ተጠንቶ የማያልቀው ስነ ከዋክብትና አዲስ መኖሪያ ፍለጋ
***************************************
የዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች 24 ፕላኔቶችን በፀሐይ ዙሪያ ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ The Cosmic Companion የተሰኘ የስነ-ከዋክብት መረጃዎችን የሚያዎጣው ተቋም እንደዘገበው ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ያላቸው 24 ፕላኔቶች የራሳቸው ከዋክብትንም የያዙ ናቸው፡፡
ፕላኔቶቹ የሚዞሯቸው አብዛኞቹ ከዋክብት ከፀሐይ በተሻለ መልኩ ለህይዎት ተስማሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ጂኦ ባዮሎጂስት የሆኑት Dirk Schulze-Makuch ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በታየባቸው ፕላኔቶች ተጨማሪ ጥናቶችን እናካሂዳለን ብለዋል፡፡
እነዚህ ምቹ መኖሪዎች ከመሬት የተሻለ ሙቀት፣ ርጥበት፣ መጠንና እድሜ ያላቸው እንደሚሆን ተገምቷል፡፡ ተመራማሪዎቹ እንዳሉት በጣም ረጅም እድሜ ያላቸው ፕላኔቶች ለአደገኛ ጨረር ሊያጋልጡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ለህይዎት አማራጭ ሊሆኑ የሚችሉት ፕላኔቶች ከ5 እስከ 8 ቢሊዮን ዓመት የሚደርስ ዕድሜ ያላቸው ናቸው፡፡
ከእድሜ በተጨማሪ የእነዚህን ፕላኔቶች ለህይዎት ምቹነት ክብደታቸውና መጠናቸው ይወስነዋል፡፡ በተጨማሪም መጠነ-ሙቀት የአዲስ ፕላኔት ፍለጋው አንድ አካል ነው፡፡ በአማካኝ 20 ዲግሪ ሴልሺየስ ያላቸው ፕላኔቶች ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ይኖራቸዋል፡፡
ምንጭ፡- The Cosmic Companion
***************************************
የዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች 24 ፕላኔቶችን በፀሐይ ዙሪያ ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ The Cosmic Companion የተሰኘ የስነ-ከዋክብት መረጃዎችን የሚያዎጣው ተቋም እንደዘገበው ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ያላቸው 24 ፕላኔቶች የራሳቸው ከዋክብትንም የያዙ ናቸው፡፡
ፕላኔቶቹ የሚዞሯቸው አብዛኞቹ ከዋክብት ከፀሐይ በተሻለ መልኩ ለህይዎት ተስማሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ጂኦ ባዮሎጂስት የሆኑት Dirk Schulze-Makuch ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በታየባቸው ፕላኔቶች ተጨማሪ ጥናቶችን እናካሂዳለን ብለዋል፡፡
እነዚህ ምቹ መኖሪዎች ከመሬት የተሻለ ሙቀት፣ ርጥበት፣ መጠንና እድሜ ያላቸው እንደሚሆን ተገምቷል፡፡ ተመራማሪዎቹ እንዳሉት በጣም ረጅም እድሜ ያላቸው ፕላኔቶች ለአደገኛ ጨረር ሊያጋልጡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ለህይዎት አማራጭ ሊሆኑ የሚችሉት ፕላኔቶች ከ5 እስከ 8 ቢሊዮን ዓመት የሚደርስ ዕድሜ ያላቸው ናቸው፡፡
ከእድሜ በተጨማሪ የእነዚህን ፕላኔቶች ለህይዎት ምቹነት ክብደታቸውና መጠናቸው ይወስነዋል፡፡ በተጨማሪም መጠነ-ሙቀት የአዲስ ፕላኔት ፍለጋው አንድ አካል ነው፡፡ በአማካኝ 20 ዲግሪ ሴልሺየስ ያላቸው ፕላኔቶች ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ይኖራቸዋል፡፡
ምንጭ፡- The Cosmic Companion
ስለ ዝሆን ምን ያህል ያውቃሉ?
ብዙዎቻችን ከልጅነት ጊዜያችን አንስቶ ስለ ዱር ስናስብ በምዕናባችን ከሚከሰቱት እንስሳት መካከል ዝሆኖች ቀዳሚ ናቸው፡፡ ዝሆኖች በምድራችን ከሚራመዱ እንስሳት ሁሉ በግዝፈታቸው ወደር የሌላቸው እና አፈጣጠራቸው ለየት ያሉ ናቸው፡፡ በረጀክሙ ኩምቢ፣ ግዙፍ ግን ልፍስፍስ ጆሮዎች፣ ወፋፍራም እግር ዝሆኖችን ከሌሎች እንስሳት የሚለዩ አካላዊ ገፅታዎቻቸው ናቸው፡፡
ብዙዎቹ ባለሙያዎች በሁለት አህጉራት የሚኖሩ ሁለት አይነት የዝሆን ዝርያዎች መኖራቸው ላይ ይስማማሉ፤ የአፍሪካ (Loxodonta africana) እና የእሲያ (Elephas maximus) ዝሆን ዝርያዎች፡፡ በእነዚህ ሁለት ዝርያዎች ስር የተለያዩ ቅርንጫረፍ ዝርያዎች አሉ፤ ምንም እንኳን ምን ያህል ናቸው በሚለው ላይ ክርክር ቢኖርም፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች የሳር ምድር (Loxodonta africana) እና የጫካ (Loxodonta cyclotis) ተብለው የተከፈሉ ሁለት የዘር ቅርንጫፍ ሲኖራቸው የእሲያዎቹ በበኩላቸው የህንድ (Elephas maximus indicus)፣ ስሪ ላንካ (Elephas maximus maximus) እና ሱማትራ (Elephas maximus sumatranus) የተሰኙ የዘር ቅርንጫፎች አሏቸው፡፡
የአፍሪካና እሲያ ዝሆኖች ልዩነት
የአፍሪካ ዝሆኖች ከሰሃራ በታች ባለው የአህጉራችን ክፍል በተለያዩ ስፍራዎች ይኖራሉ፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በበኩላቸው በኔፓል፣ ህንድ እና ደቡብ ምስራቅ እሲያ ጫካዎች ኑሯቸውን አድርገዋል፡፡ በግዝፈት ያነፃፀርን እንደሆነ የአፍሪካ ዝሆኖች ብልጫውን ይዘው እናገኛቸዋለን፡፡ ቁመታቸው ከ2.5 እስከ 4 ሜትር ሊደርስ ሲችል ክብደታቸውም ከ2,200 ኪ.ግ እስከ 6,350 ኪ.ግ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የእሲያ ዝሆኖች ከ2 እስከ 3 ሜትር ብቻ ሲረዝም ክብደታቸውም ከ2,000 እስከ 5,000 ኪ.ግ ብቻ ነው፡፡
ሁለቱ የዝሆን ዝርያዎች ከግዝፈትም ባሻገር ሌሎች ጥቂት ልዩነቶች አሏቸው፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች ጆሮ ገዘፍ ያለና ቅርፁም የአፍሪካ ካርታን የመሰለ ሲሆን የእሲያዎቹ ዝሆኖች በበኩሉ አነስ ያለና ክብ ቅርፅን የያዘ ነው፡፡ ወንዶቹም ሆነ ሴት የአፍሪካ ዝሆኖች ትላልቅ ጥርስና እቃ ለማንሳት የሚረዳ ሁለት ጣት መሰል ነገር በኩምቢያቸው ጫፍ አላቸው፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በኩምቢያቸው ላይ ያለው ጣት አንድ ብቻ ሲሆን ረጃጅም ጥርስ የሚያበቅሉትም ወንዶቹ ብቻ ናቸው፡፡ ሴቶቹ እና አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የእሲያ ዝሆኖች አነስተኛ መጠኑ አነስ ያለ ጥርስን ሲያበቅሉ ጥርሱ ወደ ውጪ ግን የማይታይ ሊሆን ይችላል፡፡
የዝሆን ጥርስ ግዙፍና ረጅም ስር ያላቸው ሲሆን ለዝሆኖቹ መቆፈርያ፣ እቃ ማንሻ፣ ምግብ መሰብሰብያ እና እራሳቸውን መከላከያ ሆኖ ሲያገለግላቸው ኩምቢውንም የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ እኛ የሰው ልጆች ግራኝ ወይም የቀኝ እጅ ተጠቃሚ እንደሆንነው ሁሉ ዝሆኖችም ግራኝ አልያም የቀኝ ቀንዳቸውን ተጠቃሚ ናቸው፡፡ የትኛውን እንደሚጠቀሙ ለማወቅ ቀላሉ መንገድ የደከመውን መለየት ነው፡፡
ሁለቱም የዝሆን ዝርያዎች የተለያዩ የሳር አይነቶችን፣ ፍራፍሬዎችን፣ ቅጠላ ቅጠሎችን፣ የዛፍ ቅርፊት እና ስር የመሳሰሉ የእፅዋት አካላትን ይመገባሉ፡፡ በቀን ውስጥ 16 ሰዓታትንም በመመገብ የሚያጠፉና በዚህም ከ75 እስከ 150 ኪ.ግ የሚሆን ምግብ የሚሰለቅጡ ናቸው፡፡
ማህበራዊ ህይወት
የዝሆኖች ቡድን ዕድሜያቸው በገፋ ሴቶች የሚመራ ነው፡፡ መንጋው በዋናነት በሴት ቤተሰቦችና ህፃናት ዝሆኖች ሲሞላ እንደ ምግብ አቅርቦቱ ከ6 እስከ 20 አባላትን ሊይዝ ይችላል፡፡ ቤተሰቡ ከሚፈለገው በላይ ሲበዛ በቅርብ አካባቢ ወደሚሰፍሩ የተለያዩ ቡድኖች ይከፈላል፡፡ መሪዋ ዝሆን ተግባሯን የምታከናውነው ልምዷን እና የትኛው ስፍራ ጥሩ ምግብ እና መጠለያ እንደያዘ የሚነግራት ትውስታዋን በመጠቀም ነው፡፡ በተጨማሪም ህፃናት ዝሆኖችን ከሌሎቹ ጋራ እንዴት መግባባት አንዳለባቸው የማስተማሩን ድርሻ ይወጣሉ፡፡
