"#እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባ እንጸልይ" ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ ከደቡብ አፍሪካ
የደቡብ አፍሪካ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል አስቸኳይ የጾም እና ጸሎት ጥሪ አቅርቧል።
የወንጌል አብሳሪዎች አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን በጁሃንስበርግ መሪ እና የካውንስሉ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ እንደገለጹት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን #እና ኤርትራውያን ስደተኞች በተለያዩ ቡድኖች ችግር እየደረሰባቸው እንደሆነ ገልጸው ነገሮች እንዲስተካከሉ እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባ እንጸልይ ብለዋል።
ዶ/ር ብርሃኑ በመልዕክታቸው በአሁኑ ሰዓት ዱዱላ የተባለ ቡድን ስደተኞችን የማይገቡ ዶክመንቶችን በመጠየቅ እያሰቸገረ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም እዛው የተወለዱ እና ያደጉ #ልጆች ሲማሩም ይሁን ትምህርት ተምረውም ከጨረሱ በኋላ ስራ ለማግኘት በመቸገር ከፍተኛ ስንለቦናዊ ጫና እያደረባቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል።
እግዚአብሔርን አምነን ፊታችንን ወደ እርሱ በማድረግ ያለውን ችግር በእርሱ ፊት እንቅረብ በማለት በፈረንጆቹ ኦገስት 5-7 / 2025 ወይም ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 01/2017 ዓ.ም ድረስ በጾም እና ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ጸሎት እንዲቀርብ ጥሪ አቅርበዋል።
በዮሐንስ ግርማ
የደቡብ አፍሪካ የወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል አስቸኳይ የጾም እና ጸሎት ጥሪ አቅርቧል።
የወንጌል አብሳሪዎች አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን በጁሃንስበርግ መሪ እና የካውንስሉ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ እንደገለጹት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን #እና ኤርትራውያን ስደተኞች በተለያዩ ቡድኖች ችግር እየደረሰባቸው እንደሆነ ገልጸው ነገሮች እንዲስተካከሉ እግዚአብሔር ጣልቃ እንዲገባ እንጸልይ ብለዋል።
ዶ/ር ብርሃኑ በመልዕክታቸው በአሁኑ ሰዓት ዱዱላ የተባለ ቡድን ስደተኞችን የማይገቡ ዶክመንቶችን በመጠየቅ እያሰቸገረ መሆኑን ጠቅሰው በተለይም እዛው የተወለዱ እና ያደጉ #ልጆች ሲማሩም ይሁን ትምህርት ተምረውም ከጨረሱ በኋላ ስራ ለማግኘት በመቸገር ከፍተኛ ስንለቦናዊ ጫና እያደረባቸው መሆኑንም ጠቅሰዋል።
እግዚአብሔርን አምነን ፊታችንን ወደ እርሱ በማድረግ ያለውን ችግር በእርሱ ፊት እንቅረብ በማለት በፈረንጆቹ ኦገስት 5-7 / 2025 ወይም ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 01/2017 ዓ.ም ድረስ በጾም እና ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ጸሎት እንዲቀርብ ጥሪ አቅርበዋል።
በዮሐንስ ግርማ
👍10❤8🙏3🕊1
የቢሾፍቱ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ አቀረበ።
ከሰሞኑ በቢሾፍቱ ከተማ ከፍተኛ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለዉ ዝናብ
በተለያዩ የከተማዋ ስፍራዎች ቤት ውስጥ ጎርፍ በመግባት ንብረቶች መበላሽት እና ጉዳት መድረሱ ይታወሳል።
ሁኔታውን አስመልክቶ የቢሾፍቱ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ አቅርቧል።
ጥሪዉን ያቀረቡት የሕብረቱ ዋና ሰብሳቢ መጋቢ ብሩክ ከበደ በከተማዋ በጣለው ንፈስ እና በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች ላይ እና በህብረታችን በታቀፋ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ላይ በደረሰው የንብረት ውድመት የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን እገልፃለሁ ብለዋል።
መጋቢ ብሩክ አክለዉ ቅዱሳን የወንድም የእህት መኖርያ ቤቶችን እንዲሁም የአጥቢያ ቤተክርስቲያናትን መሰብሰቢያ አዳራሾች መልሶ ለመስራት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ሁሉ በማድረግ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ እርስ በእርስ በመተጋገዝ አብረን እንቁም የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
እስካሁን ከአከባቢዉ በወጣዉ ዘገባ አንድ የቤተሰባችን አባል በዝናቡ ምክንያት የቤታቸው ጣራ መነሳቱን ፤ ሌላኛው አባል ደግሞ ቤታቸው በጎርፍ መጥለቅለቁን ቲክቫ ኢትዮጵያ መዘገቡ ይታወሳል።
Photo - Bayew Atiye & Social Media
ከሰሞኑ በቢሾፍቱ ከተማ ከፍተኛ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለዉ ዝናብ
በተለያዩ የከተማዋ ስፍራዎች ቤት ውስጥ ጎርፍ በመግባት ንብረቶች መበላሽት እና ጉዳት መድረሱ ይታወሳል።
ሁኔታውን አስመልክቶ የቢሾፍቱ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ አቅርቧል።
ጥሪዉን ያቀረቡት የሕብረቱ ዋና ሰብሳቢ መጋቢ ብሩክ ከበደ በከተማዋ በጣለው ንፈስ እና በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በርካታ የከተማው ነዋሪዎች ላይ እና በህብረታችን በታቀፋ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ላይ በደረሰው የንብረት ውድመት የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘን እገልፃለሁ ብለዋል።
መጋቢ ብሩክ አክለዉ ቅዱሳን የወንድም የእህት መኖርያ ቤቶችን እንዲሁም የአጥቢያ ቤተክርስቲያናትን መሰብሰቢያ አዳራሾች መልሶ ለመስራት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ሁሉ በማድረግ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ እርስ በእርስ በመተጋገዝ አብረን እንቁም የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
እስካሁን ከአከባቢዉ በወጣዉ ዘገባ አንድ የቤተሰባችን አባል በዝናቡ ምክንያት የቤታቸው ጣራ መነሳቱን ፤ ሌላኛው አባል ደግሞ ቤታቸው በጎርፍ መጥለቅለቁን ቲክቫ ኢትዮጵያ መዘገቡ ይታወሳል።
Photo - Bayew Atiye & Social Media
❤10👍5👌1😭1
