አረንጓዴ ሽንት የሸናው ግለሰብ
ሰሞኑን ታሞ ሆስፒታል አልጋ ላይ የተኙ አንድ ግለሰብ ሽንት አረንጓዴ ቀለምን መያዙ አግራሞትን ፈጥሯል፡፡ ሆኖም ድንጋጤን የሚያጭረው ይህ ክስተት ጉዳት አልባና ግለሰቡ የሚደግላቸው ህክምና ውጤት ሆኖ ተገኝቷል፡፡
በ62 ዓመት ዕድሜ ላይ የሚገኙት ግለሰቡ ክሮኒክ ኦብስትራክቲቭ ፓልሞናሪ ዲዚዝ (COPD) የተባለ የሳንባ በሽታ አጋጥሞት መተንፈስ ስለተቸገሩ ነው ወደ ሆስፒታሉ ድንገተኛ ክፍል ውስጥ እንዲገቡ የተደረገው፡፡ ሰውየው ለህይወታቸው ሊያሰጋ በሚችል አኳሀንም በደማቸው ውስጥ ከፍተኛ የካርበን ዳይ ኦክሳይድ ይዘት ተገኝቶባቸዋል፡፡ ይህን ተከትሎም ሆስፒታሉ ውስጥ ወዳለው የከፍተኛ ክትትል ክፍል ውስጥ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን የአተነፋፈስ መርጃ መሳርያ እና ፕሮፎፖል የተባለ የማደንዘዣ መድሀኒት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከአምስት ቀናት ቆይታ በኋላ በከረጢት ውስጥ ሲሰበሰብ የነበረው የታማሚው ሽንት ወደ አረንጓዴነት ለመቀየር በቅቷል፡፡
አረንጓዴ ሽንት በህክምና የጎንዮሽ ተፅዕንዖ፣ አንዳንድ ኢንፌክሽኖች እና የጉበት ችግርን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል፡፡ በዚህ ግለሰብ ላይ የሆነው ግን በፕሮፎፖል ሳብያ የመጣ ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ ይህን አይነት ህክምና ለጀነራል አንስቴዢያ ተብሎ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን አልፎ አልፎም የሰዎችን ሽንት ወደ አረንጓዴነት ሲቀይር ይታያል፡፡ እንዴት ሆነ የሚለው ግን በዘርዝር የሚታወቅ አልሆነም፡፡ ሆኖም አንዳንድ የፕሮፎፖሉ ቁሶች ተሰባብረው ሲወጡና ይህም ከጉበት ይልቅ በኩላሊት አማካኝነት ሲሆን (ለወትሮ የፕሮፎፖል ኬሚካል አፀግብሮት ወይም ሜታቦሊዝም የሚደረገው ጉበት ውስጥ ነው) ሊከሰት እንደሚችል ከ5 ዓታት በፊት ጆርናል ኦፍ ክሊኒካል ኤንድ ዲያግኖስቲክ ሪሰርች ላይ የወጣ ምርምር አመላክቶ ነበር፡፡ ሆኖም ይህ የሽንት ቀለም ለውጥ ጉዳት የሌለው እና የህክምናውን መቋረጥ ተከትሎ የሚያቆም ነው፡፡ እኚህ ታማሚም ፕሮፎፖሉ ሲነሳለት ነገሮች ወደ ቀድሞ ጤናማ ይዞታቸው ተመልሰውለታል፡፡ ኋላም ለሁለት ሳምንታት በሆስፒታሉ ቆይቶ ወደ ማገገሚያ ማዕከል አቅንቷል፡፡
የሰው ልጆች ሽንት ወደ አረንጓዴነት ብቻ ሳይሆን ሌሎች ቀለሞችንም ይዞ ሊወጣ ይችላል፡፡ ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት 2019 ላይ የሽንት መሰብሰቢያ ከረጢት ውስጥ የገባ የአንዲት ሴት ሽንት ከረጢቱ ውስጥ በተፈጠረው የኬሚካል አፀግብሮት ሳብያ ወደ ሐምራዊነት ተለውጦ ነበር፡፡
ምንጭ፡ Live Science
ሰሞኑን ታሞ ሆስፒታል አልጋ ላይ የተኙ አንድ ግለሰብ ሽንት አረንጓዴ ቀለምን መያዙ አግራሞትን ፈጥሯል፡፡ ሆኖም ድንጋጤን የሚያጭረው ይህ ክስተት ጉዳት አልባና ግለሰቡ የሚደግላቸው ህክምና ውጤት ሆኖ ተገኝቷል፡፡
በ62 ዓመት ዕድሜ ላይ የሚገኙት ግለሰቡ ክሮኒክ ኦብስትራክቲቭ ፓልሞናሪ ዲዚዝ (COPD) የተባለ የሳንባ በሽታ አጋጥሞት መተንፈስ ስለተቸገሩ ነው ወደ ሆስፒታሉ ድንገተኛ ክፍል ውስጥ እንዲገቡ የተደረገው፡፡ ሰውየው ለህይወታቸው ሊያሰጋ በሚችል አኳሀንም በደማቸው ውስጥ ከፍተኛ የካርበን ዳይ ኦክሳይድ ይዘት ተገኝቶባቸዋል፡፡ ይህን ተከትሎም ሆስፒታሉ ውስጥ ወዳለው የከፍተኛ ክትትል ክፍል ውስጥ እንዲገቡ የተደረገ ሲሆን የአተነፋፈስ መርጃ መሳርያ እና ፕሮፎፖል የተባለ የማደንዘዣ መድሀኒት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከአምስት ቀናት ቆይታ በኋላ በከረጢት ውስጥ ሲሰበሰብ የነበረው የታማሚው ሽንት ወደ አረንጓዴነት ለመቀየር በቅቷል፡፡
አረንጓዴ ሽንት በህክምና የጎንዮሽ ተፅዕንዖ፣ አንዳንድ ኢንፌክሽኖች እና የጉበት ችግርን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል፡፡ በዚህ ግለሰብ ላይ የሆነው ግን በፕሮፎፖል ሳብያ የመጣ ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ ይህን አይነት ህክምና ለጀነራል አንስቴዢያ ተብሎ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን አልፎ አልፎም የሰዎችን ሽንት ወደ አረንጓዴነት ሲቀይር ይታያል፡፡ እንዴት ሆነ የሚለው ግን በዘርዝር የሚታወቅ አልሆነም፡፡ ሆኖም አንዳንድ የፕሮፎፖሉ ቁሶች ተሰባብረው ሲወጡና ይህም ከጉበት ይልቅ በኩላሊት አማካኝነት ሲሆን (ለወትሮ የፕሮፎፖል ኬሚካል አፀግብሮት ወይም ሜታቦሊዝም የሚደረገው ጉበት ውስጥ ነው) ሊከሰት እንደሚችል ከ5 ዓታት በፊት ጆርናል ኦፍ ክሊኒካል ኤንድ ዲያግኖስቲክ ሪሰርች ላይ የወጣ ምርምር አመላክቶ ነበር፡፡ ሆኖም ይህ የሽንት ቀለም ለውጥ ጉዳት የሌለው እና የህክምናውን መቋረጥ ተከትሎ የሚያቆም ነው፡፡ እኚህ ታማሚም ፕሮፎፖሉ ሲነሳለት ነገሮች ወደ ቀድሞ ጤናማ ይዞታቸው ተመልሰውለታል፡፡ ኋላም ለሁለት ሳምንታት በሆስፒታሉ ቆይቶ ወደ ማገገሚያ ማዕከል አቅንቷል፡፡
የሰው ልጆች ሽንት ወደ አረንጓዴነት ብቻ ሳይሆን ሌሎች ቀለሞችንም ይዞ ሊወጣ ይችላል፡፡ ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት 2019 ላይ የሽንት መሰብሰቢያ ከረጢት ውስጥ የገባ የአንዲት ሴት ሽንት ከረጢቱ ውስጥ በተፈጠረው የኬሚካል አፀግብሮት ሳብያ ወደ ሐምራዊነት ተለውጦ ነበር፡፡
ምንጭ፡ Live Science
የጭንቅላት ትክክለኛ ቦታንና ጊዜን የማስታወስ ብቃት
*************************
በስነ ልቦና የትምህርት ዘርፍ በሰው ልጅ ጭንቅላት ውስጥ የረጅም፣ የመካከለኛና የአጭር ጊዜ የትውስታ ሂደት እንዳለ ይነገራል፡፡ UT Southwestern በሚባል የምርምር ተቋም የሚሰሩ ተመራማሪዎች የሰው ልጅ ጭንቅላት ትውስታዎችን እንዴት ለረጅም ጊዜያት መያዝ እንደሚችል አዲስ ፍንጭ ማግኘታቸው ተሰምቷል፡፡ የምርምሩ ውጤት ከመሰረታዊው የማስታወስ ችሎታ በተጨማሪ በአልዛይመር በሽታና በጭንቅላት ላይ በሚደርስ አደጋ ምክንያት የሚመጣን የትውስታ ማጣት ችግርን ማከም የሚያስችል መፍትሔንም ያካተተ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
