The Christian News
5.08K subscribers
3.66K photos
51 videos
911 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍና ልማት ኮሚሽን #አዲስ የተሾሙት የቦርድ አባላትን የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የእውቅና መረሃ ግብር አካሄደ።

ኮሚሽኑ በመረሃ ግብሩ በቦርድ አመራርነት እንዲሁም አባል ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትን በማመስገን እውቅና የመስጠት መረሃ ግብር በቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጽፈት ቤት አካሂዷል።

በመድረኩ የኮሚሽኑ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀርበ ሲሆን የቀጣይ አምስት ዓመት ስልታዊ እቅድ አሰራር በሚመለከት ከአዲሱ የቦርድ አባላት እና አመራር ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎል።

ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ ጨምሮ ልማት ኮሚሽኑን ላገለገሉ አካላት የእውቅና ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ጸሎት በማድረግ ዶ/ር ተስፋዬ ያዕቆብ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ፤ የኮሚሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ዳንኤል ጫዕሜቦ ፤ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ተፈራ ተሎሬን ጨምሮ የቦርድ አባላት፤ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች እና የፕሮጀክት ስራ አስተባበሪዎች ተገኝተዋል።
4👍1🔥1
እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወዳገለገለችው ጌታ ሄዳለች።

#ዜና እረፍቷን ተከትሎ የሀልዎት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሀዘኗን ገልጻለች።

ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫዋ እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ በሀልዎት አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን አባል ሆና በሀርመኒ የመዘምራን ኀብረት ውስጥ እንዲሁም በሶሎ ዝማሬ ስታገለግል የቆየች የተወደደች እህት መሆኗን በመጥቀስ ወዳገለገለችው አምላኳ ሔዳለች፤ ወደ ዘላለማዊው እረፍቷ፤ ወደ ሰማዩ ቤቷ ገብታለች ሲሉ ተናግረዋል።

ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫው በእህታችን በስጋ ከእኛ መለየት ብናዝንም ሀዘናችን ግን ተስፋ እንደሌላቸው አይደለም።

ከሞት ወዲያ ባለው ሕይወት ዳግመኛ እንደምንገናኝ ስለምናውቅ በሱ እንጽናናለን በማለት ለቡታጅራ ከተማ ምዕመናን መጋቢዎቿና አብራችኋት ስታገለግሉ ለነበራችሁ፣ ለሀልዎት አማኑኤል ኅብረት መዘምራን እንዲሁም ለቤተሰቦቿና ለጓደኞቿ መፅናናትን ተመኝታለች።

ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። …….. ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።

ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። (1 ተሰሎንቄ 4:13-18)

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በእህታችን ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለወዳጅ ዘመዶቿ ለጓደኞቿ መፅናናትን እንመኛለን።
😭8🙏42💔1
#አዲስ አመት
#አዲስ ጫማ

ዊን ሶልስ ፎር ጎድ ኢቫንጄሊካል ሚኒስትሪስ እና ብራይት ስታር ኢትዮጵያ የ2017 ዓመተ ምህረት የክረምት ወራቶች በአዲስ ዓመት አዲስ ጫማ የተሰኘውን መርኃ ግብሩን ማጀመሩን ገለጸ፡፡

በ2016 ዓመተ ምህረት የክረምት ወራቶች በአዲስ አመት አዲስ ጫማ የተሰኘ መርኃ ግብር በማስጀመር 1,100 በላይ ለሚደርሱ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን ጨምሮ ጫማ፣ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስና የተለያዩ ግብአቶችን በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ ከሚገኙ ግለሰቦች እንዲሁም ተቋማት በማሰባሰብ ድጋፍ ማድረግ ተችሎ እንደነበር የብራይት ስታር ዳይሬክተር ቄስ ዶክተር በፍርዱ መሰረት ተናግረዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ዳይሬክተሩ የ2016 ዓመተ ምህረት ንቅናቄ ግቡን እንደመታ ገልፀው ድጋፍ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል፡፡ በአዲስ አመት አዲስ ጫማ የተሰኘው መርኃ ግብር ወገኖች አሮጌ ነገራቸውን ትተው አዲስ በሆነው አመት አዳዲስ የትምህርት ግብአቶችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን የመስጠት ልማድ ለማዳበርና ባህል ከማድረግ አንፃር የተነሳ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል፡፡