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ያወጀችው የጽዕም ጸሎት #ነገ ይጀምራል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም ባወጣችው የጽሁፍ መግለጫ መሠረት ሀገራችን ኢትዮጵያን በተመለከተ የሰላምና ጸሎት ጥሪ ማቅረቧ ይታወሳል።
በመግለጫው መሠረትም ለቤተክርስቲያኒቱ አባላት፣ አገልጋዮችና መሪዎች ከነሃሴ 1 እስከ 11/2017 ዓ.ም ድረስ ስለምድራችን #ኢትዮጵያ የእግዚአብሔርን ፊት በጾምና በጸሎት እንድንፈልግ ጥሪ መተላለፉ ይታወቃል።
“እንግዲህ ከሁሉ አስቀድሞ ልመናና ጸሎት፣ ምልጃና ምስጋና ለሰዎች ሁሉ፣ ለነገስታትና ለባለስልጣናት ሁሉ እንዲደረግ አሳስባለሁ፤ ይህም በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትና በቅድስና ሁሉ፣ በሰላምና በጸጥታ እንድንኖር ነው”። 1ኛ ጢሞ. 2፥1-2 (አ.መ.ት)
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም ባወጣችው የጽሁፍ መግለጫ መሠረት ሀገራችን ኢትዮጵያን በተመለከተ የሰላምና ጸሎት ጥሪ ማቅረቧ ይታወሳል።
በመግለጫው መሠረትም ለቤተክርስቲያኒቱ አባላት፣ አገልጋዮችና መሪዎች ከነሃሴ 1 እስከ 11/2017 ዓ.ም ድረስ ስለምድራችን #ኢትዮጵያ የእግዚአብሔርን ፊት በጾምና በጸሎት እንድንፈልግ ጥሪ መተላለፉ ይታወቃል።
“እንግዲህ ከሁሉ አስቀድሞ ልመናና ጸሎት፣ ምልጃና ምስጋና ለሰዎች ሁሉ፣ ለነገስታትና ለባለስልጣናት ሁሉ እንዲደረግ አሳስባለሁ፤ ይህም በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትና በቅድስና ሁሉ፣ በሰላምና በጸጥታ እንድንኖር ነው”። 1ኛ ጢሞ. 2፥1-2 (አ.መ.ት)
❤11👍2🕊1
የሆሳዕና እናት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ወጣቶች በለምቡዳ ተራራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር አካሄዷል።
የሆሳዕና እናት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት መሪ አቶ ናትናኤል አበራ እንደገለፁት ችግኝ መትከል የመንግስት ዓላማን ከመደገፍ በተጨማሪም የልማት ተግባራትን መከናወን ከሀይማኖት ተቋማት ተልዕኮ አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኒቱ ከዚህ ቀደም በርካታ የልማት ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ጠቁመው ይህም የችግኝ ተከላ ለ7ኛ ዙር መሆኑን አንስተዋል።
በዛሬው ዕለትም የቤተክርስቲያን ወጣቶችን በማሳተፍ ከ2 ሺህ 500 በላይ የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ተናግረው የተተከሉ ችግኞችን እንክብካቤ እንደሚያደርጉም አቶ ናትናኤል ተናግረዋል።
የሌሞ ወረዳ ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት የደን ልማት ብድን መሪ አቶ ተፈራ ኤረንጎ ምድርን መጠበቀና መንከባከብ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ መሆኑና በጎ ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።
የተተከሉ ችግኞች ለውበት፣ ለጥላ፣ ለአፈርና ውሃ ጥበቃ የሚውሉ መሆናቸው ጠቁመው ይህንን የመንግስት ራዕይ ወጣቱ በቀጣይነት ማስቀጠል ይገባል ብለዋል ።
የቤተክርስቲያኑ የወጣቶች መሪ አቶ ዳዊት ወልደ ዮሐንስ በበኩላቸው ከመንፈሳዊ አገልግሎት ጎን ለጎን ምድርን መጠበቅና መንከባከብ ከአባቶች የተረከብነው አደራ ነው ብለዋል።
ቀደሚ ሲል ቤተክርስቲያኒቱ አቅመ ደካሞችን በመርዳት፣ በከተማ ጽዳትና ሌሎች የልማት ስራዎችን መከናወኑን ጠቁመው ሌሎች ሀይማኖት ተቋማት በዚህ የልማት ስራ ላይ እንዲሳተፉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የለሙቡዳ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ሰብሳቢ አቶ ሰላሙ በቀለ በበኩላቸው ችግኝ መትከል የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ተናግረው የተተከሉ ችግኞችን አስፈላጊውን እንክብካቤ እንደሚደረግ ገልፀዋል።
የሆሳዕና እናት ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት መሪ አቶ ናትናኤል አበራ እንደገለፁት ችግኝ መትከል የመንግስት ዓላማን ከመደገፍ በተጨማሪም የልማት ተግባራትን መከናወን ከሀይማኖት ተቋማት ተልዕኮ አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኒቱ ከዚህ ቀደም በርካታ የልማት ስራዎችን እያከናወነች መሆኑን ጠቁመው ይህም የችግኝ ተከላ ለ7ኛ ዙር መሆኑን አንስተዋል።
በዛሬው ዕለትም የቤተክርስቲያን ወጣቶችን በማሳተፍ ከ2 ሺህ 500 በላይ የተለያዩ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መተከላቸውን ተናግረው የተተከሉ ችግኞችን እንክብካቤ እንደሚያደርጉም አቶ ናትናኤል ተናግረዋል።
የሌሞ ወረዳ ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት የደን ልማት ብድን መሪ አቶ ተፈራ ኤረንጎ ምድርን መጠበቀና መንከባከብ የእግዚአብሔር ትዕዛዝ መሆኑና በጎ ተግባር እንደሆነም ተናግረዋል።
የተተከሉ ችግኞች ለውበት፣ ለጥላ፣ ለአፈርና ውሃ ጥበቃ የሚውሉ መሆናቸው ጠቁመው ይህንን የመንግስት ራዕይ ወጣቱ በቀጣይነት ማስቀጠል ይገባል ብለዋል ።
የቤተክርስቲያኑ የወጣቶች መሪ አቶ ዳዊት ወልደ ዮሐንስ በበኩላቸው ከመንፈሳዊ አገልግሎት ጎን ለጎን ምድርን መጠበቅና መንከባከብ ከአባቶች የተረከብነው አደራ ነው ብለዋል።
ቀደሚ ሲል ቤተክርስቲያኒቱ አቅመ ደካሞችን በመርዳት፣ በከተማ ጽዳትና ሌሎች የልማት ስራዎችን መከናወኑን ጠቁመው ሌሎች ሀይማኖት ተቋማት በዚህ የልማት ስራ ላይ እንዲሳተፉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የለሙቡዳ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ሰብሳቢ አቶ ሰላሙ በቀለ በበኩላቸው ችግኝ መትከል የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን ተናግረው የተተከሉ ችግኞችን አስፈላጊውን እንክብካቤ እንደሚደረግ ገልፀዋል።
❤4👍4🔥2👏1
የአርጀንቲና ወንጌል አማኞች ህጋዊ እውቅና አገኙ
በሃገሪቱ ህግ መሰረት ከካቶሊክ በስተቀር ለማንኛውም ሃይማኖት እውቅና አይሰጥም። የሃቪየር ሚሌ መንግስት ካቶሊክ ያልሆነ ምንግስትን ለመጀመሪያ ጊዜ እውቅና ሰጥቷል።
በማህበርነት ስም ሲመዘገብ ለቆየ የወንጌላዊያን እምነት ተከታይ ዛሬ ህጋዊ ሰውነት ማግኘት ትልቅ የምስራች ነው። ላለፉት 30 አመታት ይህግ ባለሙያዎች፡ የወንጌላዊያን ማህበራት እና አብያተ ክርስቲያናት በተደጋጋሚ ጥያቄን ሲያቀርቡ ነበረ።
እውቅናውን የሃገሪቱ ፍትህ ሚኒስቴር ፈርሞ አጽድቆታል። የአርጀንቲና ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ጥምረት ውሳኔው የእምነት እኩልነትን ያረጋገጠ፡ የሃይማኖት ነጻነትን ያረጋገጠ እና የወንጌላዊያንን ጥንካሬ ያረጋገጠ ነው ብሎታል።
