በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የተዘጋጀው አዲስ የፖሊሲ ጥናት
=====================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጥናት ዳይሬክቶሬት “Data Privacy Policy for Ethiopia and the need for Compliance with International Standards” በሚል ርዕስ የፖሊሲ ጥናት አውጥቷል፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ የተደራጀና ሁሉን አለም አቀፍ ስታንዳርዶችን ያሟላ የመረጃ/ጥሬ ሀቅ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ላይ የተለያዩ አመክንዮዎችን በመንተራስ ምክረ ሀሳብ የሚያቀርብ ነው፡፡
ያደጉት ሀገራት የዛሬ 40 እና 50 ዓመታት ገደማ ግለሰባዊ መረጃን የሚጠብቁ ሕጎችን ሲተገብሩ መኖራቸውን ያወሳው ጥናቱ በአንፃሩ ሀገራችን ላይ አሁንም ድረስ ይህን ሁኔታ ባልተደራጁና በቂ ባልሆኑ ሕጎች ለመቆጣጠር እየዳከርን መሆኑን ይጠቁማል፡፡
የፖሊሲ ጥናቱ በኢትዮጵያ የመረጃ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ በሌሎች ሀገራት ደረጃ ካለው የፖሊሲ እና ህግጋት ጋራ አለመጣጠም በተለይም ሀገራችንን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ወይም ኢ-ኮሜርስ ስርዓቱን በሚፈለገው ልክ እንዳታሳድግ እና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ብሎም ሀገራት ከእኛ ጋራ እንዲሰሩ የማያስችል ሁኔታ እንደሚፈጥር የአውሮፓ ህብረት እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሕግጋትን በተግባራዊ ምሳሌነት አስደግፎ አትቷል፡፡
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ በቅርብ መረጃ እና ግንኙነት ቴክሎጂዎችን (ICT) ጨምሮ ስድስት አባይት ዘርፎች ዋና የትኩረት ማዕከል አድርጎ የያዘ አዲስ የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ ማውጣቷ ይታወሳል፡፡ ይህ መሪ ዕቅድ ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገና ለስኬቱም ያለው ወሳኝነት የማያጠራጥር መሆኑ ዘርፉን የዲጂታል ጥሬ ሀቅን (Data) በሚቆጣጠሩ ሕግጋቶች ለመደገፍ እንደሚገደድ ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከሚከፍተው አዲስ የዕድል በር እና አሁን ያለንበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሁኔታ ያለ ሕግ እና ፖሊሲ ብዙም የማያራምድ መሆኑ በረቂቁ ላይ ተቀምጧል፡፡
ጥናቱ ግለሰባዊ መረጃን ከሚጠብቁ ፖሊሲ እና ሕግጋት አስፈላጊነት ባሻገርም በሀገራችን በአሁኑ ሰዓት ያለውን የግለሰባዊ መረጃ አጠባበቅ ሁኔታ እንዲሁም የICT ፖሊሲ እና ሌሎች ከጉዳዩ ጋራ ግንኙነት ያላቸው ወሳኝ ሕግጋቶችንም የቃኘ ነው፡፡
ሙሉ ጥናቱን ቀጥሎ የተቀመጠውን pdf ፋይል በመክፈት ያገኙታል፡፡
=====================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጥናት ዳይሬክቶሬት “Data Privacy Policy for Ethiopia and the need for Compliance with International Standards” በሚል ርዕስ የፖሊሲ ጥናት አውጥቷል፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ የተደራጀና ሁሉን አለም አቀፍ ስታንዳርዶችን ያሟላ የመረጃ/ጥሬ ሀቅ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ላይ የተለያዩ አመክንዮዎችን በመንተራስ ምክረ ሀሳብ የሚያቀርብ ነው፡፡
ያደጉት ሀገራት የዛሬ 40 እና 50 ዓመታት ገደማ ግለሰባዊ መረጃን የሚጠብቁ ሕጎችን ሲተገብሩ መኖራቸውን ያወሳው ጥናቱ በአንፃሩ ሀገራችን ላይ አሁንም ድረስ ይህን ሁኔታ ባልተደራጁና በቂ ባልሆኑ ሕጎች ለመቆጣጠር እየዳከርን መሆኑን ይጠቁማል፡፡
የፖሊሲ ጥናቱ በኢትዮጵያ የመረጃ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ በሌሎች ሀገራት ደረጃ ካለው የፖሊሲ እና ህግጋት ጋራ አለመጣጠም በተለይም ሀገራችንን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ወይም ኢ-ኮሜርስ ስርዓቱን በሚፈለገው ልክ እንዳታሳድግ እና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ብሎም ሀገራት ከእኛ ጋራ እንዲሰሩ የማያስችል ሁኔታ እንደሚፈጥር የአውሮፓ ህብረት እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሕግጋትን በተግባራዊ ምሳሌነት አስደግፎ አትቷል፡፡
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ በቅርብ መረጃ እና ግንኙነት ቴክሎጂዎችን (ICT) ጨምሮ ስድስት አባይት ዘርፎች ዋና የትኩረት ማዕከል አድርጎ የያዘ አዲስ የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ ማውጣቷ ይታወሳል፡፡ ይህ መሪ ዕቅድ ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገና ለስኬቱም ያለው ወሳኝነት የማያጠራጥር መሆኑ ዘርፉን የዲጂታል ጥሬ ሀቅን (Data) በሚቆጣጠሩ ሕግጋቶች ለመደገፍ እንደሚገደድ ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከሚከፍተው አዲስ የዕድል በር እና አሁን ያለንበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሁኔታ ያለ ሕግ እና ፖሊሲ ብዙም የማያራምድ መሆኑ በረቂቁ ላይ ተቀምጧል፡፡
ጥናቱ ግለሰባዊ መረጃን ከሚጠብቁ ፖሊሲ እና ሕግጋት አስፈላጊነት ባሻገርም በሀገራችን በአሁኑ ሰዓት ያለውን የግለሰባዊ መረጃ አጠባበቅ ሁኔታ እንዲሁም የICT ፖሊሲ እና ሌሎች ከጉዳዩ ጋራ ግንኙነት ያላቸው ወሳኝ ሕግጋቶችንም የቃኘ ነው፡፡
ሙሉ ጥናቱን ቀጥሎ የተቀመጠውን pdf ፋይል በመክፈት ያገኙታል፡፡
ሀሰተኛ መረጃ እና የአዕምሮ ጫና
================
በአለማችን የማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የሀሰተኛ መረጃ መጠንና የዝውውር ፍጥነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ሀሰተኛ መረጃ መሰራጨት ከመጀመሩ በፊት አዘጋጆቹ በቅድሚያ ሰዎች መስማት የሚፈልጉትን ወቅታዊ እና ትኩረት ሳቢ የሆነውን ጉዳይ ይለያሉ፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው በጣም ቀላል ነው፤ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከመሰረታቸው መረጃን ከአንድ ጫፍ ወደ ሌላ ጫፍ በፍጥነት በማዘዋወር የታዎቁ በመሆናቸው በደቂቃዎች ውስጥ ሰፊ ተመልካች ያገኛል፡፡ በይዘት ደረጃ ይዘቱ ምንም ዓይነት ይሁን ወቅታዊና ሰዎች መስማት የሚፈልጉት ከሆነ ሀሰተኛው መረጃ ተመርቶ ይቀርባል፡፡
የደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ተመራማሪዎች በሰሩት ትንተና በ2016 የአሜሪካ ምርጫ ወቅት 20 በመቶ የሚሆኑ የትዊተር መረጃዎች ሀሰተኛ ነበሩ፡፡
በኢቫንስቶን ሰሜን ምዕራብ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ እድገት ተመራማሪ የሆነው ዴቪድ ራፕ ሰዎች በብዛት ወቅታዊ የፖለቲካ አቋማቸውን የሚደግፍ ማንኛውንም መረጃ ይቀበላሉ ሲል ልዩ ልዩ ምርምሮችን ዋቢ አድርጎ ይናገራል፡፡ ተመራማሪው በተጨማሪም አንድ ጽሁፍ ሀሰት እንደሆነ እያወቅን እንኳን እውነት እንዲሆን ካለን ፍላጎት የተነሳ እንቀበለዋለን ይላል፡፡ የዚህ አይነቱ የተሳሳተ መረጃ በልዩ ልዩ ውሳኔዎቻችን ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳረፉ አይቀርም፡፡
ብዛት ያላቸው ሀሰተኛ መረጃዎችን ባነበብን ቁጥር አዕምሯችን በዚሁ የተሞላ ይሆናል፡፡ በዚህ ረገድ የተለያዩ ሙከራዎችን ያደረጉት የተመራማሪዎች ቡድን አንድን ሀሰተኛ መረጃ በተደጋጋሚ የምንሰማው ከሆነ ለአዕምሯችን እውነት እየሆነ ይመጣል፡፡ ለምሳሌ "ዛፎች ከመኪና ይልቅ ለአየር ብክለት መንስኤ ናቸው" የሚል ሀሰተኛ መረጃን በተደጋጋሚ ብንሰማውና እኛ የምናውቃቸው እና የምንደግፋቸው ጥቂት ሰዎች ሀሳቡን ቢቀበሉት ሀሳቡን መርህ አድርገን ተፈጥሮን ከዛፎች እንታደግ ማለታችን የማይቀር ነው፡፡ ይህ ምሳሌ የሀሰተኛ መረጃን አደገኝነትና በአዕምሯችን ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በቀላሉ የሚያሳይ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪም ልቦለዶቸ ላይ የምናነባቸው መረጃዎችን እንደ እውነተኛ መረጃዎች በመውሰድ አቋም ልንይዝባቸው እንችላለን፡፡ ይህም ከነባራዊው እውነታ ይልቅ ለማስታዎስ ከልቦለድ ጽሁፍ ያገኘነው መረጃ ለአእምሯችን ስለሚቀል ነው፡፡
ምንጭ Science news magazine
================
