አፍሪካ እና ቴክኖሎጂ
በቁስ በፅሁፍ የተገኙ እንዲሁም ቋንቋን ባህልን ጊዜን መሰርት አድርገው የተካሄዱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት አፍሪካና አፍሪካውያን ከአውሮፓ ስልጣኔ በፊት የሳይንስ እውቀት እና የቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤቶች የነበሩ መሆናቸውን ያመለክታሉ፡፡
በርካታ ተመራማሪዎች አፍሪካውያን ለአለም ያበረከቱት አስተዋጽዖ በ20ኛው ክፍለ ዘመን ከተከናወኑት ፈጠራዎች የማይተናነሱ እና ይልቁንም ከጥቁር ህዝብ የፈለቁት የጊዜ እና የወቅት መፈራረቅ ግኝት፣ የቀን አቆጣጠር፣ የሂሳብ ቀመር ግኝት፣ የእደ ጥብብ ብቃት፣ የግብርና እና የስነ ህንፃ ጥብብ ኋላ ለተፈጠሩት የሰው ልጅ የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ መሰርት ጥሏል፡፡
ቴክኖሎጂ እና የሳይንስ እውቀት የሁሉም የሰው ልጆች ንብረት እንደሆነ ሁሉ ለዚህ እውቀት እውን መሆን ሁሉም ባህሎች በአንድም ይሁን በሌላም የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዳደረጉ መዘንጋት ባይቻልም ቀደምት አፍሪካውያን በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያበረከቱትን ታላቅ አስተዋፅኦ በሚገባ መዘከር እና የወደፊቱንም አልሞ መስራት እጅግ ብልህነት ነው፡፡
ተከታዩን ዘጋባ ይከታተሉ
https://youtu.be/Sm56gb1KIsc
በቁስ በፅሁፍ የተገኙ እንዲሁም ቋንቋን ባህልን ጊዜን መሰርት አድርገው የተካሄዱ መረጃዎች እንደሚያሳዩት አፍሪካና አፍሪካውያን ከአውሮፓ ስልጣኔ በፊት የሳይንስ እውቀት እና የቴክኖሎጂ ፈጠራ ባለቤቶች የነበሩ መሆናቸውን ያመለክታሉ፡፡
በርካታ ተመራማሪዎች አፍሪካውያን ለአለም ያበረከቱት አስተዋጽዖ በ20ኛው ክፍለ ዘመን ከተከናወኑት ፈጠራዎች የማይተናነሱ እና ይልቁንም ከጥቁር ህዝብ የፈለቁት የጊዜ እና የወቅት መፈራረቅ ግኝት፣ የቀን አቆጣጠር፣ የሂሳብ ቀመር ግኝት፣ የእደ ጥብብ ብቃት፣ የግብርና እና የስነ ህንፃ ጥብብ ኋላ ለተፈጠሩት የሰው ልጅ የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ መሰርት ጥሏል፡፡
ቴክኖሎጂ እና የሳይንስ እውቀት የሁሉም የሰው ልጆች ንብረት እንደሆነ ሁሉ ለዚህ እውቀት እውን መሆን ሁሉም ባህሎች በአንድም ይሁን በሌላም የራሳቸውን አስተዋጽኦ እንዳደረጉ መዘንጋት ባይቻልም ቀደምት አፍሪካውያን በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያበረከቱትን ታላቅ አስተዋፅኦ በሚገባ መዘከር እና የወደፊቱንም አልሞ መስራት እጅግ ብልህነት ነው፡፡
ተከታዩን ዘጋባ ይከታተሉ
https://youtu.be/Sm56gb1KIsc
YouTube
አፍሪካና ቴክኖሎጂ ምንና ምን ናቸዉ?አህጉራችን አፍሪካ ለበርካታ ቴክኖሎጂዎች ቀደምት እንደሆነች ያዉቃሉ?Africa and technology
#አፍሪካና#ቴክኖሎጂ# ምንና ምን ናቸዉ?አህጉራችን አፍሪካ ለበርካታ ቴክኖሎጂዎች ቀደምት እንደሆነች ያዉቃሉ?Africa and technology
ማሊግብፅኢትዮጵያቴክኖሎጂዎችን ለመጀመር ፈር ቀዳጅ የነበሩ ሀገራት ዉስጥ ተጠቃሽ ናቸዉ::
ማሊግብፅኢትዮጵያቴክኖሎጂዎችን ለመጀመር ፈር ቀዳጅ የነበሩ ሀገራት ዉስጥ ተጠቃሽ ናቸዉ::
94.5% ውጤታማ የሆነ የኮሮና ወረርሽኝ ክትባት
****************************
በሶስት ዙሮች 43,000 ታማሚዎች በተሳተፉበት የሙከራ ስራ 94.5 በመቶ ውጤታማ የሆነ ክትባት መገኘቱን Biopharmaceutical Moderna በመባል የሚታወቀው ድርጅት ይፋ አደረገ፡፡ መረጃው ያለፈው እሁድ የመረጃ ደህንነት በሆነ ገለልተኛ አካል ተረጋግጦ የወጣ ነው፡፡
በተገኘው ክትባት በጣም ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች በታህሳስ መገባደጃ አካባቢ ስርጭትና ክትባት እንደሚጀመር ተገልጧል፡፡ በአለማችን ሁሉም አካባቢዎች እስከ ሚያዚያ ድረስ ክትባቱ ተደራሽ እንደሚሆን በተጨማሪ የተገለጸ ሲሆን ይህ መረጃ በትክክል የሚተገበር ከሆነ ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊ ችግር እንደሚፈታ ይጠበቃል፡፡
ከዚህ በፊት Pfizer እና German በተባሉ የመድሀኒት አምራች ድርጅቶች ውጤታማነቱ 90 በመቶ የሆነ ክትባት መገኘቱ እንደተገለጸ የማይዘነጋ ነው፡፡ ይህ Moderna በተባለው ድርጅት የተገኘው ክትባት በፍሪጅ ውስጥ ለ30 ቀናት ያክል መቆየት የሚችል በመሆኑ ስርጭቱን በጣም ቀላል ያደርገዋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡
ምንጭ Futurism
****************************
በሶስት ዙሮች 43,000 ታማሚዎች በተሳተፉበት የሙከራ ስራ 94.5 በመቶ ውጤታማ የሆነ ክትባት መገኘቱን Biopharmaceutical Moderna በመባል የሚታወቀው ድርጅት ይፋ አደረገ፡፡ መረጃው ያለፈው እሁድ የመረጃ ደህንነት በሆነ ገለልተኛ አካል ተረጋግጦ የወጣ ነው፡፡
በተገኘው ክትባት በጣም ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች በታህሳስ መገባደጃ አካባቢ ስርጭትና ክትባት እንደሚጀመር ተገልጧል፡፡ በአለማችን ሁሉም አካባቢዎች እስከ ሚያዚያ ድረስ ክትባቱ ተደራሽ እንደሚሆን በተጨማሪ የተገለጸ ሲሆን ይህ መረጃ በትክክል የሚተገበር ከሆነ ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊ ችግር እንደሚፈታ ይጠበቃል፡፡
ከዚህ በፊት Pfizer እና German በተባሉ የመድሀኒት አምራች ድርጅቶች ውጤታማነቱ 90 በመቶ የሆነ ክትባት መገኘቱ እንደተገለጸ የማይዘነጋ ነው፡፡ ይህ Moderna በተባለው ድርጅት የተገኘው ክትባት በፍሪጅ ውስጥ ለ30 ቀናት ያክል መቆየት የሚችል በመሆኑ ስርጭቱን በጣም ቀላል ያደርገዋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡
ምንጭ Futurism
የደም ስጦታ፤ ከኢንስቲትዩታችን ቤተሰቦች
-----------------------------------
