የእይታ ትኩረትን (focus) ማስተካከል የሚችለው መነጽር
******************************
የሰው ልጅ እድሜ እየጨመረ በሔደ ቁጥር መደበኛ ስራቸውን መስራት እየተሳናቸው የሚሔዱ የሰውነት ክፍሎች መኖራቸው ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ከእነዚህ የሰውነት ክፍሎች መካከል አይናችን በቅርበትም ሆነ በርቀት የማየት ችግር በብዛት ያጋጥመዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ሐኪም ሔደን ለአይናችን ችግር መፍትሔ ሊሆን የሚችል የአይን መነጽር ይታዘዝልናል፡፡ እዚህ ላይ ያለው ችግር በትእዛዝ የምንገዛቸው መነጽሮች ለአንድ ተግባር ብቻ የሚውሉና ዋጋቸውም በጣም ውድ መሆኑ ነው፡፡ በሐኪም ያልታዘዘ ወይም በህክምና ያልተረጋገጠ መነጽር መጠቀም ከሚሰጠው ጥቅም የሚያስከትለው ጉዳት ይበልጣል፡፡
በአይን ህክምና ረገድ በአለማችን ብዙ አዳዲስ ነገሮች ያሉ ሲሆን የተጠቃሚውን የማየት ፍላጎት ተከትሎ የእይታ ትኩረት (focus) የሚያስተካክል መነጽር አንደኛው ነው፡፡ በእስራኤሉ Deep Optics የቴክኖሎጂ ተቋም የተመረተው ይህ የአይን መነጽር ምንም አይነት ብዥታ እንዳኖር ማድረግ የሚችል ነው፡፡
መነጽሩ የተገጠመለት ሙሉ እይታ "liquid crystal" lens በኤሌክትሪካዊ መንገድ ከሴንሰሩ ወደ ፕሮሰሰሩ በሚላክ መረጃ የእታን ትኩረት (view focus) ወዲያውኑ ያስተካክላል፡፡ በዚህም ምክንያት ተጠቃሚው ከቅርብም ሆነ ከሩቅ ማየት የሚፈልገውን ማንኛውንም ነገር በግልጽ መመልከት እንዲችል ያደርገዋል፡፡ 'omnifocals' የተባለው የካምፓኒው ምርት በቅርብ ያሉ ነገሮችን የማየት ችግር (presbyopia) ለመቅረፍ ታስቦ የተሰራ ነው፡፡
ምንጭ: www.howstuffworks.com
******************************
የሰው ልጅ እድሜ እየጨመረ በሔደ ቁጥር መደበኛ ስራቸውን መስራት እየተሳናቸው የሚሔዱ የሰውነት ክፍሎች መኖራቸው ተፈጥሯዊ ነው፡፡ ከእነዚህ የሰውነት ክፍሎች መካከል አይናችን በቅርበትም ሆነ በርቀት የማየት ችግር በብዛት ያጋጥመዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ሐኪም ሔደን ለአይናችን ችግር መፍትሔ ሊሆን የሚችል የአይን መነጽር ይታዘዝልናል፡፡ እዚህ ላይ ያለው ችግር በትእዛዝ የምንገዛቸው መነጽሮች ለአንድ ተግባር ብቻ የሚውሉና ዋጋቸውም በጣም ውድ መሆኑ ነው፡፡ በሐኪም ያልታዘዘ ወይም በህክምና ያልተረጋገጠ መነጽር መጠቀም ከሚሰጠው ጥቅም የሚያስከትለው ጉዳት ይበልጣል፡፡
በአይን ህክምና ረገድ በአለማችን ብዙ አዳዲስ ነገሮች ያሉ ሲሆን የተጠቃሚውን የማየት ፍላጎት ተከትሎ የእይታ ትኩረት (focus) የሚያስተካክል መነጽር አንደኛው ነው፡፡ በእስራኤሉ Deep Optics የቴክኖሎጂ ተቋም የተመረተው ይህ የአይን መነጽር ምንም አይነት ብዥታ እንዳኖር ማድረግ የሚችል ነው፡፡
መነጽሩ የተገጠመለት ሙሉ እይታ "liquid crystal" lens በኤሌክትሪካዊ መንገድ ከሴንሰሩ ወደ ፕሮሰሰሩ በሚላክ መረጃ የእታን ትኩረት (view focus) ወዲያውኑ ያስተካክላል፡፡ በዚህም ምክንያት ተጠቃሚው ከቅርብም ሆነ ከሩቅ ማየት የሚፈልገውን ማንኛውንም ነገር በግልጽ መመልከት እንዲችል ያደርገዋል፡፡ 'omnifocals' የተባለው የካምፓኒው ምርት በቅርብ ያሉ ነገሮችን የማየት ችግር (presbyopia) ለመቅረፍ ታስቦ የተሰራ ነው፡፡
ምንጭ: www.howstuffworks.com
ትምህርትና ቅድመ ጥንቃቄ
***********************
ባለፈው ዓመት መጋቢት የሆነ ቀን ህጻናት ትምህርት ቤት ክፍላቸው ውስጥ ነበሩ፡፡ በሌላኛው ቀን ግን ያልተጠበቀ ዱብእዳ መጣና ትምህር ቤቶች ተዘጉ፡፡ ያ ተማሪዎች እንደዋዛ ጥለውት የወጡት ክፍል አሁን ምንም እንኳን ወረርሽኙን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ባይቻልም ህይወት መቀጠል አለበትና ዳግም ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በክፍል ውስጥ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል መጠቀም በመማሪያ ክፍል ውስጥ አየር በብዛት እንዳይንቀሳቀስ ያደርገዋል፡፡ ይህም የተማሪዎቹን በቫይረሱ የመያዝ እድል በተወሰነ መልኩ ይቀንሰዋል፡፡ አካላዊ ርቀትን መጠበቅና ጭንብል መልበስ እንዳለ ሆኖ ሊደረጉ የሚገባቸውን ወሳኝ ጥንቃቄዎች ልናስነብባችሁ ወደድን፡፡
1ኛ. በቂ አየር (ventilation)
አሁን ባለው ሁኔታ በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20-25 ተማሪዎችን 2 ሜትር ያክል አራርቆ ማስቀመጥ እና ማስተማር የሚያስችል የመማሪያ ክፍል ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፡፡ በመሆኑም በክፍል ውስጥ በቂ አየር እንዲዎጣ እና እንዲገባ አስፈላጊው ዝግጅት መደረግ አለበት፡፡ ይህም ሲባል የመማሪ ክፍሉ በርና መስኮቶች አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸውን ማረጋገጥና ጥብቅ በሆነ መመሪያ መከፈት ያለባቸው ተከፍተው ክፍሉ ንጹህ አየር የሚንቀሳቀስበት መሆን አለበት፡፡ ተማሪዎቹ የለበሱትን ጭንብል በየጊዜው እያወለቁ እንዳይቸገሩ ያደርጋቸዋል፡፡
2ኛ. የግቢና የክፍል ውስጥ ጥብቅ ዲሲፕሊን
በተለይ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች አካላዊ ርቀትን በመጠበቅና ጭምብል በአግባቡ በመልበስ በኩል ሊቸገሩ ይችላሉ፡፡ ከዚህ አንጻር መጀመሪያ ሊነሳ የሚችለው በእረፍት ላይ በነበሩበት ወቅት በቤት ውስጥ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ጭምብል የመልበስ ልምድ ስለማይኖራቸው በአግባቡ ላይጠቀሙት ይችላሉ፡፡ ስለዚህ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም አካል ራሱ መመሪውን በአግባቡ ተግብሮ ተማሪዎች እንዲተገብሩት ማድረግ የህይወትና የሞት ጉዳይ መሆኑን ማወቅ አለበት፡፡ በተቻለ መጠን በአመቱ ውስጥ ትልቁ የትምህርት ቤቶች ስራ ተማሪዎችና መምህራን ጤናቸው እንደተጠበቀ የመማር ማስተማር ስራውን ማስቀጠል ሊሆን ይገባዋል፡፡
3ኛ ስነ-ልቦናዊ ዝግጅት
በዚህ ወቅት በተማሪዎች አእምሮ ውስጥ ከሚርመሰመሱ ሀሳቦች መካከል ከፍተኛውን ድርሻ የሚወስደው የወረርሽኙ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም በቀጥታ በተማሪዎቹ ውጤት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል፡፡ ስለዚህ ወላጆችና መምህራን ተማሪዎች ጥንቃቄ ከማድረግ ባለፈ መጨነቅ እንደማይገባቸው እና ሙሉ ትኩረታቸውን ትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያደርጉ የምክር አገልግሎት በየጊዜው መስጠት ይኖርባቸዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች ውስጥ ከላይ የተዘረዘሩ ጥንቃቄዎች በትኩረት ሁላችንም መተግበር ከቻልን ወረርሽኙ ተስፋፍቶ ዳግም ትምህርት ቤቶች እንዳይዘጉና ተማሪዎቻችን ለሌላ ጭንቀት እንዳዳረጉ መጠበቅ እንችላለን፡፡