በአለማችን የማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የሀሰተኛ መረጃ መጠንና የዝውውር ፍጥነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ሀሰተኛ መረጃ መሰራጨት ከመጀመሩ በፊት አዘጋጆቹ በቅድሚያ ሰዎች መስማት የሚፈልጉትን ወቅታዊ እና ትኩረት ሳቢ የሆነውን ጉዳይ ይለያሉ፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው በጣም ቀላል ነው፤ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከመሰረታቸው መረጃን ከአንድ ጫፍ ወደ ሌላ ጫፍ በፍጥነት በማዘዋወር የታዎቁ በመሆናቸው በደቂቃዎች ውስጥ ሰፊ ተመልካች ያገኛል፡፡ በይዘት ደረጃ ይዘቱ ምንም ዓይነት ይሁን ወቅታዊና ሰዎች መስማት የሚፈልጉት ከሆነ ሀሰተኛው መረጃ ተመርቶ ይቀርባል፡፡
የደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ተመራማሪዎች በሰሩት ትንተና በ2016 የአሜሪካ ምርጫ ወቅት 20 በመቶ የሚሆኑ የትዊተር መረጃዎች ሀሰተኛ ነበሩ፡፡
በኢቫንስቶን ሰሜን ምዕራብ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ እድገት ተመራማሪ የሆነው ዴቪድ ራፕ ሰዎች በብዛት ወቅታዊ የፖለቲካ አቋማቸውን የሚደግፍ ማንኛውንም መረጃ ይቀበላሉ ሲል ልዩ ልዩ ምርምሮችን ዋቢ አድርጎ ይናገራል፡፡ ተመራማሪው በተጨማሪም አንድ ጽሁፍ ሀሰት እንደሆነ እያወቅን እንኳን እውነት እንዲሆን ካለን ፍላጎት የተነሳ እንቀበለዋለን ይላል፡፡ የዚህ አይነቱ የተሳሳተ መረጃ በልዩ ልዩ ውሳኔዎቻችን ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳረፉ አይቀርም፡፡
ብዛት ያላቸው ሀሰተኛ መረጃዎችን ባነበብን ቁጥር አዕምሯችን በዚሁ የተሞላ ይሆናል፡፡ በዚህ ረገድ የተለያዩ ሙከራዎችን ያደረጉት የተመራማሪዎች ቡድን አንድን ሀሰተኛ መረጃ በተደጋጋሚ የምንሰማው ከሆነ ለአዕምሯችን እውነት እየሆነ ይመጣል፡፡ ለምሳሌ "ዛፎች ከመኪና ይልቅ ለአየር ብክለት መንስኤ ናቸው" የሚል ሀሰተኛ መረጃን በተደጋጋሚ ብንሰማውና እኛ የምናውቃቸው እና የምንደግፋቸው ጥቂት ሰዎች ሀሳቡን ቢቀበሉት ሀሳቡን መርህ አድርገን ተፈጥሮን ከዛፎች እንታደግ ማለታችን የማይቀር ነው፡፡ ይህ ምሳሌ የሀሰተኛ መረጃን አደገኝነትና በአዕምሯችን ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በቀላሉ የሚያሳይ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪም ልቦለዶቸ ላይ የምናነባቸው መረጃዎችን እንደ እውነተኛ መረጃዎች በመውሰድ አቋም ልንይዝባቸው እንችላለን፡፡ ይህም ከነባራዊው እውነታ ይልቅ ለማስታዎስ ከልቦለድ ጽሁፍ ያገኘነው መረጃ ለአእምሯችን ስለሚቀል ነው፡፡
ምንጭ Science news magazine
አስደናቂው የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ
*******************************
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ እንዲሁም ሰውነታችን የሚፈልጋቸውን ጠቃሚ ንጥረ ምግቦች የያዘ ነው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የደም ግፊትን ይቀንሳል፣ አጥንትን ያጠነክራል፣ የኮሊስትሮል መጠንን ይቀንሳል፣ ክብደት ለመቀነስ ያግዛል እንዲሁም ትኩሳትንና ልዩ ልዩ የጤና መታወክን በማጥፋት ጭንቀትን ይቀንሳል፡፡ ጭማቂው በተጨማሪም ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት፣ የሰውነት ሐይልን ለመጨመር፣ የኩላሊትን ጤና ለመጠበቅ፣ቆዳን ለመንከባከብ፣ ስርዓተ እንሽርስሪትን (የምግብ መፈጨትን) ለማስተካከልና የበሽታ መከላከል አቅምን ለማሳደግ ይረዳል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ምንድን ነው?
ይህ ጭማቂ በጣእሙ ከሚታወቀው እና ለገበታ ስኳር ማምረቻ ዋና ግባት ከሆነው የሸንኮራ አገዳ ተክል የሚሰራ ነው፡፡ የዚህ ተክል በሳይንሳዊ መጠሪያው ሳቻረም ኦፊሲናረም (Saccharum officinarum) በመባል ይታወቃል፡፡ ሳቻረም የሚለው የጥፍጥናውን መጠን የሚያሳይ ነው፡፡ ጭማቂው በሸንኮራ አገዳ ምርታቸው በሚታወቁት እንደ ብራዚል፣ ህንድ እና ታይላንድ ባሉ ሀገራት የታወቀ ነው፡፡ በአብዛኛው ጭማቂው የብረት መጭመቂያ በመጠቀም ከሸንኮራ አገዳ በፍጥነት የሚዘጋጅ ነው፡፡ በብዛት ከበረዶና ከሎሚ ካር ተቀላቅሎ በቀዝቃዛ መጠጥነት የሚቀርብ ሲሆን አንኳር ጨውና ዝንጅብልም እንደመቀመሚያነት ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ለሌሎች ምርቶችም ዋና ግብአት በመሆን ያገለግላል፡፡ ለምሳሌ ያክልም ሞላሰስ፣ ኢታኖልና ባዮፊውል ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ ይዘት
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከፍተኛ መጠን ያለው ፖታሺየም፣ ካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ብረት፣ ማንጋኔዝ፣ የተለያዩ አሚኖ አሲዶች፣ ዚንክ፣ ቲያሚን እና ሪቦፍላቢን የያዘ ነው፡፡ ከ224 ግራም ጭማቂ 180 ካሎሪ እና 30 ግራም ስኳር ማግኘት እንችላለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለሰውነታችን ጤንነት በጣም አስፈላጊ የሆኑ ውህዶችን በውስጡ የያዘ ነው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ጥቅሞች
ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ዋና ዋና ጥቅሞች መካከል የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡
የሰውነት ሀይልን ከፍ ደርጋል፡ በፋብሪካዎች ተቀምመው ከሚመጡ ምግብና መጠጦች በተለየ መልኩ ለሰውነታችን ከፍተኛ ሀይል የሚሰጥ የተመጣጠነ ስኳር ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ማግኘት እንችላለን፡፡
የቆዳችንን ጤንነት ይጠብቃል፡ ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ይዘቶች አንዱ አልፋ ሀይድሮ ኦክሳይድ አሲዶች መካከል የሆነው ግላይኮሊክ አሲድ ነው፡፡ ይህ አሲድ የቆዳ ላይ ሽፍታንና ቁስለትን በማስወገድ ጥራት ያለው ቆዳ እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ እንዲሁም አዘውትረን የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምንጠጣ ከሆነ በእድሜ ምክንያት የሚመጣን የቆዳ መሸብሸብ ያስወግዳል፡፡
ምቹ ለሆነ የእርግዝና ወቅት፡ በእርግዝና ወቅት የሚወሰድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ መፈጨትን በአግባቡ እንዲከናዎን በማድረግ ጥዋት ጥዋት የሚስተዋልን የሆድ ቁርጠት ያስወግዳል፡፡ እንዲሁም በእርግዝና ወቅት የሐይል እጥረት እንዳያጋጥም ያደርጋል፡፡ ተፈጥሯዊ የሆነ የበሽታ መከላከል አቅምን ከፍ ያደርጋል፡፡
መጥፎ የአፍ ጠረንን ያስወግዳል፡ የጥርስ መበስበስን ለማስወገድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ፍቱን መድሀኒት ነው፡፡ ሸንኮራ በተፈጥሮ ካልሺየምና ፎስፈረስ የተባሉ ማዕድናት ያለው በመሆኑ የጥርስ መበስበስ ችግርን በማስወገድ ለጥርሳችን ጥንካሬን ይሰጣል፡፡ በጭማቂው ውስጥ ያለው ከፍተኛ መጠን ማዕድን በእጥረት ምክንያት የሚመጣን የአፍ ጠረን ያስወግዳል፡፡
አጥንትን ያጠነክራል፡ ጭማቂው በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙ ካልሺየም፣ ብረት፣ ፖታሺየም፣ ማግኒዢየምና የማንጋኔዝ መጠንን በማመጣጠን አጥንታችንን ያጠነክራል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከመጠን በላይ የምንጠጣ ከሆነ ተጓዳኝ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የራስ ምታት፣ የሆድ ህመም፣ ትውኪያና የእንቅልፍ ማጣት ሊያስከትል ይችላል፡፡ ይህ እንዳይሆን በቀን ውስጥ አንድ ብርችጭቆ ብቻ መጠቀም ተገቢ ነው፡፡
ምንጭ፡ www.organicfacts www.indianrecips
*******************************
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ እንዲሁም ሰውነታችን የሚፈልጋቸውን ጠቃሚ ንጥረ ምግቦች የያዘ ነው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የደም ግፊትን ይቀንሳል፣ አጥንትን ያጠነክራል፣ የኮሊስትሮል መጠንን ይቀንሳል፣ ክብደት ለመቀነስ ያግዛል እንዲሁም ትኩሳትንና ልዩ ልዩ የጤና መታወክን በማጥፋት ጭንቀትን ይቀንሳል፡፡ ጭማቂው በተጨማሪም ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት፣ የሰውነት ሐይልን ለመጨመር፣ የኩላሊትን ጤና ለመጠበቅ፣ቆዳን ለመንከባከብ፣ ስርዓተ እንሽርስሪትን (የምግብ መፈጨትን) ለማስተካከልና የበሽታ መከላከል አቅምን ለማሳደግ ይረዳል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ምንድን ነው?
