TechIn2
1.22K subscribers
1.47K photos
1 video
120 files
500 links
Technology & Innovation Institute (TechIn2), Ethiopia

የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት

ጠቃሚና ወቅታዊ የሆኑ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ፣ ጤና እና ሰብአዊ-ኣቅም ግንባታ(Human Development)መረጃዎችንና ምክሮችን በየእለቱ እናደርሶታለን።
Download Telegram
መረጃን ከብርሀን በተሸለ ፍጥነት ማስተላለፍ ይቻል ይሆን?
*********************************************************
ከአንስታይን Special Relativity እሳቤዎች አንዱ ብርሃን በወና ውስጥ ካለው ፍጥነት ሊፈጥን የሚችል ምንም ነገር የለም የሚል ነው፡፡ በዚህም እሳቤ መሰረት የብርሀን ፍጥነት አጠቃላይ የፍጥነት ልክ ተደርጎ ተወስዷል፡፡ በሳይንስ ጠንካራና አይነኬ የሚባል ህግ ማስቀመጥ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ይህ የሚሆን ከሆነ ምርምር የሚለው ሀሳብ ትርጉም ሊያጣ ይችላል፡፡ ዝርዝሩን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
ብርሃን በወና ውስጥ በአማካኝ 299,792 ኪሎ ሜትሮች ያክል በሴኮንድ ይጓዛል፡፡ በ2011 Oscillation የሚባል ፕሮጀክት የሚሰሩ የፊዚክስ ተመራማሪዎች neutrinos የተባሉ ከፊል ቅንጣቶችን (subatomic particles) ከሲውዘርላንዱ የአውሮፓ የኑክሌር ምርምር ተቋም ወደ ጣልያኑ ግራን ሳሶ ብሔራዊ ቤተ ሙከራ ከብርሃን በ60 ናኖ ሴኮንዶች ቀድሞ መላክ ችለዋል፡፡ ይህ እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ምርምር ሲያደርጉ የነበሩ ተመራማሪዎች ከገመድ ጋር የተያያዘ ችግር ወይም ስህተት በመኖሩ ምክንያት እንጂ የአንስታይንን ህግ ሊያሻሽል የሚችል ግኝት እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት አብዛኛው የአለማችን መረጃ የሚተላለፈው በኮፐር ገመድ ወይም በፋይበር ኦፕቲክ ገመድ ነው፡፡ ከነዚህም የተሸለ ፍጥነት ያለው ሁለተኛው ነው፡፡ በብርሀን ጉዞ ውስጥ ወና የሚለው ሃሳብ መሰረታዊ ሀሳብ ነው፡፡ ብርሃን በወና ውስጥ ሲጓዝና በገመድ ውስጥ ሲጓዝ ፍጥነቱ ተመሳሳይ አይደለም፡፡ ብርሀን በምንም ነገር ውስጥ ቢጓዝ በወና ውስጥ እንደሚያደርገው ጉዞ ፈጣን ሊሆን አይችልም፡፡
የብርሀን ሁለት አይነት ተፈጥሮ በተለያዩ ነገሮች ውስጥ ሲጓዝ ፍጥነቱ እንዲለያይ አድርገውታል፡፡ እነዚህም የሞገድና የቅንጣቶች ባህሪ ናቸው፡፡ ብርሃን photons የሚባሉ ቅንጣቶች ስሪት በመሆኑ በገመድ ውስጥ በቀጥታ መጓዝ አይችልም፡፡ photons ከገመዱ ሞሎኪዩሎች ጋር ሲጋጩ አቅጣጫቸውን ይቀያይራሉ፡፡
Fiber optic የሚባለው የገመድ አይነት ከኮፐር ገመድ በጣም የተሻለ ፍጥነት ሲኖረው ከኤሌክትሮ መግነጢሳዊ ጣልቃ ገብነት የጸዳ ነው፡፡ ፋይበር በሴኮንድ በመቶወች የሚቆጠር ጌጋ መረጃን እንዳንዴም በቴራባይት የሚለካ መረጃን ማስተላለፍ ይችላል፡፡ የቤት ውስጥ የኢንተርኔት አገልግሎቶች ይህ የላቀ ፍጥነት የላቸውም፡፡
በ National Institute of Standards and Technology (NIST) የሚሰሩ ተመራማሪዎች ኳንተም መጠን ያለው መረጃን ከብርሀን በተሻለ ፍጥነት ለማስተላለፍ እየሰሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ በሙከራቸውም ከ50 እስከ 90 ናኖ ሴኮንድ ከብርሃን የተሸለ ፍጥነት መመዝገብ ችለዋል፡፡ ይህ ምንም እንኳን በወና ውስጥ ቢሆንም ትርጉም ያለው መረጃ ግን አይደለም፡፡ በዚህ ዘርፍ ያለው ሌላው የምርምር መንገድ quantum teleportation ይባላል፡፡