ከአስርት አመታት በፊት 'time cells' የተባሉ ህዋሳት በአይጦች ጭንቅላት ውስጥ ተገኝተው ነበር፡፡ እነዚህ ህዋሳትም በየአጋጣሚው የሚከሰቱ ሁኔታዎችን መዝግቦ የማስቀመጥ ልዩ ሚና እንዳላቸው ታውቆ ነበር፡፡ ይህም ጭንቅላት የሚከሰቱ ሁነቶችን በቅደም ተከተላቸው ሰድሮ እንዲያስቀምጥ በማድረግ ነው፡፡ hippocampus በመባል በሚታወቀው የጭንቅላት ክፍል የሚገኙት እነዚህ ህዋሳት ነገሮችን የማደራጀት ተግባር ሲከውኑ ተስተውለዋል ያለው በምርምሩ የተሳተፈው Bradley Lega, M.D ነው፡፡
ከዚህም በመነሳት ተመራማሪዎቹ ተመሳሳይ የጭንቅላት ህዋሳት በሰዎች ውስጥ መኖርና አለመኖራቸውን ማጥናት ጀምረዋል፡፡ በሂደቱም ፈቃደኛ ሆኑ የ epilepsy ህመም ታካሚዎችን የተያዩ ምርምሮች ተሰርተዋል፡፡ ይህ በ27 ፈቃደኞች ላይ የተሰራው ምርምር 'time cells' የተሰኙ የጭንቅላት ህዋሳት በሰዎች የትውስታ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ታውቋል፡፡ ይህም ሁነቶች የተከሰቱበትን ትክክለኛ ሰዓት ሰዎች በቀላሉ እንዲያስታውሱ የሚያደርጋቸው እንደሆነ ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
በሌላ ተያያዥነት ባለው ጥናት በሰዎች እና በእንስሳት ጭንቅላት ውስጥ የሚገኙ ነገሮች የተከወኑበትን ትክክለኛ ቦታ ማስታወስ የሚያስችሉ የጭንቅላት ህዋሳት ላይ ምርምር ተደርጓል፡፡ በዚህም ጥናት እንደመጀመሪያው ሁሉ አይጦች ተመሳሳይ ሁኔታ የታየባቸው ሲሆን አይጦች ባላቸው ቦታዎችን የማስታወስ ሂደት ውስጥ እነዚህ የቦታ ህዋሳት ቦታዎች በጭንቅላት ውስጥ በቅደም ተከተል ተደራጅተው እንዲቀመጡ ያደርጋሉ፡፡
በጥናቱም በአይጦች ጭንቅላት ውስጥ የሚስተዋልን የበፊቱንና የቅርብ ጊዜውን የቦታዎች ትውስታ የማፈራረቅ ሂደት ለመመርመር አጥኝዎቹ በአይጦቹ ጭንቅላት ውስጥ ኤሌክትሮዶችን በማስገባት ጥናቶችን አድርገዋል፡፡ በዚህም place cells የሚባሉት ህዋሳት በጭንቅላት ውስጥ የተቀረጹ የቅርብ ጊዜም ሆነ የቆዩ ምስሎችን በቅደም ተከተል እያመላለሱ ሲስተላልፉ ተስተውለዋል፡፡
ከዚህ ግኝት በመነሳት ተመራማሪዎቹ ህዋሳቱ እንዲህ አይነት ተግባራትን እንዲያከናውኑ የሚያግዟቸው ሌሎች የጭንቅላት ክፍሎችን እያጠኑ ሲሆን በዚህ የሚገኘው ውጤትም በአልዛይመርና በአደጋ ምክንያት የሚመጣን የሰዎች ትውስታ ማጣትን ለማከም የሚያስችሉ መሰረታዊ እውቀቶች እንደሚገኙ ተመራማሪዎቹ ተስፋ አድርገዋል፡፡
ምንጭ medicalxpress
*************************
በስነ ልቦና የትምህርት ዘርፍ በሰው ልጅ ጭንቅላት ውስጥ የረጅም፣ የመካከለኛና የአጭር ጊዜ የትውስታ ሂደት እንዳለ ይነገራል፡፡ UT Southwestern በሚባል የምርምር ተቋም የሚሰሩ ተመራማሪዎች የሰው ልጅ ጭንቅላት ትውስታዎችን እንዴት ለረጅም ጊዜያት መያዝ እንደሚችል አዲስ ፍንጭ ማግኘታቸው ተሰምቷል፡፡ የምርምሩ ውጤት ከመሰረታዊው የማስታወስ ችሎታ በተጨማሪ በአልዛይመር በሽታና በጭንቅላት ላይ በሚደርስ አደጋ ምክንያት የሚመጣን የትውስታ ማጣት ችግርን ማከም የሚያስችል መፍትሔንም ያካተተ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
ከአስርት አመታት በፊት 'time cells' የተባሉ ህዋሳት በአይጦች ጭንቅላት ውስጥ ተገኝተው ነበር፡፡ እነዚህ ህዋሳትም በየአጋጣሚው የሚከሰቱ ሁኔታዎችን መዝግቦ የማስቀመጥ ልዩ ሚና እንዳላቸው ታውቆ ነበር፡፡ ይህም ጭንቅላት የሚከሰቱ ሁነቶችን በቅደም ተከተላቸው ሰድሮ እንዲያስቀምጥ በማድረግ ነው፡፡ hippocampus በመባል በሚታወቀው የጭንቅላት ክፍል የሚገኙት እነዚህ ህዋሳት ነገሮችን የማደራጀት ተግባር ሲከውኑ ተስተውለዋል ያለው በምርምሩ የተሳተፈው Bradley Lega, M.D ነው፡፡
ከዚህም በመነሳት ተመራማሪዎቹ ተመሳሳይ የጭንቅላት ህዋሳት በሰዎች ውስጥ መኖርና አለመኖራቸውን ማጥናት ጀምረዋል፡፡ በሂደቱም ፈቃደኛ ሆኑ የ epilepsy ህመም ታካሚዎችን የተያዩ ምርምሮች ተሰርተዋል፡፡ ይህ በ27 ፈቃደኞች ላይ የተሰራው ምርምር 'time cells' የተሰኙ የጭንቅላት ህዋሳት በሰዎች የትውስታ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ታውቋል፡፡ ይህም ሁነቶች የተከሰቱበትን ትክክለኛ ሰዓት ሰዎች በቀላሉ እንዲያስታውሱ የሚያደርጋቸው እንደሆነ ተመራማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡
በሌላ ተያያዥነት ባለው ጥናት በሰዎች እና በእንስሳት ጭንቅላት ውስጥ የሚገኙ ነገሮች የተከወኑበትን ትክክለኛ ቦታ ማስታወስ የሚያስችሉ የጭንቅላት ህዋሳት ላይ ምርምር ተደርጓል፡፡ በዚህም ጥናት እንደመጀመሪያው ሁሉ አይጦች ተመሳሳይ ሁኔታ የታየባቸው ሲሆን አይጦች ባላቸው ቦታዎችን የማስታወስ ሂደት ውስጥ እነዚህ የቦታ ህዋሳት ቦታዎች በጭንቅላት ውስጥ በቅደም ተከተል ተደራጅተው እንዲቀመጡ ያደርጋሉ፡፡
በጥናቱም በአይጦች ጭንቅላት ውስጥ የሚስተዋልን የበፊቱንና የቅርብ ጊዜውን የቦታዎች ትውስታ የማፈራረቅ ሂደት ለመመርመር አጥኝዎቹ በአይጦቹ ጭንቅላት ውስጥ ኤሌክትሮዶችን በማስገባት ጥናቶችን አድርገዋል፡፡ በዚህም place cells የሚባሉት ህዋሳት በጭንቅላት ውስጥ የተቀረጹ የቅርብ ጊዜም ሆነ የቆዩ ምስሎችን በቅደም ተከተል እያመላለሱ ሲስተላልፉ ተስተውለዋል፡፡
ከዚህ ግኝት በመነሳት ተመራማሪዎቹ ህዋሳቱ እንዲህ አይነት ተግባራትን እንዲያከናውኑ የሚያግዟቸው ሌሎች የጭንቅላት ክፍሎችን እያጠኑ ሲሆን በዚህ የሚገኘው ውጤትም በአልዛይመርና በአደጋ ምክንያት የሚመጣን የሰዎች ትውስታ ማጣትን ለማከም የሚያስችሉ መሰረታዊ እውቀቶች እንደሚገኙ ተመራማሪዎቹ ተስፋ አድርገዋል፡፡
ምንጭ medicalxpress
የህዋ ሼልን (spacecraft) እንዲሸከም ታስቦ የተሰራው ግዙፉ አውሮፕላን
****************************
በአለማችን ላይ እስከዛሬ ድረስ ከተሰሩ ግዙፍ የአየር ላይ መጓጓዣዎች መካከል Airbus Beluga፣ Boeing Dreamlifter እና Antonov AN-225 ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህም ለተለየ አገልግሎት እና በጣም ግዙፍ የሆኑ በመደበኛ አውሮፕላኖች ሊንቀሳቀሱ የማይችሉ ጭነቶችን ለማንቀሳቀስ ታስበው የተሰሩ ናቸው፡፡ ቁጥራቸው በጣም ጥቂት በመሆኑና የተለየ እይታ ያላቸው በመሆኑ በአየር መንገድ ታሪኮች ውስጥ የታወቁ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ግን በ1960ዎቹ አሜሪካን በህዋ ላይ ፉክክሩ በረዳው Super Guppy ከተባለው አውሮፕላን ውጭ የማይታሰቡ ናቸው፡፡