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሰራተኞች በ2013 የመጀመሪያቸው የሆነውን የደም ልገሳ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውነዋል፡፡ በመርሀግብሩ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ 35 የተቋማችን ሰራተኞች ተገኝተው ደማቸውን የለገሱ ሲሆን በተጨማሪም የኢትዮጵያ ባዮ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሰራተኞችም ተሳታፊ ሆነው ደማቸውን ለግሰዋል፡፡ መሰል የደም ልገሳ መርሀ ግብር ሲከናወን በተቋሙ ታሪክ የዛሬው ለአስራ ሦስተኛ ጊዜ ነው፡፡
በዝግጅቱ ላይ ደማቸውን የለገሱት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ለረጅም ጊዜያት በተከታታይ መሰል የደም ልገሳ መርሀ ግብሮችን ሲያከናውን መቆየቱን እና እርሳቸውም በእነዚህ ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ደም መስጠት ከእኛ የሚቀንሰው ነገር የሌለ ግን ደግሞ ደስ የሚያሰኝ ተግባር መሆኑን የገለፁት አቶ ሙሉቀን የዛሬውን ደም ልገሳ ልዩ የሚያደርገው ለመከላከያ ሰራዊታችን እየሰጠን መሆኑ ነው ብለዋል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተለመዱ ከመጡ የበጎ ስራ ተግባራት ውስጥ አንዱ የደም ልገሳን ማከናወን ነው፡፡ ይህ ምግባር ብዙ በተለያዩ የጤና እክሎች አስቸኳይ የደም እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ህይወት ከመታደጉም ባሻገር ለለጋሹም ጥልቅ የስሜት እርካታን የሚሰጥ ነው፡፡
-----------------------------------
የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ሰራተኞች በ2013 የመጀመሪያቸው የሆነውን የደም ልገሳ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት አከናውነዋል፡፡ በመርሀግብሩ ላይ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ 35 የተቋማችን ሰራተኞች ተገኝተው ደማቸውን የለገሱ ሲሆን በተጨማሪም የኢትዮጵያ ባዮ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሰራተኞችም ተሳታፊ ሆነው ደማቸውን ለግሰዋል፡፡ መሰል የደም ልገሳ መርሀ ግብር ሲከናወን በተቋሙ ታሪክ የዛሬው ለአስራ ሦስተኛ ጊዜ ነው፡፡
በዝግጅቱ ላይ ደማቸውን የለገሱት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ለረጅም ጊዜያት በተከታታይ መሰል የደም ልገሳ መርሀ ግብሮችን ሲያከናውን መቆየቱን እና እርሳቸውም በእነዚህ ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ደም መስጠት ከእኛ የሚቀንሰው ነገር የሌለ ግን ደግሞ ደስ የሚያሰኝ ተግባር መሆኑን የገለፁት አቶ ሙሉቀን የዛሬውን ደም ልገሳ ልዩ የሚያደርገው ለመከላከያ ሰራዊታችን እየሰጠን መሆኑ ነው ብለዋል፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተለመዱ ከመጡ የበጎ ስራ ተግባራት ውስጥ አንዱ የደም ልገሳን ማከናወን ነው፡፡ ይህ ምግባር ብዙ በተለያዩ የጤና እክሎች አስቸኳይ የደም እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ህይወት ከመታደጉም ባሻገር ለለጋሹም ጥልቅ የስሜት እርካታን የሚሰጥ ነው፡፡
ሴክሽን 230 እና ሪፐብሊካኖች
***************************
በአሜሪካ የሚገኙ ህጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በሌላው የአለም ክፍል ላይ አወንታዊም ሆነ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳደራቸው አይቀርም፡፡ ለምሳሌ ሴክሽን 230 እየተባለ የሚጠራው የገመድ አልባ አገልግሎት መሰረት የሆነውን ህግ ማንሳት ይቻላል፡፡ የዘገባችን ምንጭ እንዳስረዳው ያለዚህ ህግ በየቀኑ የምንጎበኛቸው ተፈላጊ ድረ-ገጾች ሊኖሩ አይችሉም ነበር፡፡ የዘመናዊው ገመድ አልባ አገልግሎት ከዚህ አጭር ህግ ውጭ የተለየ መልክ ሊኖረው እንደሚችል ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ህግ በወግ አጥባቂዎቹ በኩል የይሻሻል ጥያቄ ተነስቶበታል፡፡
በተደጋጋሚ የሚጎበኙ ድረገጾች በአለማቀፍ ዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ተጠቃሚዎች ሀሳባቸውን እንዲያካፍሉ፣ ፎቶዎችን፣ ቪዲዮዎችን፣ ስጦታዎች እንዲለዋወጡ አለፍ ሲልም የእርቃን ምስሎችን እንዲለዋወጡ የሆነው በዚሁ በሴክሽን 230 ምክንያት ነው፡፡ ይህ ህግ ከተወሰኑ ጉዳዮች በቀር እንደ Yelp, Reddit, እና Facebook ያሉ ድረገጾችና አገልግሎቶች ተጠቃሚዎቻቸው በሚያሰራጯቸው ነገሮች ህጋዊ ተጠያቂነት እንደሌለባቸው ይደነግጋል፡፡ ለምሳሌ Wikipedia እየተባለ የሚጠራው የመረጃ ድረገጽ ማንኛውም ተጠቃሚ አንድን ጽሁፍ ማስተካከል እንዲችል ተደርጎ የተሰራ ክፍት ድረ-ገጽ ነው፡፡
ህጉ በገመድ አልባ አገልግሎት ዙሪያ ከወጡ ህጎች በላቀ መልኩ በጣም ወሳኝ የሆነበትን ምክንያት ጥያቄ የሚያስነሳ ሲሆን ከወግ አጥባቂዎቹ በኩል በሆኑ ተጽዕኖ ፈጣሪ የኮንግረንስ አባላት በክፉ አይን መታየቱ አልቀረም፡፡ ከዚህ ህግ አንጻር ሀለት እይታዎች አሉ፡፡ በአንድ በኩል አብዛኛዎቹ ኤክስፐርቶች እንደሚስማሙት ህግ አውጭዎች የህጉን መሰረታዊ አላማ ችላ ብለው እንደሰሩት ሲታመን በሌላ በኩል ደግሞ ፖለቲካዊ ነጥብ ከማስቆጠር ያለፈ ነገር የለውም ብለው የሚያምኑ አሉ፡፡ ሴክሽን 230 ድረገጾች ፖለቲካዊ አላማ ይኑራቸውም አይኑራቸውም ሁሉንም የሚጠብቅ ህግ ነው፡፡
በሪፐብሊካኑ አባል ቤን ሻፒሮ በሚንቀሳቀሰው Daily Wire በሚባለው የዜና ምንጭ በየጽሁፎቹ አንባቢዎች ከፍተኛ ስም ማጥፋት የታከለባቸውን አስተያየቶችን ይጽፋሉ፡፡ በሴክሽን 230 ህግ መሰረት አዘጋጁም ሆነ አስተያየት ሰጭዎች ምንም አይነት ህጋዊ ተጠያቂነት የለባቸውም፡፡
ሴክሽን 230 እየተባለ የሚጠራው ህግ
“No provider or user of an interactive computer service shall be treated as the publisher or speaker of any information provided by another information content provider.”
የሚል ሲሆን በጥቅሉ በአንድ ፕላትፎርም የሚሳተፉ ተጠቃሚዎች በሚያሰራጩት መረጃ ምክንያት የፕላትፎርሙ ባለቤት ህጋዊ ተጠያቂነት የለበትም የሚል ነው፡፡ ይሁን እንጂ በ90ዎቹ በፍርድ ቤት የተወሰነ አንድ ውሳኔ በገመድ አልባ አገልግሎት በሚኖር ህጋዊ ባልሆነ ድርጊት ተጠያቂነት ሊኖር እንደሚችል ታይቷል፡፡ በዚህም ይህ አገልግሎት በህግ የተሰጠውን ሙሉ ነጻነት እንደማይጠቀም መረዳት ይቻላል፡፡
ህጉ ብዙ ችግር አለው ብለው የሚስማሙ ወግ አጥባቂዎቹ ሪፐብሊካኖች እንደ Fight Online Sex Trafficking Act (FOSTA) አይነት የተሻሻሉ ህጎችን በመጥቀስ ይህም ህግ የሶስተኛ ወገን ተጠያቂነትን በሚያመጣ መልኩ መሻሻል አለበት በማለት እየሞገቱ ነው፡፡ ከጥንስሱ ህጉን ያረቀቁት የዲሞክራቱ Ron Wyden እና የሪፐብሊካኑ Christopher Cox ግብ ያደረጉት የ pornographyን መስፋፋት መግታት ነበር፡፡
ምንጭ፡ GIZMODO (https://gizmodo.com/section-230-is-the-foundation-of-the-internet-so-why-d-1833590565)
***************************
በአሜሪካ የሚገኙ ህጎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በሌላው የአለም ክፍል ላይ አወንታዊም ሆነ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳደራቸው አይቀርም፡፡ ለምሳሌ ሴክሽን 230 እየተባለ የሚጠራው የገመድ አልባ አገልግሎት መሰረት የሆነውን ህግ ማንሳት ይቻላል፡፡ የዘገባችን ምንጭ እንዳስረዳው ያለዚህ ህግ በየቀኑ የምንጎበኛቸው ተፈላጊ ድረ-ገጾች ሊኖሩ አይችሉም ነበር፡፡ የዘመናዊው ገመድ አልባ አገልግሎት ከዚህ አጭር ህግ ውጭ የተለየ መልክ ሊኖረው እንደሚችል ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ ህግ በወግ አጥባቂዎቹ በኩል የይሻሻል ጥያቄ ተነስቶበታል፡፡
በተደጋጋሚ የሚጎበኙ ድረገጾች በአለማቀፍ ዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ ጉልህ ድርሻ አላቸው፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ተጠቃሚዎች ሀሳባቸውን እንዲያካፍሉ፣ ፎቶዎችን፣ ቪዲዮዎችን፣ ስጦታዎች እንዲለዋወጡ አለፍ ሲልም የእርቃን ምስሎችን እንዲለዋወጡ የሆነው በዚሁ በሴክሽን 230 ምክንያት ነው፡፡ ይህ ህግ ከተወሰኑ ጉዳዮች በቀር እንደ Yelp, Reddit, እና Facebook ያሉ ድረገጾችና አገልግሎቶች ተጠቃሚዎቻቸው በሚያሰራጯቸው ነገሮች ህጋዊ ተጠያቂነት እንደሌለባቸው ይደነግጋል፡፡ ለምሳሌ Wikipedia እየተባለ የሚጠራው የመረጃ ድረገጽ ማንኛውም ተጠቃሚ አንድን ጽሁፍ ማስተካከል እንዲችል ተደርጎ የተሰራ ክፍት ድረ-ገጽ ነው፡፡
ህጉ በገመድ አልባ አገልግሎት ዙሪያ ከወጡ ህጎች በላቀ መልኩ በጣም ወሳኝ የሆነበትን ምክንያት ጥያቄ የሚያስነሳ ሲሆን ከወግ አጥባቂዎቹ በኩል በሆኑ ተጽዕኖ ፈጣሪ የኮንግረንስ አባላት በክፉ አይን መታየቱ አልቀረም፡፡ ከዚህ ህግ አንጻር ሀለት እይታዎች አሉ፡፡ በአንድ በኩል አብዛኛዎቹ ኤክስፐርቶች እንደሚስማሙት ህግ አውጭዎች የህጉን መሰረታዊ አላማ ችላ ብለው እንደሰሩት ሲታመን በሌላ በኩል ደግሞ ፖለቲካዊ ነጥብ ከማስቆጠር ያለፈ ነገር የለውም ብለው የሚያምኑ አሉ፡፡ ሴክሽን 230 ድረገጾች ፖለቲካዊ አላማ ይኑራቸውም አይኑራቸውም ሁሉንም የሚጠብቅ ህግ ነው፡፡
በሪፐብሊካኑ አባል ቤን ሻፒሮ በሚንቀሳቀሰው Daily Wire በሚባለው የዜና ምንጭ በየጽሁፎቹ አንባቢዎች ከፍተኛ ስም ማጥፋት የታከለባቸውን አስተያየቶችን ይጽፋሉ፡፡ በሴክሽን 230 ህግ መሰረት አዘጋጁም ሆነ አስተያየት ሰጭዎች ምንም አይነት ህጋዊ ተጠያቂነት የለባቸውም፡፡
ሴክሽን 230 እየተባለ የሚጠራው ህግ
“No provider or user of an interactive computer service shall be treated as the publisher or speaker of any information provided by another information content provider.”
የሚል ሲሆን በጥቅሉ በአንድ ፕላትፎርም የሚሳተፉ ተጠቃሚዎች በሚያሰራጩት መረጃ ምክንያት የፕላትፎርሙ ባለቤት ህጋዊ ተጠያቂነት የለበትም የሚል ነው፡፡ ይሁን እንጂ በ90ዎቹ በፍርድ ቤት የተወሰነ አንድ ውሳኔ በገመድ አልባ አገልግሎት በሚኖር ህጋዊ ባልሆነ ድርጊት ተጠያቂነት ሊኖር እንደሚችል ታይቷል፡፡ በዚህም ይህ አገልግሎት በህግ የተሰጠውን ሙሉ ነጻነት እንደማይጠቀም መረዳት ይቻላል፡፡
ህጉ ብዙ ችግር አለው ብለው የሚስማሙ ወግ አጥባቂዎቹ ሪፐብሊካኖች እንደ Fight Online Sex Trafficking Act (FOSTA) አይነት የተሻሻሉ ህጎችን በመጥቀስ ይህም ህግ የሶስተኛ ወገን ተጠያቂነትን በሚያመጣ መልኩ መሻሻል አለበት በማለት እየሞገቱ ነው፡፡ ከጥንስሱ ህጉን ያረቀቁት የዲሞክራቱ Ron Wyden እና የሪፐብሊካኑ Christopher Cox ግብ ያደረጉት የ pornographyን መስፋፋት መግታት ነበር፡፡
ምንጭ፡ GIZMODO (https://gizmodo.com/section-230-is-the-foundation-of-the-internet-so-why-d-1833590565)
Gizmodo
Section 230 Is the Foundation of the Internet, So Why Do Republicans Want to Change It?
Without Section 230 of the Communications Decency Act, most of your favorite websites would not survive—nor would they have existed at all. The modern internet would be a much different place without this short little bit of legislation that has become a…
ያለ ባትሪ የሚሰሩ የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎችን በቅርቡ ልናይ እንችላለን
ምንም እንኳን እንደ ሀገር ያለንበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደረጃ የተሸሉ ከሚባሉት ሀገራት አንፃር አነስተኛ የሚባል ቢሆንም ብዙዎቻችን ከቀን ወደ ቀን በእንቅስቃሴ ውስጥ፣ በቤት፣ ቢሮና ሌሎችም ቦታዎች ላይ የምንጠቀማቸው ስማርት ቁሳቁሶች መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ ነው፡፡ እነዚሀ ቁሶች ስራቸውን ለማከናወን ያስችሏቸው ዘንድ በሆዳቸው የሚታቀፏቸው ባትሪዎች ወዲያው ወዲያው አቅማቸውን የሚሟጠጥ ሲሆኑ በውስጣቸውም በቀላሉ የማይገኙና መርዛማ የሆኑ ቁሶችን ይይዛሉ፡፡ ለዚህም ነው አጥኚዎች ሌላ እነዚህን ቁሶች አንቀሳቃሽ ኃይል ምንጭ ፍለጋ ተሰማርተው የሚገኙት፡፡
