ወደር የለሽ ፎቶግራፎችን የምታነሳው ሳተላይት
******************
ባለው እጅግ ከፍተኛ ጥራት የተነሳ በምድራችን ያሉ አብዛኛውን ነገሮች በጥራት መመለክከት የምትችለው ሳተላይት አሁን ላይ ለሲቪሎችም አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ ካደረጋቸው ባለ ከፍተኛ ጥራት ምስሎች መካከልም ከሳምንታት በፊት በአክሱም ኤርፖርት ላይ የደረሰውን ጉዳት የሚያሳው ይህ ምስል ይገኝበታል፡፡
ካፔላ-2 የሚል ስያሜ ያላትና ሳን ፍራንሲስኮ ውስጥ በሚገኘው ካፔላ ስፔስ በተሰኘ ተቋም የተሰራችው ሳተላይቷ ሲንተቲክ አፓቸር ራዳር (SAR) የተባለውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ለውትድርና፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ኃይል እና የሕግ ማስከበር አገልግሎቶች የሚውሉ ጥንቅቅ ያሉ ምስሎችን ታቀርባለች፡፡ አሁን ላይ ማንኛውም ሰው በይነ-መረብን በመጠቀም ተመዝግቦ በሳተላይቷ አማካኝነት ከየትኛውም የምድራችን ክፍል የተወሰደ ጥርት ያለ ምስልን ማግኘት ይችላል፡፡ ቅድሚያ ግን ተመዝጋቢው ከአሜሪካን የዓለም አቀፍ የጦር መሳርያ ዝውውር ተቆጣጣሪዎች ፍቃድ ማግኘት ይኖርበታል፡፡
50 ሴ.ሜ በ50ሴ.ሜ የሆነ ስፍራን ምስል መውሰድ የምትችለው ካፔላ ይህ ቴክኖሎጂያዊ አቅሟ ከማንኛውም ሳተላይት በላቀ የጠራ ምስል መስጠት የምትችል እንድትሆን አድርጓታል፡፡ ካፔላን ከሌሎች ይህን ቴክኖሎጂም ሆነ ተለምዶአዊውን የኦፕቲካል ፎቶግራፊክ ፕሮሰሲንግ ስልት ከሚጠቀሙ ተፎካካሪዎቿ የሚለያት ሌላው ብቃቷ ደግሞ በማንኛውም የአየር ፀባይ ውስጥ እንዲሁም በቀንም ሆነ በማታ ፎቶግራፎችን ማንሳት መቻሏ ነው፡፡ በዚህ አማካኝነትም ሳተላይቷ ሰደድ እሳቶችን፣ የነዳጅ ማውጣት እንቅስቃሴዎችን፣ በአየር ንብረት ለውጥ የተጎዱ አካባቢዎችን እንዲሁም ሕገ-ወጥ አደንን የመቆጣጠር ኃይል አላት፡፡
በቀን ውስጥ በእያንዳንዱ ሰዓት ምድራችን ግማሽ ክፍሏ ፀሐያማ የተቀረው ደግሞ በምሽት ሲዋጥ በአማካኝ ግማሹ የመሬት ክፍል በደመና ውስጥ ነው የሚለው ቀድሞ በናሳ በሲስተም መሃንዲስነት ያገለገለው የአሁኑ የካፔላ ስፔስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓያም ባናዛዲ ይህ በአማካኝ 75 በመቶ የሚሆነው የምድራችንን ክፍል ጨለማ ወይም ደመናማ የያደርገዋል ሲል ይነገራል፡፡ የሰብአዊ ስራዎችን እንደ አንድ ተግባር በመጥቀስ ካፔላ-2 ምድራችንን በየትኛውም የአየር ፀባይ እና ብርሃን ሁኔታዎች ውስጥ ሳለች እንኳን አስተማማኝ መረጃ መስጠት እንደምትችል አክሎ ተናግሯል፡፡
ፓያም ይህን ሳተላይት እውን እንዲያደርግ መነሻ የሆነለት ከ6 ዓመታት በፈት በረራ ላይ እያለ ድንገት የተሰወረው የማሌዢያ አየር መንገዱ በረራ ቁጥር 370 አውሮፕላንን ለማግኘት የተደረጉ ስኬት አልባ አሰሳዎችን በመመልከትና ነገሮችን በተሻለ ለመከታተል ብሎም የምንኖርባት ምድርንም የበለጠ ለመረዳት የሚያስችል ነገር ይኖር ዘንድ ባደረበት ፍላጎት ነው፡፡ አሁን ላይ ተቋሙ በህዋ አንድ ሳተላይት ያለችው ሲሆን በቅርቡም በስፔስ ኤክስ አማካኝነት ሌላ ለመጨመር አቅዷል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ይህ የሳተላይቷ ብቃት እርሷን አስመልክቶ እጅግ ኃይለኛ ከመሆኗ የተነሳ ወደ ህንፃዎች ውስጥ ሁሉ ለማየት ትችላለች የሚል አሉባልታን አስነስቶባት ነበር፤ ፓያምም አርብ ላይ ነገሩን በቲዊተር ገፁ ላይ እንዲያስተባብል ተገዷል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
******************
ባለው እጅግ ከፍተኛ ጥራት የተነሳ በምድራችን ያሉ አብዛኛውን ነገሮች በጥራት መመለክከት የምትችለው ሳተላይት አሁን ላይ ለሲቪሎችም አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ ካደረጋቸው ባለ ከፍተኛ ጥራት ምስሎች መካከልም ከሳምንታት በፊት በአክሱም ኤርፖርት ላይ የደረሰውን ጉዳት የሚያሳው ይህ ምስል ይገኝበታል፡፡
ካፔላ-2 የሚል ስያሜ ያላትና ሳን ፍራንሲስኮ ውስጥ በሚገኘው ካፔላ ስፔስ በተሰኘ ተቋም የተሰራችው ሳተላይቷ ሲንተቲክ አፓቸር ራዳር (SAR) የተባለውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ለውትድርና፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ኃይል እና የሕግ ማስከበር አገልግሎቶች የሚውሉ ጥንቅቅ ያሉ ምስሎችን ታቀርባለች፡፡ አሁን ላይ ማንኛውም ሰው በይነ-መረብን በመጠቀም ተመዝግቦ በሳተላይቷ አማካኝነት ከየትኛውም የምድራችን ክፍል የተወሰደ ጥርት ያለ ምስልን ማግኘት ይችላል፡፡ ቅድሚያ ግን ተመዝጋቢው ከአሜሪካን የዓለም አቀፍ የጦር መሳርያ ዝውውር ተቆጣጣሪዎች ፍቃድ ማግኘት ይኖርበታል፡፡
50 ሴ.ሜ በ50ሴ.ሜ የሆነ ስፍራን ምስል መውሰድ የምትችለው ካፔላ ይህ ቴክኖሎጂያዊ አቅሟ ከማንኛውም ሳተላይት በላቀ የጠራ ምስል መስጠት የምትችል እንድትሆን አድርጓታል፡፡ ካፔላን ከሌሎች ይህን ቴክኖሎጂም ሆነ ተለምዶአዊውን የኦፕቲካል ፎቶግራፊክ ፕሮሰሲንግ ስልት ከሚጠቀሙ ተፎካካሪዎቿ የሚለያት ሌላው ብቃቷ ደግሞ በማንኛውም የአየር ፀባይ ውስጥ እንዲሁም በቀንም ሆነ በማታ ፎቶግራፎችን ማንሳት መቻሏ ነው፡፡ በዚህ አማካኝነትም ሳተላይቷ ሰደድ እሳቶችን፣ የነዳጅ ማውጣት እንቅስቃሴዎችን፣ በአየር ንብረት ለውጥ የተጎዱ አካባቢዎችን እንዲሁም ሕገ-ወጥ አደንን የመቆጣጠር ኃይል አላት፡፡
በቀን ውስጥ በእያንዳንዱ ሰዓት ምድራችን ግማሽ ክፍሏ ፀሐያማ የተቀረው ደግሞ በምሽት ሲዋጥ በአማካኝ ግማሹ የመሬት ክፍል በደመና ውስጥ ነው የሚለው ቀድሞ በናሳ በሲስተም መሃንዲስነት ያገለገለው የአሁኑ የካፔላ ስፔስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓያም ባናዛዲ ይህ በአማካኝ 75 በመቶ የሚሆነው የምድራችንን ክፍል ጨለማ ወይም ደመናማ የያደርገዋል ሲል ይነገራል፡፡ የሰብአዊ ስራዎችን እንደ አንድ ተግባር በመጥቀስ ካፔላ-2 ምድራችንን በየትኛውም የአየር ፀባይ እና ብርሃን ሁኔታዎች ውስጥ ሳለች እንኳን አስተማማኝ መረጃ መስጠት እንደምትችል አክሎ ተናግሯል፡፡
