ህጻናት ስለደስታ የሚያስተምሩን 10 ነገሮች
1- ውስጣቸውን የተሸለ ያዳምጣሉ፡- ሀፃናት ስለ ውሳኔያቸው ትክከለኝነት ሲጨነቁ የሚያባክኑት ጊዜ የላቸውም ፡፡
2- አሁንን ይኖራሉ፡- እነርሱ ስለትናነት እያስታወሱ በትዝታ ውስጥ የሚማስኑ ፍጡች ካመሆናቸው በላይ ስለወደፊትም በምንም መልኩ አያስቡም፡፡
3- ያምናሉ፡- ህፃናት ማንኛው የተነገራቸውን ነገር የሚያምኑ ሲሆኑ በነሱ አዕምሮ ውስጥ ላይሆን ይችላል የሚል የጥረውጣሬ መንፈስ አይከሰትም፡፡ ምንም እንኳ ትናነት የተነገራቸው ነገር ዛሬ ላይ ባይከሰትም እንኳ እነርሱ ከማመን ሰንፈው አያውቁም፡፡
4- ሰራተኞች ናቸው፡- ህፃናት ሁሌም በስራ ላይ ናቸው ይቆርጣሉ፣ ይቀባሉ፣ ይስላሉ፣ ያቦካሉ ፣ያጣብቃሉ ፡፡ ህጻናት ከልባቸው ታትረው ይለፋሉ፡፡
5- ይጨፍራሉ፡- "ማንም ሰው እያያቹ እንዳልሆነ አስባችሁ ጨፍሩ " የሚለውን ንግግር ያውቁታል? አዎ ህፃናት እንደዚያ ናቸው፡፡ ማንም አጠገባቸው ቢኖር እነርሱ በራሳቸው መንገድ የራሳቸውን የነፃነት ጭፈራ በሙሉ ደስታ ይጨፍራሉ፡፡
6- ይዘፍናሉ፡- ህፃናት በየትኛውም ሰዓት ይዘፍናሉ፡፡ እየታጠቡ ፣ እየተራመዱ ፣ እየተኙም በእንቅልፍ ልብ ሳይቀር ህፃናት ከመዝፈን ወደ ኋላ አይሉም፡፡
7- ማለት የሚፈልጉትን ሁሉ ይላሉ፡- ህፃናት አዕምሯቸው ውስጥ ተከስቶ የማይተነፍሱት ነገር የለም ምናልባት ረስተውት ካልሆነ፡፡ በልባቸው ውስጥ አስቀምጠው የሚታመሙበት ጉዳይ የለም፡፡ ምናልባት አዋቂዎች እንዲህ የሚያደርጉት ለፋሲካ ዋዜማ ከጠጡ ብቻ ነው፡፡
8- ጉጉ ናቸው፡- ህፃናት በጣም ይጓጓሉ፡፡ ሆኖም ሰዓትን የመለየት ችግር ስላለባቸው ወደፊት ምን ያህል እንደሚርቅ አዕምሯቸው መቀመር አይችልም፤ ስለዚህ ልደታቸው እንደቀረበ ከሳምንት እና ከወር በፊት መናገር ለወላጆች እራስ ላይ ጦርነት እንደ ማወጅ ነው፡፡
9- አዲስ ይሁን አይሁን ግድ አይሰጣቸውም፡- ህፃናት ይመቻቸው እንጂ ፊልሙን በየቀኑ አይተውት ይሁን አይሁን አያስጨንቃቸውም፡፡ ይውደዱት እንጂ ያንን ቀሚስ በየቀኑ መልበስ ይፈልጋሉ ፡፡ ያ የወደዱትን ተረትም ቢሆን በየቀኑ መስማት ያስደስታቻል፡፡ ትልልቅ ሰዎች ግን እንደዚያ አይደሉም ፤ሁሌም አዲስ እና የመጀመሪያ ነገሮችን ብቻ የሚፈልጉ ሲሆኑ ይህ በሃሪያቸው ህይወትን ቶሎ እንዲሰለቿት ያደርጋቸዋል፡፡
10- ይቀበላሉ፡- እነርሱ በሰዎች መሃለል ስላለው ልዩነት የሚያውቁት ነገር የለም፡፡ የተማረ እና ያልተማረ ደሃ እና ሃብታም ልዩነት የለውም ህጻናት ከሁሉም ጋር እኩል ሊጫወቱም ሆነ ሁሉማ ላይ እኩል ሊጮሁ ይችላሉ፡፡ ለዛም ነው የህጻ ናት ስድብ "ልጅነት " የሚል በጎ ስያሜ የኖረው፡፡
(መረጃዉን ለወዳጆቾ ፎርዋርድ ማድረጎን አይርሱ)
ምንጭ፡-huffpost
1- ውስጣቸውን የተሸለ ያዳምጣሉ፡- ሀፃናት ስለ ውሳኔያቸው ትክከለኝነት ሲጨነቁ የሚያባክኑት ጊዜ የላቸውም ፡፡
2- አሁንን ይኖራሉ፡- እነርሱ ስለትናነት እያስታወሱ በትዝታ ውስጥ የሚማስኑ ፍጡች ካመሆናቸው በላይ ስለወደፊትም በምንም መልኩ አያስቡም፡፡
3- ያምናሉ፡- ህፃናት ማንኛው የተነገራቸውን ነገር የሚያምኑ ሲሆኑ በነሱ አዕምሮ ውስጥ ላይሆን ይችላል የሚል የጥረውጣሬ መንፈስ አይከሰትም፡፡ ምንም እንኳ ትናነት የተነገራቸው ነገር ዛሬ ላይ ባይከሰትም እንኳ እነርሱ ከማመን ሰንፈው አያውቁም፡፡
4- ሰራተኞች ናቸው፡- ህፃናት ሁሌም በስራ ላይ ናቸው ይቆርጣሉ፣ ይቀባሉ፣ ይስላሉ፣ ያቦካሉ ፣ያጣብቃሉ ፡፡ ህጻናት ከልባቸው ታትረው ይለፋሉ፡፡
5- ይጨፍራሉ፡- "ማንም ሰው እያያቹ እንዳልሆነ አስባችሁ ጨፍሩ " የሚለውን ንግግር ያውቁታል? አዎ ህፃናት እንደዚያ ናቸው፡፡ ማንም አጠገባቸው ቢኖር እነርሱ በራሳቸው መንገድ የራሳቸውን የነፃነት ጭፈራ በሙሉ ደስታ ይጨፍራሉ፡፡
6- ይዘፍናሉ፡- ህፃናት በየትኛውም ሰዓት ይዘፍናሉ፡፡ እየታጠቡ ፣ እየተራመዱ ፣ እየተኙም በእንቅልፍ ልብ ሳይቀር ህፃናት ከመዝፈን ወደ ኋላ አይሉም፡፡
7- ማለት የሚፈልጉትን ሁሉ ይላሉ፡- ህፃናት አዕምሯቸው ውስጥ ተከስቶ የማይተነፍሱት ነገር የለም ምናልባት ረስተውት ካልሆነ፡፡ በልባቸው ውስጥ አስቀምጠው የሚታመሙበት ጉዳይ የለም፡፡ ምናልባት አዋቂዎች እንዲህ የሚያደርጉት ለፋሲካ ዋዜማ ከጠጡ ብቻ ነው፡፡
8- ጉጉ ናቸው፡- ህፃናት በጣም ይጓጓሉ፡፡ ሆኖም ሰዓትን የመለየት ችግር ስላለባቸው ወደፊት ምን ያህል እንደሚርቅ አዕምሯቸው መቀመር አይችልም፤ ስለዚህ ልደታቸው እንደቀረበ ከሳምንት እና ከወር በፊት መናገር ለወላጆች እራስ ላይ ጦርነት እንደ ማወጅ ነው፡፡
9- አዲስ ይሁን አይሁን ግድ አይሰጣቸውም፡- ህፃናት ይመቻቸው እንጂ ፊልሙን በየቀኑ አይተውት ይሁን አይሁን አያስጨንቃቸውም፡፡ ይውደዱት እንጂ ያንን ቀሚስ በየቀኑ መልበስ ይፈልጋሉ ፡፡ ያ የወደዱትን ተረትም ቢሆን በየቀኑ መስማት ያስደስታቻል፡፡ ትልልቅ ሰዎች ግን እንደዚያ አይደሉም ፤ሁሌም አዲስ እና የመጀመሪያ ነገሮችን ብቻ የሚፈልጉ ሲሆኑ ይህ በሃሪያቸው ህይወትን ቶሎ እንዲሰለቿት ያደርጋቸዋል፡፡
10- ይቀበላሉ፡- እነርሱ በሰዎች መሃለል ስላለው ልዩነት የሚያውቁት ነገር የለም፡፡ የተማረ እና ያልተማረ ደሃ እና ሃብታም ልዩነት የለውም ህጻናት ከሁሉም ጋር እኩል ሊጫወቱም ሆነ ሁሉማ ላይ እኩል ሊጮሁ ይችላሉ፡፡ ለዛም ነው የህጻ ናት ስድብ "ልጅነት " የሚል በጎ ስያሜ የኖረው፡፡
(መረጃዉን ለወዳጆቾ ፎርዋርድ ማድረጎን አይርሱ)
ምንጭ፡-huffpost
ንዴቶን መቆጣጠር ይፈልጋሉ?