NASA ቀላል ክብደት ኖሮት መጠኑ ግን በጣም ከፍተኛ የሆነን ጭነት ማጓጓዝ የሚቻልበትን መንገድ ሲፈልግ ነበር፡፡ በዚህም ተቋሙ እንዲህ አይነት እቃዎችን ከሚያመርትበት ከካሊፎርኒያ እነዚህን እቃዎች ወደ ሚጠቀምበት ፈሎሪዳ ላማንቀሳቀስ የሚያስችል ከፍተኛ ስፋት ያለው አውሮፕላን ሲፈልግ እንደነበር የአቪየሽን ታሪክ ተመራማሪው Graham M ይናገራል፡፡
አሜሪካ የህዋ ፕሮግራሞችን መስራት በጀመረችበት ወቅት የተለያዩ የሮኬት ክፍሎችን ወደ Cape Kennedy በፓናማ ዋሻ ወይም በሜክሲኮ ባህረ ሰላጤ በጀልባዎች ታጓጉዝ ነበር፡፡ በ1962 የተሰራው አውሮፕላን ግን በዘመኑ ካሉት ሁሉ ከፍተኛ መጠን ያለውን ጭነት መጫን የሚያስችል በመሆን በዚህ ረገድ ያለውን ችግር መቅረፍ ችሏል፡፡ ይህም 20 ጫማ የሚደርስ ዲያሚትር የነበረው ሲሆን 18 ቀናት ይወስድ የነበረውን የማጓጓዝ ሂደት ወደ 18 ሰዓታት ዝቅ ማድረግ አስችሏል፡፡
ይህ Pregnant Guppy በመባል የሚታወቀው አውሮፕላን እስካሁን ከተሰሩት ስምንት አውሮፕላኖች ውስጥ የመጀመሪያው ነው፡፡ ከአውሮፕላኖቹ መካከል አንደኛው የ1940 ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ቢሆንም NASA አሁንም ለማጓጓዣነት ይጠቀምበታል፡፡
ምንጭ CNN Travel
****************************
በአለማችን ላይ እስከዛሬ ድረስ ከተሰሩ ግዙፍ የአየር ላይ መጓጓዣዎች መካከል Airbus Beluga፣ Boeing Dreamlifter እና Antonov AN-225 ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህም ለተለየ አገልግሎት እና በጣም ግዙፍ የሆኑ በመደበኛ አውሮፕላኖች ሊንቀሳቀሱ የማይችሉ ጭነቶችን ለማንቀሳቀስ ታስበው የተሰሩ ናቸው፡፡ ቁጥራቸው በጣም ጥቂት በመሆኑና የተለየ እይታ ያላቸው በመሆኑ በአየር መንገድ ታሪኮች ውስጥ የታወቁ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ግን በ1960ዎቹ አሜሪካን በህዋ ላይ ፉክክሩ በረዳው Super Guppy ከተባለው አውሮፕላን ውጭ የማይታሰቡ ናቸው፡፡
NASA ቀላል ክብደት ኖሮት መጠኑ ግን በጣም ከፍተኛ የሆነን ጭነት ማጓጓዝ የሚቻልበትን መንገድ ሲፈልግ ነበር፡፡ በዚህም ተቋሙ እንዲህ አይነት እቃዎችን ከሚያመርትበት ከካሊፎርኒያ እነዚህን እቃዎች ወደ ሚጠቀምበት ፈሎሪዳ ላማንቀሳቀስ የሚያስችል ከፍተኛ ስፋት ያለው አውሮፕላን ሲፈልግ እንደነበር የአቪየሽን ታሪክ ተመራማሪው Graham M ይናገራል፡፡
አሜሪካ የህዋ ፕሮግራሞችን መስራት በጀመረችበት ወቅት የተለያዩ የሮኬት ክፍሎችን ወደ Cape Kennedy በፓናማ ዋሻ ወይም በሜክሲኮ ባህረ ሰላጤ በጀልባዎች ታጓጉዝ ነበር፡፡ በ1962 የተሰራው አውሮፕላን ግን በዘመኑ ካሉት ሁሉ ከፍተኛ መጠን ያለውን ጭነት መጫን የሚያስችል በመሆን በዚህ ረገድ ያለውን ችግር መቅረፍ ችሏል፡፡ ይህም 20 ጫማ የሚደርስ ዲያሚትር የነበረው ሲሆን 18 ቀናት ይወስድ የነበረውን የማጓጓዝ ሂደት ወደ 18 ሰዓታት ዝቅ ማድረግ አስችሏል፡፡
ይህ Pregnant Guppy በመባል የሚታወቀው አውሮፕላን እስካሁን ከተሰሩት ስምንት አውሮፕላኖች ውስጥ የመጀመሪያው ነው፡፡ ከአውሮፕላኖቹ መካከል አንደኛው የ1940 ቴክኖሎጂን የሚጠቀም ቢሆንም NASA አሁንም ለማጓጓዣነት ይጠቀምበታል፡፡
ምንጭ CNN Travel
ለቆዳ ህክምና አዲስ ቴክኖሎጂ
******************
የቆዳችንን አወቃቀር በመመልከት እንደ የቆዳ ካንሰርና ሌሎች የቆዳ በሽታዎችን ማከም የሚያስችል የህክምና መሳሪያ መሰራቱ ተነገረ፡፡ T-ray Imaging የተባለው የህክምና ዘዴ ጨረርን በመጠቀም በቆዳችን ላይ የሚኖርን ማንኛውም አይነት ችግር መለየት የሚያስችል ቴክኖሎጂ እንደሆነ የዘገበው SciTechDaily ነው፡፡
Warwick በተባለ ዩኒቨርሲቲ እና በቻይናው የሆንግኮንግ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተመራማሪዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች የቴራሄርትዝ ጨረርን በመልቀቅ ውስብስብ የሆነውን የቆዳችንን አወቃቀር በግልጽ በመመሰል (detailed picture) የድርቀት መጠኑንና ሌሎች ችግሮችንን መለየት እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ ምርምሩ ለህክምናው አለም የእያንዳንዱን ሰው የቆዳ ባህሪ መለየት የሚያስችል አዲስ ግብአት እንዳስገኘም ይታመናል፡፡
ጨረሩ ቆዳችንን ለሌላ ችግር የማያጋልጥና ከቆዳችን ተንጸባርቆ ሲመለስ የቆዳችንን የርጥበት መጠን በመለየት በዚህ ዘርፍ ያለውን ህክምና ቀላልና የተሳካ ያደርገዋል፡፡ ቴክኖሎጂው እስካሁን ካሉት ቴክኖሎጂዎች የሚለየው የቆዳን የድርቀት ልክ (hydration) በትክክል ለክቶ የሚያሳውቅ መሆኑ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ቴክኖሎጂው ለቆዳ እንክብካቤ የሚያገለግሉ ቅባቶችን እንደየእንዳንዱ ሰው የቆዳ ባህሪ የተስማማ ግብዓት እና ልኬትንም ለመስራት እንደሚያስችል ተጠቁሟል፡፡ የቆዳ ካንሰር ያለባቸውን ሰዎች ቀዶ ህክምና ከመስራት በፊት ይህን የጨረር ምሰላ በማድረግ በሽታው በቆዳ ውስጥ ምንያክል እንደተስፋፋ ማወቅ ይቻላል፡፡
ሙከራውን ለመስራት ተመራማሪዎቹ ፈቃደኞች እጃቸውን በተዘጋጀው የጨረር ፈንጣቂ መሳሪያ ላይ ለ30 ደቂቃዎች ያክል እንዲያስቀምጡ በማድረግ አራት የተለያዩ ልኬቶችን ሰርተዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
******************
የቆዳችንን አወቃቀር በመመልከት እንደ የቆዳ ካንሰርና ሌሎች የቆዳ በሽታዎችን ማከም የሚያስችል የህክምና መሳሪያ መሰራቱ ተነገረ፡፡ T-ray Imaging የተባለው የህክምና ዘዴ ጨረርን በመጠቀም በቆዳችን ላይ የሚኖርን ማንኛውም አይነት ችግር መለየት የሚያስችል ቴክኖሎጂ እንደሆነ የዘገበው SciTechDaily ነው፡፡
