The Christian News
5.08K subscribers
3.66K photos
51 videos
911 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
የሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን አመራሮች #የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስን ዋና መሥሪያ ቤት ጎበኙ። 

የLWF ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ የሚጀመር ሲሆን የLWF ምክር ቤት ስብሰባ ከመጀመሩ አስቀድም ፅ/ቤቱን ገብኝተዋል።

የምክር ቤቱ ጭብጥ "ምስክሮቼ ሁኑ" የሚል ሲሆን ከሁሉም የሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን ክልሎች የተውጣጡ 48 የምክር ቤት አባላትን እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።
8👍1🔥1
"በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል" የፓስተር ጻድቁ አብዱ መፅሐፍ እየተመረቀ ነዉ።

የትንቢተ አብድዩ መጽሃፍ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀዉ መፅሐፍ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችን ጨምሮ ወዳጆቻቸዉ በተገኙበት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም እየተመረቀ ነዉ።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራዉ የምንገኝ ሲሆን ዝርዝር መረጃ ይዘን እንመለሳለን።
13👍1👌1
የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ለአገሪቱ የምግብ ዋስትና ሠራተኞቹ ጾም እና ጸሎት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ

ናይጄሪያ የምግብ ዋስትናን እንድታረጋግጥ ፈጣሪን ለመማጸን ፆም እና ጸሎት እንዲያደርጉ የአገሪቱ የእርሻ ሚኒስቴር ሠራተኞቹን መጠየቁን ተከትሎ ውዝግብ ተፈጥሯል።

በናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር የሰው ኃይል አስተዳደር ክፍል ኃላፊ አማካኝነት ለመሥርያ ቤቱ ሠራተኞች በተሰራጫው ማስታወሻ የሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ ባልደረቦች ለተከታታይ ሦስት ሰኞዎች በሚካሄደው የተማጽኖ ፆም እና ጸሎት ላይ እንዲሳተፉ ይጠይቃል።

ይህ ዜና መውጣቱን ተከትሎ አንዳንድ ናይጄሪያውያን መንግሥታቸው በአገሪቱ እያነረ ያለውን የምግብ ዋጋ እንዲቀንስ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ በመክተት ተችተዋል።

የፆም ጸሎት ጥሪው መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ ማስተባበያ ሰጥቷል።

ጥሪው በአገሪቱ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ ጸሎት የመንግሥት ይፋዊ ፖሊሲ አለመሆኑን አመልክቶ፣ ነገር ግን ጸሎቱ የሠራተኞችን ደኅንነት ለማዳበር ነው ብሏል።

ሙሉዉን BBC AMHARIC ላይ ያንብቡ
10👍3🔥1🥰1
የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ከታሪካዊ እርቅ በኋላ አዳዲስ አመራሮች መረጡ።

የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በውስጥ አለመግባባቶች ለአራት ዓመታት የዘለቀውን ክፍፍል በእርቅ ተቋጭቶ አዳዲስ አመራሮችን መርጠዋል።

በታህሳስ 9, 2013 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ክልል ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ምስረታ ምክንያት በጋሞ ዞን እና በአርባምንጭ ከተማ ወ/አ/ክ የቀድሞ አመራሮች እና በዞኑ እና በከተማዉ ህብረት መሪዎች የነበረዉ አላማግባባት ለሚመከተዉ ባለድርሻ አካል ቅሬታ ቀርቦ የነበረ ቢሆንም ሳይፈታ መቆየቱ በወንጌል እንቅስቀሴ ላይ እና በወንድሞች ህብረት ላይ ትልቅ ጫና ፈጥሮ ቆይቶል።

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃድቁ አብዶ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጽ/ቤት ሃላፊ መጋቢ ጌትነት ለማ በጥር 15/17 አራት የእርቅ አመቻት ኮሚቴ የሰየሙ ሲሆን አመቻች ኮሚቴው በዞኑ እና በከተማዉ የነበረዉን የቀድሞን ፍቅር እና ህብረት ለመመለስ ከፍተኛ ጥራት በማድራግ ሰኔ1 እርቅ ስምምናት መደረጉ ተገልጿል።