ንዴት ማለት የስሜት መረበሽ ተቀጣጣይ ውጤት ነው፡፡ በንዴት ላይ የተለያዩ ጥናቶችን በማድረግ የሚታወቀው ሳይኮሎጂስቱ ዶ/ር ቻርለስ ሰፒልበርገር እንዳለው ከሆነ እንደሌሎቹ ስሜቶች ሁሉ ንዴትም በተናዳጁ ላይ የስነልቦና እና የአካል ለውጥን ያስከትላል፡፡
አንድ ሰው ሲናደድ የልብ ምቱ፣ የደም ግፊቱ እና የኃይሉን መጠን የሚቆጣጠሩት የሆርሞኖቹ መጠን ከፍ ይላል፡፡
ንዴት ውስጣዊም ሆኑ ውጫዊ በሆኑ ምክኒያቶች ሊከሰት ይችላል፡፡ ይህም አንድ ሰው በሁለተኛ ሰው ፣ በትራፊክ መዘጋጋት አሊያም በቁስ ሊበሳጭ የሚችል ሲሆን አንዳንዴ ደግሞ ውስጣዊ በሆኑ ስሜቶቹ፣ ባለፉት ታሪኮቹ እና በትውስታዎቹ ሊበሳጭ ይችላል፡፡
ንዴት ተፈጥሯዊ እና ሰዋዊ የሆነ ስሜት በመሆኑ መከሰቱ ክፋት የለውም ፤ ይሁንና ነገሩን ከፋ የሚያደርገው የሚገለጥበት መልክ
ነው፡፡
ሰዎች ንዴታቸው በተለያየ መንገድ ይጋፈጣሉ እነዚህም በማፈን፣ በመተንፈስ አልያም ደግሞ እራስን በማረጋጋት ሊሆን ይችላል፡፡
ንዴትን መተንፈስ እና መግለጥ መጥፎ አይደለም እደውም ከብዙ ነገር አንጻር ተመራጭ ሊሆን ይችላል ጉዳዩ ግን የምንገልጥበት ስነምግባር ምን መምሰል አለበት የሚለው ነው፡፡
ሳይኮሎጂስቱ ንዴትን ማፈን ብዙ ግዜ ጥሩ ተግባቦት እና መልካም ስነምግባር ያላቸው ሰዎች በሃሪ ነው ያሉ ሲሆን፤ ይሁንና ሁለተኛውን ሰው ላለመጉዳት እና ላለማስቀየም ተብሎ የሚታፈን ንዴት እንደተዋጠ ቦንብ በመሆን መልሶ እራስን በመጉዳት እነደ ስኳር. ደም ግፊት እና ድብርት የመሳሰሉ በሽታዎች ያጋልጣል ብለዋል፡፡
ስለዚህ በትክክለኛ መንገድ የሚገለጥ ንዴት ሁሌም ለሁለቱም ወገኖች መልካም ነው ይላሉ
ንዴትን መቆጣጠር (anger management)
ንዴትን መቆጣጠር አለመቻል የሚገለጠው በምን ያህል ጊዜ እንደሚናደዱ በመለካት እና የተፈጠረውን ንዴት መቆጣጠር ባለመቻልዎ ነው፡፡
ተናዳጅ ሰው የንዴቱን መጠን እና ሁኔታ መቆጣጠር ከቻለ እራሱንም ሰዎችን ከመጉዳት ይታደጋል፡፡ንዴትን ለመቆጣጠር የተለያዩ መንገዶች ያሉ ሲሆን ከዛም ውስጥ ፡-
1- በተደጋጋሚ የሚያናዶትን ነገር ምንነት በማወቅ
ንዴት ውስጥ ባልሆኑበት ወቅት የሚናደዱበትን ሁኔታ እና ጉዳይ በደንብ ማጤን ከቻሉ እና ለመገንዘብ ከሞከሩ እነዛን ሁኔታዎች በመራቅ እና በተቻለ አቅም ርቀትን በመጠበቅ የሚናደዱበትን የጊዜ ፍጥነት ማራዘም የሚችሉ ሲሆን ቶሎ ተናዳጅ እንዳይሆኑ መሆንም ይችላሉ፡፡
2- የንዴትን የመጀመሪያ ደረጃ መለየት
ሁሌም ቢሆን ከማንፈልገው ነገር ሸሽተን መኖር አንችልም፡፡ ስለዚህ ስሜታችንን የሚያስቆጡ ነገሮች ሳናስባቸው ይከሰታሉ፤ በዚህ ጊዜ ንዴት ሲጀምረን ልብ ማለት ከቻልን መቆጣጠሩ ቀላል ይሆንልናል፡፡
ንዴት ተቀጣጠይ ስሜት በመሆኑ ከትንሽ ወደ ትልቅ እያደገ ነው የሚመጣው፡፡ በመሆኑም ልብ በማለት እና እራስን በማረጋጋት እንዲሁም በተለያዩ ነገሮች እራስን በመጥመድ ከአስከፊ ንዴት እራስን ማዳን ይቻላል፡፡
3- እራስን የማረጋጋት ቴክኒኮችን መጠቀም
ሁሉም ሰው ለራሱ የሚሆነውን መንገድ በመምረጥ እራሱን ማረጋጋት ይችላል፡፡ ምናልባትም አንድን ነገር ደጋግሞ በውስጥ በማለት፣ በረጅሙ በመተንፈስም ሆነ የተለያዩ የአካል እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ከሚከሰትብን የንዴት ማዕበል እራሳችንን ልንታደግ እንችላለን፡፡
የሰው ልጅ ከስሜቱ በላይ ነው፡፡ በመሆኑም ሊቆጣጠረው እና ሊያሸንፈው የማይችልው የስሜት ዓይነት የለም፡፡ሼር
ምንጭ ፡- American Psychological Association
ንዴት ማለት የስሜት መረበሽ ተቀጣጣይ ውጤት ነው፡፡ በንዴት ላይ የተለያዩ ጥናቶችን በማድረግ የሚታወቀው ሳይኮሎጂስቱ ዶ/ር ቻርለስ ሰፒልበርገር እንዳለው ከሆነ እንደሌሎቹ ስሜቶች ሁሉ ንዴትም በተናዳጁ ላይ የስነልቦና እና የአካል ለውጥን ያስከትላል፡፡
አንድ ሰው ሲናደድ የልብ ምቱ፣ የደም ግፊቱ እና የኃይሉን መጠን የሚቆጣጠሩት የሆርሞኖቹ መጠን ከፍ ይላል፡፡
ንዴት ውስጣዊም ሆኑ ውጫዊ በሆኑ ምክኒያቶች ሊከሰት ይችላል፡፡ ይህም አንድ ሰው በሁለተኛ ሰው ፣ በትራፊክ መዘጋጋት አሊያም በቁስ ሊበሳጭ የሚችል ሲሆን አንዳንዴ ደግሞ ውስጣዊ በሆኑ ስሜቶቹ፣ ባለፉት ታሪኮቹ እና በትውስታዎቹ ሊበሳጭ ይችላል፡፡
ንዴት ተፈጥሯዊ እና ሰዋዊ የሆነ ስሜት በመሆኑ መከሰቱ ክፋት የለውም ፤ ይሁንና ነገሩን ከፋ የሚያደርገው የሚገለጥበት መልክ
ነው፡፡
ሰዎች ንዴታቸው በተለያየ መንገድ ይጋፈጣሉ እነዚህም በማፈን፣ በመተንፈስ አልያም ደግሞ እራስን በማረጋጋት ሊሆን ይችላል፡፡
ንዴትን መተንፈስ እና መግለጥ መጥፎ አይደለም እደውም ከብዙ ነገር አንጻር ተመራጭ ሊሆን ይችላል ጉዳዩ ግን የምንገልጥበት ስነምግባር ምን መምሰል አለበት የሚለው ነው፡፡
ሳይኮሎጂስቱ ንዴትን ማፈን ብዙ ግዜ ጥሩ ተግባቦት እና መልካም ስነምግባር ያላቸው ሰዎች በሃሪ ነው ያሉ ሲሆን፤ ይሁንና ሁለተኛውን ሰው ላለመጉዳት እና ላለማስቀየም ተብሎ የሚታፈን ንዴት እንደተዋጠ ቦንብ በመሆን መልሶ እራስን በመጉዳት እነደ ስኳር. ደም ግፊት እና ድብርት የመሳሰሉ በሽታዎች ያጋልጣል ብለዋል፡፡
