት እናዳለበት የተናገሩት ዶ/ር መኩሪያ ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞም የበኩላችንን ጥረት እንደምናደርግ ተስፋ አለኝ ብለዋል፡፡
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከእኛ ጋር ለመስራት በመፍቀዱ ደስተኛ ነን ያሉት የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ ተቋማቸውን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማብራርያ የሰጡ ሲሆን ወደፊትም በጋራ የተሰሩ ስራዎችን ይዘው ተለቅ ባለ መድረክ እንደሚገናኙ ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የተፈረመው ይህ ስምምነት ለሦስት ዓመታት እንዲቆይ የታቀደለት ሲሆን አተገባበሩም በሁለቱ ተቋማት ዋና ዳይሬክተሮች የሚመራ ዓብይ ኮሚቴ አማካኝነት ክትትል ሚደረግበት ይሆናል፡፡
=====================
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ጋራ በተቋማዊ የመረጃ አያያዝ ሲስተም ዝርጋታ፣ ዲታ-ቤዝ ወይም በመረጃ አያያዝ ስርአት ግንባታ ብሎም በፖሊሲ ትንተና እና ምርምር ዘዴን ጨምሮ በ12 አባይት ጉዳዮች ላይ በጋራ እንዲሰሩ የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከ6 እስከ 7 ቢሊዮን ዶላር በሚደርስ ወጪ ወረዳ ድረስ የዘለቀ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ ብታከናውንም ስራ ላይ አለመዋሉን ያወሱት የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ሁለቱ ተቋማትም ኢንፎርሜሽን እና ኮምዩኒኬሽን ላይ ማዕከል አድርገው በሰው ኃይል ማብቃት ላይ ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ በጥቂት ወራት ውስጥ የትግበራ እቅድ ተዘጋጅቶ በቀጥታ ወደ ስራ መገባት እናዳለበት የተናገሩት ዶ/ር መኩሪያ ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞም የበኩላችንን ጥረት እንደምናደርግ ተስፋ አለኝ ብለዋል፡፡
የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከእኛ ጋር ለመስራት በመፍቀዱ ደስተኛ ነን ያሉት የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ ተቋማቸውን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ማብራርያ የሰጡ ሲሆን ወደፊትም በጋራ የተሰሩ ስራዎችን ይዘው ተለቅ ባለ መድረክ እንደሚገናኙ ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የተፈረመው ይህ ስምምነት ለሦስት ዓመታት እንዲቆይ የታቀደለት ሲሆን አተገባበሩም በሁለቱ ተቋማት ዋና ዳይሬክተሮች የሚመራ ዓብይ ኮሚቴ አማካኝነት ክትትል ሚደረግበት ይሆናል፡፡
በጀርመኑ ናዚ ተወስዶ የነበረው የፖላንድ ቤተ-ክርስቲያን ጥንታዊ ደወል
***********************************
1555 ዓመታትን ያስቆጠረው የፖላንድ ቤተ-ክርስቲያን ጥንታዊ ደወል በጀርመኖች በሁለተኛው የአለም ጦርነት ከተወሰደ ከ77 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ተወሰነ፡፡ የቤተ-ክርስቲያኗ ተከታዮች የደወሉን ፍለጋ ከሁለት አመታት በፊት የጀመሩት ሲሆን ደወሉ በመገኘቱ እጅግ እድለኞች ሆነዋል፡፡ ምክያቱም በወቅቱ ናዚ ከ80 ሺህ በላይ ደወሎችን ለመሳሪያ ማምረቻ ግብኣትነት በእሳት እንዳቀለጠ መታወቁ ነው፡፡
ከጦርነቱ በኋላ በብረት ይዞታቸው ምክንያት ያልቀለጡ ደወሎች ወደ ተዘረፉበት ቦታ የመመለስ እድል ቢገጥማቸውም ይህ 400 ኪሎ የሚመዝን ደወል ግን ከሌሎች 1300 ከሚጠጉ ደወሎች ጋር በሀምቡርግ ተቀምጦ ነበር፡፡
አንድ ቅርስ ቅርስ ሊባል የሚችለው ታሪኩ ከቅርሱ ባለቤት ጋር አብሮ የሚነገር ሲሆን ነው፡፡ ለምሳሌ ጀርመናውያን ከላይ የተገለጸውን ደወል ቅርሳችን ነው ለማለት የሚያስችል ምንም አይነት መነሻ የላቸውም፡፡ የታሪካቸው አንድ አካል ሊያደርጉት ቢፈልጉ እንኳን የዘረፋ ታሪክ ምንም የሚያኮራ ነገር ስለሌለው ወደ ቦታው እንዲመለስ መወሰናቸው ትክክለኛ ውሳኔ ነው፡፡
በዚህ ረገድ የጥንታዊው የአክሱም ስልጣኔ መገለጫ የሆነውን የአክሱም ሀውልትን ማየት መልካም ነው፡፡ ወደ ኢጣሊያ በዘረፋ ሄዶ በሮም አደባባይ ተተክሎ የነበረው ይህ ሀውልት ከኢጣሊያ ስልጣኔ፣ ባህል፣ የኪነ ህንጻ ጥበብ ከሌላም ከየትኛውም አይነት ሁኔታ ጋር የማይስማማ በመሆኑ በወቅቱ በተደረገ ጥረት ሊመለስ ችሏል፡፡
ሌሎች በተለያዩ ጊዜያት በተለይ ወደ አውሮፓ ሀገራት በተለያዩ ሁኔታዎች የተወሰዱ የሀገራችን ቅርሶች እንዳሉ እሙን ነው፡፡ አንዳንዶቹ በሚደረጉ ጥቂት ጥረቶች እየተመለሱ ቢሆንም ለምሳሌ እንግሊዞች በየሙዚየሞቻቸው በድብቅም በግልጽም ያስቀመቷቸው ልዩ ልዩ የሀገራችን ቅርሶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡
ምንም እንኳን ሙዚየሞቹ እጅግ ዘመናዊ ቢሆኑም በውስጣቸው የራስ ያልሆነ ነገርን ሰብስቦ ሙዚየም አለኝ ማለት ፍትሀዊነቱ አጠራጣሪ ነው፡፡ ይህን እንደማሳያ እና የመረጃ ምንጫችን ለሆነው BBC እናንተም ቤት እሳት አለ ለማለት አቀረብነው እንጂ በብዙዎቹ የአውሮፓ ሀገራት የሚገኙ ቅርሶቻችን ስፍ ቁጥር የላቸውም፡፡
ምንጭ BBC
***********************************
1555 ዓመታትን ያስቆጠረው የፖላንድ ቤተ-ክርስቲያን ጥንታዊ ደወል በጀርመኖች በሁለተኛው የአለም ጦርነት ከተወሰደ ከ77 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገሩ እንዲመለስ ተወሰነ፡፡ የቤተ-ክርስቲያኗ ተከታዮች የደወሉን ፍለጋ ከሁለት አመታት በፊት የጀመሩት ሲሆን ደወሉ በመገኘቱ እጅግ እድለኞች ሆነዋል፡፡ ምክያቱም በወቅቱ ናዚ ከ80 ሺህ በላይ ደወሎችን ለመሳሪያ ማምረቻ ግብኣትነት በእሳት እንዳቀለጠ መታወቁ ነው፡፡
ከጦርነቱ በኋላ በብረት ይዞታቸው ምክንያት ያልቀለጡ ደወሎች ወደ ተዘረፉበት ቦታ የመመለስ እድል ቢገጥማቸውም ይህ 400 ኪሎ የሚመዝን ደወል ግን ከሌሎች 1300 ከሚጠጉ ደወሎች ጋር በሀምቡርግ ተቀምጦ ነበር፡፡
አንድ ቅርስ ቅርስ ሊባል የሚችለው ታሪኩ ከቅርሱ ባለቤት ጋር አብሮ የሚነገር ሲሆን ነው፡፡ ለምሳሌ ጀርመናውያን ከላይ የተገለጸውን ደወል ቅርሳችን ነው ለማለት የሚያስችል ምንም አይነት መነሻ የላቸውም፡፡ የታሪካቸው አንድ አካል ሊያደርጉት ቢፈልጉ እንኳን የዘረፋ ታሪክ ምንም የሚያኮራ ነገር ስለሌለው ወደ ቦታው እንዲመለስ መወሰናቸው ትክክለኛ ውሳኔ ነው፡፡
በዚህ ረገድ የጥንታዊው የአክሱም ስልጣኔ መገለጫ የሆነውን የአክሱም ሀውልትን ማየት መልካም ነው፡፡ ወደ ኢጣሊያ በዘረፋ ሄዶ በሮም አደባባይ ተተክሎ የነበረው ይህ ሀውልት ከኢጣሊያ ስልጣኔ፣ ባህል፣ የኪነ ህንጻ ጥበብ ከሌላም ከየትኛውም አይነት ሁኔታ ጋር የማይስማማ በመሆኑ በወቅቱ በተደረገ ጥረት ሊመለስ ችሏል፡፡
ሌሎች በተለያዩ ጊዜያት በተለይ ወደ አውሮፓ ሀገራት በተለያዩ ሁኔታዎች የተወሰዱ የሀገራችን ቅርሶች እንዳሉ እሙን ነው፡፡ አንዳንዶቹ በሚደረጉ ጥቂት ጥረቶች እየተመለሱ ቢሆንም ለምሳሌ እንግሊዞች በየሙዚየሞቻቸው በድብቅም በግልጽም ያስቀመቷቸው ልዩ ልዩ የሀገራችን ቅርሶች እንዳሉ ይታወቃል፡፡
ምንም እንኳን ሙዚየሞቹ እጅግ ዘመናዊ ቢሆኑም በውስጣቸው የራስ ያልሆነ ነገርን ሰብስቦ ሙዚየም አለኝ ማለት ፍትሀዊነቱ አጠራጣሪ ነው፡፡ ይህን እንደማሳያ እና የመረጃ ምንጫችን ለሆነው BBC እናንተም ቤት እሳት አለ ለማለት አቀረብነው እንጂ በብዙዎቹ የአውሮፓ ሀገራት የሚገኙ ቅርሶቻችን ስፍ ቁጥር የላቸውም፡፡
ምንጭ BBC
የእንጨት ሳተላይት ሊሰራ ነው?