የህጋዊ እውቅና ጉዳዩ ከልታወቅ ባለፈ ክርስቲያኖች ወንጌልን በነጻነት መስበክ የሚያስችል እርምጃ ነው። የወንጌላዊያን ቁጥር በ2008 ከነበረበት የ8% በ2018 ወደ 15% አድጓል። ይሄ ወንጌል በአካባቢው ምን ያክል እየተስፋፋ እንደሚገኝ የሚያሳይ ነው።
በኦቦሌሳ አዶላ
Evangelical Focus እንዳስነበበው።
በሃገሪቱ ህግ መሰረት ከካቶሊክ በስተቀር ለማንኛውም ሃይማኖት እውቅና አይሰጥም። የሃቪየር ሚሌ መንግስት ካቶሊክ ያልሆነ ምንግስትን ለመጀመሪያ ጊዜ እውቅና ሰጥቷል።
በማህበርነት ስም ሲመዘገብ ለቆየ የወንጌላዊያን እምነት ተከታይ ዛሬ ህጋዊ ሰውነት ማግኘት ትልቅ የምስራች ነው። ላለፉት 30 አመታት ይህግ ባለሙያዎች፡ የወንጌላዊያን ማህበራት እና አብያተ ክርስቲያናት በተደጋጋሚ ጥያቄን ሲያቀርቡ ነበረ።
እውቅናውን የሃገሪቱ ፍትህ ሚኒስቴር ፈርሞ አጽድቆታል። የአርጀንቲና ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ጥምረት ውሳኔው የእምነት እኩልነትን ያረጋገጠ፡ የሃይማኖት ነጻነትን ያረጋገጠ እና የወንጌላዊያንን ጥንካሬ ያረጋገጠ ነው ብሎታል።
የህጋዊ እውቅና ጉዳዩ ከልታወቅ ባለፈ ክርስቲያኖች ወንጌልን በነጻነት መስበክ የሚያስችል እርምጃ ነው። የወንጌላዊያን ቁጥር በ2008 ከነበረበት የ8% በ2018 ወደ 15% አድጓል። ይሄ ወንጌል በአካባቢው ምን ያክል እየተስፋፋ እንደሚገኝ የሚያሳይ ነው።
በኦቦሌሳ አዶላ
Evangelical Focus እንዳስነበበው።
👍14❤10🔥3🥰1👏1
የተስፋ ብርሀን ምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎችን ለማገዝ 250 ሺህ ብር የሚያወጣ የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።
ብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴቨሎፕመንት አሶሴሽን እና ዊን ሶልስ ፎር ጎድ ኢቫንጄሊካል ሚኒስትሪስ ከአዲስ አበባ ሴቶች እና ሕጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ጋር በመተባበር በጉለሌ ክፍለ ከተማ 10 የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚ ለነበሩ ሴቶች ድጋፍ አደረጉ።
በድጋፉ ለእያንዳንዳቸው የ25 ሺህ የብር ግምት ያለው የመስሪያ እቃዎችና ግብአት (የአንጀራ መጋገሪያ ምጣድ እና የችብስ መጥበሻ) እንዲሁም ስራ ማስጀመሪያ መቋቋሚያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ ያካተተ በአጠቃላይ ግምቱ 250 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ አቋቁሟል።
በዚህ መርኃ ግብር የብራይት ስታር ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ግዛቸው አይካ፣ የአዲስ አበባ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ሶፊያ አለሙ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ቆንጂት ደበላን ጨምሮ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።
የድጋፍ ርክክቡ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ ተጠቃሚዎች በፍላጎታቸው መሠረት የተደረገላቸው መነሻ ድጋፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድጋፍን ተጠቅመው ጠንክረው በመስራት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከተረጂነት በማላቀቅ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ በማሳሰብ ቢሮውም በመዋቅሩ አማካኝነት ክትትልና ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በመጨረሻም ድጋፍ ያደረጉ አካላትን በማመስገን አሁንም በጊዜያዊ ማህበራዊ ችግር ውስጥ ሆነው መቋቋም የሚፈልጉ ነዋሪዎችን ለማገዝ አቅሙ ያላቸው ድርጅቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ቢሮው በጋራ ለመስራት ዝግጁ ስለመሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴቨሎፕመንት አሶሴሽን እና ዊን ሶልስ ፎር ጎድ ኢቫንጄሊካል ሚኒስትሪስ ከአዲስ አበባ ሴቶች እና ሕጻናት ማህበራዊ ጉዳይ ጋር በመተባበር በጉለሌ ክፍለ ከተማ 10 የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚ ለነበሩ ሴቶች ድጋፍ አደረጉ።
በድጋፉ ለእያንዳንዳቸው የ25 ሺህ የብር ግምት ያለው የመስሪያ እቃዎችና ግብአት (የአንጀራ መጋገሪያ ምጣድ እና የችብስ መጥበሻ) እንዲሁም ስራ ማስጀመሪያ መቋቋሚያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ ያካተተ በአጠቃላይ ግምቱ 250 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ አቋቁሟል።
በዚህ መርኃ ግብር የብራይት ስታር ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ግዛቸው አይካ፣ የአዲስ አበባ ሴቶች፣ ህፃናት፣ ወጣቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ሶፊያ አለሙ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ቆንጂት ደበላን ጨምሮ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።
የድጋፍ ርክክቡ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ ተጠቃሚዎች በፍላጎታቸው መሠረት የተደረገላቸው መነሻ ድጋፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ ድጋፍን ተጠቅመው ጠንክረው በመስራት ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከተረጂነት በማላቀቅ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ በማሳሰብ ቢሮውም በመዋቅሩ አማካኝነት ክትትልና ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በመጨረሻም ድጋፍ ያደረጉ አካላትን በማመስገን አሁንም በጊዜያዊ ማህበራዊ ችግር ውስጥ ሆነው መቋቋም የሚፈልጉ ነዋሪዎችን ለማገዝ አቅሙ ያላቸው ድርጅቶችና የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ቢሮው በጋራ ለመስራት ዝግጁ ስለመሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
👍3❤1
በፕሪሚየር ሊጉ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ምልክት/አርማ በተጨዋቾች የጫማ ክር እና የአምበሎች አርማ ላይ መደረግ ይቆማል።
በቀጣዩ አመት #የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በብዙዎች የሚወገዘዉ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ምልክት/አርማ በተጨዋቾች የጫማ ክር እና የአምበሎች አርማ ላይ መደረግ እንደሚቆም ተሰምቷል።
