የምስራቅ ጉጂ መሠረተ #ክርስቶስ ኮሌጅ በታሪኩ የመጀመሪያ ተማሪዎቹን አስመረቀ።
በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ የምስራቅ ጉጂ ስነ-መለኮት ኮሌጅ ዛሬ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በሻኪሶ ከተማ ተማሪዎቹን አስመርቋል።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ስር የሚገኘው ኮሌጁ በዲግሪ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን 14 ተማሪዎች ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመረቀው።
በምረቃ ፕሮራሙ ላይ የተገኙት በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የክልል ካምፓሶች ተጠሪ መምህር ታደሰ በዬቻ የእግዚአብሔር ቃል ከማቅረብ ባለፈ ባደረጉት ንግግር "በድግሪ መመረቅ ማለት ከሳሎን ወደ ግቢ መውጣት ነው ሩቅ የሄዳችሁ እንዳይመስላችሁ ስለዚህ መማራችሁን ቀጥሉ" ብለዋል።
የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ዋና ጸሐፊ መጋቢ ትዕግስቱም "ተመራቂዎች የክልሉ እድገት ማሳያና የመጀመሪያዎቹ ታሪካዊ ምሩቃን በመሆናችሁ #እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ተናግረዋል።
ተመራቂዎችም የመጀመሪያ ተመራቂዎች በመሆናቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። በፕሮግራሙ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቷል።
የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በአሁን ሰዓት 815 ተማሪዎችን በመያዝ በሀገሪቱ በሚገኙ 23 ካምፓሶች ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ምንጭ:- Meserete Kristos Church - Head Office
ሰኔ 29/2017ዓ.ም
ሻኪሶ
በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ የምስራቅ ጉጂ ስነ-መለኮት ኮሌጅ ዛሬ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በሻኪሶ ከተማ ተማሪዎቹን አስመርቋል።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ስር የሚገኘው ኮሌጁ በዲግሪ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን 14 ተማሪዎች ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመረቀው።
በምረቃ ፕሮራሙ ላይ የተገኙት በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የክልል ካምፓሶች ተጠሪ መምህር ታደሰ በዬቻ የእግዚአብሔር ቃል ከማቅረብ ባለፈ ባደረጉት ንግግር "በድግሪ መመረቅ ማለት ከሳሎን ወደ ግቢ መውጣት ነው ሩቅ የሄዳችሁ እንዳይመስላችሁ ስለዚህ መማራችሁን ቀጥሉ" ብለዋል።
የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ዋና ጸሐፊ መጋቢ ትዕግስቱም "ተመራቂዎች የክልሉ እድገት ማሳያና የመጀመሪያዎቹ ታሪካዊ ምሩቃን በመሆናችሁ #እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ተናግረዋል።
ተመራቂዎችም የመጀመሪያ ተመራቂዎች በመሆናቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። በፕሮግራሙ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቷል።
የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በአሁን ሰዓት 815 ተማሪዎችን በመያዝ በሀገሪቱ በሚገኙ 23 ካምፓሶች ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ምንጭ:- Meserete Kristos Church - Head Office
ሰኔ 29/2017ዓ.ም
ሻኪሶ
👍4❤3🔥1
"አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው ትያትር ተመረቀ።
በትላንትናው እለት ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በፕሮቪዥን ፈልሞች የተዘጋጀው እና "አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ዘንድ የመጀመሪያው የሆነው ትያትር በቫምዱስ ሲኒማ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቆ ለእይታ ቀርቧል።
የትያትሩ ደራሲና ደይሬክተር ሄኖክ በቀለ “በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ዘንድ እንደዚህ አይነት ስራ አልተለመደም” ያሉ ሲሆን #ይህ የመጀመሪያ ቢሆንም ከዚህ በኋላ ብዙ ስራዎችን በትያትር መልኩ ለመስራት እንዳቀዱ ተናግረዋል።
#እውነት እና #ፍቅር የሚያጠነጥነው አውነትን በቀጥታ መናገርና ፍቅርን መስጠት ላይ የሚያተኩር ሆኖ በሁለት መሃል ያለውን ውዝግብ የሚያሳይ እንደሆነ ደራሲው ገልጿል።
ፕሮቪዥን ፈልሞች ላለፉት ሁለት ዓመታት በጂዶ-ክርስቲያናዊ የሥነ-ምግባር ዕሴት ላይ ታንጾ በጥበብ ዘርፍ እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ሲሆን ፕሮቪዥን ፊልሞች የተቋቋመው በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት አባል ከሆኑ ቤተ ዕምነት የተወጣጡ የትያትር ፣ የሚድያ #እና የፊልም ባለሙያዎች መሆኑ ተገልጿል።
ትያትሩ 55 ደቃቅ ርዝመት የለው ሲሆን በዚህ ትያትር ላይ 4 ዋና ዋና ተዋናዮችና በረካታ ሰዎች በስራው ላይ ተሳትፈዋል።
በትያትሩ ላይ ለተሳተፉት በሙሉ የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ሲሆ በቀጣይም በየሳምንቱ በሻምዱስ ሲኒማ የምታይ መሆኑ ተገልጿል።
ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ
በትላንትናው እለት ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በፕሮቪዥን ፈልሞች የተዘጋጀው እና "አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ዘንድ የመጀመሪያው የሆነው ትያትር በቫምዱስ ሲኒማ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቆ ለእይታ ቀርቧል።