አንደኛው ለቁሶቹ ኃይል የማግኛ መንገድ ደግሞ ልክ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ፎቶቮልቴክስ ወይም PVን በመጠቀም ከቤት ውጪ እንደሚያደርጉት ሁሉ የቤት ውስጥ ብርሃንንም ለቁሶቹ የኃይል ምንጭነት መተቀም ነው፡፡ ሆኖም ከብርሃን ምንጩ ልዩነት ጋር በተያያዘ ለሶላር ፓኔሎች የሚውለው ግብዓት ተጠቅሞ የቤት ውስጥ ብርሃንን ወደ ኃይል ለመለወጥ አስቸጋሪ ነው፡፡ አሁን ላይ የለንደኑ ሮያል ኮሌጅ፣ ካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ እና የቻይናው ሶቾው ዩኒቨርሲቲ አጥኚዎች በቤት ውስጥ ያለ ብርሀንንም ወደ ኃይል ለመለወጥ የሚያስችል ሶላርፓኔል በመስራት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
የጥናቱ አካል የሆኑት ዶ/ር ሮበርት ሆዬ በቤት እና ሌሎች ህንፃዎች ውስጥ ካሉ መብራቶች (አምፖል) የሚመነጭ ብርሃንን ውጤታማ በሆነ መልኩ በመሰብሰብ ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል መለወጥ እንደሚቻል ጥናቱ እንዳሳየ ተናግረዋል፡፡
የጥናት ቡድኑ ለቀጣዩ ዘመን የሶላር ፓኔሎች ታስበው ከተሰሩት የፔሮቭስካይት ቁሶች ተወስደው ግን ደግሞ በዚህ ቁስ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ታልመው የተሰሩትን ፔሮቭስካይትን መነሻ ያደረጉ ቁሶችን መርምሯል፡፡ ፔሮቭስካይቶች ከተለምዶአዊው ሲልከን ላይ የተመሰረተ ሶላር ፓኔል አንፃር ተመሳሳይ ኃይል የሚያመነጩና ለመስራትም ርካሽ ቢሆኑም መርዛማ የሊድ ንጥረ ነገሮችን ይይዛሉ፡፡ በዚህም ሳብያ እንደ ቢዝመዝ እና አንቲሞኒን ያሉ ግብዓቶችን የሚጠቀሙ ፔሮቭስካይትን መነሻ ያደረጉ ቁሶችን የመስራት እንቅስቃሴ እንዲያድግ ሆኗል፡፡ ታድያ እነዚህ ቁሶች ለአካባቢ ተስማሚ ሆነው ቢገኙም የፀሐይ ብርሃንን በመሰብሰብ ረገድ ግን ውጤታማነታቸው ያነሰ ነው፡፡ ሆኖም እንደ ጥናት ቡድኑ ግኝት ከሆነ ቁሶቹ በአንፃራዊነት የቤት ወስጥ ብርሀንን በመሰብሰብ ረገድ እጅጉን የተሻሉ መሆናቸውን ያረጋገጡ ሲሆን በሙከራቸውም በእነዚህ ቁሶች አማካኝነት የሚገኘው ኃይል የኤሌክትሮኒክ ሰርኪቶችን ለማንቀሳቀስ የሚችል ሆኖ አግኝተውታል፡፡
እንደ ጥናታ ተሳታፊ ባለሙያዎች ከሆነ አዲሱ ግኝት አረንጓዴ ልማትን ይበልጥ የሚያጎለብትና በቅርቡም ባትሪ አልባ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ሊሰጠን የሚችል ነው፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
ምንም እንኳን እንደ ሀገር ያለንበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ደረጃ የተሸሉ ከሚባሉት ሀገራት አንፃር አነስተኛ የሚባል ቢሆንም ብዙዎቻችን ከቀን ወደ ቀን በእንቅስቃሴ ውስጥ፣ በቤት፣ ቢሮና ሌሎችም ቦታዎች ላይ የምንጠቀማቸው ስማርት ቁሳቁሶች መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ ነው፡፡ እነዚሀ ቁሶች ስራቸውን ለማከናወን ያስችሏቸው ዘንድ በሆዳቸው የሚታቀፏቸው ባትሪዎች ወዲያው ወዲያው አቅማቸውን የሚሟጠጥ ሲሆኑ በውስጣቸውም በቀላሉ የማይገኙና መርዛማ የሆኑ ቁሶችን ይይዛሉ፡፡ ለዚህም ነው አጥኚዎች ሌላ እነዚህን ቁሶች አንቀሳቃሽ ኃይል ምንጭ ፍለጋ ተሰማርተው የሚገኙት፡፡
አንደኛው ለቁሶቹ ኃይል የማግኛ መንገድ ደግሞ ልክ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ፎቶቮልቴክስ ወይም PVን በመጠቀም ከቤት ውጪ እንደሚያደርጉት ሁሉ የቤት ውስጥ ብርሃንንም ለቁሶቹ የኃይል ምንጭነት መተቀም ነው፡፡ ሆኖም ከብርሃን ምንጩ ልዩነት ጋር በተያያዘ ለሶላር ፓኔሎች የሚውለው ግብዓት ተጠቅሞ የቤት ውስጥ ብርሃንን ወደ ኃይል ለመለወጥ አስቸጋሪ ነው፡፡ አሁን ላይ የለንደኑ ሮያል ኮሌጅ፣ ካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ እና የቻይናው ሶቾው ዩኒቨርሲቲ አጥኚዎች በቤት ውስጥ ያለ ብርሀንንም ወደ ኃይል ለመለወጥ የሚያስችል ሶላርፓኔል በመስራት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡
የጥናቱ አካል የሆኑት ዶ/ር ሮበርት ሆዬ በቤት እና ሌሎች ህንፃዎች ውስጥ ካሉ መብራቶች (አምፖል) የሚመነጭ ብርሃንን ውጤታማ በሆነ መልኩ በመሰብሰብ ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል መለወጥ እንደሚቻል ጥናቱ እንዳሳየ ተናግረዋል፡፡
የጥናት ቡድኑ ለቀጣዩ ዘመን የሶላር ፓኔሎች ታስበው ከተሰሩት የፔሮቭስካይት ቁሶች ተወስደው ግን ደግሞ በዚህ ቁስ ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ታልመው የተሰሩትን ፔሮቭስካይትን መነሻ ያደረጉ ቁሶችን መርምሯል፡፡ ፔሮቭስካይቶች ከተለምዶአዊው ሲልከን ላይ የተመሰረተ ሶላር ፓኔል አንፃር ተመሳሳይ ኃይል የሚያመነጩና ለመስራትም ርካሽ ቢሆኑም መርዛማ የሊድ ንጥረ ነገሮችን ይይዛሉ፡፡ በዚህም ሳብያ እንደ ቢዝመዝ እና አንቲሞኒን ያሉ ግብዓቶችን የሚጠቀሙ ፔሮቭስካይትን መነሻ ያደረጉ ቁሶችን የመስራት እንቅስቃሴ እንዲያድግ ሆኗል፡፡ ታድያ እነዚህ ቁሶች ለአካባቢ ተስማሚ ሆነው ቢገኙም የፀሐይ ብርሃንን በመሰብሰብ ረገድ ግን ውጤታማነታቸው ያነሰ ነው፡፡ ሆኖም እንደ ጥናት ቡድኑ ግኝት ከሆነ ቁሶቹ በአንፃራዊነት የቤት ወስጥ ብርሀንን በመሰብሰብ ረገድ እጅጉን የተሻሉ መሆናቸውን ያረጋገጡ ሲሆን በሙከራቸውም በእነዚህ ቁሶች አማካኝነት የሚገኘው ኃይል የኤሌክትሮኒክ ሰርኪቶችን ለማንቀሳቀስ የሚችል ሆኖ አግኝተውታል፡፡
እንደ ጥናታ ተሳታፊ ባለሙያዎች ከሆነ አዲሱ ግኝት አረንጓዴ ልማትን ይበልጥ የሚያጎለብትና በቅርቡም ባትሪ አልባ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ሊሰጠን የሚችል ነው፡፡
ምንጭ፡ Tech Xplore
በሩሲያ ቅልጥ እሳተ ገሞራ የተገኘው አዲሱ ምስጢራዊ ማእድን
*********************
ተመራማሪዎች በሩሲያ ቅልጥ እሳተ ገሞራ አዲስ ማእድን ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ እንደሚታወቀው በአለማችን አስጨናቂ ከሆኑና ብዙ ጥፋቶችን ከሚያስከትሉ ተፈጥሯዊ ክስተቶች መካከል እሳተ ገሞራ አንዱና ዋነናው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ገሞራ ካለው ጉዳት በተቃራኒ የተፈጥሮ ምስጢራትን በመግለጥ በኩል የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተመራማሪዎች ይስማማሉ፡፡ ለዚህም ነው የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ያጠፋልም ያለማልም የሚባለው፡፡
አዲስ በተሰራ ጥናት የሩሲያ ተመራማሪዎች በገሞራ ፍንዳታ ምክንያት የተፈጠረን አንድ አዲስና ያልተለመደ ማእድን ማግኘታቸውን አሳውቀዋል፡፡ ተመራማሪዎቹ ፔትሮቫይት ሲሉ የሰየሙት አስደናቂው ደማቅ ሰማያዊና አረንጓዴ ቀለም ያለው ጠጣር ንጥረ ነገር ከዚህ በፊት በሳይንስ ተመዝግበው ካሉት ማእድናት ሁሉ የተለየ እንደሆነ ተመስክሮለታል፡፡