ፕሪሚየር ሊግ ለ 13 አመታት በዚህ ተግባር ላይ ከሚሰራ ተቋም ጋር የነበረዉ የስፖንሰርሺፕ ዉል ጊዜዉን ጨርሷል ተብሏል። የሁሉም ቡድን አምበሎች በተገኙበት በተደረገ ስብሰባ አርማዉ መደረጉ ከድጋፍ ይልቅ ተቃዉሞ እየታየበት ነዉ ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የእግር ኳስ ተመልካቾች የሚያዉቁትን አርማ ተጨዋቾች የማይጠቀሙት ይሆናል። ሆኖም ፕሪሚየር ሊጉ በራሱ የሊጉ አርማ ላይ ምልክቱን እንደሚጠቀም ተዘግቧል። ሊጉ የራሱን "የግንዛቤ ማስጨበጫ" ሲል የጠራዉን ዘመቻ እንደሚሰራም ገልጿል።
በባለፈዉ አመት የክሪስታል ፓላሱ አምበል ማርክ ጌሂ በአርማዉ ላይ "ኢየሱስን እወዳለሁ። ኢየሱስም ይወዳችኋል" ሲል በመጻፍ ተጨዋቹ የእምነቱን ህግጋት እንደሚያከብር ተናግሯል።
በተጨማሪም የኢፕስዊች ታዉን አምበሉ እና የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሙሪ አርማዉን አልጠቀምም ማለቱ አይዘነጋም። የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አርማ በፕሪሚየር ሊጉ ላይ መጠቀም ሲጀመር የቴሌቪዥን ስርጭታቸውን የሚያቋርጡ ሀገራት እንዳሉም ይታወቃል።
ይህ ተግባር ለአመታት ተቃዉሞ ሲቀርብበት የነበረ ነዉ።
በረከት ሞገስ ለዳጉ ጆርናል እንደዘገበው።
በቀጣዩ አመት #የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በብዙዎች የሚወገዘዉ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ምልክት/አርማ በተጨዋቾች የጫማ ክር እና የአምበሎች አርማ ላይ መደረግ እንደሚቆም ተሰምቷል።
ፕሪሚየር ሊግ ለ 13 አመታት በዚህ ተግባር ላይ ከሚሰራ ተቋም ጋር የነበረዉ የስፖንሰርሺፕ ዉል ጊዜዉን ጨርሷል ተብሏል። የሁሉም ቡድን አምበሎች በተገኙበት በተደረገ ስብሰባ አርማዉ መደረጉ ከድጋፍ ይልቅ ተቃዉሞ እየታየበት ነዉ ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የእግር ኳስ ተመልካቾች የሚያዉቁትን አርማ ተጨዋቾች የማይጠቀሙት ይሆናል። ሆኖም ፕሪሚየር ሊጉ በራሱ የሊጉ አርማ ላይ ምልክቱን እንደሚጠቀም ተዘግቧል። ሊጉ የራሱን "የግንዛቤ ማስጨበጫ" ሲል የጠራዉን ዘመቻ እንደሚሰራም ገልጿል።
በባለፈዉ አመት የክሪስታል ፓላሱ አምበል ማርክ ጌሂ በአርማዉ ላይ "ኢየሱስን እወዳለሁ። ኢየሱስም ይወዳችኋል" ሲል በመጻፍ ተጨዋቹ የእምነቱን ህግጋት እንደሚያከብር ተናግሯል።
በተጨማሪም የኢፕስዊች ታዉን አምበሉ እና የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሙሪ አርማዉን አልጠቀምም ማለቱ አይዘነጋም። የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አርማ በፕሪሚየር ሊጉ ላይ መጠቀም ሲጀመር የቴሌቪዥን ስርጭታቸውን የሚያቋርጡ ሀገራት እንዳሉም ይታወቃል።
ይህ ተግባር ለአመታት ተቃዉሞ ሲቀርብበት የነበረ ነዉ።
በረከት ሞገስ ለዳጉ ጆርናል እንደዘገበው።
❤15👍3👏3👌1
“በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል” መጽሐፍ በሀዋሳ ከተማ በይፋ ተመረቀ።
#በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ “በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል” በሚል ርዕስ የተጻፈው መጽሐፍ #ዛሬ ነሐሴ 4/2017 ዓ.ም በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን በይፋ ተመረቀ።
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በመፅሐፍ ምረቃው ላይ ተገኝተው መጋቢ ፃዲቁ አብዶ ትውልድን ሊያስተምር የሚችል መፅሐፍ መፃፋቸውን በመጥቀስ በቀል በቀለኛን የሚያጠፋ በመሆኑ ትውልድ ከበቀል በመውጣት በይቅርታና በፍቅር መኖር እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ በበኩላቸው ከባለቤታቸው ሰላማዊት ቡርቂቱ ጋር በመሆን መፅሐፉን በተመለከተ ንግግር አድርገዋል።
በመጽሐፍ ምረቃው ፕሮግራም ላይ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ ማርሻዬ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት መጋቢ ሰንበቶ በሼን ጨምሮ የሲዳማ ክልል እና የሀዋሳ ከተማ ወንጌውያን አማኞች ካውንስልና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ በዝማሬና በእግዚአብሔር ቃል ያገለገሉ ሲሆን የሲዳማ ክልል የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስያናት ካውንስል እና የወንጌላውያን አብያተክርስትያናት ህብረት የቦርድ ሰብሳቢዎች፤ የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን መጋቢዎች በአንድነት በመሆን የመፅሐፍ ሪቫን በመቁረጥ የመፅሐፉን መመረቅ በይፋ አብስረዋል።
ምንጭ @የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን የሚዲያ አገልግሎት
#በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ “በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል” በሚል ርዕስ የተጻፈው መጽሐፍ #ዛሬ ነሐሴ 4/2017 ዓ.ም በሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን በይፋ ተመረቀ።
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መኩሪያ መርሻዬ በመፅሐፍ ምረቃው ላይ ተገኝተው መጋቢ ፃዲቁ አብዶ ትውልድን ሊያስተምር የሚችል መፅሐፍ መፃፋቸውን በመጥቀስ በቀል በቀለኛን የሚያጠፋ በመሆኑ ትውልድ ከበቀል በመውጣት በይቅርታና በፍቅር መኖር እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ በበኩላቸው ከባለቤታቸው ሰላማዊት ቡርቂቱ ጋር በመሆን መፅሐፉን በተመለከተ ንግግር አድርገዋል።
በመጽሐፍ ምረቃው ፕሮግራም ላይ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ መኩሪያ ማርሻዬ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት መጋቢ ሰንበቶ በሼን ጨምሮ የሲዳማ ክልል እና የሀዋሳ ከተማ ወንጌውያን አማኞች ካውንስልና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እና አገልጋዮች ተገኝተዋል።
መጋቢ ተስፋዬ ጋቢሶ በዝማሬና በእግዚአብሔር ቃል ያገለገሉ ሲሆን የሲዳማ ክልል የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስያናት ካውንስል እና የወንጌላውያን አብያተክርስትያናት ህብረት የቦርድ ሰብሳቢዎች፤ የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን መጋቢዎች በአንድነት በመሆን የመፅሐፍ ሪቫን በመቁረጥ የመፅሐፉን መመረቅ በይፋ አብስረዋል።
ምንጭ @የሀዋሳ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን የሚዲያ አገልግሎት
❤5👍2👏1
ተመዝግበሻል?
