የኢትዮጵያ ወጣት ክርስቲያን ማህበር አርቲስት ሸዋፈራው ደሳለኝን የክብር አምባሳደር አድርጎ መረጠ።
አርቲስት ሽዋፈራሁ ደሳለኝ እንዲህ አይነት ወጣቶች ላይ የሚሰራ እና ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ከፍተኛ ፍሬ በማምጣት በጎ ተፅእኖ በመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ካለ ተቋም ጋር በመስራቴ እኔም እድለኛ ነኝ ብሏል።
የአምባሳደርነት ስምምነቱ ለ2 አመት ይቆያል።
የኢትዬጲያ ወጣት ክርስቲያ ማህበር /E.Y.C.A 21ኛ ዓመት የወጣቶች ምስጋና በዓል ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ" በሚል መሪ ቃል ሃምሌ 5 ቀን 2017 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት መሆኑን በመግለጫዉ ተጠቅሷል።
ከ450 ተማሪዎች በላይ የሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ኮሌጆችና የሞያ ተቋማት እንዲያገኙ መደረጉ የተጠቀሰ ሲሆን በተለያዩ ማረሚያ ቤቶችና ዩኒቨርስቲዎች በመንቀሳቀስ ማህበራዊ ግዴታውን ሲወጣ ቆይቷል።
በመግለጫዉ በሃምሌ 5 በሚሊኒየም አዳራሽ፡ 2025 ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ'' በሚል መሪ ቃል ታላቅ የምስጋና በዓል እና የወንጌል መልዕክት ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተነግሯል።
አርቲስት ሸዋፈራሁ ይህ ጉዳይ የሁሉም ሰው በመሆኑ በከፍተኛ ችግር ያለውን ህዝባችንን መርዳት እና ትውልዳችንን በወንጌል መታደግ ስራ ላይ ነፃ አገልግሎት በመስጠት ሁሉም ባለው ነገርና አቅም ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት እንደሆነ ተነስቷል።
አርቲስት ሽዋፈራሁ ደሳለኝ እንዲህ አይነት ወጣቶች ላይ የሚሰራ እና ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ከፍተኛ ፍሬ በማምጣት በጎ ተፅእኖ በመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ካለ ተቋም ጋር በመስራቴ እኔም እድለኛ ነኝ ብሏል።
የአምባሳደርነት ስምምነቱ ለ2 አመት ይቆያል።
የኢትዬጲያ ወጣት ክርስቲያ ማህበር /E.Y.C.A 21ኛ ዓመት የወጣቶች ምስጋና በዓል ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ" በሚል መሪ ቃል ሃምሌ 5 ቀን 2017 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት መሆኑን በመግለጫዉ ተጠቅሷል።
ከ450 ተማሪዎች በላይ የሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ኮሌጆችና የሞያ ተቋማት እንዲያገኙ መደረጉ የተጠቀሰ ሲሆን በተለያዩ ማረሚያ ቤቶችና ዩኒቨርስቲዎች በመንቀሳቀስ ማህበራዊ ግዴታውን ሲወጣ ቆይቷል።
በመግለጫዉ በሃምሌ 5 በሚሊኒየም አዳራሽ፡ 2025 ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ'' በሚል መሪ ቃል ታላቅ የምስጋና በዓል እና የወንጌል መልዕክት ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተነግሯል።
አርቲስት ሸዋፈራሁ ይህ ጉዳይ የሁሉም ሰው በመሆኑ በከፍተኛ ችግር ያለውን ህዝባችንን መርዳት እና ትውልዳችንን በወንጌል መታደግ ስራ ላይ ነፃ አገልግሎት በመስጠት ሁሉም ባለው ነገርና አቅም ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት እንደሆነ ተነስቷል።
❤5👍1
"በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል" - ፓስተር ጻድቁ አብዶ
መጽሃፉ፡ የበኩር መጽሃፋቸው ሲሆን፡ መነሻ ያደረገው በመድረክ ላይ ያስተምሩ ከነበረው የትንቢተ አብድዩ መጽሃፍ የተወሰደ ነው። በቅርብ ወዳጆች ጥያቄ መሰረት በመጽሃፍነት እንዲቀመጥ ተጠይቀው እነሆ ለህትመት በቅቷል።
"መንታ ወንድማማች ስር በሰደደ ጸብ ምክኒያት አንዱ ሞተ፡ አንዱ ተሰደደ። በትውልዳቸው ጥላቻ ስር ሰደደ። ኤዶማዊያን እና እስራኤላዊያን፡ ኤሳው እና ያዕቆብ። በቂም ምክኒያት ኤዶማዊያን ዛሬ የሉም፡ እስራኤላዊያን ስር ሰደዋል።
ከዚህ ታሪክ፡ ይቅርታ እና ምህረትን እንድናደርግ መጽሃፉ ይሞግታል። የቂም እና ክፋት መንገድ ወደ ጥፋት ያደርሰናል። መጽሃፉ በእግዜብሔር ቃል ከክፋት ወደ ቀናነት እንድንመለስ የሚያስተምር ነው።
መጽሃፉ ለአብያተ ክራቲያናት፡ በቀል ይቅር የተባለ ሰው ባህሪ አይደለም። አማኞች በምህረት ያለን ነን። ስለዚህ በቀል ከክርስቲያናዊ አኗኗር ትውቃራኒ ያለ ነው። ይቅር አለማለት እራስን መውደድ እና ጨካኛነት ነው። ከአዙሪት እንዴት እንውጣ፡ የሚል መልስ ይዟል።
መጽሃፉ ሃገራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮቻችንን እንድንቃኝ ያበረታታል። በ150 ገጾች የተዋቀረ ነው።
እሁድ ሰኔ 8፡ 2017 ዓ.ም አድዋ መታሰቢያ አዳራሽ ይመረቃል። በእለቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፡ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት ይመረቃል። ክርስቲያኖች በስፍራው ተገኝተው አብረው እንዲመርቁ ጥሪ ቀርቧል።