ይህ ጭማቂ በጣእሙ ከሚታወቀው እና ለገበታ ስኳር ማምረቻ ዋና ግባት ከሆነው የሸንኮራ አገዳ ተክል የሚሰራ ነው፡፡ የዚህ ተክል በሳይንሳዊ መጠሪያው ሳቻረም ኦፊሲናረም (Saccharum officinarum) በመባል ይታወቃል፡፡ ሳቻረም የሚለው የጥፍጥናውን መጠን የሚያሳይ ነው፡፡ ጭማቂው በሸንኮራ አገዳ ምርታቸው በሚታወቁት እንደ ብራዚል፣ ህንድ እና ታይላንድ ባሉ ሀገራት የታወቀ ነው፡፡ በአብዛኛው ጭማቂው የብረት መጭመቂያ በመጠቀም ከሸንኮራ አገዳ በፍጥነት የሚዘጋጅ ነው፡፡ በብዛት ከበረዶና ከሎሚ ካር ተቀላቅሎ በቀዝቃዛ መጠጥነት የሚቀርብ ሲሆን አንኳር ጨውና ዝንጅብልም እንደመቀመሚያነት ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ለሌሎች ምርቶችም ዋና ግብአት በመሆን ያገለግላል፡፡ ለምሳሌ ያክልም ሞላሰስ፣ ኢታኖልና ባዮፊውል ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ ይዘት
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከፍተኛ መጠን ያለው ፖታሺየም፣ ካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ብረት፣ ማንጋኔዝ፣ የተለያዩ አሚኖ አሲዶች፣ ዚንክ፣ ቲያሚን እና ሪቦፍላቢን የያዘ ነው፡፡ ከ224 ግራም ጭማቂ 180 ካሎሪ እና 30 ግራም ስኳር ማግኘት እንችላለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለሰውነታችን ጤንነት በጣም አስፈላጊ የሆኑ ውህዶችን በውስጡ የያዘ ነው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ጥቅሞች
ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ዋና ዋና ጥቅሞች መካከል የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡
የሰውነት ሀይልን ከፍ ደርጋል፡ በፋብሪካዎች ተቀምመው ከሚመጡ ምግብና መጠጦች በተለየ መልኩ ለሰውነታችን ከፍተኛ ሀይል የሚሰጥ የተመጣጠነ ስኳር ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ማግኘት እንችላለን፡፡
የቆዳችንን ጤንነት ይጠብቃል፡ ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ይዘቶች አንዱ አልፋ ሀይድሮ ኦክሳይድ አሲዶች መካከል የሆነው ግላይኮሊክ አሲድ ነው፡፡ ይህ አሲድ የቆዳ ላይ ሽፍታንና ቁስለትን በማስወገድ ጥራት ያለው ቆዳ እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ እንዲሁም አዘውትረን የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምንጠጣ ከሆነ በእድሜ ምክንያት የሚመጣን የቆዳ መሸብሸብ ያስወግዳል፡፡
ምቹ ለሆነ የእርግዝና ወቅት፡ በእርግዝና ወቅት የሚወሰድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ መፈጨትን በአግባቡ እንዲከናዎን በማድረግ ጥዋት ጥዋት የሚስተዋልን የሆድ ቁርጠት ያስወግዳል፡፡ እንዲሁም በእርግዝና ወቅት የሐይል እጥረት እንዳያጋጥም ያደርጋል፡፡ ተፈጥሯዊ የሆነ የበሽታ መከላከል አቅምን ከፍ ያደርጋል፡፡
መጥፎ የአፍ ጠረንን ያስወግዳል፡ የጥርስ መበስበስን ለማስወገድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ፍቱን መድሀኒት ነው፡፡ ሸንኮራ በተፈጥሮ ካልሺየምና ፎስፈረስ የተባሉ ማዕድናት ያለው በመሆኑ የጥርስ መበስበስ ችግርን በማስወገድ ለጥርሳችን ጥንካሬን ይሰጣል፡፡ በጭማቂው ውስጥ ያለው ከፍተኛ መጠን ማዕድን በእጥረት ምክንያት የሚመጣን የአፍ ጠረን ያስወግዳል፡፡
አጥንትን ያጠነክራል፡ ጭማቂው በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙ ካልሺየም፣ ብረት፣ ፖታሺየም፣ ማግኒዢየምና የማንጋኔዝ መጠንን በማመጣጠን አጥንታችንን ያጠነክራል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከመጠን በላይ የምንጠጣ ከሆነ ተጓዳኝ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የራስ ምታት፣ የሆድ ህመም፣ ትውኪያና የእንቅልፍ ማጣት ሊያስከትል ይችላል፡፡ ይህ እንዳይሆን በቀን ውስጥ አንድ ብርችጭቆ ብቻ መጠቀም ተገቢ ነው፡፡
ምንጭ፡ www.organicfacts www.indianrecips
አዲስ የሰውነት አካል ተገኘ
=============== በጉሮሮዋችን የላይኛው ክፍል ውስጥ የሳሊቫሪ እጢ ማግኘታቸውን ተመራማሪዎች አስታወቁ፡፡ ከዚህ ቀደም ኔይዞፋሪንክስ ተብሎ በሚጠራው ከአፍንጫችን ጀርባ ያለው ክፍል በጣም ጥቃቅን እና ተበታትነው የተቀመጡ ሳሊቫሪ እጢዎች ብቻ እንዳሉበት ይታሰብ ነበር፡፡ ሆኖም አዲስ የተገኘው እጢ በአማካኝ የ3.9 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያለው ሆኖ ተገኝቷል፡፡
እጢው ቶረስ ተባሪየስ በተባለው የአጥንቶች ማገናኛ (Cartilage) ውስጥ በመገኘቱ ምክንያትም የተባሪየስ ሳሊቫሪ እጢ የሚል ስያሜ ባገኙት ተመራማሪዎች ተሰጥቶታል፡፡ እጢው ምናልባትም ከአፍንጫና አፍ ጀርባ የሚገኘውን የጉሮሮዋችንን የላይኛውን ክፍል የሚያለሰልሱ እና የሚያረጥቡ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተመራማሪዎቹ የራዲዮቴራፒ እና ኦንኮሎጂ ጆርናል ላይ ባወጡት ጥናታዊ ፅሁፍ አስታውቀዋል፡፡
ታድያ ግኝቱ ድንገተኛ ግኝት ነበረ፡፡ በኔዘርላንድ የካንሰር ኢንስቲትዩት የሚገኙ ተመራማሪዎች የፕሮስቴት ካንሰርን ለማጥናት በማሰብ ሲቲ ስካን እና PSMA PET-CT ተብለው የሚታወቁትን የፖዚትሮን ኢሚሽን ቲሞግሮፊ (PET) ስካኖች በመጠቀም እየሰሩ ነበር፡፡ በPSMA PET-CT ስካን በሚደረግበት ጊዜ ሀኪሞች የራዲዮአክቲቭ መከታተያን ወደ ታማሚው ይከታሉ፡፡ ይህ መከታተያ በፕሮስቴት ካንሰር ህዋሶች ውስጥ ከፍ ብለው በሚገኙት የPSMA ፕሮቲኖች ላይ በጥሩ ሁኔታ መጣበቅ ይችላል፡፡ የህክምና ሙከራዎች እንዳሳዩት ከሆነ በPSMA PET-CT የሚደረግ ስካን ከተለምዶው ምስል የመውሰድ ስልት አንፃር የፕሮስቴትካንሰርንበተሻለ የማግኘት ብቃት አለው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በPSMA PET-CT ስካን ማድረግ PSMA ከፍ ብሎ የሚገኝበትን የሳሊቫሪ እጢ ሕብረ ሕዋስን ለይቶ በማግኘት ረገድም ጥሩ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
እስከ አሁን ድረስ ሶስት ትላልቅ የሳሊቫሪ እጢዎች በሰው ልጆች ውስጥ እንዳሉ ይታወቁ ነበሩ፤ ከምላስ በታች፣ ከመንገጭላ በታች እና ከመንገጭላ ጀርባ፡፡ ከነዚህ ባሻገር ግን በሺዎች የሚቆጠሩ እጅግ ጥቃቅን የሳሊቫሪ እጢዎች በአፍ እና ጉሮሮ የውስጥ ቆዳ (Mucosal) ሕብረ ሕዋሳት ውስጥ ተበትነው ይገኛሉ፡፡
ግኝታቸውን ለማረጋገጥ የጥናት ቡድኑ አባላት የ100 ታማሚዎችን የውስጥ ምስል የወሰዱ ሲሆን በውጤቱም ሁሉም አዲስ የታወቀው እጢ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ችለዋል፡፡ በተጨማሪም የኔይዞፋሪንክስ አካባቢን ከተለገሰ የሙት ሰው አካል ላይ ለይተው በማውጣት ምልከታ ካደረጉበት በኋላ አዲስ የተገኘው ክፍል ፈሳሽን ወደ ኔይዞፋሪንክስ በሚያደርሱ የሚኮሳል እጢ ሕብረ ሕዋሳት እና ማስተላለፊያዎች የተሞላ መሆኑን ማወቅ ችለዋል፡፡
ታድያ አዲሱ ግኝት ለካንሰር ህክምና በጎ አስተዋፅዖ ሊኖረው እንደሚችል ተገልጿል፡፡ ካንሰርን ለማከም በጭንቅላታች እና አንገታችን ላይ ጨረርን የሚጠቀሙ ሀኪሞች የሳሊቫሪ እጢዎችን በጨረሩ ላለመንካት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ለዚህም የነዚህ አካላት በጨረር መጎዳት የህይወት ዘይቤያችን ላይ መስተጓጎልን ሊፈጥር መቻሉ በምክንያትነት ይቀመጣል፡፡ ለምሳሌ ለመመገብ፣ ለመዋጥ እና ለማውራት ልንቸገር እንችላለን፡፡ ሆኖም ከዚህ በፊት ማንም ስለ ተባሪየስ ሳሊቫሪ እጢዎች በቦታው መኖር ስለማያውቅ እነርሱን ከጨረሩ ለመጠበቅ ጥረት የሚያደርግ አልነበረም፡፡
ተመራማሪዎቹ በግሮኒንገን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ ህክምናቸውን የተከታተሉ 700 የካንሰር ታማሚዎችን መዝገብ በመመልከት አዲስ በተገኘው እጢ አካበቢ ላይ የሚያርፈው ጨረር በበዛ ቁጥር ከህክምናው የሚገኘው የጎንዮሽ ጉዳትም ማሻቀቡን ለመረዳት ችለዋል፡፡ አዲሱ ግኝትም ይህን በማሻሻል ታማሚዎች ከካንሰር ህክምናቸው በኋላ የሚደርስባቸው የጎንዮሽ ጉዳት ያነሰ እንዲሆን ያስችላል ሲሉ የጥናት ቡድኑ አባል ያስረዳሉ፡፡
ምንጭ፡ Live Science