ዝሆኖች በከፍተኛ ሁኔታ ማህራዊ ኑሮን ከሚመሩ እንስሳት መካከል ናቸው፡፡ አንድ ዝሆን ከሌላው ጋራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን የሰው ልጆች መስማት የማንችለውን አነስተኛ ድምፅ በማውጣትም ከሶስት ኪ.ሜ በላይ ርቆ ያለ ዝሆንን መለየት ይችላሉ፡፡ በራሳቸውም ሆነ ሌላ ቡድን ውስጥ ላለ ዝሆንም መልካም ስነ-ምግባር በማሳየትም ይታወቃሉ፡፡ ለምሳሌ ሲገናኙ ኩምቢያቸውን ወደላይ ከፍ በማድረግ አልያም የኩምቢያቸውን ጫፍ ወደ ሌላኛው ዝሆን አፍ በመክተት ሰላምታ ይለዋወጣሉ፡፡ ከዚህ ባለፈም በመንጋቸው ውስጥ ያለ ሌላ የተጎዳ አባል ካለ የሚጠብቁና ስለሌላው የቡድኑ አባል ደህንነት ግድ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡
በሌላ መልኩ ዝሆኖች በማሰብ ችሎታቸው የማይታሙ መናቸው ይነገርላቸዋል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሆነው ውስብስብ ችግሮችን የመፍታት ብቃት ሲያሳዩ እንዲሁም ለቅሶ ሲደርሱና ሲያፅናኑ መታየታቸው ነው፡፡
ዕድሜ
ዝሆኖች ከተወለዱ ከ8 እስከ 13 ባሉት ዓመታት ውስጥ ለፆታዊ ግንኙነት ይደርሳሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ምግባቸውን ፈልገው ማግኘት እና እራሳቸውን መጠበቅ እስከቻሉ ድረስ ወንድ ዝሆኖች መንጋውን ትተው በመውጣት ለብቻቸው አልያም ከሌሎች መሰሎቻቸው ጋራ በአነስተኛ ቡድን ኑሮዋቸውን ይመራሉ፡፡
ሴቶቹ ዝሆኖች በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ እስከሚደርሱ ድረስ ልጅ የማይወልዱ ሲሆን ወንዶቹ ግን ዕድሜያቸው ሰላሳዎቹ ውስጥ እስከሚገባ ድረስም ልጅ ላይወልዱ ይችላሉ፡፡ አንድ የዝሆን ልጅ የሚወለደው ከ22 ወራት የእርግዝና ቆይታ በኋላ ነው፡፡ የሚወለዱት ጨቅላ ዝሆኖችም ከ68 እስከ 158 ኪ.ግ ክብደትና 90 ሴ.ሜ አካባቢ ቁመት ይዘው ይህችን ምድር ይቀላቀላሉ፡፡ በተጨማሪም ፀጉር እንዲሁም ረጅም ጭራና አጭር ኩምቢ ያላቸው ናቸው፡፡ ዕድገታቸው ግን እጅግ ፈጣን የሚባል ነው፤ በተወለዱ በአንድ ዓመት ውስጥ በየቀኑ ከ0.9 እስከ 1.3 ኪ.ግ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ ሶስት ዓመት ሲሞላቸውም መደበኛ ምግብ መመገብ ይጀምራሉ፡፡
አለም አቀፉ የተፈጥሮ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ሕብረት (IUCN) የእሲያ ዝሆኖች የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ናቸው ሲል ያስቀምጣቸዋል፡፡ ምንም እንኳን ሙሉ ቁጥራቸው ባይታወቅም እየቀነሱ መሆናቸው ግን ይታመናል፡፡ በአንፃሩ የአፍሪካ ዝሆኖች ቁጥራቸው በመጨመር ላይ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓትም 415,000 የአፍሪካ ዝሆኖች በየዱሩ ይገኛሉ፡፡ በአደጋ ስጋት ረገድ የአፍሪካንም ሆነ የእሲያ የዝሆን ዝርያዎችን የሚያመሳስላቸው የአደን እና የዘር ቅርንጫፎች የመጥፋት ስጋት የተጋረጠባቸው መሆኑ ነው፡፡
ምንጭ፡ Live Science
ብዙዎቻችን ከልጅነት ጊዜያችን አንስቶ ስለ ዱር ስናስብ በምዕናባችን ከሚከሰቱት እንስሳት መካከል ዝሆኖች ቀዳሚ ናቸው፡፡ ዝሆኖች በምድራችን ከሚራመዱ እንስሳት ሁሉ በግዝፈታቸው ወደር የሌላቸው እና አፈጣጠራቸው ለየት ያሉ ናቸው፡፡ በረጀክሙ ኩምቢ፣ ግዙፍ ግን ልፍስፍስ ጆሮዎች፣ ወፋፍራም እግር ዝሆኖችን ከሌሎች እንስሳት የሚለዩ አካላዊ ገፅታዎቻቸው ናቸው፡፡
ብዙዎቹ ባለሙያዎች በሁለት አህጉራት የሚኖሩ ሁለት አይነት የዝሆን ዝርያዎች መኖራቸው ላይ ይስማማሉ፤ የአፍሪካ (Loxodonta africana) እና የእሲያ (Elephas maximus) ዝሆን ዝርያዎች፡፡ በእነዚህ ሁለት ዝርያዎች ስር የተለያዩ ቅርንጫረፍ ዝርያዎች አሉ፤ ምንም እንኳን ምን ያህል ናቸው በሚለው ላይ ክርክር ቢኖርም፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች የሳር ምድር (Loxodonta africana) እና የጫካ (Loxodonta cyclotis) ተብለው የተከፈሉ ሁለት የዘር ቅርንጫፍ ሲኖራቸው የእሲያዎቹ በበኩላቸው የህንድ (Elephas maximus indicus)፣ ስሪ ላንካ (Elephas maximus maximus) እና ሱማትራ (Elephas maximus sumatranus) የተሰኙ የዘር ቅርንጫፎች አሏቸው፡፡
የአፍሪካና እሲያ ዝሆኖች ልዩነት
የአፍሪካ ዝሆኖች ከሰሃራ በታች ባለው የአህጉራችን ክፍል በተለያዩ ስፍራዎች ይኖራሉ፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በበኩላቸው በኔፓል፣ ህንድ እና ደቡብ ምስራቅ እሲያ ጫካዎች ኑሯቸውን አድርገዋል፡፡ በግዝፈት ያነፃፀርን እንደሆነ የአፍሪካ ዝሆኖች ብልጫውን ይዘው እናገኛቸዋለን፡፡ ቁመታቸው ከ2.5 እስከ 4 ሜትር ሊደርስ ሲችል ክብደታቸውም ከ2,200 ኪ.ግ እስከ 6,350 ኪ.ግ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የእሲያ ዝሆኖች ከ2 እስከ 3 ሜትር ብቻ ሲረዝም ክብደታቸውም ከ2,000 እስከ 5,000 ኪ.ግ ብቻ ነው፡፡
ሁለቱ የዝሆን ዝርያዎች ከግዝፈትም ባሻገር ሌሎች ጥቂት ልዩነቶች አሏቸው፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች ጆሮ ገዘፍ ያለና ቅርፁም የአፍሪካ ካርታን የመሰለ ሲሆን የእሲያዎቹ ዝሆኖች በበኩሉ አነስ ያለና ክብ ቅርፅን የያዘ ነው፡፡ ወንዶቹም ሆነ ሴት የአፍሪካ ዝሆኖች ትላልቅ ጥርስና እቃ ለማንሳት የሚረዳ ሁለት ጣት መሰል ነገር በኩምቢያቸው ጫፍ አላቸው፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በኩምቢያቸው ላይ ያለው ጣት አንድ ብቻ ሲሆን ረጃጅም ጥርስ የሚያበቅሉትም ወንዶቹ ብቻ ናቸው፡፡ ሴቶቹ እና አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የእሲያ ዝሆኖች አነስተኛ መጠኑ አነስ ያለ ጥርስን ሲያበቅሉ ጥርሱ ወደ ውጪ ግን የማይታይ ሊሆን ይችላል፡፡
የዝሆን ጥርስ ግዙፍና ረጅም ስር ያላቸው ሲሆን ለዝሆኖቹ መቆፈርያ፣ እቃ ማንሻ፣ ምግብ መሰብሰብያ እና እራሳቸውን መከላከያ ሆኖ ሲያገለግላቸው ኩምቢውንም የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ እኛ የሰው ልጆች ግራኝ ወይም የቀኝ እጅ ተጠቃሚ እንደሆንነው ሁሉ ዝሆኖችም ግራኝ አልያም የቀኝ ቀንዳቸውን ተጠቃሚ ናቸው፡፡ የትኛውን እንደሚጠቀሙ ለማወቅ ቀላሉ መንገድ የደከመውን መለየት ነው፡፡
ሁለቱም የዝሆን ዝርያዎች የተለያዩ የሳር አይነቶችን፣ ፍራፍሬዎችን፣ ቅጠላ ቅጠሎችን፣ የዛፍ ቅርፊት እና ስር የመሳሰሉ የእፅዋት አካላትን ይመገባሉ፡፡ በቀን ውስጥ 16 ሰዓታትንም በመመገብ የሚያጠፉና በዚህም ከ75 እስከ 150 ኪ.ግ የሚሆን ምግብ የሚሰለቅጡ ናቸው፡፡
ማህበራዊ ህይወት
የዝሆኖች ቡድን ዕድሜያቸው በገፋ ሴቶች የሚመራ ነው፡፡ መንጋው በዋናነት በሴት ቤተሰቦችና ህፃናት ዝሆኖች ሲሞላ እንደ ምግብ አቅርቦቱ ከ6 እስከ 20 አባላትን ሊይዝ ይችላል፡፡ ቤተሰቡ ከሚፈለገው በላይ ሲበዛ በቅርብ አካባቢ ወደሚሰፍሩ የተለያዩ ቡድኖች ይከፈላል፡፡ መሪዋ ዝሆን ተግባሯን የምታከናውነው ልምዷን እና የትኛው ስፍራ ጥሩ ምግብ እና መጠለያ እንደያዘ የሚነግራት ትውስታዋን በመጠቀም ነው፡፡ በተጨማሪም ህፃናት ዝሆኖችን ከሌሎቹ ጋራ እንዴት መግባባት አንዳለባቸው የማስተማሩን ድርሻ ይወጣሉ፡፡
ዝሆኖች በከፍተኛ ሁኔታ ማህራዊ ኑሮን ከሚመሩ እንስሳት መካከል ናቸው፡፡ አንድ ዝሆን ከሌላው ጋራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን የሰው ልጆች መስማት የማንችለውን አነስተኛ ድምፅ በማውጣትም ከሶስት ኪ.ሜ በላይ ርቆ ያለ ዝሆንን መለየት ይችላሉ፡፡ በራሳቸውም ሆነ ሌላ ቡድን ውስጥ ላለ ዝሆንም መልካም ስነ-ምግባር በማሳየትም ይታወቃሉ፡፡ ለምሳሌ ሲገናኙ ኩምቢያቸውን ወደላይ ከፍ በማድረግ አልያም የኩምቢያቸውን ጫፍ ወደ ሌላኛው ዝሆን አፍ በመክተት ሰላምታ ይለዋወጣሉ፡፡ ከዚህ ባለፈም በመንጋቸው ውስጥ ያለ ሌላ የተጎዳ አባል ካለ የሚጠብቁና ስለሌላው የቡድኑ አባል ደህንነት ግድ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡
በሌላ መልኩ ዝሆኖች በማሰብ ችሎታቸው የማይታሙ መናቸው ይነገርላቸዋል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሆነው ውስብስብ ችግሮችን የመፍታት ብቃት ሲያሳዩ እንዲሁም ለቅሶ ሲደርሱና ሲያፅናኑ መታየታቸው ነው፡፡