***********************
ባለፈው ዓመት መጋቢት የሆነ ቀን ህጻናት ትምህርት ቤት ክፍላቸው ውስጥ ነበሩ፡፡ በሌላኛው ቀን ግን ያልተጠበቀ ዱብእዳ መጣና ትምህር ቤቶች ተዘጉ፡፡ ያ ተማሪዎች እንደዋዛ ጥለውት የወጡት ክፍል አሁን ምንም እንኳን ወረርሽኙን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ባይቻልም ህይወት መቀጠል አለበትና ዳግም ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በክፍል ውስጥ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል መጠቀም በመማሪያ ክፍል ውስጥ አየር በብዛት እንዳይንቀሳቀስ ያደርገዋል፡፡ ይህም የተማሪዎቹን በቫይረሱ የመያዝ እድል በተወሰነ መልኩ ይቀንሰዋል፡፡ አካላዊ ርቀትን መጠበቅና ጭንብል መልበስ እንዳለ ሆኖ ሊደረጉ የሚገባቸውን ወሳኝ ጥንቃቄዎች ልናስነብባችሁ ወደድን፡፡
1ኛ. በቂ አየር (ventilation)
አሁን ባለው ሁኔታ በአንድ ክፍል ውስጥ ከ20-25 ተማሪዎችን 2 ሜትር ያክል አራርቆ ማስቀመጥ እና ማስተማር የሚያስችል የመማሪያ ክፍል ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፡፡ በመሆኑም በክፍል ውስጥ በቂ አየር እንዲዎጣ እና እንዲገባ አስፈላጊው ዝግጅት መደረግ አለበት፡፡ ይህም ሲባል የመማሪ ክፍሉ በርና መስኮቶች አገልግሎት የሚሰጡ መሆናቸውን ማረጋገጥና ጥብቅ በሆነ መመሪያ መከፈት ያለባቸው ተከፍተው ክፍሉ ንጹህ አየር የሚንቀሳቀስበት መሆን አለበት፡፡ ተማሪዎቹ የለበሱትን ጭንብል በየጊዜው እያወለቁ እንዳይቸገሩ ያደርጋቸዋል፡፡
2ኛ. የግቢና የክፍል ውስጥ ጥብቅ ዲሲፕሊን
በተለይ የ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች አካላዊ ርቀትን በመጠበቅና ጭምብል በአግባቡ በመልበስ በኩል ሊቸገሩ ይችላሉ፡፡ ከዚህ አንጻር መጀመሪያ ሊነሳ የሚችለው በእረፍት ላይ በነበሩበት ወቅት በቤት ውስጥ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች ጭምብል የመልበስ ልምድ ስለማይኖራቸው በአግባቡ ላይጠቀሙት ይችላሉ፡፡ ስለዚህ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም አካል ራሱ መመሪውን በአግባቡ ተግብሮ ተማሪዎች እንዲተገብሩት ማድረግ የህይወትና የሞት ጉዳይ መሆኑን ማወቅ አለበት፡፡ በተቻለ መጠን በአመቱ ውስጥ ትልቁ የትምህርት ቤቶች ስራ ተማሪዎችና መምህራን ጤናቸው እንደተጠበቀ የመማር ማስተማር ስራውን ማስቀጠል ሊሆን ይገባዋል፡፡
3ኛ ስነ-ልቦናዊ ዝግጅት
በዚህ ወቅት በተማሪዎች አእምሮ ውስጥ ከሚርመሰመሱ ሀሳቦች መካከል ከፍተኛውን ድርሻ የሚወስደው የወረርሽኙ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም በቀጥታ በተማሪዎቹ ውጤት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል፡፡ ስለዚህ ወላጆችና መምህራን ተማሪዎች ጥንቃቄ ከማድረግ ባለፈ መጨነቅ እንደማይገባቸው እና ሙሉ ትኩረታቸውን ትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያደርጉ የምክር አገልግሎት በየጊዜው መስጠት ይኖርባቸዋል፡፡
በትምህርት ቤቶች ውስጥ ከላይ የተዘረዘሩ ጥንቃቄዎች በትኩረት ሁላችንም መተግበር ከቻልን ወረርሽኙ ተስፋፍቶ ዳግም ትምህርት ቤቶች እንዳይዘጉና ተማሪዎቻችን ለሌላ ጭንቀት እንዳዳረጉ መጠበቅ እንችላለን፡፡
የደም ዓይነትና ኮቪድ 19
***********************
የሰዎች የደም ዓይነት በኮሮናቫይረስ ከመያዝና በጸና ህመም ከመሰቃየት ጋር ግንኙነት እንዳለው NBC news የተባለ የዜና ማሰራጫ ተቋም በዘገባው አስነብቧል፡፡ እንደማብራሪያው ይህ ሁኔታ ከደም አይነቶች መካከል አንዱ ለወረርሽኙ በጣም ተጋላጭ ያደርጋል የሚል መደምደሚያ ባይኖረውም የሚወጡት ግኝቶች ግን ከመልስ ይልቅ ብዙ ጥያቄዎችን ያስከተሉ ናቸው ተብሏል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የአሜሪካ ሄማቶሎጂ ሶሳይቲ ጆርናል ላይ የወጡት ሁለት ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን በሰዎች የደም ዓይነት እና በኮሮናቫይረስ ዙሪያ የሚነሱ ነጥቦችን በሚከተለው መልኩ ቃኝተዋቸዋል፡፡
በመጀመሪያው ጥናት በዴንማርክ 473,654 ሰዎች የኮቪድ ምርመራ ተደርጎላቸው አብዛኞቹ ነጻ ሲሆኑ ቫይረሱ የተገኘባቸው 7,422 ብቻ ነበሩ ይህም ከየካቲት እስከ ሐምሌ ድረስ ያለው መረጃ ነው፡፡ ከደም ዓይነቶች መካከል O በመባል የሚታዎቀው ያላቸው ሰዎች ለSARS-CoV-2 የተጋላጭነት እድላቸው አነስተኛ እንደሆነ ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ SARS-CoV-2 ለኮቪድ 19 መነሻ የሆነ ቫይረስ እንደሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ የጥናቱ ውጤት ከተመረመሩ ሰዎች መካከል 62 በመቶ ያክሉ ብቻ የደም አይነት መረጃ ያላቸው በመሆኑ እጥረት አለበት፡፡ መጠኑ ይነስ እንጂ O የደም ዓይነት ያላቸው ሰዎች የተጋላጭነት እድላቸው የቀነሰ ነው፡፡
ሌላኛው ጥናት በካናዳ የተደረገ ሲሆን ለሆስፒታል የሚያበቃ ህመም በገጠማቸው 95 የኮቪድ ታማሚዎች ላይ የተሰራ ነው፡፡ በጥናቱም ከታማሚዎች A ወይም AB የደም ዓነት ያላቸው ሰዎች የመተንፈሻ መሳሪያ ሲስፈልጋቸው ተስተውሏል፡፡ እንዲሁም በከፍተኛ ክትትል ክፍል (ICU) ውስጥ ረጅም ቆይታ አድርገዋል፡፡ ይህም O ወይም B የደም ዓይነት ካላቸው ሰዎች ጋር ሲነጻጸር ነው፡፡ A ወይም AB የደም ዓይነት ያላቸው ሰዎች ኩላሊታቸው የበለጠ ደም ማጣራት እንዲችል የዲያለሲስ እገዛም ተደርጎላቸዋል፡፡ በሁለቱም ጥናቶች ግን ይህ የደም አይነት የተጋላጭነት መጠኑ ዜሮ ነው የሚል ግኝት የለም፡፡
የማህበረሰብ ጤና ባለሙያዎች የትኛውም የደም ዓይነት ቢኖረንም ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችሉ መከላከያ መንገዶችን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ስለ ጥናቱ የWisconsin ሜዲካል ኮሌጅ ሀላፊ የሆኑት Dr. Roy Silverstein ለተጨማሪ ጥናቶች መነሻ የሚሆን ጥናት ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ NBC NEWS