=============== በጉሮሮዋችን የላይኛው ክፍል ውስጥ የሳሊቫሪ እጢ ማግኘታቸውን ተመራማሪዎች አስታወቁ፡፡ ከዚህ ቀደም ኔይዞፋሪንክስ ተብሎ በሚጠራው ከአፍንጫችን ጀርባ ያለው ክፍል በጣም ጥቃቅን እና ተበታትነው የተቀመጡ ሳሊቫሪ እጢዎች ብቻ እንዳሉበት ይታሰብ ነበር፡፡ ሆኖም አዲስ የተገኘው እጢ በአማካኝ የ3.9 ሴ.ሜ ርዝማኔ ያለው ሆኖ ተገኝቷል፡፡
እጢው ቶረስ ተባሪየስ በተባለው የአጥንቶች ማገናኛ (Cartilage) ውስጥ በመገኘቱ ምክንያትም የተባሪየስ ሳሊቫሪ እጢ የሚል ስያሜ ባገኙት ተመራማሪዎች ተሰጥቶታል፡፡ እጢው ምናልባትም ከአፍንጫና አፍ ጀርባ የሚገኘውን የጉሮሮዋችንን የላይኛውን ክፍል የሚያለሰልሱ እና የሚያረጥቡ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተመራማሪዎቹ የራዲዮቴራፒ እና ኦንኮሎጂ ጆርናል ላይ ባወጡት ጥናታዊ ፅሁፍ አስታውቀዋል፡፡
ታድያ ግኝቱ ድንገተኛ ግኝት ነበረ፡፡ በኔዘርላንድ የካንሰር ኢንስቲትዩት የሚገኙ ተመራማሪዎች የፕሮስቴት ካንሰርን ለማጥናት በማሰብ ሲቲ ስካን እና PSMA PET-CT ተብለው የሚታወቁትን የፖዚትሮን ኢሚሽን ቲሞግሮፊ (PET) ስካኖች በመጠቀም እየሰሩ ነበር፡፡ በPSMA PET-CT ስካን በሚደረግበት ጊዜ ሀኪሞች የራዲዮአክቲቭ መከታተያን ወደ ታማሚው ይከታሉ፡፡ ይህ መከታተያ በፕሮስቴት ካንሰር ህዋሶች ውስጥ ከፍ ብለው በሚገኙት የPSMA ፕሮቲኖች ላይ በጥሩ ሁኔታ መጣበቅ ይችላል፡፡ የህክምና ሙከራዎች እንዳሳዩት ከሆነ በPSMA PET-CT የሚደረግ ስካን ከተለምዶው ምስል የመውሰድ ስልት አንፃር የፕሮስቴትካንሰርንበተሻለ የማግኘት ብቃት አለው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በPSMA PET-CT ስካን ማድረግ PSMA ከፍ ብሎ የሚገኝበትን የሳሊቫሪ እጢ ሕብረ ሕዋስን ለይቶ በማግኘት ረገድም ጥሩ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
እስከ አሁን ድረስ ሶስት ትላልቅ የሳሊቫሪ እጢዎች በሰው ልጆች ውስጥ እንዳሉ ይታወቁ ነበሩ፤ ከምላስ በታች፣ ከመንገጭላ በታች እና ከመንገጭላ ጀርባ፡፡ ከነዚህ ባሻገር ግን በሺዎች የሚቆጠሩ እጅግ ጥቃቅን የሳሊቫሪ እጢዎች በአፍ እና ጉሮሮ የውስጥ ቆዳ (Mucosal) ሕብረ ሕዋሳት ውስጥ ተበትነው ይገኛሉ፡፡
ግኝታቸውን ለማረጋገጥ የጥናት ቡድኑ አባላት የ100 ታማሚዎችን የውስጥ ምስል የወሰዱ ሲሆን በውጤቱም ሁሉም አዲስ የታወቀው እጢ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ችለዋል፡፡ በተጨማሪም የኔይዞፋሪንክስ አካባቢን ከተለገሰ የሙት ሰው አካል ላይ ለይተው በማውጣት ምልከታ ካደረጉበት በኋላ አዲስ የተገኘው ክፍል ፈሳሽን ወደ ኔይዞፋሪንክስ በሚያደርሱ የሚኮሳል እጢ ሕብረ ሕዋሳት እና ማስተላለፊያዎች የተሞላ መሆኑን ማወቅ ችለዋል፡፡
ታድያ አዲሱ ግኝት ለካንሰር ህክምና በጎ አስተዋፅዖ ሊኖረው እንደሚችል ተገልጿል፡፡ ካንሰርን ለማከም በጭንቅላታች እና አንገታችን ላይ ጨረርን የሚጠቀሙ ሀኪሞች የሳሊቫሪ እጢዎችን በጨረሩ ላለመንካት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ለዚህም የነዚህ አካላት በጨረር መጎዳት የህይወት ዘይቤያችን ላይ መስተጓጎልን ሊፈጥር መቻሉ በምክንያትነት ይቀመጣል፡፡ ለምሳሌ ለመመገብ፣ ለመዋጥ እና ለማውራት ልንቸገር እንችላለን፡፡ ሆኖም ከዚህ በፊት ማንም ስለ ተባሪየስ ሳሊቫሪ እጢዎች በቦታው መኖር ስለማያውቅ እነርሱን ከጨረሩ ለመጠበቅ ጥረት የሚያደርግ አልነበረም፡፡
ተመራማሪዎቹ በግሮኒንገን ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ ህክምናቸውን የተከታተሉ 700 የካንሰር ታማሚዎችን መዝገብ በመመልከት አዲስ በተገኘው እጢ አካበቢ ላይ የሚያርፈው ጨረር በበዛ ቁጥር ከህክምናው የሚገኘው የጎንዮሽ ጉዳትም ማሻቀቡን ለመረዳት ችለዋል፡፡ አዲሱ ግኝትም ይህን በማሻሻል ታማሚዎች ከካንሰር ህክምናቸው በኋላ የሚደርስባቸው የጎንዮሽ ጉዳት ያነሰ እንዲሆን ያስችላል ሲሉ የጥናት ቡድኑ አባል ያስረዳሉ፡፡
ምንጭ፡ Live Science
ሌሎች የፕላስቲክ አማራጮች ተፈጥሮን ለመታደግ
-------------------------------
በዓለማችን ያሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች አንድ ጊዜ ጥቅም ላይ ውለው የሚጣሉ ፕላስቲኮችን ለማስወገድ እና ተያይዘው የሚመጡ የአካባቢ ብክለት ችግሮችን ለማስቀረት የረዥም ጊዜ እቅዶችን ቀርፀው እንደሚንቀሳቀሱ ይታወቃል፡፡ ኒውላይት ቴክኖሎጂ ኩባንያ ይህን መርህ በሚገባ ከሚከተሉ ድርጅቶች መካከል አንዱ ሲሆን ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው ፕላስቲከ መሰል የባዮዲግሬደብል ቁስ ደግሞ ከብዙዎች ተቀባይነት ያስገኘለት ነው፡፡
በካሊፎርኒያ መቀመጫወን ያደረገው ኒውላይት ቴክኖሎጂ ኩባንያ ከአስር አመት በላይ ምርምር ሲያደርግብት የቆየው (AirCarbon) የተሰኘው ይህ ቁስ የፕላስቲክ መልክ፣ ይዘት እና ግልጋሎት ኖሮት የተሰራ ቁስ ቢሆንም አጠቃላይ ስሪቱ ግን በተለያዩ ደቂቅ አካለትና ባካቴሪያዎች መበስበስ እንዲችል የተደረገ እና ምንም አይነት ብክለት እንዳይኖረው የተቀመረ ነው፡፡
ኩባንያው ይህን መሰል ፈጠራ ለማከናወን እንደመነሻ የተጠቀመው በውቅያኖስ ውስጥ መኖሪያቸውን ባደረጉ እና ለአለማችን የአየር ንብረት ለውጥ ዋና ምክንያት የሆኑትን የሚቴን እና ካርቦን ዳይኦክሳድ ጋዛችን በሚመገቡ ደቂቅ አካላት አማካኝነት ነው፡፡ አነዚህ አካላት የሚቴን እና ካርቦን ዳይኦክሳድ ጋዞችን ወደተፈጥሮ ፖሊመር በመቀየር ልክ እንደፕላስቲክ የሚተጣጠፉ እና የሚቀረፁ ቁሶችን ማውጣት የቻሉ ሲሆን ተመራማሪዎችም ከዚህ የተፈጥሮ ሂደት በመነሳት ፕላስቲኮችን በዚህ አምሳያ ለመስራት ሞክረዋል፡፡
የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ማርክ ሀርማ በምርምሩ ዙሪያ እንደተናገሩትም በዚህ ሂደት ለወጤት የበቃውን ፈጠራ (AirCarbon) ብለን የሰየምንበት ምክንያት አየርም ይሁን ካርቦን በውሃ ውስጥ በሚሆኑበት ጊዜ ሊሟሙ እና ወደፈሳሽነት ሊቀየሩ መቻላቸውን ለማሳየት ነው ብለዋል፡፡ የምርምር ውጤቱ የከባቢ አየር ጋዞችን እንደግብዓት መጠቀም ዋና አላማ አድርጎ የተነሳ በመሆኑ የተፈጥሮ ስነምህዳርን በተለያየ መልኩ የሚታደግ ይሆናል፡፡
ኒውላይት ለዚህ አስገራሚ የፈጠራ ስራው በእንግሊዝ መቀመጫቸውን ባደረጉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣነት ሙገሳን ያስገኘለት ሲሆን፤ የአሜሪካ ምግብና መድሃኒት አስተዳዳር (FDA) እና የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ (EPA) ከተፈጥሮ ጋር ወዳጀነት ለመሰረተው አስገራሚ ፈጠራ የእውቅና ሽልማት አበርክቷል፡፡
ምንጭ፡ CNN Business
-------------------------------
በዓለማችን ያሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች አንድ ጊዜ ጥቅም ላይ ውለው የሚጣሉ ፕላስቲኮችን ለማስወገድ እና ተያይዘው የሚመጡ የአካባቢ ብክለት ችግሮችን ለማስቀረት የረዥም ጊዜ እቅዶችን ቀርፀው እንደሚንቀሳቀሱ ይታወቃል፡፡ ኒውላይት ቴክኖሎጂ ኩባንያ ይህን መርህ በሚገባ ከሚከተሉ ድርጅቶች መካከል አንዱ ሲሆን ከሰሞኑ ይፋ ያደረገው ፕላስቲከ መሰል የባዮዲግሬደብል ቁስ ደግሞ ከብዙዎች ተቀባይነት ያስገኘለት ነው፡፡
በካሊፎርኒያ መቀመጫወን ያደረገው ኒውላይት ቴክኖሎጂ ኩባንያ ከአስር አመት በላይ ምርምር ሲያደርግብት የቆየው (AirCarbon) የተሰኘው ይህ ቁስ የፕላስቲክ መልክ፣ ይዘት እና ግልጋሎት ኖሮት የተሰራ ቁስ ቢሆንም አጠቃላይ ስሪቱ ግን በተለያዩ ደቂቅ አካለትና ባካቴሪያዎች መበስበስ እንዲችል የተደረገ እና ምንም አይነት ብክለት እንዳይኖረው የተቀመረ ነው፡፡
ኩባንያው ይህን መሰል ፈጠራ ለማከናወን እንደመነሻ የተጠቀመው በውቅያኖስ ውስጥ መኖሪያቸውን ባደረጉ እና ለአለማችን የአየር ንብረት ለውጥ ዋና ምክንያት የሆኑትን የሚቴን እና ካርቦን ዳይኦክሳድ ጋዛችን በሚመገቡ ደቂቅ አካላት አማካኝነት ነው፡፡ አነዚህ አካላት የሚቴን እና ካርቦን ዳይኦክሳድ ጋዞችን ወደተፈጥሮ ፖሊመር በመቀየር ልክ እንደፕላስቲክ የሚተጣጠፉ እና የሚቀረፁ ቁሶችን ማውጣት የቻሉ ሲሆን ተመራማሪዎችም ከዚህ የተፈጥሮ ሂደት በመነሳት ፕላስቲኮችን በዚህ አምሳያ ለመስራት ሞክረዋል፡፡
የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ማርክ ሀርማ በምርምሩ ዙሪያ እንደተናገሩትም በዚህ ሂደት ለወጤት የበቃውን ፈጠራ (AirCarbon) ብለን የሰየምንበት ምክንያት አየርም ይሁን ካርቦን በውሃ ውስጥ በሚሆኑበት ጊዜ ሊሟሙ እና ወደፈሳሽነት ሊቀየሩ መቻላቸውን ለማሳየት ነው ብለዋል፡፡ የምርምር ውጤቱ የከባቢ አየር ጋዞችን እንደግብዓት መጠቀም ዋና አላማ አድርጎ የተነሳ በመሆኑ የተፈጥሮ ስነምህዳርን በተለያየ መልኩ የሚታደግ ይሆናል፡፡