ዕድሜ
ዝሆኖች ከተወለዱ ከ8 እስከ 13 ባሉት ዓመታት ውስጥ ለፆታዊ ግንኙነት ይደርሳሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ምግባቸውን ፈልገው ማግኘት እና እራሳቸውን መጠበቅ እስከቻሉ ድረስ ወንድ ዝሆኖች መንጋውን ትተው በመውጣት ለብቻቸው አልያም ከሌሎች መሰሎቻቸው ጋራ በአነስተኛ ቡድን ኑሮዋቸውን ይመራሉ፡፡
ሴቶቹ ዝሆኖች በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ እስከሚደርሱ ድረስ ልጅ የማይወልዱ ሲሆን ወንዶቹ ግን ዕድሜያቸው ሰላሳዎቹ ውስጥ እስከሚገባ ድረስም ልጅ ላይወልዱ ይችላሉ፡፡ አንድ የዝሆን ልጅ የሚወለደው ከ22 ወራት የእርግዝና ቆይታ በኋላ ነው፡፡ የሚወለዱት ጨቅላ ዝሆኖችም ከ68 እስከ 158 ኪ.ግ ክብደትና 90 ሴ.ሜ አካባቢ ቁመት ይዘው ይህችን ምድር ይቀላቀላሉ፡፡ በተጨማሪም ፀጉር እንዲሁም ረጅም ጭራና አጭር ኩምቢ ያላቸው ናቸው፡፡ ዕድገታቸው ግን እጅግ ፈጣን የሚባል ነው፤ በተወለዱ በአንድ ዓመት ውስጥ በየቀኑ ከ0.9 እስከ 1.3 ኪ.ግ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ ሶስት ዓመት ሲሞላቸውም መደበኛ ምግብ መመገብ ይጀምራሉ፡፡
አለም አቀፉ የተፈጥሮ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ሕብረት (IUCN) የእሲያ ዝሆኖች የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ናቸው ሲል ያስቀምጣቸዋል፡፡ ምንም እንኳን ሙሉ ቁጥራቸው ባይታወቅም እየቀነሱ መሆናቸው ግን ይታመናል፡፡ በአንፃሩ የአፍሪካ ዝሆኖች ቁጥራቸው በመጨመር ላይ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓትም 415,000 የአፍሪካ ዝሆኖች በየዱሩ ይገኛሉ፡፡ በአደጋ ስጋት ረገድ የአፍሪካንም ሆነ የእሲያ የዝሆን ዝርያዎችን የሚያመሳስላቸው የአደን እና የዘር ቅርንጫፎች የመጥፋት ስጋት የተጋረጠባቸው መሆኑ ነው፡፡
ምንጭ፡ Live Science
የምንጊዜውም አጭሩ የጊዜ ርዝማኔ
====================
አንድን ድርጊት አከናውነን ለመፈጸም ርዝማኔው ወይም ቆይታው ይለያይ እንጂ ጊዜ ያስፈልገናል፡፡ ታዲያ አንድን ድርጊት ሰርተን የጨረስንበትን ቆይታ የተለያዩ አሀዶችን በመጠቀም እንለካለን፡፡ ይኸውም በአመታት፣ በወራት፣ በሳምንታት፣ ወይም ደግሞ በቀናት፣ በሰዓታት፣ በደቂቃዎችና በሴኮንዶች ሊሆን ይችላል፡፡
ከጊዜ መለኪያ ምድቦች አንጻር ከሴኮንድ በታች ያሉ ለመደበኛ ጊዜ መለኪያ የማንጠቀማቸው ነገር ግን ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ጥቃቅን ምድቦች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክልም ዴሲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ አስረኛ)፣ ሴንቲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ መቶኛ)፣ ሚሊ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሺኛ)፣ ማይክሮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሚሊዮንኛ)፣ ናኖ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ቢሊዮንኛ)፣ ፒኮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ትሪሊዮንኛ)፣ ፌምቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳድሪሊዮንኛ)፣ አቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳንቲሊዮንኛ)፣ ዜፕቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሲክስቲሊዮንኛ)፣ ዮክቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሴፕቲሊዮንኛ) እና ፐላንክ (Planck time) የሚታወቁት ናቸው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩት ምድቦች በጊዜ ምድብነት ይታወቁ እንጂ በቅርብ በወጣ ዘገባ ተመራማሪዎች የብርሃን ቅንጣቶች የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለመቋረጥ የሚወስድባቸውን የጊዜ ርዝማኔ መለካት ችለዋል፡፡ ይህም ልኬት እስካሁን ከተመዘገቡት ርዝማኔዎች የመጨረሻ ትንሹ የጊዜ ርዝማኔ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የብርሃን ቅንጣቶቹ የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለማቋረጥ የወሰደባቸው ጊዜም 247 ዜፕቶ ሴኮንድ (zeptoseconds) ሆኗል፡፡
ከዚህ በፊት በ1999 የኖቤል ሽልማት ማግኘት የቻለ በፌማቶ ሴኮንድ የተለካ የኬሚካል ቦንድ ለመሰራትና ለመከፈል (break and form) የሚወስደው ጊዜ ታውቆ ነበር፡፡
የዚህ ግኝት ተጨማሪ ማብራሪያዎች በጥቅምት 16 የሳይንስ ጆርናል ላይ ታትሟል፡፡
ምንጭ Science alert
====================
አንድን ድርጊት አከናውነን ለመፈጸም ርዝማኔው ወይም ቆይታው ይለያይ እንጂ ጊዜ ያስፈልገናል፡፡ ታዲያ አንድን ድርጊት ሰርተን የጨረስንበትን ቆይታ የተለያዩ አሀዶችን በመጠቀም እንለካለን፡፡ ይኸውም በአመታት፣ በወራት፣ በሳምንታት፣ ወይም ደግሞ በቀናት፣ በሰዓታት፣ በደቂቃዎችና በሴኮንዶች ሊሆን ይችላል፡፡
ከጊዜ መለኪያ ምድቦች አንጻር ከሴኮንድ በታች ያሉ ለመደበኛ ጊዜ መለኪያ የማንጠቀማቸው ነገር ግን ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ጥቃቅን ምድቦች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክልም ዴሲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ አስረኛ)፣ ሴንቲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ መቶኛ)፣ ሚሊ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሺኛ)፣ ማይክሮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሚሊዮንኛ)፣ ናኖ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ቢሊዮንኛ)፣ ፒኮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ትሪሊዮንኛ)፣ ፌምቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳድሪሊዮንኛ)፣ አቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳንቲሊዮንኛ)፣ ዜፕቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሲክስቲሊዮንኛ)፣ ዮክቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሴፕቲሊዮንኛ) እና ፐላንክ (Planck time) የሚታወቁት ናቸው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩት ምድቦች በጊዜ ምድብነት ይታወቁ እንጂ በቅርብ በወጣ ዘገባ ተመራማሪዎች የብርሃን ቅንጣቶች የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለመቋረጥ የሚወስድባቸውን የጊዜ ርዝማኔ መለካት ችለዋል፡፡ ይህም ልኬት እስካሁን ከተመዘገቡት ርዝማኔዎች የመጨረሻ ትንሹ የጊዜ ርዝማኔ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የብርሃን ቅንጣቶቹ የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለማቋረጥ የወሰደባቸው ጊዜም 247 ዜፕቶ ሴኮንድ (zeptoseconds) ሆኗል፡፡
ከዚህ በፊት በ1999 የኖቤል ሽልማት ማግኘት የቻለ በፌማቶ ሴኮንድ የተለካ የኬሚካል ቦንድ ለመሰራትና ለመከፈል (break and form) የሚወስደው ጊዜ ታውቆ ነበር፡፡
የዚህ ግኝት ተጨማሪ ማብራሪያዎች በጥቅምት 16 የሳይንስ ጆርናል ላይ ታትሟል፡፡
ምንጭ Science alert
መልካም ዜና
=======
ውድ ተከታታዮቻችን “BASIC PRODUCT SKETCHING TECHNIQUE” በሚል ርዕስ በኢንስቲትዩታችን ዩትዩብ ቻናል ላይ ያዘጋጀነውን ተከታታይ ስልጠና እየተከታተላችሁ ነው ?
ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በሰባተኛው (7ኛ) ክፍል ዲስክርፕሽን ላይ የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን የተዘጋጀውን ጥያቄ በወረቀት ላይ (A4 ወይም A3) በመስራት በኢሜይል አድራሻችን (stic.ethiopia@gmail.com) የምታደርሱን ይሆናል፡፡ ታድያ እስካሁን ጥያቄዎቹን ሞልታችሁ ለላካችሁልን ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀቱ የተዘጋጀላችሁ ሲሆን በቅርቡም ከእጃችሁ እንደምናደርስ መግለፅ እንወዳለን፡፡
ታድያ አሁንም ጊዜው አላለቀምና ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በስልጠናው ላይ የተዘጋጀውን ጥያቄ መልስ እስከ ዓርብ ጥቅምት 13 2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ በመላክ ሰርተፊኬት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ያሎት ጊዜ አጭር በመሆኑ ተከታታይ ስልጠናውን በሚገባ ተከታትለው የተዘጋጀውን ጥያቄ ሰርተው ይላኩልን ፡፡
ስለተከታተሉን እናመሰግናለን፡፡
=======
ውድ ተከታታዮቻችን “BASIC PRODUCT SKETCHING TECHNIQUE” በሚል ርዕስ በኢንስቲትዩታችን ዩትዩብ ቻናል ላይ ያዘጋጀነውን ተከታታይ ስልጠና እየተከታተላችሁ ነው ?
ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በሰባተኛው (7ኛ) ክፍል ዲስክርፕሽን ላይ የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን የተዘጋጀውን ጥያቄ በወረቀት ላይ (A4 ወይም A3) በመስራት በኢሜይል አድራሻችን (stic.ethiopia@gmail.com) የምታደርሱን ይሆናል፡፡ ታድያ እስካሁን ጥያቄዎቹን ሞልታችሁ ለላካችሁልን ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀቱ የተዘጋጀላችሁ ሲሆን በቅርቡም ከእጃችሁ እንደምናደርስ መግለፅ እንወዳለን፡፡
ታድያ አሁንም ጊዜው አላለቀምና ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በስልጠናው ላይ የተዘጋጀውን ጥያቄ መልስ እስከ ዓርብ ጥቅምት 13 2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ በመላክ ሰርተፊኬት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ያሎት ጊዜ አጭር በመሆኑ ተከታታይ ስልጠናውን በሚገባ ተከታትለው የተዘጋጀውን ጥያቄ ሰርተው ይላኩልን ፡፡
ስለተከታተሉን እናመሰግናለን፡፡
እንጀራን ለ24 ቀናት ሳይሻግት የሚያቆየው ምርምር ማብራርያ ተሰሠጠበት
===================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር እዮቤል ሙሉጌታ በትብብር የተሰራውንና እንጀራ ሳይሻግት እስከ 24 ቀናት ድረስ ማቆየት በሚችለው የምርምር ውጤት ዙርያ ዛሬ ጠዋት በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ ተገኝተው ገለፃ አቅርበዋል፡፡
ዶ/ር እዮቤል በገለፃቸው በአሁኑ ወቅት አንጀራ ከሦስት ወይም አራት ቀናት በኋላ እንደሚበላሽና ለዚህም በዋነኝነት ፔኔሲሊየም ጨምሮ ሶስት የፈንገስ አይነቶች ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ጠቅሰው እንጀራውን ሳይበላሽ ለማቆየት በሚደረገው የማሞቅ እና ሌሎች ተግባራት ወቅት የሚደርሰውን የኃይል ብክነትንና በተለይ ስራውን በዋናነት በሚያከናውኑት እናቶቻችን ላይ የሚያስከትለውን ቀላል የማይባል የስራ ጫና ገልፀዋል፡፡ ሶስት አራተኛው ኢትዮጵያውያን የእንጀራ ተመጋቢ መሆናችንን ያወሱት ዶ/ር እዩቤል የዚህ ምርምር ግኝት ወደ ተግባር መለወጥ በማህበራዊ፣ ምጣኔ ሀብት፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ኃይል ቁጠባ ብሎም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ አውንታዊ ሚናን እንደሚጫወትም አብራርተዋል፡፡
ምርምሩ ሲልቨር እና ዚንክ ኦክሳይድን በናኖ ፓርቲክል ደረጃ በመጠቀም የሚሰራ ሲሆን ውህዱን በእንጀራ ማስቀመጫው ላይ በማኖር ብቻ ነው ለዚህ ያህል ጊዜ እንዲቆይ ማድረግ የተቻለው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በምርምሩ ላይ የተገኙ ዝርዝር የቤተ ሙከራ ውጤቶችን ለታዳሚያኑ አብራርተዋል፡፡
በገለፃው ላይ ተሳታፊ የነበሩት የኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎችም በቀረበው ምርምር ዙርያ ጥያቄ እና አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡ በመድረኩ ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል የፓርቲክል መጠኑ ሁኔታ፣ የጤና ተፅዕኖው፣ በዋጋ ደረጃ ያለው ተደራሽነት፣ ከሌሎች ምርምሮች ጋራ እንዴት በተመጋጋቢነት መሄድ እንደሚችል እና በጥናቱ ላይ በዋለው የጤፍ አይነት ላይ ያውጠነጠኑት ይገኙበታል፡፡
ጥያቄዎቹ ተገቢ መሆናቸውን በምላሻቸው ያነሱት ዶ/ር እዮቤል ምርምሩ በሁለተኛ ዲግሪ ማሟያነት የቀረበና ቀሪ ስራዎች መኖራቸው ከግምት ይገባ ዘንድ አሳስበዋል፡፡ በጥያቄዎቹ ላይም ዝርዝር ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከሌሎች የፈጠራ ባለሙያና ምርምሮች ጋራም ወደፊት በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም ምርምሩ ወደ ህብረተሰቡ ከመድረሱ በፊት በጤና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተፅዕንዖ፣ የፓርቲከሎቹ መጠን ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮችም በቂ ምርምር እንደሚደረግባቸው ዶ/ር እዮቤል አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በፊት እንጀራን ሳይሻግት ለ12 ቀናት ያህል ለማቆየት የሚያስችል ምርምር የተሰራ ቢሆንም የእንጀራውን ጣዕም እንዲቀይር የያደረገ ነበር፡፡ በአንፃሩ አዲሱ መርምር የዚህ አይነት ለውጥ የማያስከትል መሆኑን ዶ/ር እዮቤል ገልፀዋል፡፡
ምርምሩ በቀጣይ ለህዝብ ይፋ የሚደረግ ሲሆን እኛም በምርምሩ ዙርያ ዝርዝር ዘገባን ይዘንልዎ የምንመጣ ይሆናል፡፡
===================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ማዕከል ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር እዮቤል ሙሉጌታ በትብብር የተሰራውንና እንጀራ ሳይሻግት እስከ 24 ቀናት ድረስ ማቆየት በሚችለው የምርምር ውጤት ዙርያ ዛሬ ጠዋት በኢንስቲትዩቱ አዳራሽ ተገኝተው ገለፃ አቅርበዋል፡፡
ዶ/ር እዮቤል በገለፃቸው በአሁኑ ወቅት አንጀራ ከሦስት ወይም አራት ቀናት በኋላ እንደሚበላሽና ለዚህም በዋነኝነት ፔኔሲሊየም ጨምሮ ሶስት የፈንገስ አይነቶች ዋነኛ ምክንያት መሆናቸውን ጠቅሰው እንጀራውን ሳይበላሽ ለማቆየት በሚደረገው የማሞቅ እና ሌሎች ተግባራት ወቅት የሚደርሰውን የኃይል ብክነትንና በተለይ ስራውን በዋናነት በሚያከናውኑት እናቶቻችን ላይ የሚያስከትለውን ቀላል የማይባል የስራ ጫና ገልፀዋል፡፡ ሶስት አራተኛው ኢትዮጵያውያን የእንጀራ ተመጋቢ መሆናችንን ያወሱት ዶ/ር እዩቤል የዚህ ምርምር ግኝት ወደ ተግባር መለወጥ በማህበራዊ፣ ምጣኔ ሀብት፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ኃይል ቁጠባ ብሎም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ አውንታዊ ሚናን እንደሚጫወትም አብራርተዋል፡፡
