ስንጥቃቸውን በራሳቸው ማደስ የሚችሉ የስማርት ስልክ ስክሪን ሽፋኖች
************************************
በአሁኑ ወቅት የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች ከሚቸገሩባቸው ነገሮች መካከል ስልካቸው በወደቀ ቁጥር የስክሪኑ ሽፋን መስታወት በቀላሉ መሰነጣጠቁ ነው፡፡ አለፍ ሲልም ከአነስተኛ እስከ ከፍ ያለ ዋጋ የሚጠይቅ የጥገና ወጭ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ምስጋና ይግባቸውና የዘርፉ ተመራማሪዎች ጊዜቸውን ራሳቸውን የሚያድሱ የስማርት ስልክ ስክሪን ሽፋኖችን ለመስራት እያዋሉ እንደሆነና ጥቅም ላይ ለማዋልም እንደተቃረቡ ተናግረዋል፡፡
በኮሪያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የምርምር ተቋም የሚገኝ አንድ የምርምር ቡድን የራሱን ስንጥቅና ሌላ አካላዊ ጉዳት መጠገን የሚችል ምስጢራዊ የሆነ ዘይትን በግብዓትነት በውስጡ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቁስ ማበልጸጉን የዘገበው ሳይንስ አለርት ነው፡፡
ይህ ልዩ ዘይት ፍላክስ ከሚባል ቃጫ መሰል ተክል ዘሮች የሚዘጋጅ ሲሆን ተመራማሪዎች ለስራቸው አመቺ የሚሆን ቀለም አልባ ግብዓትን ለማግኘት የሚያስችል የማላመድ ስራን ሰርተውበታል፡፡ ይህ ዘይት ጉዳት የደረሰበትን የስክሪኑን ሽፋን ክፍል ሰርስሮ በመግባት ስንጥቁን ወይም ስብራቱን ማስተካከል እንዲችል የታለመ ነው፡፡ ይህ ጥናት ሙሉ ለሙሉ ሲሳካ ስብራታቸውን የሚጠግኑ የስልክ ስክሪን ሽፋኖች ኖሩንና በየጊዜው የተሰነጣጠቀ ስልክ ከመያዝ ይገላግሉናል ሲል የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡
የዚህ ቴክኖሎጂ ጥቅም የተሰበረ የስልክ ስክሪን ሽፋንን ከመጠገን ባለፈ ሌሎች ቀለም አልባ ፖሊማይድ (CPI) የሚጠቀሙ እንደ የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ ንጣፎችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በቀላሉ መጠገን እንደሚያስችል ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Sciencealart
************************************
በአሁኑ ወቅት የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች ከሚቸገሩባቸው ነገሮች መካከል ስልካቸው በወደቀ ቁጥር የስክሪኑ ሽፋን መስታወት በቀላሉ መሰነጣጠቁ ነው፡፡ አለፍ ሲልም ከአነስተኛ እስከ ከፍ ያለ ዋጋ የሚጠይቅ የጥገና ወጭ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ምስጋና ይግባቸውና የዘርፉ ተመራማሪዎች ጊዜቸውን ራሳቸውን የሚያድሱ የስማርት ስልክ ስክሪን ሽፋኖችን ለመስራት እያዋሉ እንደሆነና ጥቅም ላይ ለማዋልም እንደተቃረቡ ተናግረዋል፡፡
በኮሪያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የምርምር ተቋም የሚገኝ አንድ የምርምር ቡድን የራሱን ስንጥቅና ሌላ አካላዊ ጉዳት መጠገን የሚችል ምስጢራዊ የሆነ ዘይትን በግብዓትነት በውስጡ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቁስ ማበልጸጉን የዘገበው ሳይንስ አለርት ነው፡፡
ይህ ልዩ ዘይት ፍላክስ ከሚባል ቃጫ መሰል ተክል ዘሮች የሚዘጋጅ ሲሆን ተመራማሪዎች ለስራቸው አመቺ የሚሆን ቀለም አልባ ግብዓትን ለማግኘት የሚያስችል የማላመድ ስራን ሰርተውበታል፡፡ ይህ ዘይት ጉዳት የደረሰበትን የስክሪኑን ሽፋን ክፍል ሰርስሮ በመግባት ስንጥቁን ወይም ስብራቱን ማስተካከል እንዲችል የታለመ ነው፡፡ ይህ ጥናት ሙሉ ለሙሉ ሲሳካ ስብራታቸውን የሚጠግኑ የስልክ ስክሪን ሽፋኖች ኖሩንና በየጊዜው የተሰነጣጠቀ ስልክ ከመያዝ ይገላግሉናል ሲል የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡
የዚህ ቴክኖሎጂ ጥቅም የተሰበረ የስልክ ስክሪን ሽፋንን ከመጠገን ባለፈ ሌሎች ቀለም አልባ ፖሊማይድ (CPI) የሚጠቀሙ እንደ የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ ንጣፎችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በቀላሉ መጠገን እንደሚያስችል ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Sciencealart
ከ21 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣው አዲሱ የአፕል ኤርፖድ
============================
ስመ ጥሩ የቴክኖሎጂ ኩባንያ አፕል እስከ 21,740 ብር ወይም 549 ዶላር ድረስ (በአሜሪካን የሚሸጡበት ብቻ) ዋጋ የተመነላቸው የድምፅ ማዳመጫ ኤርፖዶቹን በቅርቡ ይፋ አድርጓል፡፡ ኤርፖዱ ከብረት እና አልሙኒየም የተሰራ ሲሆን እንደየ ደረጃው ከ130 እስከ 385 ግራም ክብደት አለው፡፡ ዋናው ክብደት ጆሮ ላይ በሚለጠፉት የኤርፖዱ ክፍሎች (Ear Cups) ላይ በመሆኑም ጭንቅላት በሚነቃነቅበት ወቅት ብዙም ቦታቸውን ሳይለለቁ እንዲቆዩ ያደርጋቸዋል፡፡