***********************
የሰዎች የደም ዓይነት በኮሮናቫይረስ ከመያዝና በጸና ህመም ከመሰቃየት ጋር ግንኙነት እንዳለው NBC news የተባለ የዜና ማሰራጫ ተቋም በዘገባው አስነብቧል፡፡ እንደማብራሪያው ይህ ሁኔታ ከደም አይነቶች መካከል አንዱ ለወረርሽኙ በጣም ተጋላጭ ያደርጋል የሚል መደምደሚያ ባይኖረውም የሚወጡት ግኝቶች ግን ከመልስ ይልቅ ብዙ ጥያቄዎችን ያስከተሉ ናቸው ተብሏል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የአሜሪካ ሄማቶሎጂ ሶሳይቲ ጆርናል ላይ የወጡት ሁለት ጥናታዊ ጽሁፎች የቀረቡ ሲሆን በሰዎች የደም ዓይነት እና በኮሮናቫይረስ ዙሪያ የሚነሱ ነጥቦችን በሚከተለው መልኩ ቃኝተዋቸዋል፡፡
በመጀመሪያው ጥናት በዴንማርክ 473,654 ሰዎች የኮቪድ ምርመራ ተደርጎላቸው አብዛኞቹ ነጻ ሲሆኑ ቫይረሱ የተገኘባቸው 7,422 ብቻ ነበሩ ይህም ከየካቲት እስከ ሐምሌ ድረስ ያለው መረጃ ነው፡፡ ከደም ዓይነቶች መካከል O በመባል የሚታዎቀው ያላቸው ሰዎች ለSARS-CoV-2 የተጋላጭነት እድላቸው አነስተኛ እንደሆነ ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ SARS-CoV-2 ለኮቪድ 19 መነሻ የሆነ ቫይረስ እንደሆነ ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡ የጥናቱ ውጤት ከተመረመሩ ሰዎች መካከል 62 በመቶ ያክሉ ብቻ የደም አይነት መረጃ ያላቸው በመሆኑ እጥረት አለበት፡፡ መጠኑ ይነስ እንጂ O የደም ዓይነት ያላቸው ሰዎች የተጋላጭነት እድላቸው የቀነሰ ነው፡፡
ሌላኛው ጥናት በካናዳ የተደረገ ሲሆን ለሆስፒታል የሚያበቃ ህመም በገጠማቸው 95 የኮቪድ ታማሚዎች ላይ የተሰራ ነው፡፡ በጥናቱም ከታማሚዎች A ወይም AB የደም ዓነት ያላቸው ሰዎች የመተንፈሻ መሳሪያ ሲስፈልጋቸው ተስተውሏል፡፡ እንዲሁም በከፍተኛ ክትትል ክፍል (ICU) ውስጥ ረጅም ቆይታ አድርገዋል፡፡ ይህም O ወይም B የደም ዓይነት ካላቸው ሰዎች ጋር ሲነጻጸር ነው፡፡ A ወይም AB የደም ዓይነት ያላቸው ሰዎች ኩላሊታቸው የበለጠ ደም ማጣራት እንዲችል የዲያለሲስ እገዛም ተደርጎላቸዋል፡፡ በሁለቱም ጥናቶች ግን ይህ የደም አይነት የተጋላጭነት መጠኑ ዜሮ ነው የሚል ግኝት የለም፡፡
የማህበረሰብ ጤና ባለሙያዎች የትኛውም የደም ዓይነት ቢኖረንም ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችሉ መከላከያ መንገዶችን በአግባቡ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ስለ ጥናቱ የWisconsin ሜዲካል ኮሌጅ ሀላፊ የሆኑት Dr. Roy Silverstein ለተጨማሪ ጥናቶች መነሻ የሚሆን ጥናት ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ NBC NEWS
ቴክ-ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተሸላሚ ሆነ
====================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ተዘጋጅቶ ለአየር የሚበቃው የቴክ-ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራም የ2020 OFAB Ethiopia chapter annual award ውድድር ላይ የአንደኝነት ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡ ሽልማቱ የተበረከተው ፕሮግራሙ በቴሌቪዥን ስርጭት ዘርፍ በዓመቱ የግብርና ባዮ ቴክኖሎጂ ላይ በሰራቸው የሳይንስ ጋዜጠኝነት ስራዎች ነው፡፡
ውድድሩ ሲዘጋጅ ይህ ለአራተኛ ጊዜው ሲሆን ከቴሌቪዥን በተጨማሪም በህትመት እና ራድዮን ዘርፎች በየዓመቱ አወዳድሮ ሲሸልም ቆይቷል፡፡ ከዚህ በመቀጠልም ቴክ-ሳይንስን ጨምሮ በኢትዮጵያ ያሸነፉት ሦስት ተወዳዳሪዎች በአፍሪካ ደረጃ በሚደረገው መሰል ውድድር ተሳታፊ የሚሆኑ ይሆናል፡፡
ሽልማቱን ያበረከተው OFAB ወይም በሙሉ መጠሪያው Open Forum on Agricultural Biotechnology in Africa በዓለም አቀፉ የግብርና ከብቶች ጥናት ኢንስቲትዩት (ILRI) አማካኝነት የሚዘጋጅ ነው፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ በስምንት የአፍሪካ ሀገራት የሚንቀሳቀሰው ፎረሙ በባዮ ቴክኖሎጂ ዙርያ ያሉ ባለ ድርሻ አካላትን በእውቀት እና ልምድ በማስተሳሰር የባዮ ቴክኖሎጂን ትሩፋቶች ለአፍሪካውያን ገበሬ ብሎም ባለሀብቶች ለማቋደስ የሚሰራ ነው፡፡
ቴክ ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራምን ዘውትር ቅዳሜ በ10 ሰዓት በድጋሚ ደግሞ ማክሰኞ በ10 ሰዓት በ MOE TV ያገኙታል
በተጨማሪም የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ያመለጥዎትን ፕሮግራም እና ሌሎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዝግጅቶች ያግኙ>>> https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg
====================
በቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኢንስቲትዩት ተዘጋጅቶ ለአየር የሚበቃው የቴክ-ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራም የ2020 OFAB Ethiopia chapter annual award ውድድር ላይ የአንደኝነት ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡ ሽልማቱ የተበረከተው ፕሮግራሙ በቴሌቪዥን ስርጭት ዘርፍ በዓመቱ የግብርና ባዮ ቴክኖሎጂ ላይ በሰራቸው የሳይንስ ጋዜጠኝነት ስራዎች ነው፡፡
ውድድሩ ሲዘጋጅ ይህ ለአራተኛ ጊዜው ሲሆን ከቴሌቪዥን በተጨማሪም በህትመት እና ራድዮን ዘርፎች በየዓመቱ አወዳድሮ ሲሸልም ቆይቷል፡፡ ከዚህ በመቀጠልም ቴክ-ሳይንስን ጨምሮ በኢትዮጵያ ያሸነፉት ሦስት ተወዳዳሪዎች በአፍሪካ ደረጃ በሚደረገው መሰል ውድድር ተሳታፊ የሚሆኑ ይሆናል፡፡
ሽልማቱን ያበረከተው OFAB ወይም በሙሉ መጠሪያው Open Forum on Agricultural Biotechnology in Africa በዓለም አቀፉ የግብርና ከብቶች ጥናት ኢንስቲትዩት (ILRI) አማካኝነት የሚዘጋጅ ነው፡፡ ኢትዮጵያን ጨምሮ በስምንት የአፍሪካ ሀገራት የሚንቀሳቀሰው ፎረሙ በባዮ ቴክኖሎጂ ዙርያ ያሉ ባለ ድርሻ አካላትን በእውቀት እና ልምድ በማስተሳሰር የባዮ ቴክኖሎጂን ትሩፋቶች ለአፍሪካውያን ገበሬ ብሎም ባለሀብቶች ለማቋደስ የሚሰራ ነው፡፡
ቴክ ሳይንስ የቴሌቪዥን ፕሮግራምን ዘውትር ቅዳሜ በ10 ሰዓት በድጋሚ ደግሞ ማክሰኞ በ10 ሰዓት በ MOE TV ያገኙታል
በተጨማሪም የዩትዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ በማድረግ ያመለጥዎትን ፕሮግራም እና ሌሎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ዝግጅቶች ያግኙ>>> https://www.youtube.com/channel/UC6jvUOLRSkVEQtc5Annfwvg
የውሃ መጠን
