የ2021ዱ ታዳሽ የሀይል አማራጭ (green hydrogen)
***********************
አለማችን በከፍተኛ መጠን እየተጎዳችበት ላለው የአየር ንብረት ለውጥ መሻሻል ሀገራት በተናጥልም ሆነ በጋራ የተለያዩ እርምጃ ሲወስዱ ማየት በጣም አስደሳች ነው፡፡ ለዚህም ብዙ ርቀን ሳንሔድ ሀገራችን ኢትዮጲያ በደን ልማት ዘርፍ እያደረገችው ያለው እንቅስቃሴ በጣም የሚበረታታ ነው፡፡ ሀገራት ከደን ልማት ባሻገር ከተፈጥሮ ጋር ተስማሚ የሆኑ የሀይል አማራጮችን በመጠቀም ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት መቀነስ እንዳለባቸው ብዙዎች ይስማማሉ፡፡
ከተፈጥሮ ጋር ተስማሚ የሆኑ የሀይል አማራጮች ሲታሰቡ እንደ ንፋስና ፀሐይ ያሉ አማራጮች በሰፊው ጥቅም ላይ እየዋሉና ስለ እድገታቸውም ተደጋግሞ እየሰማን እንገኛለን፡፡ ምንም እንኳን በዚህ ረገድ ሰፊ የሆነ የ፣ስፋፋት ስራ በያንዳንዱ ሀገር የሚጠበቅና ከዘርፉ መገኘት የሚችለው የሀይል መጠን ገና ያልተደረሰበት ቢሆንም ሌሎች አማራጮችንም መዳሰስ ተፈጥሮን ለመታደግ ባለ ብዙ አማራጭ ያደርገናል፡፡
በዚህ ጽሁፍ አሜሪካውያን ጆ ባይደንን ከመምረጣቸው ጋር ተያይዞ ስሙ የተነሳውን የ2021 ተስማሚና ታዳሽ የሀይል አማራጭ ልናስቃኛችሁ ወደናል፡፡ መረጃውንም ከ abc news አግኝተነዋል፡፡ የነገሩ ጥንስስ አሜሪካ በጆርጅ ቡሽ ስትመራ በነበረበት ወቅት የተብላላ ሲሆን በወቅቱም ተመራማሪዎቹ "freedom fuel" የሚል ቅጽል ስም ሰጥተውት ነበር፡፡ እንደ ቻይና፣ ጃፓን፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ጀርመንና አውስትራሊያ ያሉ ሀገራት በዘርፉ ሰፊ በጀት መድበው እየሰሩበት እንደሆ የዘገበው የመረጃ ምንጫችን የአሜሪካ ተመራጩ ፕሬዘዳንትም ዘርፉ ከተስማሚ የሀይል አማራጭ እቅዳቸው ውስጥ እንደሚካተት ለአሜሪካውያን ቃል ገብተዋልሲል አስነብቧል፡፡
የዘርፉን ባለሙያዎች በምንጭነት የጠቀሰው ABC News የአረንጓዴ ሀይድሮጅን ልማት ገበያ በቀጣዮቹ አስርት አመታት ከፍተኛ እድገት ያስመዘግባል የሚል መረጃ አውጥቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለውን "gray" ሀይድሮጅን ለማምረት fossil fuel መጠቀም የሚያስፈልግ በመሆኑ በሂደቱ ካርቦን ዳይ ኦክሳድ ልቀት አለው፡፡ ከዚህ በተሸለ ሁኔታ በአንጻራዊ ሰማያዊ ሀይድሮጅን ያነሰ የሀይድሮጅን ልቀት እንዳለው በዘርፉ የሚሰሩ ሰውች ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ከብክለት ነጻ የሆነ ሀይድሮጅን ("green" hydrogen) በውሀ ውስጥ ያሉትን የሀይድሮጅንና የኦክስጅን ሞሎኪዩሎች ለመነጣጠል የኤሌክትሪ ሀይልን ስለሚጠቀም ምንም አይነት የካርቦን ልቀት እንደሌለው ይነገራል፡፡
በዚህ መንገድ የሚገኝ ተስማሚ ሀይድሮጅን በሌሎች አማራጮች ሊገኝ የማይችልን ከጠቅላላው ፍላጎት ከ15 እስከ 20 በመቶ የሚሆን የሀይል ፍላጎትን ሊያሟላ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ ያለውን የተስማሚ የሀይል አማራጭ ክፍተት ከመሙላት በተጨማሪ በሀይድሮጅን የሚገኘው ሀይል ሌሎች አማራጮች ሊከውኗቸው የማይችሏቸውን ከፍተኛ ፋብሪካዎችን ማንቀሳቅሰ፣ ለረጅም ርቀት ተጓዥ ከባድ ተሸከርካሪዎች፣ ለጭነት መርከቦችና አውሮፕላኖችን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን ሀይል ማሟላት ይችላል፡፡
ለዚህ አይነቱ አማራጭ ተፈላጊነት ሌላው ጉዳይ ለሀይል ማምረት ሂደቱ የሚያስፈልገው መሰረተ ልማት ሙሉ ለሙሉ የተዘጋጀ መሆኑ ነው፡፡ ለቀጣይ 30 አመታት 11 ትሪሊዮን ዶላር ዋጋ የተገመተለት ይህ ፕሮጀክት አለማችን የምትመኘውን ዜሮ የካርቦን ልቀት እቅድ ከማሳካት አንጻር ገንዘቡ እንደማያሳስብ ተነግሯል፡፡
የዘርፉ ሙያተኞች ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በሶስት ምክንያቶች እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡እነዚህም ሀይድሮጅን ለማምረት የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ሀይል ለማሟላትና የፀሐይል መሰብሰቢያ ንጣፎችን ለመዘርጋት፣ ሀይድሮጅኑን ለሚያመርቱ ማሽኖች (electrolyzers) እና ሀይድሮጅኑን ለማጓጓዝ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የሚስፈልገው ግዙፍ ፋብሪካ በ Delta, Utah እየተገነባ ነው፡፡
ምንጭ Abc News
***********************
አለማችን በከፍተኛ መጠን እየተጎዳችበት ላለው የአየር ንብረት ለውጥ መሻሻል ሀገራት በተናጥልም ሆነ በጋራ የተለያዩ እርምጃ ሲወስዱ ማየት በጣም አስደሳች ነው፡፡ ለዚህም ብዙ ርቀን ሳንሔድ ሀገራችን ኢትዮጲያ በደን ልማት ዘርፍ እያደረገችው ያለው እንቅስቃሴ በጣም የሚበረታታ ነው፡፡ ሀገራት ከደን ልማት ባሻገር ከተፈጥሮ ጋር ተስማሚ የሆኑ የሀይል አማራጮችን በመጠቀም ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት መቀነስ እንዳለባቸው ብዙዎች ይስማማሉ፡፡
ከተፈጥሮ ጋር ተስማሚ የሆኑ የሀይል አማራጮች ሲታሰቡ እንደ ንፋስና ፀሐይ ያሉ አማራጮች በሰፊው ጥቅም ላይ እየዋሉና ስለ እድገታቸውም ተደጋግሞ እየሰማን እንገኛለን፡፡ ምንም እንኳን በዚህ ረገድ ሰፊ የሆነ የ፣ስፋፋት ስራ በያንዳንዱ ሀገር የሚጠበቅና ከዘርፉ መገኘት የሚችለው የሀይል መጠን ገና ያልተደረሰበት ቢሆንም ሌሎች አማራጮችንም መዳሰስ ተፈጥሮን ለመታደግ ባለ ብዙ አማራጭ ያደርገናል፡፡
በዚህ ጽሁፍ አሜሪካውያን ጆ ባይደንን ከመምረጣቸው ጋር ተያይዞ ስሙ የተነሳውን የ2021 ተስማሚና ታዳሽ የሀይል አማራጭ ልናስቃኛችሁ ወደናል፡፡ መረጃውንም ከ abc news አግኝተነዋል፡፡ የነገሩ ጥንስስ አሜሪካ በጆርጅ ቡሽ ስትመራ በነበረበት ወቅት የተብላላ ሲሆን በወቅቱም ተመራማሪዎቹ "freedom fuel" የሚል ቅጽል ስም ሰጥተውት ነበር፡፡ እንደ ቻይና፣ ጃፓን፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ጀርመንና አውስትራሊያ ያሉ ሀገራት በዘርፉ ሰፊ በጀት መድበው እየሰሩበት እንደሆ የዘገበው የመረጃ ምንጫችን የአሜሪካ ተመራጩ ፕሬዘዳንትም ዘርፉ ከተስማሚ የሀይል አማራጭ እቅዳቸው ውስጥ እንደሚካተት ለአሜሪካውያን ቃል ገብተዋልሲል አስነብቧል፡፡
የዘርፉን ባለሙያዎች በምንጭነት የጠቀሰው ABC News የአረንጓዴ ሀይድሮጅን ልማት ገበያ በቀጣዮቹ አስርት አመታት ከፍተኛ እድገት ያስመዘግባል የሚል መረጃ አውጥቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ጥቅም ላይ እየዋለ ያለውን "gray" ሀይድሮጅን ለማምረት fossil fuel መጠቀም የሚያስፈልግ በመሆኑ በሂደቱ ካርቦን ዳይ ኦክሳድ ልቀት አለው፡፡ ከዚህ በተሸለ ሁኔታ በአንጻራዊ ሰማያዊ ሀይድሮጅን ያነሰ የሀይድሮጅን ልቀት እንዳለው በዘርፉ የሚሰሩ ሰውች ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ከብክለት ነጻ የሆነ ሀይድሮጅን ("green" hydrogen) በውሀ ውስጥ ያሉትን የሀይድሮጅንና የኦክስጅን ሞሎኪዩሎች ለመነጣጠል የኤሌክትሪ ሀይልን ስለሚጠቀም ምንም አይነት የካርቦን ልቀት እንደሌለው ይነገራል፡፡
በዚህ መንገድ የሚገኝ ተስማሚ ሀይድሮጅን በሌሎች አማራጮች ሊገኝ የማይችልን ከጠቅላላው ፍላጎት ከ15 እስከ 20 በመቶ የሚሆን የሀይል ፍላጎትን ሊያሟላ እንደሚችል ተገምቷል፡፡ ያለውን የተስማሚ የሀይል አማራጭ ክፍተት ከመሙላት በተጨማሪ በሀይድሮጅን የሚገኘው ሀይል ሌሎች አማራጮች ሊከውኗቸው የማይችሏቸውን ከፍተኛ ፋብሪካዎችን ማንቀሳቅሰ፣ ለረጅም ርቀት ተጓዥ ከባድ ተሸከርካሪዎች፣ ለጭነት መርከቦችና አውሮፕላኖችን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን ሀይል ማሟላት ይችላል፡፡