ፓያም ይህን ሳተላይት እውን እንዲያደርግ መነሻ የሆነለት ከ6 ዓመታት በፈት በረራ ላይ እያለ ድንገት የተሰወረው የማሌዢያ አየር መንገዱ በረራ ቁጥር 370 አውሮፕላንን ለማግኘት የተደረጉ ስኬት አልባ አሰሳዎችን በመመልከትና ነገሮችን በተሻለ ለመከታተል ብሎም የምንኖርባት ምድርንም የበለጠ ለመረዳት የሚያስችል ነገር ይኖር ዘንድ ባደረበት ፍላጎት ነው፡፡ አሁን ላይ ተቋሙ በህዋ አንድ ሳተላይት ያለችው ሲሆን በቅርቡም በስፔስ ኤክስ አማካኝነት ሌላ ለመጨመር አቅዷል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ይህ የሳተላይቷ ብቃት እርሷን አስመልክቶ እጅግ ኃይለኛ ከመሆኗ የተነሳ ወደ ህንፃዎች ውስጥ ሁሉ ለማየት ትችላለች የሚል አሉባልታን አስነስቶባት ነበር፤ ፓያምም አርብ ላይ ነገሩን በቲዊተር ገፁ ላይ እንዲያስተባብል ተገዷል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
ይፋ የሆነው የመሬት መንቀጥቀጥ ያለበት የውቂያኖስ ክፍል
***************************
ከዚህ በፊት ያልተለየ የውቂያኖስ ውስጥ መሬት መንቀጥቀጥ አዲስ በተሰራ ሞዴል ሊታወቅ ተችሏል፡፡ የጹኩባ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች የ2020ውን የካረቢያን የመሬት መንቀጥቀጥ ሞዴል የሲስሞ ሜትር መረጃን በመጠቀም ሰርተዋል፡፡
እስከዛሬ ድረስ ውቅያኖሳዊ የመሬት መንቀጥቀጥ እንዳለ ቢታወቅም ቀላልና ለተለያዩ ጥናቶች ግብዓት የሚውሉ እንደነበር ነው የሚታመነው፡፡ በዚህ የሞዴል ስራ ግን ተመራማሪዎቹ በጠም አስቸጋሪ የሆነና ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ሊከሰት እንደሚችል የሚያመላክት ሞዴል መስራታቸው ተሰምቷል፡፡
በጥር 28፣ 2020 የፈረንጆች አመት 7.7 የለካ የውቅያኖስ ውስጥ የመሬት መንቀጥቀጥ በጀማይካና በኩባ መካከል መከሰቱ ይታወቃል፡፡ ተመራማሪዎቹ አዲስ በተከተሉት መንገድ ከግምት ይልቅ ከጊዜና ከቦታ አንጻር የተለያዩ ምዘናዎችን አድርገዋል፡፡
ይህም ከ52 የመሬት መንቀጥቀጥ ልኬት ጣቢያዎች ያለውን መረጃ በመጠቀም ሊከሰት የሚችልን የመሬት መንቀጥቀጥ ዝርዝር መረጃ ማወቅ እንደሚያስችል ተነግሯል፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
***************************
ከዚህ በፊት ያልተለየ የውቂያኖስ ውስጥ መሬት መንቀጥቀጥ አዲስ በተሰራ ሞዴል ሊታወቅ ተችሏል፡፡ የጹኩባ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች የ2020ውን የካረቢያን የመሬት መንቀጥቀጥ ሞዴል የሲስሞ ሜትር መረጃን በመጠቀም ሰርተዋል፡፡
እስከዛሬ ድረስ ውቅያኖሳዊ የመሬት መንቀጥቀጥ እንዳለ ቢታወቅም ቀላልና ለተለያዩ ጥናቶች ግብዓት የሚውሉ እንደነበር ነው የሚታመነው፡፡ በዚህ የሞዴል ስራ ግን ተመራማሪዎቹ በጠም አስቸጋሪ የሆነና ከፍተኛ ፍጥነት ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ሊከሰት እንደሚችል የሚያመላክት ሞዴል መስራታቸው ተሰምቷል፡፡
በጥር 28፣ 2020 የፈረንጆች አመት 7.7 የለካ የውቅያኖስ ውስጥ የመሬት መንቀጥቀጥ በጀማይካና በኩባ መካከል መከሰቱ ይታወቃል፡፡ ተመራማሪዎቹ አዲስ በተከተሉት መንገድ ከግምት ይልቅ ከጊዜና ከቦታ አንጻር የተለያዩ ምዘናዎችን አድርገዋል፡፡
ይህም ከ52 የመሬት መንቀጥቀጥ ልኬት ጣቢያዎች ያለውን መረጃ በመጠቀም ሊከሰት የሚችልን የመሬት መንቀጥቀጥ ዝርዝር መረጃ ማወቅ እንደሚያስችል ተነግሯል፡፡
ምንጭ PHYS.ORG
በአዲስ መልክ ተሻሽሎ የቀረበው የመኪና ሞተር
*****************************
የቴክኖሎጂ እድገት ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት በአሁኑ ወቅት ብዙ አይነት የቴክኖሎጂ አማራጮችን ማየት የተለመደ ነው፡፡ በገበያ ከቀረቡት የቴክኖሎጂ አማራጮች መካከል አንደኛውን መርጦ ለመሸመት ሁሉም ሰው የየራሱ መመዘኛ መስፈርት ይኖረዋል፡፡ በዘመናዊው አለም አብዛኞችን የሚያስማማው ግን ጊዜን፣ ገንዘብንና ጉልበትን መቆጠብ የሚስችል እንዲሆም ለአጠቃቀም ምቹ የሆነና ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ መሆኑ ነው፡፡ የብዙዎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች አምራች ተቋማት ድካማቸውም ይህን የሰዎችን ፍላጎት በማሟላት ተፈላጊነታቸውን ማሳደግ ነው፡፡
በአዳዲስ ቴክኖሎጂ ውድድር ውስጥ ካሉ አምራቾች መካከል የመኪና መለዋወጫ አምራች ድርጅቶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የመኪና መሰረታዊ ክፍሎች የሚባሉት ጎማ፣ ሞተርና ሌሎች መለዋወጫዎች የአንድን መኪና ዘመናዊነትና ተፈላጊነት ሊያሳድጉት ይችላሉ፡፡
በተለይ በአሁኑ ወቅት አለማችን የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በምታደርገው ጥረት በካይ ያልሆኑ መኪኖች ለገበያ ማቅረብ እጅግ ትርፋማ የገበያ አማራጭ መሆኑ የማይካድ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል በኦካ ሪጅ ብሔራዊ ቤተ-ሙከራ የሚሰሩ ተመራማሪዎች ከዘመናዊ መኪኖች ጋር የተስማማ የመኪና ሞተርን በማምረት ለአለም ገበያ ለማቅረብ እየሰሩ ያሉት፡፡
ይህ ኒውትሮኒክ የመኪና ሞተር በተለይ ከፍተኛ ሙቀት ባለባቸው አካባቢዎች ሙቀትን በመቋቋም ብቁ አገልግሎግት መስጠት የሚችል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የመኪና ሞተሩ ሀይል ቆጣቢ ሲሆን ብክለትን በመቀነስ ረገድ የተዋጣለት እንደሆነ የምርምር ተቋሙ ዳይሬክተር ሮበርት ዋግነር ተናግሯል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
*****************************
የቴክኖሎጂ እድገት ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት በአሁኑ ወቅት ብዙ አይነት የቴክኖሎጂ አማራጮችን ማየት የተለመደ ነው፡፡ በገበያ ከቀረቡት የቴክኖሎጂ አማራጮች መካከል አንደኛውን መርጦ ለመሸመት ሁሉም ሰው የየራሱ መመዘኛ መስፈርት ይኖረዋል፡፡ በዘመናዊው አለም አብዛኞችን የሚያስማማው ግን ጊዜን፣ ገንዘብንና ጉልበትን መቆጠብ የሚስችል እንዲሆም ለአጠቃቀም ምቹ የሆነና ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ መሆኑ ነው፡፡ የብዙዎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች አምራች ተቋማት ድካማቸውም ይህን የሰዎችን ፍላጎት በማሟላት ተፈላጊነታቸውን ማሳደግ ነው፡፡