********************
የጃፓኑ ሱሚቶሞ ፎረስተሪ ከኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ ጋራ በመሆን እንጨትን በሳተላይት ግንባታ ለመጠቀም የሚያስችል ሙከራ እንደሚያደርግ ይፋ አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ ላይ ባለሙያዎች የተለያዩ የእንጨት ዓይነቶችን ከባድ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ እንደሚፈትኑም ተነግሯል፡፡
አሁን ላይ ሳተላይቶች በዋናነት የሚገነቡት አስቸጋሪ የአየር ንብረት እና ከፍተኛ ጨረርን መቋቋም በሚችሉት አልሙኒየም፣ ኬቭላር እና ድብልቅ አልሙኒየሞች ነው፡፡ ጠንካራ ጎናቸው ታድያ በራሱ ጉዳትም አለው፤ አገልግሎታቸው ካበቃ በኋላ እንኳን ለረጀም ጊዜ በምህዋራቸው እየተንቀዋለሉ እንዲቆዩና የጠፈር ላይ ቆሻሻ ሆነው እንዲቀሩ ያደርጋቸዋልና፡፡ እንደ ዓለም የምጣኔ ሐብት ጉባኤ (World Economic Forum) ከሆነ በዚህ ሰዓት 6ሺህ ያህል ሳተላይቶች ምድራችንን እየዞሯት ቢሆንም ከእነርሱ ውስጥ አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ከ60 በመቶ አይበልጡም፡፡ እንደ ዘርፉ ተዋናዮች ትንበያ በቀጣዩ አስር ዓመት ውስጥ አንድ ሺህ አዳዲስ ሳተላይቶች በየዓመቱ ወደ ጠፈር እነዲመጠቁ ይደረጋል፡፡ አንድ ሳተላይት አገልግሎት ውስጥ የሚቆይበትን እድሜ ከግንዛቤ ስናስገባ ይህ ሁኔታ በሺዎች የሚቆጠሩ አገልግሎታቸውን ጨርሰው የሚዞሩ ስራ-ፈት ሳተላይቶችን በቅርቡ ይፈጥርልናል ማለት ይሆናል፡፡ ታድያ ሳተላይቶቹ በህዋ ላይ ሲንቀሳቀሱ በሰዓት በሺዎች ኪሎሜትሮች ፍጥነት እንደመጓዛቸው መጠን ሰውን የጫኑትም ሆነ ያልጫኑት ሳተላይቶችን አደጋ ውስጥ ሊከቷቸው ይችላል፡፡ አሁን ላይ የጠፈር ላይ ቆሻሻ ጠንከር ያለ ችግር እየሆነ መምጣቱ ብዙዎችን ያሳምናል፡፡ ነገሩን የከፋ በሚያደርግ መልኩ ለሳተላይቶች ግንባታ ጥቅም ላይ ሚውለው አልሙኒየም ሳተላይቱ ዳግም ወደ ምድር እንዲመለስ በሚደረግበት ጊዜ የመፈረካከስ ባህርይ ያለው መሆኑ ተደርሶበታል፡፡ ይህም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ጥቃቅን የአልሚኒየም ስባሪዎች ለረጅም ዓመታት ምድራችንን ከበው በጠፈር ላይ እንዲቆዩ በማድረግ ምናልባትም ከባቢ አየር ላይ ጭምር ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ችግሮች ተደማምረው ነው ጃፓናዊያን ተመራማሪዎቹ ባህላዊ ሳተላይት መስሪያ ቁሶችን በእንጨት ለመቀየር እንዲንቀሳቀሱ ያደረጋቸው፡፡
በእንጨት ላይ ተመስርቶ የሚሰራ ሳተላይት በዋናነት የሚሰጠው ጥቅም ወደ ምድር ሲመለስ ሙሉ ለሙሉ መቃጠል መቻሉ ነው፡፡ በተጨማሪነትም የሳተላይቱን ውጪያዊ ሽፋን በእንጨት መስራት ኤሌክትሮማግኔቲካዊ ሞገዶች በውስጡ ሰርገው እንዲያልፉ በማድረግ አንቴናዎች ሳተላይቱ ውስጥ በሚቀመጡ መሳርያዎች እንዲተኩ ያስችላል፤ ይህም ሳተላይቶቹ ንድፋቸውም ሆነ ወደ ጠፈር የሚመነጠቁበትን ሂደት ቀላል እንደሚያደርገው ይታመናል፡፡ ተመራማሪዎቹ ለስራው ተገቢ የሆነውን የእንጨት አይነት መርጠው ከባዱን የጠፈር ላይ ሁኔታ እንዲቋቋም ማድረግ ይችሉ እንደሆን የሚያረጋግጡ ሙከራዎችን ለመከወን አቅደዋል፡፡ እ.አ.አ በ2023 ምርቱን አዘጋጅተው ይፋ እንደሚያደርጉም ትንበያቸው ያሳያል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