ለዚህ አይነቱ አማራጭ ተፈላጊነት ሌላው ጉዳይ ለሀይል ማምረት ሂደቱ የሚያስፈልገው መሰረተ ልማት ሙሉ ለሙሉ የተዘጋጀ መሆኑ ነው፡፡ ለቀጣይ 30 አመታት 11 ትሪሊዮን ዶላር ዋጋ የተገመተለት ይህ ፕሮጀክት አለማችን የምትመኘውን ዜሮ የካርቦን ልቀት እቅድ ከማሳካት አንጻር ገንዘቡ እንደማያሳስብ ተነግሯል፡፡
የዘርፉ ሙያተኞች ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በሶስት ምክንያቶች እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡እነዚህም ሀይድሮጅን ለማምረት የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ሀይል ለማሟላትና የፀሐይል መሰብሰቢያ ንጣፎችን ለመዘርጋት፣ ሀይድሮጅኑን ለሚያመርቱ ማሽኖች (electrolyzers) እና ሀይድሮጅኑን ለማጓጓዝ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ለዚህም የሚስፈልገው ግዙፍ ፋብሪካ በ Delta, Utah እየተገነባ ነው፡፡
ምንጭ Abc News
የወታደራዊ አመራሮችን በቀድሞ ታላላቅ ጦርነቶች አንፆ የሚያሰለጥነው አዲስ ቴክኖሎጂ
****************************
አዲስ የተሰራው የጦር ሜዳ ታሪክን ማስተማርያ ስልት በቅርቡ የወደፊት የጦር መሪዎችን ለማሰልጠን ሊውል እንደሚችል ተነገረ፡፡ የፐርጅዩ ዩኒቨርሲቲ አጥኚዎች ቨርቹዋል ሪያሊቲን ተጠቅመው በፈጠሩት የጦር አውድማ መከሰቻ ሲሙሌተር ዲ ዴይ ተብሎ የሚታወቀውንና በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የቃልኪዳን ሀገራት የፈረንሳይዋን ኖርማንዲ የባህር ዳርቻ የወረሩበትን ታላቅ የጦር ቀንን ዳግም መፍጠር ችለዋል፡፡ በፊዚክስ ትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለውን ዕውቀት ተጠቅሞ የጦር መርከቡ ከውሃው ጋር ሲቆራኝ ያለውን እውነተኛ የሚመስል ሁነት በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ አማካኝነት በመጠቀም ወታደሮችን ለማሰልጠን እንደሚገለገሉበት የሚናገሩት ፕ/ር ሶሪን አዳም ማርቴ የውትድርና መምህራንም ቴክኖሎጂውን የወደፊት የጦር መሪዎችን ስላለፉትን ታሪካዊ ጦርነቶች በማስተማር ለማነፅ ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ አስቀምጠዋል፡፡
ስራው ዓለም አቀፋዊ የረጅም ጊዜ ውትድርና፣ ፖለቲካዊ እና ተቋማዊ ውሳኔ አሰጣጥን የሚያንፁ የስትራቴጂ እና ደህንነት እንቅስቃሴዎች አማካኝነት የተረጋጋች እና ደህንነቷ የተጠበቀ ዓለምን ለማምጣት የሚከናወነውን ጥናት የሚደግፍ መሆኑ ተነግሮለታል፡፡ የጥናት ቡድኑ በአላባማ ግዛት ውስጥ ካለው የአሜሪካን አየር ኃይል የአየር ላይ ጦርነት ኮሌጅ ጋራ የሚሰራ ሲሆን የአየር ላይ ጦርነት ኮሌጁ በየዓመቱ ፀደይ ሲደርስ ወደ ኖርማንዲ መጓዝን የካሪኩለሙ አካል አድርጎ ቆይቷል፡፡
የጥናት ቡድኑ በአሜሪካን የእርስ በእርስ ጦርነት አካል የሆነው የጌቲስበርግ ጦርነትን በሲሙሌተሩ ዳግም ለመከሰት እየሰራ ሲሆን ወደፊትም ቴክኖሎጂውን ወደ ንግዱ ዓለም ለመቀላቀል በማሰብ ፎርስስ (FORCES) የተባለ አዲስ ድርጅት አቋቁሟል፡፡ ዋናው ነጥብ አዲስ የውትድርና ታሪክን መማርያ መንገድን መፍጠር እና ማጋራት ብሎም የውትድርና ጥበብ እና ሳይንስን ይበልጥ ማጥናትና መረዳት ላይ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የጥናት ቡድኑ አካል ሮበርት ከርቹቤል ናቸው፡፡ አክለውም አዲሱ ስራቸውን በመጠቀም ቀድሞ የተደረጉ ስመጥር ጦርነቶችን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዳግም ወደ አዲሱ የተማሪና ምሁራንን ትውልድ ለመመለስ ጉጉት እንዳደረባቸው ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
****************************
አዲስ የተሰራው የጦር ሜዳ ታሪክን ማስተማርያ ስልት በቅርቡ የወደፊት የጦር መሪዎችን ለማሰልጠን ሊውል እንደሚችል ተነገረ፡፡ የፐርጅዩ ዩኒቨርሲቲ አጥኚዎች ቨርቹዋል ሪያሊቲን ተጠቅመው በፈጠሩት የጦር አውድማ መከሰቻ ሲሙሌተር ዲ ዴይ ተብሎ የሚታወቀውንና በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የቃልኪዳን ሀገራት የፈረንሳይዋን ኖርማንዲ የባህር ዳርቻ የወረሩበትን ታላቅ የጦር ቀንን ዳግም መፍጠር ችለዋል፡፡ በፊዚክስ ትምህርት ዘርፍ ውስጥ ያለውን ዕውቀት ተጠቅሞ የጦር መርከቡ ከውሃው ጋር ሲቆራኝ ያለውን እውነተኛ የሚመስል ሁነት በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ አማካኝነት በመጠቀም ወታደሮችን ለማሰልጠን እንደሚገለገሉበት የሚናገሩት ፕ/ር ሶሪን አዳም ማርቴ የውትድርና መምህራንም ቴክኖሎጂውን የወደፊት የጦር መሪዎችን ስላለፉትን ታሪካዊ ጦርነቶች በማስተማር ለማነፅ ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ አስቀምጠዋል፡፡
ስራው ዓለም አቀፋዊ የረጅም ጊዜ ውትድርና፣ ፖለቲካዊ እና ተቋማዊ ውሳኔ አሰጣጥን የሚያንፁ የስትራቴጂ እና ደህንነት እንቅስቃሴዎች አማካኝነት የተረጋጋች እና ደህንነቷ የተጠበቀ ዓለምን ለማምጣት የሚከናወነውን ጥናት የሚደግፍ መሆኑ ተነግሮለታል፡፡ የጥናት ቡድኑ በአላባማ ግዛት ውስጥ ካለው የአሜሪካን አየር ኃይል የአየር ላይ ጦርነት ኮሌጅ ጋራ የሚሰራ ሲሆን የአየር ላይ ጦርነት ኮሌጁ በየዓመቱ ፀደይ ሲደርስ ወደ ኖርማንዲ መጓዝን የካሪኩለሙ አካል አድርጎ ቆይቷል፡፡
የጥናት ቡድኑ በአሜሪካን የእርስ በእርስ ጦርነት አካል የሆነው የጌቲስበርግ ጦርነትን በሲሙሌተሩ ዳግም ለመከሰት እየሰራ ሲሆን ወደፊትም ቴክኖሎጂውን ወደ ንግዱ ዓለም ለመቀላቀል በማሰብ ፎርስስ (FORCES) የተባለ አዲስ ድርጅት አቋቁሟል፡፡ ዋናው ነጥብ አዲስ የውትድርና ታሪክን መማርያ መንገድን መፍጠር እና ማጋራት ብሎም የውትድርና ጥበብ እና ሳይንስን ይበልጥ ማጥናትና መረዳት ላይ ነው ያሉት ደግሞ ሌላኛው የጥናት ቡድኑ አካል ሮበርት ከርቹቤል ናቸው፡፡ አክለውም አዲሱ ስራቸውን በመጠቀም ቀድሞ የተደረጉ ስመጥር ጦርነቶችን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ዳግም ወደ አዲሱ የተማሪና ምሁራንን ትውልድ ለመመለስ ጉጉት እንዳደረባቸው ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
ሰዎች በየአመቱ 30 ጊጋቶን የሚጠጋ ቁስ ነገሮችን ያመርታሉ
***************************
ሰው ሰራሽ የሆኑ ነገሮች ማለት የሸቀጥ ምርቶች፣ መሰረተ-ልማቶች፣ ህንፃዎች እና ሌሎች ቁስ ነገሮች ከምድር አጠቃላይ የባዮማስ መጠን በክብደት እየጨመሩ መምጣታቸውን በኔቸር ጆርናል የወጣ አዲስ ጥናት ጠቁሟል፡፡ ጥናቱ 2020ን እንደ መነሻ አድርጎ ባካሄደው ምርምር ሰዎች የሰሯቸው ቁስ ነገሮች ወይም (anthropogenic mass) በምድር ካሉ ህይወት ያለቸው ነግሮች (total biomass) በክብድት እየላቁ መምጣቸው ተጠቁሟል፡፡
አሁን ላይ የሰው ልጆች በዓመት ወደ 30 ጊጋቶን ወይም 30 ቢሊዮን ቶን የሚጠጋ ቁስ ነገሮችን በብዛት የሚያመርቱ ሲሆን ይህ የምርት መጠንም ባለፉት አስር አመታት ከፍተኛ ጭማሪ እያሰየ መምጣቱ በጥናቱ ተዳሷል፡፡ እንደአውሮፓውያኑ በ1900 ሰዎች የሰሯቸው ቁስ ነገሮች ከአጠቃላይ ባዮማስ አንፃር ሲሰላ 3% የነበረ ቢሆንም ይህ የክብደት መጠን ከ1920ዎቹ አንስቶ ይበልጥ ጭማሪ በማሳየት በተለይም በመጨረሻዎቹ 20 እና 10 አመታት ከኢንዱስትሪ ምርቶች መስፋፋት ጋር ተያይዞ መጠኑ እጅግ እየላቀ መምጣቱን አጥኚዎች ይናገራሉ፡፡
ተመራማሪዎች ይህን የሰው-ሰራሽ ቁስ ነገሮች ክብድት ከባዮማስ አጠቃላይ ክብደት ለማነፃፀርና ለመለካት በኮምፒውተር ሞዴሊንግ የተሰሩ ቀደምት ትንበያዎችን የተጠቀሙ ሲሆን፤ ከዚህ በተጨማሪም የመስክ የዳሰሳ ጥናቶች እና ለማክሮ ኢኮኖሚክ ትንተና የሚውል የስቶክ ፍሎው ሞዴሊንግ (stock-flow modeling) የምርምር ዘዴዎችን በጥናቱ ላይ ለመተግበር ሞክረዋል፡፡