በመግለጫው ስለ ርዕሱ ያብራሩት ጸሃፊው "በነብዩ አሞጽ እንደተነገረ፡ በባቢሎን ግዞት ዘመን እስራኤላዊያን በኤዶማዊያን ለመጥፋት ተቃርበው የነበረ ቢሆንም፡ በነብዩ አብድዩ አፍ ደግሞ እንዴት እንደጠፉ ያሳያል።" ብለዋል።
የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን ወደ እናንተ አደረስንላችሁ።
ግንቦት 28/2017ዓ.ም
በኦቦሌሳ አዶላ
መጽሃፉ፡ የበኩር መጽሃፋቸው ሲሆን፡ መነሻ ያደረገው በመድረክ ላይ ያስተምሩ ከነበረው የትንቢተ አብድዩ መጽሃፍ የተወሰደ ነው። በቅርብ ወዳጆች ጥያቄ መሰረት በመጽሃፍነት እንዲቀመጥ ተጠይቀው እነሆ ለህትመት በቅቷል።
"መንታ ወንድማማች ስር በሰደደ ጸብ ምክኒያት አንዱ ሞተ፡ አንዱ ተሰደደ። በትውልዳቸው ጥላቻ ስር ሰደደ። ኤዶማዊያን እና እስራኤላዊያን፡ ኤሳው እና ያዕቆብ። በቂም ምክኒያት ኤዶማዊያን ዛሬ የሉም፡ እስራኤላዊያን ስር ሰደዋል።
ከዚህ ታሪክ፡ ይቅርታ እና ምህረትን እንድናደርግ መጽሃፉ ይሞግታል። የቂም እና ክፋት መንገድ ወደ ጥፋት ያደርሰናል። መጽሃፉ በእግዜብሔር ቃል ከክፋት ወደ ቀናነት እንድንመለስ የሚያስተምር ነው።
መጽሃፉ ለአብያተ ክራቲያናት፡ በቀል ይቅር የተባለ ሰው ባህሪ አይደለም። አማኞች በምህረት ያለን ነን። ስለዚህ በቀል ከክርስቲያናዊ አኗኗር ትውቃራኒ ያለ ነው። ይቅር አለማለት እራስን መውደድ እና ጨካኛነት ነው። ከአዙሪት እንዴት እንውጣ፡ የሚል መልስ ይዟል።
መጽሃፉ ሃገራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮቻችንን እንድንቃኝ ያበረታታል። በ150 ገጾች የተዋቀረ ነው።
እሁድ ሰኔ 8፡ 2017 ዓ.ም አድዋ መታሰቢያ አዳራሽ ይመረቃል። በእለቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፡ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት ይመረቃል። ክርስቲያኖች በስፍራው ተገኝተው አብረው እንዲመርቁ ጥሪ ቀርቧል።
በመግለጫው ስለ ርዕሱ ያብራሩት ጸሃፊው "በነብዩ አሞጽ እንደተነገረ፡ በባቢሎን ግዞት ዘመን እስራኤላዊያን በኤዶማዊያን ለመጥፋት ተቃርበው የነበረ ቢሆንም፡ በነብዩ አብድዩ አፍ ደግሞ እንዴት እንደጠፉ ያሳያል።" ብለዋል።
የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን ወደ እናንተ አደረስንላችሁ።
ግንቦት 28/2017ዓ.ም
በኦቦሌሳ አዶላ
❤9👍1🔥1
ቤተክርስቲያን ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥታ መስራት አለባት ተባለ።
ይህ የተባለዉ የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የባለ ትዳሮች ቃል ኪዳን ማደስ ፕሮግራም ባደረገችበት ወቅት ነዉ።
መርሃ ግብሩ ላይ የአጥቢያ ቤተክርሲያኒቱ መስራች አባላት፣ አገልጋዮችና መሪዎች የነበሩት አቶ ማሞ ገ/መስቀል ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል፣ ወንጌላዊት ቀለሟ ሃይሌ፣ የወቅቱ የአጥቢያ መሪዎች፣ አገልጋዮች እና ባለትዳሮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር ተገኝተዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ የጋብቻ ማማከር አገልግሎት ለባለትዳሮችና ላልተጋቡ ወጣቶች ሥልጠናዎችን በመስጠት ተግታ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየ እንደሆነ የገለጹት የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና የመርሃ ግብሩ ታዳሚያን ቤተክርስቲያን ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥታ መስራት እንዳለባት አሳስበዋል።
የቃል ኪዳን ማደስ ሥነ-ሥርዓቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና መጋቢ የሆኑት መጋቢ ተስፋዬ ገመቹ “እግዚአብሄር ሁል ጊዜ ኪዳኑን ያስባል፤ ከሕዝቡ ጋር ያለውም ትስስርም ከኪዳኑ ግንኙነት የሚመነጭ ነው” በማለት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ መዓዛ መኩሪያ ጋር በመሆን ስርዓቱን መርተዋል።
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ከ65 አመታት በላይ በትዳር የቆዩ ጥንዶች እና በቅርቡ የተጋቡ አዳዲስ ሙሽሮች ኬክ ቆረሳ ያደረጉ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የአንድነት ጌዜ እንደነበራቸው ታውቋል፡፡
የቤተክርሲቲያኒቱ ሰብሳቢ የሆኑት ፕሮፌስር ብርሃኑ ቆጢሶ ሕዝቡን በፀሎት የባረኩ ሲሆን ዘማሪት ሃና ተክሌና ዘማሪ አድነው ዓለሙ በዝማሬ አገልግለዋል።
ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል በበለጠ ተስፋ፣ በበለጠ እምነትና በአንድነት በመያያዝ እግዚአብሄርን በታመነ ሕይወት ለመኖር ልትበረታቱ ያስፈልጋል በማለት የእግዚአብሄር ቃል መልዕክት አካፍለዋል።
በሮማን ከሊል