እኛ ሚስቶች እንደብልኋ ሴት ቤታችንን በእጆቻችን የምንሰራበትን ጥበቦች ልንሸምት፣ ማስተዋሎችን ልንካፈልና እውቀቶችን ልንገበይ ቀናቶችን ቀጥረናል።
2ኛው ዙር ዕንቁ ልብ የሚስቶች ት/ቤት ምዝገባ ተጀምሯል ‼️
📍በሰሊሆም የተላከ ትውልድ ቤተ-ክርስቲያን
🗓ከነሐሴ 12-23 አስር የሥራ ቀናት
⌚️ከጠዋቱ 2:30-6:30
አሰልጣኞች ፦
1. ዘለቃ በቀለ (ቃቁ)
2. ወንጌላዊት መዓዛ በቀለ
3. መጋቢ ምዕልተፀጋ ገ/መድህን (ዶ/ር)
4. እህት ዘነበች እርዳ
5. እህት ሳሮን ውድነህ
👉አድራሻ ፦ ከስታድየም ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ ጠመንጃ ያዥ ኖክ ማደያ ሳይደርስ ኦሮሚያ ባንክ ያለበት 3ኛ ፎቅ
🖊ለመመዝገብ ፦ በ0911136520/0946693468 ይደውሉ!
💯 ለውጥ ይሆንልሻል‼️
ከ1ኛ ዙር ተሳታፊዎች የተሰጠ ምስክርነት 👇
https://youtu.be/R0xrbvtxH58?si=mxOUGROh3VPDgzGB
ለበለጠ መረጃ ይህን ግሩፕ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
እኛ ሚስቶች እንደብልኋ ሴት ቤታችንን በእጆቻችን የምንሰራበትን ጥበቦች ልንሸምት፣ ማስተዋሎችን ልንካፈልና እውቀቶችን ልንገበይ ቀናቶችን ቀጥረናል።
2ኛው ዙር ዕንቁ ልብ የሚስቶች ት/ቤት ምዝገባ ተጀምሯል ‼️
📍በሰሊሆም የተላከ ትውልድ ቤተ-ክርስቲያን
🗓ከነሐሴ 12-23 አስር የሥራ ቀናት
⌚️ከጠዋቱ 2:30-6:30
አሰልጣኞች ፦
1. ዘለቃ በቀለ (ቃቁ)
2. ወንጌላዊት መዓዛ በቀለ
3. መጋቢ ምዕልተፀጋ ገ/መድህን (ዶ/ር)
4. እህት ዘነበች እርዳ
5. እህት ሳሮን ውድነህ
👉አድራሻ ፦ ከስታድየም ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ ጠመንጃ ያዥ ኖክ ማደያ ሳይደርስ ኦሮሚያ ባንክ ያለበት 3ኛ ፎቅ
🖊ለመመዝገብ ፦ በ0911136520/0946693468 ይደውሉ!
💯 ለውጥ ይሆንልሻል‼️
ከ1ኛ ዙር ተሳታፊዎች የተሰጠ ምስክርነት 👇
https://youtu.be/R0xrbvtxH58?si=mxOUGROh3VPDgzGB
ለበለጠ መረጃ ይህን ግሩፕ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
❤4👍2🔥1🙏1
#እንደ ሃገር ምን ያክል የምንጸልይ እንሆን?
ሰሞኑን የትኛዎቹ ሃገራት ምን ያክል ይጸልያሉ የሚል ጥናታዊ ግኝት ይፋ ተደርጓል።
ቪዥዋል ካፒታሊስት የተሰኘ ድህረ ገጽ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በፈረንጆቹ 2025 የ35 ሃገራትን የጸሎት መረጃ ይፋ አድርጓል። ኢንዶኔዥያ ከ269 ሚሊዮን ህዝቧ 95% ቢያንስ በየቀኑ እንደሚጸልዩ ይፋ አድርጓል።
በተለይ መካከለኛ እና አነስተኛ ኢኮኖሚ ያላቸው ሃገራት ደረጃውን የሚመሩት ሲሆን፣ ምዕራባዊያን እና ባለ ትልቅ ኢኮኖሚ ሃገራት ደግሞ በሰንጠረዡ እግርጌ ይገኛሉ።
• ኢንዶኔዥያ ከ269 ሚሊዮን ህዝቧ 95 ሚሊዮን ህዝቧ በየእለቱ ይጸልያል።
• ኬኒያ ከ47.4 እና ናይጄሪያ ከ195.5 ሚሊዮን ህዝቧ 84 በመቶ በመጸለይ ሁለተኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
• ሃንጋሪ ከ1.1 ሚሊዮን ህዝቧ 11 በመቶ እና ስዊድን ከ8 መቶ ሺህ ህዝቧ 8 በመቶ ብቻ በመጸለይ በደረጃው እግርጌ ይገኛል።
• በህንድ ከ1 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ወይም 71% ህዝብ ይጸልያል።
• ከአሜሪካ ህዝብ 149 ሚሊዮን አሜሪካዊያን ወይም 44 በመቶ ህዝብ በየቀኑ ይጸልያል።
ፒው ሪሰርች ማዕከል ከአለም ባንክ ባገኘው መረጃ ባደረገው ምርመራ አማካኝነት ባደረገው ጥናት ነው ይሄንን ውጤት ይፋ ያደረገው። 35ቱ ሃገራት የአለምን ግማሽ ህዝብ ያክላሉ ይበል እንጂ እንደ ቻይና ያሉ ግዙፍ ቁጥር ያላቸው ሃገራት መረጃ ማግኘት አለመቻሉን ይፋ ተደርጓል።
የክርስትና እና እስልምና እምነት የሚበዛባቸው ሃገራት በሰንጠረዡ ከላይ ሲቀመጡ፣ ሴኩላር እና በኢኮኖሚ የበለጸጉ የሚባሉት ሃገራት ደግሞ ከታች ተቀምጠዋል። ግኝቱ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ይፋ ያደረገው መረጃ የለም።
እናንተስ ከ132 ሚሊዮን ህዝባችን ምን ያክል % በየቀኑ ይጸልያል ትላላችሁ? ኮሜንት ላይ አስቀምጡልን
በኦቦሌሳ አዶላ
ሰሞኑን የትኛዎቹ ሃገራት ምን ያክል ይጸልያሉ የሚል ጥናታዊ ግኝት ይፋ ተደርጓል።
ቪዥዋል ካፒታሊስት የተሰኘ ድህረ ገጽ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በፈረንጆቹ 2025 የ35 ሃገራትን የጸሎት መረጃ ይፋ አድርጓል። ኢንዶኔዥያ ከ269 ሚሊዮን ህዝቧ 95% ቢያንስ በየቀኑ እንደሚጸልዩ ይፋ አድርጓል።
በተለይ መካከለኛ እና አነስተኛ ኢኮኖሚ ያላቸው ሃገራት ደረጃውን የሚመሩት ሲሆን፣ ምዕራባዊያን እና ባለ ትልቅ ኢኮኖሚ ሃገራት ደግሞ በሰንጠረዡ እግርጌ ይገኛሉ።
• ኢንዶኔዥያ ከ269 ሚሊዮን ህዝቧ 95 ሚሊዮን ህዝቧ በየእለቱ ይጸልያል።
• ኬኒያ ከ47.4 እና ናይጄሪያ ከ195.5 ሚሊዮን ህዝቧ 84 በመቶ በመጸለይ ሁለተኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
• ሃንጋሪ ከ1.1 ሚሊዮን ህዝቧ 11 በመቶ እና ስዊድን ከ8 መቶ ሺህ ህዝቧ 8 በመቶ ብቻ በመጸለይ በደረጃው እግርጌ ይገኛል።
• በህንድ ከ1 ቢሊዮን በላይ ህዝብ ወይም 71% ህዝብ ይጸልያል።
• ከአሜሪካ ህዝብ 149 ሚሊዮን አሜሪካዊያን ወይም 44 በመቶ ህዝብ በየቀኑ ይጸልያል።
ፒው ሪሰርች ማዕከል ከአለም ባንክ ባገኘው መረጃ ባደረገው ምርመራ አማካኝነት ባደረገው ጥናት ነው ይሄንን ውጤት ይፋ ያደረገው። 35ቱ ሃገራት የአለምን ግማሽ ህዝብ ያክላሉ ይበል እንጂ እንደ ቻይና ያሉ ግዙፍ ቁጥር ያላቸው ሃገራት መረጃ ማግኘት አለመቻሉን ይፋ ተደርጓል።
የክርስትና እና እስልምና እምነት የሚበዛባቸው ሃገራት በሰንጠረዡ ከላይ ሲቀመጡ፣ ሴኩላር እና በኢኮኖሚ የበለጸጉ የሚባሉት ሃገራት ደግሞ ከታች ተቀምጠዋል። ግኝቱ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ይፋ ያደረገው መረጃ የለም።
እናንተስ ከ132 ሚሊዮን ህዝባችን ምን ያክል % በየቀኑ ይጸልያል ትላላችሁ? ኮሜንት ላይ አስቀምጡልን
በኦቦሌሳ አዶላ
❤6🤔3👏1🙏1
የአዋሽ አርባ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ከከተማው አብያተ ክርስቲያናት እና ከወረዳው ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ ፕሮግራም አከናወነች።