Warwick በተባለ ዩኒቨርሲቲ እና በቻይናው የሆንግኮንግ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተመራማሪዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች የቴራሄርትዝ ጨረርን በመልቀቅ ውስብስብ የሆነውን የቆዳችንን አወቃቀር በግልጽ በመመሰል (detailed picture) የድርቀት መጠኑንና ሌሎች ችግሮችንን መለየት እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ ምርምሩ ለህክምናው አለም የእያንዳንዱን ሰው የቆዳ ባህሪ መለየት የሚያስችል አዲስ ግብአት እንዳስገኘም ይታመናል፡፡
ጨረሩ ቆዳችንን ለሌላ ችግር የማያጋልጥና ከቆዳችን ተንጸባርቆ ሲመለስ የቆዳችንን የርጥበት መጠን በመለየት በዚህ ዘርፍ ያለውን ህክምና ቀላልና የተሳካ ያደርገዋል፡፡ ቴክኖሎጂው እስካሁን ካሉት ቴክኖሎጂዎች የሚለየው የቆዳን የድርቀት ልክ (hydration) በትክክል ለክቶ የሚያሳውቅ መሆኑ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ቴክኖሎጂው ለቆዳ እንክብካቤ የሚያገለግሉ ቅባቶችን እንደየእንዳንዱ ሰው የቆዳ ባህሪ የተስማማ ግብዓት እና ልኬትንም ለመስራት እንደሚያስችል ተጠቁሟል፡፡ የቆዳ ካንሰር ያለባቸውን ሰዎች ቀዶ ህክምና ከመስራት በፊት ይህን የጨረር ምሰላ በማድረግ በሽታው በቆዳ ውስጥ ምንያክል እንደተስፋፋ ማወቅ ይቻላል፡፡
ሙከራውን ለመስራት ተመራማሪዎቹ ፈቃደኞች እጃቸውን በተዘጋጀው የጨረር ፈንጣቂ መሳሪያ ላይ ለ30 ደቂቃዎች ያክል እንዲያስቀምጡ በማድረግ አራት የተለያዩ ልኬቶችን ሰርተዋል፡፡
ምንጭ SciTechDaily
የቀለም አጠቃቀም እና ባህርያት የተዳሰሰበት የዛሬው ቴክኢን ሴሚናር
=========================
በተለያዩ ቀለሞች እርስ በእርሳዊ ጥምረት ላይ ያተኮረው የቴክኢን ሴሚናር ዛሬ በኢንስቲትዩቱ የስብሰባ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ “COLOR THEORY” በሚል ርዕስ የተካሄደው የዛሬው ሴሚናር የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ባልደረባ በሆኑት አቶ ብርሃን ታፈሰ አማካኝነት ገለፃ የቀረበበት ሲሆን ሌሎች የኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎችንም ተሳታፊ አድርጎ የተዘጋጀ ነበር፡፡
አቶ ብርሃን በገለፃቸው በተለያዩ ቀለማት መካከል ያለውን ግንኙነት እና ይህን ለማመላከት ታስቦ በታላቁ ተመራማሪ አይዛክ ኒውተን እ.አ.አ በ1666 የተፈጠረው የቀለማትን ግንኙነት መመልከቻ ስልትን (Color Wheel) የዳሰሱ ሲሆን የትኛው ቀለም ከየትኛው ቀለም ጋር ተቃርኖ እንዳለውና ይህም ሌሎች ልዩ ቀለማትን እንደሚፈጥር አስቀምጠዋል፡፡ በተጨማሪም የትኛው የቀለም ጎራ ከየትኛው ሁነት ጋራ ቁርኝት እንደሚፈጥር፣ የትኛው ቀለም ከየትኛው ቀለም የእይታ ተስማሚነት እንዳለው እንዲሁም ሌሎች የቀለም አጠቃቀምን የተመለከቱ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ተዳሰውበታል፡፡
ከታዳሚያኑም በተለይ ቀለም ከእይታና ስነ-ልቦናም ባሻገር ጤናን በተመለከተ ሊፈጥር በሚችለው ተፅዕንዖ፣ በተለያየ መልኩ የተቋማትን ገፅታና ማንነት በመገንባት ረገድ የሚጫወተው ሚና እንዲሁም በሀገራዊና ማህበረሰባዊ ማንነት ውስጥ ያለውን ቦታ የሚያትቱ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡ አቶ ብርሃንም በተነሱት ጥያቄና አስተያየቶቹ ላይ ሙያዊ ማብራርያ ሰጥተውባቸዋል፡፡
=========================
በተለያዩ ቀለሞች እርስ በእርሳዊ ጥምረት ላይ ያተኮረው የቴክኢን ሴሚናር ዛሬ በኢንስቲትዩቱ የስብሰባ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ “COLOR THEORY” በሚል ርዕስ የተካሄደው የዛሬው ሴሚናር የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ባልደረባ በሆኑት አቶ ብርሃን ታፈሰ አማካኝነት ገለፃ የቀረበበት ሲሆን ሌሎች የኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎችንም ተሳታፊ አድርጎ የተዘጋጀ ነበር፡፡
አቶ ብርሃን በገለፃቸው በተለያዩ ቀለማት መካከል ያለውን ግንኙነት እና ይህን ለማመላከት ታስቦ በታላቁ ተመራማሪ አይዛክ ኒውተን እ.አ.አ በ1666 የተፈጠረው የቀለማትን ግንኙነት መመልከቻ ስልትን (Color Wheel) የዳሰሱ ሲሆን የትኛው ቀለም ከየትኛው ቀለም ጋር ተቃርኖ እንዳለውና ይህም ሌሎች ልዩ ቀለማትን እንደሚፈጥር አስቀምጠዋል፡፡ በተጨማሪም የትኛው የቀለም ጎራ ከየትኛው ሁነት ጋራ ቁርኝት እንደሚፈጥር፣ የትኛው ቀለም ከየትኛው ቀለም የእይታ ተስማሚነት እንዳለው እንዲሁም ሌሎች የቀለም አጠቃቀምን የተመለከቱ ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ተዳሰውበታል፡፡
ከታዳሚያኑም በተለይ ቀለም ከእይታና ስነ-ልቦናም ባሻገር ጤናን በተመለከተ ሊፈጥር በሚችለው ተፅዕንዖ፣ በተለያየ መልኩ የተቋማትን ገፅታና ማንነት በመገንባት ረገድ የሚጫወተው ሚና እንዲሁም በሀገራዊና ማህበረሰባዊ ማንነት ውስጥ ያለውን ቦታ የሚያትቱ ጥያቄና አስተያየቶች ተነስተዋል፡፡ አቶ ብርሃንም በተነሱት ጥያቄና አስተያየቶቹ ላይ ሙያዊ ማብራርያ ሰጥተውባቸዋል፡፡
ከፍታው በየጊዜው የሚጨምረው ድንቁ ተራራ
***************************
የአለማችን የከፍታ ልክ የሆነው ኤቨረስት ተራራ ታላቅነቱን ለማስጠበቅ ይመስል ዛሬም ከፍታው እየጨመረ እንደሆነ ተነገረ፡፡ ቻይናና ኔፓል ተስማምተው ባወጡት መረጃ መሰረት ከፍታው 8,848.86 ሜትር ወይም 29,031 ጫማ በመድረስ ከኔፓል ልኬት የ86 ሳንቲሜትር ወይም 2.8 ጫማ ጭማሪ ከፍ እንዳለ ታውቋል፡፡ ከቻይና በኩል ደግሞ ይህ ተራራ ከ4 ሜትር በላይ ከፍ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ ይህ ልዩነት የመጣውም ቻይናና ኔፓል ተራራውን የሚለኩበት መነሻ የተለያየ በመሆኑ ነው፡፡