ኒውላይት ለዚህ አስገራሚ የፈጠራ ስራው በእንግሊዝ መቀመጫቸውን ባደረጉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣነት ሙገሳን ያስገኘለት ሲሆን፤ የአሜሪካ ምግብና መድሃኒት አስተዳዳር (FDA) እና የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ (EPA) ከተፈጥሮ ጋር ወዳጀነት ለመሰረተው አስገራሚ ፈጠራ የእውቅና ሽልማት አበርክቷል፡፡
ምንጭ፡ CNN Business
የፀሐይ ኃይል ኤሌክትሪክን በረከሰ ዋጋ በማቅረብ ታሪካዊ ሆኗል
--------------------------------------
ዓለም አቀፉ የኃይል ኤጀንሲ (IEA) በየዓመቱ በሚያወጣው ሪፖርት አባል ሃገራት በኢነርጂ አጠቃቀማቸው እና አካባቢ ጥበቃ ላይ ሊኖራቸው ስለሚችለው አተገባበር ሰፊ መረጃዎችን እና ቅድመ ትንታኔዎችን የሚያቀርብ ነው፡፡ ድርጅቱ በዚህ አመት ሪፖርቱ ከፀሃይ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል ቀድሞ ሲታሰብ ከነበረው አንጻር የዋጋ ምጣኔ በእጅጉ ያነሰ እና በቀላሉ ሰዎች ጋር በመድረስ በቀዳሚነት የሚቀመጥ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ከፀሃይ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል በአለማችን እስካሁን ከታዩት የሃይል አማራጮች ቀዳሚነቱን የያዘበት ዋና ምክንያት በታዳሽ ሃይል ኢንቨስትመንት ዘሪያ የሚኖረውን ከፍተኛ ስጋት የሚቀንሱ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በመበልፀጋቸው እና ወሳኝ የመንግስታት ፖሊሲዎች በመኖራቸው መሆኑን ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
በኤሌክትሪክ ሃይል ገበያው የፀሃይ የሃይል ምንጭነት ያለጥርጥር መንገሱን የሚናገሩት የድርጅቱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክትር ዶ/ር ፋቲ ቢሮል ከዚሀ የፖሊሲ መነሻ ተነስተን ከ2022 በኋላ የሚኖረንን የኤሌክትሪክ ሃይል አጠቃቀም መለካት እና መተንተን እንችላለን ይላሉ፡፡ የዓለም አቀፉ የኃይል ኤጀንሲ የ2020 ሪፖርት እንዳስቀመጠው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአለማችን ላይ መከሰት ኤሌክትሪክ ሃይል ፍላጎትን ለመተንበይ አስቸጋሪ ቢያደርገውም ከተለያዩ ሴናሪዮች በመነሳት በየዓመቱ ሊኖር የሚችለውን ውጤቱ መገመት እንደሚቻል የድርጅቱ ሪፖርት ያሳያል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ መጠነ ሰፊ የፀሃይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የኤሌክትሪክ ሃይልን በረከሰ ዋጋ በማቅረብ በኩል ትልቅ ለውጥ ማምጣታቸውን የሚያወሳው ሪፖርቱ በተለይም ባለፉት 10 አመታት አስገራሚ መሻሻሎች እንደነበሩ ያስቀምጣል፡፡ ለአብነት በአውሮፓውያኑ 2010 አንድ ኪሎዋት በሰዓት የኤሌክትሪክ ሃይል ለማቅረብ 38 ሳንቲም ያስወጣ የነበረ ሲሆን በ2019 ይህ ዋጋ በእጅጉ ቀንሶ 6.8 ሳንቲም ሆኗል፡፡
ይህ የዋጋ ምጣኔ በቀጣዮቹ አስር አመታት የበለጠ ተሻሽሎ የአለማችን የኤሌክትሪክ ሃይል ፍላጎት 80 በመቶው በታዳሽ የሀይል አማራጮች እንዲያዝ የሚያነሳሳ ቢሆንም አሁን ያለው አጠቃላይ ከታዳሽ ሃይል የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ40 % የሚሻገር ባለመሆኑ በቀጣዮቹ አመታት የሚሰሩት ስራዎች እጅግ ወሳኝ እንደሚያደርጋቸው ድርጅቱ በሪፖርቱ ያነሳል፡፡
በዚህ የሃይል አማራጭ መዋቅር ውስጥ የሃይድሮ ፓወር ፕሮጀክቶች ትልልቆቹ የሃይል ማመንጫ መንገዶች ቢሆኑም፤ ከፀሃይ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል አለማችን እስከዛሬ አይታ ከምታውቀው የሃይል አማራጮች በተደራሽነቱም ይሁን በኢኮኖሚ ጥቅሙ ወደር የማይገኝለት መሆኑ የ2020 የIEA ሪፖርት በሚገባ ያረጋግጣል፡፡ ምንጭ Big Think
--------------------------------------
ዓለም አቀፉ የኃይል ኤጀንሲ (IEA) በየዓመቱ በሚያወጣው ሪፖርት አባል ሃገራት በኢነርጂ አጠቃቀማቸው እና አካባቢ ጥበቃ ላይ ሊኖራቸው ስለሚችለው አተገባበር ሰፊ መረጃዎችን እና ቅድመ ትንታኔዎችን የሚያቀርብ ነው፡፡ ድርጅቱ በዚህ አመት ሪፖርቱ ከፀሃይ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል ቀድሞ ሲታሰብ ከነበረው አንጻር የዋጋ ምጣኔ በእጅጉ ያነሰ እና በቀላሉ ሰዎች ጋር በመድረስ በቀዳሚነት የሚቀመጥ መሆኑን አስታውቋል፡፡
ከፀሃይ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል በአለማችን እስካሁን ከታዩት የሃይል አማራጮች ቀዳሚነቱን የያዘበት ዋና ምክንያት በታዳሽ ሃይል ኢንቨስትመንት ዘሪያ የሚኖረውን ከፍተኛ ስጋት የሚቀንሱ የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በመበልፀጋቸው እና ወሳኝ የመንግስታት ፖሊሲዎች በመኖራቸው መሆኑን ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
በኤሌክትሪክ ሃይል ገበያው የፀሃይ የሃይል ምንጭነት ያለጥርጥር መንገሱን የሚናገሩት የድርጅቱ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክትር ዶ/ር ፋቲ ቢሮል ከዚሀ የፖሊሲ መነሻ ተነስተን ከ2022 በኋላ የሚኖረንን የኤሌክትሪክ ሃይል አጠቃቀም መለካት እና መተንተን እንችላለን ይላሉ፡፡ የዓለም አቀፉ የኃይል ኤጀንሲ የ2020 ሪፖርት እንዳስቀመጠው የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በአለማችን ላይ መከሰት ኤሌክትሪክ ሃይል ፍላጎትን ለመተንበይ አስቸጋሪ ቢያደርገውም ከተለያዩ ሴናሪዮች በመነሳት በየዓመቱ ሊኖር የሚችለውን ውጤቱ መገመት እንደሚቻል የድርጅቱ ሪፖርት ያሳያል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ መጠነ ሰፊ የፀሃይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የኤሌክትሪክ ሃይልን በረከሰ ዋጋ በማቅረብ በኩል ትልቅ ለውጥ ማምጣታቸውን የሚያወሳው ሪፖርቱ በተለይም ባለፉት 10 አመታት አስገራሚ መሻሻሎች እንደነበሩ ያስቀምጣል፡፡ ለአብነት በአውሮፓውያኑ 2010 አንድ ኪሎዋት በሰዓት የኤሌክትሪክ ሃይል ለማቅረብ 38 ሳንቲም ያስወጣ የነበረ ሲሆን በ2019 ይህ ዋጋ በእጅጉ ቀንሶ 6.8 ሳንቲም ሆኗል፡፡
ይህ የዋጋ ምጣኔ በቀጣዮቹ አስር አመታት የበለጠ ተሻሽሎ የአለማችን የኤሌክትሪክ ሃይል ፍላጎት 80 በመቶው በታዳሽ የሀይል አማራጮች እንዲያዝ የሚያነሳሳ ቢሆንም አሁን ያለው አጠቃላይ ከታዳሽ ሃይል የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ40 % የሚሻገር ባለመሆኑ በቀጣዮቹ አመታት የሚሰሩት ስራዎች እጅግ ወሳኝ እንደሚያደርጋቸው ድርጅቱ በሪፖርቱ ያነሳል፡፡
በዚህ የሃይል አማራጭ መዋቅር ውስጥ የሃይድሮ ፓወር ፕሮጀክቶች ትልልቆቹ የሃይል ማመንጫ መንገዶች ቢሆኑም፤ ከፀሃይ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል አለማችን እስከዛሬ አይታ ከምታውቀው የሃይል አማራጮች በተደራሽነቱም ይሁን በኢኮኖሚ ጥቅሙ ወደር የማይገኝለት መሆኑ የ2020 የIEA ሪፖርት በሚገባ ያረጋግጣል፡፡ ምንጭ Big Think
ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ፤ የኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ ሳይንቲስት
አለማችን በበርካታ ውስብስብ ችግሮች የተሞላች ነች፡፡ ይህንን ውስብስብ ችግር እራሱ የሰው ልጅም ሲፈጥረውና ማጣፍያው አጥሮት ሲቸገርም አስተውለናል፡፡ በተፈጥሮም ይሁን በሰው ሰራሽ ምክንያት ታዲያ ለተፈጠሩ ችግሮች የሰው ልጅ ጥልቅ አዕምሮ በተለያዩ ወቀቶች መፍትሄዎችን ለአለም ሲያበረክት ቆይቷል፡፡ በረዥሙ የሰው ልጅ ህይወትም አለም ላይ የተከሰቱ ችግሮችን በጥልቅ ምርምራቸው እና አሳቢነታቸው መፍትሄ የወለዱ እንቁ ባለሙያዎች በየሃገሩ ተፈጥረዋል፡፡ ታዲያ አትዮጵያችን ለአለም ካበረከተቻቸው ውድ ምሁራኖች መካከል ብዙዎችን መጥቀስ ብንችልም ለዛሬ ግን ስለፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ በጥቂቱ ልናስታውቹ ወደናል፡፡