ምርምሩ ሲልቨር እና ዚንክ ኦክሳይድን በናኖ ፓርቲክል ደረጃ በመጠቀም የሚሰራ ሲሆን ውህዱን በእንጀራ ማስቀመጫው ላይ በማኖር ብቻ ነው ለዚህ ያህል ጊዜ እንዲቆይ ማድረግ የተቻለው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም በምርምሩ ላይ የተገኙ ዝርዝር የቤተ ሙከራ ውጤቶችን ለታዳሚያኑ አብራርተዋል፡፡
በገለፃው ላይ ተሳታፊ የነበሩት የኢንስቲትዩቱ ተመራማሪዎችም በቀረበው ምርምር ዙርያ ጥያቄ እና አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡ በመድረኩ ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል የፓርቲክል መጠኑ ሁኔታ፣ የጤና ተፅዕኖው፣ በዋጋ ደረጃ ያለው ተደራሽነት፣ ከሌሎች ምርምሮች ጋራ እንዴት በተመጋጋቢነት መሄድ እንደሚችል እና በጥናቱ ላይ በዋለው የጤፍ አይነት ላይ ያውጠነጠኑት ይገኙበታል፡፡
ጥያቄዎቹ ተገቢ መሆናቸውን በምላሻቸው ያነሱት ዶ/ር እዮቤል ምርምሩ በሁለተኛ ዲግሪ ማሟያነት የቀረበና ቀሪ ስራዎች መኖራቸው ከግምት ይገባ ዘንድ አሳስበዋል፡፡ በጥያቄዎቹ ላይም ዝርዝር ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከሌሎች የፈጠራ ባለሙያና ምርምሮች ጋራም ወደፊት በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም ምርምሩ ወደ ህብረተሰቡ ከመድረሱ በፊት በጤና ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተፅዕንዖ፣ የፓርቲከሎቹ መጠን ሁኔታ እና ሌሎች ጉዳዮችም በቂ ምርምር እንደሚደረግባቸው ዶ/ር እዮቤል አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በፊት እንጀራን ሳይሻግት ለ12 ቀናት ያህል ለማቆየት የሚያስችል ምርምር የተሰራ ቢሆንም የእንጀራውን ጣዕም እንዲቀይር የያደረገ ነበር፡፡ በአንፃሩ አዲሱ መርምር የዚህ አይነት ለውጥ የማያስከትል መሆኑን ዶ/ር እዮቤል ገልፀዋል፡፡
ምርምሩ በቀጣይ ለህዝብ ይፋ የሚደረግ ሲሆን እኛም በምርምሩ ዙርያ ዝርዝር ዘገባን ይዘንልዎ የምንመጣ ይሆናል፡፡
የኮቪድ-19 ገጸ-በረከቶች
=============
በኮቪድ 19 ምክንያት የተጣሉ ገደቦችና የኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መቀዛቀዝ በአለማችን ጉዳት ብቻ ሳይሆን ጥቅምንም ይዘው መጥተዋል፡፡ በተለይ ከአየር ንብረት ብክለት አንጻር የታየው ለውጥ አለማችን ያላትን የኃይል አጠቃቀምና ልቀት ልምድ እንደገና መከለስ እንዳለባት በሰፊው ያመላከተ ነው፡፡ ናሽናል ጆግራፊክ መጽሔት በያዝነው ወር እትሙ ወረርሽኙ ከአየር ንብረት አንጻር ያበረከተውን አስተዋጽኦ በሶስት ከፍሎ አቅርቦታል፡፡ እኛም በዚህ መልክ በአጭሩ አዘጋጅተንላችኋል፡፡
1ኛ. በካርበን ልቀት በአንድ አመት ብቻ ትልቅ የሚባል ቅናሽ ኮቪድ 19 አምጥቷል፡፡ መጽሔቱ ይህን ለካርበን ልቀት መቆም መባቻ ይሆናል የሚል ሀሳብ አስፍሯል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ የካርቦን ልቀት አስከ 2024 የተጠበቀ ቢሆንም ኮቪድ 19 ሁኔታውን ሳያፋጥነው አልቀረም፡፡ በወረርሽኙ ምክንያት የነበረው የእንቅስቃሴ ገደብና የግዙፋን ፋብሪካዎች ስራ መቀነስ የነበረውን የካርበን ልቀት በሚገርም ሁኔታ ቀንሶታል፡፡ ይህ ግን ለጊዜው መሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ የአለም መንግስታት ከዚህ በመነሳት ለካርበን ልቀት መቀነስ ምክንያት የነበሩ ነገሮችን መጣኔ ሐብት እና ማህበራዊ እንቅስቃሴውን በማይጎዳ መልኩ ስራቸውን ከብክለት ነጻ የሚደርጉበትን መንገድ በአፋጣኝ መፈለግ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም ለተከታታይ አመታት ያክል የካርቦን ጥቅል ልቀቱ ዜሮ እስኪሆን ድረስ መሰራት አለበት፡፡
2ኛ. ኮቪድ 19 የተናጥል እርምጃ የአለም ሙቀትን ለመቀነስ በቂ እንደማይሆን አስተምሯል፡፡ ኮቪድ 19 በኃይል አጠቃቀም ዙሪያ የሚሮረውን ተጽዕኖ በሚያመለክት ትንተናው በአሁኑ ወቅት አማራጭ ኃይል መፈለግ፣ የኃይል አጠቃቀምን ማሻሻልና የትራንስፖርት ኃይል አቅርቦት አማራጭ መጠቀም ተገቢ እንደሆነ አመላክቷል፡፡ በያዝነው አመት የነዳጅ ዘይት ፍላጎት በአየርና ሌሎች ትራንስፖርት እንቅስቃሴ መቆም ምክንያት 60 በመቶ የሚሆነው ፍላጎት ቀንሷል፡፡ ይህም ከካርበን ልቀት መቀነስ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው፡፡ በ2040 የነፋስና የፀሐይ ኃይል አማራጮች ፍላጎት ከአጠቃላይ የድፍድፍ ነዳጅ ፍላጎት 34 በመቶ የሚሆነውን ይሸፍናሉ ተብሎ ተገምቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት እየመጡ ያሉ ቴክኖሎጂዎች እና በትኩረት የሚሰሩ ፖሊሲዎች የአለም አቀፍ የኃይል አማራጭ ሽግግሩን ያፋጥኑታል፡፡ በኮቪድ ምክንያት የታየውን የካርበን ልቀት መቀነስ ካሉን የፖሊሲ ግቦች ጋር ማስተሳሰር የመነሻ ትግባር ሊሆን ይገባል፡፡
3ኛ. የዛሬ የምጣኔ-ሐብት ማገገሚያ እቅዶች የወደፊት የአየር ንብረት ሁኔታን ይወስናሉ፡፡ ከኃይል ጋር የተያያዘ ኢንቨስትመንት በ2020 ያድጋል ተብሎ የታለመ ቢሆንም በኮቪድ ምክንት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የነዳጅ ዘይት ዋጋ እና የገበያ ተፈላጊነት በዚያው ልክ ወርዷል፡፡ መንግስታት በአሁኑ ወቀት የነበረውን የምጣኔ-ሐብት መቀዛቀዝ ሊያነቃቁ የሚችሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ላይ ናቸው፡፡ በመሆኑም አለማችን አሁን ካለው የካርበን ልቀት በላይ ላታስተናግድ ስለምትችል የሚሰሩት የምጣኔ ሐብት ማነቃቂያ ተግባራት ከተፈጥሮ ጋር የተስማሙ ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡
ምንጭ National Geographic
=============
በኮቪድ 19 ምክንያት የተጣሉ ገደቦችና የኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች መቀዛቀዝ በአለማችን ጉዳት ብቻ ሳይሆን ጥቅምንም ይዘው መጥተዋል፡፡ በተለይ ከአየር ንብረት ብክለት አንጻር የታየው ለውጥ አለማችን ያላትን የኃይል አጠቃቀምና ልቀት ልምድ እንደገና መከለስ እንዳለባት በሰፊው ያመላከተ ነው፡፡ ናሽናል ጆግራፊክ መጽሔት በያዝነው ወር እትሙ ወረርሽኙ ከአየር ንብረት አንጻር ያበረከተውን አስተዋጽኦ በሶስት ከፍሎ አቅርቦታል፡፡ እኛም በዚህ መልክ በአጭሩ አዘጋጅተንላችኋል፡፡
1ኛ. በካርበን ልቀት በአንድ አመት ብቻ ትልቅ የሚባል ቅናሽ ኮቪድ 19 አምጥቷል፡፡ መጽሔቱ ይህን ለካርበን ልቀት መቆም መባቻ ይሆናል የሚል ሀሳብ አስፍሯል፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ የካርቦን ልቀት አስከ 2024 የተጠበቀ ቢሆንም ኮቪድ 19 ሁኔታውን ሳያፋጥነው አልቀረም፡፡ በወረርሽኙ ምክንያት የነበረው የእንቅስቃሴ ገደብና የግዙፋን ፋብሪካዎች ስራ መቀነስ የነበረውን የካርበን ልቀት በሚገርም ሁኔታ ቀንሶታል፡፡ ይህ ግን ለጊዜው መሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ የአለም መንግስታት ከዚህ በመነሳት ለካርበን ልቀት መቀነስ ምክንያት የነበሩ ነገሮችን መጣኔ ሐብት እና ማህበራዊ እንቅስቃሴውን በማይጎዳ መልኩ ስራቸውን ከብክለት ነጻ የሚደርጉበትን መንገድ በአፋጣኝ መፈለግ ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም ለተከታታይ አመታት ያክል የካርቦን ጥቅል ልቀቱ ዜሮ እስኪሆን ድረስ መሰራት አለበት፡፡