ከላይ ለተነሳንበት ጥያቄ አሁናዊ መልስ ትርጉም ያለው መረጃ ከብርሀን በተሻለ ፍጥነት ሊጓዝ አይችልም ነው፡፡ አንድ ትርጉም ያለው መረጃ ከብርሃን በተሻለ ፍጥነት ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ማስተላለፍ ከተቻለ ለወደፊቱ የመረጃ አለም ትልቅ ለውጥ ማምጣቱ የማይቀር ነው፡፡ ይህም ከፍተኛ ጥራት ያለው የቴሌቪዥን ፕሮግራም ለመከታተልና ልዩ ልዩ ድረ- ገጾችን በፍጥነት ለመክፈት ያስችላል፡፡
ምንጭ፡ www.howstuffworks.com
የጭንቀት በሽታ መገኛው ይታወቅ ይሆን
ከእውቀት አንጻር ሲታይ, ጭንቀት በጣም አስፈላጊ የአዕምሮ ሁኔታ ነው፤ ነገር ግን ከቁጥጥር ውጪ ሲሆን የድባቴ (ድብርት) ስሜት ውስጥ በማስገባት የመገለል ስሜትን ይፈጥራል፡፡ አሁን ላይ ያሉት ፀረ-ጭንቀት መድሃኒቶች ደግሞ አንዳንድ አሉታዊ የጎንዮሽ ጉዳቶች ይመጣሉ፡፡ ይህን ችግር ለመቅረፍ ተመራማሪዎች አንድ መላ ያገኙ ይመስላል፡፡ በማክስ ፕላን ኢንስትቲዩት የህክምና ሙከራ ተመራማሪዎች ይህን የጭንቀት በሽታ ለመከላከል ዋናው እና ቁልፍ የሆነውን በአንገጎላችን ውስጥ የሚገኘውን ፕሮቲን ለይተው አግኝተውታል፡፡
አንጎላችን እጅግ ውስብስብ አካል ሲሆን ጭንቀትን የሚፈጥረው ችግር በርግጠኝነት የትኛው የአንጎላችን ክፍል እንደሆነ ማወቅ አይቻልም፡፡ ነገርግን አሚግዳላ (amygdala) ችግሩ የሚከሰትበት የአንጎላችን ክፍል እንደሆነ ይታመናል፡፡ አሚግዳላ በአንጎላችን ውስጥ የሚገኝ ክፍል ሲሆን እንደ ጭንቀት እና ፍርሀት ያሉትን ስሜቶች የሚሰተናገዱበት የአዕምሮ ክፍል ነው፡፡ ከልክ ያለፈ የአሚግዳላ እንቅስቃሴ የጭንቀት መዛባትን (anxiety disorder) ያመጣል፡፡
አሁን ላይ ያሉት የጭንቀት መድሀነኒቶች በተለይም ደግሞ ቤንዞዲያስፒን በዋናነት አሚግዳላ ኢላማ አድርጎ የሚሰራ መድሀኒት ሲሆን ተግባሩም በአሚግዳላ አካባቢ ያሉ የነርቭ እንቅስቃሴዎችን በመቀነስ በጭንቀት ወይም በፍርሀት ውስጥ ያለን ሰው እንዲረጋጋ ያደርጋል፡፡ ይሁንና እንደዚህ ያሉ መድሀኒቶች በሚወሰዱበት ጊዜ ሌላ የጎንዮሽ ጉዳት እንደ ከፍተኛ የሆነ እንቅልፍ እና የትኩረት ማጣት ያስከትላሉ፡፡
በሆኑም እንዚህን የጎንዮሽ ችግር ለመቅረፍ እና ውጤታማ የሆነ የጭንቀት መደሀኒት ለመስራት የማክስ ፕላን ኢንስትቲዩት ተመራማሪዎች IgSF9b የተባለ በአንጎላችን ውስጥ የሚገኝ ፕሮቲን አግኝተዋል፡፡ የዚህ ፕሮቲን ተግባር በአጋጅ ሲናፕሲስ መካከል የሚገኘውን ክፈተት መሙላት ሲሆን ከዚህ ባለፈም ለአእምሮ ስጋት የሆኑ ተግባራትን በማገድ የጭንቀት መዛባትን መከላከል የሚያስችል ፕሮቲን ነው፡፡ ይህን የምርምር ውጤት በቤተ ሙከራ አይጥ ላይ በመሞከር ውጤታማነቱን ማረጋገጥ መቻሉን የሚያስረዱት ተመራማሪዎች የፕትሮቲን ተለይቶ መታወቁ የጭንቀት መዛባትን ለመቅረፍ በእጅጉ እንደሚረዳ ይናገራሉ፡፡
ምንጭ፡ Medicalxpress
TechIn2 pinned a file
በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዙሪያ ያለው የማህበረሰባችን ግንዛቤ/Perception/፤ በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በቅርቡ ይፋ የተደረገ ሀገራዊ የዳሰሳ ጥናት
====================
ለአንድ ሀገር እድገት የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አስተዋፆ ጉዳይ አጠያያቂ አይሆን ዘንድ ማህበረሰቡ በጉዳዩ ላይ ያለው ግንዛቤ (perception) እጅግ ወሳኝ ይሆናል፡፡ መንግስትን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት በዘርፉ ሚናቸውን በሚገባ እንዲወጡም ከፖሊሲ ቀረፃ ጀምሮ ማህበረሰቡ ያለበትን የግንዛቤ ደረጃ ማወቅና መገንዘብ ተገቢና ቀዳሚው ተግባር ሊሆን ይገባዋል፡፡
ምናልባትም ማህበረሰባችን ለሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ያለው ምልከታ እምብዛም ነው ብለው ያስቡ ይሆን?
የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢንስትቲዩት (TechIn) አስር-ሺህ (10,000) ከሚጠጉ የማህበረሰባችን ክፍሎች በጉዳዩ ላይ መረጃዎችን በሳይንሳዊ መንገድ በመሰብሰብ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገራዊ የዳሰሳ ጥናት በማድረግ በቅርቡ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ጥናቱ በአጠቃላይ ማህበረሰባችን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጅና ኢኖቬሽን ጉዳዮች ዙሪያ ያለውን የግንዛቤ (awareness)፣ የእውቀት (knowledge)፣ የፍላጎት (interest) እና አመለካከት (attitude) ደረጃ ያሳየ ሲሆን በተጨማሪም የመረጃ ምንጮቻቸውን ይዳስሳል፡፡
ሪፖርቱ እንሚያሳየው ማህበረሰባችን ለሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ያለው ፍላጎት እና አመለካከት ከእውቀት እና ግንዛቤ አኳያ ሲታይ የተሻለና ጥሩ ደረጃ ላይ እንደሆነ ያመለክታል፡፡
በሌላ በኩል (ከጥናቱ እንደሚጠበቀው) ከገጠር ይልቅ የከተማው፤ ከሴቶች ይልቅ የወንዶች እንዲሁም በተሻለ የትምህርት ደረጃ ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች በአንፃራዊነት በአማካይ የተሻሉ መሆናቸውን በሪፖርቱ ተዳሷል፡፡
በአጠቃላይ በጥናቱ ሰፊ ጉዳዮች ላይ ዳሰሳ የተካሄደ ሲሆን ከአስገራሚ ግኝቶችም መካከል አንዱ የግብርና ጉዳዮችን በተመለከተ የታየ ግኝት ነው ይህም ከነዚህም ውስጥ የትምህርት ደረጃ ሲጨምር ለዘርፋ (ማለትም ለግብርናው ዘርፍ) የሚኖር ፍላጎት (interest) በመጠኑም ቢሆን እንደሚቀንስ የሚያሳይ እንደሆነ ያመላክታል፡፡ ይህም ግብርናችንን በተማረ የሰው ኃይል ለመምራት፣ ለማሳለጥና ለማዘመን ለሚደረገው ከፍተኛ ጥረት ትልቅ ማነቆ መሆኑን በማመላከት ጥናቱ የመፍትሄ ሃሳብ ጠቆም ያደርጋል፡፡
ሌሎች በርካታ የጥናቱን ዉጤቶች ከላይ በተቀመጠው PDF ፋይል አማካኝነት ከሪፖርቱ ትመለከቱ ዘንድ እንጋብዛለን፡፡
የሰውነት በሽታ መከላከል ብቃት እና የአፍ እጥበት
***********************************************
በአሁኑ ወቅት ንጽህና የአለማችን ትልቁ መርህ እየሆነ ይገኛል፡፡ ይህም በእያንዳንዱ ቅጽበት ለንጽህናችን ጥንቃቄ ማድረግ እንዲኖርብን ያደርገናል፡፡ ንጽህናን መጠበቅ የባክቴሪንና የቫይረስን መስፋፋት ለማስቆምና ጤናችንን ለመጠበቅ እጅግ ትልቅ ጥቅም አለው፡፡ ለዚህም ማሳያ እንዲሆን እጅን መታጠብ ከብዙ ተላላፊ በሽታዎች የሚጠብቅ መሆኑን ማስታወስ ይቻላል፡፡
ንጽህናን መጠበቅ ያለው ጥቅም ምንም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ነገር አይደለም፡፡ በአንጻሩ ግን በተለይ የአፍ ጤናን ለመጠበቅ ብለን ጥርሳችንን ከሚገባው በላይ የምንታጠብ ከሆነ በሽታ የመከላከል አቅማችንን ልንጎዳው እንችላለን ብለው የሚያስቡ ተመራማሪዎችን ቁጥራቸው ቀላል አይደለም፡፡ እንደነዚህ ተመራማሪዎቹ ከሆነ ከዚህም ከዚያም የሚገኙ ጥቂት ጀርሞች የሰውነታችን በሽታ ተከላካይ ክፍል እንዳይዘናጋና በተጠንቀቅ እንዲቆም ያደርጉታል፡፡