የትያትሩ ደራሲና ደይሬክተር ሄኖክ በቀለ “በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ዘንድ እንደዚህ አይነት ስራ አልተለመደም” ያሉ ሲሆን #ይህ የመጀመሪያ ቢሆንም ከዚህ በኋላ ብዙ ስራዎችን በትያትር መልኩ ለመስራት እንዳቀዱ ተናግረዋል።
#እውነት እና #ፍቅር የሚያጠነጥነው አውነትን በቀጥታ መናገርና ፍቅርን መስጠት ላይ የሚያተኩር ሆኖ በሁለት መሃል ያለውን ውዝግብ የሚያሳይ እንደሆነ ደራሲው ገልጿል።
ፕሮቪዥን ፈልሞች ላለፉት ሁለት ዓመታት በጂዶ-ክርስቲያናዊ የሥነ-ምግባር ዕሴት ላይ ታንጾ በጥበብ ዘርፍ እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ሲሆን ፕሮቪዥን ፊልሞች የተቋቋመው በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት አባል ከሆኑ ቤተ ዕምነት የተወጣጡ የትያትር ፣ የሚድያ #እና የፊልም ባለሙያዎች መሆኑ ተገልጿል።
ትያትሩ 55 ደቃቅ ርዝመት የለው ሲሆን በዚህ ትያትር ላይ 4 ዋና ዋና ተዋናዮችና በረካታ ሰዎች በስራው ላይ ተሳትፈዋል።
በትያትሩ ላይ ለተሳተፉት በሙሉ የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ሲሆ በቀጣይም በየሳምንቱ በሻምዱስ ሲኒማ የምታይ መሆኑ ተገልጿል።
ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ
❤2👍2👌1
21ኛው የክርስቲያን ሴቶች ኮንፈረንስ በቤዛ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን ተካሄደ።
"አንቺን ለፅድቅ" በሚል በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር የፀሎት የትምህርትና የአንድነት ጊዜም ተደርጓል። ከሰኔ 24 እስከ 27 2017 ዓ.ም በተካሄደው በዚህ ጉባኤም ከተለያዩ ከባህር ማዶ እና ከሀገር ውስጥ የመጡ አገልጋይ እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
#ይህ የሴቶች ጉባኤ ከተጀመረ ሁለት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን ቀደም ሲል በሰሜን #አሜሪካ ፣ በካናዳና በአውሮፓ ሲካሄድም ቆይቷል።
አገልጋይ ሶፊያ አሰፋ እንደገለፁትም ከተለያዩ የአሜሪካ እስቴት እህቶች ተሳታፊ መሆናቸውን በመግለፅ ሁሉም በቅድስና መመላለስ እንደሚገባም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በሌላ በኩል ፓስተር ህሊና ግርማ የነበረው የአንድነት ጊዜ #መልካም መሆኑን በመግለፅ ኮንፈረንሱ እህቶች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ማድረጉን ገልፀዋል።
በእለቱም በኪንግደም ሳውንድ የዝማሬና የጋራ የአንድነት ጊዜ የተካሄደም ሲሆን የኢትዮጵያ ኢቫንጄሊካል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ዶክተር ትሁት አስፋው በእግዚአብሔር ቃል አገልግለዋል። በመልዕክታቸውም ሁሉም በተሰጠው ፀጋ አገልግሎቱ እንደሚቀጥልም በመግለፅ ይህም አገልግሎት ከትውልድ ትውልድ እንደሚሻገርም ገልፀዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም ሁሉም አማኝ በተሰማራበት ሁሉ በትክክልኛ ክርስቲያናዊ አሰራር መስራት እና ማገልገል እንዳለባቸውም ገልፀዋል። ማንኛውም ክርስቲያን አዎንታዊ ተፅዕኖዎችን ማስተጋባት እና ማሻገር እንደሚችል እና ይህንንም ለማድረግ በቅድስና መመላለስ እንደሚገባም በትምህርቱ ወቅት ተወስቷል።
መረጃው የGMM TV Ethiopia ነው።
ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ
"አንቺን ለፅድቅ" በሚል በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር የፀሎት የትምህርትና የአንድነት ጊዜም ተደርጓል። ከሰኔ 24 እስከ 27 2017 ዓ.ም በተካሄደው በዚህ ጉባኤም ከተለያዩ ከባህር ማዶ እና ከሀገር ውስጥ የመጡ አገልጋይ እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
#ይህ የሴቶች ጉባኤ ከተጀመረ ሁለት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን ቀደም ሲል በሰሜን #አሜሪካ ፣ በካናዳና በአውሮፓ ሲካሄድም ቆይቷል።
አገልጋይ ሶፊያ አሰፋ እንደገለፁትም ከተለያዩ የአሜሪካ እስቴት እህቶች ተሳታፊ መሆናቸውን በመግለፅ ሁሉም በቅድስና መመላለስ እንደሚገባም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በሌላ በኩል ፓስተር ህሊና ግርማ የነበረው የአንድነት ጊዜ #መልካም መሆኑን በመግለፅ ኮንፈረንሱ እህቶች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ማድረጉን ገልፀዋል።
በእለቱም በኪንግደም ሳውንድ የዝማሬና የጋራ የአንድነት ጊዜ የተካሄደም ሲሆን የኢትዮጵያ ኢቫንጄሊካል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ዶክተር ትሁት አስፋው በእግዚአብሔር ቃል አገልግለዋል። በመልዕክታቸውም ሁሉም በተሰጠው ፀጋ አገልግሎቱ እንደሚቀጥልም በመግለፅ ይህም አገልግሎት ከትውልድ ትውልድ እንደሚሻገርም ገልፀዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም ሁሉም አማኝ በተሰማራበት ሁሉ በትክክልኛ ክርስቲያናዊ አሰራር መስራት እና ማገልገል እንዳለባቸውም ገልፀዋል። ማንኛውም ክርስቲያን አዎንታዊ ተፅዕኖዎችን ማስተጋባት እና ማሻገር እንደሚችል እና ይህንንም ለማድረግ በቅድስና መመላለስ እንደሚገባም በትምህርቱ ወቅት ተወስቷል።
መረጃው የGMM TV Ethiopia ነው።
ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ
❤3👍3🔥1🥰1👌1
#የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍና ልማት ኮሚሽን #አዲስ የተሾሙት የቦርድ አባላትን የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የእውቅና መረሃ ግብር አካሄደ።
ኮሚሽኑ በመረሃ ግብሩ በቦርድ አመራርነት እንዲሁም አባል ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትን በማመስገን እውቅና የመስጠት መረሃ ግብር በቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጽፈት ቤት አካሂዷል።