በአዳዲስ ቴክኖሎጂ ውድድር ውስጥ ካሉ አምራቾች መካከል የመኪና መለዋወጫ አምራች ድርጅቶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የመኪና መሰረታዊ ክፍሎች የሚባሉት ጎማ፣ ሞተርና ሌሎች መለዋወጫዎች የአንድን መኪና ዘመናዊነትና ተፈላጊነት ሊያሳድጉት ይችላሉ፡፡
በተለይ በአሁኑ ወቅት አለማችን የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም በምታደርገው ጥረት በካይ ያልሆኑ መኪኖች ለገበያ ማቅረብ እጅግ ትርፋማ የገበያ አማራጭ መሆኑ የማይካድ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል በኦካ ሪጅ ብሔራዊ ቤተ-ሙከራ የሚሰሩ ተመራማሪዎች ከዘመናዊ መኪኖች ጋር የተስማማ የመኪና ሞተርን በማምረት ለአለም ገበያ ለማቅረብ እየሰሩ ያሉት፡፡
ይህ ኒውትሮኒክ የመኪና ሞተር በተለይ ከፍተኛ ሙቀት ባለባቸው አካባቢዎች ሙቀትን በመቋቋም ብቁ አገልግሎግት መስጠት የሚችል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የመኪና ሞተሩ ሀይል ቆጣቢ ሲሆን ብክለትን በመቀነስ ረገድ የተዋጣለት እንደሆነ የምርምር ተቋሙ ዳይሬክተር ሮበርት ዋግነር ተናግሯል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
እርግዝናና የኮቪድ 19 ክትባት
***************
ምንም እንኳን የሚያጠቡና ነብሰጡር ሴቶች በክትባቱ ሙከራ ጊዜ ባይሳተፉም የመረጃ ምንጫችን ላይቭ ሳይንስ ከሙያተኞች አገኘሁት ያለው መረጃ መድሀኒቱ በሚያጠቡ እናቶችና በነብሰጡሮች ላይ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ሲል ዘግቧል፡፡ በጉዳዩ ላይ መረጃ የሰጡትን ዶክተር ስቴፋኔ ጋው ጠቅሶ የዘገበው የመረጃ ምንጫችን በጉዳዩ ያለው ትልቁ ጉዳት ሳይንሳዊ የሆነ መረጃ አለመኖሩ ነው ሲል አስነብቧል፡፡ ለዚህም እስካሁን እውቅና በተሰጣቸው ሁለቱ የፊዘርና የሞደርና መድሀኒቶች በሰውነት ውስጥ የሚሰባበርና የሚሰራጭ ኢንፌክሽን የማያስከትል mRNA የተሰኘ ሞሎኪዩል የያዙ መሆናቸውን ዶክተሯ ተናግረዋል፡፡
በጥቅሉ ሲታይ ለነብሰጡሮች የሚሰጡ መድሀኒቶች በሙከራ ወቅት መደበኛ የሆነ ክሊኒካዊ ሙካራ በነብሰጡሮች የማይደረግባቸው መሆኑን በ2014 የወጣ የአለም ጤና ድጅት መረጃ ያመለክታል፡፡ ይሁን እንጂ መረጃዎች ቀጥታ ባልሆነ መንገድ በእንስሳትና በሌሎች ምልከታዎች ተሰብስበው የትርፍና ኪሳራ ስሌት እንደሚሰራ ይነገራል፡፡
ተመራማሪዎች እደሚሉት ከሆነ እርግዝና በኮቪድ 19 ምክንያት በጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ የመቆየት እድልን ከፍ ያደርጋል፡፡ በዚህም የሚያጠቡ እናቶችና ነብሰጡሮች መድሀኒቱን ከመውሰዳቸው በፊት ከጤና ግልጋሎት ሰጭዎች ጋር በእርግዝና ወይም በማጥባት ወቅት መድሀኒቱን መውሰድ ባለው ጥቅምና ጉዳት ዙሪያ መነጋገር እንዳለባቸውና መድሀኒቱን በመውሰድና ተጨማሪ መረጃ እስከሚገኝ በመጠበቅ ዙሪያ መወሰን ይኖርባቸዋል ተብሏል፡፡ ዶክተሯ አክለውም የተጋላጭነት መጠናቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ከመጠበቅ ይልቅ ፈጥነው መድሀኒቱን ቢወስዱ እንደሚሻል ተናግረዋል፡፡
የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ማእከል (CDC) መድሀኒቱን የወሰዱ የሚያጠቡና ነብሰጡር ሴቶችን ለይቶ ክትትል እያደረገ መሆኑን የዘገበው የመረጃ ምንጫችን በቀጣዩ ወር በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ እንደሚኖር አመልክቷል፡፡ መረጃውንም የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ማእከል (CDC) እና የምግብና መድሀኒት አስተዳደር (FDA) አሁን ላይ ያሉ የመረጃ መሰብሰቢያ መንገዶችን በመጠቀም እንደሚሰበስቡ ተነግሯል፡፡
ባጠቃላይ ለላይቭ ሳይንስ መረጃ የሰጡት ዶክተር በአብዛኛው ጥቅም ላይ የዋሉ ክትባቶች በእርግዝና ላይ የከፋ ጉዳት የማያደርሱ መሆናቸውን ቢናገሩም ስሞልፎክስ፣ MMR የተሰኙ ደካማ የሆኑ ቫይረሶችን የተሸከሙ ክትባቶች ለነብሰጡሮችና ለአጥቢዎች የማይሰጡ መሆናቸው መዘንጋት እንደሌለበት አሳስበዋል፡፡
እንደ ምክረ ሀሳብ ዶክተሯ አጥቢና ነብሰጡር እናቶች ሌሎች ሰዎች ከሚወስዱት መጠን ያነሰ ክትባት ቢወስዱ የተሻለ መሆኑን ሲገልጹ አስተማማኝ የሚሆነው ግን ተገቢ የሆነ ክሊኒካዊ ሙከራ መደረጉ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Live science
***************
ምንም እንኳን የሚያጠቡና ነብሰጡር ሴቶች በክትባቱ ሙከራ ጊዜ ባይሳተፉም የመረጃ ምንጫችን ላይቭ ሳይንስ ከሙያተኞች አገኘሁት ያለው መረጃ መድሀኒቱ በሚያጠቡ እናቶችና በነብሰጡሮች ላይ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ሲል ዘግቧል፡፡ በጉዳዩ ላይ መረጃ የሰጡትን ዶክተር ስቴፋኔ ጋው ጠቅሶ የዘገበው የመረጃ ምንጫችን በጉዳዩ ያለው ትልቁ ጉዳት ሳይንሳዊ የሆነ መረጃ አለመኖሩ ነው ሲል አስነብቧል፡፡ ለዚህም እስካሁን እውቅና በተሰጣቸው ሁለቱ የፊዘርና የሞደርና መድሀኒቶች በሰውነት ውስጥ የሚሰባበርና የሚሰራጭ ኢንፌክሽን የማያስከትል mRNA የተሰኘ ሞሎኪዩል የያዙ መሆናቸውን ዶክተሯ ተናግረዋል፡፡
በጥቅሉ ሲታይ ለነብሰጡሮች የሚሰጡ መድሀኒቶች በሙከራ ወቅት መደበኛ የሆነ ክሊኒካዊ ሙካራ በነብሰጡሮች የማይደረግባቸው መሆኑን በ2014 የወጣ የአለም ጤና ድጅት መረጃ ያመለክታል፡፡ ይሁን እንጂ መረጃዎች ቀጥታ ባልሆነ መንገድ በእንስሳትና በሌሎች ምልከታዎች ተሰብስበው የትርፍና ኪሳራ ስሌት እንደሚሰራ ይነገራል፡፡
ተመራማሪዎች እደሚሉት ከሆነ እርግዝና በኮቪድ 19 ምክንያት በጽኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ የመቆየት እድልን ከፍ ያደርጋል፡፡ በዚህም የሚያጠቡ እናቶችና ነብሰጡሮች መድሀኒቱን ከመውሰዳቸው በፊት ከጤና ግልጋሎት ሰጭዎች ጋር በእርግዝና ወይም በማጥባት ወቅት መድሀኒቱን መውሰድ ባለው ጥቅምና ጉዳት ዙሪያ መነጋገር እንዳለባቸውና መድሀኒቱን በመውሰድና ተጨማሪ መረጃ እስከሚገኝ በመጠበቅ ዙሪያ መወሰን ይኖርባቸዋል ተብሏል፡፡ ዶክተሯ አክለውም የተጋላጭነት መጠናቸው ከፍ ያሉ ሰዎች ከመጠበቅ ይልቅ ፈጥነው መድሀኒቱን ቢወስዱ እንደሚሻል ተናግረዋል፡፡
የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ማእከል (CDC) መድሀኒቱን የወሰዱ የሚያጠቡና ነብሰጡር ሴቶችን ለይቶ ክትትል እያደረገ መሆኑን የዘገበው የመረጃ ምንጫችን በቀጣዩ ወር በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ እንደሚኖር አመልክቷል፡፡ መረጃውንም የበሽታ መቆጣጠርና መከላከል ማእከል (CDC) እና የምግብና መድሀኒት አስተዳደር (FDA) አሁን ላይ ያሉ የመረጃ መሰብሰቢያ መንገዶችን በመጠቀም እንደሚሰበስቡ ተነግሯል፡፡
ባጠቃላይ ለላይቭ ሳይንስ መረጃ የሰጡት ዶክተር በአብዛኛው ጥቅም ላይ የዋሉ ክትባቶች በእርግዝና ላይ የከፋ ጉዳት የማያደርሱ መሆናቸውን ቢናገሩም ስሞልፎክስ፣ MMR የተሰኙ ደካማ የሆኑ ቫይረሶችን የተሸከሙ ክትባቶች ለነብሰጡሮችና ለአጥቢዎች የማይሰጡ መሆናቸው መዘንጋት እንደሌለበት አሳስበዋል፡፡
እንደ ምክረ ሀሳብ ዶክተሯ አጥቢና ነብሰጡር እናቶች ሌሎች ሰዎች ከሚወስዱት መጠን ያነሰ ክትባት ቢወስዱ የተሻለ መሆኑን ሲገልጹ አስተማማኝ የሚሆነው ግን ተገቢ የሆነ ክሊኒካዊ ሙከራ መደረጉ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Live science
ስንጥቃቸውን በራሳቸው ማደስ የሚችሉ የስማርት ስልክ ስክሪን ሽፋኖች
************************************
በአሁኑ ወቅት የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች ከሚቸገሩባቸው ነገሮች መካከል ስልካቸው በወደቀ ቁጥር የስክሪኑ ሽፋን መስታወት በቀላሉ መሰነጣጠቁ ነው፡፡ አለፍ ሲልም ከአነስተኛ እስከ ከፍ ያለ ዋጋ የሚጠይቅ የጥገና ወጭ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ምስጋና ይግባቸውና የዘርፉ ተመራማሪዎች ጊዜቸውን ራሳቸውን የሚያድሱ የስማርት ስልክ ስክሪን ሽፋኖችን ለመስራት እያዋሉ እንደሆነና ጥቅም ላይ ለማዋልም እንደተቃረቡ ተናግረዋል፡፡
በኮሪያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የምርምር ተቋም የሚገኝ አንድ የምርምር ቡድን የራሱን ስንጥቅና ሌላ አካላዊ ጉዳት መጠገን የሚችል ምስጢራዊ የሆነ ዘይትን በግብዓትነት በውስጡ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቁስ ማበልጸጉን የዘገበው ሳይንስ አለርት ነው፡፡
ይህ ልዩ ዘይት ፍላክስ ከሚባል ቃጫ መሰል ተክል ዘሮች የሚዘጋጅ ሲሆን ተመራማሪዎች ለስራቸው አመቺ የሚሆን ቀለም አልባ ግብዓትን ለማግኘት የሚያስችል የማላመድ ስራን ሰርተውበታል፡፡ ይህ ዘይት ጉዳት የደረሰበትን የስክሪኑን ሽፋን ክፍል ሰርስሮ በመግባት ስንጥቁን ወይም ስብራቱን ማስተካከል እንዲችል የታለመ ነው፡፡ ይህ ጥናት ሙሉ ለሙሉ ሲሳካ ስብራታቸውን የሚጠግኑ የስልክ ስክሪን ሽፋኖች ኖሩንና በየጊዜው የተሰነጣጠቀ ስልክ ከመያዝ ይገላግሉናል ሲል የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡
የዚህ ቴክኖሎጂ ጥቅም የተሰበረ የስልክ ስክሪን ሽፋንን ከመጠገን ባለፈ ሌሎች ቀለም አልባ ፖሊማይድ (CPI) የሚጠቀሙ እንደ የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ ንጣፎችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በቀላሉ መጠገን እንደሚያስችል ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Sciencealart
************************************
በአሁኑ ወቅት የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች ከሚቸገሩባቸው ነገሮች መካከል ስልካቸው በወደቀ ቁጥር የስክሪኑ ሽፋን መስታወት በቀላሉ መሰነጣጠቁ ነው፡፡ አለፍ ሲልም ከአነስተኛ እስከ ከፍ ያለ ዋጋ የሚጠይቅ የጥገና ወጭ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ምስጋና ይግባቸውና የዘርፉ ተመራማሪዎች ጊዜቸውን ራሳቸውን የሚያድሱ የስማርት ስልክ ስክሪን ሽፋኖችን ለመስራት እያዋሉ እንደሆነና ጥቅም ላይ ለማዋልም እንደተቃረቡ ተናግረዋል፡፡
በኮሪያ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የምርምር ተቋም የሚገኝ አንድ የምርምር ቡድን የራሱን ስንጥቅና ሌላ አካላዊ ጉዳት መጠገን የሚችል ምስጢራዊ የሆነ ዘይትን በግብዓትነት በውስጡ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቁስ ማበልጸጉን የዘገበው ሳይንስ አለርት ነው፡፡
ይህ ልዩ ዘይት ፍላክስ ከሚባል ቃጫ መሰል ተክል ዘሮች የሚዘጋጅ ሲሆን ተመራማሪዎች ለስራቸው አመቺ የሚሆን ቀለም አልባ ግብዓትን ለማግኘት የሚያስችል የማላመድ ስራን ሰርተውበታል፡፡ ይህ ዘይት ጉዳት የደረሰበትን የስክሪኑን ሽፋን ክፍል ሰርስሮ በመግባት ስንጥቁን ወይም ስብራቱን ማስተካከል እንዲችል የታለመ ነው፡፡ ይህ ጥናት ሙሉ ለሙሉ ሲሳካ ስብራታቸውን የሚጠግኑ የስልክ ስክሪን ሽፋኖች ኖሩንና በየጊዜው የተሰነጣጠቀ ስልክ ከመያዝ ይገላግሉናል ሲል የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡
የዚህ ቴክኖሎጂ ጥቅም የተሰበረ የስልክ ስክሪን ሽፋንን ከመጠገን ባለፈ ሌሎች ቀለም አልባ ፖሊማይድ (CPI) የሚጠቀሙ እንደ የጸሐይ ሀይል መሰብሰቢያ ንጣፎችና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በቀላሉ መጠገን እንደሚያስችል ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ Sciencealart
ከ21 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣው አዲሱ የአፕል ኤርፖድ
============================