********
የምድራችን 70 በመቶ የሚሆነው በውሀ የተሸፈነ እንደሆነ ይነገራል፡፡ የውቅያኖሶች አማካኝ ጥልቀት 12ሺ አንድ መቶ ጫማ ይደርሳል፡፡ ለመሆኑ በምድር ምን ያክል መጠን ውሀ አለ? መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ 326,000,000,000,000,000,000 (ሶስት መቶ ሀያ ስድስት ኳንቲሊዮን) ወይም 326 ሚሊዮን ትሪሊዮን ጋሎን ውሀ በምድራችን ላይ ይገኛል፡፡ ይህም በሊትር 1,260,000,000,000,000,000,000 ሊትር (አንድ ሲክስቲሊዮን ሁለት መቶ ስድሳ ኳንቲሊዮን) ይሆናል፡፡ ይህም የውሀ መጠን በመደበኛነት በዑደት የሚኖር ነው፡፡ የውቂያኖስ ውሃ በሙቀት ይተንና ተመልሶ ይዘንባል፡፡
በምድራችን ካለው የውሀ መጠን 98 በመቶ የሚሆነው የሚገኘው በውቂያኖስ ነው፡፡ ይህም በጨዋማነቱ የተነሳ ለመጠጥነት የማይውል ነው፡፡ ቀሪው ከ 3 በመቶ በታች የሚሆነው ውሀ ለመጠጥ መዋል የሚችል ቢሆንም ከዚህ ውስጥ 1.6 በመቶ የሚሆነው ከበረዶ በታች ያለ በመሆኑ መገኘት አይችልም፡፡ እንዲሁም ደግሞ 0.36 በመቶ የሚሆነው ከመሬት በታች የሚገኝ ነው፡፡
0.036 የሚሆነው ውሃ በወንዞችና በሀይቆች ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ይህ በጋሎን በሺዎች የሚቆጠር ትሪሊዮን ቢያክልም ከጠቅላላው አንጻር ዝቅተኛ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ያለው የምድራችን ውሀ በደመና መልክ እየተንቀሳቀሰ ወይም በእጽዋት ውስጥ ይገኛል፡፡ ከዚህም ሌላ አንድ ሰው 65 በመቶ የሚሆነው አካሉ ውሀ መሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡
ምንጭ www.hoestuffworks.com
********
የምድራችን 70 በመቶ የሚሆነው በውሀ የተሸፈነ እንደሆነ ይነገራል፡፡ የውቅያኖሶች አማካኝ ጥልቀት 12ሺ አንድ መቶ ጫማ ይደርሳል፡፡ ለመሆኑ በምድር ምን ያክል መጠን ውሀ አለ? መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ 326,000,000,000,000,000,000 (ሶስት መቶ ሀያ ስድስት ኳንቲሊዮን) ወይም 326 ሚሊዮን ትሪሊዮን ጋሎን ውሀ በምድራችን ላይ ይገኛል፡፡ ይህም በሊትር 1,260,000,000,000,000,000,000 ሊትር (አንድ ሲክስቲሊዮን ሁለት መቶ ስድሳ ኳንቲሊዮን) ይሆናል፡፡ ይህም የውሀ መጠን በመደበኛነት በዑደት የሚኖር ነው፡፡ የውቂያኖስ ውሃ በሙቀት ይተንና ተመልሶ ይዘንባል፡፡
በምድራችን ካለው የውሀ መጠን 98 በመቶ የሚሆነው የሚገኘው በውቂያኖስ ነው፡፡ ይህም በጨዋማነቱ የተነሳ ለመጠጥነት የማይውል ነው፡፡ ቀሪው ከ 3 በመቶ በታች የሚሆነው ውሀ ለመጠጥ መዋል የሚችል ቢሆንም ከዚህ ውስጥ 1.6 በመቶ የሚሆነው ከበረዶ በታች ያለ በመሆኑ መገኘት አይችልም፡፡ እንዲሁም ደግሞ 0.36 በመቶ የሚሆነው ከመሬት በታች የሚገኝ ነው፡፡
0.036 የሚሆነው ውሃ በወንዞችና በሀይቆች ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ይህ በጋሎን በሺዎች የሚቆጠር ትሪሊዮን ቢያክልም ከጠቅላላው አንጻር ዝቅተኛ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ያለው የምድራችን ውሀ በደመና መልክ እየተንቀሳቀሰ ወይም በእጽዋት ውስጥ ይገኛል፡፡ ከዚህም ሌላ አንድ ሰው 65 በመቶ የሚሆነው አካሉ ውሀ መሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡
ምንጭ www.hoestuffworks.com
ተጠንቶ የማያልቀው ስነ ከዋክብትና አዲስ መኖሪያ ፍለጋ
***************************************
የዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች 24 ፕላኔቶችን በፀሐይ ዙሪያ ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ The Cosmic Companion የተሰኘ የስነ-ከዋክብት መረጃዎችን የሚያዎጣው ተቋም እንደዘገበው ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ያላቸው 24 ፕላኔቶች የራሳቸው ከዋክብትንም የያዙ ናቸው፡፡
ፕላኔቶቹ የሚዞሯቸው አብዛኞቹ ከዋክብት ከፀሐይ በተሻለ መልኩ ለህይዎት ተስማሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ጂኦ ባዮሎጂስት የሆኑት Dirk Schulze-Makuch ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በታየባቸው ፕላኔቶች ተጨማሪ ጥናቶችን እናካሂዳለን ብለዋል፡፡
እነዚህ ምቹ መኖሪዎች ከመሬት የተሻለ ሙቀት፣ ርጥበት፣ መጠንና እድሜ ያላቸው እንደሚሆን ተገምቷል፡፡ ተመራማሪዎቹ እንዳሉት በጣም ረጅም እድሜ ያላቸው ፕላኔቶች ለአደገኛ ጨረር ሊያጋልጡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ለህይዎት አማራጭ ሊሆኑ የሚችሉት ፕላኔቶች ከ5 እስከ 8 ቢሊዮን ዓመት የሚደርስ ዕድሜ ያላቸው ናቸው፡፡
ከእድሜ በተጨማሪ የእነዚህን ፕላኔቶች ለህይዎት ምቹነት ክብደታቸውና መጠናቸው ይወስነዋል፡፡ በተጨማሪም መጠነ-ሙቀት የአዲስ ፕላኔት ፍለጋው አንድ አካል ነው፡፡ በአማካኝ 20 ዲግሪ ሴልሺየስ ያላቸው ፕላኔቶች ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ይኖራቸዋል፡፡
ምንጭ፡- The Cosmic Companion
***************************************
የዋሽንግተን ስቴት ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች 24 ፕላኔቶችን በፀሐይ ዙሪያ ማግኘታቸው ተሰማ፡፡ The Cosmic Companion የተሰኘ የስነ-ከዋክብት መረጃዎችን የሚያዎጣው ተቋም እንደዘገበው ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ያላቸው 24 ፕላኔቶች የራሳቸው ከዋክብትንም የያዙ ናቸው፡፡
ፕላኔቶቹ የሚዞሯቸው አብዛኞቹ ከዋክብት ከፀሐይ በተሻለ መልኩ ለህይዎት ተስማሚ ሊሆኑ እንደሚችሉ ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡ በዩኒቨርሲቲው ጂኦ ባዮሎጂስት የሆኑት Dirk Schulze-Makuch ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በታየባቸው ፕላኔቶች ተጨማሪ ጥናቶችን እናካሂዳለን ብለዋል፡፡
እነዚህ ምቹ መኖሪዎች ከመሬት የተሻለ ሙቀት፣ ርጥበት፣ መጠንና እድሜ ያላቸው እንደሚሆን ተገምቷል፡፡ ተመራማሪዎቹ እንዳሉት በጣም ረጅም እድሜ ያላቸው ፕላኔቶች ለአደገኛ ጨረር ሊያጋልጡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ለህይዎት አማራጭ ሊሆኑ የሚችሉት ፕላኔቶች ከ5 እስከ 8 ቢሊዮን ዓመት የሚደርስ ዕድሜ ያላቸው ናቸው፡፡
ከእድሜ በተጨማሪ የእነዚህን ፕላኔቶች ለህይዎት ምቹነት ክብደታቸውና መጠናቸው ይወስነዋል፡፡ በተጨማሪም መጠነ-ሙቀት የአዲስ ፕላኔት ፍለጋው አንድ አካል ነው፡፡ በአማካኝ 20 ዲግሪ ሴልሺየስ ያላቸው ፕላኔቶች ከምድራችን የተሻለ ምቹነት ይኖራቸዋል፡፡
ምንጭ፡- The Cosmic Companion
ስለ ዝሆን ምን ያህል ያውቃሉ?