በመድረኩ የኮሚሽኑ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀርበ ሲሆን የቀጣይ አምስት ዓመት ስልታዊ እቅድ አሰራር በሚመለከት ከአዲሱ የቦርድ አባላት እና አመራር ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎል።
ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ ጨምሮ ልማት ኮሚሽኑን ላገለገሉ አካላት የእውቅና ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ጸሎት በማድረግ ዶ/ር ተስፋዬ ያዕቆብ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ፤ የኮሚሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ዳንኤል ጫዕሜቦ ፤ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ተፈራ ተሎሬን ጨምሮ የቦርድ አባላት፤ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች እና የፕሮጀክት ስራ አስተባበሪዎች ተገኝተዋል።
ኮሚሽኑ በመረሃ ግብሩ በቦርድ አመራርነት እንዲሁም አባል ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትን በማመስገን እውቅና የመስጠት መረሃ ግብር በቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጽፈት ቤት አካሂዷል።
በመድረኩ የኮሚሽኑ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀርበ ሲሆን የቀጣይ አምስት ዓመት ስልታዊ እቅድ አሰራር በሚመለከት ከአዲሱ የቦርድ አባላት እና አመራር ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎል።
ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ ጨምሮ ልማት ኮሚሽኑን ላገለገሉ አካላት የእውቅና ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ጸሎት በማድረግ ዶ/ር ተስፋዬ ያዕቆብ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ፤ የኮሚሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ዳንኤል ጫዕሜቦ ፤ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ተፈራ ተሎሬን ጨምሮ የቦርድ አባላት፤ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች እና የፕሮጀክት ስራ አስተባበሪዎች ተገኝተዋል።
❤4👍1🔥1
እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወዳገለገለችው ጌታ ሄዳለች።
#ዜና እረፍቷን ተከትሎ የሀልዎት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሀዘኗን ገልጻለች።
ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫዋ እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ በሀልዎት አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን አባል ሆና በሀርመኒ የመዘምራን ኀብረት ውስጥ እንዲሁም በሶሎ ዝማሬ ስታገለግል የቆየች የተወደደች እህት መሆኗን በመጥቀስ ወዳገለገለችው አምላኳ ሔዳለች፤ ወደ ዘላለማዊው እረፍቷ፤ ወደ ሰማዩ ቤቷ ገብታለች ሲሉ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫው በእህታችን በስጋ ከእኛ መለየት ብናዝንም ሀዘናችን ግን ተስፋ እንደሌላቸው አይደለም።
ከሞት ወዲያ ባለው ሕይወት ዳግመኛ እንደምንገናኝ ስለምናውቅ በሱ እንጽናናለን በማለት ለቡታጅራ ከተማ ምዕመናን መጋቢዎቿና አብራችኋት ስታገለግሉ ለነበራችሁ፣ ለሀልዎት አማኑኤል ኅብረት መዘምራን እንዲሁም ለቤተሰቦቿና ለጓደኞቿ መፅናናትን ተመኝታለች።
ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። …….. ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።
ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። (1 ተሰሎንቄ 4:13-18)
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በእህታችን ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለወዳጅ ዘመዶቿ ለጓደኞቿ መፅናናትን እንመኛለን።
#ዜና እረፍቷን ተከትሎ የሀልዎት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሀዘኗን ገልጻለች።
ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫዋ እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ በሀልዎት አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን አባል ሆና በሀርመኒ የመዘምራን ኀብረት ውስጥ እንዲሁም በሶሎ ዝማሬ ስታገለግል የቆየች የተወደደች እህት መሆኗን በመጥቀስ ወዳገለገለችው አምላኳ ሔዳለች፤ ወደ ዘላለማዊው እረፍቷ፤ ወደ ሰማዩ ቤቷ ገብታለች ሲሉ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫው በእህታችን በስጋ ከእኛ መለየት ብናዝንም ሀዘናችን ግን ተስፋ እንደሌላቸው አይደለም።
ከሞት ወዲያ ባለው ሕይወት ዳግመኛ እንደምንገናኝ ስለምናውቅ በሱ እንጽናናለን በማለት ለቡታጅራ ከተማ ምዕመናን መጋቢዎቿና አብራችኋት ስታገለግሉ ለነበራችሁ፣ ለሀልዎት አማኑኤል ኅብረት መዘምራን እንዲሁም ለቤተሰቦቿና ለጓደኞቿ መፅናናትን ተመኝታለች።
ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። …….. ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።
ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። (1 ተሰሎንቄ 4:13-18)
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በእህታችን ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለወዳጅ ዘመዶቿ ለጓደኞቿ መፅናናትን እንመኛለን።
😭8🙏4❤2💔1
#አዲስ አመት
#አዲስ ጫማ
ዊን ሶልስ ፎር ጎድ ኢቫንጄሊካል ሚኒስትሪስ እና ብራይት ስታር ኢትዮጵያ የ2017 ዓመተ ምህረት የክረምት ወራቶች በአዲስ ዓመት አዲስ ጫማ የተሰኘውን መርኃ ግብሩን ማጀመሩን ገለጸ፡፡