ስመ ጥሩ የቴክኖሎጂ ኩባንያ አፕል እስከ 21,740 ብር ወይም 549 ዶላር ድረስ (በአሜሪካን የሚሸጡበት ብቻ) ዋጋ የተመነላቸው የድምፅ ማዳመጫ ኤርፖዶቹን በቅርቡ ይፋ አድርጓል፡፡ ኤርፖዱ ከብረት እና አልሙኒየም የተሰራ ሲሆን እንደየ ደረጃው ከ130 እስከ 385 ግራም ክብደት አለው፡፡ ዋናው ክብደት ጆሮ ላይ በሚለጠፉት የኤርፖዱ ክፍሎች (Ear Cups) ላይ በመሆኑም ጭንቅላት በሚነቃነቅበት ወቅት ብዙም ቦታቸውን ሳይለለቁ እንዲቆዩ ያደርጋቸዋል፡፡
ኤርፖዶቹ ከውጭ ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴከኖሎጂ (Noise-Cancelling) የተገጠመላቸው ሲሆኑ በአንድ ቻርጅ ብቻ እስከ 20 ሰዓት ያክል አገልግሎት እየሰጡ መቆየት እንደሚችሉ አፕል ተናግሯል፡፡ ኤርፖዶቹ የአፕል ኤች1 ቺፕ የተገጠመለት በመሆኑም ብሉቱዝ 5.0 ያላቸውና የተለያዩ የኦዲዮ አይነቶችንም ማጫወት የሚችሉ አድርጓቸዋል፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ተዕዛዝ መቀበል እንዲሁም አጭር የፅሁፍ መልዕክቶችን እንደገቡ ማንበብ የሚችል ነው፡፡ ኤርፖዱ ከአፕል ውጪም ከሌሎች ምርቶች ጋራ መገናኘት የሚችል ቢሆንም አንዳንድ ገፅታዎቹ ግን ከአፕል ምርቶች ጋር ሲሆኑ ብቻ ይሆናል የሚሰሩት፡፡
ኤርፖዶቹ ያላቸው ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴክኖሎጂ ማይክሮፎኖችን በመጠቀም ያልተፈለጉ ድምፆች ሁሉ ከጆሮ እንዳይደርሱ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እንበልና ኤርፖዱን ያደረገ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲራመድ በዙርያው ያሉ የመንገድ ዳር እና ሌሎች ረባሽ ድምፆች ምንም እንዳልተፈጠሩ ሁሉ ሳይሰማቸው ሙዚቃውን ማጣጣም ይችላል ማለት ነው፡፡ ሆኖም ይህ ሰው በዙርያው የመኪና እና ሌሎች ድምፆችን እየሰማ እራሱን ጠብቆ ለመጓዝ ካሻው ትራንስፓረንት ሞድ ላይ በማድረግ ኤርፖዱን ያላደረገ እስኪመስለው ድረስ የውጭ ድምፅ እንዲገባ ማድረግ ያስችለዋል፡፡
የባትሪያቸውን ቆይታ ያየን እንደሆን ድምፅ እንዳይገባ ማድረጊያው በርቶ እስከ 20 ሰዓት ድረስ አገልግሎት መሰጠት የሚችሉ ሲሆን ይህ ጠፍቶ ግን ከዚያ ለበለጠ ጊዜም ግልጋሎት መስጠት የሚችል ነው፡፡ ይህ ከቦስ ኤርፖዶች ጋራ ተመሳሳይ ቢሆንም ከB&W አቻዎቹ አንፃር ግን በ10 ሰዓት ያነሰ ያደርጋቸዋል፡፡ የ5 ዋት እና ከዚያ በላይ የሆነ የዩኤስቢ ቻርጀር በመጠቀምም ኤርፖዱን ሙሉ ለሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ሁለት ሰዓታት መጠበቅ ግድ የሚል ቢሆንም ለ5 ደቂቃ ብቻ ቻርጅ አድርጎ ለ90 ደቂቃ ሙዚቃ ማጫወት የሚያስችለውን ኃይል ማግኘት ይችላል፡፡
ኤርፖዶቹ ባላቸው የድምፅ ጥራት፣ ቴክኖሎጂ እና ቅንጦት ብዙ ሰዎችን መሳብ የቻሉ ቢሆንም ዋጋቸው ግን እጅጉን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ከአንዳንድ የቅርብ ተፎካካሪ የሆኑ ተመሳሳይ ምርቶች አንፃር እንኳን 200 ዶላር እና ከዚያ የዋጋ ልዩነት አላቸው፡፡ በተጨማሪም ከአሜሪካ ውጪ ሲሸጡ ዋጋቸው ከዚህም በላይ እየጨመረ ይሄዳል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
============================
ስመ ጥሩ የቴክኖሎጂ ኩባንያ አፕል እስከ 21,740 ብር ወይም 549 ዶላር ድረስ (በአሜሪካን የሚሸጡበት ብቻ) ዋጋ የተመነላቸው የድምፅ ማዳመጫ ኤርፖዶቹን በቅርቡ ይፋ አድርጓል፡፡ ኤርፖዱ ከብረት እና አልሙኒየም የተሰራ ሲሆን እንደየ ደረጃው ከ130 እስከ 385 ግራም ክብደት አለው፡፡ ዋናው ክብደት ጆሮ ላይ በሚለጠፉት የኤርፖዱ ክፍሎች (Ear Cups) ላይ በመሆኑም ጭንቅላት በሚነቃነቅበት ወቅት ብዙም ቦታቸውን ሳይለለቁ እንዲቆዩ ያደርጋቸዋል፡፡
ኤርፖዶቹ ከውጭ ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴከኖሎጂ (Noise-Cancelling) የተገጠመላቸው ሲሆኑ በአንድ ቻርጅ ብቻ እስከ 20 ሰዓት ያክል አገልግሎት እየሰጡ መቆየት እንደሚችሉ አፕል ተናግሯል፡፡ ኤርፖዶቹ የአፕል ኤች1 ቺፕ የተገጠመለት በመሆኑም ብሉቱዝ 5.0 ያላቸውና የተለያዩ የኦዲዮ አይነቶችንም ማጫወት የሚችሉ አድርጓቸዋል፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ተዕዛዝ መቀበል እንዲሁም አጭር የፅሁፍ መልዕክቶችን እንደገቡ ማንበብ የሚችል ነው፡፡ ኤርፖዱ ከአፕል ውጪም ከሌሎች ምርቶች ጋራ መገናኘት የሚችል ቢሆንም አንዳንድ ገፅታዎቹ ግን ከአፕል ምርቶች ጋር ሲሆኑ ብቻ ይሆናል የሚሰሩት፡፡
ኤርፖዶቹ ያላቸው ድምፅ እንዳይገባ የማድረጊያ ቴክኖሎጂ ማይክሮፎኖችን በመጠቀም ያልተፈለጉ ድምፆች ሁሉ ከጆሮ እንዳይደርሱ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እንበልና ኤርፖዱን ያደረገ አንድ ሰው በመንገድ ላይ ሲራመድ በዙርያው ያሉ የመንገድ ዳር እና ሌሎች ረባሽ ድምፆች ምንም እንዳልተፈጠሩ ሁሉ ሳይሰማቸው ሙዚቃውን ማጣጣም ይችላል ማለት ነው፡፡ ሆኖም ይህ ሰው በዙርያው የመኪና እና ሌሎች ድምፆችን እየሰማ እራሱን ጠብቆ ለመጓዝ ካሻው ትራንስፓረንት ሞድ ላይ በማድረግ ኤርፖዱን ያላደረገ እስኪመስለው ድረስ የውጭ ድምፅ እንዲገባ ማድረግ ያስችለዋል፡፡
የባትሪያቸውን ቆይታ ያየን እንደሆን ድምፅ እንዳይገባ ማድረጊያው በርቶ እስከ 20 ሰዓት ድረስ አገልግሎት መሰጠት የሚችሉ ሲሆን ይህ ጠፍቶ ግን ከዚያ ለበለጠ ጊዜም ግልጋሎት መስጠት የሚችል ነው፡፡ ይህ ከቦስ ኤርፖዶች ጋራ ተመሳሳይ ቢሆንም ከB&W አቻዎቹ አንፃር ግን በ10 ሰዓት ያነሰ ያደርጋቸዋል፡፡ የ5 ዋት እና ከዚያ በላይ የሆነ የዩኤስቢ ቻርጀር በመጠቀምም ኤርፖዱን ሙሉ ለሙሉ ቻርጅ ለማድረግ ሁለት ሰዓታት መጠበቅ ግድ የሚል ቢሆንም ለ5 ደቂቃ ብቻ ቻርጅ አድርጎ ለ90 ደቂቃ ሙዚቃ ማጫወት የሚያስችለውን ኃይል ማግኘት ይችላል፡፡
ኤርፖዶቹ ባላቸው የድምፅ ጥራት፣ ቴክኖሎጂ እና ቅንጦት ብዙ ሰዎችን መሳብ የቻሉ ቢሆንም ዋጋቸው ግን እጅጉን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ከአንዳንድ የቅርብ ተፎካካሪ የሆኑ ተመሳሳይ ምርቶች አንፃር እንኳን 200 ዶላር እና ከዚያ የዋጋ ልዩነት አላቸው፡፡ በተጨማሪም ከአሜሪካ ውጪ ሲሸጡ ዋጋቸው ከዚህም በላይ እየጨመረ ይሄዳል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian
ከሌላው ዓለም ፍጡራን የተላከ ሊሆን ይችላል የተባለለት አዲስ የራዲዮ ሞገድ
=========================
የሌላ ዓለም ፍጡራንን ፍለጋ ውስጥ በቀዳሚነት በሚቀመጠው ፕሮጀክት ስር የሚሰሩት ተመራማሪዎች ለፀሐይ በቅርብ ርቀት ከምትገኘውና ከምድር የ4.2 ብርሃን ዓመት ርቀት ካላት ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ኮከብ አቅጣጫ የመጡ የሚመስሉ አጠራጣሪ የሬዲዮ ሞገዶችን እየመረመሩ ናቸው፡፡ የሬዲዮ ሞገዶቹ አውስትራሊያ ውስጥ ባለው የፓርከስ ቴሌስኮፕ አማካኝነት ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ሚያዝያ እና ግንቦት ወራት ላይ ነው የተገኙት፡፡ ሲግናሉ ከተላከበት ጊዜ አንስቶ በተመራማሪዎቹ ትንተና እየተደረገበት ሲሆን ዝርዝሩ እስካሁን ለህዝብ ይፋ አልተደረገም፡፡
ተመራማሪዎቹ ምዕራብ ቨርጂኒያ ውስጥ ባለው ቴሌስኮፕ አማካኝነት መሰል የራዲዮ ዌቮችን መስማታቸው የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም እነዚህ ሞገዶች የሰው ልጆች ተፅዕንዖን ተከትለው የተገኙ ሲሆን ይህን ግን ለየት የሚያደርገው 980 ሜጋ ኸርዝ በሆነው የሬዲዮ ሞገዱ ባንዶች ውስጥ ሰው ሰራሽ የሆኑ ሳተላይትም ሆነ ቁስ ሲግናል አልተገኘበትም፡፡
ሲግናሉ በአውሮፓውያኑ 1977 ከተገኘውና “ዋው ሲግናል” ተብሎ ከሚታወቀው በኋላ በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ሲግናል እንደሆነም በባለሙያዎች ዘንድ ተነግሮለታል፡፡ ሲግናሉን የመተንተኑን ስራ ስትመራ የቆየችው ሶፊያ ሼክ በፕሮጀክታቸው ውስጥ እስከዛሬ ከተሰሙት ሁሉ አጓጊው ሲግናል መሆኑን ትናገራለች፡፡ ሲግናሉንም ብሬክስሩ ሊስን ካንዲዴት 1 (BLC1) ብለውታል፡፡
በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ውስጥ ከሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መካከል አንዱ ከእነዚህ ፍጡራን ጋራ የመገናኛው/መግባብያው መንገድ አለመታወቁ ነው፡፡ በተጨማሪም በዩኒቨርስ ውስጥ የሚፈጠሩ የሬዲዮ ሞገዶች ምንጭ ሊሆኑ የሚችሉት ተፈጥሮአዊ መነሻዎችም ቢሆን ሙሉ በሙሉ አይታወቁም፡፡ ስለዚህም ብዙውን እንደዚህ አይነት ሲግናሎች ሲገኙ ቴክኖሎጂ አፈራሽ እንደሆኑ ግምት የሚወሰድና ከተፈጥሮአዊ ምንጭ መሆናቸውን የሚያስረዳ ማብራርያንም በቀላሉ የማይገኝባቸው ሲሆን ነገሩን ወደ ሌላኛው ዓለም ፍጡራን መውሰዱ ግን ትኩረት ሳቢ ነው፡፡ ስለ ሲግናሉ የሚገልፅ መረጃ ለህዝብ ይፋ ያልተደረገ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ወደፊት ይፋ ቢሆን እንኳን ልክ እንደ ዋው ሲግናል ሁሉ በማስረጃ የዋጀ ድምዳሜ ላይ የሚደረስበት አይመስልም፡፡
ከማንኛውም ኮከብ በላይ ለምድር በምትቀርበው ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ውስጥ ቢያንስ ሁለት የሚዞሯት ፕላኔቶች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ አንደኛው በጋዝ የተሞላ ሲሆን ሌላኛው ግን ባለው ለውሃ ፍሰት የተስማማ ሙቀት ሳብያ ሰውን ሊያኖሩ ይችላሉ ተብለው ግምት ከሚወሰድባቸው ፕላኔቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ይህች ፕላኔት ከምድር በ17 በመቶ የግዝፈት ብልጫ ያላት ድንጋያማ ስፍራ ናት፡፡ ፕሮክሲማ ቢ በሚል ስያሜ የምትታወቀው ፕላኔቷ በየ 11 ቀናቱ ኮከቧን የምትዞር ናት፡፡ ሆኖም ለሰው ልጆች ኑሮ አደገኛ ልትሆንም እንደምትችል ይነገራል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት የናሳ ተመራማሪዎች የኮምፒውተር ሞዴልን ተጠቅመው ፕላኔቷ በቀላሉ ለከባድ ጨረር እና ድንገተኛ የኮከብ ብርሃን ነበልባል የተጋለጠች ልትሆን እንደምትችል አሳይተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian እና Live Science
=========================
የሌላ ዓለም ፍጡራንን ፍለጋ ውስጥ በቀዳሚነት በሚቀመጠው ፕሮጀክት ስር የሚሰሩት ተመራማሪዎች ለፀሐይ በቅርብ ርቀት ከምትገኘውና ከምድር የ4.2 ብርሃን ዓመት ርቀት ካላት ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ኮከብ አቅጣጫ የመጡ የሚመስሉ አጠራጣሪ የሬዲዮ ሞገዶችን እየመረመሩ ናቸው፡፡ የሬዲዮ ሞገዶቹ አውስትራሊያ ውስጥ ባለው የፓርከስ ቴሌስኮፕ አማካኝነት ባለፈው የፈረንጆች ዓመት ሚያዝያ እና ግንቦት ወራት ላይ ነው የተገኙት፡፡ ሲግናሉ ከተላከበት ጊዜ አንስቶ በተመራማሪዎቹ ትንተና እየተደረገበት ሲሆን ዝርዝሩ እስካሁን ለህዝብ ይፋ አልተደረገም፡፡
ተመራማሪዎቹ ምዕራብ ቨርጂኒያ ውስጥ ባለው ቴሌስኮፕ አማካኝነት መሰል የራዲዮ ዌቮችን መስማታቸው የተለመደ ነው፡፡ ሆኖም እነዚህ ሞገዶች የሰው ልጆች ተፅዕንዖን ተከትለው የተገኙ ሲሆን ይህን ግን ለየት የሚያደርገው 980 ሜጋ ኸርዝ በሆነው የሬዲዮ ሞገዱ ባንዶች ውስጥ ሰው ሰራሽ የሆኑ ሳተላይትም ሆነ ቁስ ሲግናል አልተገኘበትም፡፡
ሲግናሉ በአውሮፓውያኑ 1977 ከተገኘውና “ዋው ሲግናል” ተብሎ ከሚታወቀው በኋላ በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጠው ሲግናል እንደሆነም በባለሙያዎች ዘንድ ተነግሮለታል፡፡ ሲግናሉን የመተንተኑን ስራ ስትመራ የቆየችው ሶፊያ ሼክ በፕሮጀክታቸው ውስጥ እስከዛሬ ከተሰሙት ሁሉ አጓጊው ሲግናል መሆኑን ትናገራለች፡፡ ሲግናሉንም ብሬክስሩ ሊስን ካንዲዴት 1 (BLC1) ብለውታል፡፡
በሌላው ዓለም ፍጡራን ፍለጋ ውስጥ ከሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች መካከል አንዱ ከእነዚህ ፍጡራን ጋራ የመገናኛው/መግባብያው መንገድ አለመታወቁ ነው፡፡ በተጨማሪም በዩኒቨርስ ውስጥ የሚፈጠሩ የሬዲዮ ሞገዶች ምንጭ ሊሆኑ የሚችሉት ተፈጥሮአዊ መነሻዎችም ቢሆን ሙሉ በሙሉ አይታወቁም፡፡ ስለዚህም ብዙውን እንደዚህ አይነት ሲግናሎች ሲገኙ ቴክኖሎጂ አፈራሽ እንደሆኑ ግምት የሚወሰድና ከተፈጥሮአዊ ምንጭ መሆናቸውን የሚያስረዳ ማብራርያንም በቀላሉ የማይገኝባቸው ሲሆን ነገሩን ወደ ሌላኛው ዓለም ፍጡራን መውሰዱ ግን ትኩረት ሳቢ ነው፡፡ ስለ ሲግናሉ የሚገልፅ መረጃ ለህዝብ ይፋ ያልተደረገ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ወደፊት ይፋ ቢሆን እንኳን ልክ እንደ ዋው ሲግናል ሁሉ በማስረጃ የዋጀ ድምዳሜ ላይ የሚደረስበት አይመስልም፡፡