ተመራማሪዎች እንደሚያስረዱት አብዛኞቹ ጥቅም ላይ የዋሉት የምርምር ዘዴዎች ፍፁም ልክ ሊባል የሚችል ቁጠራዊ መረጃ የሚሰጡ ባይሆንም አጠቃላይ የክብደት ንፃሬውን ያልተወሳሰበና የተስተካከለ ለማድረግ በባዮማስ በኩል የውሃ መጠንን በሰው-ሰራሽ በኩል ደግሞ የቁስ ውጋጆችን በትንበያው ላይ አለማካተታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተመራማሪዎች እንደሚገልፁት ይህ የምርምር ውጤት የሰው ልጅ በምድር ላይ እያስከተለ ያለውን ከፍተኛ ጫና የሚያሳይ ከመሆኑም ባለፈ በጂዎሎጂካል የጊዜ ምጣኔ አዲስ ዘምን ወደሆነው አንትሮፔሲን (Anthropocene) እየገባን መሆኑን የሚያመለክት ነው ይላሉ፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
***************************
ሰው ሰራሽ የሆኑ ነገሮች ማለት የሸቀጥ ምርቶች፣ መሰረተ-ልማቶች፣ ህንፃዎች እና ሌሎች ቁስ ነገሮች ከምድር አጠቃላይ የባዮማስ መጠን በክብደት እየጨመሩ መምጣታቸውን በኔቸር ጆርናል የወጣ አዲስ ጥናት ጠቁሟል፡፡ ጥናቱ 2020ን እንደ መነሻ አድርጎ ባካሄደው ምርምር ሰዎች የሰሯቸው ቁስ ነገሮች ወይም (anthropogenic mass) በምድር ካሉ ህይወት ያለቸው ነግሮች (total biomass) በክብድት እየላቁ መምጣቸው ተጠቁሟል፡፡
አሁን ላይ የሰው ልጆች በዓመት ወደ 30 ጊጋቶን ወይም 30 ቢሊዮን ቶን የሚጠጋ ቁስ ነገሮችን በብዛት የሚያመርቱ ሲሆን ይህ የምርት መጠንም ባለፉት አስር አመታት ከፍተኛ ጭማሪ እያሰየ መምጣቱ በጥናቱ ተዳሷል፡፡ እንደአውሮፓውያኑ በ1900 ሰዎች የሰሯቸው ቁስ ነገሮች ከአጠቃላይ ባዮማስ አንፃር ሲሰላ 3% የነበረ ቢሆንም ይህ የክብደት መጠን ከ1920ዎቹ አንስቶ ይበልጥ ጭማሪ በማሳየት በተለይም በመጨረሻዎቹ 20 እና 10 አመታት ከኢንዱስትሪ ምርቶች መስፋፋት ጋር ተያይዞ መጠኑ እጅግ እየላቀ መምጣቱን አጥኚዎች ይናገራሉ፡፡
ተመራማሪዎች ይህን የሰው-ሰራሽ ቁስ ነገሮች ክብድት ከባዮማስ አጠቃላይ ክብደት ለማነፃፀርና ለመለካት በኮምፒውተር ሞዴሊንግ የተሰሩ ቀደምት ትንበያዎችን የተጠቀሙ ሲሆን፤ ከዚህ በተጨማሪም የመስክ የዳሰሳ ጥናቶች እና ለማክሮ ኢኮኖሚክ ትንተና የሚውል የስቶክ ፍሎው ሞዴሊንግ (stock-flow modeling) የምርምር ዘዴዎችን በጥናቱ ላይ ለመተግበር ሞክረዋል፡፡
ተመራማሪዎች እንደሚያስረዱት አብዛኞቹ ጥቅም ላይ የዋሉት የምርምር ዘዴዎች ፍፁም ልክ ሊባል የሚችል ቁጠራዊ መረጃ የሚሰጡ ባይሆንም አጠቃላይ የክብደት ንፃሬውን ያልተወሳሰበና የተስተካከለ ለማድረግ በባዮማስ በኩል የውሃ መጠንን በሰው-ሰራሽ በኩል ደግሞ የቁስ ውጋጆችን በትንበያው ላይ አለማካተታቸውን ተናግረዋል፡፡ ተመራማሪዎች እንደሚገልፁት ይህ የምርምር ውጤት የሰው ልጅ በምድር ላይ እያስከተለ ያለውን ከፍተኛ ጫና የሚያሳይ ከመሆኑም ባለፈ በጂዎሎጂካል የጊዜ ምጣኔ አዲስ ዘምን ወደሆነው አንትሮፔሲን (Anthropocene) እየገባን መሆኑን የሚያመለክት ነው ይላሉ፡፡
ምንጭ፡ Scientific American
የ Surface Web እና Deep Web ልዩነት
===================
የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች እንደሚያስረዱት በጎግልና በሌሎች የመፈለጊያ መሳሪያዎች ሊገኙ የሚችሉ ብዙ ሚሊዮን የበይነ መረብ ገፆች ቢኖሩም ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ገፆች ግን በየትኛውም የመፈለጊያ መሳሪያዎች ሊገኙ የማይችሉ ናቸው፡፡ ይህ ማለት በኢንተርኔት ላይ ማግኘት የማንችላቸው ነገሮች ማግኘት ከምንችላቸው ነገሮች ጋር ሲነፃፀሩ የሰማይ እና የምድር ልዩነት ያላቸው ናቸው ማለት ነው፡፡
ባለሙያዎች የሰርፌስ ዌብ (Surface Web) እና ዲፕ ዌብ (Deep Web) ልዩነት በቀላሉ ለማስቀመጥ የውቂያኖስን ምሳሌ ይጠቀማሉ፡፡ ድር ወይም ዌብ የሚባለውን ነገር እንደውቂያኖስ ቢታሰብ ሰርፌስ ዌብ የምንለው የውቂያኖሱ የላይኛው አካል ወይም መንካት የምንችለው የውሃ ክፍል ሲሆን ዲፕ ዌብ የሚባለው ደግሞ ጥለቁ የውቂያኖስ ክፍል ሆኖ በቀላሉ መንካት የማንችለው የውሃ አካል ነው፡፡
በዚህ መሰረት በአለም አቀፍ ድር (World Wide Web) አጠቃቀም እንደጎግልና ያሆ ያሉ ስታንዳርድ የመፈለጊያ መሳሪያዎችን ተጠቅመን በቀላሉ ልናገኘው የምንችለው የበይነ መረብ አካል ሰርፌስ ዌብ ይባላል፡፡ ይህ የዌብ አይነት ሁሌ የምንጠቀምባቸውን እንደፌስቡክ፣ ጎግል፣ ዊኪፒዲያ እና ሌሎች ድረ-ገፆችን በቀላሉ እንድንጠቀም የሚያስችል እና ምንም አይነት ገደብ የሌለብት የበይነ መረብ አካል ነው፡፡
ዲፕ ዌብ በአለም አቀፍ ድር (World Wide Web) አጠቃቀም እንደጎግልና ያሆ ያሉ ስታንዳርድ የመፈለጊያ መሳሪያዎችን ተጠቅምን በፍፁም ልናገኘው ወይም (access) ልናደርገው የማንችለው የበይነ መረብ አካል ነው፡፡ በዚህ የዌብ አይነት እነደ ኢሜል ኢንቦክስ፣ የኦንላይን ባንኪንግ እና ሌሎችም በይልፍ ቃል የታጠሩ እና የራሳቸው ቀጥተኛ URL ወይም IP አድራሻ (address) ያላቸው ይዘቶች ይገኛሉ፡፡
በዚህ አለም አቀፍ የድር አጠቃቀም ከዲፕ ዌብ በታች ያለውን እና ልዩ መተግበሪያዎች ተጠቅመን ማግኘት የምንችለውን የዌብ አይነት Dark Web እንለዋለን፡፡ ዳርክ ዌብ በውቂያኖሱ ምሳሌ ከጥልቁ የውሃ ክፍል በታች ያለውን ዝቅተኛ ስፋራ ወይም (bottom of the ocean) ሊባል ይቻል፡፡ ይህን የዌብ አይነት access ለማድረግ በተደራቢ አውታረመረቦች ወይም (overlay networks) ማለፈ የሚገባ ሲሆን ይህን ማስጠቀም የሚችሉ ልዩ መተግበሪያዎችም የግድ ያስፈልጋሉ፡፡ የዳርክ ዌብ ገፆች ማንነታቸው ባልታወቀ አካለት የሚዘጋጅ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ድብቅ ፎረሞች፣ ህገ-ወጥ ግብይቶች እና ሌሎች አግባብነት የሌላቸው ነገሮች ይካሄዱበታል ተብሎ ይታሰባል፡፡
ምንጭ፡ Ciso Platform
===================
የሳይበር ደህንነት ባለሙያዎች እንደሚያስረዱት በጎግልና በሌሎች የመፈለጊያ መሳሪያዎች ሊገኙ የሚችሉ ብዙ ሚሊዮን የበይነ መረብ ገፆች ቢኖሩም ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ገፆች ግን በየትኛውም የመፈለጊያ መሳሪያዎች ሊገኙ የማይችሉ ናቸው፡፡ ይህ ማለት በኢንተርኔት ላይ ማግኘት የማንችላቸው ነገሮች ማግኘት ከምንችላቸው ነገሮች ጋር ሲነፃፀሩ የሰማይ እና የምድር ልዩነት ያላቸው ናቸው ማለት ነው፡፡
ባለሙያዎች የሰርፌስ ዌብ (Surface Web) እና ዲፕ ዌብ (Deep Web) ልዩነት በቀላሉ ለማስቀመጥ የውቂያኖስን ምሳሌ ይጠቀማሉ፡፡ ድር ወይም ዌብ የሚባለውን ነገር እንደውቂያኖስ ቢታሰብ ሰርፌስ ዌብ የምንለው የውቂያኖሱ የላይኛው አካል ወይም መንካት የምንችለው የውሃ ክፍል ሲሆን ዲፕ ዌብ የሚባለው ደግሞ ጥለቁ የውቂያኖስ ክፍል ሆኖ በቀላሉ መንካት የማንችለው የውሃ አካል ነው፡፡
በዚህ መሰረት በአለም አቀፍ ድር (World Wide Web) አጠቃቀም እንደጎግልና ያሆ ያሉ ስታንዳርድ የመፈለጊያ መሳሪያዎችን ተጠቅመን በቀላሉ ልናገኘው የምንችለው የበይነ መረብ አካል ሰርፌስ ዌብ ይባላል፡፡ ይህ የዌብ አይነት ሁሌ የምንጠቀምባቸውን እንደፌስቡክ፣ ጎግል፣ ዊኪፒዲያ እና ሌሎች ድረ-ገፆችን በቀላሉ እንድንጠቀም የሚያስችል እና ምንም አይነት ገደብ የሌለብት የበይነ መረብ አካል ነው፡፡
ዲፕ ዌብ በአለም አቀፍ ድር (World Wide Web) አጠቃቀም እንደጎግልና ያሆ ያሉ ስታንዳርድ የመፈለጊያ መሳሪያዎችን ተጠቅምን በፍፁም ልናገኘው ወይም (access) ልናደርገው የማንችለው የበይነ መረብ አካል ነው፡፡ በዚህ የዌብ አይነት እነደ ኢሜል ኢንቦክስ፣ የኦንላይን ባንኪንግ እና ሌሎችም በይልፍ ቃል የታጠሩ እና የራሳቸው ቀጥተኛ URL ወይም IP አድራሻ (address) ያላቸው ይዘቶች ይገኛሉ፡፡