በአፋር ክልል ዞን 3 አሚባራ ወረዳ በአዋሽ አርባ ከተማ የምትገኘው የአዋሽ አርባ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ከከተማው አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ጋር በመተባበር በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰተዉን የእናቶች ሞት ለመቀነስ የደም ልገሳ አከናዉነዋል።
በመርሀ ግብሩ ደም ለሚለግሱ ወገኖችም የግንዛቤ ማስጨበጫ የተሰጠም ሲሆን በግሬት ኮምሽን ኢትዮጵያ የተማሪዎች የሚሽን አገልግሎት ህብረት በጋራ የፕሮግራሙ አካል በመሆን ደም ለግሰዋል።
በእለቱም በተደረገ ልገሳ 43 ዩኒት የተሰበሰበ ሲሆን በወረዳውም የመጀመሪያ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቧል።
በእለቱ በአዋሽ አርባ ከተማ የሚገኙ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት አባላት ከዚህ ቀደም በከተማዋ በሚከናወን የማሕበራዊ በጎ ስራዎች ላይ ሲሳተፉ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ማህበረሰብን በሁለንተናዊ መልክ በማገልገል ረገድ አሁንሕ የተጠናከረ ስራ እንደሚሰራ መሪዎቹ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያንም በዚህ ፕሮግራም ተሳታፊ የነበሩ ተቋማትንና ደም የለገሱ ቅዱሳንን አመስግነዋል።
አልዓዘር ማቴዎስ
በአፋር ክልል ዞን 3 አሚባራ ወረዳ በአዋሽ አርባ ከተማ የምትገኘው የአዋሽ አርባ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ከከተማው አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ጋር በመተባበር በደም እጥረት ምክንያት የሚከሰተዉን የእናቶች ሞት ለመቀነስ የደም ልገሳ አከናዉነዋል።
በመርሀ ግብሩ ደም ለሚለግሱ ወገኖችም የግንዛቤ ማስጨበጫ የተሰጠም ሲሆን በግሬት ኮምሽን ኢትዮጵያ የተማሪዎች የሚሽን አገልግሎት ህብረት በጋራ የፕሮግራሙ አካል በመሆን ደም ለግሰዋል።
በእለቱም በተደረገ ልገሳ 43 ዩኒት የተሰበሰበ ሲሆን በወረዳውም የመጀመሪያ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቧል።
በእለቱ በአዋሽ አርባ ከተማ የሚገኙ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት አባላት ከዚህ ቀደም በከተማዋ በሚከናወን የማሕበራዊ በጎ ስራዎች ላይ ሲሳተፉ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ማህበረሰብን በሁለንተናዊ መልክ በማገልገል ረገድ አሁንሕ የተጠናከረ ስራ እንደሚሰራ መሪዎቹ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያንም በዚህ ፕሮግራም ተሳታፊ የነበሩ ተቋማትንና ደም የለገሱ ቅዱሳንን አመስግነዋል።
አልዓዘር ማቴዎስ
❤6👍1
ለሲኖዶሶች የመንፈሳዊ መጽሐፍት ድጋፍ ተደረገ።
የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ለመማር ማስተማር ህደት እና ለአገልጋዮች የሚረዱ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤጊ ግዳሚ ሲኖዶስ (ቤጊ): ለቦረናና አካባቢው ሲኖዶስ (ያቤሎ): ለአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ (አዶላ ወዩ) የመጽሐፍት ድጋፍ አበርክቷል።
መጽሐፍቶቹም በየሲኖዶሶቹ ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት እና ምዕመናን አገልግሎት የሚውሉ እንደሆነም ተገልጿል።
የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት 'Rafiki Foundation' fi 'Lutheran Heritage Foundation' እና ሌሎችንም በማመስገን : መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ሴሚናሪዎች: መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች እና ማ/ምዕመናን ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ለመማር ማስተማር ህደት እና ለአገልጋዮች የሚረዱ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤጊ ግዳሚ ሲኖዶስ (ቤጊ): ለቦረናና አካባቢው ሲኖዶስ (ያቤሎ): ለአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ (አዶላ ወዩ) የመጽሐፍት ድጋፍ አበርክቷል።
መጽሐፍቶቹም በየሲኖዶሶቹ ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት እና ምዕመናን አገልግሎት የሚውሉ እንደሆነም ተገልጿል።
የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሳ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት 'Rafiki Foundation' fi 'Lutheran Heritage Foundation' እና ሌሎችንም በማመስገን : መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ሴሚናሪዎች: መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች እና ማ/ምዕመናን ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
👍3❤2
5 ቀን ቀረው‼️
ተመዝግበሻል?
#እኛ ሚስቶች እንደብልኋ ሴት ቤታችንን በእጆቻችን የምንሰራበትን ጥበቦች ልንሸምት፣ ማስተዋሎችን ልንካፈልና እውቀቶችን ልንገበይ ቀናቶችን ቀጥረናል።
2ኛው ዙር ዕንቁ ልብ የሚስቶች ት/ቤት ምዝገባ ተጀምሯል ‼️
📍በሰሊሆም የተላከ ትውልድ ቤተ-ክርስቲያን
🗓 ከነሐሴ 12-23 አስር የሥራ ቀናት
⌚ከጠዋቱ 2:30-6:30
አሰልጣኞች ፦
1. ዘለቃ በቀለ (ቃቁ)
2. ወንጌላዊት መዓዛ በቀለ
3. መጋቢ ምዕልተፀጋ ገ/መድህን (ዶ/ር)
4. እህት ዘነበች እርዳ
5. እህት ሳሮን ውድነህ
👉አድራሻ ፦ ከስታድየም ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ ጠመንጃ ያዥ ኖክ ማደያ ሳይደርስ ኦሮሚያ ባንክ ያለበት 3ኛ ፎቅ
🖊ለመመዝገብ ፦ በ0911136520/0946693468 ይደውሉ!