የመስጠት ባህላችንን ለማሳደግ ታልሞ እየተሰራ የሚገኘው ንቅናቄ ከተቋሙም ባሻገር ሰዎች በአካባቢያቸው ለሚገኙ ወገኖች አዳዲስ ነገሮችን መስጠት እንዲችሉም ተጠቁሟል፡፡

በዘንድሮው2017 ዓመትም የክረምት እንቅስቃሴ እንደ አምናው ሁሉ ከአንድ ሺ አንድ መቶ በላይ ጫማዎችን ጨምሮ የተለያዩ የትምህርት ግብአቶችን ለማሰባሰብ መታቀዱን የብራይት ስታር ዳይሬክተር ጨምረው ገልፀዋል፡፡

መረጃውን ጋዜጠኛ ጸጋህይብዛ ኢሳይያስ አደረሰን
4👍1🙏1
#ቦታ ሞልቷል፣ እንዳያመልጠን ለምትሉ 2 ጥንዶች እድል እንሰጣለን! አሁኑኑ ተመዝገቡ!

ከሀሙስ ከምሽቱ 2:00 በኋላ ምዝገባ አንቀበልም‼️

በጎጆዬ የጋብቻና የልጆች አስተዳደግ የተገኙ ባለትዳሮች ምን ያገኛሉ?

የመጀመሪያው ቅዳሜ

የጋብቻቸውን ትርጉም እና ዓላማ ያድሳሉ፣ የጋራ ራዕይ ይሰንቃሉ፣ ይቀርፃሉ፤

ሁለተኛው ቅዳሜ

እንደባልና ሚስት ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን ማንነት በጥልቀት ያስተውላሉ፣ እርስ በርስ ስለቀደሙ ብዠታዎች ይቅር ይባባላሉ ፣ ለማክበር እና ለመተባበር ቃል ይገባባሉ፤

ሦስተኛው ቅዳሜ

ዋና ዋና ጉዳዮች ይዳሰሳሉ ፣ ፍቅር ፣ ተግባቦት ፣ ወሲብ እናም ከእነዚህም መካከል ወሳኝ ስለሆነው የተግባቦት ጥበብና ክህሎት ይቀስማሉ ፣ ይለማመዳሉ ፤

አራተኛው ቅዳሜ

እንደወላጅ ለልጆቻቸው የጋራ ራዕይን ይሰንቃሉ፣
እነዚህ ቀናት በግል የምክር አገልግሎት ይጠናቀቃሉ።

ከእነዚህ ቀናት በኋላ ፦
👉 ትዳራቸው ይታደሳል ፣
👉የጋራ ቋንቋ ያዳብራሉ፣
👉ትናንትናን በይቅርታ ይዘጋሉ፣
👉ነገን በጥበብ ፣ ማስተዋልና እውቀት ለመምራት ይታጠቃሉ፣ ይወስናሉ ፣ ቃል ይገባባሉ፤

ውድ ባለትዳሮች ፣ እናንተስ?

ዛሬውኑ ተመዝገቡ!

ቀን፣ ሐምሌ 5፣ 12፣ 19፣ 26
ሰዓት፦ ከቀኑ 8:00-11:00
ቦታ፦ በቀድሞው ኢሞፔሪያል ውሃ ልማት በጨጨሆ ገባ ብሎ!
ለመመዝገብ፦ 0911136520/0946693468

ከዚህ በፊት የሰራናቸውን ስራዎች ለማወቅ 👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
yebetesebkitiradash.org
Yebeteseb Kitir Adash
4👍3🔥1
በታንዛኒያ ከመላው #አለም የተወጣጡ ክርስቲያኖች ለ5 ቀናት ተሰብስበዋል።