በ2016 ዓመተ ምህረት የክረምት ወራቶች በአዲስ አመት አዲስ ጫማ የተሰኘ መርኃ ግብር በማስጀመር 1,100 በላይ ለሚደርሱ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን ጨምሮ ጫማ፣ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስና የተለያዩ ግብአቶችን በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ ከሚገኙ ግለሰቦች እንዲሁም ተቋማት በማሰባሰብ ድጋፍ ማድረግ ተችሎ እንደነበር የብራይት ስታር ዳይሬክተር ቄስ ዶክተር በፍርዱ መሰረት ተናግረዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ዳይሬክተሩ የ2016 ዓመተ ምህረት ንቅናቄ ግቡን እንደመታ ገልፀው ድጋፍ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል፡፡ በአዲስ አመት አዲስ ጫማ የተሰኘው መርኃ ግብር ወገኖች አሮጌ ነገራቸውን ትተው አዲስ በሆነው አመት አዳዲስ የትምህርት ግብአቶችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን የመስጠት ልማድ ለማዳበርና ባህል ከማድረግ አንፃር የተነሳ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል፡፡
የመስጠት ባህላችንን ለማሳደግ ታልሞ እየተሰራ የሚገኘው ንቅናቄ ከተቋሙም ባሻገር ሰዎች በአካባቢያቸው ለሚገኙ ወገኖች አዳዲስ ነገሮችን መስጠት እንዲችሉም ተጠቁሟል፡፡
በዘንድሮው2017 ዓመትም የክረምት እንቅስቃሴ እንደ አምናው ሁሉ ከአንድ ሺ አንድ መቶ በላይ ጫማዎችን ጨምሮ የተለያዩ የትምህርት ግብአቶችን ለማሰባሰብ መታቀዱን የብራይት ስታር ዳይሬክተር ጨምረው ገልፀዋል፡፡
መረጃውን ጋዜጠኛ ጸጋህይብዛ ኢሳይያስ አደረሰን
#አዲስ ጫማ
ዊን ሶልስ ፎር ጎድ ኢቫንጄሊካል ሚኒስትሪስ እና ብራይት ስታር ኢትዮጵያ የ2017 ዓመተ ምህረት የክረምት ወራቶች በአዲስ ዓመት አዲስ ጫማ የተሰኘውን መርኃ ግብሩን ማጀመሩን ገለጸ፡፡
በ2016 ዓመተ ምህረት የክረምት ወራቶች በአዲስ አመት አዲስ ጫማ የተሰኘ መርኃ ግብር በማስጀመር 1,100 በላይ ለሚደርሱ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሶችን ጨምሮ ጫማ፣ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስና የተለያዩ ግብአቶችን በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ ከሚገኙ ግለሰቦች እንዲሁም ተቋማት በማሰባሰብ ድጋፍ ማድረግ ተችሎ እንደነበር የብራይት ስታር ዳይሬክተር ቄስ ዶክተር በፍርዱ መሰረት ተናግረዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ዳይሬክተሩ የ2016 ዓመተ ምህረት ንቅናቄ ግቡን እንደመታ ገልፀው ድጋፍ ያደረጉ አካላትን አመስግነዋል፡፡ በአዲስ አመት አዲስ ጫማ የተሰኘው መርኃ ግብር ወገኖች አሮጌ ነገራቸውን ትተው አዲስ በሆነው አመት አዳዲስ የትምህርት ግብአቶችንና የተለያዩ ቁሳቁሶችን የመስጠት ልማድ ለማዳበርና ባህል ከማድረግ አንፃር የተነሳ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል፡፡
የመስጠት ባህላችንን ለማሳደግ ታልሞ እየተሰራ የሚገኘው ንቅናቄ ከተቋሙም ባሻገር ሰዎች በአካባቢያቸው ለሚገኙ ወገኖች አዳዲስ ነገሮችን መስጠት እንዲችሉም ተጠቁሟል፡፡
በዘንድሮው2017 ዓመትም የክረምት እንቅስቃሴ እንደ አምናው ሁሉ ከአንድ ሺ አንድ መቶ በላይ ጫማዎችን ጨምሮ የተለያዩ የትምህርት ግብአቶችን ለማሰባሰብ መታቀዱን የብራይት ስታር ዳይሬክተር ጨምረው ገልፀዋል፡፡
መረጃውን ጋዜጠኛ ጸጋህይብዛ ኢሳይያስ አደረሰን
❤4👍1🙏1
#ቦታ ሞልቷል፣ እንዳያመልጠን ለምትሉ 2 ጥንዶች እድል እንሰጣለን! አሁኑኑ ተመዝገቡ!
ከሀሙስ ከምሽቱ 2:00 በኋላ ምዝገባ አንቀበልም‼️
በጎጆዬ የጋብቻና የልጆች አስተዳደግ የተገኙ ባለትዳሮች ምን ያገኛሉ?
የመጀመሪያው ቅዳሜ
የጋብቻቸውን ትርጉም እና ዓላማ ያድሳሉ፣ የጋራ ራዕይ ይሰንቃሉ፣ ይቀርፃሉ፤
ሁለተኛው ቅዳሜ
እንደባልና ሚስት ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን ማንነት በጥልቀት ያስተውላሉ፣ እርስ በርስ ስለቀደሙ ብዠታዎች ይቅር ይባባላሉ ፣ ለማክበር እና ለመተባበር ቃል ይገባባሉ፤
ሦስተኛው ቅዳሜ
ዋና ዋና ጉዳዮች ይዳሰሳሉ ፣ ፍቅር ፣ ተግባቦት ፣ ወሲብ እናም ከእነዚህም መካከል ወሳኝ ስለሆነው የተግባቦት ጥበብና ክህሎት ይቀስማሉ ፣ ይለማመዳሉ ፤
አራተኛው ቅዳሜ
እንደወላጅ ለልጆቻቸው የጋራ ራዕይን ይሰንቃሉ፣
እነዚህ ቀናት በግል የምክር አገልግሎት ይጠናቀቃሉ።
ከእነዚህ ቀናት በኋላ ፦
👉 ትዳራቸው ይታደሳል ፣
👉የጋራ ቋንቋ ያዳብራሉ፣
👉ትናንትናን በይቅርታ ይዘጋሉ፣
👉ነገን በጥበብ ፣ ማስተዋልና እውቀት ለመምራት ይታጠቃሉ፣ ይወስናሉ ፣ ቃል ይገባባሉ፤
ውድ ባለትዳሮች ፣ እናንተስ?
ዛሬውኑ ተመዝገቡ!
ቀን፣ ሐምሌ 5፣ 12፣ 19፣ 26
ሰዓት፦ ከቀኑ 8:00-11:00
ቦታ፦ በቀድሞው ኢሞፔሪያል ውሃ ልማት በጨጨሆ ገባ ብሎ!
ለመመዝገብ፦ 0911136520/0946693468
ከዚህ በፊት የሰራናቸውን ስራዎች ለማወቅ 👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
yebetesebkitiradash.org
Yebeteseb Kitir Adash
ከሀሙስ ከምሽቱ 2:00 በኋላ ምዝገባ አንቀበልም‼️
በጎጆዬ የጋብቻና የልጆች አስተዳደግ የተገኙ ባለትዳሮች ምን ያገኛሉ?
የመጀመሪያው ቅዳሜ
የጋብቻቸውን ትርጉም እና ዓላማ ያድሳሉ፣ የጋራ ራዕይ ይሰንቃሉ፣ ይቀርፃሉ፤
ሁለተኛው ቅዳሜ
እንደባልና ሚስት ከእግዚአብሔር የተቀበሉትን ማንነት በጥልቀት ያስተውላሉ፣ እርስ በርስ ስለቀደሙ ብዠታዎች ይቅር ይባባላሉ ፣ ለማክበር እና ለመተባበር ቃል ይገባባሉ፤
ሦስተኛው ቅዳሜ
ዋና ዋና ጉዳዮች ይዳሰሳሉ ፣ ፍቅር ፣ ተግባቦት ፣ ወሲብ እናም ከእነዚህም መካከል ወሳኝ ስለሆነው የተግባቦት ጥበብና ክህሎት ይቀስማሉ ፣ ይለማመዳሉ ፤
አራተኛው ቅዳሜ
እንደወላጅ ለልጆቻቸው የጋራ ራዕይን ይሰንቃሉ፣
እነዚህ ቀናት በግል የምክር አገልግሎት ይጠናቀቃሉ።
ከእነዚህ ቀናት በኋላ ፦
👉 ትዳራቸው ይታደሳል ፣
👉የጋራ ቋንቋ ያዳብራሉ፣
👉ትናንትናን በይቅርታ ይዘጋሉ፣
👉ነገን በጥበብ ፣ ማስተዋልና እውቀት ለመምራት ይታጠቃሉ፣ ይወስናሉ ፣ ቃል ይገባባሉ፤
ውድ ባለትዳሮች ፣ እናንተስ?