በቀድሞ አመራሮች እጅ የነበረዉ የህብረቱ የንብረት እርክክብ ያደረገ ሲሆን የክልሉ ም/ፕሬዝደንት መጋቢ ወንድማገኝ አስፋ በመገኘት ንብረቱን የመረካካብ ሥርዓት ማስፈጸማቸው ይታወሳል።

ሰኔ 07/17 በክልሉ ፀሐፊ ዶ/ር ማርቆስ አቢሶ መሪነት የተካሄደው ምርጫ በመስራች አብያተ ክርስቲያናት መካከል እርቅን የፈጠረ አዲስ ጅማሬ እንደሆነም ተገልጿል።

በዚህም መሰረት ወ/ም ቹቹ ቹርኮ የጋሞ ዞን ወ/አ/ክ/ ህብረት ሰብሳቢ እና ወ/ም ደፋርሼ ሻንካ የአርባ ምንጭ ከተማ ወ/አ/ክ/ህብረት ሰብሳቢ ተደርገው ተመርጠዋል።
4👍2🔥1
#አስደሳች ዜና

በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)

መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።

ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው

1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)

ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

ቦታ፡ አዲስ አበባ እና ሀዋሳ

(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ህይወት ብርሃን)

አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲቂቆስ ሚዲያ ፤ የክርስቲያን ዜና በጋራ

ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822

ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ይጠቀሙ።

https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
👍106🔥1
ISIS በሶሪያ 25 ክርስቲያኖችን ገደለ

ጥቃቱ የተፈጸመው በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት ደርሶባቸዋል።

እሁድ ጠዋት ክርስቲያኖች ቅዱስ ኤሊያስ በተባለው ቤተ ክርስቲያን ለጸሎት ተሰብስበው ነበረ። ጥቃት አድራሹ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ ተኩስ ከከፈተ በኋላ የአጥፍቶ ማጥፋት ፍንዳታውን እንዳደረገ ተገልጿል።

በግሪክ ኦሮቶዶክስ ቤ/ክ የአንጾኪያ ፓትሪያርክ አደጋውን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ጸሎት እናድርግ፣ ለተጎዱ ሰዎች ደግሞ ድጋፍ እናድርግ ሲሉ ተደምጠዋል። የሃገሪቱ ባለስልጣናት በበኩላቸው ሃገሪቱ በሽግግር ላይ ባለችበት ወቅት ወደ ቀውስ ለማስገባት የተደረግ ሙከራ ነው ሲል ገልጾታል።

ISIS ለጥቃቱ ሃላፊነት የወሰደ ሲሆን፣ በአረብ ሃገራት እና በሌሎች አካባቢዎችም ክርስቲያኖችን እና አአስተኛ የሚባሉ ቡድኖችን ለማጥፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

በሽር አል አሳድ ከስልጣ ከተወገዱ በኋላ ይሄ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ከባድ ጥቃት ነው። ISIS በሰሜናዊ ሶሪያ አካባቢዎች ድጋሚ ለመንቀሳቀስ ሙከራ እያደረገ ይገኛል።

ሶሪያ ማለት የመጀምሪያ ክርስቲያኖች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም ያገኙባት #አንጾኪያ መገኛ የሆነች ምድር ናት። ዋና ከተማዋ ደማስቆ ደግሞ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊያሳድድ ሲሄድ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የተገናኘባት ምድር ናት።

The Christian Post & Allarab News እንዳስነበቡት
💔111🕊1😭1
የሶሪያ የክርስቲያን መሪዎች በቤተክርስቲያን የቦምብ ጥቃት ላይ መንግስትን ወቀሱ።

የሶሪያ ከፍተኛ የክርስቲያን መሪ በእሁድ ቀን በርካታ ሰዎችን ለገደለው የቤተክርስቲያን ፍንዳታ የሶሪያውን ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራአን መንግስትን ወቅሰዋል።