2ኛ. ኮቪድ 19 የተናጥል እርምጃ የአለም ሙቀትን ለመቀነስ በቂ እንደማይሆን አስተምሯል፡፡ ኮቪድ 19 በኃይል አጠቃቀም ዙሪያ የሚሮረውን ተጽዕኖ በሚያመለክት ትንተናው በአሁኑ ወቅት አማራጭ ኃይል መፈለግ፣ የኃይል አጠቃቀምን ማሻሻልና የትራንስፖርት ኃይል አቅርቦት አማራጭ መጠቀም ተገቢ እንደሆነ አመላክቷል፡፡ በያዝነው አመት የነዳጅ ዘይት ፍላጎት በአየርና ሌሎች ትራንስፖርት እንቅስቃሴ መቆም ምክንያት 60 በመቶ የሚሆነው ፍላጎት ቀንሷል፡፡ ይህም ከካርበን ልቀት መቀነስ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው፡፡ በ2040 የነፋስና የፀሐይ ኃይል አማራጮች ፍላጎት ከአጠቃላይ የድፍድፍ ነዳጅ ፍላጎት 34 በመቶ የሚሆነውን ይሸፍናሉ ተብሎ ተገምቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት እየመጡ ያሉ ቴክኖሎጂዎች እና በትኩረት የሚሰሩ ፖሊሲዎች የአለም አቀፍ የኃይል አማራጭ ሽግግሩን ያፋጥኑታል፡፡ በኮቪድ ምክንያት የታየውን የካርበን ልቀት መቀነስ ካሉን የፖሊሲ ግቦች ጋር ማስተሳሰር የመነሻ ትግባር ሊሆን ይገባል፡፡
3ኛ. የዛሬ የምጣኔ-ሐብት ማገገሚያ እቅዶች የወደፊት የአየር ንብረት ሁኔታን ይወስናሉ፡፡ ከኃይል ጋር የተያያዘ ኢንቨስትመንት በ2020 ያድጋል ተብሎ የታለመ ቢሆንም በኮቪድ ምክንት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ የነዳጅ ዘይት ዋጋ እና የገበያ ተፈላጊነት በዚያው ልክ ወርዷል፡፡ መንግስታት በአሁኑ ወቀት የነበረውን የምጣኔ-ሐብት መቀዛቀዝ ሊያነቃቁ የሚችሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ላይ ናቸው፡፡ በመሆኑም አለማችን አሁን ካለው የካርበን ልቀት በላይ ላታስተናግድ ስለምትችል የሚሰሩት የምጣኔ ሐብት ማነቃቂያ ተግባራት ከተፈጥሮ ጋር የተስማሙ ሊሆኑ ይገባቸዋል፡፡
ምንጭ National Geographic
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የተዘጋጀው አዲስ የፖሊሲ ጥናት
=====================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጥናት ዳይሬክቶሬት “Data Privacy Policy for Ethiopia and the need for Compliance with International Standards” በሚል ርዕስ የፖሊሲ ጥናት አውጥቷል፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ የተደራጀና ሁሉን አለም አቀፍ ስታንዳርዶችን ያሟላ የመረጃ/ጥሬ ሀቅ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ላይ የተለያዩ አመክንዮዎችን በመንተራስ ምክረ ሀሳብ የሚያቀርብ ነው፡፡
ያደጉት ሀገራት የዛሬ 40 እና 50 ዓመታት ገደማ ግለሰባዊ መረጃን የሚጠብቁ ሕጎችን ሲተገብሩ መኖራቸውን ያወሳው ጥናቱ በአንፃሩ ሀገራችን ላይ አሁንም ድረስ ይህን ሁኔታ ባልተደራጁና በቂ ባልሆኑ ሕጎች ለመቆጣጠር እየዳከርን መሆኑን ይጠቁማል፡፡
የፖሊሲ ጥናቱ በኢትዮጵያ የመረጃ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ በሌሎች ሀገራት ደረጃ ካለው የፖሊሲ እና ህግጋት ጋራ አለመጣጠም በተለይም ሀገራችንን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ወይም ኢ-ኮሜርስ ስርዓቱን በሚፈለገው ልክ እንዳታሳድግ እና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ብሎም ሀገራት ከእኛ ጋራ እንዲሰሩ የማያስችል ሁኔታ እንደሚፈጥር የአውሮፓ ህብረት እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሕግጋትን በተግባራዊ ምሳሌነት አስደግፎ አትቷል፡፡
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ በቅርብ መረጃ እና ግንኙነት ቴክሎጂዎችን (ICT) ጨምሮ ስድስት አባይት ዘርፎች ዋና የትኩረት ማዕከል አድርጎ የያዘ አዲስ የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ ማውጣቷ ይታወሳል፡፡ ይህ መሪ ዕቅድ ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገና ለስኬቱም ያለው ወሳኝነት የማያጠራጥር መሆኑ ዘርፉን የዲጂታል ጥሬ ሀቅን (Data) በሚቆጣጠሩ ሕግጋቶች ለመደገፍ እንደሚገደድ ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከሚከፍተው አዲስ የዕድል በር እና አሁን ያለንበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሁኔታ ያለ ሕግ እና ፖሊሲ ብዙም የማያራምድ መሆኑ በረቂቁ ላይ ተቀምጧል፡፡
ጥናቱ ግለሰባዊ መረጃን ከሚጠብቁ ፖሊሲ እና ሕግጋት አስፈላጊነት ባሻገርም በሀገራችን በአሁኑ ሰዓት ያለውን የግለሰባዊ መረጃ አጠባበቅ ሁኔታ እንዲሁም የICT ፖሊሲ እና ሌሎች ከጉዳዩ ጋራ ግንኙነት ያላቸው ወሳኝ ሕግጋቶችንም የቃኘ ነው፡፡
ሙሉ ጥናቱን ቀጥሎ የተቀመጠውን pdf ፋይል በመክፈት ያገኙታል፡፡
=====================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ጥናት ዳይሬክቶሬት “Data Privacy Policy for Ethiopia and the need for Compliance with International Standards” በሚል ርዕስ የፖሊሲ ጥናት አውጥቷል፡፡ ጥናቱ በኢትዮጵያ የተደራጀና ሁሉን አለም አቀፍ ስታንዳርዶችን ያሟላ የመረጃ/ጥሬ ሀቅ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ላይ የተለያዩ አመክንዮዎችን በመንተራስ ምክረ ሀሳብ የሚያቀርብ ነው፡፡
ያደጉት ሀገራት የዛሬ 40 እና 50 ዓመታት ገደማ ግለሰባዊ መረጃን የሚጠብቁ ሕጎችን ሲተገብሩ መኖራቸውን ያወሳው ጥናቱ በአንፃሩ ሀገራችን ላይ አሁንም ድረስ ይህን ሁኔታ ባልተደራጁና በቂ ባልሆኑ ሕጎች ለመቆጣጠር እየዳከርን መሆኑን ይጠቁማል፡፡
የፖሊሲ ጥናቱ በኢትዮጵያ የመረጃ ጥበቃ ፖሊሲ አልያም ሕግ መኖር አስፈላጊነት ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ በሌሎች ሀገራት ደረጃ ካለው የፖሊሲ እና ህግጋት ጋራ አለመጣጠም በተለይም ሀገራችንን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ወይም ኢ-ኮሜርስ ስርዓቱን በሚፈለገው ልክ እንዳታሳድግ እና ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ብሎም ሀገራት ከእኛ ጋራ እንዲሰሩ የማያስችል ሁኔታ እንደሚፈጥር የአውሮፓ ህብረት እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሕግጋትን በተግባራዊ ምሳሌነት አስደግፎ አትቷል፡፡
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ በቅርብ መረጃ እና ግንኙነት ቴክሎጂዎችን (ICT) ጨምሮ ስድስት አባይት ዘርፎች ዋና የትኩረት ማዕከል አድርጎ የያዘ አዲስ የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ ማውጣቷ ይታወሳል፡፡ ይህ መሪ ዕቅድ ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገና ለስኬቱም ያለው ወሳኝነት የማያጠራጥር መሆኑ ዘርፉን የዲጂታል ጥሬ ሀቅን (Data) በሚቆጣጠሩ ሕግጋቶች ለመደገፍ እንደሚገደድ ተነግሯል፡፡ በተጨማሪም ከሚከፍተው አዲስ የዕድል በር እና አሁን ያለንበት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሁኔታ ያለ ሕግ እና ፖሊሲ ብዙም የማያራምድ መሆኑ በረቂቁ ላይ ተቀምጧል፡፡