ኤርፖዶቹ ከውጭ ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴከኖሎጂ (Noise-Cancelling) የተገጠመላቸው ሲሆኑ በአንድ ቻርጅ ብቻ እስከ 20 ሰዓት ያክል አገልግሎት እየሰጡ መቆየት እንደሚችሉ አፕል ተናግሯል፡፡ ኤርፖዶቹ የአፕል ኤች1 ቺፕ የተገጠመለት በመሆኑም ብሉቱዝ 5.0 ያላቸውና የተለያዩ የኦዲዮ አይነቶችንም ማጫወት የሚችሉ አድርጓቸዋል፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ተዕዛዝ መቀበል እንዲሁም አጭር የፅሁፍ መልዕክቶችን እንደገቡ ማንበብ የሚችል ነው፡፡ ኤርፖዱ ከአፕል ውጪም ከሌሎች ምርቶች ጋራ መገናኘት የሚችል ቢሆንም አንዳንድ ገፅታዎቹ ግን ከአፕል ምርቶች ጋር ሲሆኑ ብቻ ይሆናል የሚሰሩት፡፡
ኤርፖዶቹ ያላቸው ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴክኖሎጂ ማይክሮፎኖችን በመጠቀም ያልተፈለጉ ድምፆች ሁሉ ከጆሮ እንዳይደርሱ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እንበልና ኤርፖዱን ያደረገ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲራመድ በዙርያው ያሉ የመንገድ ዳር እና ሌሎች ረባሽ ድምፆች ምንም እንዳልተፈጠሩ ሁሉ ሳይሰማቸው ሙዚቃውን ማጣጣም ይችላል ማለት ነው፡፡ ሆኖም ይህ ሰው በዙርያው የመኪና እና ሌሎች ድምፆችን እየሰማ እራሱን ጠብቆ ለመጓዝ ካሻው ትራንስፓረንት ሞድ ላይ በማድረግ ኤርፖዱን ያላደረገ እስኪመስለው ድረስ የውጭ ድምፅ እንዲገባ ማድረግ ያስችለዋል፡፡
የባትሪያቸውን ቆይታ ያየን እንደሆን ድምፅ እንዳይገባ ማድረጊያው በርቶ እስከ 20 ሰዓት ድረስ አገልግሎት መሰጠት የሚችሉ ሲሆን ይህ ጠፍቶ ግን ከዚያ ለበለጠ ጊዜም ግልጋሎት መስጠት የሚችል ነው፡፡ ይህ ከቦስ ኤርፖዶች ጋራ ተመሳሳይ ቢሆንም ከB&W አቻዎቹ አንፃር ግን በ10 ሰዓት ያነሰ ያደርጋቸዋል፡፡ የ5 ዋት እና ከዚያ በላይ የሆነ የዩኤስቢ ቻርጀር በመጠቀምም ኤርፖዱን ሙሉ ለሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ሁለት ሰዓታት መጠበቅ ግድ የሚል ቢሆንም ለ5 ደቂቃ ብቻ ቻርጅ አድርጎ ለ90 ደቂቃ ሙዚቃ ማጫወት የሚያስችለውን ኃይል ማግኘት ይችላል፡፡
ኤርፖዶቹ ባላቸው የድምፅ ጥራት፣ ቴክኖሎጂ እና ቅንጦት ብዙ ሰዎችን መሳብ የቻሉ ቢሆንም ዋጋቸው ግን እጅጉን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ከአንዳንድ የቅርብ ተፎካካሪ የሆኑ ተመሳሳይ ምርቶች አንፃር እንኳን 200 ዶላር እና ከዚያ የዋጋ ልዩነት አላቸው፡፡ በተጨማሪም ከአሜሪካ ውጪ ሲሸጡ ዋጋቸው ከዚህም በላይ እየጨመረ ይሄዳል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
============================
ስመ ጥሩ የቴክኖሎጂ ኩባንያ አፕል እስከ 21,740 ብር ወይም 549 ዶላር ድረስ (በአሜሪካን የሚሸጡበት ብቻ) ዋጋ የተመነላቸው የድምፅ ማዳመጫ ኤርፖዶቹን በቅርቡ ይፋ አድርጓል፡፡ ኤርፖዱ ከብረት እና አልሙኒየም የተሰራ ሲሆን እንደየ ደረጃው ከ130 እስከ 385 ግራም ክብደት አለው፡፡ ዋናው ክብደት ጆሮ ላይ በሚለጠፉት የኤርፖዱ ክፍሎች (Ear Cups) ላይ በመሆኑም ጭንቅላት በሚነቃነቅበት ወቅት ብዙም ቦታቸውን ሳይለለቁ እንዲቆዩ ያደርጋቸዋል፡፡
ኤርፖዶቹ ከውጭ ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴከኖሎጂ (Noise-Cancelling) የተገጠመላቸው ሲሆኑ በአንድ ቻርጅ ብቻ እስከ 20 ሰዓት ያክል አገልግሎት እየሰጡ መቆየት እንደሚችሉ አፕል ተናግሯል፡፡ ኤርፖዶቹ የአፕል ኤች1 ቺፕ የተገጠመለት በመሆኑም ብሉቱዝ 5.0 ያላቸውና የተለያዩ የኦዲዮ አይነቶችንም ማጫወት የሚችሉ አድርጓቸዋል፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ተዕዛዝ መቀበል እንዲሁም አጭር የፅሁፍ መልዕክቶችን እንደገቡ ማንበብ የሚችል ነው፡፡ ኤርፖዱ ከአፕል ውጪም ከሌሎች ምርቶች ጋራ መገናኘት የሚችል ቢሆንም አንዳንድ ገፅታዎቹ ግን ከአፕል ምርቶች ጋር ሲሆኑ ብቻ ይሆናል የሚሰሩት፡፡
ኤርፖዶቹ ያላቸው ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴክኖሎጂ ማይክሮፎኖችን በመጠቀም ያልተፈለጉ ድምፆች ሁሉ ከጆሮ እንዳይደርሱ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እንበልና ኤርፖዱን ያደረገ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲራመድ በዙርያው ያሉ የመንገድ ዳር እና ሌሎች ረባሽ ድምፆች ምንም እንዳልተፈጠሩ ሁሉ ሳይሰማቸው ሙዚቃውን ማጣጣም ይችላል ማለት ነው፡፡ ሆኖም ይህ ሰው በዙርያው የመኪና እና ሌሎች ድምፆችን እየሰማ እራሱን ጠብቆ ለመጓዝ ካሻው ትራንስፓረንት ሞድ ላይ በማድረግ ኤርፖዱን ያላደረገ እስኪመስለው ድረስ የውጭ ድምፅ እንዲገባ ማድረግ ያስችለዋል፡፡