********************
የጃፓኑ ሱሚቶሞ ፎረስተሪ ከኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ ጋራ በመሆን እንጨትን በሳተላይት ግንባታ ለመጠቀም የሚያስችል ሙከራ እንደሚያደርግ ይፋ አድርጓል፡፡ ፕሮጀክቱ ላይ ባለሙያዎች የተለያዩ የእንጨት ዓይነቶችን ከባድ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ እንደሚፈትኑም ተነግሯል፡፡
አሁን ላይ ሳተላይቶች በዋናነት የሚገነቡት አስቸጋሪ የአየር ንብረት እና ከፍተኛ ጨረርን መቋቋም በሚችሉት አልሙኒየም፣ ኬቭላር እና ድብልቅ አልሙኒየሞች ነው፡፡ ጠንካራ ጎናቸው ታድያ በራሱ ጉዳትም አለው፤ አገልግሎታቸው ካበቃ በኋላ እንኳን ለረጀም ጊዜ በምህዋራቸው እየተንቀዋለሉ እንዲቆዩና የጠፈር ላይ ቆሻሻ ሆነው እንዲቀሩ ያደርጋቸዋልና፡፡ እንደ ዓለም የምጣኔ ሐብት ጉባኤ (World Economic Forum) ከሆነ በዚህ ሰዓት 6ሺህ ያህል ሳተላይቶች ምድራችንን እየዞሯት ቢሆንም ከእነርሱ ውስጥ አገልግሎት እየሰጡ ያሉት ከ60 በመቶ አይበልጡም፡፡ እንደ ዘርፉ ተዋናዮች ትንበያ በቀጣዩ አስር ዓመት ውስጥ አንድ ሺህ አዳዲስ ሳተላይቶች በየዓመቱ ወደ ጠፈር እነዲመጠቁ ይደረጋል፡፡ አንድ ሳተላይት አገልግሎት ውስጥ የሚቆይበትን እድሜ ከግንዛቤ ስናስገባ ይህ ሁኔታ በሺዎች የሚቆጠሩ አገልግሎታቸውን ጨርሰው የሚዞሩ ስራ-ፈት ሳተላይቶችን በቅርቡ ይፈጥርልናል ማለት ይሆናል፡፡ ታድያ ሳተላይቶቹ በህዋ ላይ ሲንቀሳቀሱ በሰዓት በሺዎች ኪሎሜትሮች ፍጥነት እንደመጓዛቸው መጠን ሰውን የጫኑትም ሆነ ያልጫኑት ሳተላይቶችን አደጋ ውስጥ ሊከቷቸው ይችላል፡፡ አሁን ላይ የጠፈር ላይ ቆሻሻ ጠንከር ያለ ችግር እየሆነ መምጣቱ ብዙዎችን ያሳምናል፡፡ ነገሩን የከፋ በሚያደርግ መልኩ ለሳተላይቶች ግንባታ ጥቅም ላይ ሚውለው አልሙኒየም ሳተላይቱ ዳግም ወደ ምድር እንዲመለስ በሚደረግበት ጊዜ የመፈረካከስ ባህርይ ያለው መሆኑ ተደርሶበታል፡፡ ይህም በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ጥቃቅን የአልሚኒየም ስባሪዎች ለረጅም ዓመታት ምድራችንን ከበው በጠፈር ላይ እንዲቆዩ በማድረግ ምናልባትም ከባቢ አየር ላይ ጭምር ጉዳት ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ችግሮች ተደማምረው ነው ጃፓናዊያን ተመራማሪዎቹ ባህላዊ ሳተላይት መስሪያ ቁሶችን በእንጨት ለመቀየር እንዲንቀሳቀሱ ያደረጋቸው፡፡
በእንጨት ላይ ተመስርቶ የሚሰራ ሳተላይት በዋናነት የሚሰጠው ጥቅም ወደ ምድር ሲመለስ ሙሉ ለሙሉ መቃጠል መቻሉ ነው፡፡ በተጨማሪነትም የሳተላይቱን ውጪያዊ ሽፋን በእንጨት መስራት ኤሌክትሮማግኔቲካዊ ሞገዶች በውስጡ ሰርገው እንዲያልፉ በማድረግ አንቴናዎች ሳተላይቱ ውስጥ በሚቀመጡ መሳርያዎች እንዲተኩ ያስችላል፤ ይህም ሳተላይቶቹ ንድፋቸውም ሆነ ወደ ጠፈር የሚመነጠቁበትን ሂደት ቀላል እንደሚያደርገው ይታመናል፡፡ ተመራማሪዎቹ ለስራው ተገቢ የሆነውን የእንጨት አይነት መርጠው ከባዱን የጠፈር ላይ ሁኔታ እንዲቋቋም ማድረግ ይችሉ እንደሆን የሚያረጋግጡ ሙከራዎችን ለመከወን አቅደዋል፡፡ እ.አ.አ በ2023 ምርቱን አዘጋጅተው ይፋ እንደሚያደርጉም ትንበያቸው ያሳያል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
በአነስተኛ ዋጋ ከፍተኛ ብቃት ያለው መተንፈሻ መሳሪያ
************************
የእንግሊዝ ተመራማሪዎቹ አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት የሚገኙ በኮቪድ ምክንያት ከፍተኛ የአተነፋፈስ ችግር ላጋጠማቸው ህሙማን የሚውሉና በአነስተኛ ዋጋ ተመርተው ከፍተኛ ግልጋሎት የሚሰጡ የመተንፈሻ መሳሪያወችን እንዲያመርቱ የበጀት ድጋፍ ተደረገላቸው፡፡ መካኒካል ቬንትሌሽን ከመተንፈሻ ጋር ለተያያዙ ችግሮች እጅግ ከፍተኛ የሆነ የህይወት አድን ስራ መስራት የሚያስችል መሳሪያ ነው፡፡