ንጥረ ነገሩ የተገኘው በሩሲያ ሩቅ ምስራቅ በሚገኝ ካምቻትካ ከፍታ ቶልባቺክ በሚባል እሳተ ገሞራ ነው፡፡ ቶልባቺክ ገሞራ ከሺህ አመታት በላይ ታሪክ ያለው የገሞራ ፍንዳታ ሲሆን ሁለት በጣም የታወቁ ፍንዳታዎች አሉት፡፡ ከእነዚህም አንዱ ከ1975–1976 የተከሰተው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከ2012–2013 የተከሰተው ነው፡፡
በመጀመሪያው በነበረው ከፍተኛ ሀይል ያለው ፍንዳታ ብዛት ያላቸው የእሳት ፍንጥርጣሪዎች እና የትም ቦታ ታይተው የማይታወቁ ማእድናት ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ የቶለባቺክ ገሞራ 130 ዓይነት በዚህ አካባቢ ብቻ የሚገኙ ማእድናትን አስገኝቷል፡፡ ከእነዚህ ማእድናት የቅርብ ጊዜው ፔትሪቫይት ነው፡፡ ይህም ሰማያዊ ቀለም ያለው ባለ ድቦልቡል ቅርጽ ሰልፌት ማእድን ነው፡፡
በአዲሱ ማእድን የተገኘው የኮፐር ቅንጣት የልተለመደና በቀላሉ የማይገኝ ከ7 የኦክስጅን ቅንጣቶች ጋር የተጣመረ ነው፡፡ የዚህ አይነት ባህሪ የሚገኘው በውህዶች ብቻ እንደሆነ የSt Petersburg University የምርምሩ መሪ ተናግሯል፡፡ የፔተሮቫየት ሞሎኪዩላዊ ቀመሩ (molecular framework) ኦክስጅን፣ ሶዲየም፣ ሳልፈርና ኮፐር በተፈጥሮ አብረው የተሰሩ ናቸው፡፡
ምንጭ Science alert
*********************
ተመራማሪዎች በሩሲያ ቅልጥ እሳተ ገሞራ አዲስ ማእድን ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ እንደሚታወቀው በአለማችን አስጨናቂ ከሆኑና ብዙ ጥፋቶችን ከሚያስከትሉ ተፈጥሯዊ ክስተቶች መካከል እሳተ ገሞራ አንዱና ዋነናው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ገሞራ ካለው ጉዳት በተቃራኒ የተፈጥሮ ምስጢራትን በመግለጥ በኩል የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው ተመራማሪዎች ይስማማሉ፡፡ ለዚህም ነው የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ያጠፋልም ያለማልም የሚባለው፡፡
አዲስ በተሰራ ጥናት የሩሲያ ተመራማሪዎች በገሞራ ፍንዳታ ምክንያት የተፈጠረን አንድ አዲስና ያልተለመደ ማእድን ማግኘታቸውን አሳውቀዋል፡፡ ተመራማሪዎቹ ፔትሮቫይት ሲሉ የሰየሙት አስደናቂው ደማቅ ሰማያዊና አረንጓዴ ቀለም ያለው ጠጣር ንጥረ ነገር ከዚህ በፊት በሳይንስ ተመዝግበው ካሉት ማእድናት ሁሉ የተለየ እንደሆነ ተመስክሮለታል፡፡
ንጥረ ነገሩ የተገኘው በሩሲያ ሩቅ ምስራቅ በሚገኝ ካምቻትካ ከፍታ ቶልባቺክ በሚባል እሳተ ገሞራ ነው፡፡ ቶልባቺክ ገሞራ ከሺህ አመታት በላይ ታሪክ ያለው የገሞራ ፍንዳታ ሲሆን ሁለት በጣም የታወቁ ፍንዳታዎች አሉት፡፡ ከእነዚህም አንዱ ከ1975–1976 የተከሰተው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከ2012–2013 የተከሰተው ነው፡፡
በመጀመሪያው በነበረው ከፍተኛ ሀይል ያለው ፍንዳታ ብዛት ያላቸው የእሳት ፍንጥርጣሪዎች እና የትም ቦታ ታይተው የማይታወቁ ማእድናት ተገኝተዋል፡፡ በአጠቃላይ የቶለባቺክ ገሞራ 130 ዓይነት በዚህ አካባቢ ብቻ የሚገኙ ማእድናትን አስገኝቷል፡፡ ከእነዚህ ማእድናት የቅርብ ጊዜው ፔትሪቫይት ነው፡፡ ይህም ሰማያዊ ቀለም ያለው ባለ ድቦልቡል ቅርጽ ሰልፌት ማእድን ነው፡፡
በአዲሱ ማእድን የተገኘው የኮፐር ቅንጣት የልተለመደና በቀላሉ የማይገኝ ከ7 የኦክስጅን ቅንጣቶች ጋር የተጣመረ ነው፡፡ የዚህ አይነት ባህሪ የሚገኘው በውህዶች ብቻ እንደሆነ የSt Petersburg University የምርምሩ መሪ ተናግሯል፡፡ የፔተሮቫየት ሞሎኪዩላዊ ቀመሩ (molecular framework) ኦክስጅን፣ ሶዲየም፣ ሳልፈርና ኮፐር በተፈጥሮ አብረው የተሰሩ ናቸው፡፡
ምንጭ Science alert
ስለ አርዲ እና ቀደምት የሰው ቅሪተ አካላት የተጻፈው መጽሀፍ
**************
በKermit Pattison የተጻፈው ‘Fossil Men’ የተሰኘው መጽሐፍ ሳይንስንና ድራማን በማዋሀድ ስለ ጥንታዊው ስነ-ሰብ የሚተርክ ሲሆን በአለማችን እጅግ ታዋቂ የሆኑት ቅሪተ አካላት የታሪኩ ክፍል ሆነዋል፡፡ እንደ ዘገባ ምንጫችን Science News እጅግ አስገራሚዋ እና በስነ ቁፋሮ ሳይንስ እስካሁን ከተገኙ ጥንታዊ የሰው ዘር ቅሪተ አካት መካከል ልዩ የሆነችው አርዲ እና ተመራማሪዎቿ በመጽሀፉ ውስጥ ተካትተዋል፡፡
በመጽሐፉ ውስጥ ጋዜጠኛው Kermit Pattison በአርዲ ፍለጋ ላይ የተሳተፉ ተመራማሪዎች በሰው ዘር ዝግመተ ለውጥ ታሪክ ውስጥ የታወቀውን እሳቤ ለመሞገት የሄዱበትን መንገድ ማራኪ ታሪኮችን በመጠቀም ያስነብባል፡፡ በተጨማሪም የአርዲ ቅሬተ አካል ከሌሎች ቅሬተ አካላት የተለየ የሆነበትን ምክንያትም መጽሀፉ ያስረዳል፡፡
የቁፋሮ ምርምር ቡድኑ በምርምር ሂደቱ የያዛቸውን ፎቶዎች ቪዲዮዎችና ልዩ ልዩ ማስታዎሻዎች ያካተተው መጽሐፉ አርዲ የተገኘችበትን የመጀመሪያ ቅጽበት የገለጸበት መንገድ ሳቢ ነው፡፡ ጋዜጠኛው ሁኔታውን ሲያስረዳ የምርምር ቡድኑ ብቸኛ ጥበቃ የሆነው የአፋሩ ጋዲ ከምርምር ቡድኑ ጋር አብሮ ይንቀሳቀስ በነበረበት ወቅት ከቁፋሮው ስፍራ አንድ ጥርስ እንዳገኘ ይናገራል፡፡ ይህ ጋዲ ያገኘው ጥርስ በቁፋሮ ከተገኙት የአርዲ አስር ጥርሶች መካከል አንዱ ነበር፡፡
ምንጭ Science News Magazine
**************
በKermit Pattison የተጻፈው ‘Fossil Men’ የተሰኘው መጽሐፍ ሳይንስንና ድራማን በማዋሀድ ስለ ጥንታዊው ስነ-ሰብ የሚተርክ ሲሆን በአለማችን እጅግ ታዋቂ የሆኑት ቅሪተ አካላት የታሪኩ ክፍል ሆነዋል፡፡ እንደ ዘገባ ምንጫችን Science News እጅግ አስገራሚዋ እና በስነ ቁፋሮ ሳይንስ እስካሁን ከተገኙ ጥንታዊ የሰው ዘር ቅሪተ አካት መካከል ልዩ የሆነችው አርዲ እና ተመራማሪዎቿ በመጽሀፉ ውስጥ ተካትተዋል፡፡
በመጽሐፉ ውስጥ ጋዜጠኛው Kermit Pattison በአርዲ ፍለጋ ላይ የተሳተፉ ተመራማሪዎች በሰው ዘር ዝግመተ ለውጥ ታሪክ ውስጥ የታወቀውን እሳቤ ለመሞገት የሄዱበትን መንገድ ማራኪ ታሪኮችን በመጠቀም ያስነብባል፡፡ በተጨማሪም የአርዲ ቅሬተ አካል ከሌሎች ቅሬተ አካላት የተለየ የሆነበትን ምክንያትም መጽሀፉ ያስረዳል፡፡
የቁፋሮ ምርምር ቡድኑ በምርምር ሂደቱ የያዛቸውን ፎቶዎች ቪዲዮዎችና ልዩ ልዩ ማስታዎሻዎች ያካተተው መጽሐፉ አርዲ የተገኘችበትን የመጀመሪያ ቅጽበት የገለጸበት መንገድ ሳቢ ነው፡፡ ጋዜጠኛው ሁኔታውን ሲያስረዳ የምርምር ቡድኑ ብቸኛ ጥበቃ የሆነው የአፋሩ ጋዲ ከምርምር ቡድኑ ጋር አብሮ ይንቀሳቀስ በነበረበት ወቅት ከቁፋሮው ስፍራ አንድ ጥርስ እንዳገኘ ይናገራል፡፡ ይህ ጋዲ ያገኘው ጥርስ በቁፋሮ ከተገኙት የአርዲ አስር ጥርሶች መካከል አንዱ ነበር፡፡