መስከረም 7.1928 ዓ/ም በጅጅጋ ወረዳ ከእናታቸው ወ/ሮ አየለች ለማ እና ከአባታቸው በቀለ ወልደየስ ተወለዱ የያኔው ህጻን አክሊሉ፡፡ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ያኔው ቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ ዩኒቨርሲቲ ያሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመግባት ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በ1960 ከዊንስከንሲን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ወስደዋል፡፡ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በሚያጠኑበት ወቅት በብላሀርዝያ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ነበራቸው፡፡ እኚህ ወጣት ተመራማሪ በየቀኑ ሴቶች በወንዝ ዳር ልብስ በሚያጥቡበት ወቅት በትኩረት ይከታተሉ ነበር፡፡ ሴቶቹ ልብሱን እንዶድ በሚባል ተክል ነበር የሚያጥቡት፤ በወቅቱ እንዶድ በርካታ የብላሀርዝያ ትሎችን መግደል የሚችል ተክል በመሆኑ ፕሮፌሰሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰተውት ነበር፡፡ በ1966ም በቤተ ሙከራ ውስጥ ከተሞከረ በኋላ ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ በሳይንስ ፎረም ላይ አቀረቡት፡፡ በወቅቱ በአፍሪካ ውስጥ የሺስቶስሚያሲስ በሽታ ይከሰት ስለነበር እና የፕሮፌሰሩ ግኝት በዝቅተኛ ዋጋ በሽታ አምጪ የሆነውን ትል የሚገድል በመሆኑ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት ነበር፡፡
በዚያን ወቅት ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ በሜዲካል ኮሌጅ የፓራሳይቶሎጂ ፕሮግራም ጀምረው ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ታሪካ በሳይንስ ፋካሊቲ ውስጥ የመጀመሪያው ዲን ሆነውም አገልግለዋል፡፡ በዚያን ወቅት ፕሮፌሰር አክሊሉ ወደ ስታምፎርድ ዩኒቨርሲቲ በማቅናት ትኩሳትና ሌሎች የጥገኛ በሽታ አምጪ ህዋስያን ለመዋጋት የሚያስችል የእንዶድን ኬሚካላዊ ባህሪያቶች ላይ ጥናት ለማድረግ ለሁለት አመት ቆይተዋል፡፡ በዚህ አጋጣሚ መግለጽ የሚያስፈልገው ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ የእንዶድ ተክል ቀንድ አውጣውን ለመግደል ስለሚችል እና በሂደትም በሽታውን ለመቆጣጠር እንደሚረዳ ስለደረሱበት ዕውቅና እንዲሰጣቸው ተደርጓል።ቴክ-ሳይንስ 92
ስለ እንዶድ ጥቅምና የውኃ ትላትል ገዳይነት በማግኘታቸው የዩናይትድ ስቴትስ የፈጠራ ባለቤትነት ወይም ፓተንቶች ኣግኝተዋል። እንዶድ ሳይንሳዊ መጠሪያ ስሙ (Phy¬tolacca dodecandra) ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ በወንዝ ዳርቻዎች ይበቅላል፡፡ በኢትዮጵያ ገጠራማ አካባቢዎች ልክ እንደሳሙና በሰፊው ለልብስ ማጠቢያነት የሚያገለግለው እንዶድ፣ ከተክሉ የሚገኘው ጭማቂ ወይም ፍሬው ደግሞ ለብላሀርዝያ በሽታ የሚዳርገውን ተውሳክ የሚያስጠልለውን ቀንድ አውጣ ስለሚገድል ለመድኃኒትነት ያገለግላል፡፡ ከተክሉ የሚገኝ ጭማቂ አልቅትንም ስለሚገድል በውኃ ውስጥ የአልቅቶችን ቁጥር ለመቆጣጠር ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ ተክሉ ለከብቶች የማይስማማ በመሆኑ እንስሳት ለምግብነት አይመርጡትም፡፡
ሺስቶሶሚያሲስ (ብላሀርዝያ ወይም ካታያማ ትኩሳት) በመባል ይታወቃል፡፡ ፕሮፌሰር አክሊሉ ስለዚህ በሽታ ባደረጉት ሰፊ ምርምር የመተላለፊያውን መንገድ፣ ምልክቶቹን እና ህክምናውን ከሌሎች ጉዳዮች ጋር አብራርተው ሊያሳትሙ ችለዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር አክሊሉ ጥናት በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትል በሆነው የሺስቶሶማ ህዋስ ዓይነት ሲሆን የሽንት መተላለፊያን ወይም አንጀትን ሊያጠቃ ይችላል፡፡ የሕመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል፡፡ ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትልበት ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ደግሞ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል፡፡
በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ በሚገኙበት ውኃ ስፍራ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው፡፡ እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በደሃ አገራት በሚገኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ ልጆቹ በተበከለ ውኃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪም በእለት ተእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለ ውኃ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠላባቸው የህበረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡
ህክምናውን በተመለከተ ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች ሽንት ወይም ሰገራ ላይ መኖራቸውን በመመርመር ሲሆን፤ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ በሽታው መኖሩን ማረጋገጥም ይቻላል፡፡ የብላሀርዝያን በሽታ ለመከላከል ንፁህ የውኃ አቅርቦትን ማሻሻል እና የቀንድ ኣውጣ ቁጥርን መቀነስ ዋነኞቹ ቢሆንም በሽታው በተስፋፋበት አካባቢ በአንድ ጊዜ ሁሉንም ሰዎች ፕራዚኩዋንትል በተባለ መድኃኒት በየዓመቱ ማከም በሽታውን ለማጥፋት ሌላኛው መንገድ ነው፡፡ ይህ እርምጃ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስና የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ያስችላል፡ ፡ ፕራዚኩዋንትል በበሽታው የተጠቁትን ለማከም በ(World Health Organization) የሚመከር የሕክምና ዘዴ ነው፡፡ የበሽታው መስፋፊያ ዘዴ የትሉ እንቁላሎች በሽንትና ሰገራ አማካኘነት ከሰው አካል ወጥተው ቀንድ ኣውጣ ውስጥ በመግባት የሚባዙ በመሆኑ በሽታውን ለመከላከል ሕዝቡ ሽንቱንና ሰገራውን ከሚጠጣው ውኃ እንዲያርቅ ማስተማር ያስፈልጋል፤ እንዲሁም የሚጠቀመው የኩሬ ወይም የወንዝ ውኃ ከሆነ ውኃውን ማከም እንደሚገባው ማስተማር ያስፈልጋል።
ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ የሚያጠቃ ሲሆን፤ ከ12,000 እስከ 200,000 የሚሆነ ሕዝብ በዓመት ውስጥ በዚህ በሽታ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በአፍሪካ፣ በእስያና ደቡም አሜሪካ ነው፡፡ እንዲሁም ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ፣ ከ70 በላይ አገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀጥሎ በሁለተኛነት የሚቀመጥና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው፡ ፡
እ.ኤ.አ. በ1993 እስከ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ በነበረው ጊዜያቸው በጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ትስስር በመፍጠር ለአገሬው ተወላጅ የአቅም ግንባታ ያደረጉት ፕሮፌሰር አክሊሉ፤ የሳይንሳዊ ምርምሮችን በማስተዋወቅም ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል፡ ፡ ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ ሶስት ፓተንቶችን፤ አምስት መጽሐፍቶችን እና 60 ሳይንሳዊ የጥናት ጽሁፎችን በስማቸው አስመዝግበዋል፡፡ በ1969 በንጉስ ቀዳማዊ ሓይለ ስላሴ የወርቅ ሜዳሊያ እና ሌሎች በርካታ ሽልማቶችን ያገኙት እኝህ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ምሁር ከብዙ ትሩፋቶቻቸው በኋላ ይህችን አለም በ62 አመታቸው ተሰናብተዋል፡፡
ከቴክ ሳይንስ ቅፅ 17 የተወሰደ
አለማችን በበርካታ ውስብስብ ችግሮች የተሞላች ነች፡፡ ይህንን ውስብስብ ችግር እራሱ የሰው ልጅም ሲፈጥረውና ማጣፍያው አጥሮት ሲቸገርም አስተውለናል፡፡ በተፈጥሮም ይሁን በሰው ሰራሽ ምክንያት ታዲያ ለተፈጠሩ ችግሮች የሰው ልጅ ጥልቅ አዕምሮ በተለያዩ ወቀቶች መፍትሄዎችን ለአለም ሲያበረክት ቆይቷል፡፡ በረዥሙ የሰው ልጅ ህይወትም አለም ላይ የተከሰቱ ችግሮችን በጥልቅ ምርምራቸው እና አሳቢነታቸው መፍትሄ የወለዱ እንቁ ባለሙያዎች በየሃገሩ ተፈጥረዋል፡፡ ታዲያ አትዮጵያችን ለአለም ካበረከተቻቸው ውድ ምሁራኖች መካከል ብዙዎችን መጥቀስ ብንችልም ለዛሬ ግን ስለፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ በጥቂቱ ልናስታውቹ ወደናል፡፡