በገበያ ላይ ያሉት መተንፈሻ መሳሪያዎች ዋጋቸው ከፍተኛ ከመሆኑ ባሻገር ጥቅም ላይ ለማዋል የአጠቃቀም ስልጠና ወይም ክህሎት የሚጠይቁ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የመተንፈሻ መሳሪያወቹ በብዙ ሀገራት የማይገኙ የጤና መሰረተ ልማቶችን የሚጠይቁ በመሆናቸው ተደራሽነታቸው ከሀገራቱ የኢኮኖሚ አቅም ጋር እጅግ የተቆራኘ ነው፡፡
በእንግሊዝ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ግብዓቶች ካውንስል የተደራጀው የምርምር ቡድን በቀላል ዋጋ የሚቀርቡ፣ ብቁና ለአጠቃቀም ምቹ የሆኑ እንዲሁም የተለየ መሰረተ ልማት የማይፈልጉ የመተንፈሻ መሳሪያዎችን በሙከራ ደረጃ ለማምረት ተግባራትን ጀምሯል፡፡ በተጨማሪም የምርምር ቡድኑ የምርት ስራውን የጥገናና የማጓጓዣ ወጭን ከግምት ውስጥ በማስገባት በሁሉም የአለማችን ክፍሎች ለማከናወን አቅድ እንዳለው አሳውቋል፡፡
ምንጭ SciTechDialy
************************
የእንግሊዝ ተመራማሪዎቹ አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት የሚገኙ በኮቪድ ምክንያት ከፍተኛ የአተነፋፈስ ችግር ላጋጠማቸው ህሙማን የሚውሉና በአነስተኛ ዋጋ ተመርተው ከፍተኛ ግልጋሎት የሚሰጡ የመተንፈሻ መሳሪያወችን እንዲያመርቱ የበጀት ድጋፍ ተደረገላቸው፡፡ መካኒካል ቬንትሌሽን ከመተንፈሻ ጋር ለተያያዙ ችግሮች እጅግ ከፍተኛ የሆነ የህይወት አድን ስራ መስራት የሚያስችል መሳሪያ ነው፡፡
በገበያ ላይ ያሉት መተንፈሻ መሳሪያዎች ዋጋቸው ከፍተኛ ከመሆኑ ባሻገር ጥቅም ላይ ለማዋል የአጠቃቀም ስልጠና ወይም ክህሎት የሚጠይቁ ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የመተንፈሻ መሳሪያወቹ በብዙ ሀገራት የማይገኙ የጤና መሰረተ ልማቶችን የሚጠይቁ በመሆናቸው ተደራሽነታቸው ከሀገራቱ የኢኮኖሚ አቅም ጋር እጅግ የተቆራኘ ነው፡፡
በእንግሊዝ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ግብዓቶች ካውንስል የተደራጀው የምርምር ቡድን በቀላል ዋጋ የሚቀርቡ፣ ብቁና ለአጠቃቀም ምቹ የሆኑ እንዲሁም የተለየ መሰረተ ልማት የማይፈልጉ የመተንፈሻ መሳሪያዎችን በሙከራ ደረጃ ለማምረት ተግባራትን ጀምሯል፡፡ በተጨማሪም የምርምር ቡድኑ የምርት ስራውን የጥገናና የማጓጓዣ ወጭን ከግምት ውስጥ በማስገባት በሁሉም የአለማችን ክፍሎች ለማከናወን አቅድ እንዳለው አሳውቋል፡፡
ምንጭ SciTechDialy
የትኛው ይበጀናል፤ የኤሌክትሪክ መስመርን መዘርጋት ወይስ የፀሐይ ኃይል ቁሳቁሶችን ማቅረብ
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ጨምሮ ከግማሽ ቢሊዮን በላይ የሚሆነው አፍሪካዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ አይደለም፡፡ ይህ በምድራችን ካለው ኤሌክትሪክን ከማይጠቀም ሰው መካከል 72 በመቶው በአፍሪካ ውስጥ ይኖራል ማለት ነው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ያስቀመጣቸው የዘላቂ ልማት ግቦችን የተመለከትን እንደሆነ በአውሮፓውያኑ 2030 ሁሉንም የምድራችን ዜጎች በተመጣኝ ዋጋ ዘላቂ፣ አስተማማኝ እና የዘመነ የኃይል አቅርቦት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚገባቸው ያስቀምጣል፡፡ ታድያ ይህን ለእናት አህጉራችን እንዴት ማሳካት ይቻላል? የትኛውን መንገድ ብንጠቀምስ በአነስተኛ ወጪ ከስኬት እንደርሳለን? ጥናቶች መልሱን ይዘው መጥተዋል፡፡