የባትሪያቸውን ቆይታ ያየን እንደሆን ድምፅ እንዳይገባ ማድረጊያው በርቶ እስከ 20 ሰዓት ድረስ አገልግሎት መሰጠት የሚችሉ ሲሆን ይህ ጠፍቶ ግን ከዚያ ለበለጠ ጊዜም ግልጋሎት መስጠት የሚችል ነው፡፡ ይህ ከቦስ ኤርፖዶች ጋራ ተመሳሳይ ቢሆንም ከB&W አቻዎቹ አንፃር ግን በ10 ሰዓት ያነሰ ያደርጋቸዋል፡፡ የ5 ዋት እና ከዚያ በላይ የሆነ የዩኤስቢ ቻርጀር በመጠቀምም ኤርፖዱን ሙሉ ለሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ሁለት ሰዓታት መጠበቅ ግድ የሚል ቢሆንም ለ5 ደቂቃ ብቻ ቻርጅ አድርጎ ለ90 ደቂቃ ሙዚቃ ማጫወት የሚያስችለውን ኃይል ማግኘት ይችላል፡፡
ኤርፖዶቹ ባላቸው የድምፅ ጥራት፣ ቴክኖሎጂ እና ቅንጦት ብዙ ሰዎችን መሳብ የቻሉ ቢሆንም ዋጋቸው ግን እጅጉን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ከአንዳንድ የቅርብ ተፎካካሪ የሆኑ ተመሳሳይ ምርቶች አንፃር እንኳን 200 ዶላር እና ከዚያ የዋጋ ልዩነት አላቸው፡፡ በተጨማሪም ከአሜሪካ ውጪ ሲሸጡ ዋጋቸው ከዚህም በላይ እየጨመረ ይሄዳል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ከሌላው ዓለም ፍጡራን የተላከ ሊሆን ይችላል የተባለለት አዲስ የራዲዮ ሞገድ
=========================
የሌላ ዓለም ፍጡራንን ፍለጋ ውስጥ በቀዳሚነት በሚቀመጠው ፕሮጀክት ስር የሚሰሩት ተመራማሪዎች ለፀሐይ በቅርብ ርቀት ከምትገኘውና ከምድር የ4.2 ብርሃን ዓመት ርቀት ካላት ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ኮከብ አቅጣጫ የመጡ የሚመስሉ አጠራጣሪ የሬዲዮ ሞገዶችን እየመረመሩ ናቸው፡፡ የሬዲዮ ሞገዶቹ አውስትራሊያ ውስጥ ባለው የፓርከስ ቴሌስኮፕ አማካኝነት ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ሚያዝያ እና ግንቦት ወራት ላይ ነው የተገኙት፡፡ ሲግናሉ ከተላከበት ጊዜ አንስቶ በተመራማሪዎቹ ትንተና እየተደረገበት ሲሆን ዝርዝሩ እስካሁን ለህዝብ ይፋ አልተደረገም፡፡
ተመራማሪዎቹ ምዕራብ ቨርጂኒያ ውስጥ ባለው ቴሌስኮፕ አማካኝነት መሰል የራዲዮ ዌቮችን መስማታቸው የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም እነዚህ ሞገዶች የሰው ልጆች ተፅዕንዖን ተከትለው የተገኙ ሲሆን ይህን ግን ለየት የሚያደርገው 980 ሜጋ ኸርዝ በሆነው የሬዲዮ ሞገዱ ባንዶች ውስጥ ሰው ሰራሽ የሆኑ ሳተላይትም ሆነ ቁስ ሲግናል አልተገኘበትም፡፡
ሲግናሉ በአውሮፓውያኑ 1977 ከተገኘውና “ዋው ሲግናል” ተብሎ ከሚታወቀው በኋላ በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ሲግናል እንደሆነም በባለሙያዎች ዘንድ ተነግሮለታል፡፡ ሲግናሉን የመተንተኑን ስራ ስትመራ የቆየችው ሶፊያ ሼክ በፕሮጀክታቸው ውስጥ እስከዛሬ ከተሰሙት ሁሉ አጓጊው ሲግናል መሆኑን ትናገራለች፡፡ ሲግናሉንም ብሬክስሩ ሊስን ካንዲዴት 1 (BLC1) ብለውታል፡፡
በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ውስጥ ከሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መካከል አንዱ ከእነዚህ ፍጡራን ጋራ የመገናኛው/መግባብያው መንገድ አለመታወቁ ነው፡፡ በተጨማሪም በዩኒቨርስ ውስጥ የሚፈጠሩ የሬዲዮ ሞገዶች ምንጭ ሊሆኑ የሚችሉት ተፈጥሮአዊ መነሻዎችም ቢሆን ሙሉ በሙሉ አይታወቁም፡፡ ስለዚህም ብዙውን እንደዚህ አይነት ሲግናሎች ሲገኙ ቴክኖሎጂ አፈራሽ እንደሆኑ ግምት የሚወሰድና ከተፈጥሮአዊ ምንጭ መሆናቸውን የሚያስረዳ ማብራርያንም በቀላሉ የማይገኝባቸው ሲሆን ነገሩን ወደ ሌላኛው ዓለም ፍጡራን መውሰዱ ግን ትኩረት ሳቢ ነው፡፡ ስለ ሲግናሉ የሚገልፅ መረጃ ለህዝብ ይፋ ያልተደረገ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ወደፊት ይፋ ቢሆን እንኳን ልክ እንደ ዋው ሲግናል ሁሉ በማስረጃ የዋጀ ድምዳሜ ላይ የሚደረስበት አይመስልም፡፡
ከማንኛውም ኮከብ በላይ ለምድር በምትቀርበው ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ውስጥ ቢያንስ ሁለት የሚዞሯት ፕላኔቶች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ አንደኛው በጋዝ የተሞላ ሲሆን ሌላኛው ግን ባለው ለውሃ ፍሰት የተስማማ ሙቀት ሳብያ ሰውን ሊያኖሩ ይችላሉ ተብለው ግምት ከሚወሰድባቸው ፕላኔቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ይህች ፕላኔት ከምድር በ17 በመቶ የግዝፈት ብልጫ ያላት ድንጋያማ ስፍራ ናት፡፡ ፕሮክሲማ ቢ በሚል ስያሜ የምትታወቀው ፕላኔቷ በየ 11 ቀናቱ ኮከቧን የምትዞር ናት፡፡ ሆኖም ለሰው ልጆች ኑሮ አደገኛ ልትሆንም እንደምትችል ይነገራል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት የናሳ ተመራማሪዎች የኮምፒውተር ሞዴልን ተጠቅመው ፕላኔቷ በቀላሉ ለከባድ ጨረር እና ድንገተኛ የኮከብ ብርሃን ነበልባል የተጋለጠች ልትሆን እንደምትችል አሳይተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian እና Live Science