ይህ የተባለዉ የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የባለ ትዳሮች ቃል ኪዳን ማደስ ፕሮግራም ባደረገችበት ወቅት ነዉ።
መርሃ ግብሩ ላይ የአጥቢያ ቤተክርሲያኒቱ መስራች አባላት፣ አገልጋዮችና መሪዎች የነበሩት አቶ ማሞ ገ/መስቀል ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል፣ ወንጌላዊት ቀለሟ ሃይሌ፣ የወቅቱ የአጥቢያ መሪዎች፣ አገልጋዮች እና ባለትዳሮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር ተገኝተዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ የጋብቻ ማማከር አገልግሎት ለባለትዳሮችና ላልተጋቡ ወጣቶች ሥልጠናዎችን በመስጠት ተግታ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየ እንደሆነ የገለጹት የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና የመርሃ ግብሩ ታዳሚያን ቤተክርስቲያን ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥታ መስራት እንዳለባት አሳስበዋል።
የቃል ኪዳን ማደስ ሥነ-ሥርዓቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና መጋቢ የሆኑት መጋቢ ተስፋዬ ገመቹ “እግዚአብሄር ሁል ጊዜ ኪዳኑን ያስባል፤ ከሕዝቡ ጋር ያለውም ትስስርም ከኪዳኑ ግንኙነት የሚመነጭ ነው” በማለት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ መዓዛ መኩሪያ ጋር በመሆን ስርዓቱን መርተዋል።
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ከ65 አመታት በላይ በትዳር የቆዩ ጥንዶች እና በቅርቡ የተጋቡ አዳዲስ ሙሽሮች ኬክ ቆረሳ ያደረጉ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የአንድነት ጌዜ እንደነበራቸው ታውቋል፡፡
የቤተክርሲቲያኒቱ ሰብሳቢ የሆኑት ፕሮፌስር ብርሃኑ ቆጢሶ ሕዝቡን በፀሎት የባረኩ ሲሆን ዘማሪት ሃና ተክሌና ዘማሪ አድነው ዓለሙ በዝማሬ አገልግለዋል።
ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል በበለጠ ተስፋ፣ በበለጠ እምነትና በአንድነት በመያያዝ እግዚአብሄርን በታመነ ሕይወት ለመኖር ልትበረታቱ ያስፈልጋል በማለት የእግዚአብሄር ቃል መልዕክት አካፍለዋል።
በሮማን ከሊል
❤4👏3❤🔥1
#የእግር #ኳስ #ዜና #አይደለም
ሶስት የፈረንሳይ ሊግ ተጨዋቾች #ግብረሰዶማዊነትን #በመቃወማቸዉ ቅጣት ተጣለባቸው
የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ (ኤልኤፍፒ) የዲሲፕሊን ኮሚቴ በሶስት የፈረንሳይ ሊግ 1 ተጫዋቾች ላይ ቅጣት ጥሏል።
የሊዮኑ ተጨዋች ኒማንያ ማቲች ፣ የሌንንሱ ተጨዋች ጆናታን ግራዲት ፣ እና ለሌ ሃቭሬ የሚጫወተዉ አህመድ ሀሰን በጸረ-ግብረ ሰዶም ቀን የግብረሰዶማውያን ባንዲራ ያለበትን አርማ ባለማድረጋቸዉ "ጥላቻ" በተሰኘ ተግባራቸዉ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
ጆናታን ግራዲት አንድ ጨዋታ ኒማንያ ማቲች እና አህመድ ሀሰን ሁለት ጨዋታዎችን እንዲቀጡ ተብሏል።
በፈረንሳይ ሊግ በተጨዋቾች እጅጌ መለያቸዉ ላይ የግብረ ሰዶማውያን መለያ አርማ ቢለጠፍም ኒማንያ ማቲች አርማዉን በፕላስተር ሸፍኖት ታይቶ ነበር። በዚህም ድርጊቱ ለሁለት ጨዋታ እንዲቀ ወስነዉበታል።
በተጨማሪም የፈረንሳይ እግር ኳስ ግብረሰዶማዉያን ላይ ሰራዋለሁ በሚለዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ እንዲሳተፍ ታዝዟል።
ዳጉ ጆርዳል እንዳስነበበው
ሶስት የፈረንሳይ ሊግ ተጨዋቾች #ግብረሰዶማዊነትን #በመቃወማቸዉ ቅጣት ተጣለባቸው
የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ (ኤልኤፍፒ) የዲሲፕሊን ኮሚቴ በሶስት የፈረንሳይ ሊግ 1 ተጫዋቾች ላይ ቅጣት ጥሏል።
የሊዮኑ ተጨዋች ኒማንያ ማቲች ፣ የሌንንሱ ተጨዋች ጆናታን ግራዲት ፣ እና ለሌ ሃቭሬ የሚጫወተዉ አህመድ ሀሰን በጸረ-ግብረ ሰዶም ቀን የግብረሰዶማውያን ባንዲራ ያለበትን አርማ ባለማድረጋቸዉ "ጥላቻ" በተሰኘ ተግባራቸዉ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
ጆናታን ግራዲት አንድ ጨዋታ ኒማንያ ማቲች እና አህመድ ሀሰን ሁለት ጨዋታዎችን እንዲቀጡ ተብሏል።
በፈረንሳይ ሊግ በተጨዋቾች እጅጌ መለያቸዉ ላይ የግብረ ሰዶማውያን መለያ አርማ ቢለጠፍም ኒማንያ ማቲች አርማዉን በፕላስተር ሸፍኖት ታይቶ ነበር። በዚህም ድርጊቱ ለሁለት ጨዋታ እንዲቀ ወስነዉበታል።
በተጨማሪም የፈረንሳይ እግር ኳስ ግብረሰዶማዉያን ላይ ሰራዋለሁ በሚለዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ እንዲሳተፍ ታዝዟል።
ዳጉ ጆርዳል እንዳስነበበው
👍10👏3❤2🔥1
ጆሽዋ፡ በአሜሪካን ሃገር በ2021 ህይወቱ ያለፈ ታዳጊ ልጅ ነው። በለጋ እድሜው ወንጌልን ለእኩዮቹ መስበክ ጀምሮ ነበር።
አሁን ጆሽዋ ወደሚወደው ጌታ ቢሄድም፡ ቤተሰቦቹ በርሱ ስም Joshua Keep Shining የተሰኘ ፋውንዴሽን አቋቁመዋል።