ለ5ቀናት በሚቆየው ስብሰባ ክርስቲያኖች እና ቤተ ክርስቲያን በዚህ ተለዋዋጭ አለም የሚኖራቸው ሚና ላይ ጸሎት ያደርጋል፣ ውይይት ይካሄዳል፣ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ፣ ተብሎ ይጠበቃል።

መረሃ ግብሩ የሚካሄደው “Dancing in Faith – Drumming up Hope” የጉባኤው መሪ ቃል ነው።

ጉባኤውን ያዘጋጀችው የታንዛኒያ ሉተራን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ስትሆን የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች ጉባኤው በታንዛኒያ ምድር በመካሄዱ ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ለምድራችንም ለቤተ ክርስቲያንም ትልቅ በረከት ይሆናል ብለዋል።

የአለም ዲያቆኒያ ፌደሬሽን ጉባኤ በተባለለት በዚህ ጉባኤ የመጽሃፍ ቅዱስ ጥናት፣ የአምልኮ፣ ባህላዊ እሴቶችን ማሳወቅ፣ የዲያቆናት አገልግሎትን በተመለከተ ውይይቶች ይኖራል ተብሏል ሲል ያስነበበው የአለም ሉተራን ፌደሬሽን ነው።

ሐምሌ 4 /2017 ዓ.ም
5👍2🔥1👌1
"አባካኙ #ልጅ" ተመረቀ።

በተወዳጇ ዘማሪት ቤተልሔም ተዘራና በባለቤቷ መንግስተ አብ ተገኝ የሚመራው የሊቪንግ ዊትነስ ሚኒስትሪ ራዕይውን በማስተዋወቅ "አባካኙ ልጅ" የተሰኘውን አጭር ፊልም ለተመልካች አቀረበ።

በትላንትናው እለት በሽራተን ሆቴል በተደረገው መረሃ ግብር የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ አገልጋዮች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ወንድም መንግስተአብ ተገኝ ለጉባኤው የሊቪንግ ዊትነስ ሚኒስትሪ ራዕይን ያስተዋወቁ ሲሆን የዘማሪት ቤተልሔም ተዘራ የዝማሬ አገልግሎት የሚተርክ ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል።

"አባካኙ ልጅ" የተሰኘው ይህ ሙዚቃዊ አጭር ፊልም ሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ላይ የተመሰረተው ሲሆን ፓስተር በቀለ ወልደኪዳንን እና ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ ጨምሮ የተለያዩ አንጋፋ ዘማሪዎች እና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ለጉባኤው በማቅረብ የእግዚአብሔርን የፍቅር ጥግ ምን ያህል እንደሆነ በመግለጽ ግንዛቤ ፈጥሯል።

#የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ በጸሎት ዘማሪ ህሊና ዳዊት ዝማሬ በማቅረብ ቄስ ትግስቱ ሞገስ የእግዚአብሔርን ቃል መልዕክት በማቅረብ አገልግለዋል።

በመጨረሻም በፊልሙ ላይ ለተሳተፋ ወገኖች የሰርተፍኬት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።

ምንጭ #GMM TV ETHIOPIA

ሐምሌ 4 /2017 ዓ.ም
9👍4🔥1👌1
#ነገ ይጀመራል። #ቅዳሜ ሐምሌ 05/2017 ዓ.ም በ5ኪሎ መካነየሱስ 8:00 ሰዓት ይጀመራል።

በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች) የተመዘገባችሁ በሙሉ

መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ነገ እንደሚጀመር ልናሳዉቃችሁ እንወዳለን።

ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

📍 ቦታ፡ #አዲስ አበባ 5ኪሎ መካነየሱስ ቤተክርስቲያን

(5ኪሎ መ/ኢየሱስ)

አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን

ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822

ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።

https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
👍51
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት #ስልጠና መስጠት ተጀመረ።

ክረምትን አስመልክቶ የተዘጋጀው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና #በአዲስ አበባ (5ኪሎ) መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተጀምሯል።