ብዙዎቻችን ከልጅነት ጊዜያችን አንስቶ ስለ ዱር ስናስብ በምዕናባችን ከሚከሰቱት እንስሳት መካከል ዝሆኖች ቀዳሚ ናቸው፡፡ ዝሆኖች በምድራችን ከሚራመዱ እንስሳት ሁሉ በግዝፈታቸው ወደር የሌላቸው እና አፈጣጠራቸው ለየት ያሉ ናቸው፡፡ በረጀክሙ ኩምቢ፣ ግዙፍ ግን ልፍስፍስ ጆሮዎች፣ ወፋፍራም እግር ዝሆኖችን ከሌሎች እንስሳት የሚለዩ አካላዊ ገፅታዎቻቸው ናቸው፡፡
ብዙዎቹ ባለሙያዎች በሁለት አህጉራት የሚኖሩ ሁለት አይነት የዝሆን ዝርያዎች መኖራቸው ላይ ይስማማሉ፤ የአፍሪካ (Loxodonta africana) እና የእሲያ (Elephas maximus) ዝሆን ዝርያዎች፡፡ በእነዚህ ሁለት ዝርያዎች ስር የተለያዩ ቅርንጫረፍ ዝርያዎች አሉ፤ ምንም እንኳን ምን ያህል ናቸው በሚለው ላይ ክርክር ቢኖርም፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች የሳር ምድር (Loxodonta africana) እና የጫካ (Loxodonta cyclotis) ተብለው የተከፈሉ ሁለት የዘር ቅርንጫፍ ሲኖራቸው የእሲያዎቹ በበኩላቸው የህንድ (Elephas maximus indicus)፣ ስሪ ላንካ (Elephas maximus maximus) እና ሱማትራ (Elephas maximus sumatranus) የተሰኙ የዘር ቅርንጫፎች አሏቸው፡፡
የአፍሪካና እሲያ ዝሆኖች ልዩነት
የአፍሪካ ዝሆኖች ከሰሃራ በታች ባለው የአህጉራችን ክፍል በተለያዩ ስፍራዎች ይኖራሉ፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በበኩላቸው በኔፓል፣ ህንድ እና ደቡብ ምስራቅ እሲያ ጫካዎች ኑሯቸውን አድርገዋል፡፡ በግዝፈት ያነፃፀርን እንደሆነ የአፍሪካ ዝሆኖች ብልጫውን ይዘው እናገኛቸዋለን፡፡ ቁመታቸው ከ2.5 እስከ 4 ሜትር ሊደርስ ሲችል ክብደታቸውም ከ2,200 ኪ.ግ እስከ 6,350 ኪ.ግ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የእሲያ ዝሆኖች ከ2 እስከ 3 ሜትር ብቻ ሲረዝም ክብደታቸውም ከ2,000 እስከ 5,000 ኪ.ግ ብቻ ነው፡፡
ሁለቱ የዝሆን ዝርያዎች ከግዝፈትም ባሻገር ሌሎች ጥቂት ልዩነቶች አሏቸው፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች ጆሮ ገዘፍ ያለና ቅርፁም የአፍሪካ ካርታን የመሰለ ሲሆን የእሲያዎቹ ዝሆኖች በበኩሉ አነስ ያለና ክብ ቅርፅን የያዘ ነው፡፡ ወንዶቹም ሆነ ሴት የአፍሪካ ዝሆኖች ትላልቅ ጥርስና እቃ ለማንሳት የሚረዳ ሁለት ጣት መሰል ነገር በኩምቢያቸው ጫፍ አላቸው፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በኩምቢያቸው ላይ ያለው ጣት አንድ ብቻ ሲሆን ረጃጅም ጥርስ የሚያበቅሉትም ወንዶቹ ብቻ ናቸው፡፡ ሴቶቹ እና አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የእሲያ ዝሆኖች አነስተኛ መጠኑ አነስ ያለ ጥርስን ሲያበቅሉ ጥርሱ ወደ ውጪ ግን የማይታይ ሊሆን ይችላል፡፡
የዝሆን ጥርስ ግዙፍና ረጅም ስር ያላቸው ሲሆን ለዝሆኖቹ መቆፈርያ፣ እቃ ማንሻ፣ ምግብ መሰብሰብያ እና እራሳቸውን መከላከያ ሆኖ ሲያገለግላቸው ኩምቢውንም የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ እኛ የሰው ልጆች ግራኝ ወይም የቀኝ እጅ ተጠቃሚ እንደሆንነው ሁሉ ዝሆኖችም ግራኝ አልያም የቀኝ ቀንዳቸውን ተጠቃሚ ናቸው፡፡ የትኛውን እንደሚጠቀሙ ለማወቅ ቀላሉ መንገድ የደከመውን መለየት ነው፡፡
ሁለቱም የዝሆን ዝርያዎች የተለያዩ የሳር አይነቶችን፣ ፍራፍሬዎችን፣ ቅጠላ ቅጠሎችን፣ የዛፍ ቅርፊት እና ስር የመሳሰሉ የእፅዋት አካላትን ይመገባሉ፡፡ በቀን ውስጥ 16 ሰዓታትንም በመመገብ የሚያጠፉና በዚህም ከ75 እስከ 150 ኪ.ግ የሚሆን ምግብ የሚሰለቅጡ ናቸው፡፡
ማህበራዊ ህይወት
የዝሆኖች ቡድን ዕድሜያቸው በገፋ ሴቶች የሚመራ ነው፡፡ መንጋው በዋናነት በሴት ቤተሰቦችና ህፃናት ዝሆኖች ሲሞላ እንደ ምግብ አቅርቦቱ ከ6 እስከ 20 አባላትን ሊይዝ ይችላል፡፡ ቤተሰቡ ከሚፈለገው በላይ ሲበዛ በቅርብ አካባቢ ወደሚሰፍሩ የተለያዩ ቡድኖች ይከፈላል፡፡ መሪዋ ዝሆን ተግባሯን የምታከናውነው ልምዷን እና የትኛው ስፍራ ጥሩ ምግብ እና መጠለያ እንደያዘ የሚነግራት ትውስታዋን በመጠቀም ነው፡፡ በተጨማሪም ህፃናት ዝሆኖችን ከሌሎቹ ጋራ እንዴት መግባባት አንዳለባቸው የማስተማሩን ድርሻ ይወጣሉ፡፡
ዝሆኖች በከፍተኛ ሁኔታ ማህራዊ ኑሮን ከሚመሩ እንስሳት መካከል ናቸው፡፡ አንድ ዝሆን ከሌላው ጋራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን የሰው ልጆች መስማት የማንችለውን አነስተኛ ድምፅ በማውጣትም ከሶስት ኪ.ሜ በላይ ርቆ ያለ ዝሆንን መለየት ይችላሉ፡፡ በራሳቸውም ሆነ ሌላ ቡድን ውስጥ ላለ ዝሆንም መልካም ስነ-ምግባር በማሳየትም ይታወቃሉ፡፡ ለምሳሌ ሲገናኙ ኩምቢያቸውን ወደላይ ከፍ በማድረግ አልያም የኩምቢያቸውን ጫፍ ወደ ሌላኛው ዝሆን አፍ በመክተት ሰላምታ ይለዋወጣሉ፡፡ ከዚህ ባለፈም በመንጋቸው ውስጥ ያለ ሌላ የተጎዳ አባል ካለ የሚጠብቁና ስለሌላው የቡድኑ አባል ደህንነት ግድ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡
በሌላ መልኩ ዝሆኖች በማሰብ ችሎታቸው የማይታሙ መናቸው ይነገርላቸዋል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሆነው ውስብስብ ችግሮችን የመፍታት ብቃት ሲያሳዩ እንዲሁም ለቅሶ ሲደርሱና ሲያፅናኑ መታየታቸው ነው፡፡
ዕድሜ
ዝሆኖች ከተወለዱ ከ8 እስከ 13 ባሉት ዓመታት ውስጥ ለፆታዊ ግንኙነት ይደርሳሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ምግባቸውን ፈልገው ማግኘት እና እራሳቸውን መጠበቅ እስከቻሉ ድረስ ወንድ ዝሆኖች መንጋውን ትተው በመውጣት ለብቻቸው አልያም ከሌሎች መሰሎቻቸው ጋራ በአነስተኛ ቡድን ኑሮዋቸውን ይመራሉ፡፡