የሰው ልጅ በሽታ የመከላከል ብቃት የጦር ሜዳ ልምድ ለውን ወታደርን ይመስላል፡፡ ይህ ልምድ ያለው ወታደር ልምድ ከሌለው ወታደር ይልቅ እንዴት መከላከል እና እንዴት ማጥቃት እንዳለበት የተሸለ ያውቃል፡፡ በመሆኑም የተሻለ ጠላትን የመቋቋም ብቃት አለው፡፡ ይህ ሲባል ግን የአፍ ንጽህና በጠበቅን እናቁም ማለት እንዳልሆነ መረዳት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ጉዳዩ ከመጠን በላይ ስለሆነ እጥበት ነው፡፡
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እንደ አለርጂ እና ከሰውነት የበሽታ መከላከል አቅም ጋር የተያያዙ በሽታዎች በተለይ በምእራቡ አለም እየተስፋፉ ነው፡፡ በ2016 በተሰራ ጥናት በአሜሪካ ከሚገኙ ህጻናት 40 በመቶ የሚሆኑት ከሰውነት የበሽታ መከላከል ብቃት ማነስ ጋር በተያያዘ ወደ ህክምና ተቋማት ያመራሉ፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያትነት የተነሳው ከልክ በላይ የሆነ የንጽህና አጠባበቅ ባህል ነው፡፡
በሰውነታችን ውስጥ ሊኖሩ የሚገባቸው ጠቃሚ ትላትሎች (worms) ደቂቅ ዘአካላት (microbes) ሙሉ በሙሉ ከሰውነታችን የሚጠፉ ከሆነ የሰውነታችን በሽታ ተከላካይ ክፍል ስራ ፈት ይሆናል፡፡ ይህ በሂደት የበሽታ መከላከል አቅምን ያደክምና በአጋጣሚ በሚመጡ አነስተኛ ህመሞች ሳይቀር በቀላሉ እንድንጠቃ ያደርገናል፡፡ ከኮቪድ 19 ጋር ያለው የመጠቃት መጠንም ከዚሁ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል መገመት አያዳግትም፡፡ ይህ ሲባል ግን መቆሸሽ በየትኛውም መንገድ መፍትሔ ሊሆን እንደማይችል ሊሰመርበት ይገባል፡፡
ምንጭ፡ www.howstuffworks.com እና www.theconversation.com
፲ የኦንላይን የደህንነት ምክሮች ከጎግል
--------------------------------------------
ባለፉት ወራቶች የሳይበር ደህንነት ማስገንዘቢያ መርሃ ግብሮች ሲካሄዱ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡ በተለይም የጥቅምት ወር ይህን የግንዛቤ ስራ ለማካሄድ በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ስትውል ተመልክተናል፡፡ ይህን በማከናወን ሂደት ግዙፉ የጎግል ኩባንያ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ድርጅት ሲሆን በአሰራር ፕሮቶኮሉም የበይነ-መረብ ተጠቃሚዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ መልኩ ስራቸውን እንዲያከናውኑ ትልቅ እገዛ ያደርጋል፡፡ እነዚህ የምትመለከቷቸው የጎግል የደህንነት ማሻሻያ አማራጮች በኢንተርኔት ላይ የሚኖረንን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ከማስጠበቅ አልፎ ለስራችን መሳካትም ትልቅ ሚና ሊኖራቸው ስለሚችል በሚገባ ማየቱ ጠቃሚ ነው፡፡
፩. በአይነታቸው የተለዩ እና ለመገመት አስቸጋሪ የሆኑ የይለፍ ቃሎችን ለመፍጠር የጎግልን የይለፍ ቃል አስተዳደር (password manager) መጠቀም የመጀመሪያው የጥንቃቄ መንገድ ነው፡፡
፪. በዴስክቶፕ እና በሞባይል የኦፕሬቲንግ ስርዓቶች የሚጫኑ የድር ማሰሻ (web browser) መተግበሪያዎች ምንግዜም የመጨረሻው ማዘመኛ (up-to-date) የተደረገላቸው መሆን አለባቸው፡፡ ይህ ደግሞ የምንጠቀማቸውን የኦንላይን ቴክኖሎጂዎች ከደህንነት ስጋት ውጭ ያደርጋቸዋል፡፡