ስለዚህ በትክክለኛ መንገድ የሚገለጥ ንዴት ሁሌም ለሁለቱም ወገኖች መልካም ነው ይላሉ
ንዴትን መቆጣጠር (anger management)
ንዴትን መቆጣጠር አለመቻል የሚገለጠው በምን ያህል ጊዜ እንደሚናደዱ በመለካት እና የተፈጠረውን ንዴት መቆጣጠር ባለመቻልዎ ነው፡፡
ተናዳጅ ሰው የንዴቱን መጠን እና ሁኔታ መቆጣጠር ከቻለ እራሱንም ሰዎችን ከመጉዳት ይታደጋል፡፡ንዴትን ለመቆጣጠር የተለያዩ መንገዶች ያሉ ሲሆን ከዛም ውስጥ ፡-
1- በተደጋጋሚ የሚያናዶትን ነገር ምንነት በማወቅ
ንዴት ውስጥ ባልሆኑበት ወቅት የሚናደዱበትን ሁኔታ እና ጉዳይ በደንብ ማጤን ከቻሉ እና ለመገንዘብ ከሞከሩ እነዛን ሁኔታዎች በመራቅ እና በተቻለ አቅም ርቀትን በመጠበቅ የሚናደዱበትን የጊዜ ፍጥነት ማራዘም የሚችሉ ሲሆን ቶሎ ተናዳጅ እንዳይሆኑ መሆንም ይችላሉ፡፡
2- የንዴትን የመጀመሪያ ደረጃ መለየት
ሁሌም ቢሆን ከማንፈልገው ነገር ሸሽተን መኖር አንችልም፡፡ ስለዚህ ስሜታችንን የሚያስቆጡ ነገሮች ሳናስባቸው ይከሰታሉ፤ በዚህ ጊዜ ንዴት ሲጀምረን ልብ ማለት ከቻልን መቆጣጠሩ ቀላል ይሆንልናል፡፡
ንዴት ተቀጣጠይ ስሜት በመሆኑ ከትንሽ ወደ ትልቅ እያደገ ነው የሚመጣው፡፡ በመሆኑም ልብ በማለት እና እራስን በማረጋጋት እንዲሁም በተለያዩ ነገሮች እራስን በመጥመድ ከአስከፊ ንዴት እራስን ማዳን ይቻላል፡፡
3- እራስን የማረጋጋት ቴክኒኮችን መጠቀም
ሁሉም ሰው ለራሱ የሚሆነውን መንገድ በመምረጥ እራሱን ማረጋጋት ይችላል፡፡ ምናልባትም አንድን ነገር ደጋግሞ በውስጥ በማለት፣ በረጅሙ በመተንፈስም ሆነ የተለያዩ የአካል እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ከሚከሰትብን የንዴት ማዕበል እራሳችንን ልንታደግ እንችላለን፡፡
የሰው ልጅ ከስሜቱ በላይ ነው፡፡ በመሆኑም ሊቆጣጠረው እና ሊያሸንፈው የማይችልው የስሜት ዓይነት የለም፡፡ሼር
ምንጭ ፡- American Psychological Association
እርጅናን ለመከላከል የሚረዱ ምግቦች
እርጅና የሚቀር አይደለም፤ ማንም ሰው እድሜው ከፈቀደለት እና በህይወት ከቆየ ይህንን እድል ማየቱ የማይቀር ነው፡፡ ይሁንና እርጅናን መከላከል ሲባል በእርጅና ሳቢያ የሚመጣ የቆዳ መሸብሸብ ፣ የድካም ስሜት እና የመጫጫን ስሜቶች ሳይኖሩ መቆየት መቻል ማለት ነው፡፡
1- በለስ
በለስ የሚጣል ክፍል የሌለው ድንቅ ተክል ነው፡፡ ከቆዳው አንስቶ እስከ ፍሬው ድረስ ለአዕምሮ ጤና እና ለተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ጥቅም የሚሰጥ መሆኑ የተረጋገጠ ነው፡፡ እርጅናን በተመለከተም በበለስ ውስጥ የሚገኘው ፋይሰን ተሰኘው ኢንዛይም በእድሜ ሳቢያ ሊከሰቱ የሚችሉ ብግነቶችን በመከላከል ትልቅ አስተዋፅዖ ያደርጋል፡፡
2- እርድ
እርድ ከቁንጅና እስከ ህክምና ድረስ መጠነ ሰፊ ጥቅም ያለው ተክል ነው፡፡ በ እርድ ውስጥ የሚገኘው ቱምርን እርጅናን የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ በመሆኑ በምንመገበው ምግብ ውስጥ እርድን መቀላቀል ባህል ማሳደግ ይኖርብናል፡፡
3- አቮካዶ
1 አቮካዶ በቀን መብላት የቆዳ ሃኪም ጋር ድርሽ እንዳይሉ ያደርጋል የሚለው አባባል በጣም ታዋቂ እና እውን ነው፡፡ ለቆዳ ፍካት እና ውበት ከመጥቀሙ ባሻገር እርጅናን መከላከል አቅሙም የሚናቅ አይደለም፡፡
ሼር
ምንጭ፡- ANCIENT MEDICINE TODAY
እርጅና የሚቀር አይደለም፤ ማንም ሰው እድሜው ከፈቀደለት እና በህይወት ከቆየ ይህንን እድል ማየቱ የማይቀር ነው፡፡ ይሁንና እርጅናን መከላከል ሲባል በእርጅና ሳቢያ የሚመጣ የቆዳ መሸብሸብ ፣ የድካም ስሜት እና የመጫጫን ስሜቶች ሳይኖሩ መቆየት መቻል ማለት ነው፡፡
1- በለስ
በለስ የሚጣል ክፍል የሌለው ድንቅ ተክል ነው፡፡ ከቆዳው አንስቶ እስከ ፍሬው ድረስ ለአዕምሮ ጤና እና ለተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ጥቅም የሚሰጥ መሆኑ የተረጋገጠ ነው፡፡ እርጅናን በተመለከተም በበለስ ውስጥ የሚገኘው ፋይሰን ተሰኘው ኢንዛይም በእድሜ ሳቢያ ሊከሰቱ የሚችሉ ብግነቶችን በመከላከል ትልቅ አስተዋፅዖ ያደርጋል፡፡
2- እርድ
እርድ ከቁንጅና እስከ ህክምና ድረስ መጠነ ሰፊ ጥቅም ያለው ተክል ነው፡፡ በ እርድ ውስጥ የሚገኘው ቱምርን እርጅናን የመከላከል አቅሙ ከፍተኛ በመሆኑ በምንመገበው ምግብ ውስጥ እርድን መቀላቀል ባህል ማሳደግ ይኖርብናል፡፡
3- አቮካዶ
1 አቮካዶ በቀን መብላት የቆዳ ሃኪም ጋር ድርሽ እንዳይሉ ያደርጋል የሚለው አባባል በጣም ታዋቂ እና እውን ነው፡፡ ለቆዳ ፍካት እና ውበት ከመጥቀሙ ባሻገር እርጅናን መከላከል አቅሙም የሚናቅ አይደለም፡፡
ሼር
ምንጭ፡- ANCIENT MEDICINE TODAY
ሃሳብን መቀየር ለምን ይከብዳል?