ባሳለፍነው እሁድ በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል።

መሪዎቹ በመንግስት ጥበቃ በሚሰጠው ዋስትና ላይ መመካት አለመቻላቸውን እና ያላቸውን ጥርጣቄ አጠናክሯል ተብሏል።

በአንጾኪያ የግሪክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ጆን (ኤክስ) ያዚጊ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ “በፍቅር እና በአክብሮት ክቡር ፕሬዝደንት ሀዘናችሁን ለመግለፅ በስልክ መነጋገራቸውን ገልጸው ለስልክ ጥሪው አመስጋኞች ነን ግን የተፈጠረው ወንጀል ከዚህ ትንሽ ይበልጣል ሲሉ ተናግረዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ "ጨካኝ እና ፈሪነት የተሞላበት ጥቃት" ሲል የገለፀውን ድርጊት አውግዞ የሶሪያ መንግስት ሁከት ፈጣሪዎችን ሁሉ በህግ እንዲጠየቅ እና የሃይማኖት እና የጎሳ አባላትን ጨምሮ የመላው ሶሪያውያን ደህንነት እንዲያረጋግጥ ጠይቋል።

ከጦርነት በፊት ከነበሩት 22 ሚሊዮን የሶሪያ ህዝብ 10 በመቶ ያህሉ ናቸው ነገር ግን በ 14 ግጭት ዓመታት ቁጥራቸው በስደት ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ሲሆን አሁን በሶሪያ እንደሚኖሩ የሚገመተው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ናቸው።

በሟቾች የቀብር ስነ-ስረዓት ላይ በሶሪያ አዲስ መንግስት ውስጥ ብቸኛዋ ክርስቲያን እና ብቸኛ ሴት የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ሂንድ ካባዋት መገኘታቸውን የዎርዚ ኒውስ በዘገባው አክሎ ገልጿል።

ሶሪያ ለክርስትና አስቸጋሪ ከሆኑ 50 ሀገራት መካከል 18ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
7😭4💔3🕊1
"አንተን አልጣ እንጂ" ዘማሪ አስፋው መለሰ

ይሄ 6ኛ አልበም፡ ማቴዎስ 6፥31 ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሲሆን

በ20 ዓመታት የአገልግሎት ጊዜዬ በማግኘትም በማጣትም ጌታን ብቻ ዋናዬ ነበረ። ልደታ አሴምብልስ ኦፍ ጋድ ቤ/ክ ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም ይመረቃል።

መጋቢ አስፋው በ20 ዓመታት አገልግሎቱ በከተማም በገጠርም በትጋት እና በታማኝነት አገልግሏል ከዚህ በፊት የነበሩት መዝሙሮች ለቤተ ክርስቲያን መታነጽ፡ ለትውልድ መባረክ ምክንያት ሆነዋል። ይሄኛውም አልበም ብዙዎችን እንደሚባርክ እርግጠኛ ነን።

ጉባኤ እግዚአብሄር ቤ/ክ ከ20 ዓመታት በላይ አገልግሏል። ቤተ ክርስቲያኗ የምታምንበትን ሰው ጌታን ካለው ምንም ያጣም ብላ ስለምታምን፡ ይሄንን መዝሙር ለክርስቲያኖች በረከት ይሆናል።

በዚህ መዝሙር ግለሰቦች እና ቤ/ክ ብቻ ሳይሆን ሃገር ይጠቀማል። ሐምሌ 6 በሚኖረው የአምልኮ ድግስ ተገናኝተን እናምልክ።

"አንተን አልጣ እንጂ" የሙዚቃ ዝግጅት ስራ ላይ ከ2 ዓመት በላይ ፈጅቷል። ይሁን እንጂ ዘማሪ ስለሆንኩኝ ሁሌም መዝሙር እዘምራለሁ። መዝሙሩን

ሐዋ 4፥4 መሰረት አድርጎ ከባለቤቴ እና ልጆቼ ጋር አንድ ክሊፕ አለው። ሰንዱቁ 11 መዝሙሮችን ይዟል። ሚሊኒየም አዳራሽ ድግስ አትጠብቁ!