መስከረም 7.1928 ዓ/ም በጅጅጋ ወረዳ ከእናታቸው ወ/ሮ አየለች ለማ እና ከአባታቸው በቀለ ወልደየስ ተወለዱ የያኔው ህጻን አክሊሉ፡፡ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ያኔው ቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ ዩኒቨርሲቲ ያሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመግባት ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በ1960 ከዊንስከንሲን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ወስደዋል፡፡ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በሚያጠኑበት ወቅት በብላሀርዝያ ላይ ከፍተኛ ትኩረት ነበራቸው፡፡ እኚህ ወጣት ተመራማሪ በየቀኑ ሴቶች በወንዝ ዳር ልብስ በሚያጥቡበት ወቅት በትኩረት ይከታተሉ ነበር፡፡ ሴቶቹ ልብሱን እንዶድ በሚባል ተክል ነበር የሚያጥቡት፤ በወቅቱ እንዶድ በርካታ የብላሀርዝያ ትሎችን መግደል የሚችል ተክል በመሆኑ ፕሮፌሰሩ ከፍተኛ ትኩረት ሰተውት ነበር፡፡ በ1966ም በቤተ ሙከራ ውስጥ ከተሞከረ በኋላ ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ በሳይንስ ፎረም ላይ አቀረቡት፡፡ በወቅቱ በአፍሪካ ውስጥ የሺስቶስሚያሲስ በሽታ ይከሰት ስለነበር እና የፕሮፌሰሩ ግኝት በዝቅተኛ ዋጋ በሽታ አምጪ የሆነውን ትል የሚገድል በመሆኑ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት ነበር፡፡
በዚያን ወቅት ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ በሜዲካል ኮሌጅ የፓራሳይቶሎጂ ፕሮግራም ጀምረው ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ታሪካ በሳይንስ ፋካሊቲ ውስጥ የመጀመሪያው ዲን ሆነውም አገልግለዋል፡፡ በዚያን ወቅት ፕሮፌሰር አክሊሉ ወደ ስታምፎርድ ዩኒቨርሲቲ በማቅናት ትኩሳትና ሌሎች የጥገኛ በሽታ አምጪ ህዋስያን ለመዋጋት የሚያስችል የእንዶድን ኬሚካላዊ ባህሪያቶች ላይ ጥናት ለማድረግ ለሁለት አመት ቆይተዋል፡፡ በዚህ አጋጣሚ መግለጽ የሚያስፈልገው ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ የእንዶድ ተክል ቀንድ አውጣውን ለመግደል ስለሚችል እና በሂደትም በሽታውን ለመቆጣጠር እንደሚረዳ ስለደረሱበት ዕውቅና እንዲሰጣቸው ተደርጓል።ቴክ-ሳይንስ 92
ስለ እንዶድ ጥቅምና የውኃ ትላትል ገዳይነት በማግኘታቸው የዩናይትድ ስቴትስ የፈጠራ ባለቤትነት ወይም ፓተንቶች ኣግኝተዋል። እንዶድ ሳይንሳዊ መጠሪያ ስሙ (Phy¬tolacca dodecandra) ሲሆን አብዛኛውን ጊዜ በወንዝ ዳርቻዎች ይበቅላል፡፡ በኢትዮጵያ ገጠራማ አካባቢዎች ልክ እንደሳሙና በሰፊው ለልብስ ማጠቢያነት የሚያገለግለው እንዶድ፣ ከተክሉ የሚገኘው ጭማቂ ወይም ፍሬው ደግሞ ለብላሀርዝያ በሽታ የሚዳርገውን ተውሳክ የሚያስጠልለውን ቀንድ አውጣ ስለሚገድል ለመድኃኒትነት ያገለግላል፡፡ ከተክሉ የሚገኝ ጭማቂ አልቅትንም ስለሚገድል በውኃ ውስጥ የአልቅቶችን ቁጥር ለመቆጣጠር ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ ተክሉ ለከብቶች የማይስማማ በመሆኑ እንስሳት ለምግብነት አይመርጡትም፡፡
ሺስቶሶሚያሲስ (ብላሀርዝያ ወይም ካታያማ ትኩሳት) በመባል ይታወቃል፡፡ ፕሮፌሰር አክሊሉ ስለዚህ በሽታ ባደረጉት ሰፊ ምርምር የመተላለፊያውን መንገድ፣ ምልክቶቹን እና ህክምናውን ከሌሎች ጉዳዮች ጋር አብራርተው ሊያሳትሙ ችለዋል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር አክሊሉ ጥናት በሽታው የሚተላለፈው ጥገኛ ትል በሆነው የሺስቶሶማ ህዋስ ዓይነት ሲሆን የሽንት መተላለፊያን ወይም አንጀትን ሊያጠቃ ይችላል፡፡ የሕመሙ ምልክት የሆድ ህመም፣ ተቅማጥ፣ ደም የተቀላቀለበት ሰገራ ወይም በሽንት ላይ ደም መታየትን ያጠቃልላል፡፡ ለረጅም ጊዜ ህመሙ የቆየበት ሰው የጉበት ህመም፣ የኩላሊት ስራ ማቆም፣ መሃንነት ፣ ወይም የፊኛ ካንሰር ሊያስከትልበት ይችላል፡፡ በልጆች ላይ ደግሞ ዝቅተኛ እድገትና የመማር ችግር ሊያስከትል ይችላል፡፡
በሽታው የሚሰራጨው ትላትሎቹ በሚገኙበት ውኃ ስፍራ በሚፈጠር የቆዳ ንክኪ ነው፡፡ እነዚህ ትላትሎች የሚመነጩት ከተበከሉ ቀንድ አውጣዎች ነው፡፡ ይህ በሽታ በደሃ አገራት በሚገኙ ታዳጊዎች ላይ የተለመደ ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ ልጆቹ በተበከለ ውኃ የመጫወታቸው አጋጣሚ ሰፊ በመሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪም በእለት ተእለት ስራ አማካኝነት ማለትም ገበሬዎች፣ አሳ አጥማጆችና ሌሎች የተበከለ ውኃ የሚጠቀሙ ሰዎች የበሽታው ስጋት የሚያጠላባቸው የህበረተሰብ ክፍሎች ናቸው፡፡
ህክምናውን በተመለከተ ምርመመራው የሚደረገው የትሉን እንቁላሎች ሽንት ወይም ሰገራ ላይ መኖራቸውን በመመርመር ሲሆን፤ በደም ላይ ፀረ እንግዳ አካል በመፈለግ በሽታው መኖሩን ማረጋገጥም ይቻላል፡፡ የብላሀርዝያን በሽታ ለመከላከል ንፁህ የውኃ አቅርቦትን ማሻሻል እና የቀንድ ኣውጣ ቁጥርን መቀነስ ዋነኞቹ ቢሆንም በሽታው በተስፋፋበት አካባቢ በአንድ ጊዜ ሁሉንም ሰዎች ፕራዚኩዋንትል በተባለ መድኃኒት በየዓመቱ ማከም በሽታውን ለማጥፋት ሌላኛው መንገድ ነው፡፡ ይህ እርምጃ በበሽታው የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስና የበሽታውን ስርጭት ለመግታት ያስችላል፡ ፡ ፕራዚኩዋንትል በበሽታው የተጠቁትን ለማከም በ(World Health Organization) የሚመከር የሕክምና ዘዴ ነው፡፡ የበሽታው መስፋፊያ ዘዴ የትሉ እንቁላሎች በሽንትና ሰገራ አማካኘነት ከሰው አካል ወጥተው ቀንድ ኣውጣ ውስጥ በመግባት የሚባዙ በመሆኑ በሽታውን ለመከላከል ሕዝቡ ሽንቱንና ሰገራውን ከሚጠጣው ውኃ እንዲያርቅ ማስተማር ያስፈልጋል፤ እንዲሁም የሚጠቀመው የኩሬ ወይም የወንዝ ውኃ ከሆነ ውኃውን ማከም እንደሚገባው ማስተማር ያስፈልጋል።
ሲስቶሶሚያሲስ በዓለም ላይ ወደ 210 ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ የሚያጠቃ ሲሆን፤ ከ12,000 እስከ 200,000 የሚሆነ ሕዝብ በዓመት ውስጥ በዚህ በሽታ ይሞታል ተብሎ ይገመታል፡፡ በሽታው በስፋት የሚታየው በአፍሪካ፣ በእስያና ደቡም አሜሪካ ነው፡፡ እንዲሁም ወደ 700 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ፣ ከ70 በላይ አገራት፣ በሽታው በስፋት በተሰራጨበት አካባቢ ይኖራል፡፡ ሲስቶሶሚያሲስ ከወባ ወይም ማላሪያ ቀጥሎ በሁለተኛነት የሚቀመጥና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተፅእኖ ያለው በሽታ ነው፡ ፡
እ.ኤ.አ. በ1993 እስከ ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ በነበረው ጊዜያቸው በጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ትስስር በመፍጠር ለአገሬው ተወላጅ የአቅም ግንባታ ያደረጉት ፕሮፌሰር አክሊሉ፤ የሳይንሳዊ ምርምሮችን በማስተዋወቅም ከፍተኛ ተሳትፎ አድርገዋል፡ ፡ ፕሮፌሰር አክሊሉ ለማ ሶስት ፓተንቶችን፤ አምስት መጽሐፍቶችን እና 60 ሳይንሳዊ የጥናት ጽሁፎችን በስማቸው አስመዝግበዋል፡፡ በ1969 በንጉስ ቀዳማዊ ሓይለ ስላሴ የወርቅ ሜዳሊያ እና ሌሎች በርካታ ሽልማቶችን ያገኙት እኝህ ብርቅዬ ኢትዮጵያዊ ምሁር ከብዙ ትሩፋቶቻቸው በኋላ ይህችን አለም በ62 አመታቸው ተሰናብተዋል፡፡
ከቴክ ሳይንስ ቅፅ 17 የተወሰደ
ስለ GMO (ልውጠ ህያዋን) የተዘጋጀ ልዩ ፕሮግራም፡፡ GMO (ልውጠ ህያዋን) አሉታዊ ወይስ አወንታዊ ጎኑ ያመዝናል? ሙሉ ዝግጅቱን በዩትዩብ ቻናላችን ይዘንልዎ ቀርበናል፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=Eka5wceAA1A
ያስታውሱ!!! ዘውትር ቅዳሜ በ10 ሰዓት በድጋሚ ደግሞ ማክሰኞ በ10 ሰዓት በ MOE TV ይከታተሉን
(Nilesat 12520/v/27500)
(በተጨማሪም Ethiosat ላይ እንገኛለን)
ያስታውሱ!!! ዘውትር ቅዳሜ በ10 ሰዓት በድጋሚ ደግሞ ማክሰኞ በ10 ሰዓት በ MOE TV ይከታተሉን
(Nilesat 12520/v/27500)
(በተጨማሪም Ethiosat ላይ እንገኛለን)
YouTube
ስለ GMO (ልውጠ ህያዋን) የተዘጋጀ ልዩ ፕሮግራም፡፡ GMO (ልውጠ ህያዋን) አሉታዊ ወይስ አወንታዊ ጎኑ ያመዝናል?A special program on GMO.