የሚቀየር እና የማይቀየር ሃሳብ ስንል እምነት ማለታችን ነው፡፡ የሰው ልጅ የሆነ ኢንፎርሜሽንን በአዕሮው ውስጥ ሲያከማች እና ያከማቸውን ነገር በሆነ መንገድ ቅርፅ አስይዞ በቀን የቀን ተቀን ህወቱን በእርሱ ተፅዕኖ ስር እንዲውል ሲፈቅድ አመነ እንላለን፡፡
አመለካከት፣ ሃሳብ እና እምነት የተሰኙት ፅንሰ ሓሳቦች ለዘመናት ብዙ ፈላስፎችን ያነጋገሩ ሲሆኑ የሳይንቲስቶችና የስነ-አዕምሮ ባለሞያዎችም ትኩረት ከሳቡ ሰነባብተዋል፡፡
ሳይካትሪስቱ ራልፍ ሌዊስ እንዳስረዳው ከሆነ ሃሳቦች ልክ ሆኑም አልሆኑም አንዴ አእምሮ ውስጥ ኑረውና ወደ እምነትነት ከተቀየሩ በቀላሉ እነሱን መቀይር አይቻልም፡፡
እምነት ማለት አዕምሯችን የተወሳሰበውን ዓለም ለመረዳት የሚያሰምረው የራሱ መንገድ ነው፡፡ ነገሮች ከነገሮች ጋር በምን መንገድ መተሳሰር እንደሚኖርባቸው የሚያትትበት እና ነገሮች በምን መንገድ መተግበር እንደሚኖርባቸው ቀድሞ የራሱን ግምት የሚያስቀምጥበት ሂደትም ጭምር ነው፡፡
እምነቶች የመማር አቅማችንን የመወሰን ስልጣን ያላቸው ከመሆኑም በተጨማሪ የመኖር ምክኒያታችን እስከመሆንም ጭምር ይደርሳሉ፡፡
አዕምሮ ኃይል አሟጣጭ አካል ነው፡፡ የሰውነታችንንን አብዛኛውን ኃይል ከመውሰዱም በተጨማሪ የወሰደውን ኃይል በቁጠባ እና በአግባቡ መጠቀም ይኖርበታል፡፡ ይህንን ለማድረግ ደግሞ የተለያዩ ዘዴዎችን የሚጠቀም ሲሆን ከዛም ውስጥ አንደኛው መንገድ የሆነ ጊዜ ላይ በሆነ መንገድ ተሰርተው የተቀመጡ ኢንፎርሜሽኖችን አንዴ ‹ሴቭ› አድርጎ በማስቀመጥ በሚፈልገው ሰዓት እሱን እንደ ፋይል ‹ክሊክ› በማድረግ እየመነዘሩ መጠቀም ነው፡፡
ይህ ለአዕምሮ ስራ አቅላይ ከመሆኑም በተጨማሪ ኃይል ቆጣቢ አሰራርም ነው፡፡ ምክኒያቱም አንድን ነገር ማሰብ ማደራጀት መተንተን እና መደምደሚያ ላይ መድረስ ከባድ ስራ ነው፤ በመሆኑም ያንን ሁላ መንገድ ሳይጓዝ አዕምሮ በቀላሉ ነገሮችን እያጠጋጋ እና እያመሳሰለ የተሳሳተ መደምደሚያ ላይ በመድረስ አቅሙን መቆጠብን እንደ አማራጭ ያየዋል፡፡
ስለዚህ ይህ የአዕምሮ ስንፍና እኛን በአንድ ሃሳብ ላይ ፀንተን እንድንቆይ ከማድረጉም በላይ ለየትኛውም አዲስ እውቀትም ሆነ አዲስ አመለካከት ክፍት እንዳንሆን ያደርገናል፡፡
መረጃን መተንተን፣ ማመሳከር ፣ ማዋቀር እና መደምደም ትልቅ ስራ ነው ስለሆነም ከአንዳንድ ግልሰቦች ውጭ ይሄንን ሂደት ለመስበረር የሚደፍር የለም፡፡
አዕምሮን በማላመድ እና ይሄንን የአስተሳሰብ ‹ትሬንድ› በመስበር የተሻለ አዕምሮን መፍጠር እንችላለን፡፡ ሼር
ምንጭ ፡- Psychology Today
የሚቀየር እና የማይቀየር ሃሳብ ስንል እምነት ማለታችን ነው፡፡ የሰው ልጅ የሆነ ኢንፎርሜሽንን በአዕሮው ውስጥ ሲያከማች እና ያከማቸውን ነገር በሆነ መንገድ ቅርፅ አስይዞ በቀን የቀን ተቀን ህወቱን በእርሱ ተፅዕኖ ስር እንዲውል ሲፈቅድ አመነ እንላለን፡፡
አመለካከት፣ ሃሳብ እና እምነት የተሰኙት ፅንሰ ሓሳቦች ለዘመናት ብዙ ፈላስፎችን ያነጋገሩ ሲሆኑ የሳይንቲስቶችና የስነ-አዕምሮ ባለሞያዎችም ትኩረት ከሳቡ ሰነባብተዋል፡፡
ሳይካትሪስቱ ራልፍ ሌዊስ እንዳስረዳው ከሆነ ሃሳቦች ልክ ሆኑም አልሆኑም አንዴ አእምሮ ውስጥ ኑረውና ወደ እምነትነት ከተቀየሩ በቀላሉ እነሱን መቀይር አይቻልም፡፡
እምነት ማለት አዕምሯችን የተወሳሰበውን ዓለም ለመረዳት የሚያሰምረው የራሱ መንገድ ነው፡፡ ነገሮች ከነገሮች ጋር በምን መንገድ መተሳሰር እንደሚኖርባቸው የሚያትትበት እና ነገሮች በምን መንገድ መተግበር እንደሚኖርባቸው ቀድሞ የራሱን ግምት የሚያስቀምጥበት ሂደትም ጭምር ነው፡፡
እምነቶች የመማር አቅማችንን የመወሰን ስልጣን ያላቸው ከመሆኑም በተጨማሪ የመኖር ምክኒያታችን እስከመሆንም ጭምር ይደርሳሉ፡፡
አዕምሮ ኃይል አሟጣጭ አካል ነው፡፡ የሰውነታችንንን አብዛኛውን ኃይል ከመውሰዱም በተጨማሪ የወሰደውን ኃይል በቁጠባ እና በአግባቡ መጠቀም ይኖርበታል፡፡ ይህንን ለማድረግ ደግሞ የተለያዩ ዘዴዎችን የሚጠቀም ሲሆን ከዛም ውስጥ አንደኛው መንገድ የሆነ ጊዜ ላይ በሆነ መንገድ ተሰርተው የተቀመጡ ኢንፎርሜሽኖችን አንዴ ‹ሴቭ› አድርጎ በማስቀመጥ በሚፈልገው ሰዓት እሱን እንደ ፋይል ‹ክሊክ› በማድረግ እየመነዘሩ መጠቀም ነው፡፡
ይህ ለአዕምሮ ስራ አቅላይ ከመሆኑም በተጨማሪ ኃይል ቆጣቢ አሰራርም ነው፡፡ ምክኒያቱም አንድን ነገር ማሰብ ማደራጀት መተንተን እና መደምደሚያ ላይ መድረስ ከባድ ስራ ነው፤ በመሆኑም ያንን ሁላ መንገድ ሳይጓዝ አዕምሮ በቀላሉ ነገሮችን እያጠጋጋ እና እያመሳሰለ የተሳሳተ መደምደሚያ ላይ በመድረስ አቅሙን መቆጠብን እንደ አማራጭ ያየዋል፡፡
ስለዚህ ይህ የአዕምሮ ስንፍና እኛን በአንድ ሃሳብ ላይ ፀንተን እንድንቆይ ከማድረጉም በላይ ለየትኛውም አዲስ እውቀትም ሆነ አዲስ አመለካከት ክፍት እንዳንሆን ያደርገናል፡፡
መረጃን መተንተን፣ ማመሳከር ፣ ማዋቀር እና መደምደም ትልቅ ስራ ነው ስለሆነም ከአንዳንድ ግልሰቦች ውጭ ይሄንን ሂደት ለመስበረር የሚደፍር የለም፡፡