ምንጭ Science News Magazine
ሲንጋፖር የቴክኖሎጂ ፈጠራ ተሰጥኦ ላላቸው ሰዎች አዲስ ቪዛ አዘጋጀች
*********************
ለባለ ተሰጥኦዎች የተዘረጋ ቀይ ምንጣፍ ያላት ሲንጋፖር 500 ሰዎች የሚሳተፉበት ልዩ የተሰጥኦ ማሳያ ዝግጅት አቅዳለች፡፡ ለዝግጅቱም በቴክኖሎጂው አለም ተሞክሮ ያለፈ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች እንደሚሳተፉ ተገልጧል፡፡ Tech.Pass program በተሰኘው እቅድ አዲስ ቪዛ የተዘጋጀላቸው ሰዎች ብቃታቸው የተረጋገጠ እና ወደ ከተማዋ መጥተው ከአንድ በላይ ተቋም ገንብተው አልሚዎች እንዲሆኑ ወይም ለጀማሪ ተቋማት አማካሪ እና አሰልጣኝ እንዲሆኑ የታሰበ ነው፡፡ይህም ድርጅቶች የሚፈልጉትን ሰው ስፖንሰር በማድረግ ብቻ ወደከተማዋ እንዲያስገቡ የሚፈቅደው የመንግስት መመሪያ እየተሸሻለ መሄዱን የሚያሳይ ነው፡፡
የሁለት አመታት የጊዜ ርዝማኔ ያለው ቪዛ የተፈቀደው መካከለኛ ክህሎት ላላቸውና የአካባቢውን ገበያ ለሚሻሙ የፈጠራ ሙያተኞች ሳይሆን ከተማዋ የቀጠናው የቴክኖሎጂ ማእከል ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ ሊያቀላትፉ የሚችሉ ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን የቴክኖሎጂ ሰዎች ለማምጣት ያለመ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስራ ለውጭ ዜጎች የሚሰጥበትን መመሪያ እንዲጠብቅ በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና ስላደረበትም እንደሆነ የዘገባችን ምንጭ ገልጧል፡፡
የከተማዋ የገበያና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሆኑት Chan Chun Sing ፕሮግራሙ በቀጠናው የምንፈልገውን ቴክኖሎጂ የበላይነት እንድናመጣ ከፍተኛ ሚና ያለውና መንገዱንም ቀላል የሚያደርግልን ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የፊታችን ጥር በሚጀምረው ምልመላ ተወዳዳሪዎች ለውድድር ከማመልከታቸው በፊት ካሉት ሶስት መስፈርቶች መካከል ቢያንስ ሁለቱን ማሟላት እንዳለባቸው ተነግሯል፡፡
ለማመልከትም ቢያንስ አምስት አመት የስራ ልምድ የቴክኖሎጆ ተቋምን በመምራት ወይም በቴክኖሎጂ ተቋም በመስራት ተቋሙ ቢያን 500 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ እንዲያገኝ ያደረገ/ች ወይም በባለሙያነት በተሰራ ስራ ቢያንስ 100,000 ተጠቃሚዎች ያሉት ፈጠራን የሰራ/ች እና በስራ ዘመን ከ14,800 ዶላር ያላነሰ ተከፋይ የሆነ/ች መሆን እንዳለበት ተገልጧል፡፡
ምንጭ Bloomberg Technology
*********************
ለባለ ተሰጥኦዎች የተዘረጋ ቀይ ምንጣፍ ያላት ሲንጋፖር 500 ሰዎች የሚሳተፉበት ልዩ የተሰጥኦ ማሳያ ዝግጅት አቅዳለች፡፡ ለዝግጅቱም በቴክኖሎጂው አለም ተሞክሮ ያለፈ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች እንደሚሳተፉ ተገልጧል፡፡ Tech.Pass program በተሰኘው እቅድ አዲስ ቪዛ የተዘጋጀላቸው ሰዎች ብቃታቸው የተረጋገጠ እና ወደ ከተማዋ መጥተው ከአንድ በላይ ተቋም ገንብተው አልሚዎች እንዲሆኑ ወይም ለጀማሪ ተቋማት አማካሪ እና አሰልጣኝ እንዲሆኑ የታሰበ ነው፡፡ይህም ድርጅቶች የሚፈልጉትን ሰው ስፖንሰር በማድረግ ብቻ ወደከተማዋ እንዲያስገቡ የሚፈቅደው የመንግስት መመሪያ እየተሸሻለ መሄዱን የሚያሳይ ነው፡፡
የሁለት አመታት የጊዜ ርዝማኔ ያለው ቪዛ የተፈቀደው መካከለኛ ክህሎት ላላቸውና የአካባቢውን ገበያ ለሚሻሙ የፈጠራ ሙያተኞች ሳይሆን ከተማዋ የቀጠናው የቴክኖሎጂ ማእከል ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ ሊያቀላትፉ የሚችሉ ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን የቴክኖሎጂ ሰዎች ለማምጣት ያለመ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስራ ለውጭ ዜጎች የሚሰጥበትን መመሪያ እንዲጠብቅ በመንግስት ላይ ከፍተኛ ጫና ስላደረበትም እንደሆነ የዘገባችን ምንጭ ገልጧል፡፡
የከተማዋ የገበያና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሆኑት Chan Chun Sing ፕሮግራሙ በቀጠናው የምንፈልገውን ቴክኖሎጂ የበላይነት እንድናመጣ ከፍተኛ ሚና ያለውና መንገዱንም ቀላል የሚያደርግልን ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የፊታችን ጥር በሚጀምረው ምልመላ ተወዳዳሪዎች ለውድድር ከማመልከታቸው በፊት ካሉት ሶስት መስፈርቶች መካከል ቢያንስ ሁለቱን ማሟላት እንዳለባቸው ተነግሯል፡፡
ለማመልከትም ቢያንስ አምስት አመት የስራ ልምድ የቴክኖሎጆ ተቋምን በመምራት ወይም በቴክኖሎጂ ተቋም በመስራት ተቋሙ ቢያን 500 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ እንዲያገኝ ያደረገ/ች ወይም በባለሙያነት በተሰራ ስራ ቢያንስ 100,000 ተጠቃሚዎች ያሉት ፈጠራን የሰራ/ች እና በስራ ዘመን ከ14,800 ዶላር ያላነሰ ተከፋይ የሆነ/ች መሆን እንዳለበት ተገልጧል፡፡
ምንጭ Bloomberg Technology
ከምድር የመጥፋት አደጋ የተጋረጠበት የዱር ህይወት 9 አሳዛኝ እውነታዎች
የምድር እጣፈንታ እና የአለማችን የተፈጥሮ ገፅታ ከመቼውም ጊዜ በላይ በከባድ ስጋት ውስጥ እንደሚገኝ የማያጠራጥር ነው፡፡ የምድርን የተፈጥሮ ሚዛኗ ሊያስቱ የሚችሉ አያሌ አደጋዎች በሰው ልጆች የህይወት ዘመን ውስጥ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መፈፀማቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ዓለማችን ከዕለት ወደ ዕለት የሙቀት መጠኗ እየጨመረ፣ አቅፋ የያዘቻቸው የተለያዩ ሰብሎችና እንስሳት የመጥፋት አደጋ እየተጋረጠባቸው ይገኛል፡፡
ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዘጠኝ እውነታዎች ወይም ምክንያቶች መኖሪያችን ብለን በምንጠራት መሬት እየተከሰቱ ያሉ እና የኛን ፈጣን ምላሽ የሚጠብቁ አሳዛኛ ሁኔታዎች ናቸው፡፡
1 - አሁን ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በሰው ልጆች ታሪክ እስካሁን ያልታየ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኗል፡፡ የተቋሙ መረጃ እንደሚያሳየው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል፡፡
2 - የዱር አንስሳት ብዛት ከ1970 በኋላ በ2/3ኛ ቀንሷል