ከዴንቨር ኮሎራዶ አሜሪካ የተነሳው ፋውንዴሽኑ፡ ታዳጊዎች በወንጌል እንዳያፍሩና ወንጌል እንዲሰብኩ ይሰራል። ከዚህ በተጨማሪ የማህበረሰብ አገዝ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።
ጆሽዋ በትንሽነቱ ወንጌል የመስበክ ልብ የነበረው ልጅ ስለነበረ፡ ምንም እንኳን ወደ ጌታ ቢሄድም የልቡን መሻት ግን በዚህ ፋውንዴሽን በኩል እዉን እናደርጋለን ሲትል እናቱ ፋሲካ ለክርስቲያን ዜና ሃሳቧን አጋርታለች።
እስካሁን ከ6 አበያተ ክርስቲያናት ጋር እየሰራ ያለ ሲሆን፡ በእነዚሁ አብያተ ክርስቲያናት የታዳጊዎች የወንጌል ስርጭት ቡድኖች ተቋቁሟል።
ወንጌላዊት አልማዝ ከካውንስሉ ተገኝተው፡ ዛሬ እንደተሰራው የወንጌል ስራ ነገ በደንብ ሂዱና ወንጌል ስበኩ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጆሽዋ ዛሬ ለጀመረው ስራ እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን ብለዋል።
በወንጌል ስርጭት ዘመቻው የተሳተፉ አብያተ ክርስቲያናት፡ ሚኒስትሪዎች እና ግለሰቦች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
በኦቦሌሳ አዶላ
አሁን ጆሽዋ ወደሚወደው ጌታ ቢሄድም፡ ቤተሰቦቹ በርሱ ስም Joshua Keep Shining የተሰኘ ፋውንዴሽን አቋቁመዋል።
ከዴንቨር ኮሎራዶ አሜሪካ የተነሳው ፋውንዴሽኑ፡ ታዳጊዎች በወንጌል እንዳያፍሩና ወንጌል እንዲሰብኩ ይሰራል። ከዚህ በተጨማሪ የማህበረሰብ አገዝ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።
ጆሽዋ በትንሽነቱ ወንጌል የመስበክ ልብ የነበረው ልጅ ስለነበረ፡ ምንም እንኳን ወደ ጌታ ቢሄድም የልቡን መሻት ግን በዚህ ፋውንዴሽን በኩል እዉን እናደርጋለን ሲትል እናቱ ፋሲካ ለክርስቲያን ዜና ሃሳቧን አጋርታለች።
እስካሁን ከ6 አበያተ ክርስቲያናት ጋር እየሰራ ያለ ሲሆን፡ በእነዚሁ አብያተ ክርስቲያናት የታዳጊዎች የወንጌል ስርጭት ቡድኖች ተቋቁሟል።
ወንጌላዊት አልማዝ ከካውንስሉ ተገኝተው፡ ዛሬ እንደተሰራው የወንጌል ስራ ነገ በደንብ ሂዱና ወንጌል ስበኩ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። ጆሽዋ ዛሬ ለጀመረው ስራ እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን ብለዋል።
በወንጌል ስርጭት ዘመቻው የተሳተፉ አብያተ ክርስቲያናት፡ ሚኒስትሪዎች እና ግለሰቦች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።
በኦቦሌሳ አዶላ
❤9👍1
በብራዚል የወንጌል አማኞች ቁጥር ሲጨምር በአንፃሩ የካቶሊክ #እምነት ተከታዮች ቁጥር እየቀነሰ ነው።
የዓለማችን ትልቁ የሮማ ካቶሊክ መኖሪያ በሆነችው ብራዚል በ2022 የካቶሊክ ህዝብ ቁጥር እየቀነሰ ሲሆን በአንፃሩ የወንጌላውያኑ ክርስቲያኖች እና ምንም አይነት ሃይማኖት የሌላቸው #ሰዎች #ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የስታስቲክስ ኤጀንሲ ባወጣው የህዝብ ቆጠራ መረጃ ያሳያል።
ቆጠራው እንደሚያመለክተው በ2022 ብራዚል 100.2 ሚሊዮን የሮማ ካቶሊኮች አማኞች ወይም ከሀገሬው ህዝብ 56.7% የሚሆነውን #ህዝብ ድርሻ ይዟል። ይህም በ2010 ቆጠራ ከተመዘገበው 65.1 በመቶ ወይም 105.4 ሚሊዮን ያነሰ ሆኗል።
#ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የወንጌላውያን ክርስቲያኖች ድርሻ ባለፈው ዓመት ወደ 26.9 በመቶ ከፍ ብሏል፣ በ2010 ከነበረበት 21.6 በመቶ ወይም 12 ሚሊዮን ተከታዮችን በመጨመር ወደ 47.4 ሚሊዮን ደርሷል።
ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጭማሪ ተመዝግቧል። የወንጌል አማኞች ቁጥር መጨመር በብራዚሉ ግራ ዘመም ፕሬዝደንት ሉዊዝ ኢናሲዮ ሉላ ዳ ሲልቫ አገዛዝ ላይ ችግር ሊፈጥር ይችላል። ገዢው የሰራተኞች ፓርቲ በወንጌላውያን ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ሲታገል ቆይቷል።
በቅርቡ በተደረገ የሕዝብ ቆጠራ እንደሚያሳየው 45 በመቶ ካቶሊኮች የሉላ አስተዳደርን ሲቀበሉ 30 በመቶ የሚሆኑት ወንጌላውያን ብቻ መንግስትን ይደግፋሉ።
በአዲሱ የህዝብ ቆጠራ መረጃ መሰረት ሃይማኖት የለንም የሚሉ ብራዚላውያን ቁጥር ከ7.9 በመቶ ወደ 9.3 በመቶ ከፍ ማለቱን አረጋግጧል ይህም በአጠቃላይ 16.4 ሚሊዮን ህዝብ ደርሷል።
እንደ ኡምባንዳ #እና ካንዶምብል ያሉ አፍሮ ብራዚሊያውያን ሃይማኖቶችም የተከታዮች ቁጥር ከ 0.3 ወደ 1 በመቶ ማደጉን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
በስምኦን ደረጄ
ምንጭ #ዳጉ_ጆርናል
የዓለማችን ትልቁ የሮማ ካቶሊክ መኖሪያ በሆነችው ብራዚል በ2022 የካቶሊክ ህዝብ ቁጥር እየቀነሰ ሲሆን በአንፃሩ የወንጌላውያኑ ክርስቲያኖች እና ምንም አይነት ሃይማኖት የሌላቸው #ሰዎች #ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የስታስቲክስ ኤጀንሲ ባወጣው የህዝብ ቆጠራ መረጃ ያሳያል።