ጥናቱ ግለሰባዊ መረጃን ከሚጠብቁ ፖሊሲ እና ሕግጋት አስፈላጊነት ባሻገርም በሀገራችን በአሁኑ ሰዓት ያለውን የግለሰባዊ መረጃ አጠባበቅ ሁኔታ እንዲሁም የICT ፖሊሲ እና ሌሎች ከጉዳዩ ጋራ ግንኙነት ያላቸው ወሳኝ ሕግጋቶችንም የቃኘ ነው፡፡
ሙሉ ጥናቱን ቀጥሎ የተቀመጠውን pdf ፋይል በመክፈት ያገኙታል፡፡
ሀሰተኛ መረጃ እና የአዕምሮ ጫና
================
በአለማችን የማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የሀሰተኛ መረጃ መጠንና የዝውውር ፍጥነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ሀሰተኛ መረጃ መሰራጨት ከመጀመሩ በፊት አዘጋጆቹ በቅድሚያ ሰዎች መስማት የሚፈልጉትን ወቅታዊ እና ትኩረት ሳቢ የሆነውን ጉዳይ ይለያሉ፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው በጣም ቀላል ነው፤ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከመሰረታቸው መረጃን ከአንድ ጫፍ ወደ ሌላ ጫፍ በፍጥነት በማዘዋወር የታዎቁ በመሆናቸው በደቂቃዎች ውስጥ ሰፊ ተመልካች ያገኛል፡፡ በይዘት ደረጃ ይዘቱ ምንም ዓይነት ይሁን ወቅታዊና ሰዎች መስማት የሚፈልጉት ከሆነ ሀሰተኛው መረጃ ተመርቶ ይቀርባል፡፡
የደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ተመራማሪዎች በሰሩት ትንተና በ2016 የአሜሪካ ምርጫ ወቅት 20 በመቶ የሚሆኑ የትዊተር መረጃዎች ሀሰተኛ ነበሩ፡፡
በኢቫንስቶን ሰሜን ምዕራብ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ እድገት ተመራማሪ የሆነው ዴቪድ ራፕ ሰዎች በብዛት ወቅታዊ የፖለቲካ አቋማቸውን የሚደግፍ ማንኛውንም መረጃ ይቀበላሉ ሲል ልዩ ልዩ ምርምሮችን ዋቢ አድርጎ ይናገራል፡፡ ተመራማሪው በተጨማሪም አንድ ጽሁፍ ሀሰት እንደሆነ እያወቅን እንኳን እውነት እንዲሆን ካለን ፍላጎት የተነሳ እንቀበለዋለን ይላል፡፡ የዚህ አይነቱ የተሳሳተ መረጃ በልዩ ልዩ ውሳኔዎቻችን ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳረፉ አይቀርም፡፡
ብዛት ያላቸው ሀሰተኛ መረጃዎችን ባነበብን ቁጥር አዕምሯችን በዚሁ የተሞላ ይሆናል፡፡ በዚህ ረገድ የተለያዩ ሙከራዎችን ያደረጉት የተመራማሪዎች ቡድን አንድን ሀሰተኛ መረጃ በተደጋጋሚ የምንሰማው ከሆነ ለአዕምሯችን እውነት እየሆነ ይመጣል፡፡ ለምሳሌ "ዛፎች ከመኪና ይልቅ ለአየር ብክለት መንስኤ ናቸው" የሚል ሀሰተኛ መረጃን በተደጋጋሚ ብንሰማውና እኛ የምናውቃቸው እና የምንደግፋቸው ጥቂት ሰዎች ሀሳቡን ቢቀበሉት ሀሳቡን መርህ አድርገን ተፈጥሮን ከዛፎች እንታደግ ማለታችን የማይቀር ነው፡፡ ይህ ምሳሌ የሀሰተኛ መረጃን አደገኝነትና በአዕምሯችን ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በቀላሉ የሚያሳይ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪም ልቦለዶቸ ላይ የምናነባቸው መረጃዎችን እንደ እውነተኛ መረጃዎች በመውሰድ አቋም ልንይዝባቸው እንችላለን፡፡ ይህም ከነባራዊው እውነታ ይልቅ ለማስታዎስ ከልቦለድ ጽሁፍ ያገኘነው መረጃ ለአእምሯችን ስለሚቀል ነው፡፡
ምንጭ Science news magazine
================
በአለማችን የማህበራዊ ሚዲያ እየተስፋፋ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ የሀሰተኛ መረጃ መጠንና የዝውውር ፍጥነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ሀሰተኛ መረጃ መሰራጨት ከመጀመሩ በፊት አዘጋጆቹ በቅድሚያ ሰዎች መስማት የሚፈልጉትን ወቅታዊ እና ትኩረት ሳቢ የሆነውን ጉዳይ ይለያሉ፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው በጣም ቀላል ነው፤ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከመሰረታቸው መረጃን ከአንድ ጫፍ ወደ ሌላ ጫፍ በፍጥነት በማዘዋወር የታዎቁ በመሆናቸው በደቂቃዎች ውስጥ ሰፊ ተመልካች ያገኛል፡፡ በይዘት ደረጃ ይዘቱ ምንም ዓይነት ይሁን ወቅታዊና ሰዎች መስማት የሚፈልጉት ከሆነ ሀሰተኛው መረጃ ተመርቶ ይቀርባል፡፡
የደቡብ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ተመራማሪዎች በሰሩት ትንተና በ2016 የአሜሪካ ምርጫ ወቅት 20 በመቶ የሚሆኑ የትዊተር መረጃዎች ሀሰተኛ ነበሩ፡፡
በኢቫንስቶን ሰሜን ምዕራብ ዩኒቨርሲቲ የስነ-አዕምሮ እድገት ተመራማሪ የሆነው ዴቪድ ራፕ ሰዎች በብዛት ወቅታዊ የፖለቲካ አቋማቸውን የሚደግፍ ማንኛውንም መረጃ ይቀበላሉ ሲል ልዩ ልዩ ምርምሮችን ዋቢ አድርጎ ይናገራል፡፡ ተመራማሪው በተጨማሪም አንድ ጽሁፍ ሀሰት እንደሆነ እያወቅን እንኳን እውነት እንዲሆን ካለን ፍላጎት የተነሳ እንቀበለዋለን ይላል፡፡ የዚህ አይነቱ የተሳሳተ መረጃ በልዩ ልዩ ውሳኔዎቻችን ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ማሳረፉ አይቀርም፡፡
ብዛት ያላቸው ሀሰተኛ መረጃዎችን ባነበብን ቁጥር አዕምሯችን በዚሁ የተሞላ ይሆናል፡፡ በዚህ ረገድ የተለያዩ ሙከራዎችን ያደረጉት የተመራማሪዎች ቡድን አንድን ሀሰተኛ መረጃ በተደጋጋሚ የምንሰማው ከሆነ ለአዕምሯችን እውነት እየሆነ ይመጣል፡፡ ለምሳሌ "ዛፎች ከመኪና ይልቅ ለአየር ብክለት መንስኤ ናቸው" የሚል ሀሰተኛ መረጃን በተደጋጋሚ ብንሰማውና እኛ የምናውቃቸው እና የምንደግፋቸው ጥቂት ሰዎች ሀሳቡን ቢቀበሉት ሀሳቡን መርህ አድርገን ተፈጥሮን ከዛፎች እንታደግ ማለታችን የማይቀር ነው፡፡ ይህ ምሳሌ የሀሰተኛ መረጃን አደገኝነትና በአዕምሯችን ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በቀላሉ የሚያሳይ ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪም ልቦለዶቸ ላይ የምናነባቸው መረጃዎችን እንደ እውነተኛ መረጃዎች በመውሰድ አቋም ልንይዝባቸው እንችላለን፡፡ ይህም ከነባራዊው እውነታ ይልቅ ለማስታዎስ ከልቦለድ ጽሁፍ ያገኘነው መረጃ ለአእምሯችን ስለሚቀል ነው፡፡
ምንጭ Science news magazine
አስደናቂው የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ
*******************************
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ እንዲሁም ሰውነታችን የሚፈልጋቸውን ጠቃሚ ንጥረ ምግቦች የያዘ ነው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የደም ግፊትን ይቀንሳል፣ አጥንትን ያጠነክራል፣ የኮሊስትሮል መጠንን ይቀንሳል፣ ክብደት ለመቀነስ ያግዛል እንዲሁም ትኩሳትንና ልዩ ልዩ የጤና መታወክን በማጥፋት ጭንቀትን ይቀንሳል፡፡ ጭማቂው በተጨማሪም ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት፣ የሰውነት ሐይልን ለመጨመር፣ የኩላሊትን ጤና ለመጠበቅ፣ቆዳን ለመንከባከብ፣ ስርዓተ እንሽርስሪትን (የምግብ መፈጨትን) ለማስተካከልና የበሽታ መከላከል አቅምን ለማሳደግ ይረዳል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ምንድን ነው?