በ1859 እንግሊዛውን ቀኝ ገዢ የስነ ምድር አጥኚዎች ተራራው 8840 ሜትር ወይም 29,002 ጫማ ከባህር ጠለል በላይ ከፍ እንደሚል ተናግረው ነበር፡፡ በኋላ ላይ ኢድሙንድ ሂላሪ እና ቴንዚንግ ኖርጋይ የተባሉ ሰዎች ከተራራው ጫፍ ድረስ ግንቦት 1953 መውጣት በመቻላቸው የከፍታ ልኬቱ ተስተካክሎ 8,840 ሜትር ወይም 29,002 ጫማ ከባህር ጠለል በላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡
ምንም እንኳን ኔፓል በመንግስት ደረጃ ባትቀበለውም በ1999 የአሜሪካ ብሔራዊ ስነምድር ማህበረሰብ (US National Geographic Society) የኤቨረስት ተራራ ከፍታ was 8,850 ሜትር ወይም 29,035 ጫማ እንደሆነ ደምድሞ ነበር፡፡ ቻይና በሂደት የራሷን ትናት እያደረገች ቆይታ በ2005 ተራራው 8,844.43 ሜትር ወይም 29,015 ጫማ ከፍታ አለው የሚል መረጃ ሰጥታለች፡፡
ከዚያም ኔፓል በኋላ ላይ ቻይና የተካተተችበትን ጥናት በ2015 የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ የተራራውን ከፍታ ቀይሮታል የሚል ሀሳብ በነበረበት ወቅት ሰርታለች፡፡ የመረጃ ስብሰባውን ስራ 300 የሚጠጉ ኔፓላውያን በእግርና በሔሊኮፍተር በመሆን የሰሩ ሲሆን የጥናቱም ውጤት በ2019 በኔፓል አማካኝነት ሊወጣ የነበረ ቢሆንም ፐሬዘዳንት Xi Jinping ኔፓልን በጎበኙበት ወቅት በጥናቱ ላይ ቻይናም እንድትሳተፍበት ተስማምተው በመመለሳቸው ውጤቱ ሳይገለጽ ቀርቷል፡፡ በያዝነው የፈረንጆች አመት የቻይና የተራራ ላይ ተመራማሪዎች በኮቪድ ምክንያት ብቸኛ ተራራ ወጭዎች በመሆናቸው ለስራቸው የተመቻቸላቸው ይመስላል፡፡
ምንጭ sciencealert
***************************
የአለማችን የከፍታ ልክ የሆነው ኤቨረስት ተራራ ታላቅነቱን ለማስጠበቅ ይመስል ዛሬም ከፍታው እየጨመረ እንደሆነ ተነገረ፡፡ ቻይናና ኔፓል ተስማምተው ባወጡት መረጃ መሰረት ከፍታው 8,848.86 ሜትር ወይም 29,031 ጫማ በመድረስ ከኔፓል ልኬት የ86 ሳንቲሜትር ወይም 2.8 ጫማ ጭማሪ ከፍ እንዳለ ታውቋል፡፡ ከቻይና በኩል ደግሞ ይህ ተራራ ከ4 ሜትር በላይ ከፍ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ ይህ ልዩነት የመጣውም ቻይናና ኔፓል ተራራውን የሚለኩበት መነሻ የተለያየ በመሆኑ ነው፡፡
በ1859 እንግሊዛውን ቀኝ ገዢ የስነ ምድር አጥኚዎች ተራራው 8840 ሜትር ወይም 29,002 ጫማ ከባህር ጠለል በላይ ከፍ እንደሚል ተናግረው ነበር፡፡ በኋላ ላይ ኢድሙንድ ሂላሪ እና ቴንዚንግ ኖርጋይ የተባሉ ሰዎች ከተራራው ጫፍ ድረስ ግንቦት 1953 መውጣት በመቻላቸው የከፍታ ልኬቱ ተስተካክሎ 8,840 ሜትር ወይም 29,002 ጫማ ከባህር ጠለል በላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡
ምንም እንኳን ኔፓል በመንግስት ደረጃ ባትቀበለውም በ1999 የአሜሪካ ብሔራዊ ስነምድር ማህበረሰብ (US National Geographic Society) የኤቨረስት ተራራ ከፍታ was 8,850 ሜትር ወይም 29,035 ጫማ እንደሆነ ደምድሞ ነበር፡፡ ቻይና በሂደት የራሷን ትናት እያደረገች ቆይታ በ2005 ተራራው 8,844.43 ሜትር ወይም 29,015 ጫማ ከፍታ አለው የሚል መረጃ ሰጥታለች፡፡
ከዚያም ኔፓል በኋላ ላይ ቻይና የተካተተችበትን ጥናት በ2015 የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ የተራራውን ከፍታ ቀይሮታል የሚል ሀሳብ በነበረበት ወቅት ሰርታለች፡፡ የመረጃ ስብሰባውን ስራ 300 የሚጠጉ ኔፓላውያን በእግርና በሔሊኮፍተር በመሆን የሰሩ ሲሆን የጥናቱም ውጤት በ2019 በኔፓል አማካኝነት ሊወጣ የነበረ ቢሆንም ፐሬዘዳንት Xi Jinping ኔፓልን በጎበኙበት ወቅት በጥናቱ ላይ ቻይናም እንድትሳተፍበት ተስማምተው በመመለሳቸው ውጤቱ ሳይገለጽ ቀርቷል፡፡ በያዝነው የፈረንጆች አመት የቻይና የተራራ ላይ ተመራማሪዎች በኮቪድ ምክንያት ብቸኛ ተራራ ወጭዎች በመሆናቸው ለስራቸው የተመቻቸላቸው ይመስላል፡፡
ምንጭ sciencealert
እንደ አፍንጫ ሽታን የሚያነፈንፈው ድሮን
**********************
ሲቪል ድሮኖች ካሏቸው ጠቀሜታዎች ውስጥ አንዱ የሰው ልጆች መድረስ በማይችሉባቸው ቦታዎች መድረስ መቻላቸው ነው፤ ለአብነት በደረሰባቸው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የቀድሞ አቋማቸው ላይ የማይገኙ ህንፃዎች እንዲሁም ሊፈነዱ የሚችሉ ቁሶች ያሉባቸው አደገኛ አከባቢዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አጥኚዎች ታድያ እነዚህን በመሳሰሉ አደገኛ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ ከአደጋ የተረፉ ሰዎችን እንዲሁም ፈንጂ፣ በተቀደደ ትቦ የሚፈስ ጋዝ እና ሌሎች ችግሮችንም በሚያመነጩት ሽታ ለመለየት የሚችል ድሮን የመስራት ፍላጎትን አድሮባቸው ቆይተዋል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተፈጠሩት ሴንሰሮች እነዚህ ሽታዎችን በብቃት እና በሚያስፈልገው ፍጥነትም ለመለየት እየተቸገሩ ነበር፡፡
አሁን ግን በዩኒቨርቲ ኦፍ ዋሽንግተን ምሁራን የሚመራው ምርምር ይህን የሚቀርፍ መስሏል፡፡ ስሜሊኮፍተር የሚል ስያሜን ያገኘው አዲሱ የድሮን ፈጠራ የተገጠመለትን የአፍንጫ አንቴና በመጠቀም ተፈላጊው ሽታ ወዳለበት አቅጣጫ የሚያመራ ነው፡፡ ድሮኑ የተገጠመለት አንቴና በአባቢው ያሉ ኬሚካሎችን ጠረን በመለየት ምግብ እንዲከሁም ሰዎች ወዳሉበት ስፍራ መምራት ይችላል፡፡
ስሜሊኮፍተሩ ሽታን ለማፈላለግ ማንኛውንም እርዳታ ከተመራሪዎቹ መውሰድ አላስፈለገውም፡፡ ይህን ለመከወን ከፍጡራን አፍንጫ የሚመሳሰል ስልትን ይጠቀማል፤ ፍለጋውን ቅድሚያ በተወሰነ ርቀት ወደ ግራ አቅጣጫ በማቅናት የሚጀምር ሲሆን በዚያ የፈለገውን ሽታ ካላገኘ ተመልሶ በተመሳይ ርቀት ወደ ቀኝ ይጓዛል፡፡ በዚህ ሂደት የሚፈልገውን ጠረን ያገኘ እንደሆነ የበረራ አኳሀኑን በመለወጥ ወደ እርሱ ይገሰግሳል፡፡
ስሜሎኮፍተሩ በዙርያው ያሉትን ነገሮች ቅርበት በየ አንድ ሴኮንዱ ለአስር ጊዜ ያህል እንዲለካ በሚያስችሉት አራቱ ሴንሰሮቹን በመጠቀም እራሱን ከመሰናክሎች ይጠብቃል፡፡ አንድ ቁስ በ20 ሴ.ሜ ቀርቦት ሲገኝ የጉዞ አቅጣጫ ማስተካከያ ያደርጋል፡፡