አዕምሮን በማላመድ እና ይሄንን የአስተሳሰብ ‹ትሬንድ› በመስበር የተሻለ አዕምሮን መፍጠር እንችላለን፡፡ ሼር
ምንጭ ፡- Psychology Today
የወንዶች ስነ-ተዋልዶ ጤናን ቀያሪ ሁናቴዎች
የወንድ ዘር ፍሬ ከሴት እንቁላል ዘንድ ደርሶ ዘር ማፍራት እንዲችል ጤናማና ጠንካራ መሆን አለበት፡፡ በተለይም የዘር ፍሬው በቂ የብዛት መጠን እና ቅርፅ፣ ትክክለኛ የጉዞ አቅጣጫ እንዲሁም ወደ እንቁላሉ ሊያደርሰው የሚችል በቂ ፈሳሽ እንዲኖረው ይገባል፡፡ ልጅ መውለድ ያለመቻልን ሊያመጡ ይችላሉ ከሚባሉት ምክንያቶች ውስጥ 80 በመቶዎቹ በህክምና ባለሙያዎች ሲታወቁ ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉ በወንዶች አማካኝነት የሚከሰት ነው፡፡ የወንዶችን ስነ-ተዋልዶ ቁመና በመወሰን ረገድ ትልቅ ድርሻ ያላቸው እንደሚከተለው ተቀምጠዋል፡-
፩. ክብደትን መቀነስ፡- በተለያዩ ጥናቶች መሰረት የወንዱ ክብደት ከፍተኛ የሆነባቸው ጥንዶች ለመውለድ በመቸገር ረገድ ከፍ ያለ እድል አላቸው፡፡ ይህ ከፍተኛ ክብደት የወንዱን የዘር ፍሬ ብዛትና ጥራት ከመቀነስና የዘረ-መሉ ላይ ጉዳት ከማድረሱም በተጨማሪ የመንሳፈፍ ብቃቱንም ይጎዱታል፡፡
፪. ተጓዳኝ የጤና ችግሮችን መከላከል፡- እንደ ስኳርና ደም ግፊት ያሉ ዘላቂ በሽታዎችን መከላከል የማስረገዝ ብቃትን የተሸለ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ ሆኖም እነዚህን በሽታዎች ጨምሮ ድብርትን፣ መረበሽን፣ ራሰ በረሃነትን የሚያክሙ እና ህመምን አስታጋሽ መድሃኒትና ህክምናዎችን መውሰድ የመውለድ ብቃት ላይ ችግርን ሊያመጡ ይችላሉ፡፡
፫. ጤናማ ምግቦችን መመገብ፡- ሳይንስ ጤናማ ምግቦችን መመገብ ከስነ-ተዋልዶ ጤና ጋር ያለው ግንኙነት በግልፅ ባያስቀምጥም የወን የዘር ፍሬን በጥራት ለማምረት የሚችሉ እንደ ሃባብ፣ ብርቱካን፣ ምስር ቲማቲም እና እንጆሪን ያሉ የፍራፍሬ፣ ጥራጥሬና አትክልት ምግቦችን መመገብ ግን ይመከራል፡፡
፬. የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፡- የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በየዕለቱ መከወን ዘላቂ አካላዊና ውስጣዊ ጤናን ይሠጣል፡፡ ምንም እንኳን እነዚህን ጥቅሞች መስጠት ቢችሉም ማራቶንን የመሰሉ ከባባድ እንቅስቃሴዎች ግን በስነ ተዋልዶ ላይ ተፅዕንዖ ሊኖራቸው እንደሚችል ጥናቶች ያሳያሉ፡፡
፭. ቫይታሚን ሰጪ መድሃኒቶች (Multivitamin)፡- ቫይታሚንንና ሌሎች ንጥረ ነገሮችን ለሰውነት እንዲሰጡ ታስበው የሚዋጡት እነዚህ መድሃኒቶች በጎም ሆነ አሉታዊ ተፅዕኖን ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ የቫይታሚን ሲ እና ኢ እንክብሎችም የዘር ፍሬን ጥራትና እንቅስቃሴን በማሻሻል እንደሚረዱ ተቀምጧል፡፡
፮. ዕድሜ፡- ምንም እንኳን ከሴቶች አንፃር ዘግይቶ ቢገጥማቸውም የወንዶች ዕድሜ መጨመር በስነ-ተዋልዶ ጤና ላይ ተፅዕኖን ያመጣል፡፡ ይህም በተለይ የዘር ፍሬ ጤናማነትና የዘረ-መል መጎዳት እንዲሁም በመጠንና ጥራቱ ላይ ማነስ መኖሩን ነው፡፡
፯. ተጓዳኝ ሱሶች፡- ጥናቶች እንደሚያሳዩን ሲጋራን ማጨስ የወንድ ዘር ፍሬ እንቅስቃሴ እና ብዛትን ከመቀነስም ባሻገር የቅርፅ ለውጥን ያስከትላል፡፡ ከፍተኛ የአልኮል አጠቃቀምም የዘር ፍሬውን ጤና ይጎዳል፡፡ ከነዚህ በተጨማሪ ማሪዋናና በሰውነት ግንባታ ተወዳዳሪዎች ጥቅም ላይ የሚውለው ስቴሪኦድን መሰል ቁሶችም ተመሳሳይ አሉታዊ ጉዳቶች አሏቸው፡፡
፰. ሙቀት፡- በሙቅ ገንዳ፣ ሳውናና ስቲሞች ውስጥ ለበዛ ሰሠዓታት መቆየትና ደጋግሞ መጠቀም የመራቢያ አካላትን ሙቀት በመጨመር ለዘር ፍሬ መመንመንና ጥራት መውረድ ሊዳርግ ይችላል፡፡ ሆኖም ግን ይህን መሰል ጉዳቶች ዘላቂ አይደሉም፤ ከነዚህ ተግባራት ስንርቅ መደ ጤናማ አኳኋን እንመለሳለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን በሰውነት አካል ላይ አኑሮ መጠቀም ተመሳሳይ ጉዳቶችን ሊያስከትል ይችላል፡፡
፱. የህክምና እርዳታ፡- የሴቷ እድሜ ከሰላሳ አምስት ዓመት በታች የሆነባቸው ጥንዶች የህክምና እርዳታን ከመሻታቸው አስቀድሞ በመካከላቸው ያለ ወሊድ መከላከያ ለአንድ ዓመት ያህል ተከታታይ ሩካቤ ስጋን እየፈፀሙ ልጅ ለመፀነስ መሞከር እንዳለባቸው ይመከራል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ሙከራ የሴቷ ዕድሜ ከሰላሳ አምስት በላይ ከሆነ ስድስት ወር እንዳለፈ ወደ ህክምና ማቅናት ይኖርባቸዋል፡፡
ምንጭ፡- Live Science
የወንድ ዘር ፍሬ ከሴት እንቁላል ዘንድ ደርሶ ዘር ማፍራት እንዲችል ጤናማና ጠንካራ መሆን አለበት፡፡ በተለይም የዘር ፍሬው በቂ የብዛት መጠን እና ቅርፅ፣ ትክክለኛ የጉዞ አቅጣጫ እንዲሁም ወደ እንቁላሉ ሊያደርሰው የሚችል በቂ ፈሳሽ እንዲኖረው ይገባል፡፡ ልጅ መውለድ ያለመቻልን ሊያመጡ ይችላሉ ከሚባሉት ምክንያቶች ውስጥ 80 በመቶዎቹ በህክምና ባለሙያዎች ሲታወቁ ከዚህ ውስጥ ግማሽ ያህሉ በወንዶች አማካኝነት የሚከሰት ነው፡፡ የወንዶችን ስነ-ተዋልዶ ቁመና በመወሰን ረገድ ትልቅ ድርሻ ያላቸው እንደሚከተለው ተቀምጠዋል፡-