ዛሬውኑ ተመዝገቡ!
ቀን፣ ሐምሌ 5፣ 12፣ 19፣ 26
ሰዓት፦ ከቀኑ 8:00-11:00
ቦታ፦ በቀድሞው ኢሞፔሪያል ውሃ ልማት በጨጨሆ ገባ ብሎ!
ለመመዝገብ፦ 0911136520/0946693468
ከዚህ በፊት የሰራናቸውን ስራዎች ለማወቅ 👇
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
yebetesebkitiradash.org
Yebeteseb Kitir Adash
❤4👍3🔥1
በታንዛኒያ ከመላው #አለም የተወጣጡ ክርስቲያኖች ለ5 ቀናት ተሰብስበዋል።
ለ5ቀናት በሚቆየው ስብሰባ ክርስቲያኖች እና ቤተ ክርስቲያን በዚህ ተለዋዋጭ አለም የሚኖራቸው ሚና ላይ ጸሎት ያደርጋል፣ ውይይት ይካሄዳል፣ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ፣ ተብሎ ይጠበቃል።
መረሃ ግብሩ የሚካሄደው “Dancing in Faith – Drumming up Hope” የጉባኤው መሪ ቃል ነው።
ጉባኤውን ያዘጋጀችው የታንዛኒያ ሉተራን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ስትሆን የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች ጉባኤው በታንዛኒያ ምድር በመካሄዱ ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ለምድራችንም ለቤተ ክርስቲያንም ትልቅ በረከት ይሆናል ብለዋል።
የአለም ዲያቆኒያ ፌደሬሽን ጉባኤ በተባለለት በዚህ ጉባኤ የመጽሃፍ ቅዱስ ጥናት፣ የአምልኮ፣ ባህላዊ እሴቶችን ማሳወቅ፣ የዲያቆናት አገልግሎትን በተመለከተ ውይይቶች ይኖራል ተብሏል ሲል ያስነበበው የአለም ሉተራን ፌደሬሽን ነው።
ሐምሌ 4 /2017 ዓ.ም
ለ5ቀናት በሚቆየው ስብሰባ ክርስቲያኖች እና ቤተ ክርስቲያን በዚህ ተለዋዋጭ አለም የሚኖራቸው ሚና ላይ ጸሎት ያደርጋል፣ ውይይት ይካሄዳል፣ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ፣ ተብሎ ይጠበቃል።
መረሃ ግብሩ የሚካሄደው “Dancing in Faith – Drumming up Hope” የጉባኤው መሪ ቃል ነው።
ጉባኤውን ያዘጋጀችው የታንዛኒያ ሉተራን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ስትሆን የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች ጉባኤው በታንዛኒያ ምድር በመካሄዱ ትልቅ ደስታ ተሰምቶናል፣ ለምድራችንም ለቤተ ክርስቲያንም ትልቅ በረከት ይሆናል ብለዋል።
የአለም ዲያቆኒያ ፌደሬሽን ጉባኤ በተባለለት በዚህ ጉባኤ የመጽሃፍ ቅዱስ ጥናት፣ የአምልኮ፣ ባህላዊ እሴቶችን ማሳወቅ፣ የዲያቆናት አገልግሎትን በተመለከተ ውይይቶች ይኖራል ተብሏል ሲል ያስነበበው የአለም ሉተራን ፌደሬሽን ነው።
ሐምሌ 4 /2017 ዓ.ም
❤5👍2🔥1👌1
"አባካኙ #ልጅ" ተመረቀ።
በተወዳጇ ዘማሪት ቤተልሔም ተዘራና በባለቤቷ መንግስተ አብ ተገኝ የሚመራው የሊቪንግ ዊትነስ ሚኒስትሪ ራዕይውን በማስተዋወቅ "አባካኙ ልጅ" የተሰኘውን አጭር ፊልም ለተመልካች አቀረበ።
በትላንትናው እለት በሽራተን ሆቴል በተደረገው መረሃ ግብር የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ አገልጋዮች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ወንድም መንግስተአብ ተገኝ ለጉባኤው የሊቪንግ ዊትነስ ሚኒስትሪ ራዕይን ያስተዋወቁ ሲሆን የዘማሪት ቤተልሔም ተዘራ የዝማሬ አገልግሎት የሚተርክ ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል።
"አባካኙ ልጅ" የተሰኘው ይህ ሙዚቃዊ አጭር ፊልም ሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ላይ የተመሰረተው ሲሆን ፓስተር በቀለ ወልደኪዳንን እና ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ ጨምሮ የተለያዩ አንጋፋ ዘማሪዎች እና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ለጉባኤው በማቅረብ የእግዚአብሔርን የፍቅር ጥግ ምን ያህል እንደሆነ በመግለጽ ግንዛቤ ፈጥሯል።
#የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ በጸሎት ዘማሪ ህሊና ዳዊት ዝማሬ በማቅረብ ቄስ ትግስቱ ሞገስ የእግዚአብሔርን ቃል መልዕክት በማቅረብ አገልግለዋል።
በመጨረሻም በፊልሙ ላይ ለተሳተፋ ወገኖች የሰርተፍኬት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ምንጭ #GMM TV ETHIOPIA
ሐምሌ 4 /2017 ዓ.ም
በተወዳጇ ዘማሪት ቤተልሔም ተዘራና በባለቤቷ መንግስተ አብ ተገኝ የሚመራው የሊቪንግ ዊትነስ ሚኒስትሪ ራዕይውን በማስተዋወቅ "አባካኙ ልጅ" የተሰኘውን አጭር ፊልም ለተመልካች አቀረበ።
በትላንትናው እለት በሽራተን ሆቴል በተደረገው መረሃ ግብር የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ አገልጋዮች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ወንድም መንግስተአብ ተገኝ ለጉባኤው የሊቪንግ ዊትነስ ሚኒስትሪ ራዕይን ያስተዋወቁ ሲሆን የዘማሪት ቤተልሔም ተዘራ የዝማሬ አገልግሎት የሚተርክ ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል።
"አባካኙ ልጅ" የተሰኘው ይህ ሙዚቃዊ አጭር ፊልም ሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ላይ የተመሰረተው ሲሆን ፓስተር በቀለ ወልደኪዳንን እና ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ ጨምሮ የተለያዩ አንጋፋ ዘማሪዎች እና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ለጉባኤው በማቅረብ የእግዚአብሔርን የፍቅር ጥግ ምን ያህል እንደሆነ በመግለጽ ግንዛቤ ፈጥሯል።
#የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሀፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ በጸሎት ዘማሪ ህሊና ዳዊት ዝማሬ በማቅረብ ቄስ ትግስቱ ሞገስ የእግዚአብሔርን ቃል መልዕክት በማቅረብ አገልግለዋል።
በመጨረሻም በፊልሙ ላይ ለተሳተፋ ወገኖች የሰርተፍኬት እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
ምንጭ #GMM TV ETHIOPIA
ሐምሌ 4 /2017 ዓ.ም