ከሃምሌ 5 እስከ ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 8 ሳምንታት የሚቆየው ስልጠና በዋናነት የጋዜጠኝነት መሰረታዊያን ፤ የዜና አጻጻፍ እና ሀሰተኛ የዜና ስርጭቶችን መቀነስ ፤ ስነጽሁፍ እና ዲጂታል ሚዲያን ጨምሮ ዘጋቢ ፊልምን በተግባር ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።

በሚኖሩት ሳምንታት እራሳቸውን በስነምግባር ብቁ አድርገው ቤተክርስቲያንን በዲጅታል ሚዲያ በማገዝ እንዲሁም የሚሰሩትን ስራ በተግባር እንዲያሳድጉ ሊያደርግ የሚችል የስልጠና ጊዜ እንደሚኖር በነበረው የመክፈቻ መረሃ ግብር የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም ደመላሽ ዶላ ተናግረዋል።

ስልጠናው The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከየደስ ደስ መልቲ ሚዲያ እና ቲኪቆስ ሚዲያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ስልጠና ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ከአዲስ አበባ ባሻገር በሃዋሳ እንደሚጀምር ታውቋል።
👍71🔥1🙏1
#አዲሱ ዋዪማ እና #አስፋው መለሰ 6ኛ የመዝሙር አልበማቸውን አስመረቁ።

ዛሬ ቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ እና ልደታ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤ/ክ ነው ያስመረቁት።

የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ አልበም “Bara Baraakoo” የሚሰኝ ሲሆን፣ የዘማሪ አስፋው መለሰ አልበም “አንተን አልጣ እንጂ” ነው። የአዲሱ ዋዪማ አልበም 13 መዝሙሮች ሲኖረው፣ የዘማሪ አስፋው አልበም 11 መዝሙሮች አለው።

ሁለቱም ዘማሪዎች ወዳጆች፣ ተጋባዥ ዘማሪዎች እና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት በስኬት ተመርቋል። በሚያኮራ ሁኔታ ሁለቱም ዘማሪዎች አልበማቸውን የመረቁት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ቆመው ነው።

የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ አልበሞች
• “Eenyudharee gootni”
• “Utuu badnee kanaan dura”
• “Attamiin galaanni na ittisa”
• “Amanannaakoo”
• “Duulli kun duula lubbuuti”
• “Ijibbaata”
• 6ኛ “Bara baraakoo”

የመጋቢ እና ዘማሪ አስፋው መለሰ አልበሞች
• “ብዙ ዘመን ራራህልኝ”
• “በጅምር አይቀርም የኔ ነገር”
• “ትላንት ዛሬ አይደለም”
• “የሩቅ ህልሞቼ”
• “ይሁን”
• 6ኛ "አንተን አልጣ እንጂ” ናቸው

ሁለቱም በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከ20 አመታት በላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በታማኝነት አገልግለዋል።

የክርስቲያን ዜና ትውልድ ለተሻገረ፣ ብዙዎችን ላጽናና፣ ለብዙዎች በረከት የሆነ አገልግሎታችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይላል።

መዝሙሮቻቸውን በዩቱብ ገጾቻቸው ማግኘት ትችላላችሁ።

ዘማሪና መጋቢ አስፋው መለሰ
https://www.youtube.com/@asfawmelese

ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ
https://www.youtube.com/@addisuwayima

በኦቦሌሳ አዶላ
9👍2🙏2🔥1
ፓስተር ጆን ማከርተር አረፉ

በከሜሪካን ሃገር ግሬስ ኮሚኒቲ ቤ/ክ ለ56 አመታት ሲያገለገሉ የነበሩት ፓስተር ጆን ዛሬ ማለዳ ማረፋቸውን 'Grace to You" የተሰኘው ሚኒስትሪያቸው አስታውቋል።