፩. ክብደትን መቀነስ፡- በተለያዩ ጥናቶች መሰረት የወንዱ ክብደት ከፍተኛ የሆነባቸው ጥንዶች ለመውለድ በመቸገር ረገድ ከፍ ያለ እድል አላቸው፡፡ ይህ ከፍተኛ ክብደት የወንዱን የዘር ፍሬ ብዛትና ጥራት ከመቀነስና የዘረ-መሉ ላይ ጉዳት ከማድረሱም በተጨማሪ የመንሳፈፍ ብቃቱንም ይጎዱታል፡፡
፪. ተጓዳኝ የጤና ችግሮችን መከላከል፡- እንደ ስኳርና ደም ግፊት ያሉ ዘላቂ በሽታዎችን መከላከል የማስረገዝ ብቃትን የተሸለ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ ሆኖም እነዚህን በሽታዎች ጨምሮ ድብርትን፣ መረበሽን፣ ራሰ በረሃነትን የሚያክሙ እና ህመምን አስታጋሽ መድሃኒትና ህክምናዎችን መውሰድ የመውለድ ብቃት ላይ ችግርን ሊያመጡ ይችላሉ፡፡
፫. ጤናማ ምግቦችን መመገብ፡- ሳይንስ ጤናማ ምግቦችን መመገብ ከስነ-ተዋልዶ ጤና ጋር ያለው ግንኙነት በግልፅ ባያስቀምጥም የወን የዘር ፍሬን በጥራት ለማምረት የሚችሉ እንደ ሃባብ፣ ብርቱካን፣ ምስር ቲማቲም እና እንጆሪን ያሉ የፍራፍሬ፣ ጥራጥሬና አትክልት ምግቦችን መመገብ ግን ይመከራል፡፡
፬. የአካል ብቃት እንቅስቃሴ፡- የአካል ብቃት እንቅስቃሴን በየዕለቱ መከወን ዘላቂ አካላዊና ውስጣዊ ጤናን ይሠጣል፡፡ ምንም እንኳን እነዚህን ጥቅሞች መስጠት ቢችሉም ማራቶንን የመሰሉ ከባባድ እንቅስቃሴዎች ግን በስነ ተዋልዶ ላይ ተፅዕንዖ ሊኖራቸው እንደሚችል ጥናቶች ያሳያሉ፡፡
፭. ቫይታሚን ሰጪ መድሃኒቶች (Multivitamin)፡- ቫይታሚንንና ሌሎች ንጥረ ነገሮችን ለሰውነት እንዲሰጡ ታስበው የሚዋጡት እነዚህ መድሃኒቶች በጎም ሆነ አሉታዊ ተፅዕኖን ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ የቫይታሚን ሲ እና ኢ እንክብሎችም የዘር ፍሬን ጥራትና እንቅስቃሴን በማሻሻል እንደሚረዱ ተቀምጧል፡፡
፮. ዕድሜ፡- ምንም እንኳን ከሴቶች አንፃር ዘግይቶ ቢገጥማቸውም የወንዶች ዕድሜ መጨመር በስነ-ተዋልዶ ጤና ላይ ተፅዕኖን ያመጣል፡፡ ይህም በተለይ የዘር ፍሬ ጤናማነትና የዘረ-መል መጎዳት እንዲሁም በመጠንና ጥራቱ ላይ ማነስ መኖሩን ነው፡፡
፯. ተጓዳኝ ሱሶች፡- ጥናቶች እንደሚያሳዩን ሲጋራን ማጨስ የወንድ ዘር ፍሬ እንቅስቃሴ እና ብዛትን ከመቀነስም ባሻገር የቅርፅ ለውጥን ያስከትላል፡፡ ከፍተኛ የአልኮል አጠቃቀምም የዘር ፍሬውን ጤና ይጎዳል፡፡ ከነዚህ በተጨማሪ ማሪዋናና በሰውነት ግንባታ ተወዳዳሪዎች ጥቅም ላይ የሚውለው ስቴሪኦድን መሰል ቁሶችም ተመሳሳይ አሉታዊ ጉዳቶች አሏቸው፡፡
፰. ሙቀት፡- በሙቅ ገንዳ፣ ሳውናና ስቲሞች ውስጥ ለበዛ ሰሠዓታት መቆየትና ደጋግሞ መጠቀም የመራቢያ አካላትን ሙቀት በመጨመር ለዘር ፍሬ መመንመንና ጥራት መውረድ ሊዳርግ ይችላል፡፡ ሆኖም ግን ይህን መሰል ጉዳቶች ዘላቂ አይደሉም፤ ከነዚህ ተግባራት ስንርቅ መደ ጤናማ አኳኋን እንመለሳለን፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን በሰውነት አካል ላይ አኑሮ መጠቀም ተመሳሳይ ጉዳቶችን ሊያስከትል ይችላል፡፡
፱. የህክምና እርዳታ፡- የሴቷ እድሜ ከሰላሳ አምስት ዓመት በታች የሆነባቸው ጥንዶች የህክምና እርዳታን ከመሻታቸው አስቀድሞ በመካከላቸው ያለ ወሊድ መከላከያ ለአንድ ዓመት ያህል ተከታታይ ሩካቤ ስጋን እየፈፀሙ ልጅ ለመፀነስ መሞከር እንዳለባቸው ይመከራል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ሙከራ የሴቷ ዕድሜ ከሰላሳ አምስት በላይ ከሆነ ስድስት ወር እንዳለፈ ወደ ህክምና ማቅናት ይኖርባቸዋል፡፡
ምንጭ፡- Live Science
ከሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል እስከ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት የተደረገ የስኬት ጉዞ!!!
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1908960295878713&id=563821287059294
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1908960295878713&id=563821287059294
Facebook
Science and Technology Information Center-STIC Ethiopia
ከሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል እስከ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት የተደረገ የስኬት ጉዞ፡፡ ኢቢሲ በተቋማችን ያደረገውን ምልከታና የኢኒስቲትዩታችን ዋና ዳይሬክተር ከኢቢሲ ጋር ያደረጉትን ቆይታ እነሆ ተጋበዙልን!!