❤9👍4🔥1👌1
#ነገ ይጀመራል። #ቅዳሜ ሐምሌ 05/2017 ዓ.ም በ5ኪሎ መካነየሱስ 8:00 ሰዓት ይጀመራል።
በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች) የተመዘገባችሁ በሙሉ
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ነገ እንደሚጀመር ልናሳዉቃችሁ እንወዳለን።
ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም
📍 ቦታ፡ #አዲስ አበባ 5ኪሎ መካነየሱስ ቤተክርስቲያን
(5ኪሎ መ/ኢየሱስ)
አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን
ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822
ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።
https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች) የተመዘገባችሁ በሙሉ
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ነገ እንደሚጀመር ልናሳዉቃችሁ እንወዳለን።
ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም
📍 ቦታ፡ #አዲስ አበባ 5ኪሎ መካነየሱስ ቤተክርስቲያን
(5ኪሎ መ/ኢየሱስ)
አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን
ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822
ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።
https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
👍5❤1
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት #ስልጠና መስጠት ተጀመረ።
ክረምትን አስመልክቶ የተዘጋጀው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና #በአዲስ አበባ (5ኪሎ) መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተጀምሯል።
ከሃምሌ 5 እስከ ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 8 ሳምንታት የሚቆየው ስልጠና በዋናነት የጋዜጠኝነት መሰረታዊያን ፤ የዜና አጻጻፍ እና ሀሰተኛ የዜና ስርጭቶችን መቀነስ ፤ ስነጽሁፍ እና ዲጂታል ሚዲያን ጨምሮ ዘጋቢ ፊልምን በተግባር ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
በሚኖሩት ሳምንታት እራሳቸውን በስነምግባር ብቁ አድርገው ቤተክርስቲያንን በዲጅታል ሚዲያ በማገዝ እንዲሁም የሚሰሩትን ስራ በተግባር እንዲያሳድጉ ሊያደርግ የሚችል የስልጠና ጊዜ እንደሚኖር በነበረው የመክፈቻ መረሃ ግብር የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም ደመላሽ ዶላ ተናግረዋል።
ስልጠናው The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከየደስ ደስ መልቲ ሚዲያ እና ቲኪቆስ ሚዲያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ስልጠና ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ከአዲስ አበባ ባሻገር በሃዋሳ እንደሚጀምር ታውቋል።
ክረምትን አስመልክቶ የተዘጋጀው መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና #በአዲስ አበባ (5ኪሎ) መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ተጀምሯል።
ከሃምሌ 5 እስከ ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም ለተከታታይ 8 ሳምንታት የሚቆየው ስልጠና በዋናነት የጋዜጠኝነት መሰረታዊያን ፤ የዜና አጻጻፍ እና ሀሰተኛ የዜና ስርጭቶችን መቀነስ ፤ ስነጽሁፍ እና ዲጂታል ሚዲያን ጨምሮ ዘጋቢ ፊልምን በተግባር ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
በሚኖሩት ሳምንታት እራሳቸውን በስነምግባር ብቁ አድርገው ቤተክርስቲያንን በዲጅታል ሚዲያ በማገዝ እንዲሁም የሚሰሩትን ስራ በተግባር እንዲያሳድጉ ሊያደርግ የሚችል የስልጠና ጊዜ እንደሚኖር በነበረው የመክፈቻ መረሃ ግብር የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም ደመላሽ ዶላ ተናግረዋል።
ስልጠናው The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከየደስ ደስ መልቲ ሚዲያ እና ቲኪቆስ ሚዲያ ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ስልጠና ሲሆን በሚቀጥለው ሳምንት ከአዲስ አበባ ባሻገር በሃዋሳ እንደሚጀምር ታውቋል።
👍7❤1🔥1🙏1
#አዲሱ ዋዪማ እና #አስፋው መለሰ 6ኛ የመዝሙር አልበማቸውን አስመረቁ።
ዛሬ ቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ እና ልደታ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤ/ክ ነው ያስመረቁት።
የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ አልበም “Bara Baraakoo” የሚሰኝ ሲሆን፣ የዘማሪ አስፋው መለሰ አልበም “አንተን አልጣ እንጂ” ነው። የአዲሱ ዋዪማ አልበም 13 መዝሙሮች ሲኖረው፣ የዘማሪ አስፋው አልበም 11 መዝሙሮች አለው።
ሁለቱም ዘማሪዎች ወዳጆች፣ ተጋባዥ ዘማሪዎች እና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት በስኬት ተመርቋል። በሚያኮራ ሁኔታ ሁለቱም ዘማሪዎች አልበማቸውን የመረቁት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ቆመው ነው።
የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ አልበሞች
• “Eenyudharee gootni”
• “Utuu badnee kanaan dura”
• “Attamiin galaanni na ittisa”
• “Amanannaakoo”
• “Duulli kun duula lubbuuti”
• “Ijibbaata”
• 6ኛ “Bara baraakoo”
የመጋቢ እና ዘማሪ አስፋው መለሰ አልበሞች
• “ብዙ ዘመን ራራህልኝ”
• “በጅምር አይቀርም የኔ ነገር”
• “ትላንት ዛሬ አይደለም”
• “የሩቅ ህልሞቼ”