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው እንደአውሮፓውያኑ ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ የዱር አንስሳ ብዛት መጠን በአማካይ በ68% መቀነስ አሳይቷል፡፡ በዚህ የእንስሳት መጠን ውስጥ ወፎች፣ አጥቢ አሳዎች፣ ተሳቢና አምፊቢያን እንስሳቶች በዋናነት በዝርዝር ውስጥ የሚገኙት ናቸው፡፡
3 - የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልሎች በውድቀት ላይ መገኘት
የዱር አንስሳት በብዛት ከሚገኝባው አካባቢዎች ቀዳሚ የሆነው ይህ ንኡስ ክልል ከ1970 ጀምሮ 94% የሚሆነው የዱር አንስሳ የጠፋበት አካባቢ ነው፡፡ የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ እንዳመለከተውም የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልል በየትኛውም የምድር ክፍል ያልተመዘገበ የዱር አንስሳት ጥፋት የታየበት አካባቢ ነው፡፡
4 - ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በተደጋጋሚ የሚሞቱ ዝርያዎች መብዛት
በአሜሪካ በሚገኘው የብራውን ዩኒቨርስቲ በ2014 የተደረገ ጥናት እንደሚያሳው የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከመምጣቱ አስቀድሞ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ አልፎ አልፎ የመጥፈት እድል ነበረው፡፡ ይሁንና ሰዎች ይህችን ምድር ከተቀላቀሉ በኋላ የተለያዩ ዝርያዎች ከምድር የመጥፋት እድላቸው 1,000 ጊዜ ብልጫ እንዳለው እና ይህም ተደጋግሞ እንደሚፈፀምም ጥናቱ አመላክቷል፡፡
5 - በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት መቀነስ
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች ከሌሎች የዱር አንስሳት በተለየ በፍጥነት በመቀነስ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሪፖርቱ እንደተመለከተው ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ በአማካይ 84 በመቶው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት በመቀነስ ላይ ናቸው፡፡
6 - የትሮፒካል ደን በተለያዩ ምክንያቶች መጥፋት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው አንደአውሮፓውያኑ ከ1980 አንስቶ እስከ 2000 ድረስ ብቻ 100 ሚሊዮን ሄክታር ደን በትሮፒካል የምድር አካባቢ ጠፍቷል፡፡ ይህ የደን ጭፍጨፋ በብዛት የተመዘገበው በላቲን አሜሪካ እና በደቡብ ምስራቅ እስያ ሲሆን በዋናነትም ለከብት እርባታ እና ለግብርና በሚል የተከናወነ ነው፡፡
7 - 40 በመቶው እፅዋት የመጥፋት አደጋ
የአለም የእፅዋትና ፈንገስ ሪፖርት በስሩ በሚገኘው ሮያል ቦታኒክ ጋርደን እንደሚያመለክተው ከአስሩ አፅዋቶች አራቱ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ሲሆን ይህም የ39.4% ልኬት ይታይበታል፡፡ በዚህ የመጥፋት አደጋ ውስጥ ከባዱ ስራ እፅዋቶቹ ከመጥፋታቸው በፊት የመለየት ስራ ሲሆን፣ በ2019 ብቻ 1,942 የእፅዋት ዝርያዎች ተለይተው ተመዝግበዋል፡፡
8 - ከግብርና ኢንዱስትሪ ጋር ተያይዞ በአያለው የቀነሱት ነፍሳቶች (insects)
በአለማችን ከግብርና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በአስር አመት ብቻ ከ40 በመቶ በላይ የነፍሳት ዝርያዎች ከምድር ላይ መጥፋታቸውን በሳይንስ ዳይሬክት ላይ በቅርቡ የወጣ አዲስ ምርምር አስታውቋል፡፡
9 - በራሪ የወፍ ዝርያዎች ብዛታቸው እየቀነሰ መምጣት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በአንድ ሃገር ውስጥ መኖሪያቸውን አድርገው የሚራቡ 3.5% የሚሆኑ የወፍ ዝርያዎች ከ2016 ጀምሮ የጠፉ ሲሆን ሌሎች 23 በመቶ የሚሸፍኑ ወፎች ደግሞ በአየር ንብርት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ የመጥፋት አደጋ ያለባቸው ናቸው፡፡
እነዚህ የተፈጥሮ ሃብቶች በዚህ መልኩ አደጋ ውስጥ መገኘታቸው ለኛ ለሰው ልጆች ትልቅ የህልውና ጥያቄ ነው፡፡ የብዛ ህይወት ሃብቶች ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ የተላበሱ በመሆናቸው ማናቸውም በብዛ ህይወት ላይ የሚደርሱ አደጋዎች ለአየር ንብረት መቀያየር ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ በመሆኑም አነዚህ አሳዛኝ አውነታዎች አኛኑ ወደማጥፋት ከመሄዳቸው በፊት ተፈጥሮን ከጥፋት መታደግ የዕለት ተዕለት ተግበራችን ሊሆን ይገባል፡፡
ምንጭ፡ World Economic Forum
የምድር እጣፈንታ እና የአለማችን የተፈጥሮ ገፅታ ከመቼውም ጊዜ በላይ በከባድ ስጋት ውስጥ እንደሚገኝ የማያጠራጥር ነው፡፡ የምድርን የተፈጥሮ ሚዛኗ ሊያስቱ የሚችሉ አያሌ አደጋዎች በሰው ልጆች የህይወት ዘመን ውስጥ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መፈፀማቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ዓለማችን ከዕለት ወደ ዕለት የሙቀት መጠኗ እየጨመረ፣ አቅፋ የያዘቻቸው የተለያዩ ሰብሎችና እንስሳት የመጥፋት አደጋ እየተጋረጠባቸው ይገኛል፡፡
ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ዘጠኝ እውነታዎች ወይም ምክንያቶች መኖሪያችን ብለን በምንጠራት መሬት እየተከሰቱ ያሉ እና የኛን ፈጣን ምላሽ የሚጠብቁ አሳዛኛ ሁኔታዎች ናቸው፡፡
1 - አሁን ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በሰው ልጆች ታሪክ እስካሁን ያልታየ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ የመጥፋት አደጋ ተደቅኗል፡፡ የተቋሙ መረጃ እንደሚያሳየው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዝርያዎች የመጥፋት አደጋ ተጋርጦባቸዋል፡፡
2 - የዱር አንስሳት ብዛት ከ1970 በኋላ በ2/3ኛ ቀንሷል
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው እንደአውሮፓውያኑ ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ የዱር አንስሳ ብዛት መጠን በአማካይ በ68% መቀነስ አሳይቷል፡፡ በዚህ የእንስሳት መጠን ውስጥ ወፎች፣ አጥቢ አሳዎች፣ ተሳቢና አምፊቢያን እንስሳቶች በዋናነት በዝርዝር ውስጥ የሚገኙት ናቸው፡፡
3 - የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልሎች በውድቀት ላይ መገኘት
የዱር አንስሳት በብዛት ከሚገኝባው አካባቢዎች ቀዳሚ የሆነው ይህ ንኡስ ክልል ከ1970 ጀምሮ 94% የሚሆነው የዱር አንስሳ የጠፋበት አካባቢ ነው፡፡ የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ እንዳመለከተውም የአሜሪካ ሞቃታማ ንኡስ ክልል በየትኛውም የምድር ክፍል ያልተመዘገበ የዱር አንስሳት ጥፋት የታየበት አካባቢ ነው፡፡