ባለፈው አስር ዓመት ውስጥ ከተለምዶአዊው የኤሌክትሪክ መስመሮች የተነጠሉ እንደ ፀሐይ ኃይል ተጠቃሚ ቁሶች ያሉ አዳዲስ የኃይል ምንጮችን መስፋፋት አስመልክቶናል፡፡ እነዚህ አማራጮች ማሽኖችን ለማንቀሳቀስ ባይችሉም መብራትን ያበራሉ፣ ስልኮችን ቻርጅ ያደርጋሉ፣ ለራዲዮን እና ቴሌቪዥንም ኃይል ይሰጣሉ፡፡ በዋጋ ረገድም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚከናወነው የኃይል መስመር ዝርጋታ በአንፃራዊነት ዋጋቸው የተሻለ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪካ ኃይል መስመሮች ለኢንዱስትሪ ማንቀሳቀስ እና ሌሎች መሰል አገልግሎቶች የሚበቃ ኃይልን በመስጠታቸው ምክንያት ለረጅም ጊዜ እድገት ተቀዳሚ ምርጫ ሊሆኑ እንደሚገባ ይነገራል፡፡ ሆኖም በእሲያና ደቡባዊ አሜሪካን በተሰራው መልኩአፍሪካ ላይ መስራቱ በዙም እንደማያዋጣ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በተለያዩ አፍሪካ ገጠራማ ክፍሎች መታዘብ እንደተቻለው እነዚህ ስፍራዎች ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በዋናነት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው ለመብራት እና መሰል አነስተኛ እንቅስቃሴዎች ነው፡፡
ሁለት በቅርብ ቡርኪና ፋሶ፣ ሩዋንዳ እና ሴኔጋልን ማዕከል አድርገው የተሰሩ ….ጥናቶች እንደሚያሳዩት ብዙ አፍሪካውያን አባወራዎች ከወርሀዊ ገቢያቸው ውስጥ ከፍ ያለ ድርሸ ኤሌክትሪክ ለማግኘት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ነው፡፡ ጥናቶቹ ማሳየት እንደቻሉት እነዚህ ቤተሰቦች ከ16 እስከ 23 በመቶ የሚሆነውን ወርሀዊ ገቢያቸውን በመስመር ለሚመጣላቸውየኤሌክትሪካ ኃይል አገልግሎት ለማዋል ፈቃደኛ ሲሆኑ ከመስመር ጋር ላልተያያዙት ደግሞ ከ6 እስከ 15 በመቶ ለመክፈል ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ርዋንዳ ላይ ብቻ የተደረገው ሁለተኛው ጥናት እንደሚያሳየው ደግሞ አባወራዎች 20 በመቶ የሚሆነውን ገቢያቸውን ለአነስተኛ በፀሐይ ኃይል ለምትሰራ አምፖል ግዢ ለማዋልበ ፍቃደኛ ሲሆኑ የፀሐይ ኃይል ቁሱ ስክን ቻርጅ ማድረግ ካስቻለ ወጪው እስከ 70 በመቶ ለማሳደግ ያላቸውን ፈቃደኝነት አሳይቷል፡፡ ከዚህ ባሻገር ግን 20 ኪሎ ዋት ማቅረብ እና ከመብራትም ባለፈ ስልክ ቻርጅ ማድረግ ብሎም እንደ ተቪና ራዲዮን ያሉ የመዝናኛ መሳርያዎቸን ኃይል መስጠት በሚችል የፀሐይ ኃይል መሳርያ ላይ ግን ሶስት ወር ገቢያቸውን አውጥተው ለመግዛት ፈቃደኛ ናቸው፡፡
ይህ ከፍተኛ ወጪን ለማውጣት ያለ ፍቃደኝነት ግን እነዚህ የገጠር ቤተሰቦች ገቢያቸው አነስተኛ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የፀሐይ ኃይል መሳርያዎቹን ለመግዛትና ለማስገጠም ከሚያስፈልገው ገንዘብ አንፃር እጅግ ዝቅተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ለምሳሌ በረሩዋንዳ አባወራ ቤተሰቦቹ ለመክፈል ፍቃደኛ የሆኑት እነዚህ ፀሐይ ኃይል ቁሳቁሶች ገበያ ላይ ከሚያወጡት ዋጋ 30 እና 40 በመቶውን ብቻ ነው፡፡