በዚህ አለም አቀፍ የድር አጠቃቀም ከዲፕ ዌብ በታች ያለውን እና ልዩ መተግበሪያዎች ተጠቅመን ማግኘት የምንችለውን የዌብ አይነት Dark Web እንለዋለን፡፡ ዳርክ ዌብ በውቂያኖሱ ምሳሌ ከጥልቁ የውሃ ክፍል በታች ያለውን ዝቅተኛ ስፋራ ወይም (bottom of the ocean) ሊባል ይቻል፡፡ ይህን የዌብ አይነት access ለማድረግ በተደራቢ አውታረመረቦች ወይም (overlay networks) ማለፈ የሚገባ ሲሆን ይህን ማስጠቀም የሚችሉ ልዩ መተግበሪያዎችም የግድ ያስፈልጋሉ፡፡ የዳርክ ዌብ ገፆች ማንነታቸው ባልታወቀ አካለት የሚዘጋጅ ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ ድብቅ ፎረሞች፣ ህገ-ወጥ ግብይቶች እና ሌሎች አግባብነት የሌላቸው ነገሮች ይካሄዱበታል ተብሎ ይታሰባል፡፡
ምንጭ፡ Ciso Platform
በቂና የተመጣጠነ ምግብ ለሁሉም
-----------------------------
የአመጋገብ ባህላችንን መቀየሩ ቀላል ቢሆን ኖሮ በንጥረ ነገሮች የበለፀገ ተመጣጣኝ ምግብ ካለመመገብ ጋራ የተያያዙ ሁሉም ችግሮች ከዘመናት በፊት በተወገዱ ነበር፡፡ ሁሉም የምድራችን ነዋሪም በጤና ሊያቆየው የሚችለውን ምግብ በበቂ ሁኔታ ማግኘት በቻለ ነበር፡፡ 44 የዓለም ሀገራትን ተሳታፊ አድርጎ በአውሮፓውያኑ 1943 በተካሄደው ታሪካዊው የሆት ስፕሪንግ ምግብና ግብርና ኮንፈረንስ ላይ “ደህንነቱ የተጠበቀ በቂና ዘላቂ የምግብ አቅርቦት ለሁሉም” የሚለውን ሀሳብ ወደ ዓለም መድረክ የመጣና እንዲሁም ከሰላሳ ዓመታት በኋላ የተካሄደው የ1974ቱን የሮም የምግብ እና ግብርና ኮንፈረንስ ላይ ሁሉም የሰው ልጅ ከረሀብ ነፃ የመሆን እና ለተሟላ እድገት መረጋገጥ መሰረታዊ በሆኑ ንጥረ ነገሮች የዳበረ ምግብን የማግኘት መብት እንዳለው የተመጠ ቢሆንም ይህ ሁሉ ግን በምኞት ብቻ የቀረ ሆኗል፡፡
እውነታው እኛ የሰው ልጆች ዛሬም መጠነ ሰፊ የአመጋገብ ችግር ውስጥ መሆናችን ነው፡፡ ሁኔታው እጅግ የተወሳሰበ እና ብዙ ነገሮችን የያዘ ቢሆንም ቅሉ እንዲሁ በጠቅላላው ስናየው ግን አሁንም ብዙዎች ይራባሉ፣ በንጥረ ነገሮች የበለፀገ ተመጣጣኝ ምግብን በማግኘት ረገድ በደሃ እና ሀብታም ሀገራት ወይም ክፍለዓተ ዓለማት መካከል ያለው ልዩነት እጅጉን ሰፊ ነው፣ ከምርት እስከ ማከፋፈል ድረስ የሚዘረጋው የምግብ አቅርቦት ስርዓታችንም ቢሆን እኛንም ሆነ ምድራችንን እየጎዳ ይገኛል፡፡ ወደ አንደኛ ዓመቱ የተጠጋው የኮቪድ-19 ወረርሺኝ ደግሞ በምግብ ስርዓታችን ውስጥ ያሉ ችግሮችን ይባስ ያጋለጠ ሆኗል፡፡ የፖለቲካ፣ ምጣኔ-ሐብት እና ባህል ተግዳሮቶችም ዘላቂ በሆነ ሁኔታ ዓለም አቀፋዊውን የዓመጋገብ ልማድ እንዳይለወጥ አድርገዋል፡፡ የቱን እንመገብ በሚለው ላይ ከስምምነት ተደረሰ ብንልም እንኳን ይህን በስፋት መተግበሩ ትልቅ እና በደንብም ያልተጠና ተግዳሮት ነው፡፡
የስነ-ምግብ ተመራማሪዎች አንደሚያሰቀምጡት ከሆነ ለሰው ልጆች አካላዊም ሆነ አዕምሮአዊ ጤና ብሎም ለተፈጥሮ አካባቢ ተስማሚነት ከስጋና ስጋ ተዋፅዖዎች ይልቅ በዋናነት እፅዋትን መሰረት ያደረገ አመጋገብን መከተሉ አስፈላጊ ነው፡፡
ግን ደግሞ ያለ መፍትሄ ፍለጋ ዝም ብለን አልተቀመጥንም፤ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የተለያዩ እርምጃዎች በመወሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ በግብርና የሚገኘውን ስጋ ለመቀነስ በዓለም ዙርያ ያሉ ተመራማሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ልናገኛቸው የምንችላቸው የፕሮቲን አማራጮችን ወደ መመገቢያ ትሪያችን ለማምጣት እየታተሩ ይገኛሉ፡፡ አሁን ላይ በሚወጡ ትንበያዎች መሰረትም የዛሬ 30 ዓመት በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚከወነው የአሳ እርባታ (Aquaculture) የሚገነው የአሳ ምርት ከተፈጥሮ የውሃ አካላት ተጠምዶ ከሚገኘው የላቀ ምርትን እንደሚያስገኝ ነው፡፡ የግብርና ምርትን የሚያሳድጉ ግን ደግሞ የተፈጥሮ አካባቢንም በዘላቂነት የሚጠብቁ የግብርና ስልቶችን የመጠቀም ልምዳችንም ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡
በአውሮፓውያኑ 2050 በምድራችን ላይ የሚኖረው ሰው ብዛት 10 ቢሊዮን እንደሚደርስ ከትንበያዎች መረዳት እንችላለን፡፡ ይህ አሁን ባለው ህዝብ ላይ ሌላ የቻይናን ህዝብ ሁለት እጥፍ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ አዳዲስ ምግብ ፈላጊ ነዋሪዎችን መጨመር ማለት ነውና ለዚህ ሁሉ ህዝብ የተመጣጠነ ምግብንም አቅርቦ የምንኖርባት ምድርንም ከከፋ ጉዳት ጠብቆ መጓዙ ሁሉን አቀፍ የጋራ ስራን ይጠይቃል፡፡ ታድያ ዘላቂ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ለሁላችንም የሚያረጋግጥ መፍትሄ ከአንድ ወገን ብቻ ማግነቱ ለስኬት አይረዳም፡፡ አሁን ያለንበት የኮቪድ-19 ወረርሺኝ የተቀናጀና ሁሉን ያስተባበረ ዓለም አቀፋዊ ምላሽን እንደሚሻው ሁሉ የሰው ልጆችን በንጥረ ነገሮች በበለፀገ ተመጣጣኝ ምግብ መመገቡም እንዲሁ በሳይንስ የታገዘና የተቀናጀ ዘላቂ ዓለም አቀፋዊ ተግባርን ይጠይቃል፡፡
ምንጭ፡ ቴክ ሳይንስ መሔት (ቅፅ 5 ቁ.17) እና Nature
-----------------------------
የአመጋገብ ባህላችንን መቀየሩ ቀላል ቢሆን ኖሮ በንጥረ ነገሮች የበለፀገ ተመጣጣኝ ምግብ ካለመመገብ ጋራ የተያያዙ ሁሉም ችግሮች ከዘመናት በፊት በተወገዱ ነበር፡፡ ሁሉም የምድራችን ነዋሪም በጤና ሊያቆየው የሚችለውን ምግብ በበቂ ሁኔታ ማግኘት በቻለ ነበር፡፡ 44 የዓለም ሀገራትን ተሳታፊ አድርጎ በአውሮፓውያኑ 1943 በተካሄደው ታሪካዊው የሆት ስፕሪንግ ምግብና ግብርና ኮንፈረንስ ላይ “ደህንነቱ የተጠበቀ በቂና ዘላቂ የምግብ አቅርቦት ለሁሉም” የሚለውን ሀሳብ ወደ ዓለም መድረክ የመጣና እንዲሁም ከሰላሳ ዓመታት በኋላ የተካሄደው የ1974ቱን የሮም የምግብ እና ግብርና ኮንፈረንስ ላይ ሁሉም የሰው ልጅ ከረሀብ ነፃ የመሆን እና ለተሟላ እድገት መረጋገጥ መሰረታዊ በሆኑ ንጥረ ነገሮች የዳበረ ምግብን የማግኘት መብት እንዳለው የተመጠ ቢሆንም ይህ ሁሉ ግን በምኞት ብቻ የቀረ ሆኗል፡፡
እውነታው እኛ የሰው ልጆች ዛሬም መጠነ ሰፊ የአመጋገብ ችግር ውስጥ መሆናችን ነው፡፡ ሁኔታው እጅግ የተወሳሰበ እና ብዙ ነገሮችን የያዘ ቢሆንም ቅሉ እንዲሁ በጠቅላላው ስናየው ግን አሁንም ብዙዎች ይራባሉ፣ በንጥረ ነገሮች የበለፀገ ተመጣጣኝ ምግብን በማግኘት ረገድ በደሃ እና ሀብታም ሀገራት ወይም ክፍለዓተ ዓለማት መካከል ያለው ልዩነት እጅጉን ሰፊ ነው፣ ከምርት እስከ ማከፋፈል ድረስ የሚዘረጋው የምግብ አቅርቦት ስርዓታችንም ቢሆን እኛንም ሆነ ምድራችንን እየጎዳ ይገኛል፡፡ ወደ አንደኛ ዓመቱ የተጠጋው የኮቪድ-19 ወረርሺኝ ደግሞ በምግብ ስርዓታችን ውስጥ ያሉ ችግሮችን ይባስ ያጋለጠ ሆኗል፡፡ የፖለቲካ፣ ምጣኔ-ሐብት እና ባህል ተግዳሮቶችም ዘላቂ በሆነ ሁኔታ ዓለም አቀፋዊውን የዓመጋገብ ልማድ እንዳይለወጥ አድርገዋል፡፡ የቱን እንመገብ በሚለው ላይ ከስምምነት ተደረሰ ብንልም እንኳን ይህን በስፋት መተግበሩ ትልቅ እና በደንብም ያልተጠና ተግዳሮት ነው፡፡
የስነ-ምግብ ተመራማሪዎች አንደሚያሰቀምጡት ከሆነ ለሰው ልጆች አካላዊም ሆነ አዕምሮአዊ ጤና ብሎም ለተፈጥሮ አካባቢ ተስማሚነት ከስጋና ስጋ ተዋፅዖዎች ይልቅ በዋናነት እፅዋትን መሰረት ያደረገ አመጋገብን መከተሉ አስፈላጊ ነው፡፡