፫. ስልካችን ጠፍቶ ቢገኝና በፍፁም የማናገኝበት ሁኔታ ቢፈጠር በጎግል አካውንታችን አማካኝነት ( myaccount.google.com.) በመግባት ከየኛውም ቦታ ሆነን ስልካችንን መቆለፍ እና ሚገኝበትን አካባቢ መረዳት እንችላለን፡፡
፬. የበይነ መረብ አገልግሎት ስንጠቀም የግል መረጃዎቻችንን የሚያጠምዱ የተለያዩ ድረ ገፆች ሊያጋጥሙን ይችላሉ፡፡ እነዚህ የመረጃ አጥማጆች በተከታታይ የሚቀርቡልንን ጥያቂዎች በንቃት መከታተል አንደኛው የመጠበቂያ መንገድ ሲሆን፤ ከዚያ በለፈም በመተግበሪያችን (browser) ላይ ሊጫኑ ወይም (extended) ሊደረጉ የሚችሉ መሳሪያዎችን በማከል ችግሩን ማስቀረት አንችላለን፡፡ በዚህ አንፃር የጎግል ሳይቶች ያልሆኑ (non-Google site) አድረሻዎች ላይ የይለፍ ቃል ስናስገባ ማስጠንቀቂያ የሚልክልን እንደ (Password Alert extension) ያለ መሳሪያ በመተግበሪያችን ላይ መቀላቀል እንችላለን፡፡
፭. አንዳንድ ጊዜ የመረጃ መንታፊዎች ወይም ሃካሮች የኛኑ የመጠቀሚያ ስም (username) እና የይለፍ ቃል በአካውንታችን ላይ በማስገባት አጠቃላይ መረጃችንን ሊሰርቁና ሊያጠቁን ይችላሉ፡፡ ይህ ሊሆን የሚችልበት ምክንያት የተለያየ ቢሆንም አብዛኛውን ጊዜ ግን የጠነከረ የይለፍ ቃል ሳይኖር ሲቀርና የተለያዩ ማዘመኛዎች ሳናደርግ ስንቀር ነው፡፡ አነዚህ የአጠቃቀም ክፍቶች ብዙዎቻችን ላይ የሚስተዋሉ ቢሆንም ካዛ ባለፈ በስራቸው ላይ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ሰዎች ግን በጎግል አካውንት ላይ (security.google.com) በመግባት የሁለተኛ ደረጃ ማረጋገጫ (2-Step Verification) በማስቻል እያንዷንዷን እንቅስቃሴያቸውን መመልከት ይኖርባቸዋል፡፡
፮. አሁን አሁን ከየትኛውም የማህበረሰብ ክፍል በላይ የፖለቲካ መሪዎች እና የማህበረሰብ አክቲቪስቶች ለሳይበር ጥቃት እጀግ ተጋላጭ እየሆኑ መምጣቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ታዲያ አንደዚህ አይነት ግለሰቦችና ሌሎች ከፍተኛ የሳይበር ስጋት ያለባቸው አካላት ጎግል የሚያቀርበውን የላቀ የጥበቃ መርሃ-ግብር (Advanced Protection Program) መጠቀም ይችላሉ፡፡ ይህ ፕሮግራም መረጃ አጥማጆችን በሚገባ ለመከላከል የሚጠቅም ሲሆን በታመኑ መተግበሪያዎች ላይ የኔትወርክ አጠቃቀችንን ለመገደብ እና አካውንታችንን አጭበርብረው ለሚጠቀሙ ሃከሮችም ጥሩ መፍትሄ ነው፡፡
፯. አብዛኛውን ጊዜ በስልካችን የምናወርዳቸው ምንጫቸው ያልታመነ መተግበሪያዎች ለየትኛውም የሳይበር ጥቃት በቀላሉ ሊያጋልጡን ይችላሉ፡፡ ከጎግል ፕለይ ያወረድናቸው መተገበሪያዎች እንኳን አልፎ አልፎ መሰል ስጋት ስለሚኖርባቸው የጎግል ፕለይ ጥበቃ ላይ (Google Play Protect) የደህነት ፍተሻ መድረግ እጅግ ተመራጭ ይሆናል፡፡
፷. በጎግል የበይነ መረብ አጠቃቀማችን ላይ እያንዷንዷን እንቅስቃሴያችንን በየጊዜው ለመፈተሸና ለመከታተል የጎግልን (Security Checkup) በቀላሉ መጠቀም እንችላለን፡፡ ይህ ሲስተም የጎግል አካውንታችንን ደህንነት ለመተንተን እና ያጋጠሙ ችግሮችንም በቀላሉ ለመፍታት የሚያገለግለን ነው፡፡