ሴቶቹ ዝሆኖች በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ እስከሚደርሱ ድረስ ልጅ የማይወልዱ ሲሆን ወንዶቹ ግን ዕድሜያቸው ሰላሳዎቹ ውስጥ እስከሚገባ ድረስም ልጅ ላይወልዱ ይችላሉ፡፡ አንድ የዝሆን ልጅ የሚወለደው ከ22 ወራት የእርግዝና ቆይታ በኋላ ነው፡፡ የሚወለዱት ጨቅላ ዝሆኖችም ከ68 እስከ 158 ኪ.ግ ክብደትና 90 ሴ.ሜ አካባቢ ቁመት ይዘው ይህችን ምድር ይቀላቀላሉ፡፡ በተጨማሪም ፀጉር እንዲሁም ረጅም ጭራና አጭር ኩምቢ ያላቸው ናቸው፡፡ ዕድገታቸው ግን እጅግ ፈጣን የሚባል ነው፤ በተወለዱ በአንድ ዓመት ውስጥ በየቀኑ ከ0.9 እስከ 1.3 ኪ.ግ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ ሶስት ዓመት ሲሞላቸውም መደበኛ ምግብ መመገብ ይጀምራሉ፡፡
አለም አቀፉ የተፈጥሮ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ሕብረት (IUCN) የእሲያ ዝሆኖች የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ናቸው ሲል ያስቀምጣቸዋል፡፡ ምንም እንኳን ሙሉ ቁጥራቸው ባይታወቅም እየቀነሱ መሆናቸው ግን ይታመናል፡፡ በአንፃሩ የአፍሪካ ዝሆኖች ቁጥራቸው በመጨመር ላይ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓትም 415,000 የአፍሪካ ዝሆኖች በየዱሩ ይገኛሉ፡፡ በአደጋ ስጋት ረገድ የአፍሪካንም ሆነ የእሲያ የዝሆን ዝርያዎችን የሚያመሳስላቸው የአደን እና የዘር ቅርንጫፎች የመጥፋት ስጋት የተጋረጠባቸው መሆኑ ነው፡፡
ምንጭ፡ Live Science
ብዙዎቻችን ከልጅነት ጊዜያችን አንስቶ ስለ ዱር ስናስብ በምዕናባችን ከሚከሰቱት እንስሳት መካከል ዝሆኖች ቀዳሚ ናቸው፡፡ ዝሆኖች በምድራችን ከሚራመዱ እንስሳት ሁሉ በግዝፈታቸው ወደር የሌላቸው እና አፈጣጠራቸው ለየት ያሉ ናቸው፡፡ በረጀክሙ ኩምቢ፣ ግዙፍ ግን ልፍስፍስ ጆሮዎች፣ ወፋፍራም እግር ዝሆኖችን ከሌሎች እንስሳት የሚለዩ አካላዊ ገፅታዎቻቸው ናቸው፡፡
ብዙዎቹ ባለሙያዎች በሁለት አህጉራት የሚኖሩ ሁለት አይነት የዝሆን ዝርያዎች መኖራቸው ላይ ይስማማሉ፤ የአፍሪካ (Loxodonta africana) እና የእሲያ (Elephas maximus) ዝሆን ዝርያዎች፡፡ በእነዚህ ሁለት ዝርያዎች ስር የተለያዩ ቅርንጫረፍ ዝርያዎች አሉ፤ ምንም እንኳን ምን ያህል ናቸው በሚለው ላይ ክርክር ቢኖርም፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች የሳር ምድር (Loxodonta africana) እና የጫካ (Loxodonta cyclotis) ተብለው የተከፈሉ ሁለት የዘር ቅርንጫፍ ሲኖራቸው የእሲያዎቹ በበኩላቸው የህንድ (Elephas maximus indicus)፣ ስሪ ላንካ (Elephas maximus maximus) እና ሱማትራ (Elephas maximus sumatranus) የተሰኙ የዘር ቅርንጫፎች አሏቸው፡፡
የአፍሪካና እሲያ ዝሆኖች ልዩነት
የአፍሪካ ዝሆኖች ከሰሃራ በታች ባለው የአህጉራችን ክፍል በተለያዩ ስፍራዎች ይኖራሉ፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በበኩላቸው በኔፓል፣ ህንድ እና ደቡብ ምስራቅ እሲያ ጫካዎች ኑሯቸውን አድርገዋል፡፡ በግዝፈት ያነፃፀርን እንደሆነ የአፍሪካ ዝሆኖች ብልጫውን ይዘው እናገኛቸዋለን፡፡ ቁመታቸው ከ2.5 እስከ 4 ሜትር ሊደርስ ሲችል ክብደታቸውም ከ2,200 ኪ.ግ እስከ 6,350 ኪ.ግ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የእሲያ ዝሆኖች ከ2 እስከ 3 ሜትር ብቻ ሲረዝም ክብደታቸውም ከ2,000 እስከ 5,000 ኪ.ግ ብቻ ነው፡፡
ሁለቱ የዝሆን ዝርያዎች ከግዝፈትም ባሻገር ሌሎች ጥቂት ልዩነቶች አሏቸው፡፡ የአፍሪካ ዝሆኖች ጆሮ ገዘፍ ያለና ቅርፁም የአፍሪካ ካርታን የመሰለ ሲሆን የእሲያዎቹ ዝሆኖች በበኩሉ አነስ ያለና ክብ ቅርፅን የያዘ ነው፡፡ ወንዶቹም ሆነ ሴት የአፍሪካ ዝሆኖች ትላልቅ ጥርስና እቃ ለማንሳት የሚረዳ ሁለት ጣት መሰል ነገር በኩምቢያቸው ጫፍ አላቸው፡፡ የእሲያ ዝሆኖች በኩምቢያቸው ላይ ያለው ጣት አንድ ብቻ ሲሆን ረጃጅም ጥርስ የሚያበቅሉትም ወንዶቹ ብቻ ናቸው፡፡ ሴቶቹ እና አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የእሲያ ዝሆኖች አነስተኛ መጠኑ አነስ ያለ ጥርስን ሲያበቅሉ ጥርሱ ወደ ውጪ ግን የማይታይ ሊሆን ይችላል፡፡
የዝሆን ጥርስ ግዙፍና ረጅም ስር ያላቸው ሲሆን ለዝሆኖቹ መቆፈርያ፣ እቃ ማንሻ፣ ምግብ መሰብሰብያ እና እራሳቸውን መከላከያ ሆኖ ሲያገለግላቸው ኩምቢውንም የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ እኛ የሰው ልጆች ግራኝ ወይም የቀኝ እጅ ተጠቃሚ እንደሆንነው ሁሉ ዝሆኖችም ግራኝ አልያም የቀኝ ቀንዳቸውን ተጠቃሚ ናቸው፡፡ የትኛውን እንደሚጠቀሙ ለማወቅ ቀላሉ መንገድ የደከመውን መለየት ነው፡፡
ሁለቱም የዝሆን ዝርያዎች የተለያዩ የሳር አይነቶችን፣ ፍራፍሬዎችን፣ ቅጠላ ቅጠሎችን፣ የዛፍ ቅርፊት እና ስር የመሳሰሉ የእፅዋት አካላትን ይመገባሉ፡፡ በቀን ውስጥ 16 ሰዓታትንም በመመገብ የሚያጠፉና በዚህም ከ75 እስከ 150 ኪ.ግ የሚሆን ምግብ የሚሰለቅጡ ናቸው፡፡
ማህበራዊ ህይወት
የዝሆኖች ቡድን ዕድሜያቸው በገፋ ሴቶች የሚመራ ነው፡፡ መንጋው በዋናነት በሴት ቤተሰቦችና ህፃናት ዝሆኖች ሲሞላ እንደ ምግብ አቅርቦቱ ከ6 እስከ 20 አባላትን ሊይዝ ይችላል፡፡ ቤተሰቡ ከሚፈለገው በላይ ሲበዛ በቅርብ አካባቢ ወደሚሰፍሩ የተለያዩ ቡድኖች ይከፈላል፡፡ መሪዋ ዝሆን ተግባሯን የምታከናውነው ልምዷን እና የትኛው ስፍራ ጥሩ ምግብ እና መጠለያ እንደያዘ የሚነግራት ትውስታዋን በመጠቀም ነው፡፡ በተጨማሪም ህፃናት ዝሆኖችን ከሌሎቹ ጋራ እንዴት መግባባት አንዳለባቸው የማስተማሩን ድርሻ ይወጣሉ፡፡