💯 ለውጥ ይሆንልሻል‼️
ከ1ኛ ዙር ተሳታፊዎች የተሰጠ ምስክርነት 👇
https://youtu.be/R0xrbvtxH58?si=mxOUGROh3VPDgzGB
ለበለጠ መረጃ ይህን ግሩፕ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
ተመዝግበሻል?
#እኛ ሚስቶች እንደብልኋ ሴት ቤታችንን በእጆቻችን የምንሰራበትን ጥበቦች ልንሸምት፣ ማስተዋሎችን ልንካፈልና እውቀቶችን ልንገበይ ቀናቶችን ቀጥረናል።
2ኛው ዙር ዕንቁ ልብ የሚስቶች ት/ቤት ምዝገባ ተጀምሯል ‼️
📍በሰሊሆም የተላከ ትውልድ ቤተ-ክርስቲያን
🗓 ከነሐሴ 12-23 አስር የሥራ ቀናት
⌚ከጠዋቱ 2:30-6:30
አሰልጣኞች ፦
1. ዘለቃ በቀለ (ቃቁ)
2. ወንጌላዊት መዓዛ በቀለ
3. መጋቢ ምዕልተፀጋ ገ/መድህን (ዶ/ር)
4. እህት ዘነበች እርዳ
5. እህት ሳሮን ውድነህ
👉አድራሻ ፦ ከስታድየም ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ ጠመንጃ ያዥ ኖክ ማደያ ሳይደርስ ኦሮሚያ ባንክ ያለበት 3ኛ ፎቅ
🖊ለመመዝገብ ፦ በ0911136520/0946693468 ይደውሉ!
💯 ለውጥ ይሆንልሻል‼️
ከ1ኛ ዙር ተሳታፊዎች የተሰጠ ምስክርነት 👇
https://youtu.be/R0xrbvtxH58?si=mxOUGROh3VPDgzGB
ለበለጠ መረጃ ይህን ግሩፕ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
❤3👍2🔥2👏1
#የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን ታሪክ የሚመዘግብ ስምምነት ተፈረመ
ዋይክሊፍ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር ነው የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረመው። ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በኢትዮጵያ የወንጌላዊያንን ታሪክ መሰነድ እና አትሞ ይፋ ማድረግ ላይ በጋራ ይሰራሉ ተብሏል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝደንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ እና የዋይክሊፍ ኢትዮጵያ መጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ማህበር አመራሮች ናቸው። በዚህ ስራ የረጅም አመታት የወንጌላዊያን ታሪክን ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ያስችላል ተብሏል።
ምንጭ፡ ዋይክሊፍ ኢትዮጵያ
ዋይክሊፍ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር ነው የመግባቢያ ስምምነቱን የተፈራረመው። ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በኢትዮጵያ የወንጌላዊያንን ታሪክ መሰነድ እና አትሞ ይፋ ማድረግ ላይ በጋራ ይሰራሉ ተብሏል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝደንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ እና የዋይክሊፍ ኢትዮጵያ መጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ማህበር አመራሮች ናቸው። በዚህ ስራ የረጅም አመታት የወንጌላዊያን ታሪክን ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ ያስችላል ተብሏል።
ምንጭ፡ ዋይክሊፍ ኢትዮጵያ
👏12🔥4🙏3👍1
የጉዲና ቱምሳ ሌጋሲ ቀን በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ።
“Reading the Signs of the Times ወይም የጊዜውን ምልክቶች ማንበብ የሚል መሪ ቃል የተሰጠው የዘንድሮው አመት ጉባኤ በአድዋ ድል መታዘቢያ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ። መድረኩ ቄስ ጉዲና ቱምሳ የነበራቸውን ሁለንተናዊ አገልግሎት ራዕይ ዛሬ ድረስ በተግባር የሚያሳይ ነው ተብሏል።
መድረኩን ቄስ ሃረገወይን በጸሎት ያስጀመሩ ሲሆን፣ የፋውንዴሽኑ ዳሬክተር ወ/ሮ ሌንሳ ጉዲና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አቅርበዋል። ከ1ሺህ በላይ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የማህበርሰብ ልማት ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዶ/ር ለማ ደገፋ፣ ዶ/ር ምህረት ደበበ፣ ዶ/ር ሳሙኤል ዮናስ እና ቄስ ዶ/ር ገለታ ሲሜሶ በመድረኩ ጥናታዊ ጽሁፎችን አቅርበዋል። ወንድም አሳየኸኝ ለገሰ፣ የወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በዲጂታል ሚድያ ዘመን የቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ ከማስፈጸም እና ጥአንካራ የማህበረሰብ ግንኙነትን ከመፍጠር አንጻር ንግግር አድርጓል።
ሌላው በመድረኩ የተነሳው ጉዳይ ቄስ ጉዲና የነበራቸው ባለራዕይ የስነ መለኮት አረዳድ በዛሬ ጊዜ አተገባበር ላይ የፓነል ውይይት ተካሂዷል።
ቄስ ጉዲና ቱምሳ የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጠቅላይ ጸሃፊ ሲሆኑ በ1971 ዓ.ም በደርግ መንግስት ነው የተገደሉት። ጉዲና ቱምሳ ፋውንዴሽን በሳቸው ስም የተሰየመ እና ከ1984 ጀምሮ በኢትዮጵያ የግብረ ሰናይ ስራዎችን የሚሰራ ተቋም ነው።
“Reading the Signs of the Times ወይም የጊዜውን ምልክቶች ማንበብ የሚል መሪ ቃል የተሰጠው የዘንድሮው አመት ጉባኤ በአድዋ ድል መታዘቢያ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ። መድረኩ ቄስ ጉዲና ቱምሳ የነበራቸውን ሁለንተናዊ አገልግሎት ራዕይ ዛሬ ድረስ በተግባር የሚያሳይ ነው ተብሏል።
መድረኩን ቄስ ሃረገወይን በጸሎት ያስጀመሩ ሲሆን፣ የፋውንዴሽኑ ዳሬክተር ወ/ሮ ሌንሳ ጉዲና የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አቅርበዋል። ከ1ሺህ በላይ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የማህበርሰብ ልማት ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ዶ/ር ለማ ደገፋ፣ ዶ/ር ምህረት ደበበ፣ ዶ/ር ሳሙኤል ዮናስ እና ቄስ ዶ/ር ገለታ ሲሜሶ በመድረኩ ጥናታዊ ጽሁፎችን አቅርበዋል። ወንድም አሳየኸኝ ለገሰ፣ የወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በዲጂታል ሚድያ ዘመን የቤተ ክርስቲያንን ተልዕኮ ከማስፈጸም እና ጥአንካራ የማህበረሰብ ግንኙነትን ከመፍጠር አንጻር ንግግር አድርጓል።
ሌላው በመድረኩ የተነሳው ጉዳይ ቄስ ጉዲና የነበራቸው ባለራዕይ የስነ መለኮት አረዳድ በዛሬ ጊዜ አተገባበር ላይ የፓነል ውይይት ተካሂዷል።
ቄስ ጉዲና ቱምሳ የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ጠቅላይ ጸሃፊ ሲሆኑ በ1971 ዓ.ም በደርግ መንግስት ነው የተገደሉት። ጉዲና ቱምሳ ፋውንዴሽን በሳቸው ስም የተሰየመ እና ከ1984 ጀምሮ በኢትዮጵያ የግብረ ሰናይ ስራዎችን የሚሰራ ተቋም ነው።
❤8👍2🙏1👌1
ከግብረ ሰዶማዊነት ጋር በተያያዘ እየተሠራጨ ያለውን ስም የማጥፋት ዘመቻ የተሳሳተ እና ቤተክርስቲያንን የማይወክል ነው ስትል የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የዐቋም መግለጫ አወጣች።
መግለጫው ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ አስተምህሮን ሳይነጣጠል፣ ሳይጣስና ሳይሸራረፍ አማኞች በሕይወታቸው ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጽኑ አቋሟን በትጋት የምታስተምር ቤተከርስቲያን መሆኗን በመጥቀስ በቅርቡ በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነትና ተቃራኒ እንዲሁም ከኢትዮጵያዊው ባሕል ተጻራሪ ከሆነው ከግብረ ሰዶማዊነት ጋር በተያያዘ የቤተ ከርስቲያናችን ስም ሲነሣ መታዘቧን ጠቅሳለች።
በመግለጫው ቤተክርስቲያን ይህ ተግባር መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት ለሌለው እስከዛሬ እየተቃወመችው ያለ አሁንም አጠናክራ የምትቀጥለው ጉዳይ እንደሆነ በመግለጽ የምታምነውን እና በመሰረተ እምነቷ የተቀመጡ እየተገበረች ያለችውን 6 ነጥቦች በግልጽ አስቀምጣለች።
በሌላ በኩል የግል ፍላጎቶቻቸውን ለማሳካት የቤተከርስቲያናችንን መልካም ስም በማጥፋት የተጠመዱ ወገኖች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲታቀቡም ማሳሰቢያ ሰጥታለች።
ሙሉ መግለጫውን እንድታነቡት እናሳስባለን!!!