ሌላው ይህ ድሮኑ እንዳለው የተነገረለት ጥቅም ለዚህ እንቅስቃው የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂን አለመጠየቁ ነው፤ ይልቁንም ልዩ ልዩ በራሪ ነፍሳት አይኖቻቸውን ተጠቅመው ሲያደርጉት እንደሚታየው ሁሉ እርሱም የተገጠመለትን ካሜራ በመጠቀም ዙርያውን ይቆጣጠራል፡፡ ይህ ደግሞ ድሮኑን ትቦ ወይም ጉድጓድን ለመሳሰሉ የምድር በታች እና ውስጥ ለውስጥ ተልዕኮዎች ስል ያደርገዋል፡፡
በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዋሽንግተን ውስጥ በተደረጉት ሙከራዎች ድሮኑ ከአበባዎች የሚገኙትን የመሳሰሉ ጠረኖችን እንዲለይና ወደ እነርሱም እንዲያቀና ተደርጎ ነበር፡፡ ሆኖም ስራዎች በዚህ አያልቁም፤ ወደፊት በፍርስራሾች ውስጥ የተቀበሩ ሰዎች ትንፋሽ የሚወጣ ካርበን ዳይ ኦክሳይድን በማሽተት እንዲሁም ያልፈነዱ ፈንጂዎችን የሚለቁት የኬሚካል ጠረን በመለየት ህይወት የመታደግ ስራዎችን የመስራት ዓቅም እንደሚኖረው ተመራማሪዎቹ ተስፋ አድርገዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
**********************
ሲቪል ድሮኖች ካሏቸው ጠቀሜታዎች ውስጥ አንዱ የሰው ልጆች መድረስ በማይችሉባቸው ቦታዎች መድረስ መቻላቸው ነው፤ ለአብነት በደረሰባቸው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት የቀድሞ አቋማቸው ላይ የማይገኙ ህንፃዎች እንዲሁም ሊፈነዱ የሚችሉ ቁሶች ያሉባቸው አደገኛ አከባቢዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ አጥኚዎች ታድያ እነዚህን በመሳሰሉ አደገኛ ሁኔታዎች ውስጥ ያሉ ከአደጋ የተረፉ ሰዎችን እንዲሁም ፈንጂ፣ በተቀደደ ትቦ የሚፈስ ጋዝ እና ሌሎች ችግሮችንም በሚያመነጩት ሽታ ለመለየት የሚችል ድሮን የመስራት ፍላጎትን አድሮባቸው ቆይተዋል፡፡ ሆኖም እስካሁን የተፈጠሩት ሴንሰሮች እነዚህ ሽታዎችን በብቃት እና በሚያስፈልገው ፍጥነትም ለመለየት እየተቸገሩ ነበር፡፡
አሁን ግን በዩኒቨርቲ ኦፍ ዋሽንግተን ምሁራን የሚመራው ምርምር ይህን የሚቀርፍ መስሏል፡፡ ስሜሊኮፍተር የሚል ስያሜን ያገኘው አዲሱ የድሮን ፈጠራ የተገጠመለትን የአፍንጫ አንቴና በመጠቀም ተፈላጊው ሽታ ወዳለበት አቅጣጫ የሚያመራ ነው፡፡ ድሮኑ የተገጠመለት አንቴና በአባቢው ያሉ ኬሚካሎችን ጠረን በመለየት ምግብ እንዲከሁም ሰዎች ወዳሉበት ስፍራ መምራት ይችላል፡፡
ስሜሊኮፍተሩ ሽታን ለማፈላለግ ማንኛውንም እርዳታ ከተመራሪዎቹ መውሰድ አላስፈለገውም፡፡ ይህን ለመከወን ከፍጡራን አፍንጫ የሚመሳሰል ስልትን ይጠቀማል፤ ፍለጋውን ቅድሚያ በተወሰነ ርቀት ወደ ግራ አቅጣጫ በማቅናት የሚጀምር ሲሆን በዚያ የፈለገውን ሽታ ካላገኘ ተመልሶ በተመሳይ ርቀት ወደ ቀኝ ይጓዛል፡፡ በዚህ ሂደት የሚፈልገውን ጠረን ያገኘ እንደሆነ የበረራ አኳሀኑን በመለወጥ ወደ እርሱ ይገሰግሳል፡፡
ስሜሎኮፍተሩ በዙርያው ያሉትን ነገሮች ቅርበት በየ አንድ ሴኮንዱ ለአስር ጊዜ ያህል እንዲለካ በሚያስችሉት አራቱ ሴንሰሮቹን በመጠቀም እራሱን ከመሰናክሎች ይጠብቃል፡፡ አንድ ቁስ በ20 ሴ.ሜ ቀርቦት ሲገኝ የጉዞ አቅጣጫ ማስተካከያ ያደርጋል፡፡
ሌላው ይህ ድሮኑ እንዳለው የተነገረለት ጥቅም ለዚህ እንቅስቃው የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂን አለመጠየቁ ነው፤ ይልቁንም ልዩ ልዩ በራሪ ነፍሳት አይኖቻቸውን ተጠቅመው ሲያደርጉት እንደሚታየው ሁሉ እርሱም የተገጠመለትን ካሜራ በመጠቀም ዙርያውን ይቆጣጠራል፡፡ ይህ ደግሞ ድሮኑን ትቦ ወይም ጉድጓድን ለመሳሰሉ የምድር በታች እና ውስጥ ለውስጥ ተልዕኮዎች ስል ያደርገዋል፡፡
በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዋሽንግተን ውስጥ በተደረጉት ሙከራዎች ድሮኑ ከአበባዎች የሚገኙትን የመሳሰሉ ጠረኖችን እንዲለይና ወደ እነርሱም እንዲያቀና ተደርጎ ነበር፡፡ ሆኖም ስራዎች በዚህ አያልቁም፤ ወደፊት በፍርስራሾች ውስጥ የተቀበሩ ሰዎች ትንፋሽ የሚወጣ ካርበን ዳይ ኦክሳይድን በማሽተት እንዲሁም ያልፈነዱ ፈንጂዎችን የሚለቁት የኬሚካል ጠረን በመለየት ህይወት የመታደግ ስራዎችን የመስራት ዓቅም እንደሚኖረው ተመራማሪዎቹ ተስፋ አድርገዋል፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
ለሀሰተኛ ዜናዎች ቴክኖሎጂ እንደ መፍትሄ
**************************
የሀሰተኛ ዜናዎችን ስርጭት ለመግታት አዲስ ቴክኖሎጂ መሰራቱን Tech Xplore በእለታዊ ዘገባው አስነብቧል፡፡ የRice ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ ተቋማት በፕላት ፎርሞቻቸው ሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይሰራጩ ለመቆጣጠር የሚያግዛቸው ውጤታማ የሆነ በሰው ሰራሽ አስታውሎት የሚታገዝ ዘዴን መስራታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ይህም የዩኒቨርሲቲው የኮምፒውተር ሳይንቲስት በሆነው Anshumali Shrivastava መሪነት የተዘጋጀ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በምርምሩም ለግማሽ ምዕት ዓመታት ያክል ጥቅም ላይ የዋለውን Bloom filters የመፈጸም ብቃት ማሻሻል ችለዋል፡፡
የሙከራ ዳታ ቤዞችን በመጠቀም የተሻሻለው መንገድ ሀሰተኛ ዜናዎችንና የኮምፒውተር ቫይረሶችን ለማጣራት ከበፊቱ በ50 በመቶ ያነሰ የሚሞሪ ፍላጎት እንዳለው ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ ለምሳሌ ያክልም ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ዝውውር ያለበትን ቲውተርን ማሳያ አድርገዋል፡፡ ቲውተር ባወጣው መረጃ መሰረት በአሁኑ ሰዓት በቀን ከ500 ሚሊዮን መልእክቶች በላ ይዘዋወራሉ፡፡ አንድ ሰው አንድ መልእክትን በላከ በአንድ ሴኮንድ ውስጥ መረጃው ይሰራጫል፡፡
የእነዚህን ሁሉ መልእክቶች ትክክለኝነት ለማረጋገጥ ቲውተር ባይገልጸውም Bloom filterን ይጠቀማል ተብሎ እንደሚታሰብ የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡ ይህን ከፍተኛ ቁጥር ያለው መረጃ በዚህ የማጣሪያ ስልት ለመፈተሽ የማይቻል በመሆኑ አንዳንድ ሀሰተኛ መረጃዎች በቀላሉ ሲዘዋወሩ ይታያል፡፡