አሁን የሚወጡ መዝሙሮች ገቢ ማግኛ ሳይሆኑ ለእግዚአብሄር የሚቀርቡ መስዋዕቶች ስለሆኑ ገቢ ማግኛ አይደሉም።

"አሁን የሚወጡ መዝሙሮች እና ዘማሪዎች ከወጪ እና ገቢ አንጻር ወዶ ዘማች ናቸው።" ዘማሪ መስፍን ጉቱ

ዘማሪና መጋቢ አስፋው "ብዙ ዘመን ራራህልኝ"፡ "በጅምር አይቀርም የኔ ነገር"፡ "ትላንት ዛሬ አይደለም"፡ "የሩቅ ህልሞቼ"፡ "ይሁን" እና 6ኛ አልበም "አንተን አልጣ እንጂ" የዘመራቸው መዝሙር አልበሞች ናቸው።

ዝማሬዎቹ ሐምሌ 6 በፓስተር አስፋው መለሰ ክራስት ግሎሪ ዩቲዩብ ገጹ ይለቀቃል።
23👍3🔥1👏1
#አስደሳች #ዜና

በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)

መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።

ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው

1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)

ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

ቦታ፡ #አዲስ አበባ #እና ሀዋሳ

(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ሕይወት ብርሃን ቤ/ክ)

አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን

ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822

ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።

https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
6👍1
እውቁ የወንጌል አገልጋይ ጂሚ ስዋጋርት በ90 ዓመታቸው አረፉ።

ጂሚ ስዋጋርት ሚኒስትሪ በፌስቡክ ገጹ ይፋ እንዳደረገው ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት አገልጋዩ ጂሚ ስዋጋርት ወዳገለገለው ጌታ ተሰብስቧል ሲል ገልጿል።

ባለፈው ወር ጁን 15 በልብ ህመም ሆስፒታል የገባ ሲሆን ዛሬ ማለዳ ወዳገለገለው ጌታ መሄዱን ሚኒስትሪው አስታውቋል።

ጂሚ ከ8 ዓመቱ ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ በታማኝነት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያገለግል መቆየቱን ሚኒስትሪው በፌስቡክ ገጹ አሳውቋል።

ከ1969 ዓ.ም በራድዮ፡ በ1970 በመጽሄት ህትመት እና በ1973 ጀምሮ ደግሞ በቴሌቭዥን የወንጌል አገልግሎት ይታወቃል።

ጂሚ በተለይ በ1987 ዓ.ም በብራዚል ሪዮ ዲ ጃኔሮ በነበረው የወንጌል ክሩሴድ ከ127 ሺህ ሰዎች ወንጌል ሰምተዋል።

ጂሚ ስዋጋርት በተደጋጋሚ የወሲብ ቅሌት ስሙ የሚነሳ የነበረ ቢሆንም በንስሃ ተመልሶ ሲያገለግል ነበረ።
ተሶሼትድ ፕሬስ እና ክርስቲያን ፖስት ናቸው ያስነበቡት።
🕊12🙏61😭1
#እግዚአብሔር ቀን አለዉ ለሁሉ የተሰኘዉ ቁጥር 1 የዝማሬ አልበሙን ጨምር

#ቃል ያለዉ አይወድቅም" የሚል መጠርያ ባለዉ በቁጥር 2 አልበሙ ዛሬም ድረስ ብዙዎች ይፅናኑበታል።

ለቅሶ ማታ ቢሆንም ጠዋት ደስታ ይሆናል
ሁሉን ቻዩ ጌታ እግዚአብሔር ቀን ያዛል ዛሬም ድረስ ለብዙዎች በእለፍኛቸዉ ከጌታ ጋር የሚወያዩበት እና ምላሽ የሚጠይቁበት ዝማሬያቸዉ ነዉ።

ላለፉት 2 አስርት አመታት በተሻገረ በዝማሬዎቹ ተባርከንበታል። #ጌታ በሰጠዉ ፀጋ ምዕመናንን ቃሉን በመመገብ ወደ ኋላ አላለም።

ፖስተር ካሳሁን ለማ #አሁን ደግሞ የልቀት ሚስጥር በሚል #አዲስ መፅሐፍ ይዞልን መጥቷል።

ሰኔ 29 እሑድ ከ 08:00 ጀምሮ

ይህንን #ድንቅ ቀን በአንድነት ጌታን እናከብር ዘንድ በአክብሮት ጥሪ እናቀርባለን ።

👉 አድራሻ ቦሌ ኤርፖርት አዲሱ VIP መንገድ ጫፍ ላይ ።
7👍5👌1
#ደረሰ #ደረሰ

በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)

መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።

ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው

1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)

ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

ቦታ፡ #አዲስ አበባ #እና ሀዋሳ

(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ሕይወት ብርሃን ቤ/ክ)

አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን

ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822

ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።

https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
4👍1
💍 ለተጋቡ ጥንዶች ብቻ!