የጤና ባለሙያዎች እና ተጋላጭ ማህበረሰቦች በጥር ወር ማለቂያ ክትባት ሊያገኙ ይችላሉ
የኮሮናቫይረስ ህይወታቸውን አደጋ ውስጥ ለከተተው ግለሰቦች እና ቫይረሱን ፊት ለፊት እየተጋፈጡ ለሚገኙት የጤና ባለሙያዎች በፈረንጆቹ ጥር ወር ማለቂያ ላይ ክትባት ሊደርሳቸው እንደሚችል የአሜሪካ የጤና እና ሰብዓዊ አገልግሎቶች (HHS) ተቋም ዋና ፀሃፊ አሌክስ አዛር በትላንትናው ዕለት ገልፀዋል፡፡
ዋና ፀሃፊው በዕለቱ በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ የኮሮናቫይስ ክትባቶች አስተማማኝ እና ውጤታማ በሆነ መልኩ ሰዎች ጋር የመድረሳቸው ሁኔታ በመጨረሻዎቹ የክትባቶቹ የሙከራ ሂደት ላይ ሊወሰን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ጥቅም ላይ ለመዋል ከጫፍ የደረሱ ክትባቶች ፍፁም ደህንነታቸው ተረጋግጦ ሰዎች ጋር መድረስ እንዲችሉ በሶስተኛው የክሊኒካል ሙከራ አማካኘነት ብዙ ሺ ሰዎች ላይ ሊሞከሩ እንደሚገባም ዋና ጸሃፊው አስረድተዋል፡፡
በፋርማሲዩቲካል ዘርፍ እጅግ የገዘፈ ስም ያለው ፋይዘር (Pfizer) የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚያዘጋጀው ክትባት አስተማማኝነቱን እና ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ የሚስችል መረጃ በቀጣዩ ህዳር ወር መጠናቀቂያ የሚጠበቅ ሲሆን ክትባቱ መልካም ውጤቱ ከታየበትም የድንገተኛ ጊዜ አጠቃቀም ባለስልጣን (EUA) በሚፈቅው መሰረት ጥቅም ላይ የሚውልበት እድል አለ፡፡
በዓመቱ መጠናቀቂያ የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) በሚፈቅደው መሰረት ክትባቶችን ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ፀሃፊው በቅድሚያም በበሽታው እጅግ ለተጎዱ እና ለተጋለጡ ሰዎች የሚቀርብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በማስከተልም በጥ ወር መጠናቀቂያ ላይ በሁለም ዘርፍ የሚገኙ ሲኒየር ሃኪሞች የጤና ባለሙያዎች እና ተንከባካቢዎች ክትባቱን እንዲያገኙ እንደሚደረግ ሚስተር አዛር ተናግረዋል፡፡
ዋና ጸሃፊው ከዚህ ውጭ ያለው የማህበረሰብ ክፍል በመጋቢት እና ሚያዚያ ወር ላይ ክትባቱን የማግኘት እድል እንዳለው ቢገልፁም ክትባቱን ብስፋት የመምረት ሁኔታ የስርጭቱ አካሄድ ገና ያልተረጋገጠ ጉዳይ መሆኑን አልሸሸጉም፡፡ አንዳንድ የጤና ኤክስፐርቶች እንደሚገልፁት ክትባት ከማግኘት እኩል በአስተማማኝ ሁኔታ ሰዎች ጋር የማሳራጨት ስራ እጅግ ከባድ ሲሆን፤ ከዚህም በላይ ክትባቱ ሰዎች ጋር ደርሶም ውጤታማነቱ እና ድህንነቱ 100% ማረጋገጥ አስቸጋሪ እንደሚሆን ይናገራሉ፡፡ ምንጭ፡ Livescience
የኮሮናቫይረስ ህይወታቸውን አደጋ ውስጥ ለከተተው ግለሰቦች እና ቫይረሱን ፊት ለፊት እየተጋፈጡ ለሚገኙት የጤና ባለሙያዎች በፈረንጆቹ ጥር ወር ማለቂያ ላይ ክትባት ሊደርሳቸው እንደሚችል የአሜሪካ የጤና እና ሰብዓዊ አገልግሎቶች (HHS) ተቋም ዋና ፀሃፊ አሌክስ አዛር በትላንትናው ዕለት ገልፀዋል፡፡
ዋና ፀሃፊው በዕለቱ በነበራቸው ጋዜጣዊ መግለጫ የኮሮናቫይስ ክትባቶች አስተማማኝ እና ውጤታማ በሆነ መልኩ ሰዎች ጋር የመድረሳቸው ሁኔታ በመጨረሻዎቹ የክትባቶቹ የሙከራ ሂደት ላይ ሊወሰን እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ ጥቅም ላይ ለመዋል ከጫፍ የደረሱ ክትባቶች ፍፁም ደህንነታቸው ተረጋግጦ ሰዎች ጋር መድረስ እንዲችሉ በሶስተኛው የክሊኒካል ሙከራ አማካኘነት ብዙ ሺ ሰዎች ላይ ሊሞከሩ እንደሚገባም ዋና ጸሃፊው አስረድተዋል፡፡
በፋርማሲዩቲካል ዘርፍ እጅግ የገዘፈ ስም ያለው ፋይዘር (Pfizer) የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የሚያዘጋጀው ክትባት አስተማማኝነቱን እና ውጤታማነቱን ለማረጋገጥ የሚስችል መረጃ በቀጣዩ ህዳር ወር መጠናቀቂያ የሚጠበቅ ሲሆን ክትባቱ መልካም ውጤቱ ከታየበትም የድንገተኛ ጊዜ አጠቃቀም ባለስልጣን (EUA) በሚፈቅው መሰረት ጥቅም ላይ የሚውልበት እድል አለ፡፡
በዓመቱ መጠናቀቂያ የምግብ እና መድሃኒት አስተዳደር (FDA) በሚፈቅደው መሰረት ክትባቶችን ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ፀሃፊው በቅድሚያም በበሽታው እጅግ ለተጎዱ እና ለተጋለጡ ሰዎች የሚቀርብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በማስከተልም በጥ ወር መጠናቀቂያ ላይ በሁለም ዘርፍ የሚገኙ ሲኒየር ሃኪሞች የጤና ባለሙያዎች እና ተንከባካቢዎች ክትባቱን እንዲያገኙ እንደሚደረግ ሚስተር አዛር ተናግረዋል፡፡
ዋና ጸሃፊው ከዚህ ውጭ ያለው የማህበረሰብ ክፍል በመጋቢት እና ሚያዚያ ወር ላይ ክትባቱን የማግኘት እድል እንዳለው ቢገልፁም ክትባቱን ብስፋት የመምረት ሁኔታ የስርጭቱ አካሄድ ገና ያልተረጋገጠ ጉዳይ መሆኑን አልሸሸጉም፡፡ አንዳንድ የጤና ኤክስፐርቶች እንደሚገልፁት ክትባት ከማግኘት እኩል በአስተማማኝ ሁኔታ ሰዎች ጋር የማሳራጨት ስራ እጅግ ከባድ ሲሆን፤ ከዚህም በላይ ክትባቱ ሰዎች ጋር ደርሶም ውጤታማነቱ እና ድህንነቱ 100% ማረጋገጥ አስቸጋሪ እንደሚሆን ይናገራሉ፡፡ ምንጭ፡ Livescience
ሁለት ጾታ ያለው ወፍ
*****************
ተመራማሪዎች ግማሽ ጎኑ ሴት ግማሽ ጎኑ ደግሞ ወንድ የሆነ ወፍ ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ CNN ባወጣው ዘገባ ባለሁለት ጾታው ወፍ አዘውትሮ በመዘመር የሚታወቅ ድምጸ መረዋ ነው፡፡ ይህንም ግኝት ተመራማሪዎቹ የመከሰት እድሉ በጣም ጠባብ ነው ብለዋል፡፡
ከ15 ዓመታት በፊት የተፈጥሮና ታሪክ ሙዚየም የሆነው ካርኔጅ ሙዚየም ተመሳሳይ የወፍ አይነት ማግኘቱን ገልጾ ነበር፡፡ ይህም ተቋሙ ካያቸው 800,000 ከሚደርሱ ወፎች መካከል አምስተኛው እንደሆነ ተገልጧል፡፡
የዚህ አይነት ወፎች የራሳቸው መለያ ቀለም ያላቸው ሲሆን ወንዶቹ ሮዝ ነጠብጣብ ላባ ሲኖራቸው ሴቶቹ ደግሞ ቢጫና ቡናማ ቅልቅል ላባ አላቸው፡፡ አሁን ተገኘ የተባለውም ወፍ በአንዱ ክንፉ የወንድ ቀለም ሲኖረው በሌላ ክንፉ ደግሞ የሴት ቀለም አለው፡፡ በሳይንሳዊ (በዘረመል) መጠሪያው ጂናንድሮሞረፊዝም የሚባል ክስተት እንደሆነ ተመራማሪዎቹ ለCNN ተናግረዋል፡፡
ይህ አይነቱ ክስተት በሌሎች እንደ ሸረሪት፣ አሳዎችና በዶሮዎችም ሊከሰት እንደሚችል ተመራማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡
ምንጭ፡ CNN
*****************
ተመራማሪዎች ግማሽ ጎኑ ሴት ግማሽ ጎኑ ደግሞ ወንድ የሆነ ወፍ ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ CNN ባወጣው ዘገባ ባለሁለት ጾታው ወፍ አዘውትሮ በመዘመር የሚታወቅ ድምጸ መረዋ ነው፡፡ ይህንም ግኝት ተመራማሪዎቹ የመከሰት እድሉ በጣም ጠባብ ነው ብለዋል፡፡
ከ15 ዓመታት በፊት የተፈጥሮና ታሪክ ሙዚየም የሆነው ካርኔጅ ሙዚየም ተመሳሳይ የወፍ አይነት ማግኘቱን ገልጾ ነበር፡፡ ይህም ተቋሙ ካያቸው 800,000 ከሚደርሱ ወፎች መካከል አምስተኛው እንደሆነ ተገልጧል፡፡
የዚህ አይነት ወፎች የራሳቸው መለያ ቀለም ያላቸው ሲሆን ወንዶቹ ሮዝ ነጠብጣብ ላባ ሲኖራቸው ሴቶቹ ደግሞ ቢጫና ቡናማ ቅልቅል ላባ አላቸው፡፡ አሁን ተገኘ የተባለውም ወፍ በአንዱ ክንፉ የወንድ ቀለም ሲኖረው በሌላ ክንፉ ደግሞ የሴት ቀለም አለው፡፡ በሳይንሳዊ (በዘረመል) መጠሪያው ጂናንድሮሞረፊዝም የሚባል ክስተት እንደሆነ ተመራማሪዎቹ ለCNN ተናግረዋል፡፡
ጂን`- በግሪክ ቋንቋ ለሴት የሚነገር ሲሆን `አንድሮ ደግሞ ወንድ ማለት ነው፡፡ ሞርፍ የሚለው ቃል ስብጥርን የሚያመለክት ነው፡፡ይህ አይነቱ ክስተት በሌሎች እንደ ሸረሪት፣ አሳዎችና በዶሮዎችም ሊከሰት እንደሚችል ተመራማሪዎቹ አክለው ገልጸዋል፡፡
ምንጭ፡ CNN