ይህ ጭማቂ በጣእሙ ከሚታወቀው እና ለገበታ ስኳር ማምረቻ ዋና ግባት ከሆነው የሸንኮራ አገዳ ተክል የሚሰራ ነው፡፡ የዚህ ተክል በሳይንሳዊ መጠሪያው ሳቻረም ኦፊሲናረም (Saccharum officinarum) በመባል ይታወቃል፡፡ ሳቻረም የሚለው የጥፍጥናውን መጠን የሚያሳይ ነው፡፡ ጭማቂው በሸንኮራ አገዳ ምርታቸው በሚታወቁት እንደ ብራዚል፣ ህንድ እና ታይላንድ ባሉ ሀገራት የታወቀ ነው፡፡ በአብዛኛው ጭማቂው የብረት መጭመቂያ በመጠቀም ከሸንኮራ አገዳ በፍጥነት የሚዘጋጅ ነው፡፡ በብዛት ከበረዶና ከሎሚ ካር ተቀላቅሎ በቀዝቃዛ መጠጥነት የሚቀርብ ሲሆን አንኳር ጨውና ዝንጅብልም እንደመቀመሚያነት ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ለሌሎች ምርቶችም ዋና ግብአት በመሆን ያገለግላል፡፡ ለምሳሌ ያክልም ሞላሰስ፣ ኢታኖልና ባዮፊውል ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ ይዘት
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከፍተኛ መጠን ያለው ፖታሺየም፣ ካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ብረት፣ ማንጋኔዝ፣ የተለያዩ አሚኖ አሲዶች፣ ዚንክ፣ ቲያሚን እና ሪቦፍላቢን የያዘ ነው፡፡ ከ224 ግራም ጭማቂ 180 ካሎሪ እና 30 ግራም ስኳር ማግኘት እንችላለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለሰውነታችን ጤንነት በጣም አስፈላጊ የሆኑ ውህዶችን በውስጡ የያዘ ነው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ጥቅሞች
ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ዋና ዋና ጥቅሞች መካከል የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡
የሰውነት ሀይልን ከፍ ደርጋል፡ በፋብሪካዎች ተቀምመው ከሚመጡ ምግብና መጠጦች በተለየ መልኩ ለሰውነታችን ከፍተኛ ሀይል የሚሰጥ የተመጣጠነ ስኳር ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ማግኘት እንችላለን፡፡
የቆዳችንን ጤንነት ይጠብቃል፡ ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ይዘቶች አንዱ አልፋ ሀይድሮ ኦክሳይድ አሲዶች መካከል የሆነው ግላይኮሊክ አሲድ ነው፡፡ ይህ አሲድ የቆዳ ላይ ሽፍታንና ቁስለትን በማስወገድ ጥራት ያለው ቆዳ እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ እንዲሁም አዘውትረን የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምንጠጣ ከሆነ በእድሜ ምክንያት የሚመጣን የቆዳ መሸብሸብ ያስወግዳል፡፡
ምቹ ለሆነ የእርግዝና ወቅት፡ በእርግዝና ወቅት የሚወሰድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ መፈጨትን በአግባቡ እንዲከናዎን በማድረግ ጥዋት ጥዋት የሚስተዋልን የሆድ ቁርጠት ያስወግዳል፡፡ እንዲሁም በእርግዝና ወቅት የሐይል እጥረት እንዳያጋጥም ያደርጋል፡፡ ተፈጥሯዊ የሆነ የበሽታ መከላከል አቅምን ከፍ ያደርጋል፡፡
መጥፎ የአፍ ጠረንን ያስወግዳል፡ የጥርስ መበስበስን ለማስወገድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ፍቱን መድሀኒት ነው፡፡ ሸንኮራ በተፈጥሮ ካልሺየምና ፎስፈረስ የተባሉ ማዕድናት ያለው በመሆኑ የጥርስ መበስበስ ችግርን በማስወገድ ለጥርሳችን ጥንካሬን ይሰጣል፡፡ በጭማቂው ውስጥ ያለው ከፍተኛ መጠን ማዕድን በእጥረት ምክንያት የሚመጣን የአፍ ጠረን ያስወግዳል፡፡
አጥንትን ያጠነክራል፡ ጭማቂው በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙ ካልሺየም፣ ብረት፣ ፖታሺየም፣ ማግኒዢየምና የማንጋኔዝ መጠንን በማመጣጠን አጥንታችንን ያጠነክራል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከመጠን በላይ የምንጠጣ ከሆነ ተጓዳኝ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የራስ ምታት፣ የሆድ ህመም፣ ትውኪያና የእንቅልፍ ማጣት ሊያስከትል ይችላል፡፡ ይህ እንዳይሆን በቀን ውስጥ አንድ ብርችጭቆ ብቻ መጠቀም ተገቢ ነው፡፡
ምንጭ፡ www.organicfacts www.indianrecips
*******************************
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ እንዲሁም ሰውነታችን የሚፈልጋቸውን ጠቃሚ ንጥረ ምግቦች የያዘ ነው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የደም ግፊትን ይቀንሳል፣ አጥንትን ያጠነክራል፣ የኮሊስትሮል መጠንን ይቀንሳል፣ ክብደት ለመቀነስ ያግዛል እንዲሁም ትኩሳትንና ልዩ ልዩ የጤና መታወክን በማጥፋት ጭንቀትን ይቀንሳል፡፡ ጭማቂው በተጨማሪም ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት፣ የሰውነት ሐይልን ለመጨመር፣ የኩላሊትን ጤና ለመጠበቅ፣ቆዳን ለመንከባከብ፣ ስርዓተ እንሽርስሪትን (የምግብ መፈጨትን) ለማስተካከልና የበሽታ መከላከል አቅምን ለማሳደግ ይረዳል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ምንድን ነው?
ይህ ጭማቂ በጣእሙ ከሚታወቀው እና ለገበታ ስኳር ማምረቻ ዋና ግባት ከሆነው የሸንኮራ አገዳ ተክል የሚሰራ ነው፡፡ የዚህ ተክል በሳይንሳዊ መጠሪያው ሳቻረም ኦፊሲናረም (Saccharum officinarum) በመባል ይታወቃል፡፡ ሳቻረም የሚለው የጥፍጥናውን መጠን የሚያሳይ ነው፡፡ ጭማቂው በሸንኮራ አገዳ ምርታቸው በሚታወቁት እንደ ብራዚል፣ ህንድ እና ታይላንድ ባሉ ሀገራት የታወቀ ነው፡፡ በአብዛኛው ጭማቂው የብረት መጭመቂያ በመጠቀም ከሸንኮራ አገዳ በፍጥነት የሚዘጋጅ ነው፡፡ በብዛት ከበረዶና ከሎሚ ካር ተቀላቅሎ በቀዝቃዛ መጠጥነት የሚቀርብ ሲሆን አንኳር ጨውና ዝንጅብልም እንደመቀመሚያነት ሊያገለግሉ ይችላሉ፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ለሌሎች ምርቶችም ዋና ግብአት በመሆን ያገለግላል፡፡ ለምሳሌ ያክልም ሞላሰስ፣ ኢታኖልና ባዮፊውል ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ ይዘት
አንድ ብርጭቆ ያልተቀመመ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ መጠጣት በጣም አስደናቂ የሆነ የጤና ጥቅም አለው፡፡ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከፍተኛ መጠን ያለው ፖታሺየም፣ ካልሺየም፣ ማግኒዥየም፣ ብረት፣ ማንጋኔዝ፣ የተለያዩ አሚኖ አሲዶች፣ ዚንክ፣ ቲያሚን እና ሪቦፍላቢን የያዘ ነው፡፡ ከ224 ግራም ጭማቂ 180 ካሎሪ እና 30 ግራም ስኳር ማግኘት እንችላለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለሰውነታችን ጤንነት በጣም አስፈላጊ የሆኑ ውህዶችን በውስጡ የያዘ ነው፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ጥቅሞች
ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ዋና ዋና ጥቅሞች መካከል የሚከተሉትን ማየት ይቻላል፡፡
የሰውነት ሀይልን ከፍ ደርጋል፡ በፋብሪካዎች ተቀምመው ከሚመጡ ምግብና መጠጦች በተለየ መልኩ ለሰውነታችን ከፍተኛ ሀይል የሚሰጥ የተመጣጠነ ስኳር ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ማግኘት እንችላለን፡፡
የቆዳችንን ጤንነት ይጠብቃል፡ ከሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ይዘቶች አንዱ አልፋ ሀይድሮ ኦክሳይድ አሲዶች መካከል የሆነው ግላይኮሊክ አሲድ ነው፡፡ ይህ አሲድ የቆዳ ላይ ሽፍታንና ቁስለትን በማስወገድ ጥራት ያለው ቆዳ እንዲኖረን ያደርጋል፡፡ እንዲሁም አዘውትረን የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምንጠጣ ከሆነ በእድሜ ምክንያት የሚመጣን የቆዳ መሸብሸብ ያስወግዳል፡፡
ምቹ ለሆነ የእርግዝና ወቅት፡ በእርግዝና ወቅት የሚወሰድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ የምግብ መፈጨትን በአግባቡ እንዲከናዎን በማድረግ ጥዋት ጥዋት የሚስተዋልን የሆድ ቁርጠት ያስወግዳል፡፡ እንዲሁም በእርግዝና ወቅት የሐይል እጥረት እንዳያጋጥም ያደርጋል፡፡ ተፈጥሯዊ የሆነ የበሽታ መከላከል አቅምን ከፍ ያደርጋል፡፡
መጥፎ የአፍ ጠረንን ያስወግዳል፡ የጥርስ መበስበስን ለማስወገድ የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ፍቱን መድሀኒት ነው፡፡ ሸንኮራ በተፈጥሮ ካልሺየምና ፎስፈረስ የተባሉ ማዕድናት ያለው በመሆኑ የጥርስ መበስበስ ችግርን በማስወገድ ለጥርሳችን ጥንካሬን ይሰጣል፡፡ በጭማቂው ውስጥ ያለው ከፍተኛ መጠን ማዕድን በእጥረት ምክንያት የሚመጣን የአፍ ጠረን ያስወግዳል፡፡
አጥንትን ያጠነክራል፡ ጭማቂው በሰውነታችን ውስጥ የሚገኙ ካልሺየም፣ ብረት፣ ፖታሺየም፣ ማግኒዢየምና የማንጋኔዝ መጠንን በማመጣጠን አጥንታችንን ያጠነክራል፡፡
የሸንኮራ አገዳ ጭማቂ ከመጠን በላይ የምንጠጣ ከሆነ ተጓዳኝ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የራስ ምታት፣ የሆድ ህመም፣ ትውኪያና የእንቅልፍ ማጣት ሊያስከትል ይችላል፡፡ ይህ እንዳይሆን በቀን ውስጥ አንድ ብርችጭቆ ብቻ መጠቀም ተገቢ ነው፡፡
ምንጭ፡ www.organicfacts www.indianrecips