በተለይ በምርጫ ወቅቶች 10 ሺህ የሚያክሉ መልእክቶች በሴኮንድ ውስጥ ይሰራጫሉ፡፡ ታዲያ በቀደመው መንገድ እያንዳንዱን መልእክት በማንበብ ሀሰት ነው ተብሎ በሚገመተው ላይ ፍለጋ ለማድረግ የማይቻል ነው፡፡ በጥርጣሬ የተያዙ መልእክቶች በበዙ ቁጥር በወረቀት (በማንዋል) የማረጋገጥ ስራውን እጅግ አስቸጋሪና የማይቻል ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ በዚህ ረገድ አዲሱ መንገድ የተሻለ የሀሰተኛ መረጃ ቁጥጥር ብቃት እንሚኖረው ታምኖበታል፡፡
ምንጭ Tech Xplore
**************************
የሀሰተኛ ዜናዎችን ስርጭት ለመግታት አዲስ ቴክኖሎጂ መሰራቱን Tech Xplore በእለታዊ ዘገባው አስነብቧል፡፡ የRice ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ ተቋማት በፕላት ፎርሞቻቸው ሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይሰራጩ ለመቆጣጠር የሚያግዛቸው ውጤታማ የሆነ በሰው ሰራሽ አስታውሎት የሚታገዝ ዘዴን መስራታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ይህም የዩኒቨርሲቲው የኮምፒውተር ሳይንቲስት በሆነው Anshumali Shrivastava መሪነት የተዘጋጀ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በምርምሩም ለግማሽ ምዕት ዓመታት ያክል ጥቅም ላይ የዋለውን Bloom filters የመፈጸም ብቃት ማሻሻል ችለዋል፡፡
የሙከራ ዳታ ቤዞችን በመጠቀም የተሻሻለው መንገድ ሀሰተኛ ዜናዎችንና የኮምፒውተር ቫይረሶችን ለማጣራት ከበፊቱ በ50 በመቶ ያነሰ የሚሞሪ ፍላጎት እንዳለው ተመራማሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ ለምሳሌ ያክልም ከፍተኛ የሆነ የመረጃ ዝውውር ያለበትን ቲውተርን ማሳያ አድርገዋል፡፡ ቲውተር ባወጣው መረጃ መሰረት በአሁኑ ሰዓት በቀን ከ500 ሚሊዮን መልእክቶች በላ ይዘዋወራሉ፡፡ አንድ ሰው አንድ መልእክትን በላከ በአንድ ሴኮንድ ውስጥ መረጃው ይሰራጫል፡፡
የእነዚህን ሁሉ መልእክቶች ትክክለኝነት ለማረጋገጥ ቲውተር ባይገልጸውም Bloom filterን ይጠቀማል ተብሎ እንደሚታሰብ የመረጃ ምንጫችን አስነብቧል፡፡ ይህን ከፍተኛ ቁጥር ያለው መረጃ በዚህ የማጣሪያ ስልት ለመፈተሽ የማይቻል በመሆኑ አንዳንድ ሀሰተኛ መረጃዎች በቀላሉ ሲዘዋወሩ ይታያል፡፡
በተለይ በምርጫ ወቅቶች 10 ሺህ የሚያክሉ መልእክቶች በሴኮንድ ውስጥ ይሰራጫሉ፡፡ ታዲያ በቀደመው መንገድ እያንዳንዱን መልእክት በማንበብ ሀሰት ነው ተብሎ በሚገመተው ላይ ፍለጋ ለማድረግ የማይቻል ነው፡፡ በጥርጣሬ የተያዙ መልእክቶች በበዙ ቁጥር በወረቀት (በማንዋል) የማረጋገጥ ስራውን እጅግ አስቸጋሪና የማይቻል ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ በዚህ ረገድ አዲሱ መንገድ የተሻለ የሀሰተኛ መረጃ ቁጥጥር ብቃት እንሚኖረው ታምኖበታል፡፡
ምንጭ Tech Xplore
የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ የትግበራ እቅድ
*********************************
የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ የትግበራ እቅድ / “Digital Skill Country Action Plan for Higher Education and TVET 2030” የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ግብ ትኩረት ያደረገባቸውን ኢኮኖሚ ደጋፊ ዘርፎችና በብሔራዊ ደረጃ የተያዙ የስራ እድል ፈጠራ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ማሳደግ እና አካታች ብልጽግና የማረጋገጥ ግቦችን እዉን ለማድረግ የሚያስችሉ በመካከለኛና በከፍተኛ የዲጂታል ክህሎት የሰለጠኑ ምሩቃንን በማውጣት እንዲደግፉ ያስችላል፡፡
እቅዱ ህዳር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በአዳማ ከተማ በተካሄደው የከፍተኛ ትምህርት የስትራቴጂክ ዕቅድ ግምገማ መድረክ ላይ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ባለዳርሻ አካላት በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ ወደስራ ገብቷል፡፡ በመድረኩ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ እቅዱ ለሁሉም ሴክተሮችና ለአራተኛዉ የኢንዱስትሪ አቢዮት (4th industrial revolutions) የሚያስፈልጉ በዲጂታል ክህሎት ብቃታቸው የተረጋገጠ ምሩቃንና ዜጎችን ለማፍራት እንዲቻልና የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት የትምህርት፣ ምርምርና አስተዳደር ስራዎችን በኢንፎሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ የተደገፉ ለማድረግ እንዲቻል ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ እቅዱ፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የአስር አመት ስትራቴጂክ እቅድ፣ ከሀገሪቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ፣ ከአፍሪካ ህብረት አህጉራዊ የዲጂታል ስትራቴጂ እና ከተባበሩት መንግስታት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጣመ መልኩ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ሲጸድቅ፣ ሁሉም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከእቅዱ በመነሳት የራሳቸውን ዘርፍ ማስፈጸሚያ እቅድ እንዲያዘጋጁ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የራሱን ድርሻ በመውሰድ እቅድ ማዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ የትግበራ እቅድ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ላይ የተቀመጡትን ግቦች ለማሳካት የሚተገበር መሆኑን ገልጸው በኢትዮጵያ ያለዉን ዝቅተኛ የዲጂታል ክህሎት ለማሻሻል እንደሚያግዝም አብራርተዋል፡፡ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ተማሪዎችንና መምህራንን ለዚህ ክህሎት ለማዘጋጀት አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል፡፡