በሌላ መልኩ ለኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ እንደየሁኔታው የሚያይ ቢሆንም በሺዎች የሚቆተር ዶላሮችን ያስወጣል፡፡ እያንዳንዱን ሰው ለበኤሌክትሪክ መስመሮች አማካኝነት ተጠቃሚ ለማድረግ በነፍስ ወከፍ 1,100 ዶላር ያስፈልጋል ቢባል እንኳን እነዚህ ቤተሰቦች መክፈል በሚችሉት ተመጣጣኝ በሆነ ወርሀዊ ክፍያ ዋጋ ብናሰላውበዚህ መስመር ዝርጋታ ላይ የሚወጣውን ወጪ ለመመለስ ከ5 እስከ 18 ዓመታት ይፈጃል፡፡
ጥናቱ በገጠራማይቱ የአፍሪካ ክፍል ከፍተኛ ሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት መኖሩን ማረጋገጥ የቻለ ሲሆን ፍጆጆታን የተመለከትን እንደሆነም በመስመር የሚቀርብን ኃይልንም ሆነ ከዚህ ውጪ የሚመጣውን ኃይል ላይ ያለው ፍጆታ መጠን ተመሳሳይ መሆኑን ማወቅ ተችሏል፡፡
በአጠቃላይ ከዚህ እና ቀድሞ ከተጠቀሱት ውጤቶች በመነሳት ቢያን ለአሁን ከመስመር ውጪ ያሉ አማራጮችን መጠቀሙ ከአጠቃላይ ዋጋ አንፃር አዋጪ ሆኖ ይገኛል፡፡ ሆነም ሁለቱንም አማራጮች ተጠቅሞ የኤሌክትሪካ ኃይልን ለነዋሪዎች ማድረሱ በእቅድ ላይ በተቀመተውጊዜ ውስጥ መሳካት የሚችል አይመስልም፡፡ ጥናቱ መንግስታት የኤሌክትሪካ ኃይልን ለመላው ህዝባቸው ለማድረስ የትኛው የፖሊሲ አማራጭ እንደሚያዋጣቸው ዕይታን የሚሰጥ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህን ለማሳካት መንግስታት ሁለቱንም አማራጮች ቢጠቀሙም እንኳን ዜጎች ድጋፍ ካልተደረገላቸው የኤሌክትሪክ ኃይልን ለመተቀም እጅ እንደሚያጥራቸው ነው፡፡
ምንጭ፡ the conversation
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ጨምሮ ከግማሽ ቢሊዮን በላይ የሚሆነው አፍሪካዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ አይደለም፡፡ ይህ በምድራችን ካለው ኤሌክትሪክን ከማይጠቀም ሰው መካከል 72 በመቶው በአፍሪካ ውስጥ ይኖራል ማለት ነው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ያስቀመጣቸው የዘላቂ ልማት ግቦችን የተመለከትን እንደሆነ በአውሮፓውያኑ 2030 ሁሉንም የምድራችን ዜጎች በተመጣኝ ዋጋ ዘላቂ፣ አስተማማኝ እና የዘመነ የኃይል አቅርቦት ተጠቃሚ ሊሆኑ እንደሚገባቸው ያስቀምጣል፡፡ ታድያ ይህን ለእናት አህጉራችን እንዴት ማሳካት ይቻላል? የትኛውን መንገድ ብንጠቀምስ በአነስተኛ ወጪ ከስኬት እንደርሳለን? ጥናቶች መልሱን ይዘው መጥተዋል፡፡
ባለፈው አስር ዓመት ውስጥ ከተለምዶአዊው የኤሌክትሪክ መስመሮች የተነጠሉ እንደ ፀሐይ ኃይል ተጠቃሚ ቁሶች ያሉ አዳዲስ የኃይል ምንጮችን መስፋፋት አስመልክቶናል፡፡ እነዚህ አማራጮች ማሽኖችን ለማንቀሳቀስ ባይችሉም መብራትን ያበራሉ፣ ስልኮችን ቻርጅ ያደርጋሉ፣ ለራዲዮን እና ቴሌቪዥንም ኃይል ይሰጣሉ፡፡ በዋጋ ረገድም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚከናወነው የኃይል መስመር ዝርጋታ በአንፃራዊነት ዋጋቸው የተሻለ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ሀገር አቀፍ የኤሌክትሪካ ኃይል መስመሮች ለኢንዱስትሪ ማንቀሳቀስ እና ሌሎች መሰል አገልግሎቶች የሚበቃ ኃይልን በመስጠታቸው ምክንያት ለረጅም ጊዜ እድገት ተቀዳሚ ምርጫ ሊሆኑ እንደሚገባ ይነገራል፡፡ ሆኖም በእሲያና ደቡባዊ አሜሪካን በተሰራው መልኩአፍሪካ ላይ መስራቱ በዙም እንደማያዋጣ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ በተለያዩ አፍሪካ ገጠራማ ክፍሎች መታዘብ እንደተቻለው እነዚህ ስፍራዎች ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በዋናነት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው ለመብራት እና መሰል አነስተኛ እንቅስቃሴዎች ነው፡፡