ግን ደግሞ ያለ መፍትሄ ፍለጋ ዝም ብለን አልተቀመጥንም፤ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የተለያዩ እርምጃዎች በመወሰድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ በግብርና የሚገኘውን ስጋ ለመቀነስ በዓለም ዙርያ ያሉ ተመራማሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ልናገኛቸው የምንችላቸው የፕሮቲን አማራጮችን ወደ መመገቢያ ትሪያችን ለማምጣት እየታተሩ ይገኛሉ፡፡ አሁን ላይ በሚወጡ ትንበያዎች መሰረትም የዛሬ 30 ዓመት በሰው ሰራሽ መንገዶች ከሚከወነው የአሳ እርባታ (Aquaculture) የሚገነው የአሳ ምርት ከተፈጥሮ የውሃ አካላት ተጠምዶ ከሚገኘው የላቀ ምርትን እንደሚያስገኝ ነው፡፡ የግብርና ምርትን የሚያሳድጉ ግን ደግሞ የተፈጥሮ አካባቢንም በዘላቂነት የሚጠብቁ የግብርና ስልቶችን የመጠቀም ልምዳችንም ከጊዜ ወደ ጊዜ በማደግ ላይ ይገኛል፡፡
በአውሮፓውያኑ 2050 በምድራችን ላይ የሚኖረው ሰው ብዛት 10 ቢሊዮን እንደሚደርስ ከትንበያዎች መረዳት እንችላለን፡፡ ይህ አሁን ባለው ህዝብ ላይ ሌላ የቻይናን ህዝብ ሁለት እጥፍ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ አዳዲስ ምግብ ፈላጊ ነዋሪዎችን መጨመር ማለት ነውና ለዚህ ሁሉ ህዝብ የተመጣጠነ ምግብንም አቅርቦ የምንኖርባት ምድርንም ከከፋ ጉዳት ጠብቆ መጓዙ ሁሉን አቀፍ የጋራ ስራን ይጠይቃል፡፡ ታድያ ዘላቂ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ለሁላችንም የሚያረጋግጥ መፍትሄ ከአንድ ወገን ብቻ ማግነቱ ለስኬት አይረዳም፡፡ አሁን ያለንበት የኮቪድ-19 ወረርሺኝ የተቀናጀና ሁሉን ያስተባበረ ዓለም አቀፋዊ ምላሽን እንደሚሻው ሁሉ የሰው ልጆችን በንጥረ ነገሮች በበለፀገ ተመጣጣኝ ምግብ መመገቡም እንዲሁ በሳይንስ የታገዘና የተቀናጀ ዘላቂ ዓለም አቀፋዊ ተግባርን ይጠይቃል፡፡
ምንጭ፡ ቴክ ሳይንስ መሔት (ቅፅ 5 ቁ.17) እና Nature
የ3D ማተሚያዎች የሚያስከትሉት የጤና ችግር
**********************
የ3D ማተሚያዎች የሚለቋቸው ቅንጣቶች ወደ ሳንባችን ዘልቀው በመግባት ከፍተኛ የጤና ችግር እንደሚያስከትሉ ተነገረ፡፡ ተመራማሪዎች ይህ ተፈላጊነቱ ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ የመጣው የ3D ህትመት በተጠቃሚዎች እንዲሁም በህጻናት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን የጤና እክል ከፍተኛ ሆኖ በመታየቱ ትልቅ ጥያቄ አንስተውበታል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ በተለይ በቤት ውስጥ፣ በትምህርት ቤቶች፣ በቤተ-መጽሐፍቶች እና በሌሎች ሰዎች በብዛት ጊዜያቸውን በሚያሳልፉባቸው ቦታዎች ተፈላጊነቱ እየጨመረ መጥቷል፡፡
በህትመት ወቅት የሚለቀቁት ብናኞች በጣም ጥቃቅን በመሆናቸው ወደ ሳንባችን ዘልቀው መግባት የሚችሉ ሲሆኑ የአንድን አካባቢ የአየር ጥራት በመቀነስ የህብረተሰብ ጤና ጉዳት ያስከትላሉ፡፡ ለጊዜው የተለያዩ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎችን መጠቀም እንደ መፍትሔ የተወሰደ ቢሆንም ዘለቄታዊ መፍትሔ ሊሆን እንደማይችል ግን ተመራማሪዎቹ ይናገራሉ፡፡
በያዝነው የታህሳስ ወር ቁጥራቸው ብዙ የሆነ የ3D ማተሚያ ብናኞችን መጠን፣ በአየር ላይ ያላቸውን የቆይታ ጊዜ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ጥናቶች በኢንተርኔት በተካሄደው አመታዊው ሊደርሱ የሚችሉ ጉዳቶችን የሚተነትን ጉባኤ (Society for Risk Analysis) ቀርበዋል፡፡
ለ3D ህትመት የሚስፈልጉት መሰረታዊ ግብዓቶች ቴርሞፕላስቲክ፣ ብረት፣ ብረት ነክ ያልሆኑ ነገሮች፣ እንዲሁም ተቀጣጣይ የሆኑና ተቀጣጣይ ያልሆኑ ኬሚካሎች ናቸው፡፡ የህትመት ስራው ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ በሂደቱ የተለያዩ የኬሚካል ተረፈ ምርቶችና ብናኞች ይለቀቃሉ፡፡ በተሰሩ ጥናቶችም እነዚህ ብናኖች በሰዎች የሳንባ ህዋሳት ላይ ጉዳት እንደሚደርሱ ታውቋል፡፡
ይህ የህትመት ሂደት አለማችን በእጅጉ እየተጎሳቆለችበት ያለውን የፕላስቲክ ምርቶች ብክለት ለመቀነስ የሚስችልና ከዋጋ አንጻርም ቀላል በመሆኑ አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ ነው፡፡ ነገር ግን በጊዜ ሂደት በሰዎች ጤና ላይ ጉዳት የሚያደር ከሆነ አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው ነው ሲሉ በዘርፉ ላይ ጥናት ያካሔዱ ተመራማሪዎች ይመክራሉ፡፡ በዚህም የ3D ህትመት ቴክኖሎጂ እየተስፋፋ የሚሔድ በመሆኑ አምራቾች፣ ተቆጣጣሪዎችና ተጠቃሚዎች ስጋትን በሚቀንስ መልኩ ስራዎችን መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
**********************
የ3D ማተሚያዎች የሚለቋቸው ቅንጣቶች ወደ ሳንባችን ዘልቀው በመግባት ከፍተኛ የጤና ችግር እንደሚያስከትሉ ተነገረ፡፡ ተመራማሪዎች ይህ ተፈላጊነቱ ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ የመጣው የ3D ህትመት በተጠቃሚዎች እንዲሁም በህጻናት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን የጤና እክል ከፍተኛ ሆኖ በመታየቱ ትልቅ ጥያቄ አንስተውበታል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ በተለይ በቤት ውስጥ፣ በትምህርት ቤቶች፣ በቤተ-መጽሐፍቶች እና በሌሎች ሰዎች በብዛት ጊዜያቸውን በሚያሳልፉባቸው ቦታዎች ተፈላጊነቱ እየጨመረ መጥቷል፡፡
በህትመት ወቅት የሚለቀቁት ብናኞች በጣም ጥቃቅን በመሆናቸው ወደ ሳንባችን ዘልቀው መግባት የሚችሉ ሲሆኑ የአንድን አካባቢ የአየር ጥራት በመቀነስ የህብረተሰብ ጤና ጉዳት ያስከትላሉ፡፡ ለጊዜው የተለያዩ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎችን መጠቀም እንደ መፍትሔ የተወሰደ ቢሆንም ዘለቄታዊ መፍትሔ ሊሆን እንደማይችል ግን ተመራማሪዎቹ ይናገራሉ፡፡
በያዝነው የታህሳስ ወር ቁጥራቸው ብዙ የሆነ የ3D ማተሚያ ብናኞችን መጠን፣ በአየር ላይ ያላቸውን የቆይታ ጊዜ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ጥናቶች በኢንተርኔት በተካሄደው አመታዊው ሊደርሱ የሚችሉ ጉዳቶችን የሚተነትን ጉባኤ (Society for Risk Analysis) ቀርበዋል፡፡
ለ3D ህትመት የሚስፈልጉት መሰረታዊ ግብዓቶች ቴርሞፕላስቲክ፣ ብረት፣ ብረት ነክ ያልሆኑ ነገሮች፣ እንዲሁም ተቀጣጣይ የሆኑና ተቀጣጣይ ያልሆኑ ኬሚካሎች ናቸው፡፡ የህትመት ስራው ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ በሂደቱ የተለያዩ የኬሚካል ተረፈ ምርቶችና ብናኞች ይለቀቃሉ፡፡ በተሰሩ ጥናቶችም እነዚህ ብናኖች በሰዎች የሳንባ ህዋሳት ላይ ጉዳት እንደሚደርሱ ታውቋል፡፡
ይህ የህትመት ሂደት አለማችን በእጅጉ እየተጎሳቆለችበት ያለውን የፕላስቲክ ምርቶች ብክለት ለመቀነስ የሚስችልና ከዋጋ አንጻርም ቀላል በመሆኑ አስፈላጊነቱ የማያጠያይቅ ነው፡፡ ነገር ግን በጊዜ ሂደት በሰዎች ጤና ላይ ጉዳት የሚያደር ከሆነ አፋጣኝ መፍትሔ የሚያሻው ነው ሲሉ በዘርፉ ላይ ጥናት ያካሔዱ ተመራማሪዎች ይመክራሉ፡፡ በዚህም የ3D ህትመት ቴክኖሎጂ እየተስፋፋ የሚሔድ በመሆኑ አምራቾች፣ ተቆጣጣሪዎችና ተጠቃሚዎች ስጋትን በሚቀንስ መልኩ ስራዎችን መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
TECHIN seminar
በዚህ ሳምንቱ የቴክኢን ሴሚናር “Understanding and Managing Change” በሚል ርዕስ በአቶ አብዱለጢፍ ሀቢብ ገለፃ አቅራቢነት የሚመራ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡
ስፍራው፡ 4 ኪሎ በሚገኘው የዋናው ቢሮዋችን መሰብሰቢያ አዳራሽ
ቀን፡ ነገ ሐሙስ ታህሳስ 07፤ 2013 ዓ.ም
ሰዓት፡ ከጠዋቱ 3፡00-4፡30
In this week’s TECHIN seminar Mr. Abduletif Habib will discuss Understanding and Managing Change.