መግለጫው ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ አስተምህሮን ሳይነጣጠል፣ ሳይጣስና ሳይሸራረፍ አማኞች በሕይወታቸው ተግባራዊ እንዲያደርጉ ጽኑ አቋሟን በትጋት የምታስተምር ቤተከርስቲያን መሆኗን በመጥቀስ በቅርቡ በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያዎች ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነትና ተቃራኒ እንዲሁም ከኢትዮጵያዊው ባሕል ተጻራሪ ከሆነው ከግብረ ሰዶማዊነት ጋር በተያያዘ የቤተ ከርስቲያናችን ስም ሲነሣ መታዘቧን ጠቅሳለች።
በመግለጫው ቤተክርስቲያን ይህ ተግባር መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት ለሌለው እስከዛሬ እየተቃወመችው ያለ አሁንም አጠናክራ የምትቀጥለው ጉዳይ እንደሆነ በመግለጽ የምታምነውን እና በመሰረተ እምነቷ የተቀመጡ እየተገበረች ያለችውን 6 ነጥቦች በግልጽ አስቀምጣለች።
በሌላ በኩል የግል ፍላጎቶቻቸውን ለማሳካት የቤተከርስቲያናችንን መልካም ስም በማጥፋት የተጠመዱ ወገኖች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲታቀቡም ማሳሰቢያ ሰጥታለች።
ሙሉ መግለጫውን እንድታነቡት እናሳስባለን!!!
👍9❤6🙏1👌1
የምስራቅ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ዘላቂ #ሰላም ማምጣት እንዲቻል የሁሉም ባለድርሻ ካላት ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ አስታወቀች።
ቤተክርስቲያኗ GRAND project ጋር በመተባበር በሰላም ግንባታ ዙሪያ ያተኮረ የምክክር መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩም ከጋምቤላ ከተማ ከአምስቱም ቀበሌ ከአኝዋሃ ዞን እና ጎግ ወረዳ የተወጣጡ የሀይማኖት አባቶች ፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የምስራቅ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ መካነ ኢየሱስ ፕሬዝዳንት ቄስ ኝጎዎ ኡሞድ በመድረኩ እንደተናገሩት ዘላቂ ሰላም እንዲኖር የሰላም ግንባታ ማዳበር እንዲቻል የሀይማኖት ተቋማት የሀገር ሽማግሌዎች ጨምሮ ሁሉም አካላት ለሰላም ዘብ ሊቆሙ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ሰላም ለሰዉ ልጅ ከሚያስፈልጉት እጅግ መሰረታዊ ነገሮች ዉስጥ አንዱና ግንባር ቀደም መሆኑን ገልፀዉ የክልሉን ማህበረሰብ ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ዋነኛ ተግባር አድርጋ ቤተክርስቲያኗ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
የሰላም እጦት በክልሉ ባለፉት ጊዜያት በተፈጠሩ አለመግባባቶች ብዙ የልማት ስራዎች ሳንሰራ የቀረን ሲሆን የሰላምን ዋጋ በመገንዘብ የሰላም ግንባታዉ እንዲዳብር ብዙ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የእምነት ተቋማቱ በጋራ በመሆን ያለዉን ሰላም ለማስቀጠል የጋራ የሆኑ ጉዳዮች ላይ ልንሰራ ይገባልም ብለዋል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው።
ተጨማሪ ዝርዝር በፌስቡክ ገጻችን መመልከት ትችላላችሁ
ቤተክርስቲያኗ GRAND project ጋር በመተባበር በሰላም ግንባታ ዙሪያ ያተኮረ የምክክር መድረክ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩም ከጋምቤላ ከተማ ከአምስቱም ቀበሌ ከአኝዋሃ ዞን እና ጎግ ወረዳ የተወጣጡ የሀይማኖት አባቶች ፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
የምስራቅ ጋምቤላ ቤቴል ሲኖዶስ መካነ ኢየሱስ ፕሬዝዳንት ቄስ ኝጎዎ ኡሞድ በመድረኩ እንደተናገሩት ዘላቂ ሰላም እንዲኖር የሰላም ግንባታ ማዳበር እንዲቻል የሀይማኖት ተቋማት የሀገር ሽማግሌዎች ጨምሮ ሁሉም አካላት ለሰላም ዘብ ሊቆሙ እንደሚገባ ተናግረዋል።
ሰላም ለሰዉ ልጅ ከሚያስፈልጉት እጅግ መሰረታዊ ነገሮች ዉስጥ አንዱና ግንባር ቀደም መሆኑን ገልፀዉ የክልሉን ማህበረሰብ ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ዋነኛ ተግባር አድርጋ ቤተክርስቲያኗ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
የሰላም እጦት በክልሉ ባለፉት ጊዜያት በተፈጠሩ አለመግባባቶች ብዙ የልማት ስራዎች ሳንሰራ የቀረን ሲሆን የሰላምን ዋጋ በመገንዘብ የሰላም ግንባታዉ እንዲዳብር ብዙ መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የእምነት ተቋማቱ በጋራ በመሆን ያለዉን ሰላም ለማስቀጠል የጋራ የሆኑ ጉዳዮች ላይ ልንሰራ ይገባልም ብለዋል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ነው።
ተጨማሪ ዝርዝር በፌስቡክ ገጻችን መመልከት ትችላላችሁ
❤4👍2👏1🙏1