እንኳን ደስ አለን❗️❗️❗️
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት የስልጣን፣ ተግባርና አደረጃጀት ደንብ በሚኒስትሮች ምክርቤት ጸደቀ።
የሚኒስትሮች ምክርቤት በትላንትናው እለት ህዳር 5/2011 ባካሄደው ስብሰባ መንግስት በቅርቡ ያደረገውን ለውጥ ተከትሎ የፌደራል መንግስት አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባርን ለመወሰን በወጣው አዋጅ መሰረት የተደራጀውን የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ስልጣን፣ ተግባር እና አደረጃጀት ለመወሰን ተዘጋጅቶ በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እንዲወጣና በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃን በማዕከላዊነት ለመምራት በሚኒስትሮች ምክርቤት ደንብ ቁጥር 257/2004 የተቋቋመው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል ከተቋቋመበት ከ2004 ጀምሮ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት እስከሆነበት ጥቅምት 2011 ድረስ ለቴክኖሎጂ፣ ለምርምርና ለማምረቻ ተቋማት ግብአት የሚሆኑ እሴት የታከለባቸውን መረጃዎች በማሰራጨት ሀገራዊ ተልዕኮውን ሲወጣ ቆይቷል።
በአዲሱ አደረጃጀርት መሰረትም ኢኒስቲትዩቱ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ የምርምር መሰረተ ልማቶችን መገንባትን፣ ለኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ግብአት የሚሆኑ መረጃዎችን ማሰባሰብና እሴት አክሎ ማሰራጨት፣ በአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በመንግስት ተለይተው ቅድሚያ በሚሰጣቸው ሴክተሮች ላይ ምርምርና ልማት ስራዎችን መስራትና መሰል የጥናትና ምርምር ስራዎችን መደገፍና ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ ሰፋፊ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ልማት ተልዕኮዎችን አንግቦ ይሰራል።
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት የስልጣን፣ ተግባርና አደረጃጀት ደንብ በሚኒስትሮች ምክርቤት ጸደቀ።
የሚኒስትሮች ምክርቤት በትላንትናው እለት ህዳር 5/2011 ባካሄደው ስብሰባ መንግስት በቅርቡ ያደረገውን ለውጥ ተከትሎ የፌደራል መንግስት አስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባርን ለመወሰን በወጣው አዋጅ መሰረት የተደራጀውን የቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ስልጣን፣ ተግባር እና አደረጃጀት ለመወሰን ተዘጋጅቶ በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በስፋት ከተወያየ በኋላ ደንቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እንዲወጣና በስራ ላይ እንዲውል ወስኗል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃን በማዕከላዊነት ለመምራት በሚኒስትሮች ምክርቤት ደንብ ቁጥር 257/2004 የተቋቋመው የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል ከተቋቋመበት ከ2004 ጀምሮ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት እስከሆነበት ጥቅምት 2011 ድረስ ለቴክኖሎጂ፣ ለምርምርና ለማምረቻ ተቋማት ግብአት የሚሆኑ እሴት የታከለባቸውን መረጃዎች በማሰራጨት ሀገራዊ ተልዕኮውን ሲወጣ ቆይቷል።
በአዲሱ አደረጃጀርት መሰረትም ኢኒስቲትዩቱ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ የምርምር መሰረተ ልማቶችን መገንባትን፣ ለኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ልማት ግብአት የሚሆኑ መረጃዎችን ማሰባሰብና እሴት አክሎ ማሰራጨት፣ በአምራችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በመንግስት ተለይተው ቅድሚያ በሚሰጣቸው ሴክተሮች ላይ ምርምርና ልማት ስራዎችን መስራትና መሰል የጥናትና ምርምር ስራዎችን መደገፍና ተደራሽ ማድረግን ጨምሮ ሰፋፊ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ልማት ተልዕኮዎችን አንግቦ ይሰራል።
ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ መራሽ ማህበረሰብ
የዓለማችን ለውጥ የሰው ልጆችን ለአደጋ እየጋረጠ ይመስላል፡፡ እስከ 2050 ድረስ የዓለም ህዝብ ቁጥር እስከ 9 .6 ቢሊዮን ይደርሳል ተብሎ ተገምቷል፡፡ ስልጣኔ እያመጣው ያለውን ለውጥ እና ቀውስ በስልጣኔ እና በስልጣኔ ብቻ ነው መቋመቋም የሚቻለው፡፡
በዚህ ሰዓት ከባባድ ኢንደስትሪዎች ያስፈልጋሉ ፤ ይህንን ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝብ መመገብም ሆነ ማከም ቀላል የሚባል ስራ አይሆንም፤ በእነዚህ ግዙፍ ኢንደስትሪዎች የሚፈጠሩ ብክለቶችንም ለመከላከል ያላሰለሰ ጥረት ያስፈልጋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከ 1ቢሊዮን በላይ የሚሆን ህዝብ በቂ ምግብ በቂ ትምህርት እና በቂ ህክምና እያገኘ አይደለም፡፡
ንግድም ቢሆን መልኩን ቀይሯል፤ ግብይት አንድ ለአንድ ከመሆን አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሁሉን አካታች እና ውስብስብ ወደ ሆነ መንገድ መጥቷል፡፡ ስለዚህ ስለሁሉም የሚገባው ሁሉም ነው፡፡
አገራት ዓለም መንደር እየሆነች መምጣቷን ተገንዝበው በዛ መንገድ መንቀሳቀስ ከጀመሩ ሰነባብተዋል ፡፡ ባተረፉት ነገር ያጎደሉት ካለ እሱን ለመሙላት ዓለም እያስገደደቻቸው ነው፡፡ በመሆንም በግዙፍ እንደስትሪዎቻቸው ያተረፉትን እንደመቀማመሳቸውም ሁሉ በኢንደስትሪዎቻቸው ላደረሱት ብክለትም ከተጠያቂነት ለመዳን የተሻለን መንገድ ማፈላለግ የግድ ይላቸዋል፡፡
ከትርፉም ሳይቋደሱ የገፈቱ ግን ግንባር ቀደም ተጠቂ የሆኑም አሉ፡፡ ታዳጊ አገራት እንዲህ ካለው ቀውስ ለመላቀቅ እና እየሮጡ ካሉት ተቀዳሚ አገራት ረድፍ ውስጥ ለመሰደር ያላቸው የማያዳግም አማራጭ በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ የበለፀገች አገር ወደ መገንባት ፊትን ማዞር ብቻ ነው፡፡
ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ መራሽ እድገት የስኬት አቋራጭ መንግድ ነው፡፡ ይህንንም ማሳካት የሚቻለው ለሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ንቁ የሆነ ማህበረሰብን መፍጠር እና ማነፅ ሲቻል ብቻ ነው፡፡
….የቴክኖሎጂ እና የኢኖቬሽን ኢኒስቲቲዩት
የዓለማችን ለውጥ የሰው ልጆችን ለአደጋ እየጋረጠ ይመስላል፡፡ እስከ 2050 ድረስ የዓለም ህዝብ ቁጥር እስከ 9 .6 ቢሊዮን ይደርሳል ተብሎ ተገምቷል፡፡ ስልጣኔ እያመጣው ያለውን ለውጥ እና ቀውስ በስልጣኔ እና በስልጣኔ ብቻ ነው መቋመቋም የሚቻለው፡፡