=========================
የሌላ ዓለም ፍጡራንን ፍለጋ ውስጥ በቀዳሚነት በሚቀመጠው ፕሮጀክት ስር የሚሰሩት ተመራማሪዎች ለፀሐይ በቅርብ ርቀት ከምትገኘውና ከምድር የ4.2 ብርሃን ዓመት ርቀት ካላት ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ኮከብ አቅጣጫ የመጡ የሚመስሉ አጠራጣሪ የሬዲዮ ሞገዶችን እየመረመሩ ናቸው፡፡ የሬዲዮ ሞገዶቹ አውስትራሊያ ውስጥ ባለው የፓርከስ ቴሌስኮፕ አማካኝነት ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ሚያዝያ እና ግንቦት ወራት ላይ ነው የተገኙት፡፡ ሲግናሉ ከተላከበት ጊዜ አንስቶ በተመራማሪዎቹ ትንተና እየተደረገበት ሲሆን ዝርዝሩ እስካሁን ለህዝብ ይፋ አልተደረገም፡፡
ተመራማሪዎቹ ምዕራብ ቨርጂኒያ ውስጥ ባለው ቴሌስኮፕ አማካኝነት መሰል የራዲዮ ዌቮችን መስማታቸው የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም እነዚህ ሞገዶች የሰው ልጆች ተፅዕንዖን ተከትለው የተገኙ ሲሆን ይህን ግን ለየት የሚያደርገው 980 ሜጋ ኸርዝ በሆነው የሬዲዮ ሞገዱ ባንዶች ውስጥ ሰው ሰራሽ የሆኑ ሳተላይትም ሆነ ቁስ ሲግናል አልተገኘበትም፡፡
ሲግናሉ በአውሮፓውያኑ 1977 ከተገኘውና “ዋው ሲግናል” ተብሎ ከሚታወቀው በኋላ በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ሲግናል እንደሆነም በባለሙያዎች ዘንድ ተነግሮለታል፡፡ ሲግናሉን የመተንተኑን ስራ ስትመራ የቆየችው ሶፊያ ሼክ በፕሮጀክታቸው ውስጥ እስከዛሬ ከተሰሙት ሁሉ አጓጊው ሲግናል መሆኑን ትናገራለች፡፡ ሲግናሉንም ብሬክስሩ ሊስን ካንዲዴት 1 (BLC1) ብለውታል፡፡
በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ውስጥ ከሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መካከል አንዱ ከእነዚህ ፍጡራን ጋራ የመገናኛው/መግባብያው መንገድ አለመታወቁ ነው፡፡ በተጨማሪም በዩኒቨርስ ውስጥ የሚፈጠሩ የሬዲዮ ሞገዶች ምንጭ ሊሆኑ የሚችሉት ተፈጥሮአዊ መነሻዎችም ቢሆን ሙሉ በሙሉ አይታወቁም፡፡ ስለዚህም ብዙውን እንደዚህ አይነት ሲግናሎች ሲገኙ ቴክኖሎጂ አፈራሽ እንደሆኑ ግምት የሚወሰድና ከተፈጥሮአዊ ምንጭ መሆናቸውን የሚያስረዳ ማብራርያንም በቀላሉ የማይገኝባቸው ሲሆን ነገሩን ወደ ሌላኛው ዓለም ፍጡራን መውሰዱ ግን ትኩረት ሳቢ ነው፡፡ ስለ ሲግናሉ የሚገልፅ መረጃ ለህዝብ ይፋ ያልተደረገ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ወደፊት ይፋ ቢሆን እንኳን ልክ እንደ ዋው ሲግናል ሁሉ በማስረጃ የዋጀ ድምዳሜ ላይ የሚደረስበት አይመስልም፡፡
ከማንኛውም ኮከብ በላይ ለምድር በምትቀርበው ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ውስጥ ቢያንስ ሁለት የሚዞሯት ፕላኔቶች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ አንደኛው በጋዝ የተሞላ ሲሆን ሌላኛው ግን ባለው ለውሃ ፍሰት የተስማማ ሙቀት ሳብያ ሰውን ሊያኖሩ ይችላሉ ተብለው ግምት ከሚወሰድባቸው ፕላኔቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ይህች ፕላኔት ከምድር በ17 በመቶ የግዝፈት ብልጫ ያላት ድንጋያማ ስፍራ ናት፡፡ ፕሮክሲማ ቢ በሚል ስያሜ የምትታወቀው ፕላኔቷ በየ 11 ቀናቱ ኮከቧን የምትዞር ናት፡፡ ሆኖም ለሰው ልጆች ኑሮ አደገኛ ልትሆንም እንደምትችል ይነገራል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት የናሳ ተመራማሪዎች የኮምፒውተር ሞዴልን ተጠቅመው ፕላኔቷ በቀላሉ ለከባድ ጨረር እና ድንገተኛ የኮከብ ብርሃን ነበልባል የተጋለጠች ልትሆን እንደምትችል አሳይተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian እና Live Science
ናኖ ቴክኖሎጂ ለዘመናዊ ግብርና
የግብርና ቴክኖሎጂ መሠረታዊ መለኪያው የምርት መጠንን መጨመር፣ የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ የሥራ ቅልጥፍና መፍጠርና ማቀነባበርን ያካትታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኢንዱስትሪ የበለፀጉ ሀገራት የናኖ ቴክኖሎጂን የሚደግፉ ተቋማትን በመመስረት ምርምር በሰፊው ከማካሄድ ባለፈ ወደ ምርት ተግባር መግባታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከቅርብ ዓመታት በኋላ ታዳጊ ሀገራትም ናኖ ቴክኖሎጂን በኢንዱስትሪዎቻቸው ውስጥ እየተጠቀሙባቸው ይገኛል፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ የምርት ጥራትና ብዛት ማሳደግ የሚያስችል በመሆኑ በግብርና ምርት ላይ መጠቀም የሚፈለገዉን ለዉጥ ለማምጣት ያግዛል፡፡ ከዚህም በተጓዳኝ ናኖ ቴክኖሎጂ በግብርና ኬሚካል ቅመም በመጠቀም የአፈር፣ የውሃና የአየር ብክለትን በመቀነስ ግብርናው የበለጠ አስተማማኝ እንዲሆን ያደርጋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በድረ-ገጹ ባወጣው የግብርና ፖሊሲ መግለጫ በ2050 የዓለም ህዝብ ብዛት 9 ቢሊዮን እንደሚደርስና እየጨመረ ያለውን የህዝብ ቁጥር ለመመገብ ግብርናውን ማዘመን የግድ እንደሚል አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ደግሞ ናኖ ቴክኖሎጂ መፍትሄ ያመጣል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታ፡፡ ናኖ ቴክኖሎጂ የምርትን ጥራትና ብዛት ከመጨመር ባሻገር ለዘላቂ የውሃ አጠቃቀም፣ ለንፁህ ዘር አቅርቦት፣ ተባይ እና በሽታን ለመለየት፣ አልሚ የምግብ አቅርቦትን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የእፅዋት ጥበቃና ተፈጥሮ ሃብት ከብክለት ነፃ ለማድረግ ወይም ለመቀነስ የሚረዳ መድሃኒት ማቅረብ ትኩረት ሊደረግበት የሚገባ ነው፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ በተፈጥሮ ላይ የጎንዮሽ ጉዳት ሳይደርስ ሚዛኑን ጠብቆ አረንጓዴና የተመቻቸ ስነ-ምህዳራዊ አካባቢን በመፍጠር የግብርና ምርትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ይሁን እንጅ በበለፀጉትና በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የናኖ ቅንጣቶች በረዥም ጊዜ አደጋ ያስከትላሉ ብሎ በመጠራጠር ለመቀበል መቸገር እንደሚስተዋል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ማንኛውም የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች እንደሚሰጡት ትሩፋት ሁሉ መጠነኛ ጉዳት ሊኖራቸው ስለሚችል የአጠቃቀም ሁኔታን ይበልጥ በማሻሻል እና ተሞክሮዎችን በመቀመር የቴክኖሎጂውን ፍሬ በበልሃት መጠቀም ግድ ይላል፡፡ የናኖ ቴክኖሎጂ ወጭ ቆጣ፤ ምርታማነትን ይበልጥ የሚያሳድግ እና ወቅቱን የዋጀ ቴክኖሎጂ መሆኑን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር በአጠቃቀም ሂደቱ ላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው፡፡
ምንጭ፡ Frontiersin
የግብርና ቴክኖሎጂ መሠረታዊ መለኪያው የምርት መጠንን መጨመር፣ የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ የሥራ ቅልጥፍና መፍጠርና ማቀነባበርን ያካትታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኢንዱስትሪ የበለፀጉ ሀገራት የናኖ ቴክኖሎጂን የሚደግፉ ተቋማትን በመመስረት ምርምር በሰፊው ከማካሄድ ባለፈ ወደ ምርት ተግባር መግባታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከቅርብ ዓመታት በኋላ ታዳጊ ሀገራትም ናኖ ቴክኖሎጂን በኢንዱስትሪዎቻቸው ውስጥ እየተጠቀሙባቸው ይገኛል፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ የምርት ጥራትና ብዛት ማሳደግ የሚያስችል በመሆኑ በግብርና ምርት ላይ መጠቀም የሚፈለገዉን ለዉጥ ለማምጣት ያግዛል፡፡ ከዚህም በተጓዳኝ ናኖ ቴክኖሎጂ በግብርና ኬሚካል ቅመም በመጠቀም የአፈር፣ የውሃና የአየር ብክለትን በመቀነስ ግብርናው የበለጠ አስተማማኝ እንዲሆን ያደርጋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በድረ-ገጹ ባወጣው የግብርና ፖሊሲ መግለጫ በ2050 የዓለም ህዝብ ብዛት 9 ቢሊዮን እንደሚደርስና እየጨመረ ያለውን የህዝብ ቁጥር ለመመገብ ግብርናውን ማዘመን የግድ እንደሚል አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ደግሞ ናኖ ቴክኖሎጂ መፍትሄ ያመጣል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታ፡፡ ናኖ ቴክኖሎጂ የምርትን ጥራትና ብዛት ከመጨመር ባሻገር ለዘላቂ የውሃ አጠቃቀም፣ ለንፁህ ዘር አቅርቦት፣ ተባይ እና በሽታን ለመለየት፣ አልሚ የምግብ አቅርቦትን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የእፅዋት ጥበቃና ተፈጥሮ ሃብት ከብክለት ነፃ ለማድረግ ወይም ለመቀነስ የሚረዳ መድሃኒት ማቅረብ ትኩረት ሊደረግበት የሚገባ ነው፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ በተፈጥሮ ላይ የጎንዮሽ ጉዳት ሳይደርስ ሚዛኑን ጠብቆ አረንጓዴና የተመቻቸ ስነ-ምህዳራዊ አካባቢን በመፍጠር የግብርና ምርትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ይሁን እንጅ በበለፀጉትና በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የናኖ ቅንጣቶች በረዥም ጊዜ አደጋ ያስከትላሉ ብሎ በመጠራጠር ለመቀበል መቸገር እንደሚስተዋል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ማንኛውም የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች እንደሚሰጡት ትሩፋት ሁሉ መጠነኛ ጉዳት ሊኖራቸው ስለሚችል የአጠቃቀም ሁኔታን ይበልጥ በማሻሻል እና ተሞክሮዎችን በመቀመር የቴክኖሎጂውን ፍሬ በበልሃት መጠቀም ግድ ይላል፡፡ የናኖ ቴክኖሎጂ ወጭ ቆጣ፤ ምርታማነትን ይበልጥ የሚያሳድግ እና ወቅቱን የዋጀ ቴክኖሎጂ መሆኑን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር በአጠቃቀም ሂደቱ ላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው፡፡
ምንጭ፡ Frontiersin
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከልሳን ቴክኖሎጂ ጋራ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከልሳን ቴክኖሎጂ ጋራ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ፡፡ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በዋና አላማነት አንግቦ የተካሄደው የመግባብያ ስምምነቱ በሁለቱም ተቋማት ያሉ ተመራማሪዎችን በማስተባበር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤት እንደሚያስገኝም ታምኖበታል፡፡ ስምምነቱን በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በኩል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሙሉቀን ቀሬ ሲፈርሙ ልሳን ቴክኖሎጂን በመወከል ደግሞ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ አዳም ቦዶዊን ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡
ስምምነቱ ሁለቱ አካላት በማሽን ትራንስሌሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዲሁም በሁለቱም ተቋማት የሚገኙ ተመራማሪዎች፣ ሶፍትዌር መሀንዲሶች እና ሌሎች ባለሙያዎች በጋራ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ልሳን የስልጠና እንዲሁም የማሽን ትራንስሌሽን እና ኦፕቲካል ካራክተር ሪኮግኒሽን (OCR) ሲስተሞች ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ኢንስቲትዩቱም ለጋራ ምርምር የሚያስፈልግ መሰረተልማት፣ ቁሳቁስ እና አስተዳደራዊ አቅርቦቶችን የሚያከናውን ይሆናል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ ኢንስቲትዩቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በስልጠና፣ ጥናት እና ቢዝነስ መካከል ድልድይ መሆኑንና በሀገሪቱ ስትራቴጂዎች ውስጥም ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አውስተው ስምምነቱ በፍጥነት ወደ ተግባር እንዲለወጥ ያላቸውን ፍላጎት አንፀባርቀዋል፡፡ አቶ አዳም በበኩላቸው ተቋማቸው በዋናነት መቀመጫውን ጀርመን ሀገር አድርጎ እንደሚሰራ ገልፀው ሀገራዊ ቋንቋዎችን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እና በኢትዮጵያ እየሰሩ ያሏቸውን ቴክኖሎጂያዊ ስራዎች አስተዋውቀዋል፡፡
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከልሳን ቴክኖሎጂ ጋራ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ፡፡ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በዋና አላማነት አንግቦ የተካሄደው የመግባብያ ስምምነቱ በሁለቱም ተቋማት ያሉ ተመራማሪዎችን በማስተባበር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤት እንደሚያስገኝም ታምኖበታል፡፡ ስምምነቱን በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በኩል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሙሉቀን ቀሬ ሲፈርሙ ልሳን ቴክኖሎጂን በመወከል ደግሞ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ አዳም ቦዶዊን ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡
ስምምነቱ ሁለቱ አካላት በማሽን ትራንስሌሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዲሁም በሁለቱም ተቋማት የሚገኙ ተመራማሪዎች፣ ሶፍትዌር መሀንዲሶች እና ሌሎች ባለሙያዎች በጋራ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ልሳን የስልጠና እንዲሁም የማሽን ትራንስሌሽን እና ኦፕቲካል ካራክተር ሪኮግኒሽን (OCR) ሲስተሞች ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ኢንስቲትዩቱም ለጋራ ምርምር የሚያስፈልግ መሰረተልማት፣ ቁሳቁስ እና አስተዳደራዊ አቅርቦቶችን የሚያከናውን ይሆናል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ ኢንስቲትዩቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በስልጠና፣ ጥናት እና ቢዝነስ መካከል ድልድይ መሆኑንና በሀገሪቱ ስትራቴጂዎች ውስጥም ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አውስተው ስምምነቱ በፍጥነት ወደ ተግባር እንዲለወጥ ያላቸውን ፍላጎት አንፀባርቀዋል፡፡ አቶ አዳም በበኩላቸው ተቋማቸው በዋናነት መቀመጫውን ጀርመን ሀገር አድርጎ እንደሚሰራ ገልፀው ሀገራዊ ቋንቋዎችን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እና በኢትዮጵያ እየሰሩ ያሏቸውን ቴክኖሎጂያዊ ስራዎች አስተዋውቀዋል፡፡
ካርቦንዳይ ኦክሳይድን በመጠቀም የአውሮፕላን ነዳጅን ማምረት ተቻለ
******************************
በእንግሊዝ የሚገኝ አንድ የምርምር ቡድን ሳውዲ አረቢያ ከሚገኝ አንድ ተቋምና ከሌሎች የምርምር ተቋማት ጋር በመሆን በዋናነት ካርቦንዳይ ኦክሳይድን በግብአትነት ተጠቅመው የአውሮፕላን ነዳጅ ማምረት የሚስችላቸው ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተነገረ፡፡ ተመራማሪዎች በከባቢ አየር ላይ ያለውን የካርቦንዳይ ኦክሳይድ መጠን ለመቀነስ በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ይህንን የተቃጠለ አየር ጥቅም ላይ ማዋል የሚቻልበትን መንገድ መፈለግ እንደ አንድ አማራጭ እየተጠቀሙት ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም መንገዶች አንዱ በተበከለ አየር ልቀት 12 በመቶ ድርሻ ያለው የአየር ትራንስፖርት ዘርፍ መሆኑ ታውቋል፡፡
በአቪየሽን ኢንዱስትሪው የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የሚደረገው ሙከራ ክብደት ያላቸውን ባትሪዎች በአውሮፕላኖች ላይ መግጠም ለአደጋ ሊያጋልጥ የሚችል በመሆኑ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ በዚህኛው ምርምር ግን ተመራማሪዎች ካርቦን አልባ የሆነ ነዳጅን ማምረት የሚያስችል ኬሚካዊ ሂደት ማበልጸጋቸው ተሰምቷል፡፡
በሂደቱም ተመራማሪዎቹ በአየር ላይ ያለን ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ወደ አውሮፕላን ነዳጅና ሌሎች ምርቶች ለመቀየር የሚያስችል ኦርጋኒክ ኮምባስሽን የሚባል መንገድን ተጠቅመዋል፡፡ እንደ መረጃ ምንጫችን ከሆነ ፖታሺየምና ማንጋኔዝ ያሉበት የብረት ውህድ፣ ሀይድሮጅን፣ ሲትሪክ አሲድ እና ካርቦንዳይ ኦክሳይድን በ350 ዲግሪ ሙቀት በማንደድ በ CO2 ውስጥ የሚገኝ ካርቦን ተለይቶ ከሀይድሮጅን ጋር እንዲጣመር ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም ፈሳሽ የአውሮፕላን ነዳጅ የያዘ ሀይድሮ ካርቦን ሞሎኪዩል ማግኘት ችለዋል፡፡ በተጨማሪም ውሃና ሌሎች ምርቶች ተገኝተዋል፡፡
በሙከራው ወቅት ጥቅም ላይ ከዋለው ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ውስጥ 38 በመቶው ወደ አውሮፕላን ነዳጅነትና ወደ ሌሎች ምርቶች የተለወጠ ሲሆን ከአጠቃላይ ምርቱም የአውሮፕላን ነዳጁ 48 በመቶውን የሚይዝ ነው፡፡ ቀሪው 52 በመቶ ደግሞ ውሃ፣ ፐሮፕሌን እና ኢታሊንን የያዘ ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ የተጠቀሙት መንገድ የአውሮፕላን ነዳጅን ለማምረት ከሚያስችሉ ሌሎች መንገዶች በተሸለ አነስተኛ ወጭ የሚያስወጣ እንደሆነና በአሁኑ ወቅት ከፍኛውን የካርቦንዳይ ኦክሳይድ መጠን የሚለቁ ግዙፍ ፋብሪካዎችም መንገዱን ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
******************************
በእንግሊዝ የሚገኝ አንድ የምርምር ቡድን ሳውዲ አረቢያ ከሚገኝ አንድ ተቋምና ከሌሎች የምርምር ተቋማት ጋር በመሆን በዋናነት ካርቦንዳይ ኦክሳይድን በግብአትነት ተጠቅመው የአውሮፕላን ነዳጅ ማምረት የሚስችላቸው ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተነገረ፡፡ ተመራማሪዎች በከባቢ አየር ላይ ያለውን የካርቦንዳይ ኦክሳይድ መጠን ለመቀነስ በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ይህንን የተቃጠለ አየር ጥቅም ላይ ማዋል የሚቻልበትን መንገድ መፈለግ እንደ አንድ አማራጭ እየተጠቀሙት ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም መንገዶች አንዱ በተበከለ አየር ልቀት 12 በመቶ ድርሻ ያለው የአየር ትራንስፖርት ዘርፍ መሆኑ ታውቋል፡፡