በአገልግሎት ዘመናቸው ለህትመት የበቁ እና አርትኦት የሰሩባቸው ከ150 በላይ መጽሃፍት ለአንባቢያን አድርሰዋል። በቤተ ቤተርስቲያን አገልግሎት፡ በሴሚናሮች በማስተማር እና ከ1969 ዓ.ም ጀምሮ "Grace to you" በተሰኘ ሚድያ ወንጌል ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

ጆን ማከርተር በገጠማቸው የሳምባ ምች (Pneumonia) በሽታ ታመው ሆስፒታል በገቡበት በ86 አመታቸው ማረፋቸውን ሚኒስትሪያቸው አሳውቋል።

በኦቦሌሳ አዶላ
22🔥4😭1
50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዬቤልዩ

በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ የደቡብ ምስራቅ ክልል የባሌ ጎባ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።

በክብረ በዓሉ መረሃ ግብር ላይ በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩት የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት መጋቢ ጻዲቁ አብዱን ጨምሮ ከመጋቢ ጻዲቁ አብዱ ጋር ከጅማሬው አንስቶ በጋራ ወንጌልን ያገለገሉ እና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡

የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ለአባላቱ በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻውን ጨምሮ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

በበዓሉ ላይም የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡

በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ በታላቅ ደስታና መጽናናት እንደሚሆን #መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
9👍2🔥1👏1
#በሱዳን አንድ አብያተ ክርስቲያን በወታደር እገዛ መፍረሱ ተነግረ።

የሱዳን ጴንጤቆስጤ ቤተ ክርስቲያን መካከል አንዷ በካርቱም ምስራቅ ናይል በሚባልበት አካባቢ ያለችው ቤ/ክ ናት የፈረሰችው። ቤተ ክርስቲያን ህንጻ ፈረሳው ሲካሄድ፣ የፖሊስ እና ወታደራዊ አካላት በስፍራው የነበሩ ሲሆን ህንጻውን ያፈረሱት ደግሞ ከ20 የማያንሱ ግለሰቦች ናቸው።

የቤተ ክርስቲያን ህንጻ የተገነባው በ1990 ሲሆን፣ የአምልኮ አገልግሎት እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል። ፖሊሶች በስፍራው ግለሰቦች ሲያፈርሱ ማንም ሰው እንዳይቀርጽ ሲከለክሉ ነበር።

የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች ቤተ ክርስቲያኗ መልሳ እንድትገነባ እና ክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ስደት እንዲቆም ጸሎት ይደረግልን ሲሉ ጠይቀዋል። ክርስቲያኖችን ከሱዳን የማውጣት እንቅስቃሴ በሰፊው እየተካሄደ ይገኛል ተብሏል።

የተለያየ አይነት አመጽ፣ አስገድዶ ጋብቻ፣ ጾታዊ ጥቃት፣ ልጆችን መነጠቅ፣ ርስት መነጠቅ እና ሃሰተኛ ክሶች በሱዳን ያሉ ክርስቲያኖች በየ እለቱ የሚያልፉባቸው መከራዎች ናቸው። ከዚህ ባለፈ፣ በጦርነት ወቅት በሚያጋጥም፣ ርሃብ ወቅት ክርስቲያኖች ተለይተው ምግብ አይደርሳቸውም።

ከሙሉ ህዝቧ 2 ሚሊዮን የሚሆነው ወይም 4.1 % የሚሆነው ክርስቲያን ቢሆንም የክርስቲያኖች ግድያ እና ጠለፋ በተደጋጋሚ ይስተዋላል። ሱዳን በኦፕን ዶርስ አመታዊ መረጃ መሰረት 5ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
አሁንም የሱዳን ክርስቲያኖች ጥያቄያቸው ግን “ጸሎት” ብቻ ነው ሲል ያስነበበው ዎርዚ ኒውስ ነው።

በኦቦሌሳ አዶላ
😭176🙏6🕊2💔1
በአሮሬሳ መጆ #ሙሉ #ወንጌል አማኞች #ቤተክርስቲያን በቡቤ-ቦሬ ቀበሌ ሐዳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ከስድስት ወራት በፊት የተተከለችው ሐዳ አዳጊ ቤተክርስቲያን የአምልኮ አዳራሿን መስራት ጀምራለች።