፱. ምንግዜም ቢሆን የህዝብ ወይም ነፃ የዋይፋይ ኔትወርኮችን ስንጠቀም በምላሹ ሊኖር ስለሚችለው የደህንነት ስጋት መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ የዋይፋይ ኔትወርኩ የይለፍ ቃል የታከለበት ቢሆንም እንኳን መረጃዎቻችንን አሳልፎ እንዳይሰጥ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
፲. ከእነዚህ ጥንቃቄዎች በተጨማሪ በጎግል አካውንታችን ላይ የደህንነት ቁልፍ (security key) በማዋቀር አጠቃላይ የበይነ መረብ አንቅስቀሴያችንን ማስጠበቅ እንችላለን፡፡
ምንጭ፡ Gadgets Africa
የፕሮጀክት ማኔጅመንት ስልጠና በመካሄድ ላይ ነው
-----------------------------------
በቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኢኒስቲትዩት የተዘጋጀው በፕሮጀክት ማኔጅመንት ላይ ያተኮረ መርሃ ገብር በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በኢኒስቲትዩቱ በቅርብ ጊዜ በተቋቋመው የፕሮጀክት ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀው ይህ ስልጠና ከተለያዩ ዳይሬክቶሬቶች ለተወጣጡ የፕሮጀክት ማናጀሮች መሰረታዊ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሂደቶችን የሚያስቃኝ ነው፡፡
በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ሃሳባቸውን ያካፈሉት የኢኒስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ቀሬ በቅሩቡ የተቋቋመው የፕሮጀክት ማኔጅመንት ዳይሬክትር ተቋሙ የሚያከናውናቸውን የፕሮጀክት ስራዎች በማዕከላዊነት ለማስተዳደር እና በቀጣይም ትልልቅ ሃሳቦችን ከመነሻው አንስቶ አስከመጠናቀቂያው ጊዜ ድርስ በስኬት ለማጠናቅ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀን በሚቆየው በዚህ የስልጠና መረሃ ግብር የፕሮጀክት አፈፃፀም ሂደት ላይ ያሉ ክፍተቶች፣ ከፕሮጀክት መነሻ ሃሳብ እስከ ማጠናቀቅ ብሎም የፕሮጀክቱን ዓላማ ከማሳካት አኳያ ያሉ ሂደቶችን፣ በቀጣይ መሻሻል ስለሚገባቸው ጉዳዮች፣ ከመምራት እስከ መፈፀም ድረስ መከተል ስለሚገባን የስነምግባርበ ሂደቶች እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እንደሚቆይ ይጠበቃል፡፡
ለሁለተኛ ዙር የሚካሄደው ይህ ስልጠና የኢኒስቲትዩትን የፕሮጀክት የአሰራር ሂደት አለም አቀፍ ስታንዳርድ በተላበሰ መልኩ ለማስኬድ እና የፕሮጀክት እቅዶችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ለመምራትና ለማስፈፀም አላማ አድርጎ የሚካሄድ ነው፡፡
በቀን የሚያስፈልገን የኦክስጅን መጠን
********************************
አንድ ጎልማሳ በአማካኝ በደቂቃ ከ7 እስከ 8 ሊትር የሚሆን አየር ወደውስጥ ስቦ ያስወጣል፡፡ በሌላ መ ልኩ 388 ኪዩቢክ ጫማ እንደማለት ነው፡፡ ይህም አንድ ሰው በቀን የሚጠቀመውን አየር ወደ 11 ሺህ ሊትር ያደርሰዋል፡፡ መጠቀም የሚለው ቃል ኦክስጅን ወደ ውስጥ መማግንና የተቃጠለውን አየር ማስወጣትን የሚገልጽ ነው፡፡
ወደ ሰውነታችን ከምናስገባው አየር ውስጥ 20 በመቶ የሚሆነው ኦክስጅን ሲሆን በእምጋት ከምናስወጣው አየር ውስጥ ኦክስጅን 15 በመቶ የሚሆነውን ይሸፍናል፡፡ ስለዚህ በየአንዳንዱ ትንፋሽ 5 በመቶ የሚሆን ኦክስጅን ለአጠቃላይ ስርዓተ-ሰውነት አገልግሎት ይውላል ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አንድ ሰው ከወጭ ቀሪ 550 ሊትር ንጹህ ኦክስጅን ይጠቀማል ማለት ነው፡፡