በዚህ ሰዓት ከባባድ ኢንደስትሪዎች ያስፈልጋሉ ፤ ይህንን ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ህዝብ መመገብም ሆነ ማከም ቀላል የሚባል ስራ አይሆንም፤ በእነዚህ ግዙፍ ኢንደስትሪዎች የሚፈጠሩ ብክለቶችንም ለመከላከል ያላሰለሰ ጥረት ያስፈልጋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከ 1ቢሊዮን በላይ የሚሆን ህዝብ በቂ ምግብ በቂ ትምህርት እና በቂ ህክምና እያገኘ አይደለም፡፡
ንግድም ቢሆን መልኩን ቀይሯል፤ ግብይት አንድ ለአንድ ከመሆን አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሁሉን አካታች እና ውስብስብ ወደ ሆነ መንገድ መጥቷል፡፡ ስለዚህ ስለሁሉም የሚገባው ሁሉም ነው፡፡
አገራት ዓለም መንደር እየሆነች መምጣቷን ተገንዝበው በዛ መንገድ መንቀሳቀስ ከጀመሩ ሰነባብተዋል ፡፡ ባተረፉት ነገር ያጎደሉት ካለ እሱን ለመሙላት ዓለም እያስገደደቻቸው ነው፡፡ በመሆንም በግዙፍ እንደስትሪዎቻቸው ያተረፉትን እንደመቀማመሳቸውም ሁሉ በኢንደስትሪዎቻቸው ላደረሱት ብክለትም ከተጠያቂነት ለመዳን የተሻለን መንገድ ማፈላለግ የግድ ይላቸዋል፡፡
ከትርፉም ሳይቋደሱ የገፈቱ ግን ግንባር ቀደም ተጠቂ የሆኑም አሉ፡፡ ታዳጊ አገራት እንዲህ ካለው ቀውስ ለመላቀቅ እና እየሮጡ ካሉት ተቀዳሚ አገራት ረድፍ ውስጥ ለመሰደር ያላቸው የማያዳግም አማራጭ በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ የበለፀገች አገር ወደ መገንባት ፊትን ማዞር ብቻ ነው፡፡
ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ መራሽ እድገት የስኬት አቋራጭ መንግድ ነው፡፡ ይህንንም ማሳካት የሚቻለው ለሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ንቁ የሆነ ማህበረሰብን መፍጠር እና ማነፅ ሲቻል ብቻ ነው፡፡
….የቴክኖሎጂ እና የኢኖቬሽን ኢኒስቲቲዩት
ቀጭኔዎች ልክ እንደ ሰዉ ልጆች ከጓደኞቻቸዉ ጋር መመገብን ይመርጣሉ ተባለ፡፡
ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ብሎም ከእንስሳት ሁሉ በቁመት የሚወዳደር የሌላት ቀጭኔ በማህበራዊ ህይወቷ ዙሪያ ከሰሞኑ አዲስ ጥናት ብቅ ብሏል ።ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው።
በብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ በተደረገ ጥናት በእንስሳት አለም ዉስጥ ካሉት ሌሎች እንስሳት ዉስጥ በተለየ ሁኔታ ቀጭኔዎች ምግብ በሚመገቡበት ሰአት ልክ እንደ ሰዉ ልጅ በጋራ መመገብን እና በጋራ መሆንን እንደሚመርጡ ጥናቱ አስታዉቋል፡፡
በዩኒቨርሲቲዉ ምርምሩን የመሩት ዶ/ር ዙ ሙለር እንደገለጹት "ጥናቱን ያካሄድነዉ ለሁለት አመታት በኬንያ በታችኛዉ ስምጥ ሸለቆ በሚገኙ ቀጭኔዎች ላይ ሲሆን በረጃዉን በምናሰባስብበት ሰአትም ሁሉም ጥንድ የሆኑ ቀጭኔዎች ከምግብ ፍለጋ አንስቶ እስከሚበሉበት ሰአት ድርስ አብረዉ እንደሚያሳልፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡የሚያስገርመዉ ነገር ደግሞ ቀጭኔዎቹ ምግብ መብላትም የሚፈልጉት ከሚተዋወቁት ቀጭኔዎች ጋር ነዉ፡፡"ብለዋል
ምንጭ፡technology.org
ግዙፍ አካል፣ ከፍተኛ ፍጥነት፣ ቅልጥፍናና የማየት ችሎታ ብሎም ከእንስሳት ሁሉ በቁመት የሚወዳደር የሌላት ቀጭኔ በማህበራዊ ህይወቷ ዙሪያ ከሰሞኑ አዲስ ጥናት ብቅ ብሏል ።ቀጭኔዎች ከ2 እስከ 50 የሚደርሱ አባላት ባሉት መንጋዎች ተደራጅተው አንድ ላይ የሚኖሩ ማኅበራዊ ፍጥረታት ናቸው።
በብሪስቶል ዩኒቨርሲቲ በተደረገ ጥናት በእንስሳት አለም ዉስጥ ካሉት ሌሎች እንስሳት ዉስጥ በተለየ ሁኔታ ቀጭኔዎች ምግብ በሚመገቡበት ሰአት ልክ እንደ ሰዉ ልጅ በጋራ መመገብን እና በጋራ መሆንን እንደሚመርጡ ጥናቱ አስታዉቋል፡፡
በዩኒቨርሲቲዉ ምርምሩን የመሩት ዶ/ር ዙ ሙለር እንደገለጹት "ጥናቱን ያካሄድነዉ ለሁለት አመታት በኬንያ በታችኛዉ ስምጥ ሸለቆ በሚገኙ ቀጭኔዎች ላይ ሲሆን በረጃዉን በምናሰባስብበት ሰአትም ሁሉም ጥንድ የሆኑ ቀጭኔዎች ከምግብ ፍለጋ አንስቶ እስከሚበሉበት ሰአት ድርስ አብረዉ እንደሚያሳልፉ ለማወቅ ተችሏል፡፡የሚያስገርመዉ ነገር ደግሞ ቀጭኔዎቹ ምግብ መብላትም የሚፈልጉት ከሚተዋወቁት ቀጭኔዎች ጋር ነዉ፡፡"ብለዋል
ምንጭ፡technology.org
*የቡና ሰአት ከቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ቤተሰቦች ጋር*
"የስራ ባልደረቦች ብቻ ሳንሆን ቤተሰቦችም ጭምር ነን!"
በየአስራ አምስት ቀኑ የሚዘጋጀው የቡና ስነስረአት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ቤተሰቦችን ዛሬም እነሆ አሰባስቦ ደስታና ፈገግታን ከጨዋታና ቁምነገር ጋር እያስኮመኮመ ቤተሰባዊ የሆነች ግዜን ሰጥቶ አልፏል።
ይህ የቡና ስነስረኣት በሰራተኞች መሃል ያለ መስተጋብርን ከማጎልበትና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ከማጠናከር አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ከመሆኑም በላይ ከተጨናነቀና ከተወጠረ የስራ ስነልቦና ለኣፍታም ቢሆን በመውጣት አዳዲስ ሃሳቦችን እና መፍትሄዎችን የምናፈልቅበት እድል ያመቻቻል።
ይህን በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በወር ሁለት ግዜ የሚካሄድ የቡና ስነስርኣት የኢኒስቲትዩቱ የስራ ክፍሎች በየተራ ሙሉ ሽርጉዱን በመሸፈን የሚያስተናግዱት መሆኑ ሌላው ይህን መሰናዶ ቤተሰባዊ በሆነ መንፈስ ሁሉም የሚሳተፍበት አድርጎታል።
ይህን መሰሉ ተሞክሮ በሌሎችም ተቋማት ቢለመድ የሰራተኞችን ማህበራዊ መስተጋብር ከማጠናከሩ ባሻገር ጥሩ የሆነ የስራ ከባቢንና የአብሮነት መንፈስን በስራተኞች ዘንድ ለመዝራት ምቹ መደላድል መፍጠር ይቻላል።
"የስራ ባልደረቦች ብቻ ሳንሆን ቤተሰቦችም ጭምር ነን!"
በየአስራ አምስት ቀኑ የሚዘጋጀው የቡና ስነስረአት የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት ቤተሰቦችን ዛሬም እነሆ አሰባስቦ ደስታና ፈገግታን ከጨዋታና ቁምነገር ጋር እያስኮመኮመ ቤተሰባዊ የሆነች ግዜን ሰጥቶ አልፏል።
ይህ የቡና ስነስረኣት በሰራተኞች መሃል ያለ መስተጋብርን ከማጎልበትና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ከማጠናከር አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ከመሆኑም በላይ ከተጨናነቀና ከተወጠረ የስራ ስነልቦና ለኣፍታም ቢሆን በመውጣት አዳዲስ ሃሳቦችን እና መፍትሄዎችን የምናፈልቅበት እድል ያመቻቻል።
ይህን በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት በወር ሁለት ግዜ የሚካሄድ የቡና ስነስርኣት የኢኒስቲትዩቱ የስራ ክፍሎች በየተራ ሙሉ ሽርጉዱን በመሸፈን የሚያስተናግዱት መሆኑ ሌላው ይህን መሰናዶ ቤተሰባዊ በሆነ መንፈስ ሁሉም የሚሳተፍበት አድርጎታል።
ይህን መሰሉ ተሞክሮ በሌሎችም ተቋማት ቢለመድ የሰራተኞችን ማህበራዊ መስተጋብር ከማጠናከሩ ባሻገር ጥሩ የሆነ የስራ ከባቢንና የአብሮነት መንፈስን በስራተኞች ዘንድ ለመዝራት ምቹ መደላድል መፍጠር ይቻላል።