ቆጠራው እንደሚያመለክተው በ2022 ብራዚል 100.2 ሚሊዮን የሮማ ካቶሊኮች አማኞች ወይም ከሀገሬው ህዝብ 56.7% የሚሆነውን #ህዝብ ድርሻ ይዟል። ይህም በ2010 ቆጠራ ከተመዘገበው 65.1 በመቶ ወይም 105.4 ሚሊዮን ያነሰ ሆኗል።
#ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የወንጌላውያን ክርስቲያኖች ድርሻ ባለፈው ዓመት ወደ 26.9 በመቶ ከፍ ብሏል፣ በ2010 ከነበረበት 21.6 በመቶ ወይም 12 ሚሊዮን ተከታዮችን በመጨመር ወደ 47.4 ሚሊዮን ደርሷል።
ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጭማሪ ተመዝግቧል። የወንጌል አማኞች ቁጥር መጨመር በብራዚሉ ግራ ዘመም ፕሬዝደንት ሉዊዝ ኢናሲዮ ሉላ ዳ ሲልቫ አገዛዝ ላይ ችግር ሊፈጥር ይችላል። ገዢው የሰራተኞች ፓርቲ በወንጌላውያን ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ሲታገል ቆይቷል።
በቅርቡ በተደረገ የሕዝብ ቆጠራ እንደሚያሳየው 45 በመቶ ካቶሊኮች የሉላ አስተዳደርን ሲቀበሉ 30 በመቶ የሚሆኑት ወንጌላውያን ብቻ መንግስትን ይደግፋሉ።
በአዲሱ የህዝብ ቆጠራ መረጃ መሰረት ሃይማኖት የለንም የሚሉ ብራዚላውያን ቁጥር ከ7.9 በመቶ ወደ 9.3 በመቶ ከፍ ማለቱን አረጋግጧል ይህም በአጠቃላይ 16.4 ሚሊዮን ህዝብ ደርሷል።
እንደ ኡምባንዳ #እና ካንዶምብል ያሉ አፍሮ ብራዚሊያውያን ሃይማኖቶችም የተከታዮች ቁጥር ከ 0.3 ወደ 1 በመቶ ማደጉን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
በስምኦን ደረጄ
ምንጭ #ዳጉ_ጆርናል
❤13👍8👏4🔥1🙏1
#ካወንስሉ በከተማው ለሚከናወነው የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት 17 ሚሊየን ብር አሰባሰበ።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካወንስል በስሩ ያሉ የተለያዩ ቤተ እምነቶች በከተማው ለሚከናወነው የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም የኢቫንጄሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ (ETC) ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ፕሬዝደንት ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ የእንኳን ደህና መጣቸዉ ንግግር በማድረግ ኤርምያስ 29፡4 ያለውን የእግዚአብሔርን ቃል በመከፈል ሁላችንም የሃገር አደራ አለብን በዚህ ስራ መሳተፋችን ለትውልድ ትልቅ ነገር ጥሎ መሄድ ነው ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
በማስቀጠልም የካውንስሉ ምክትል ፕሬዝደንት ሐዋርያው ዮሐንስ ግርማ የዚህ ፕሮግራም አላማ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑን በመግለጽ ተፈጥሮን መንከባከብና መጠበቅ የእግዚአብሔር ትዛዝ ነው። በዚህ ወስጥ ልጆችንን እና አፍሪካን የሚያኮራ ስራ ልንሰራ ይገባል።
አቶ ጥላሁን ወርቁ የወንዝ ዳር ልማት የፕሮጀክትን አላማ በመግለጽ በጸሎታቸው እና በመንከባከብ ፣በመጠበቅ ፣በማስተማር እንዲሁም በገንዘባቸው ከጎናችን እንድትቆሙ ስሉ አሳስበዋል።
በወንድም ጥላሁን ጉግሳ የገንዘብ ማሳሰቢያ ፕሮግራም የተደረገ ሲሆን በአጠቃላይ የተሰበሰበው ገቢ 17 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር መሆን በመድረኩ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካወንስል በስሩ ያሉ የተለያዩ ቤተ እምነቶች በከተማው ለሚከናወነው የወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የተዘጋጀ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም የኢቫንጄሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ (ETC) ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ፕሬዝደንት ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ የእንኳን ደህና መጣቸዉ ንግግር በማድረግ ኤርምያስ 29፡4 ያለውን የእግዚአብሔርን ቃል በመከፈል ሁላችንም የሃገር አደራ አለብን በዚህ ስራ መሳተፋችን ለትውልድ ትልቅ ነገር ጥሎ መሄድ ነው ሲሉ መልክታቸውን አስተላልፈዋል።
በማስቀጠልም የካውንስሉ ምክትል ፕሬዝደንት ሐዋርያው ዮሐንስ ግርማ የዚህ ፕሮግራም አላማ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑን በመግለጽ ተፈጥሮን መንከባከብና መጠበቅ የእግዚአብሔር ትዛዝ ነው። በዚህ ወስጥ ልጆችንን እና አፍሪካን የሚያኮራ ስራ ልንሰራ ይገባል።
አቶ ጥላሁን ወርቁ የወንዝ ዳር ልማት የፕሮጀክትን አላማ በመግለጽ በጸሎታቸው እና በመንከባከብ ፣በመጠበቅ ፣በማስተማር እንዲሁም በገንዘባቸው ከጎናችን እንድትቆሙ ስሉ አሳስበዋል።
በወንድም ጥላሁን ጉግሳ የገንዘብ ማሳሰቢያ ፕሮግራም የተደረገ ሲሆን በአጠቃላይ የተሰበሰበው ገቢ 17 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር መሆን በመድረኩ ተገልጿል።