ዝሆኖች በከፍተኛ ሁኔታ ማህራዊ ኑሮን ከሚመሩ እንስሳት መካከል ናቸው፡፡ አንድ ዝሆን ከሌላው ጋራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን የሰው ልጆች መስማት የማንችለውን አነስተኛ ድምፅ በማውጣትም ከሶስት ኪ.ሜ በላይ ርቆ ያለ ዝሆንን መለየት ይችላሉ፡፡ በራሳቸውም ሆነ ሌላ ቡድን ውስጥ ላለ ዝሆንም መልካም ስነ-ምግባር በማሳየትም ይታወቃሉ፡፡ ለምሳሌ ሲገናኙ ኩምቢያቸውን ወደላይ ከፍ በማድረግ አልያም የኩምቢያቸውን ጫፍ ወደ ሌላኛው ዝሆን አፍ በመክተት ሰላምታ ይለዋወጣሉ፡፡ ከዚህ ባለፈም በመንጋቸው ውስጥ ያለ ሌላ የተጎዳ አባል ካለ የሚጠብቁና ስለሌላው የቡድኑ አባል ደህንነት ግድ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡
በሌላ መልኩ ዝሆኖች በማሰብ ችሎታቸው የማይታሙ መናቸው ይነገርላቸዋል፡፡ ለዚህ ማሳያ የሆነው ውስብስብ ችግሮችን የመፍታት ብቃት ሲያሳዩ እንዲሁም ለቅሶ ሲደርሱና ሲያፅናኑ መታየታቸው ነው፡፡
ዕድሜ
ዝሆኖች ከተወለዱ ከ8 እስከ 13 ባሉት ዓመታት ውስጥ ለፆታዊ ግንኙነት ይደርሳሉ፡፡ በዚህ ሰዓት ምግባቸውን ፈልገው ማግኘት እና እራሳቸውን መጠበቅ እስከቻሉ ድረስ ወንድ ዝሆኖች መንጋውን ትተው በመውጣት ለብቻቸው አልያም ከሌሎች መሰሎቻቸው ጋራ በአነስተኛ ቡድን ኑሮዋቸውን ይመራሉ፡፡
ሴቶቹ ዝሆኖች በአስራዎቹ አጋማሽ ላይ እስከሚደርሱ ድረስ ልጅ የማይወልዱ ሲሆን ወንዶቹ ግን ዕድሜያቸው ሰላሳዎቹ ውስጥ እስከሚገባ ድረስም ልጅ ላይወልዱ ይችላሉ፡፡ አንድ የዝሆን ልጅ የሚወለደው ከ22 ወራት የእርግዝና ቆይታ በኋላ ነው፡፡ የሚወለዱት ጨቅላ ዝሆኖችም ከ68 እስከ 158 ኪ.ግ ክብደትና 90 ሴ.ሜ አካባቢ ቁመት ይዘው ይህችን ምድር ይቀላቀላሉ፡፡ በተጨማሪም ፀጉር እንዲሁም ረጅም ጭራና አጭር ኩምቢ ያላቸው ናቸው፡፡ ዕድገታቸው ግን እጅግ ፈጣን የሚባል ነው፤ በተወለዱ በአንድ ዓመት ውስጥ በየቀኑ ከ0.9 እስከ 1.3 ኪ.ግ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ ሶስት ዓመት ሲሞላቸውም መደበኛ ምግብ መመገብ ይጀምራሉ፡፡
አለም አቀፉ የተፈጥሮ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ሕብረት (IUCN) የእሲያ ዝሆኖች የመጥፋት አደጋ የተጋረጠባቸው ናቸው ሲል ያስቀምጣቸዋል፡፡ ምንም እንኳን ሙሉ ቁጥራቸው ባይታወቅም እየቀነሱ መሆናቸው ግን ይታመናል፡፡ በአንፃሩ የአፍሪካ ዝሆኖች ቁጥራቸው በመጨመር ላይ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓትም 415,000 የአፍሪካ ዝሆኖች በየዱሩ ይገኛሉ፡፡ በአደጋ ስጋት ረገድ የአፍሪካንም ሆነ የእሲያ የዝሆን ዝርያዎችን የሚያመሳስላቸው የአደን እና የዘር ቅርንጫፎች የመጥፋት ስጋት የተጋረጠባቸው መሆኑ ነው፡፡
ምንጭ፡ Live Science
የምንጊዜውም አጭሩ የጊዜ ርዝማኔ
====================
አንድን ድርጊት አከናውነን ለመፈጸም ርዝማኔው ወይም ቆይታው ይለያይ እንጂ ጊዜ ያስፈልገናል፡፡ ታዲያ አንድን ድርጊት ሰርተን የጨረስንበትን ቆይታ የተለያዩ አሀዶችን በመጠቀም እንለካለን፡፡ ይኸውም በአመታት፣ በወራት፣ በሳምንታት፣ ወይም ደግሞ በቀናት፣ በሰዓታት፣ በደቂቃዎችና በሴኮንዶች ሊሆን ይችላል፡፡
ከጊዜ መለኪያ ምድቦች አንጻር ከሴኮንድ በታች ያሉ ለመደበኛ ጊዜ መለኪያ የማንጠቀማቸው ነገር ግን ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ጥቃቅን ምድቦች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክልም ዴሲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ አስረኛ)፣ ሴንቲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ መቶኛ)፣ ሚሊ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሺኛ)፣ ማይክሮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሚሊዮንኛ)፣ ናኖ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ቢሊዮንኛ)፣ ፒኮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ትሪሊዮንኛ)፣ ፌምቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳድሪሊዮንኛ)፣ አቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳንቲሊዮንኛ)፣ ዜፕቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሲክስቲሊዮንኛ)፣ ዮክቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሴፕቲሊዮንኛ) እና ፐላንክ (Planck time) የሚታወቁት ናቸው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩት ምድቦች በጊዜ ምድብነት ይታወቁ እንጂ በቅርብ በወጣ ዘገባ ተመራማሪዎች የብርሃን ቅንጣቶች የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለመቋረጥ የሚወስድባቸውን የጊዜ ርዝማኔ መለካት ችለዋል፡፡ ይህም ልኬት እስካሁን ከተመዘገቡት ርዝማኔዎች የመጨረሻ ትንሹ የጊዜ ርዝማኔ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የብርሃን ቅንጣቶቹ የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለማቋረጥ የወሰደባቸው ጊዜም 247 ዜፕቶ ሴኮንድ (zeptoseconds) ሆኗል፡፡
ከዚህ በፊት በ1999 የኖቤል ሽልማት ማግኘት የቻለ በፌማቶ ሴኮንድ የተለካ የኬሚካል ቦንድ ለመሰራትና ለመከፈል (break and form) የሚወስደው ጊዜ ታውቆ ነበር፡፡