ከሰሞኑ ቤተክርስቲያኒቷ የአምልኮ አዳራሿን ለመሥራት መሠረት የጣለች ሲሆን የአሮሬሳ መጆ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ አባላት በነፍስ ወከፍ በመውጣት ለግንባታው ሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለግሰዋል።

በሂደቱም የአሮሬሳ መጆ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን፣ የአሮሬሳ መጆ ስታዲየም ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን እና የሶዶ አዳጊ ቤተክርስቲያን አባላት ተሳትፈዋል።

በቀጣይነት ሁላችንም ወደ ሶዶ አዳጊ ቤተክርስቲያን እንደምንዘምት ፓ/ር በቀለ ሐዴሶ ገልጸዋል።

ክብር ሁሉ ለሥራው ባለቤት ለእግዚአብሔር ይሁን !!!
9🔥3👍2🥰1🙏1👌1
ታላቅ የአምልኮ ኮንሰርት እና የወንጌል ድግስ በሚሊኒየም አዳራሽ ሊካሄድ ነው።

በመጋቢ ትዝታው ሳሙኤል የምትመራው የዘላለም ሕይወት ዓለም አቀፍ ቤተክርስቲያን አዘጋጅነት ሐምሌ 26 ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ የሚካሄደውን የወንጌል ኮንሰርቱን አስመልክቶ በዛሬው እለት ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል።

በመግለጫው ከ13 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገር የተመለሰው መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል “ዛሬ ለኢየሱስ” በሚል ርዕስ #እግዚአብሔር በሰጠን ጸጋ በዝማሬ እንደሚያገለግል ተገልጿል።

ኮንሰርቱ 3 ዓላማዎች እንዳሉት የተገለጸ ሲሆን የመጀመሪያው አምላካችንን በዝማሬ ማክበር ሲሆን ፤ በሁለተኛ ደረጃ ወንጌል በማወጅ አዳዲስ ነብሳትን ለክርስቶስ መማረክ እንዲሁም ለምድራችን እና ለሕዝባችን እረፍት እንዲሆን ጸሎት ማድረግ እንደሆነ መግለጫውን የሰጡት መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል ተናግረዋል።

ለበርካታ አመታት ከምወዳቸው ሕዝቦች ጋር በጋራ ለማገልገል ብዙ ሲመኝ እንደነበር እና ይህ ከ13 ዓመት በኋላ መሳካቱን በመጥቀስ ነጭ ለብሳችሁ በመምጣት አብረን እንድናመልክ መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል ጥሪ አቅርበዋል።

መግለጫውን መጋቢ በጋሻው ደሳለኝ ፤ መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል እና ዘማሪት ዘርፌ ከበደ የሰጡ ሲሆን በእነዚህ ወንድሞች እና እህታችን አገልግሎት የተባረኩ በሙሉ በአዲስ አበባ እና አከባቢው የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች ተገኝተው አብረውን እንዲያመልኩ ጥሪ አቅርበዋል።

መጋቢ ትዝታው ሳሙኤል ዘማሪ፤መጋቢ እና የዝማሬ ግጥሞችን የሚጽፍ ሲሆን “ሊነጋ ሲል ይጨልማል” “መርከቤ” “ስመሰክር” እና “ማን ቀረ ከሜዳን” ጨምሮ ከ15 በላይ ዝማሬዎችን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ያበረከተ መጋቢ ሲሆን በተለይ በ90 ዎቹ እጅግ ተወዳጅ ከነበሩ ዘማሪዎች መካከል አንዱ እንደነበር ይታወሳል።