❤12👍2🔥1👌1
የሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን አመራሮች #የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስን ዋና መሥሪያ ቤት ጎበኙ።
የLWF ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ የሚጀመር ሲሆን የLWF ምክር ቤት ስብሰባ ከመጀመሩ አስቀድም ፅ/ቤቱን ገብኝተዋል።
የምክር ቤቱ ጭብጥ "ምስክሮቼ ሁኑ" የሚል ሲሆን ከሁሉም የሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን ክልሎች የተውጣጡ 48 የምክር ቤት አባላትን እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።
የLWF ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ የሚጀመር ሲሆን የLWF ምክር ቤት ስብሰባ ከመጀመሩ አስቀድም ፅ/ቤቱን ገብኝተዋል።
የምክር ቤቱ ጭብጥ "ምስክሮቼ ሁኑ" የሚል ሲሆን ከሁሉም የሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን ክልሎች የተውጣጡ 48 የምክር ቤት አባላትን እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።
❤8👍1🔥1
የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ለአገሪቱ የምግብ ዋስትና ሠራተኞቹ ጾም እና ጸሎት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ።
ናይጄሪያ የምግብ ዋስትናን እንድታረጋግጥ ፈጣሪን ለመማጸን ፆም እና ጸሎት እንዲያደርጉ የአገሪቱ የእርሻ ሚኒስቴር ሠራተኞቹን መጠየቁን ተከትሎ ውዝግብ ተፈጥሯል።
በናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር የሰው ኃይል አስተዳደር ክፍል ኃላፊ አማካኝነት ለመሥርያ ቤቱ ሠራተኞች በተሰራጫው ማስታወሻ የሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ ባልደረቦች ለተከታታይ ሦስት ሰኞዎች በሚካሄደው የተማጽኖ ፆም እና ጸሎት ላይ እንዲሳተፉ ይጠይቃል።
ይህ ዜና መውጣቱን ተከትሎ አንዳንድ ናይጄሪያውያን መንግሥታቸው በአገሪቱ እያነረ ያለውን የምግብ ዋጋ እንዲቀንስ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ በመክተት ተችተዋል።
የፆም ጸሎት ጥሪው መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ ማስተባበያ ሰጥቷል።
ጥሪው በአገሪቱ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ ጸሎት የመንግሥት ይፋዊ ፖሊሲ አለመሆኑን አመልክቶ፣ ነገር ግን ጸሎቱ የሠራተኞችን ደኅንነት ለማዳበር ነው ብሏል።
ሙሉዉን BBC AMHARIC ላይ ያንብቡ
ናይጄሪያ የምግብ ዋስትናን እንድታረጋግጥ ፈጣሪን ለመማጸን ፆም እና ጸሎት እንዲያደርጉ የአገሪቱ የእርሻ ሚኒስቴር ሠራተኞቹን መጠየቁን ተከትሎ ውዝግብ ተፈጥሯል።
በናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር የሰው ኃይል አስተዳደር ክፍል ኃላፊ አማካኝነት ለመሥርያ ቤቱ ሠራተኞች በተሰራጫው ማስታወሻ የሚኒስትር መሥሪያ ቤቱ ባልደረቦች ለተከታታይ ሦስት ሰኞዎች በሚካሄደው የተማጽኖ ፆም እና ጸሎት ላይ እንዲሳተፉ ይጠይቃል።
ይህ ዜና መውጣቱን ተከትሎ አንዳንድ ናይጄሪያውያን መንግሥታቸው በአገሪቱ እያነረ ያለውን የምግብ ዋጋ እንዲቀንስ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ጥያቄ ውስጥ በመክተት ተችተዋል።
የፆም ጸሎት ጥሪው መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ የናይጄሪያ እርሻ ሚኒስቴር ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ ማስተባበያ ሰጥቷል።
ጥሪው በአገሪቱ ያለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ ጸሎት የመንግሥት ይፋዊ ፖሊሲ አለመሆኑን አመልክቶ፣ ነገር ግን ጸሎቱ የሠራተኞችን ደኅንነት ለማዳበር ነው ብሏል።
ሙሉዉን BBC AMHARIC ላይ ያንብቡ
❤10👍3🔥1🥰1
የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ከታሪካዊ እርቅ በኋላ አዳዲስ አመራሮች መረጡ።
የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በውስጥ አለመግባባቶች ለአራት ዓመታት የዘለቀውን ክፍፍል በእርቅ ተቋጭቶ አዳዲስ አመራሮችን መርጠዋል።
በታህሳስ 9, 2013 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ክልል ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ምስረታ ምክንያት በጋሞ ዞን እና በአርባምንጭ ከተማ ወ/አ/ክ የቀድሞ አመራሮች እና በዞኑ እና በከተማዉ ህብረት መሪዎች የነበረዉ አላማግባባት ለሚመከተዉ ባለድርሻ አካል ቅሬታ ቀርቦ የነበረ ቢሆንም ሳይፈታ መቆየቱ በወንጌል እንቅስቀሴ ላይ እና በወንድሞች ህብረት ላይ ትልቅ ጫና ፈጥሮ ቆይቶል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃድቁ አብዶ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጽ/ቤት ሃላፊ መጋቢ ጌትነት ለማ በጥር 15/17 አራት የእርቅ አመቻት ኮሚቴ የሰየሙ ሲሆን አመቻች ኮሚቴው በዞኑ እና በከተማዉ የነበረዉን የቀድሞን ፍቅር እና ህብረት ለመመለስ ከፍተኛ ጥራት በማድራግ ሰኔ1 እርቅ ስምምናት መደረጉ ተገልጿል።