ከማንኛውም ኮከብ በላይ ለምድር በምትቀርበው ፕሮክሲማ ሴንታዎሪ ውስጥ ቢያንስ ሁለት የሚዞሯት ፕላኔቶች መኖራቸው ይታወቃል፡፡ አንደኛው በጋዝ የተሞላ ሲሆን ሌላኛው ግን ባለው ለውሃ ፍሰት የተስማማ ሙቀት ሳብያ ሰውን ሊያኖሩ ይችላሉ ተብለው ግምት ከሚወሰድባቸው ፕላኔቶች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ይህች ፕላኔት ከምድር በ17 በመቶ የግዝፈት ብልጫ ያላት ድንጋያማ ስፍራ ናት፡፡ ፕሮክሲማ ቢ በሚል ስያሜ የምትታወቀው ፕላኔቷ በየ 11 ቀናቱ ኮከቧን የምትዞር ናት፡፡ ሆኖም ለሰው ልጆች ኑሮ አደገኛ ልትሆንም እንደምትችል ይነገራል፡፡ ከሦስት ዓመታት በፊት የናሳ ተመራማሪዎች የኮምፒውተር ሞዴልን ተጠቅመው ፕላኔቷ በቀላሉ ለከባድ ጨረር እና ድንገተኛ የኮከብ ብርሃን ነበልባል የተጋለጠች ልትሆን እንደምትችል አሳይተዋል፡፡
ምንጭ፡ The Guardian እና Live Science
ናኖ ቴክኖሎጂ ለዘመናዊ ግብርና
የግብርና ቴክኖሎጂ መሠረታዊ መለኪያው የምርት መጠንን መጨመር፣ የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ የሥራ ቅልጥፍና መፍጠርና ማቀነባበርን ያካትታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኢንዱስትሪ የበለፀጉ ሀገራት የናኖ ቴክኖሎጂን የሚደግፉ ተቋማትን በመመስረት ምርምር በሰፊው ከማካሄድ ባለፈ ወደ ምርት ተግባር መግባታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከቅርብ ዓመታት በኋላ ታዳጊ ሀገራትም ናኖ ቴክኖሎጂን በኢንዱስትሪዎቻቸው ውስጥ እየተጠቀሙባቸው ይገኛል፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ የምርት ጥራትና ብዛት ማሳደግ የሚያስችል በመሆኑ በግብርና ምርት ላይ መጠቀም የሚፈለገዉን ለዉጥ ለማምጣት ያግዛል፡፡ ከዚህም በተጓዳኝ ናኖ ቴክኖሎጂ በግብርና ኬሚካል ቅመም በመጠቀም የአፈር፣ የውሃና የአየር ብክለትን በመቀነስ ግብርናው የበለጠ አስተማማኝ እንዲሆን ያደርጋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በድረ-ገጹ ባወጣው የግብርና ፖሊሲ መግለጫ በ2050 የዓለም ህዝብ ብዛት 9 ቢሊዮን እንደሚደርስና እየጨመረ ያለውን የህዝብ ቁጥር ለመመገብ ግብርናውን ማዘመን የግድ እንደሚል አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ደግሞ ናኖ ቴክኖሎጂ መፍትሄ ያመጣል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታ፡፡ ናኖ ቴክኖሎጂ የምርትን ጥራትና ብዛት ከመጨመር ባሻገር ለዘላቂ የውሃ አጠቃቀም፣ ለንፁህ ዘር አቅርቦት፣ ተባይ እና በሽታን ለመለየት፣ አልሚ የምግብ አቅርቦትን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የእፅዋት ጥበቃና ተፈጥሮ ሃብት ከብክለት ነፃ ለማድረግ ወይም ለመቀነስ የሚረዳ መድሃኒት ማቅረብ ትኩረት ሊደረግበት የሚገባ ነው፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ በተፈጥሮ ላይ የጎንዮሽ ጉዳት ሳይደርስ ሚዛኑን ጠብቆ አረንጓዴና የተመቻቸ ስነ-ምህዳራዊ አካባቢን በመፍጠር የግብርና ምርትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ይሁን እንጅ በበለፀጉትና በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የናኖ ቅንጣቶች በረዥም ጊዜ አደጋ ያስከትላሉ ብሎ በመጠራጠር ለመቀበል መቸገር እንደሚስተዋል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ማንኛውም የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች እንደሚሰጡት ትሩፋት ሁሉ መጠነኛ ጉዳት ሊኖራቸው ስለሚችል የአጠቃቀም ሁኔታን ይበልጥ በማሻሻል እና ተሞክሮዎችን በመቀመር የቴክኖሎጂውን ፍሬ በበልሃት መጠቀም ግድ ይላል፡፡ የናኖ ቴክኖሎጂ ወጭ ቆጣ፤ ምርታማነትን ይበልጥ የሚያሳድግ እና ወቅቱን የዋጀ ቴክኖሎጂ መሆኑን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር በአጠቃቀም ሂደቱ ላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው፡፡
ምንጭ፡ Frontiersin
የግብርና ቴክኖሎጂ መሠረታዊ መለኪያው የምርት መጠንን መጨመር፣ የጥራት ደረጃ ማሻሻል፣ የሥራ ቅልጥፍና መፍጠርና ማቀነባበርን ያካትታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በኢንዱስትሪ የበለፀጉ ሀገራት የናኖ ቴክኖሎጂን የሚደግፉ ተቋማትን በመመስረት ምርምር በሰፊው ከማካሄድ ባለፈ ወደ ምርት ተግባር መግባታቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከቅርብ ዓመታት በኋላ ታዳጊ ሀገራትም ናኖ ቴክኖሎጂን በኢንዱስትሪዎቻቸው ውስጥ እየተጠቀሙባቸው ይገኛል፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ የምርት ጥራትና ብዛት ማሳደግ የሚያስችል በመሆኑ በግብርና ምርት ላይ መጠቀም የሚፈለገዉን ለዉጥ ለማምጣት ያግዛል፡፡ ከዚህም በተጓዳኝ ናኖ ቴክኖሎጂ በግብርና ኬሚካል ቅመም በመጠቀም የአፈር፣ የውሃና የአየር ብክለትን በመቀነስ ግብርናው የበለጠ አስተማማኝ እንዲሆን ያደርጋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በድረ-ገጹ ባወጣው የግብርና ፖሊሲ መግለጫ በ2050 የዓለም ህዝብ ብዛት 9 ቢሊዮን እንደሚደርስና እየጨመረ ያለውን የህዝብ ቁጥር ለመመገብ ግብርናውን ማዘመን የግድ እንደሚል አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ደግሞ ናኖ ቴክኖሎጂ መፍትሄ ያመጣል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታ፡፡ ናኖ ቴክኖሎጂ የምርትን ጥራትና ብዛት ከመጨመር ባሻገር ለዘላቂ የውሃ አጠቃቀም፣ ለንፁህ ዘር አቅርቦት፣ ተባይ እና በሽታን ለመለየት፣ አልሚ የምግብ አቅርቦትን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የእፅዋት ጥበቃና ተፈጥሮ ሃብት ከብክለት ነፃ ለማድረግ ወይም ለመቀነስ የሚረዳ መድሃኒት ማቅረብ ትኩረት ሊደረግበት የሚገባ ነው፡፡