Location፡ TECHIN meeting hall in our head office (4 kilo)
Date: Thursday, December 17, 2020
Time: 9:00-10:30 AM
በዚህ ሳምንቱ የቴክኢን ሴሚናር “Understanding and Managing Change” በሚል ርዕስ በአቶ አብዱለጢፍ ሀቢብ ገለፃ አቅራቢነት የሚመራ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡
ስፍራው፡ 4 ኪሎ በሚገኘው የዋናው ቢሮዋችን መሰብሰቢያ አዳራሽ
ቀን፡ ነገ ሐሙስ ታህሳስ 07፤ 2013 ዓ.ም
ሰዓት፡ ከጠዋቱ 3፡00-4፡30
In this week’s TECHIN seminar Mr. Abduletif Habib will discuss Understanding and Managing Change.
Location፡ TECHIN meeting hall in our head office (4 kilo)
Date: Thursday, December 17, 2020
Time: 9:00-10:30 AM
20ዎቹ የምንግዜም ታላላቅ ኢኖቬሽኖች
በሰው ልጆች ረዥም የህይወት ጉዞ ውስጥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚና እንዲ በቀላሉ የሚገለፅ ጉዳይ አይደለም፡፡ ሰዎች ወደዚች ምድር ከመጡ አንስቶ አካላዊውን ዓለም ለመግራት የሚያስችሉ የተለያዩ ፈጠራዎችንና የኢኖቬሽን ውጤቶች ያለማቋረጥ ሲተገብሩ ቆይተዋል፡፡ እነዚህ መሳሪያዎች አለም አሁን ያላትን መልክ ያጎናፀፏት እና የቀጣዩንም ትውልድ እጣ ፋንታ በበጎም ይሁን በክፉ የመወሰን አቅማቸው በእጅጉ የተጠበቀ ነው፡፡ አለማችን እስካሁን ያየቻቸውን የኢኖቬሽን ውጤቶች ለሰው ልጆች ከሰጡት ግልጋሎት እና በታሪክ ውስጥ ካላቸው ተጽዕኖ አንፃር ተመልክተን ለማስቀመጥ ከሞከርን የሚከተሉት ኢኖቬሽኖች ከምንግዜም ታላላቆቹ መካከል ይገኙበታል፡፡ በዘመን ቅደም ተከተል ፡
1. እሳት (FIRE) - ስለእሳት ስናነሳ ብዙዎች የሚከራከሩበት ጉዳይ ቢኖር እሳት ተፈለሰፈ ከሚባል ይልቅ ተገኝቷል የሚለው ሃሳብ እጅግ ተስማሚ መሆኑን ነው፡፡ ቀደምት የሰው ዘሮች እሳትን እንዴት መፍጠር እና መቆጣጠር እንደሚችሉ ከማወቃቸው በፊት የእሳትን አደጋዎች በየአጋጣሚው ተመልክተው ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን የእሳትን ምንነት ከተረዱና የሚሰጣቸውን ጥቅም ካወቁ በኋላ እሳትን እንደ አንድ ትልቅ መገልገያ መጠቀም ጀምረዋል፡፡ አንዳንድ የአርኪዎሎጂ አጥኝዎች እሳት ጥቅም ላይ የዋለው ከ2 ሚሊዮን አመት በፊት ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ 125 ሺ አመታት እንዳስቆጠረ ይገልፃሉ፡፡ ይህ ክርክር ምንም ተባለ ምንም በሰው ልጆች ታሪክ ታላቅ ግኝት የሆነው እሳት ሰዎች ራሳቸውን ከተለያዩ ነገሮች እንዲከላከሉ እና ማብሰል የሚባለውን ትልቅ ክህሎት እንዲረዱ ያስቻል አስገራሚ ግኝት ነው፡፡
2. ተሽከርካሪ ጎማ (WHEEL) - ይህ ፈጠራ የተገኘው በ3500 ዓመተ ዓለም (B.C) በሜሶፖታሚያ የስልጣኔ ዘመን ነበር፡፡ የሜሶፖታሚያ ህዝቦች ይህንን አስገራሚ ፈጠራ የሸክላ ቁሳቁሶችን ለማበጃጀት ሲጠቀሙበት የቆየ ቢሆንም ከሶስትና አራት መቶ አመታት በኋላ ፈጠራው ለሰረገላ ማሽከርከሪያ ጥቅም ላይ ከዋለ በኋላ የመሳሪያው ተፅዕኖ እጅግ እየናኘ ሄዷል፡፡ ተሽከርካሪ ጎማ ለሰው ልጆች የመጓጓዣ እና የንድግ ስርዓት መፈጠር ትልቅ ሚና ያለው ግኝት ነው፡፡
3. ኦፕቲካል ሌንሶች (OPTICAL LENSES) - የሰዎችን የእይታ አቅም ይበልጥ ለመጨመር እንደ ኦፕቲካል ሌንሶች ያሉ አስገራሚ ግኝቶች እጅግ ወሳኝ ነበሩ፡፡ ረዥም የፈጠራ ሂደት የነበራቸው እነዚህ ግኝቶች በጥንቱ የግብፅ እና የሜሶፖታሚያ የስልጣኔ ዘመን እንደበለፀጉ የሚታመን ሲሆን ከግሪክ የተገኙት የብርሃን ንድፈ ሃሳቦች ደግሞ ለግኝቱ እውን መሆን ትልቅ ሚና ነበራቸው፡፡ ኦፕቲካል ሌንሶች እንደቴሊቭዥን፣ ፎቶግራፍ እና ፊልም ያሉ ትልልቅ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች እንዲፈጠሩ መንገድ የጠረጉም ናቸው፡፡
4. ኮምፓስ (COMPASS) - ይህ እንቅስቃሴን ለመምራት የተዘየደው የቴክኖሎጂ ግኝት የሰው ልጆችን የአሰሳ ጥበብና አቅም ወደ አዲስ ምዕራፍ በመወሰድ ተተኪ የማይገኝለት አስገራሚ ግኝት ነው፡፡ የመጀሪያዎቹ ኮምፓሶች በተፈጥሮ የመግነጢሳዊ ይዘት ባላቸው የማዕድን ቁራጮች ወይም (lodestone) አማካኝነት የተሰሩ ሲሆን፤ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ 300 እና 200 አመተ አለም አካባቢ በቻይና እንደተሰሩም ይነገራል፡፡
5. ወረቀት (PAPER) - በ100 ዓመተ አለም አካባቢ በቻይና የተፈለሰፈው ይህ ግኘት የሰው ልጆችን የፅህፈት እና ሃሳብን የማጋራት ልምድ በእጅጉ የቀየረ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ ከዚህ ጊዜ በፊት በግብፅ እና በሜክሲኮ የስልጣኔ ዘመናት የተፈለሰፉት እንደ ፓፒረስና አሜት ያሉ የመፃፊያ ቁሶች ለወረቅት መፈጠር አስተዋፅዖ ቢኖራቸውም በቻይና የነበረው ግኝት ግን አሁን ላለው የወረቀት ቴክሎጂ ትልቅ መሰረት የጣለ ነው፡፡
6. ባሩድ (GUNPOWDER) - ከተለያዩ የኬሚካል ንጥረ ነገሮች ተቀይጦ የሚሰራው ይህ ተቀጣጣይ ፈንጂ በ9ኛው ክፍለ ዘመን በቻይና እንደተፈለሰፈ የሚነገር ሲሆን ለዘመናዊው የጦር ቴክኖሎጂ መስፋፋትም ፈር ቀዳጅ የሚባል ነው፡፡ ይህ ግኘት በሰው ልጆች የውጊያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ተፅዕኖ ያሳደረ መሆኑም ይነገርለታል፡፡
7. ማተሚያ (PRINTING PRESS) - እንደአውሮፓውያኑ በ1439 በጀርመናዊው ዮሃንስ ጉተንበርግ የተፈጠረው ይህ መሳሪያ ለሰው ልጆች የአዲስ ህይወት መጀመሪያ ዘመን ተደርጎ በብዙዎች ይወሰዳል፡፡ ይህ አስገራሚ ቴክኖሎጂ በሰዎች እጅ እየተፃፈ የሚሰራጨውን አድካሚ የፅህፈት ስርዓት በሜካናይዝድ ማሽን በመተካት የእውቀት አድማስ በሰዎች ዘንድ በቀላሉ እንዲሰፋፋ እና የሃይማኖት አስተምህሮዎች በአለም ላይ በፍጥነት እንዲናኙ ያስቻለ አስገራሚ ግኘት ነው፡፡
8. ኤሌክትሪክ (ELECTRICITY) - የኤሌክትሪክ ፈጠራ ብዙ ብሩህ አዕምሮዎች ለሺህና ከዚያ በላይ አመታት አስተዋፅዖ ያደረጉበት እፁብ ድንቅ የሆነ የቴክኖሎጂ ግኝት ነው፡፡ በ18ኛው ክፍለ ዘመን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ቤንጃሚን ፍራንክሊን ስለኤሌክትሪክ የነበረውን የአለም መረዳት አንድ እርምጃ ያራመደ የመሪነት አበርክቶት እንደነበረው የሚገለፅ ሲሆን በምርምር ዘርፍ ደረጃ ለመስኩ የሰጠው ሁለንተናዊ ትኩረት የቴክኖሎጂውን እድገት በእጅጉ አፋጥኖታል፡፡ ከዚህ ሂደት በማስከተል በ1879 የቶማስ ኤዲሰን የብርሃን አምፖል መፈጠር የኤሌክትሪክ ቴክኖሎጂ ይበልጥ ወደሰዎች እንዲቀርብ ያስቻለ ክስተት ነው፡፡ ይህ የምንግዜም ታላቅ ፈጠራ የሰው ልጆችን የህይወት መንገድ እስከወዲያኘው የቀየረ ግሩም ቴክኖሎጂ ነው፡፡