የዚህ ግኝት ተጨማሪ ማብራሪያዎች በጥቅምት 16 የሳይንስ ጆርናል ላይ ታትሟል፡፡
ምንጭ Science alert
====================
አንድን ድርጊት አከናውነን ለመፈጸም ርዝማኔው ወይም ቆይታው ይለያይ እንጂ ጊዜ ያስፈልገናል፡፡ ታዲያ አንድን ድርጊት ሰርተን የጨረስንበትን ቆይታ የተለያዩ አሀዶችን በመጠቀም እንለካለን፡፡ ይኸውም በአመታት፣ በወራት፣ በሳምንታት፣ ወይም ደግሞ በቀናት፣ በሰዓታት፣ በደቂቃዎችና በሴኮንዶች ሊሆን ይችላል፡፡
ከጊዜ መለኪያ ምድቦች አንጻር ከሴኮንድ በታች ያሉ ለመደበኛ ጊዜ መለኪያ የማንጠቀማቸው ነገር ግን ለልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ጥቃቅን ምድቦች አሉ፡፡ ለምሳሌ ያክልም ዴሲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ አስረኛ)፣ ሴንቲ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ መቶኛ)፣ ሚሊ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሺኛ)፣ ማይክሮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሚሊዮንኛ)፣ ናኖ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ቢሊዮንኛ)፣ ፒኮ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ትሪሊዮንኛ)፣ ፌምቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳድሪሊዮንኛ)፣ አቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ኳንቲሊዮንኛ)፣ ዜፕቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሲክስቲሊዮንኛ)፣ ዮክቶ ሴኮንድ (የሴኮንድ አንድ ሴፕቲሊዮንኛ) እና ፐላንክ (Planck time) የሚታወቁት ናቸው፡፡
ከላይ የተዘረዘሩት ምድቦች በጊዜ ምድብነት ይታወቁ እንጂ በቅርብ በወጣ ዘገባ ተመራማሪዎች የብርሃን ቅንጣቶች የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለመቋረጥ የሚወስድባቸውን የጊዜ ርዝማኔ መለካት ችለዋል፡፡ ይህም ልኬት እስካሁን ከተመዘገቡት ርዝማኔዎች የመጨረሻ ትንሹ የጊዜ ርዝማኔ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ የብርሃን ቅንጣቶቹ የሃይድሮጅን ሞሎኪዩልን ለማቋረጥ የወሰደባቸው ጊዜም 247 ዜፕቶ ሴኮንድ (zeptoseconds) ሆኗል፡፡
ከዚህ በፊት በ1999 የኖቤል ሽልማት ማግኘት የቻለ በፌማቶ ሴኮንድ የተለካ የኬሚካል ቦንድ ለመሰራትና ለመከፈል (break and form) የሚወስደው ጊዜ ታውቆ ነበር፡፡
የዚህ ግኝት ተጨማሪ ማብራሪያዎች በጥቅምት 16 የሳይንስ ጆርናል ላይ ታትሟል፡፡
ምንጭ Science alert
መልካም ዜና
=======
ውድ ተከታታዮቻችን “BASIC PRODUCT SKETCHING TECHNIQUE” በሚል ርዕስ በኢንስቲትዩታችን ዩትዩብ ቻናል ላይ ያዘጋጀነውን ተከታታይ ስልጠና እየተከታተላችሁ ነው ?
ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በሰባተኛው (7ኛ) ክፍል ዲስክርፕሽን ላይ የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን የተዘጋጀውን ጥያቄ በወረቀት ላይ (A4 ወይም A3) በመስራት በኢሜይል አድራሻችን (stic.ethiopia@gmail.com) የምታደርሱን ይሆናል፡፡ ታድያ እስካሁን ጥያቄዎቹን ሞልታችሁ ለላካችሁልን ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀቱ የተዘጋጀላችሁ ሲሆን በቅርቡም ከእጃችሁ እንደምናደርስ መግለፅ እንወዳለን፡፡
ታድያ አሁንም ጊዜው አላለቀምና ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በስልጠናው ላይ የተዘጋጀውን ጥያቄ መልስ እስከ ዓርብ ጥቅምት 13 2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ በመላክ ሰርተፊኬት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ያሎት ጊዜ አጭር በመሆኑ ተከታታይ ስልጠናውን በሚገባ ተከታትለው የተዘጋጀውን ጥያቄ ሰርተው ይላኩልን ፡፡
ስለተከታተሉን እናመሰግናለን፡፡
=======
ውድ ተከታታዮቻችን “BASIC PRODUCT SKETCHING TECHNIQUE” በሚል ርዕስ በኢንስቲትዩታችን ዩትዩብ ቻናል ላይ ያዘጋጀነውን ተከታታይ ስልጠና እየተከታተላችሁ ነው ?
ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በሰባተኛው (7ኛ) ክፍል ዲስክርፕሽን ላይ የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን የተዘጋጀውን ጥያቄ በወረቀት ላይ (A4 ወይም A3) በመስራት በኢሜይል አድራሻችን (stic.ethiopia@gmail.com) የምታደርሱን ይሆናል፡፡ ታድያ እስካሁን ጥያቄዎቹን ሞልታችሁ ለላካችሁልን ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀቱ የተዘጋጀላችሁ ሲሆን በቅርቡም ከእጃችሁ እንደምናደርስ መግለፅ እንወዳለን፡፡
ታድያ አሁንም ጊዜው አላለቀምና ስልጠናውን ከተከታተላችሁ በኋላ በስልጠናው ላይ የተዘጋጀውን ጥያቄ መልስ እስከ ዓርብ ጥቅምት 13 2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ በመላክ ሰርተፊኬት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ያሎት ጊዜ አጭር በመሆኑ ተከታታይ ስልጠናውን በሚገባ ተከታትለው የተዘጋጀውን ጥያቄ ሰርተው ይላኩልን ፡፡
ስለተከታተሉን እናመሰግናለን፡፡