ተመዝግበዋልን?

ትዳራችንን ቆም ብለን ለማጤን ጊዜው አሁን ነው። እኛ ባለትዳሮች ስለትዳራችን እና ልጆቻችን ቁጭ ብለን የምንመክርበት ልዩ ቀናት፣

🛖 የልብ ልባችንን የምንጨዋወትበት ፣ አንድነታችን የሚጠናከርበት እና ቃልኪዳናችንን የምናድስበት እድል፣
💬 ተግባቦታችንን የምንቃኝበት፣ የተሰበረ ልባችን የሚፈወስበት፣ መሰረታችን የሚጠናከርበት፣
👨‍👩‍👧 ልጆችን ለማሳደግ በዓላማ የምንታጠቅበት ፣ በአንድ ልብ ለማሳደግ የሚያስችል እሳቤ የምንሸምትበት
የቀረን ቦታ ለ4 ጥንዶች ብቻ ነው።
ዛሬውኑ ይመዝገቡ! ከጥቂቶቹ መካከል ለመሆን ይወስኑ!

ቀን፦ ከሐምሌ 5-26 ቅዳሜ ፣ ቅዳሜ ከ8:00-12:00

ቦታ:- የቀድሞው ኢምፔሪያል ውሃ ልማት አካባቢ በጨጨሆ ገባ ብሎ

ለመመዝገብ በ0911136520/0946693468 ይደውሉ!

📣 ቦታ አነስተኛ ነው— ለ4 ጥንዶች ብቻ! 
ለትዳሬ ስምረት ምንስ ብከፍልለት!

ስለትምህርቶቻችን ለማወቅ፦

https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
4👍2🔥1🙏1
#ደረሰ #ደረሰ

በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)

መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።

ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው

1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)

ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

ቦታ፡ #አዲስ አበባ #እና ሀዋሳ

(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ሕይወት ብርሃን ቤ/ክ)

አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን

ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822

ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።

https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
1👍1🔥1
#በቁጥር 31 ሰዎች ለወንጌል አገልግሎት የደቀመዛሙርት ትምህርት ተከታትሎ ወደ አገልግሎት ደረሱ።

#ክብር ምስጋና ለሥራው ባለቤት ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን ከእኔ ጋር ጌታን አመስግኑት #በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ምዕራብ ደቡብ ቀጣና ቦንጋ ዙሪያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ሕብረት የቦባ ገጫ ቃ/ሕ/ቤ/ክ በተከታታይ በቤተክርስቲያን የሚሰጠውን የአገልግሎት እና የደቀመዛሙርት ትምህርት የተማሩትን በማስመረቅ እንዲያገለግሉ በቃለ #እግዚአብሔር አስታጠቀች።

በቦባ ገጫ እናት አጥቢያ ሥር የሚገኙት ሁለቱ ተከላዎች ማለትም "የገባ ተከላ ቃ/ሕ/ቤ/ክ የድክ ተከላ ቃ/ሕ/ቤተክርስቲያን የሚገኙት የደቀመዛሙርት ትምህርት የተከታተሉት የተዘጋጀውን ሰርቲፕኬት በመውሰድ በጉባኤ ፊት ማለትም በሦስቱ ቤተክርስቲያን ስብስብ አንድነት ለማገልገል ቃል ኪዳን በመግባት ተመረቁ።

ሰዎችን ሁሉ የእውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዛሙርት የማድረግ አገልግሎት ይልቁንም የሚያስፈልግበት ዘመን ይህ ነው ምክንያቱም ብዙ ነገሮች በዘመናችን ቤተክርስቲያን እየተከሰቱ ነው ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሰነ-ስርዓት ወደ ገሃድ የወጣበት ዘመን ላይ ነን ስለዚህ ትውልድን በቃለ እግዚአብሔር እናስታጥቅ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠውን ታላቁን ተልዕኮ ማስቀጠል አለብን ተልዕኮም የሚፈጸመው በመሄድ ወንጌልን በመስበክ ያመኑትን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ማድረግ ነውና እናስቀጥል።