9. የእንፋሎት ሞተር (STEAM ENGINE) - በስኮትላንዳዊው የፈጠራ ባለሙያ ጀምስ ዋት ከ1763 እስከ 1775 ተሰራ የሚባለው የእንፋሎት ሞተር ሌላኛው ለሰው ልጆች ትልቅ መሰረት የጣለ አስደናቂ የፈጠራ ውጤት ነው፡፡ ይህ የቴክኖሎጂ ግኝት በጊዜው ለነበሩት ባቡሮች፣ መርከቦች እና በጠቅላለው ለኢንዱስትሪው አብዮት ዋና የሃይል ምንጭ በመሆን ተከትሎ ለመጣው የሰው ልጅ አብርሆት ታላቅ ውለታ ያደረገ አስገራሚ ፈጠራ ነው፡፡
10. የነዳጅ ሞተር (INTERNAL COMBUSTION ENGINE) - በ19ኛው ክፍለዘመን የተዋወቀው ይህ የቴክኖሎጂ ፈጠራ በመጀመሪያ በቤልጄሚያዊው ኢንጅነር ኢትየን ሌኖየር (በ1859) የተፈጠረ ሲሆን ከጥቂት አመታት በኋላ በጀርመናዊው ኒኮላስ ኦቶ ይበልጥ ሊሻሻል ችሏል፡፡ ይህ አስገራሚ ፈጠራ የኬሚካል ኢነርጂን ወደ ሜካኒካል ኢነርጂ በመቀየር ቀድሞ የእንፋሎት ሞተር ሲሰጥ የነበረውን ግልጋሎት በተሻለ ሁኔታ በመተካት ለዘመናዊ መኪናዎችና አውሮፕላኖች ማገልገል የቻለ አስገራሚ ፈጠራ ነው፡፡
ምንጭ፡ Bigthink
ውድ የፔጃችን ተከታዮች 10ን የኢኖቬሽን ውጠቶች በቀጣይ ፅሁፍ የምናቀርብላችሁ ይሆናል፡፡
በሰው ልጆች ረዥም የህይወት ጉዞ ውስጥ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚና እንዲ በቀላሉ የሚገለፅ ጉዳይ አይደለም፡፡ ሰዎች ወደዚች ምድር ከመጡ አንስቶ አካላዊውን ዓለም ለመግራት የሚያስችሉ የተለያዩ ፈጠራዎችንና የኢኖቬሽን ውጤቶች ያለማቋረጥ ሲተገብሩ ቆይተዋል፡፡ እነዚህ መሳሪያዎች አለም አሁን ያላትን መልክ ያጎናፀፏት እና የቀጣዩንም ትውልድ እጣ ፋንታ በበጎም ይሁን በክፉ የመወሰን አቅማቸው በእጅጉ የተጠበቀ ነው፡፡ አለማችን እስካሁን ያየቻቸውን የኢኖቬሽን ውጤቶች ለሰው ልጆች ከሰጡት ግልጋሎት እና በታሪክ ውስጥ ካላቸው ተጽዕኖ አንፃር ተመልክተን ለማስቀመጥ ከሞከርን የሚከተሉት ኢኖቬሽኖች ከምንግዜም ታላላቆቹ መካከል ይገኙበታል፡፡ በዘመን ቅደም ተከተል ፡
1. እሳት (FIRE) - ስለእሳት ስናነሳ ብዙዎች የሚከራከሩበት ጉዳይ ቢኖር እሳት ተፈለሰፈ ከሚባል ይልቅ ተገኝቷል የሚለው ሃሳብ እጅግ ተስማሚ መሆኑን ነው፡፡ ቀደምት የሰው ዘሮች እሳትን እንዴት መፍጠር እና መቆጣጠር እንደሚችሉ ከማወቃቸው በፊት የእሳትን አደጋዎች በየአጋጣሚው ተመልክተው ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን የእሳትን ምንነት ከተረዱና የሚሰጣቸውን ጥቅም ካወቁ በኋላ እሳትን እንደ አንድ ትልቅ መገልገያ መጠቀም ጀምረዋል፡፡ አንዳንድ የአርኪዎሎጂ አጥኝዎች እሳት ጥቅም ላይ የዋለው ከ2 ሚሊዮን አመት በፊት ነው ሲሉ ሌሎች ደግሞ 125 ሺ አመታት እንዳስቆጠረ ይገልፃሉ፡፡ ይህ ክርክር ምንም ተባለ ምንም በሰው ልጆች ታሪክ ታላቅ ግኝት የሆነው እሳት ሰዎች ራሳቸውን ከተለያዩ ነገሮች እንዲከላከሉ እና ማብሰል የሚባለውን ትልቅ ክህሎት እንዲረዱ ያስቻል አስገራሚ ግኝት ነው፡፡
2. ተሽከርካሪ ጎማ (WHEEL) - ይህ ፈጠራ የተገኘው በ3500 ዓመተ ዓለም (B.C) በሜሶፖታሚያ የስልጣኔ ዘመን ነበር፡፡ የሜሶፖታሚያ ህዝቦች ይህንን አስገራሚ ፈጠራ የሸክላ ቁሳቁሶችን ለማበጃጀት ሲጠቀሙበት የቆየ ቢሆንም ከሶስትና አራት መቶ አመታት በኋላ ፈጠራው ለሰረገላ ማሽከርከሪያ ጥቅም ላይ ከዋለ በኋላ የመሳሪያው ተፅዕኖ እጅግ እየናኘ ሄዷል፡፡ ተሽከርካሪ ጎማ ለሰው ልጆች የመጓጓዣ እና የንድግ ስርዓት መፈጠር ትልቅ ሚና ያለው ግኝት ነው፡፡
3. ኦፕቲካል ሌንሶች (OPTICAL LENSES) - የሰዎችን የእይታ አቅም ይበልጥ ለመጨመር እንደ ኦፕቲካል ሌንሶች ያሉ አስገራሚ ግኝቶች እጅግ ወሳኝ ነበሩ፡፡ ረዥም የፈጠራ ሂደት የነበራቸው እነዚህ ግኝቶች በጥንቱ የግብፅ እና የሜሶፖታሚያ የስልጣኔ ዘመን እንደበለፀጉ የሚታመን ሲሆን ከግሪክ የተገኙት የብርሃን ንድፈ ሃሳቦች ደግሞ ለግኝቱ እውን መሆን ትልቅ ሚና ነበራቸው፡፡ ኦፕቲካል ሌንሶች እንደቴሊቭዥን፣ ፎቶግራፍ እና ፊልም ያሉ ትልልቅ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች እንዲፈጠሩ መንገድ የጠረጉም ናቸው፡፡
4. ኮምፓስ (COMPASS) - ይህ እንቅስቃሴን ለመምራት የተዘየደው የቴክኖሎጂ ግኝት የሰው ልጆችን የአሰሳ ጥበብና አቅም ወደ አዲስ ምዕራፍ በመወሰድ ተተኪ የማይገኝለት አስገራሚ ግኝት ነው፡፡ የመጀሪያዎቹ ኮምፓሶች በተፈጥሮ የመግነጢሳዊ ይዘት ባላቸው የማዕድን ቁራጮች ወይም (lodestone) አማካኝነት የተሰሩ ሲሆን፤ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ 300 እና 200 አመተ አለም አካባቢ በቻይና እንደተሰሩም ይነገራል፡፡
5. ወረቀት (PAPER) - በ100 ዓመተ አለም አካባቢ በቻይና የተፈለሰፈው ይህ ግኘት የሰው ልጆችን የፅህፈት እና ሃሳብን የማጋራት ልምድ በእጅጉ የቀየረ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ ከዚህ ጊዜ በፊት በግብፅ እና በሜክሲኮ የስልጣኔ ዘመናት የተፈለሰፉት እንደ ፓፒረስና አሜት ያሉ የመፃፊያ ቁሶች ለወረቅት መፈጠር አስተዋፅዖ ቢኖራቸውም በቻይና የነበረው ግኝት ግን አሁን ላለው የወረቀት ቴክሎጂ ትልቅ መሰረት የጣለ ነው፡፡
6. ባሩድ (GUNPOWDER) - ከተለያዩ የኬሚካል ንጥረ ነገሮች ተቀይጦ የሚሰራው ይህ ተቀጣጣይ ፈንጂ በ9ኛው ክፍለ ዘመን በቻይና እንደተፈለሰፈ የሚነገር ሲሆን ለዘመናዊው የጦር ቴክኖሎጂ መስፋፋትም ፈር ቀዳጅ የሚባል ነው፡፡ ይህ ግኘት በሰው ልጆች የውጊያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ተፅዕኖ ያሳደረ መሆኑም ይነገርለታል፡፡
7. ማተሚያ (PRINTING PRESS) - እንደአውሮፓውያኑ በ1439 በጀርመናዊው ዮሃንስ ጉተንበርግ የተፈጠረው ይህ መሳሪያ ለሰው ልጆች የአዲስ ህይወት መጀመሪያ ዘመን ተደርጎ በብዙዎች ይወሰዳል፡፡ ይህ አስገራሚ ቴክኖሎጂ በሰዎች እጅ እየተፃፈ የሚሰራጨውን አድካሚ የፅህፈት ስርዓት በሜካናይዝድ ማሽን በመተካት የእውቀት አድማስ በሰዎች ዘንድ በቀላሉ እንዲሰፋፋ እና የሃይማኖት አስተምህሮዎች በአለም ላይ በፍጥነት እንዲናኙ ያስቻለ አስገራሚ ግኘት ነው፡፡
8. ኤሌክትሪክ (ELECTRICITY) - የኤሌክትሪክ ፈጠራ ብዙ ብሩህ አዕምሮዎች ለሺህና ከዚያ በላይ አመታት አስተዋፅዖ ያደረጉበት እፁብ ድንቅ የሆነ የቴክኖሎጂ ግኝት ነው፡፡ በ18ኛው ክፍለ ዘመን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ቤንጃሚን ፍራንክሊን ስለኤሌክትሪክ የነበረውን የአለም መረዳት አንድ እርምጃ ያራመደ የመሪነት አበርክቶት እንደነበረው የሚገለፅ ሲሆን በምርምር ዘርፍ ደረጃ ለመስኩ የሰጠው ሁለንተናዊ ትኩረት የቴክኖሎጂውን እድገት በእጅጉ አፋጥኖታል፡፡ ከዚህ ሂደት በማስከተል በ1879 የቶማስ ኤዲሰን የብርሃን አምፖል መፈጠር የኤሌክትሪክ ቴክኖሎጂ ይበልጥ ወደሰዎች እንዲቀርብ ያስቻለ ክስተት ነው፡፡ ይህ የምንግዜም ታላቅ ፈጠራ የሰው ልጆችን የህይወት መንገድ እስከወዲያኘው የቀየረ ግሩም ቴክኖሎጂ ነው፡፡