ነገር ግን አንድ ሰው አዘውትሮ የሰውነት እንቅስቃሴ የሚሰራ ከሆነ ከዚህ የበለጠ የኦክስጅን መጠን ይጠቀማል፡፡ በሳንባችን ውስጥ የሚንቀሳቀሰውን አየር ይዘቱ በሚታወቅ ፕላስቲክ ወደውጭ በመተንፈስ መጠኑን መለካት እንችላለን፡፡
ምንጭ፡ www.howstuffworks.com
ኢትዮጵያ በ15 ዓመታት ውስጥ 10 ሳተላይቶችን ለማምጠቅ አቅዳለች
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሽሩን አለማየሁ ዛሬ በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት በመገኘት ስለ ሳተላይት እና የኢትዮጵያ ሳተላይት ፕሮግራም ዙርያ ማብራርያ ሰጥተዋል፡፡ የኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎችን ተሳታፊ በሆኑበት በዚህ ዝግጅት ዶ/ር ይሽሩን በሳተላይቶች ታሪክ፣ አይነት እንዲሁም በግብርና፣ ጤና፣ መጓጓዣ፣ የህዝብ አሰፋፈር….ረገድ ሳተላይቶች ሊያቀርቡ ስለሚችሉት ጥልቅ ግልጋሎት ለታዳምያኑ አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በህዋ ምርምር ረገድ እስካሁን የተራመደቻቸውን እርምጃዎች እንዲሁም አሁን ያሉ እቅድ እና እንቅስቃሴዎችን ዳይሬክተሩ የዳሰሱ ሲሆን ከነዚህ መካከል የሆነውን በ15 ዓመታት ውስጥ 10 ሳተላይቶችን የማምጠቅ ዕቅድንም አውስተዋል፡፡ የዚህ ግዙፍ እቅድ አካል የሆኑት ከ3-4 ባሉት ዓመታት ውስጥ የኮምዩኒኬሽን እና የምድር ምልከታ ሳተላይቶችን እንዲሁም በ 10 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የአየር ትንበያ ሳተላይት የማምጠቅ እቅዶችንም ማብራርያ ቀርቦባቸዋል፡፡
ሌላው በመድረኩ ማብራርያ ያገኘው ኢትዮጵያ በያዝነው ዓመት ታህሳስ 11 ዕለተ እሁድ እንደምታመጥቀው የሚጠበቀው አዲስ ሳተላይት ጉዳይ ነው፡፡ ከአንድ ዓመት የበለጠ የአገልግሎት ዘመን እንደሚኖራት የሚጠበቀው አዲሷ ሳተላይት ከምድር በ512 ኪ.ሜ ከፍታ ላይ በመሽከርከር መረጃ የምታቀብል ይሆናል፡፡ ሳተላይቷ ET-SMART-RSS የሚል ስያሜን ያገኘች ሲሆን መጠኗ አንድ አመት ቀድማት ወደ ህዋ ከተጓዘችው ETRSS-1 አንፃር አነስ ያለች (8.9 ኪ.ግ የምትመዝን) ስትሆን በቻይናዋ ሃይናን ግዛት ውስጥ ካለው ዌንቻንግ የማምጠቂያ ማዕከል የምትመጥቅ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ቀድሞ የመጠቀችው ሳተላይት ባስገኘቸችው ምጣኔ ሐብታዊና ሌሎች ጥቅሞች ብሎም በሀገሪቱ የተከሰቱ የተፈጥሮ አደጋዎችን በመተንበይ ረገድ ስለነበረባት ክፍተት ጥያቄ የተነሳ ሲሆን ዳይሬክተሩም የተለያዩ የሀገራችን ተቋማት ቀድሞ ከሌላ ያገኟቸው የነበሩትን መረጃ አሁን በሳተላይቷ አማካኝነት ማግኘት መጀመራቸውን በማውሳት ጭምር ምላሽ ሰጥተውበታል፡፡ በህዋ ምርምር ዙርያ ታዳጊዎችን በማውጣት ረገድ ኢንስቲትዩቱ እየሰራቸው ስላሉት ስራዎችም ተጠይቀው ኢንስቲትዩታቸው በበቂ ደረጃ ታዳጊዎችን በዘርፉ የማብቃት ስራዎችን እየሰራ እንዳልሆነ አምነው ወደፊት ግን በትምህርት ካሪኩለሙ ውስጥ እስከማካተት የሚደርስ ታዳጊዎችን የማብቃት ስራ ለመስራት እንደታሰበ ዶ/ር ይሽሩን ተናግረዋል፡፡
በሽታው የጋራችን፤ ክትባቱ የግላችን?