ናኖ ቴክኖሎጂ በተፈጥሮ ላይ የጎንዮሽ ጉዳት ሳይደርስ ሚዛኑን ጠብቆ አረንጓዴና የተመቻቸ ስነ-ምህዳራዊ አካባቢን በመፍጠር የግብርና ምርትን ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል፡፡ ይሁን እንጅ በበለፀጉትና በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የናኖ ቅንጣቶች በረዥም ጊዜ አደጋ ያስከትላሉ ብሎ በመጠራጠር ለመቀበል መቸገር እንደሚስተዋል መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ማንኛውም የቴክኖሎጂ ፈጠራዎች እንደሚሰጡት ትሩፋት ሁሉ መጠነኛ ጉዳት ሊኖራቸው ስለሚችል የአጠቃቀም ሁኔታን ይበልጥ በማሻሻል እና ተሞክሮዎችን በመቀመር የቴክኖሎጂውን ፍሬ በበልሃት መጠቀም ግድ ይላል፡፡ የናኖ ቴክኖሎጂ ወጭ ቆጣ፤ ምርታማነትን ይበልጥ የሚያሳድግ እና ወቅቱን የዋጀ ቴክኖሎጂ መሆኑን ለማህበረሰቡ ግንዛቤ መፍጠር በአጠቃቀም ሂደቱ ላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው፡፡
ምንጭ፡ Frontiersin
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከልሳን ቴክኖሎጂ ጋራ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከልሳን ቴክኖሎጂ ጋራ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ፡፡ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በዋና አላማነት አንግቦ የተካሄደው የመግባብያ ስምምነቱ በሁለቱም ተቋማት ያሉ ተመራማሪዎችን በማስተባበር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤት እንደሚያስገኝም ታምኖበታል፡፡ ስምምነቱን በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በኩል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሙሉቀን ቀሬ ሲፈርሙ ልሳን ቴክኖሎጂን በመወከል ደግሞ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ አዳም ቦዶዊን ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡
ስምምነቱ ሁለቱ አካላት በማሽን ትራንስሌሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዲሁም በሁለቱም ተቋማት የሚገኙ ተመራማሪዎች፣ ሶፍትዌር መሀንዲሶች እና ሌሎች ባለሙያዎች በጋራ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ልሳን የስልጠና እንዲሁም የማሽን ትራንስሌሽን እና ኦፕቲካል ካራክተር ሪኮግኒሽን (OCR) ሲስተሞች ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ኢንስቲትዩቱም ለጋራ ምርምር የሚያስፈልግ መሰረተልማት፣ ቁሳቁስ እና አስተዳደራዊ አቅርቦቶችን የሚያከናውን ይሆናል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ ኢንስቲትዩቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በስልጠና፣ ጥናት እና ቢዝነስ መካከል ድልድይ መሆኑንና በሀገሪቱ ስትራቴጂዎች ውስጥም ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አውስተው ስምምነቱ በፍጥነት ወደ ተግባር እንዲለወጥ ያላቸውን ፍላጎት አንፀባርቀዋል፡፡ አቶ አዳም በበኩላቸው ተቋማቸው በዋናነት መቀመጫውን ጀርመን ሀገር አድርጎ እንደሚሰራ ገልፀው ሀገራዊ ቋንቋዎችን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እና በኢትዮጵያ እየሰሩ ያሏቸውን ቴክኖሎጂያዊ ስራዎች አስተዋውቀዋል፡፡
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ከልሳን ቴክኖሎጂ ጋራ በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ፡፡ የቴክኖሎጂ ሽግግርን በዋና አላማነት አንግቦ የተካሄደው የመግባብያ ስምምነቱ በሁለቱም ተቋማት ያሉ ተመራማሪዎችን በማስተባበር የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ ውጤት እንደሚያስገኝም ታምኖበታል፡፡ ስምምነቱን በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በኩል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሙሉቀን ቀሬ ሲፈርሙ ልሳን ቴክኖሎጂን በመወከል ደግሞ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ አዳም ቦዶዊን ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡
ስምምነቱ ሁለቱ አካላት በማሽን ትራንስሌሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዲሁም በሁለቱም ተቋማት የሚገኙ ተመራማሪዎች፣ ሶፍትዌር መሀንዲሶች እና ሌሎች ባለሙያዎች በጋራ እንዲሰሩ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ልሳን የስልጠና እንዲሁም የማሽን ትራንስሌሽን እና ኦፕቲካል ካራክተር ሪኮግኒሽን (OCR) ሲስተሞች ድጋፍ የሚያደርግ ሲሆን ኢንስቲትዩቱም ለጋራ ምርምር የሚያስፈልግ መሰረተልማት፣ ቁሳቁስ እና አስተዳደራዊ አቅርቦቶችን የሚያከናውን ይሆናል፡፡
በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ ኢንስቲትዩቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በስልጠና፣ ጥናት እና ቢዝነስ መካከል ድልድይ መሆኑንና በሀገሪቱ ስትራቴጂዎች ውስጥም ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት አውስተው ስምምነቱ በፍጥነት ወደ ተግባር እንዲለወጥ ያላቸውን ፍላጎት አንፀባርቀዋል፡፡ አቶ አዳም በበኩላቸው ተቋማቸው በዋናነት መቀመጫውን ጀርመን ሀገር አድርጎ እንደሚሰራ ገልፀው ሀገራዊ ቋንቋዎችን ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እና በኢትዮጵያ እየሰሩ ያሏቸውን ቴክኖሎጂያዊ ስራዎች አስተዋውቀዋል፡፡