• “ይሁን”
• 6ኛ "አንተን አልጣ እንጂ” ናቸው
ሁለቱም በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከ20 አመታት በላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በታማኝነት አገልግለዋል።
የክርስቲያን ዜና ትውልድ ለተሻገረ፣ ብዙዎችን ላጽናና፣ ለብዙዎች በረከት የሆነ አገልግሎታችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይላል።
መዝሙሮቻቸውን በዩቱብ ገጾቻቸው ማግኘት ትችላላችሁ።
ዘማሪና መጋቢ አስፋው መለሰ
https://www.youtube.com/@asfawmelese
ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ
https://www.youtube.com/@addisuwayima
በኦቦሌሳ አዶላ
ዛሬ ቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ እና ልደታ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤ/ክ ነው ያስመረቁት።
የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ አልበም “Bara Baraakoo” የሚሰኝ ሲሆን፣ የዘማሪ አስፋው መለሰ አልበም “አንተን አልጣ እንጂ” ነው። የአዲሱ ዋዪማ አልበም 13 መዝሙሮች ሲኖረው፣ የዘማሪ አስፋው አልበም 11 መዝሙሮች አለው።
ሁለቱም ዘማሪዎች ወዳጆች፣ ተጋባዥ ዘማሪዎች እና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት በስኬት ተመርቋል። በሚያኮራ ሁኔታ ሁለቱም ዘማሪዎች አልበማቸውን የመረቁት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ቆመው ነው።
የዘማሪ አዲሱ ዋዪማ አልበሞች
• “Eenyudharee gootni”
• “Utuu badnee kanaan dura”
• “Attamiin galaanni na ittisa”
• “Amanannaakoo”
• “Duulli kun duula lubbuuti”
• “Ijibbaata”
• 6ኛ “Bara baraakoo”
የመጋቢ እና ዘማሪ አስፋው መለሰ አልበሞች
• “ብዙ ዘመን ራራህልኝ”
• “በጅምር አይቀርም የኔ ነገር”
• “ትላንት ዛሬ አይደለም”
• “የሩቅ ህልሞቼ”
• “ይሁን”
• 6ኛ "አንተን አልጣ እንጂ” ናቸው
ሁለቱም በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከ20 አመታት በላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በታማኝነት አገልግለዋል።
የክርስቲያን ዜና ትውልድ ለተሻገረ፣ ብዙዎችን ላጽናና፣ ለብዙዎች በረከት የሆነ አገልግሎታችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ ይላል።
መዝሙሮቻቸውን በዩቱብ ገጾቻቸው ማግኘት ትችላላችሁ።
ዘማሪና መጋቢ አስፋው መለሰ
https://www.youtube.com/@asfawmelese
ዘማሪ አዲሱ ዋዪማ
https://www.youtube.com/@addisuwayima
በኦቦሌሳ አዶላ
❤9👍2🙏2🔥1
ፓስተር ጆን ማከርተር አረፉ
በከሜሪካን ሃገር ግሬስ ኮሚኒቲ ቤ/ክ ለ56 አመታት ሲያገለገሉ የነበሩት ፓስተር ጆን ዛሬ ማለዳ ማረፋቸውን 'Grace to You" የተሰኘው ሚኒስትሪያቸው አስታውቋል።
በአገልግሎት ዘመናቸው ለህትመት የበቁ እና አርትኦት የሰሩባቸው ከ150 በላይ መጽሃፍት ለአንባቢያን አድርሰዋል። በቤተ ቤተርስቲያን አገልግሎት፡ በሴሚናሮች በማስተማር እና ከ1969 ዓ.ም ጀምሮ "Grace to you" በተሰኘ ሚድያ ወንጌል ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
ጆን ማከርተር በገጠማቸው የሳምባ ምች (Pneumonia) በሽታ ታመው ሆስፒታል በገቡበት በ86 አመታቸው ማረፋቸውን ሚኒስትሪያቸው አሳውቋል።
በኦቦሌሳ አዶላ
በከሜሪካን ሃገር ግሬስ ኮሚኒቲ ቤ/ክ ለ56 አመታት ሲያገለገሉ የነበሩት ፓስተር ጆን ዛሬ ማለዳ ማረፋቸውን 'Grace to You" የተሰኘው ሚኒስትሪያቸው አስታውቋል።
በአገልግሎት ዘመናቸው ለህትመት የበቁ እና አርትኦት የሰሩባቸው ከ150 በላይ መጽሃፍት ለአንባቢያን አድርሰዋል። በቤተ ቤተርስቲያን አገልግሎት፡ በሴሚናሮች በማስተማር እና ከ1969 ዓ.ም ጀምሮ "Grace to you" በተሰኘ ሚድያ ወንጌል ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
ጆን ማከርተር በገጠማቸው የሳምባ ምች (Pneumonia) በሽታ ታመው ሆስፒታል በገቡበት በ86 አመታቸው ማረፋቸውን ሚኒስትሪያቸው አሳውቋል።
በኦቦሌሳ አዶላ
❤22🔥4😭1
50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዬቤልዩ
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ የደቡብ ምስራቅ ክልል የባሌ ጎባ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።
በክብረ በዓሉ መረሃ ግብር ላይ በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩት የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት መጋቢ ጻዲቁ አብዱን ጨምሮ ከመጋቢ ጻዲቁ አብዱ ጋር ከጅማሬው አንስቶ በጋራ ወንጌልን ያገለገሉ እና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡
የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ለአባላቱ በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻውን ጨምሮ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ላይም የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡
በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ በታላቅ ደስታና መጽናናት እንደሚሆን #መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ የደቡብ ምስራቅ ክልል የባሌ ጎባ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።
በክብረ በዓሉ መረሃ ግብር ላይ በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩት የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት መጋቢ ጻዲቁ አብዱን ጨምሮ ከመጋቢ ጻዲቁ አብዱ ጋር ከጅማሬው አንስቶ በጋራ ወንጌልን ያገለገሉ እና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡
የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ለአባላቱ በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻውን ጨምሮ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ላይም የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡
በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ በታላቅ ደስታና መጽናናት እንደሚሆን #መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
❤9👍2🔥1👏1
#በሱዳን አንድ አብያተ ክርስቲያን በወታደር እገዛ መፍረሱ ተነግረ።
የሱዳን ጴንጤቆስጤ ቤተ ክርስቲያን መካከል አንዷ በካርቱም ምስራቅ ናይል በሚባልበት አካባቢ ያለችው ቤ/ክ ናት የፈረሰችው። ቤተ ክርስቲያን ህንጻ ፈረሳው ሲካሄድ፣ የፖሊስ እና ወታደራዊ አካላት በስፍራው የነበሩ ሲሆን ህንጻውን ያፈረሱት ደግሞ ከ20 የማያንሱ ግለሰቦች ናቸው።
የቤተ ክርስቲያን ህንጻ የተገነባው በ1990 ሲሆን፣ የአምልኮ አገልግሎት እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል። ፖሊሶች በስፍራው ግለሰቦች ሲያፈርሱ ማንም ሰው እንዳይቀርጽ ሲከለክሉ ነበር።
የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች ቤተ ክርስቲያኗ መልሳ እንድትገነባ እና ክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ስደት እንዲቆም ጸሎት ይደረግልን ሲሉ ጠይቀዋል። ክርስቲያኖችን ከሱዳን የማውጣት እንቅስቃሴ በሰፊው እየተካሄደ ይገኛል ተብሏል።
የተለያየ አይነት አመጽ፣ አስገድዶ ጋብቻ፣ ጾታዊ ጥቃት፣ ልጆችን መነጠቅ፣ ርስት መነጠቅ እና ሃሰተኛ ክሶች በሱዳን ያሉ ክርስቲያኖች በየ እለቱ የሚያልፉባቸው መከራዎች ናቸው። ከዚህ ባለፈ፣ በጦርነት ወቅት በሚያጋጥም፣ ርሃብ ወቅት ክርስቲያኖች ተለይተው ምግብ አይደርሳቸውም።
ከሙሉ ህዝቧ 2 ሚሊዮን የሚሆነው ወይም 4.1 % የሚሆነው ክርስቲያን ቢሆንም የክርስቲያኖች ግድያ እና ጠለፋ በተደጋጋሚ ይስተዋላል። ሱዳን በኦፕን ዶርስ አመታዊ መረጃ መሰረት 5ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
አሁንም የሱዳን ክርስቲያኖች ጥያቄያቸው ግን “ጸሎት” ብቻ ነው ሲል ያስነበበው ዎርዚ ኒውስ ነው።
በኦቦሌሳ አዶላ
የሱዳን ጴንጤቆስጤ ቤተ ክርስቲያን መካከል አንዷ በካርቱም ምስራቅ ናይል በሚባልበት አካባቢ ያለችው ቤ/ክ ናት የፈረሰችው። ቤተ ክርስቲያን ህንጻ ፈረሳው ሲካሄድ፣ የፖሊስ እና ወታደራዊ አካላት በስፍራው የነበሩ ሲሆን ህንጻውን ያፈረሱት ደግሞ ከ20 የማያንሱ ግለሰቦች ናቸው።
የቤተ ክርስቲያን ህንጻ የተገነባው በ1990 ሲሆን፣ የአምልኮ አገልግሎት እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል። ፖሊሶች በስፍራው ግለሰቦች ሲያፈርሱ ማንም ሰው እንዳይቀርጽ ሲከለክሉ ነበር።
የቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች ቤተ ክርስቲያኗ መልሳ እንድትገነባ እና ክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ስደት እንዲቆም ጸሎት ይደረግልን ሲሉ ጠይቀዋል። ክርስቲያኖችን ከሱዳን የማውጣት እንቅስቃሴ በሰፊው እየተካሄደ ይገኛል ተብሏል።
የተለያየ አይነት አመጽ፣ አስገድዶ ጋብቻ፣ ጾታዊ ጥቃት፣ ልጆችን መነጠቅ፣ ርስት መነጠቅ እና ሃሰተኛ ክሶች በሱዳን ያሉ ክርስቲያኖች በየ እለቱ የሚያልፉባቸው መከራዎች ናቸው። ከዚህ ባለፈ፣ በጦርነት ወቅት በሚያጋጥም፣ ርሃብ ወቅት ክርስቲያኖች ተለይተው ምግብ አይደርሳቸውም።
ከሙሉ ህዝቧ 2 ሚሊዮን የሚሆነው ወይም 4.1 % የሚሆነው ክርስቲያን ቢሆንም የክርስቲያኖች ግድያ እና ጠለፋ በተደጋጋሚ ይስተዋላል። ሱዳን በኦፕን ዶርስ አመታዊ መረጃ መሰረት 5ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
አሁንም የሱዳን ክርስቲያኖች ጥያቄያቸው ግን “ጸሎት” ብቻ ነው ሲል ያስነበበው ዎርዚ ኒውስ ነው።
በኦቦሌሳ አዶላ
😭17❤6🙏6🕊2💔1
በአሮሬሳ መጆ #ሙሉ #ወንጌል አማኞች #ቤተክርስቲያን በቡቤ-ቦሬ ቀበሌ ሐዳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ከስድስት ወራት በፊት የተተከለችው ሐዳ አዳጊ ቤተክርስቲያን የአምልኮ አዳራሿን መስራት ጀምራለች።
ከሰሞኑ ቤተክርስቲያኒቷ የአምልኮ አዳራሿን ለመሥራት መሠረት የጣለች ሲሆን የአሮሬሳ መጆ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ አባላት በነፍስ ወከፍ በመውጣት ለግንባታው ሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለግሰዋል።
በሂደቱም የአሮሬሳ መጆ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን፣ የአሮሬሳ መጆ ስታዲየም ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን እና የሶዶ አዳጊ ቤተክርስቲያን አባላት ተሳትፈዋል።
በቀጣይነት ሁላችንም ወደ ሶዶ አዳጊ ቤተክርስቲያን እንደምንዘምት ፓ/ር በቀለ ሐዴሶ ገልጸዋል።
ክብር ሁሉ ለሥራው ባለቤት ለእግዚአብሔር ይሁን !!!
ከሰሞኑ ቤተክርስቲያኒቷ የአምልኮ አዳራሿን ለመሥራት መሠረት የጣለች ሲሆን የአሮሬሳ መጆ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ አባላት በነፍስ ወከፍ በመውጣት ለግንባታው ሥራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ለግሰዋል።
በሂደቱም የአሮሬሳ መጆ ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን፣ የአሮሬሳ መጆ ስታዲየም ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን እና የሶዶ አዳጊ ቤተክርስቲያን አባላት ተሳትፈዋል።
በቀጣይነት ሁላችንም ወደ ሶዶ አዳጊ ቤተክርስቲያን እንደምንዘምት ፓ/ር በቀለ ሐዴሶ ገልጸዋል።
ክብር ሁሉ ለሥራው ባለቤት ለእግዚአብሔር ይሁን !!!
❤9🔥3👍2🥰1🙏1👌1