በአቪየሽን ኢንዱስትሪው የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የሚደረገው ሙከራ ክብደት ያላቸውን ባትሪዎች በአውሮፕላኖች ላይ መግጠም ለአደጋ ሊያጋልጥ የሚችል በመሆኑ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ በዚህኛው ምርምር ግን ተመራማሪዎች ካርቦን አልባ የሆነ ነዳጅን ማምረት የሚያስችል ኬሚካዊ ሂደት ማበልጸጋቸው ተሰምቷል፡፡
በሂደቱም ተመራማሪዎቹ በአየር ላይ ያለን ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ወደ አውሮፕላን ነዳጅና ሌሎች ምርቶች ለመቀየር የሚያስችል ኦርጋኒክ ኮምባስሽን የሚባል መንገድን ተጠቅመዋል፡፡ እንደ መረጃ ምንጫችን ከሆነ ፖታሺየምና ማንጋኔዝ ያሉበት የብረት ውህድ፣ ሀይድሮጅን፣ ሲትሪክ አሲድ እና ካርቦንዳይ ኦክሳይድን በ350 ዲግሪ ሙቀት በማንደድ በ CO2 ውስጥ የሚገኝ ካርቦን ተለይቶ ከሀይድሮጅን ጋር እንዲጣመር ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም ፈሳሽ የአውሮፕላን ነዳጅ የያዘ ሀይድሮ ካርቦን ሞሎኪዩል ማግኘት ችለዋል፡፡ በተጨማሪም ውሃና ሌሎች ምርቶች ተገኝተዋል፡፡
በሙከራው ወቅት ጥቅም ላይ ከዋለው ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ውስጥ 38 በመቶው ወደ አውሮፕላን ነዳጅነትና ወደ ሌሎች ምርቶች የተለወጠ ሲሆን ከአጠቃላይ ምርቱም የአውሮፕላን ነዳጁ 48 በመቶውን የሚይዝ ነው፡፡ ቀሪው 52 በመቶ ደግሞ ውሃ፣ ፐሮፕሌን እና ኢታሊንን የያዘ ነው፡፡
ተመራማሪዎቹ የተጠቀሙት መንገድ የአውሮፕላን ነዳጅን ለማምረት ከሚያስችሉ ሌሎች መንገዶች በተሸለ አነስተኛ ወጭ የሚያስወጣ እንደሆነና በአሁኑ ወቅት ከፍኛውን የካርቦንዳይ ኦክሳይድ መጠን የሚለቁ ግዙፍ ፋብሪካዎችም መንገዱን ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
የመጀመሪያው አርተፊሻል ልብ በአውሮፓ ለገበያ እንዲውል ፈቃድ አገኘ
****************************
በአውሮፓ የዘርፉ ተቆጣጣሪዎች የመጀመሪያ የሆነውን ሰው ሰራሽ ልብ ለገበያ እንዲውል ፈቃድ መስጠታቸው ተሰምቷል፡፡ ለሀያ ሰባት አመታት ያክል ሲለፋበት የነበረውና ስኬት አግኝቶ ከሰባት አመታት በፊት ፈቃድ የተሰጠው ሰው ሰራሽ ልብ ለአምራቹ ኬርሜት ትልቅ ተስፋን ሰጥቷል፡፡ ኬርሜት በዘርፉ ስቶክ ገበያ ውስጥ 66 በመቶ ድርሻ ያለው ሲሆን ይህም የገበያ ዋጋውን 407 ሚሊዮን ይሮ አድርሶለታል፡፡
ድጅቱ በያዝነው ሳምንት ምርቱን በአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ውስጥ መሸጥ የሚያስችለውን ፈቃድ ማግኘቱን የዘገበው ብሉምበርግ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ይህም በልብ በሽታ እየተሰቃዩ ላሉ ህሙማን የልብ ንቅለ ተከላ ማድረግ የሚያስችላቸውን እድል ይፈጥርላቸዋል ተብሏል፡፡
ሰርጅንና የልብ ቱቦ (heart-valve) ፈጠራ ባለቤት ያደረጉት ስምምነት በፈረንሳይ ሰው ሰራሽ ልብ የሚመረትበትን መንገድ በ1993 ከፍቷል፡፡ የድርጅቱንም ድርሻ ኬርሜትና ኬርፔንቴር የተባሉ ባለቤቶች ይዘውታል፡፡ በመሆኑም የሽያጭ ፈቃዱን በማግኘቱ ኬርሜት የፊታችን ጥር የምርት ሂደቱን እንደሚጀምር አሳውቋል፡፡
ይህ አርቲፍሻል ልብ ተመርቶ ለገበያ ከቀረበ በኋላ ለኬርሜት ከ700 ሚሊዮን ዩሮ በላይ አመታዊ ገቢ እስከ 2030 እንደሚያስገኝለት ተገምቷል፡፡ ምርቱንም በፈረንጆቹ 2021 ሁለተኛ ሩብ አመት ለገበያ እንደሚያቀርብ ድጅቱ አሳውቋል፡፡
ምንጭ Bloomberg Technology
****************************
በአውሮፓ የዘርፉ ተቆጣጣሪዎች የመጀመሪያ የሆነውን ሰው ሰራሽ ልብ ለገበያ እንዲውል ፈቃድ መስጠታቸው ተሰምቷል፡፡ ለሀያ ሰባት አመታት ያክል ሲለፋበት የነበረውና ስኬት አግኝቶ ከሰባት አመታት በፊት ፈቃድ የተሰጠው ሰው ሰራሽ ልብ ለአምራቹ ኬርሜት ትልቅ ተስፋን ሰጥቷል፡፡ ኬርሜት በዘርፉ ስቶክ ገበያ ውስጥ 66 በመቶ ድርሻ ያለው ሲሆን ይህም የገበያ ዋጋውን 407 ሚሊዮን ይሮ አድርሶለታል፡፡
ድጅቱ በያዝነው ሳምንት ምርቱን በአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ውስጥ መሸጥ የሚያስችለውን ፈቃድ ማግኘቱን የዘገበው ብሉምበርግ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ይህም በልብ በሽታ እየተሰቃዩ ላሉ ህሙማን የልብ ንቅለ ተከላ ማድረግ የሚያስችላቸውን እድል ይፈጥርላቸዋል ተብሏል፡፡
ሰርጅንና የልብ ቱቦ (heart-valve) ፈጠራ ባለቤት ያደረጉት ስምምነት በፈረንሳይ ሰው ሰራሽ ልብ የሚመረትበትን መንገድ በ1993 ከፍቷል፡፡ የድርጅቱንም ድርሻ ኬርሜትና ኬርፔንቴር የተባሉ ባለቤቶች ይዘውታል፡፡ በመሆኑም የሽያጭ ፈቃዱን በማግኘቱ ኬርሜት የፊታችን ጥር የምርት ሂደቱን እንደሚጀምር አሳውቋል፡፡
ይህ አርቲፍሻል ልብ ተመርቶ ለገበያ ከቀረበ በኋላ ለኬርሜት ከ700 ሚሊዮን ዩሮ በላይ አመታዊ ገቢ እስከ 2030 እንደሚያስገኝለት ተገምቷል፡፡ ምርቱንም በፈረንጆቹ 2021 ሁለተኛ ሩብ አመት ለገበያ እንደሚያቀርብ ድጅቱ አሳውቋል፡፡
ምንጭ Bloomberg Technology