ሁለት በቅርብ ቡርኪና ፋሶ፣ ሩዋንዳ እና ሴኔጋልን ማዕከል አድርገው የተሰሩ ….ጥናቶች እንደሚያሳዩት ብዙ አፍሪካውያን አባወራዎች ከወርሀዊ ገቢያቸው ውስጥ ከፍ ያለ ድርሸ ኤሌክትሪክ ለማግኘት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ነው፡፡ ጥናቶቹ ማሳየት እንደቻሉት እነዚህ ቤተሰቦች ከ16 እስከ 23 በመቶ የሚሆነውን ወርሀዊ ገቢያቸውን በመስመር ለሚመጣላቸውየኤሌክትሪካ ኃይል አገልግሎት ለማዋል ፈቃደኛ ሲሆኑ ከመስመር ጋር ላልተያያዙት ደግሞ ከ6 እስከ 15 በመቶ ለመክፈል ዝግጁነታቸውን አረጋግጠዋል፡፡ ርዋንዳ ላይ ብቻ የተደረገው ሁለተኛው ጥናት እንደሚያሳየው ደግሞ አባወራዎች 20 በመቶ የሚሆነውን ገቢያቸውን ለአነስተኛ በፀሐይ ኃይል ለምትሰራ አምፖል ግዢ ለማዋልበ ፍቃደኛ ሲሆኑ የፀሐይ ኃይል ቁሱ ስክን ቻርጅ ማድረግ ካስቻለ ወጪው እስከ 70 በመቶ ለማሳደግ ያላቸውን ፈቃደኝነት አሳይቷል፡፡ ከዚህ ባሻገር ግን 20 ኪሎ ዋት ማቅረብ እና ከመብራትም ባለፈ ስልክ ቻርጅ ማድረግ ብሎም እንደ ተቪና ራዲዮን ያሉ የመዝናኛ መሳርያዎቸን ኃይል መስጠት በሚችል የፀሐይ ኃይል መሳርያ ላይ ግን ሶስት ወር ገቢያቸውን አውጥተው ለመግዛት ፈቃደኛ ናቸው፡፡
ይህ ከፍተኛ ወጪን ለማውጣት ያለ ፍቃደኝነት ግን እነዚህ የገጠር ቤተሰቦች ገቢያቸው አነስተኛ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የፀሐይ ኃይል መሳርያዎቹን ለመግዛትና ለማስገጠም ከሚያስፈልገው ገንዘብ አንፃር እጅግ ዝቅተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ለምሳሌ በረሩዋንዳ አባወራ ቤተሰቦቹ ለመክፈል ፍቃደኛ የሆኑት እነዚህ ፀሐይ ኃይል ቁሳቁሶች ገበያ ላይ ከሚያወጡት ዋጋ 30 እና 40 በመቶውን ብቻ ነው፡፡
በሌላ መልኩ ለኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ እንደየሁኔታው የሚያይ ቢሆንም በሺዎች የሚቆተር ዶላሮችን ያስወጣል፡፡ እያንዳንዱን ሰው ለበኤሌክትሪክ መስመሮች አማካኝነት ተጠቃሚ ለማድረግ በነፍስ ወከፍ 1,100 ዶላር ያስፈልጋል ቢባል እንኳን እነዚህ ቤተሰቦች መክፈል በሚችሉት ተመጣጣኝ በሆነ ወርሀዊ ክፍያ ዋጋ ብናሰላውበዚህ መስመር ዝርጋታ ላይ የሚወጣውን ወጪ ለመመለስ ከ5 እስከ 18 ዓመታት ይፈጃል፡፡
ጥናቱ በገጠራማይቱ የአፍሪካ ክፍል ከፍተኛ ሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት መኖሩን ማረጋገጥ የቻለ ሲሆን ፍጆጆታን የተመለከትን እንደሆነም በመስመር የሚቀርብን ኃይልንም ሆነ ከዚህ ውጪ የሚመጣውን ኃይል ላይ ያለው ፍጆታ መጠን ተመሳሳይ መሆኑን ማወቅ ተችሏል፡፡
በአጠቃላይ ከዚህ እና ቀድሞ ከተጠቀሱት ውጤቶች በመነሳት ቢያን ለአሁን ከመስመር ውጪ ያሉ አማራጮችን መጠቀሙ ከአጠቃላይ ዋጋ አንፃር አዋጪ ሆኖ ይገኛል፡፡ ሆነም ሁለቱንም አማራጮች ተጠቅሞ የኤሌክትሪካ ኃይልን ለነዋሪዎች ማድረሱ በእቅድ ላይ በተቀመተውጊዜ ውስጥ መሳካት የሚችል አይመስልም፡፡ ጥናቱ መንግስታት የኤሌክትሪካ ኃይልን ለመላው ህዝባቸው ለማድረስ የትኛው የፖሊሲ አማራጭ እንደሚያዋጣቸው ዕይታን የሚሰጥ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህን ለማሳካት መንግስታት ሁለቱንም አማራጮች ቢጠቀሙም እንኳን ዜጎች ድጋፍ ካልተደረገላቸው የኤሌክትሪክ ኃይልን ለመተቀም እጅ እንደሚያጥራቸው ነው፡፡
ምንጭ፡ the conversation