4 - ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በተደጋጋሚ የሚሞቱ ዝርያዎች መብዛት
በአሜሪካ በሚገኘው የብራውን ዩኒቨርስቲ በ2014 የተደረገ ጥናት እንደሚያሳው የሰው ልጅ ወደዚች ምድር ከመምጣቱ አስቀድሞ የእንስሳትና የእፅዋት ዝርያ አልፎ አልፎ የመጥፈት እድል ነበረው፡፡ ይሁንና ሰዎች ይህችን ምድር ከተቀላቀሉ በኋላ የተለያዩ ዝርያዎች ከምድር የመጥፋት እድላቸው 1,000 ጊዜ ብልጫ እንዳለው እና ይህም ተደጋግሞ እንደሚፈፀምም ጥናቱ አመላክቷል፡፡
5 - በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት መቀነስ
የዓለም የዱር እንስሳት ፈንድ ሊቪንግ ፕላኔት ኢንዴክስ በተባለው የ2020 አመታዊ ሪፖርቱ እንዳመለከተው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች ከሌሎች የዱር አንስሳት በተለየ በፍጥነት በመቀነስ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሪፖርቱ እንደተመለከተው ከ1970 አንስቶ እስከ 2018 ድረስ በአማካይ 84 በመቶው በውሃ ውስጥ የሚኖሩ ዝርያዎች በፍጥነት በመቀነስ ላይ ናቸው፡፡
6 - የትሮፒካል ደን በተለያዩ ምክንያቶች መጥፋት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው አንደአውሮፓውያኑ ከ1980 አንስቶ እስከ 2000 ድረስ ብቻ 100 ሚሊዮን ሄክታር ደን በትሮፒካል የምድር አካባቢ ጠፍቷል፡፡ ይህ የደን ጭፍጨፋ በብዛት የተመዘገበው በላቲን አሜሪካ እና በደቡብ ምስራቅ እስያ ሲሆን በዋናነትም ለከብት እርባታ እና ለግብርና በሚል የተከናወነ ነው፡፡
7 - 40 በመቶው እፅዋት የመጥፋት አደጋ
የአለም የእፅዋትና ፈንገስ ሪፖርት በስሩ በሚገኘው ሮያል ቦታኒክ ጋርደን እንደሚያመለክተው ከአስሩ አፅዋቶች አራቱ የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ሲሆን ይህም የ39.4% ልኬት ይታይበታል፡፡ በዚህ የመጥፋት አደጋ ውስጥ ከባዱ ስራ እፅዋቶቹ ከመጥፋታቸው በፊት የመለየት ስራ ሲሆን፣ በ2019 ብቻ 1,942 የእፅዋት ዝርያዎች ተለይተው ተመዝግበዋል፡፡
8 - ከግብርና ኢንዱስትሪ ጋር ተያይዞ በአያለው የቀነሱት ነፍሳቶች (insects)
በአለማችን ከግብርና ኢንዱስትሪ መስፋፋት ጋር ተያይዞ በአስር አመት ብቻ ከ40 በመቶ በላይ የነፍሳት ዝርያዎች ከምድር ላይ መጥፋታቸውን በሳይንስ ዳይሬክት ላይ በቅርቡ የወጣ አዲስ ምርምር አስታውቋል፡፡
9 - በራሪ የወፍ ዝርያዎች ብዛታቸው እየቀነሰ መምጣት
የአለም አቀፉ የብዛ ህይወትና ስነምህዳር አገልግሎት በሳይንስ ፖሊሲ ፕላትፎርም ላይ እንዳስታወቀው በአንድ ሃገር ውስጥ መኖሪያቸውን አድርገው የሚራቡ 3.5% የሚሆኑ የወፍ ዝርያዎች ከ2016 ጀምሮ የጠፉ ሲሆን ሌሎች 23 በመቶ የሚሸፍኑ ወፎች ደግሞ በአየር ንብርት ለውጥ ምክንያት ከፍተኛ የመጥፋት አደጋ ያለባቸው ናቸው፡፡
እነዚህ የተፈጥሮ ሃብቶች በዚህ መልኩ አደጋ ውስጥ መገኘታቸው ለኛ ለሰው ልጆች ትልቅ የህልውና ጥያቄ ነው፡፡ የብዛ ህይወት ሃብቶች ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ የተላበሱ በመሆናቸው ማናቸውም በብዛ ህይወት ላይ የሚደርሱ አደጋዎች ለአየር ንብረት መቀያየር ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ በመሆኑም አነዚህ አሳዛኝ አውነታዎች አኛኑ ወደማጥፋት ከመሄዳቸው በፊት ተፈጥሮን ከጥፋት መታደግ የዕለት ተዕለት ተግበራችን ሊሆን ይገባል፡፡
ምንጭ፡ World Economic Forum
በጆሯችን አካባቢ የሚፈጠርን ምናባዊ ድምጽ (tinnitus) ለማከም ሰውሰራሽ ክህሎትን መጠቀም
*********************
በጆሯችን የምንሰማውን በገሀዱ አለም የሌለ ምናባዊ ድምጽ ለማስተካከል የጭንቅላት ምስሎችን መጠቀም የሚያስችል ሰውሰራሽ ክህሎት በመጠቀም እንደተቻለ የመረጃ ምንጫችን New scientist ዘገበ፡፡ በአውስትራሊያ ሜልቦርን በሚገኝ አንድ የምርምር ተቋም በአንድ ሰው ጭንቅላት ውስጥ ምናባዊ ድምጽ መኖር አለመኖሩንና ሊያስከትል የሚችለውን የጉዳት መጠን መለካት የሚያስችል የክትትል ሂደት (algorithm) መዘጋጀቱ ተሰምቷል፡፡
ሰውሰራሽ ክህሎቱ በጭንቅላት ውስጥ የሚፈጠርን ድምጽ በ78 በመቶ ትክክለኝነት ከቀላል እስከ ከባድ ደረጃ ያለውን መለካት ያስችላል፡፡ 15 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሶች ከባድ በሚባል ምናባዊ ድምጽ የሚጠቁ ሲሆን በአብዛኛው የጀሮ የመስማት አቅምን በመለካትና ታማሚው በሚያቀርበው መረጃ መሰረት ህክምና ይሰጣል፡፡
የምርምር ቡድኑ በመጀመሪያ functional near-infrared spectroscopy, ወይም fNIRS የተሰኘ ሳይንሳዊ መንገድን በከባድ ችግር ላይ ባሉ 25 ሰዎችና ችግሩ በሌለባቸው 21 ሰዎች ተግባራዊ አደረጉ፡፡
ተመራማሪዎች የተለያዩ ልኬቶችን ከሰሩ በኋላ ቀደም ብለው ያዘጋጁትን አሊጎሪዝም ከ fNIRS ጋር የማላመድ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በዚህም በዘርፉ አዲስ ውጤት ይገኛል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ፡ new scientist
*********************
በጆሯችን የምንሰማውን በገሀዱ አለም የሌለ ምናባዊ ድምጽ ለማስተካከል የጭንቅላት ምስሎችን መጠቀም የሚያስችል ሰውሰራሽ ክህሎት በመጠቀም እንደተቻለ የመረጃ ምንጫችን New scientist ዘገበ፡፡ በአውስትራሊያ ሜልቦርን በሚገኝ አንድ የምርምር ተቋም በአንድ ሰው ጭንቅላት ውስጥ ምናባዊ ድምጽ መኖር አለመኖሩንና ሊያስከትል የሚችለውን የጉዳት መጠን መለካት የሚያስችል የክትትል ሂደት (algorithm) መዘጋጀቱ ተሰምቷል፡፡
ሰውሰራሽ ክህሎቱ በጭንቅላት ውስጥ የሚፈጠርን ድምጽ በ78 በመቶ ትክክለኝነት ከቀላል እስከ ከባድ ደረጃ ያለውን መለካት ያስችላል፡፡ 15 በመቶ የሚሆኑ ጎልማሶች ከባድ በሚባል ምናባዊ ድምጽ የሚጠቁ ሲሆን በአብዛኛው የጀሮ የመስማት አቅምን በመለካትና ታማሚው በሚያቀርበው መረጃ መሰረት ህክምና ይሰጣል፡፡
የምርምር ቡድኑ በመጀመሪያ functional near-infrared spectroscopy, ወይም fNIRS የተሰኘ ሳይንሳዊ መንገድን በከባድ ችግር ላይ ባሉ 25 ሰዎችና ችግሩ በሌለባቸው 21 ሰዎች ተግባራዊ አደረጉ፡፡
ተመራማሪዎች የተለያዩ ልኬቶችን ከሰሩ በኋላ ቀደም ብለው ያዘጋጁትን አሊጎሪዝም ከ fNIRS ጋር የማላመድ ስራ እየሰሩ ነው፡፡ በዚህም በዘርፉ አዲስ ውጤት ይገኛል ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ፡ new scientist