=======================
የሐብታም ሀገራት መንግስታት 8.8 ቢሊዮን ፍሬ ክትባት ለመግዛት የሚያስችላቸውን ስምምነት እያከናወኑ ሲሆን ይህም ደሀ ሀገራት ክትባቶቹን ቢያንስ እስከ አውሮፓውያኑ 2024 ድረስ እንዳያገኙ የሚያደርግ መሆኑ ተነግሯል፡፡
እስካሁን በሙከራ እና ሌሎች ሂደቶች ውስጥ እያለፉ ካሉት 320 በላይ ክትባቶች ውስጥ አንዳቸውም ጥቅም ላይ እንዲውሉ ፍቃድ ያልተሰጣቸው ቢሆንም እስካሁን ድረስ የሐብታም ሀገራት መንግስታት 3.73 ቢሊዮን ፍሬዎችን ለመግዛት የሚያስችል ስምምነት ከመድሃኒት አምራች ኩባንያዎች ጋራ ገብተዋል፤ 5 ቢሊዮን ፍሬ ለመግዛት የሚያስችሉት ስምምነቶችም በቅርብ የሚደረሱ ይሆናሉ፡፡
የመድሃኒት አምራቾች በአሁኑ ሰዓት ያላቸው አቅም እነዚህ እጩ ክትባቶችን በማምረት ብቻ የተወሰነ ነው፤ ይህ ማለት ክትባቶችን ወደተቀረው የዓለማችን ህዝብ በማድረስ ከወረርሺኙ ለመታደግ ሦስት አልያም አራት ዓመታት ሚያስፈልጉ ይሆናል፡፡ በነዚህ ወቅቶች የደሃ ሀገራት ዜጎች በክትባት አማካኝነት ከወረርሺኙ ከመጠበቃቸው አስቀድሞ ሐብታም ሀገራት ጠቅላላው ህዝባቸውን በተደጋጋሚ ክትባት ለማስከተብ የሚችሉ ይሆናል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት ኮቫክስ (Covax) በተባለው እቅዱ አማካኝነት ፈራሚ ሀገራት ስኬታማ የሆኑትን ክትባቶች በእኩል መጠን እንዲካፈሉ ለማድረግ እየሰራ ነው፡፡ በዚህም ክትባቶቹን በመጀመሪያ ለጤና እና የደህንነት ባለሙያዎች፤ በመቀጠልም ቢያንስ 20 በመቶ ለሚደርሰው የሀገራቱ ህዝብ ለማድረስ ለማድረስ አስቧል፡፡ ታድያ ሐብታም ሀገራቱ ለዚህ እቅድ ድጋፍ ሲያደርጉ ቢቆዩም አሁን ግን ከመድሃኒት አምራቾቹ ጋራ ከጥታ ስምምነት ውስጥ ገብተዋል፡፡ ይህም በኮቫክስ አማካኝነት በእኩሌታ ይከፋፈል የነበረውን ክትባት ለራሳቸው ብቻ ያስቀረ ነው፡፡
ኢትዮጵያን ለምሳሌ ብናነሳ በኮቫክ አማካኝነት 20 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ ክትባቱን ያገኝ የነበረ ቢሆንም ምንም አይነት የጎንዮሽ ስመምነት ውስጥ ሰባለመግባቷ ምክንያት እንደ እንግሊዝ ያሉት ሀገራት ህዝባቸውን ሙሉ ለሙሉ ከበሽታው ሲጠበቁ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ግን ለዓመታት ክትባቱን ሳያገኝ ይቀራል፡፡
ሌላኛው በክትባት ዙርያ ያለ ችግር በቅዝቃዜ ስፍራ መቀመጥ ላለባቸው ክትባቶችን እንዲሁም በከፍተኛ ሙቀት መቀመጥ የሚገባቸው ቁሳቁሶችን ለማስቀመጫ የሚሆን በቂ መሰረተ ልማረትና አቅም ማጣት ነው፡፡ ጆንሰን እና ጆንሰን ድርጅት በቅድሚያ የሚያመርታቸው በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆተሩ በመጠነኛ የማቀዝቀዣ ቅዝቃዜ ውስጥ ያለምንም ችግር ለብዙ ወራት መቀመጥ የሚችሉ እጩ ክትባቶች ይህን የማቀዝቀዣ ችግር ሊያቃልሉ የሚችሉ ናቸው፤ ሆኖም እነዚህ ክትባቶችንም አሜሪካን፣ ካናዳ፣ እንግሊዝ እና የአውሮፓ ሕብረት አስቀድመው በገፍ ገዝተዋቸዋል፡፡
ኮቫክስ እስካሁን ድረስ 250 ሚሊዮን ህዝብን መከተብ የሚችል ክትባት መግዛቱ ታውቋል፡፡ ይህ ግን ቀድሞ ሊሸፍነው አስቦት ከነበረው 1.14 ቢሊዮን ህዝብ አንፃር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ ቸርነት ካሳዩት ጥቂት ሐብታም ሀገራት መካከል የሆነችው አውስትራሊያ ለ25 ሚሊዮን ህዝቧ ለመግዛት ከተስማማችው 80 ሚሊዮን ክትባቶች ውስጥ ለደሀ ሀገራትም ለማካፈል ፍቃደኝነቷን ገልፃለች፤ ምንም እንኳን የምታካፍለው በህዝብ ብዛት ሚጢጢ ለሚባሉት እንደ ቫኑአቱ እና ፊጂ ላሉ ጎረቤት ሀገራት ቢሆንም፡፡
ከዚህ ቀደም ከጤና ባለሙያዎች ሰፈር ሀገራት ግብዓቶቻቸውን ለራሳቸው በመሰብሰብ እና ወደውጭ የሚላኩት ላይም ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ የሚከናወን የክትባት ብሔረተኝነትን የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ይበልጥ ላልተፈለገ ጊዜ በዓለም ላይ እንዲቆይ ያደርግ ይሆናል የሚል ስጋታቸውን ሲያነሱ ነበር፡፡
ምንጭ፡ The Guardian