በዮሐንስ ግርማ
35❤‍🔥2🔥2👍1👌1
እዩ ጩፋ ካውንስሉን ይቅርታ ጠየቀ

የክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል በቅርቡ በሚዲያ ላይ እንደሰማችሁት ለተፈጠሩት ክፍተቶች ከካውንስሉ የስነ መለኮት ኮሚሽን እና የህግ ኮሚሽን ጋር ዉይይት ካደረገን በኋላ ቤተክርስቲያናችን በጉዳዩ ላይ ስንፀልይና ስንመካከር ቆይተን የደረስንበትን ስምምነት እንደሚከተለው እናቀርባለን።

ካውንስሉን እና የካውንስል አመራሮች በተመለከተ በቴሌቭዥን እና በማህበራዊ ሚዲያዎች ለተጠቀምናቸው ያልተገባ ቃላት ቅር የተሰኛችሁ ሁሉ ይቅርታ እንጠይቃለን።

ከዚህ ቀን ጀምሮ ካውንስሉን ከሚመሩ መሪዎቻችን ጋር በቅርበት እየተነጋገርን እንደ አባት እና ልጅ ተቀራርበን የክርስቶስን ወንጌል መንፈሳዊ ጨዋነት ተከትለን ቀዳሚዎቻችንን አክብረን ለማገልገል የተስማማን መሆኑን እየገለፅን ካውንስሉም ይቅርታችንን ተቀብሎ አባታዊ በሆነ መንገድ እየመከረን እና እያስተማረን እንዲመራን በመተማመን ይህንን መግለጫ እንደ ቤተክርስቲያን አውጥተናል።
👍34👏12🤣106🔥2👌1
አታዋሌ - “Let Jesus Reign”

#ኢየሱስ #ይንገስ ወይም #“Let Jesus Reign” በሚል መሪ ቃል በሐልዎት አማኑኤል ህብረት ቤ/ክ የወጣቶች ኮንፈራንስ ተካሄደ። ፕሮግራሙ በአታዋሌ ኢንተርናሽናል ሚኒስትሪ እና ፒስ ጌት ሆሊስቲክ ሚኒስትሪ በጋራ የተዘጋጀ ነው።

ፕሮግራሙ በተለይ ወጣት አገልጋዮችን ማስታጠቅ ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን፣ ሜንቶሪንግ፣ ተተኪ መሪዎች ማፍራት፣ አውዳዊ የወንጌል ስርጭት እና ድንበር ዘለል የወንጌል ስርጭት በኮንፈረንሱ የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

የኮንፈራንሱ መሪ ቃል “Let Jesus Reign” ወይም ኢየሱስ ይንገስ በሁሉም ነገር ላይ ኢየሱስ ብቻ መንገስት አለበት የሚለውን ሃሳብ ከፍ አድርጎ ለማሳየት የታሰበ መሆኑን የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም #ሳሙኤል በላይነህ ለክርስቲያን ዜና ተናግረዋል።

በፕሮግራም እንዲያስተምሩ የተጋበዙት የአታዋሌ ኢንተርናሽናል ሚኒስትሪ መሪ ፓስተር #ራምጃኒ ጆሽዋ እና በአለም አቀፍ የተማሪዎች አገልግሎት ሪጅናል ዳሬክተር ወንድም #ዘላለም አበበ ናቸው። ተናጋሪዎቹ በትምህርቱ ነገ ወጥቶ ከድንበሩ ያለፈ ወንጌል ሰባኪ እና ከፊቱ ሰው ያለ እና ከኋላውም የሚረከበው እንዲሁም የሚያማክረው ሰው መኖር አገልግሎት አስፈላጊነት ዙሪያ አስተምረዋል።

የፒስ ጌት ሆሊስቲክ ሚኒስትሪ ዳይሬክተር ወንድም ሳሙኤል በላይነህ፣ የኮንፈራንሱ ተሳታፊዎች የተፈጠሩበትን አላማ ማወቅ እና ለአላማቸው መኖርን ከዚህ ሰንቀው መውጣትን እና አላማቸውን ደግሞ በሚገባ መኖርን ከእነርሱ እንጠብቃለን ብለዋል።

#“አታዋሌ” የስዋህሊ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ኢየሱስ ይንገስ ማለት ነው።
9👍1🔥1👌1