እቅዱ በሃገራቸን ትኩረት ተደርጎ እየተሰራባቸው ለሚገኙት አካታች ብልጽግናን የሚያረጋገጡ ግቦችን ለማሳካት የሚያስፈልጉ የሰዉ ሃይል ለማፍራትና የዲጂታል ዕውቀትን ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን አምስት የዲጂታል አስቻይ መሪ ግቦችን አካትቷል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
*********************************
የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ የትግበራ እቅድ / “Digital Skill Country Action Plan for Higher Education and TVET 2030” የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ግብ ትኩረት ያደረገባቸውን ኢኮኖሚ ደጋፊ ዘርፎችና በብሔራዊ ደረጃ የተያዙ የስራ እድል ፈጠራ፣ የውጭ ምንዛሪ ግኝት ማሳደግ እና አካታች ብልጽግና የማረጋገጥ ግቦችን እዉን ለማድረግ የሚያስችሉ በመካከለኛና በከፍተኛ የዲጂታል ክህሎት የሰለጠኑ ምሩቃንን በማውጣት እንዲደግፉ ያስችላል፡፡
እቅዱ ህዳር 30 ቀን 2013 ዓ.ም በአዳማ ከተማ በተካሄደው የከፍተኛ ትምህርት የስትራቴጂክ ዕቅድ ግምገማ መድረክ ላይ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ባለዳርሻ አካላት በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ ወደስራ ገብቷል፡፡ በመድረኩ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ እቅዱ ለሁሉም ሴክተሮችና ለአራተኛዉ የኢንዱስትሪ አቢዮት (4th industrial revolutions) የሚያስፈልጉ በዲጂታል ክህሎት ብቃታቸው የተረጋገጠ ምሩቃንና ዜጎችን ለማፍራት እንዲቻልና የዲጂታል መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት የትምህርት፣ ምርምርና አስተዳደር ስራዎችን በኢንፎሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ የተደገፉ ለማድረግ እንዲቻል ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ እቅዱ፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የአስር አመት ስትራቴጂክ እቅድ፣ ከሀገሪቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ፣ ከአፍሪካ ህብረት አህጉራዊ የዲጂታል ስትራቴጂ እና ከተባበሩት መንግስታት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጣመ መልኩ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ሲጸድቅ፣ ሁሉም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ከእቅዱ በመነሳት የራሳቸውን ዘርፍ ማስፈጸሚያ እቅድ እንዲያዘጋጁ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የራሱን ድርሻ በመውሰድ እቅድ ማዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት የዲጂታል ክህሎት ሃገራዊ የትግበራ እቅድ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ላይ የተቀመጡትን ግቦች ለማሳካት የሚተገበር መሆኑን ገልጸው በኢትዮጵያ ያለዉን ዝቅተኛ የዲጂታል ክህሎት ለማሻሻል እንደሚያግዝም አብራርተዋል፡፡ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ተማሪዎችንና መምህራንን ለዚህ ክህሎት ለማዘጋጀት አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል፡፡
እቅዱ በሃገራቸን ትኩረት ተደርጎ እየተሰራባቸው ለሚገኙት አካታች ብልጽግናን የሚያረጋገጡ ግቦችን ለማሳካት የሚያስፈልጉ የሰዉ ሃይል ለማፍራትና የዲጂታል ዕውቀትን ለማሳደግ በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን አምስት የዲጂታል አስቻይ መሪ ግቦችን አካትቷል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር
ቴክ-ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራም፤ በዚህ ሳምንትም፡-
• በአብይ ፕሮግራም፤ የሚጥል በሽታን (Epilepsy) ፣
• በብላቴናት፤ ድሮን የሰራውን ታዳጊ፣
• በተመራማሪዎች ታሪክ፤ ዶ/ር ሀብቴ ጀቤሳ (ክፍል ፬)፣
• በተቋማት፤ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣
• በቴክኖሎጂ ታሪክ፤ ስለ ቨርቹዋል ሪያሊቲ ዝግጅቶችን አጠናቅረን እየጠበቅናችሁ ነው፡፡
እርሰዎም ነገ ቅዳሜ 10 ሰዓት ላይ የቻናል ምርጫዎን MOE ቴሌቪዥን ላይ በማድረግ ብቻ ይከታተሉን፡፡
በየሳምንቱ ቅዳሜ እንዲሁም በድጋሚ ማክሰኞ 10 ሰዓት በMOE ቴሌቪዥን ከሚቀርበው በተጨማሪ ወደ ዩትዩብ ቻናላችንም ጎራ በማለት አዳዲሶቹን ጨምሮ እስከዛሬ የተሰሩትን ፕሮግራሞች በሙሉ መመልከት ይችላሉ ( https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg )፡፡
• በአብይ ፕሮግራም፤ የሚጥል በሽታን (Epilepsy) ፣
• በብላቴናት፤ ድሮን የሰራውን ታዳጊ፣
• በተመራማሪዎች ታሪክ፤ ዶ/ር ሀብቴ ጀቤሳ (ክፍል ፬)፣
• በተቋማት፤ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣
• በቴክኖሎጂ ታሪክ፤ ስለ ቨርቹዋል ሪያሊቲ ዝግጅቶችን አጠናቅረን እየጠበቅናችሁ ነው፡፡
እርሰዎም ነገ ቅዳሜ 10 ሰዓት ላይ የቻናል ምርጫዎን MOE ቴሌቪዥን ላይ በማድረግ ብቻ ይከታተሉን፡፡
በየሳምንቱ ቅዳሜ እንዲሁም በድጋሚ ማክሰኞ 10 ሰዓት በMOE ቴሌቪዥን ከሚቀርበው በተጨማሪ ወደ ዩትዩብ ቻናላችንም ጎራ በማለት አዳዲሶቹን ጨምሮ እስከዛሬ የተሰሩትን ፕሮግራሞች በሙሉ መመልከት ይችላሉ ( https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg )፡፡