“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”

ማቴዎስ 28፥19-20
የክርስቶስ ወንጌል ከትውልድ ወደ ትውልድ ይቀጥላል ኢየሱስ ክርስቶስ ያድናል።

✍️ሚሽነሪ አክሊሉ ነኝ ከካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ
6👍1👌1
የምስራቅ ጉጂ መሠረተ #ክርስቶስ ኮሌጅ በታሪኩ የመጀመሪያ ተማሪዎቹን አስመረቀ።

በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ የምስራቅ ጉጂ ስነ-መለኮት ኮሌጅ ዛሬ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በሻኪሶ ከተማ ተማሪዎቹን አስመርቋል።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ስር የሚገኘው ኮሌጁ በዲግሪ መርሐ ግብር ያስተማራቸውን 14 ተማሪዎች ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመረቀው።

በምረቃ ፕሮራሙ ላይ የተገኙት በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የክልል ካምፓሶች ተጠሪ መምህር ታደሰ በዬቻ የእግዚአብሔር ቃል ከማቅረብ ባለፈ ባደረጉት ንግግር "በድግሪ መመረቅ ማለት ከሳሎን ወደ ግቢ መውጣት ነው ሩቅ የሄዳችሁ እንዳይመስላችሁ ስለዚህ መማራችሁን ቀጥሉ" ብለዋል።

የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ዋና ጸሐፊ መጋቢ ትዕግስቱም "ተመራቂዎች የክልሉ እድገት ማሳያና የመጀመሪያዎቹ ታሪካዊ ምሩቃን በመሆናችሁ #እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

ተመራቂዎችም የመጀመሪያ ተመራቂዎች በመሆናቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። በፕሮግራሙ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቷል።

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በአሁን ሰዓት 815 ተማሪዎችን በመያዝ በሀገሪቱ በሚገኙ 23 ካምፓሶች ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል።

ምንጭ:- Meserete Kristos Church - Head Office

ሰኔ 29/2017ዓ.ም
ሻኪሶ
👍43🔥1
"አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው ትያትር ተመረቀ።

በትላንትናው እለት ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በፕሮቪዥን ፈልሞች የተዘጋጀው እና "አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ዘንድ የመጀመሪያው የሆነው ትያትር በቫምዱስ ሲኒማ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቆ ለእይታ ቀርቧል።

የትያትሩ ደራሲና ደይሬክተር ሄኖክ በቀለ “በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ዘንድ እንደዚህ አይነት ስራ አልተለመደም” ያሉ ሲሆን #ይህ የመጀመሪያ ቢሆንም ከዚህ በኋላ ብዙ ስራዎችን በትያትር መልኩ ለመስራት እንዳቀዱ ተናግረዋል።

#እውነት እና #ፍቅር የሚያጠነጥነው አውነትን በቀጥታ መናገርና ፍቅርን መስጠት ላይ የሚያተኩር ሆኖ በሁለት መሃል ያለውን ውዝግብ የሚያሳይ እንደሆነ ደራሲው ገልጿል።

ፕሮቪዥን ፈልሞች ላለፉት ሁለት ዓመታት በጂዶ-ክርስቲያናዊ የሥነ-ምግባር ዕሴት ላይ ታንጾ በጥበብ ዘርፍ እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ሲሆን ፕሮቪዥን ፊልሞች የተቋቋመው በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት አባል ከሆኑ ቤተ ዕምነት የተወጣጡ የትያትር ፣ የሚድያ #እና የፊልም ባለሙያዎች መሆኑ ተገልጿል።

ትያትሩ 55 ደቃቅ ርዝመት የለው ሲሆን በዚህ ትያትር ላይ 4 ዋና ዋና ተዋናዮችና በረካታ ሰዎች በስራው ላይ ተሳትፈዋል።

በትያትሩ ላይ ለተሳተፉት በሙሉ የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ሲሆ በቀጣይም በየሳምንቱ በሻምዱስ ሲኒማ የምታይ መሆኑ ተገልጿል።

ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ
2👍2👌1