9. የእንፋሎት ሞተር (STEAM ENGINE) - በስኮትላንዳዊው የፈጠራ ባለሙያ ጀምስ ዋት ከ1763 እስከ 1775 ተሰራ የሚባለው የእንፋሎት ሞተር ሌላኛው ለሰው ልጆች ትልቅ መሰረት የጣለ አስደናቂ የፈጠራ ውጤት ነው፡፡ ይህ የቴክኖሎጂ ግኝት በጊዜው ለነበሩት ባቡሮች፣ መርከቦች እና በጠቅላለው ለኢንዱስትሪው አብዮት ዋና የሃይል ምንጭ በመሆን ተከትሎ ለመጣው የሰው ልጅ አብርሆት ታላቅ ውለታ ያደረገ አስገራሚ ፈጠራ ነው፡፡
10. የነዳጅ ሞተር (INTERNAL COMBUSTION ENGINE) - በ19ኛው ክፍለዘመን የተዋወቀው ይህ የቴክኖሎጂ ፈጠራ በመጀመሪያ በቤልጄሚያዊው ኢንጅነር ኢትየን ሌኖየር (በ1859) የተፈጠረ ሲሆን ከጥቂት አመታት በኋላ በጀርመናዊው ኒኮላስ ኦቶ ይበልጥ ሊሻሻል ችሏል፡፡ ይህ አስገራሚ ፈጠራ የኬሚካል ኢነርጂን ወደ ሜካኒካል ኢነርጂ በመቀየር ቀድሞ የእንፋሎት ሞተር ሲሰጥ የነበረውን ግልጋሎት በተሻለ ሁኔታ በመተካት ለዘመናዊ መኪናዎችና አውሮፕላኖች ማገልገል የቻለ አስገራሚ ፈጠራ ነው፡፡
ምንጭ፡ Bigthink
ውድ የፔጃችን ተከታዮች 10ን የኢኖቬሽን ውጠቶች በቀጣይ ፅሁፍ የምናቀርብላችሁ ይሆናል፡፡
“ጆሮውን ሰጥቶ ለሚሰማ አለማችን ሁሌም ቢሆን የለዉጥ ያለህ በሚል የማያቋርጥ ጩኸት ውሰጥ እንዳለች ያስተዉላል”
===================
“ለዉጥን መረዳትና ማስተዳደር” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የዚህ ሳምንቱ የቴክኢን ሴሚናር ዛሬ ማለዳ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ተካሂዷል፡፡ መድረኩ ላይ በኢንስቲትዩቱ ውስጥ በተመራማሪት በሚያገለግሉት አቶ አብዱለጢፍ ሀቢብ አማካኝነት ስለ ለውጥ ምንነት፣ ባህርያት እና ሌሎችም ዝርዝር ጉዳዮች ገለፃ ቀርቦበታል፡፡
“ጆሮውን ሰጥቶ ለሚሰማ አለማችን ሁሌም ቢሆን የለዉጥ ያለህ በሚል የማያቋርጥ ጩኸት ውሰጥ እንዳለች ያስተዉላል” ያለው አቶ አብዱለጢፍ እኛ የሰው ልጆች ከአደን ሕይወት አንስቶ አሁን እስካለንበት የመረጃ ዘመን ድረስ ታላላቅ ለውጦችን ማስተናገዳችንን ጠቅሷል፡፡ በለውጥ ሂደት ውስጥ ሁለት ተፃራሪ ኃይሎች፤ ማለትም ቆስቋሽ እና መካች ኃይሎች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን በዚህ የለውጥ ሂደት ውስጥም ተቀዳሚው ፈተና የአመለካከት ውስንነት መሆኑ ተቀምጧል፡፡ በተጨማሪም የለውጥ ዋና ምሰሶዎች የሆኑትን ስለ ለውጥ አስፈላጊነት ግንዛቤ መፍጠር፣ በለውጡ ላይ ለመሳተፍ እና ለመደገፍ ያለ ጽኑ ፍላጎት፣ ለውጡ እንዴት እንደሚመጣ ያለ ዕውቀት፣ ለውጡን ለመተግበር /ለማከናወን የሚያስፈልግ ችሎታ/ክሕሎት እና ለውጡን ለማስቀጠል የሚደረገግ ማበረታቻ በአግባቡ ተሟልተው ከተገኙ አንድን ለውጥ ስኬታማ እንደሚያደርገው ተነግሯል፡፡
የለውጥ አመራር ሂደቶችን በተመለከተም ለውጥ ሲሳካ ወይም ተሰናክሎ የሚቀርበት ዋናው ምክንያት የለውጥ አመራሩን ሰብዓዊ ጎን በበቂ ሁኔታ መምራት ባለመቻሉ ነው ሲል አቶ አብዱለጢፍ ተናግሯል፡፡ አከሎም የለውጥ አመራር በዋናነት የለውጥ እንቅፋቶችን ለመምራት፣ የስኬት ዕድሉን ለማስፋት እና የሽግግር ጊዜውን ለማሳጠር እንደሚያስፈል ተናገሮ በአንፃሩ የለውጥ ሰብዓዊ ጎኑን መምራት አለመቻል የአሰራሮች ወደ ኃላ መመለስ፣ የምርታማነት መቀነስ፣ ግልፅ እና ስውር ተቃዉሞዎች እንዲሁም የእኛ እና የእነሱ የሚል ቡድናዊ አመለካከት መፈጠርን ጨምሮ በርካታ ተፅዕኖዎችን እንደሚፈጥር አስቀምጧል፡፡
መድረኩ ሌሎች የኢንስቲትዩቱ ሰራተኞችንም ተሳታፊ ያደረገ እንደመሆኑ የለውጥ አይነቶች፣ ከማህበረሰብ አንፃር ስለሚኖረው ግበረ መልስ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ቀርበው በአቶ አብዱለጢፍ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
===================
“ለዉጥን መረዳትና ማስተዳደር” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የዚህ ሳምንቱ የቴክኢን ሴሚናር ዛሬ ማለዳ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ተካሂዷል፡፡ መድረኩ ላይ በኢንስቲትዩቱ ውስጥ በተመራማሪት በሚያገለግሉት አቶ አብዱለጢፍ ሀቢብ አማካኝነት ስለ ለውጥ ምንነት፣ ባህርያት እና ሌሎችም ዝርዝር ጉዳዮች ገለፃ ቀርቦበታል፡፡
“ጆሮውን ሰጥቶ ለሚሰማ አለማችን ሁሌም ቢሆን የለዉጥ ያለህ በሚል የማያቋርጥ ጩኸት ውሰጥ እንዳለች ያስተዉላል” ያለው አቶ አብዱለጢፍ እኛ የሰው ልጆች ከአደን ሕይወት አንስቶ አሁን እስካለንበት የመረጃ ዘመን ድረስ ታላላቅ ለውጦችን ማስተናገዳችንን ጠቅሷል፡፡ በለውጥ ሂደት ውስጥ ሁለት ተፃራሪ ኃይሎች፤ ማለትም ቆስቋሽ እና መካች ኃይሎች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን በዚህ የለውጥ ሂደት ውስጥም ተቀዳሚው ፈተና የአመለካከት ውስንነት መሆኑ ተቀምጧል፡፡ በተጨማሪም የለውጥ ዋና ምሰሶዎች የሆኑትን ስለ ለውጥ አስፈላጊነት ግንዛቤ መፍጠር፣ በለውጡ ላይ ለመሳተፍ እና ለመደገፍ ያለ ጽኑ ፍላጎት፣ ለውጡ እንዴት እንደሚመጣ ያለ ዕውቀት፣ ለውጡን ለመተግበር /ለማከናወን የሚያስፈልግ ችሎታ/ክሕሎት እና ለውጡን ለማስቀጠል የሚደረገግ ማበረታቻ በአግባቡ ተሟልተው ከተገኙ አንድን ለውጥ ስኬታማ እንደሚያደርገው ተነግሯል፡፡
የለውጥ አመራር ሂደቶችን በተመለከተም ለውጥ ሲሳካ ወይም ተሰናክሎ የሚቀርበት ዋናው ምክንያት የለውጥ አመራሩን ሰብዓዊ ጎን በበቂ ሁኔታ መምራት ባለመቻሉ ነው ሲል አቶ አብዱለጢፍ ተናግሯል፡፡ አከሎም የለውጥ አመራር በዋናነት የለውጥ እንቅፋቶችን ለመምራት፣ የስኬት ዕድሉን ለማስፋት እና የሽግግር ጊዜውን ለማሳጠር እንደሚያስፈል ተናገሮ በአንፃሩ የለውጥ ሰብዓዊ ጎኑን መምራት አለመቻል የአሰራሮች ወደ ኃላ መመለስ፣ የምርታማነት መቀነስ፣ ግልፅ እና ስውር ተቃዉሞዎች እንዲሁም የእኛ እና የእነሱ የሚል ቡድናዊ አመለካከት መፈጠርን ጨምሮ በርካታ ተፅዕኖዎችን እንደሚፈጥር አስቀምጧል፡፡
መድረኩ ሌሎች የኢንስቲትዩቱ ሰራተኞችንም ተሳታፊ ያደረገ እንደመሆኑ የለውጥ አይነቶች፣ ከማህበረሰብ አንፃር ስለሚኖረው ግበረ መልስ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ቀርበው በአቶ አብዱለጢፍ ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