በቀድሞ አመራሮች እጅ የነበረዉ የህብረቱ የንብረት እርክክብ ያደረገ ሲሆን የክልሉ ም/ፕሬዝደንት መጋቢ ወንድማገኝ አስፋ በመገኘት ንብረቱን የመረካካብ ሥርዓት ማስፈጸማቸው ይታወሳል።
ሰኔ 07/17 በክልሉ ፀሐፊ ዶ/ር ማርቆስ አቢሶ መሪነት የተካሄደው ምርጫ በመስራች አብያተ ክርስቲያናት መካከል እርቅን የፈጠረ አዲስ ጅማሬ እንደሆነም ተገልጿል።
በዚህም መሰረት ወ/ም ቹቹ ቹርኮ የጋሞ ዞን ወ/አ/ክ/ ህብረት ሰብሳቢ እና ወ/ም ደፋርሼ ሻንካ የአርባ ምንጭ ከተማ ወ/አ/ክ/ህብረት ሰብሳቢ ተደርገው ተመርጠዋል።
የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በውስጥ አለመግባባቶች ለአራት ዓመታት የዘለቀውን ክፍፍል በእርቅ ተቋጭቶ አዳዲስ አመራሮችን መርጠዋል።
በታህሳስ 9, 2013 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ክልል ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ምስረታ ምክንያት በጋሞ ዞን እና በአርባምንጭ ከተማ ወ/አ/ክ የቀድሞ አመራሮች እና በዞኑ እና በከተማዉ ህብረት መሪዎች የነበረዉ አላማግባባት ለሚመከተዉ ባለድርሻ አካል ቅሬታ ቀርቦ የነበረ ቢሆንም ሳይፈታ መቆየቱ በወንጌል እንቅስቀሴ ላይ እና በወንድሞች ህብረት ላይ ትልቅ ጫና ፈጥሮ ቆይቶል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃድቁ አብዶ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጽ/ቤት ሃላፊ መጋቢ ጌትነት ለማ በጥር 15/17 አራት የእርቅ አመቻት ኮሚቴ የሰየሙ ሲሆን አመቻች ኮሚቴው በዞኑ እና በከተማዉ የነበረዉን የቀድሞን ፍቅር እና ህብረት ለመመለስ ከፍተኛ ጥራት በማድራግ ሰኔ1 እርቅ ስምምናት መደረጉ ተገልጿል።
በቀድሞ አመራሮች እጅ የነበረዉ የህብረቱ የንብረት እርክክብ ያደረገ ሲሆን የክልሉ ም/ፕሬዝደንት መጋቢ ወንድማገኝ አስፋ በመገኘት ንብረቱን የመረካካብ ሥርዓት ማስፈጸማቸው ይታወሳል።
ሰኔ 07/17 በክልሉ ፀሐፊ ዶ/ር ማርቆስ አቢሶ መሪነት የተካሄደው ምርጫ በመስራች አብያተ ክርስቲያናት መካከል እርቅን የፈጠረ አዲስ ጅማሬ እንደሆነም ተገልጿል።
በዚህም መሰረት ወ/ም ቹቹ ቹርኮ የጋሞ ዞን ወ/አ/ክ/ ህብረት ሰብሳቢ እና ወ/ም ደፋርሼ ሻንካ የአርባ ምንጭ ከተማ ወ/አ/ክ/ህብረት ሰብሳቢ ተደርገው ተመርጠዋል።
❤4👍2🔥1
ተበዳይ አትበቀል ለእግዚአብሔር ተው ይሄ ነገር ከባድ ነው። እንዴት ይቻላል? ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ / Dr. Mamusha Fenta / Amazing teaching https://www.youtube.com/watch?v=gN1gWVaMhTs
YouTube
ተበዳይ አትበቀል ለእግዚአብሔር ተው ይሄ ነገር ከባድ ነው። እንዴት ይቻላል? ዶ/ር ማሙሻ ፈንታ / Dr. Mamusha Fenta / Amazing teaching
#gospel #billy
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews #ethiopiantvshow…
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews #ethiopiantvshow…
❤5👍1🔥1
#አስደሳች ዜና
በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።
ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው
1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)
ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም
ቦታ፡ አዲስ አበባ እና ሀዋሳ
(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ህይወት ብርሃን)
አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲቂቆስ ሚዲያ ፤ የክርስቲያን ዜና በጋራ
ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822
ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።
ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው
1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)
ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም
ቦታ፡ አዲስ አበባ እና ሀዋሳ
(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ህይወት ብርሃን)
አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲቂቆስ ሚዲያ ፤ የክርስቲያን ዜና በጋራ
ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822
ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
👍10❤6🔥1
ISIS በሶሪያ 25 ክርስቲያኖችን ገደለ
ጥቃቱ የተፈጸመው በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት ደርሶባቸዋል።
እሁድ ጠዋት ክርስቲያኖች ቅዱስ ኤሊያስ በተባለው ቤተ ክርስቲያን ለጸሎት ተሰብስበው ነበረ። ጥቃት አድራሹ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ ተኩስ ከከፈተ በኋላ የአጥፍቶ ማጥፋት ፍንዳታውን እንዳደረገ ተገልጿል።
በግሪክ ኦሮቶዶክስ ቤ/ክ የአንጾኪያ ፓትሪያርክ አደጋውን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ጸሎት እናድርግ፣ ለተጎዱ ሰዎች ደግሞ ድጋፍ እናድርግ ሲሉ ተደምጠዋል። የሃገሪቱ ባለስልጣናት በበኩላቸው ሃገሪቱ በሽግግር ላይ ባለችበት ወቅት ወደ ቀውስ ለማስገባት የተደረግ ሙከራ ነው ሲል ገልጾታል።
ISIS ለጥቃቱ ሃላፊነት የወሰደ ሲሆን፣ በአረብ ሃገራት እና በሌሎች አካባቢዎችም ክርስቲያኖችን እና አአስተኛ የሚባሉ ቡድኖችን ለማጥፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በሽር አል አሳድ ከስልጣ ከተወገዱ በኋላ ይሄ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ከባድ ጥቃት ነው። ISIS በሰሜናዊ ሶሪያ አካባቢዎች ድጋሚ ለመንቀሳቀስ ሙከራ እያደረገ ይገኛል።
ሶሪያ ማለት የመጀምሪያ ክርስቲያኖች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም ያገኙባት #አንጾኪያ መገኛ የሆነች ምድር ናት። ዋና ከተማዋ ደማስቆ ደግሞ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊያሳድድ ሲሄድ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የተገናኘባት ምድር ናት።
The Christian Post & Allarab News እንዳስነበቡት
ጥቃቱ የተፈጸመው በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነው። አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት ደርሶባቸዋል።
እሁድ ጠዋት ክርስቲያኖች ቅዱስ ኤሊያስ በተባለው ቤተ ክርስቲያን ለጸሎት ተሰብስበው ነበረ። ጥቃት አድራሹ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ ተኩስ ከከፈተ በኋላ የአጥፍቶ ማጥፋት ፍንዳታውን እንዳደረገ ተገልጿል።
በግሪክ ኦሮቶዶክስ ቤ/ክ የአንጾኪያ ፓትሪያርክ አደጋውን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ጸሎት እናድርግ፣ ለተጎዱ ሰዎች ደግሞ ድጋፍ እናድርግ ሲሉ ተደምጠዋል። የሃገሪቱ ባለስልጣናት በበኩላቸው ሃገሪቱ በሽግግር ላይ ባለችበት ወቅት ወደ ቀውስ ለማስገባት የተደረግ ሙከራ ነው ሲል ገልጾታል።
ISIS ለጥቃቱ ሃላፊነት የወሰደ ሲሆን፣ በአረብ ሃገራት እና በሌሎች አካባቢዎችም ክርስቲያኖችን እና አአስተኛ የሚባሉ ቡድኖችን ለማጥፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
በሽር አል አሳድ ከስልጣ ከተወገዱ በኋላ ይሄ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመ ከባድ ጥቃት ነው። ISIS በሰሜናዊ ሶሪያ አካባቢዎች ድጋሚ ለመንቀሳቀስ ሙከራ እያደረገ ይገኛል።
ሶሪያ ማለት የመጀምሪያ ክርስቲያኖች “ክርስቲያን” የሚለውን ስም ያገኙባት #አንጾኪያ መገኛ የሆነች ምድር ናት። ዋና ከተማዋ ደማስቆ ደግሞ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሊያሳድድ ሲሄድ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የተገናኘባት ምድር ናት።
The Christian Post & Allarab News እንዳስነበቡት
💔11❤1🕊1😭1
የሶሪያ የክርስቲያን መሪዎች በቤተክርስቲያን የቦምብ ጥቃት ላይ መንግስትን ወቀሱ።
የሶሪያ ከፍተኛ የክርስቲያን መሪ በእሁድ ቀን በርካታ ሰዎችን ለገደለው የቤተክርስቲያን ፍንዳታ የሶሪያውን ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራአን መንግስትን ወቅሰዋል።
ባሳለፍነው እሁድ በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል።
መሪዎቹ በመንግስት ጥበቃ በሚሰጠው ዋስትና ላይ መመካት አለመቻላቸውን እና ያላቸውን ጥርጣቄ አጠናክሯል ተብሏል።
በአንጾኪያ የግሪክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ጆን (ኤክስ) ያዚጊ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ “በፍቅር እና በአክብሮት ክቡር ፕሬዝደንት ሀዘናችሁን ለመግለፅ በስልክ መነጋገራቸውን ገልጸው ለስልክ ጥሪው አመስጋኞች ነን ግን የተፈጠረው ወንጀል ከዚህ ትንሽ ይበልጣል ሲሉ ተናግረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ "ጨካኝ እና ፈሪነት የተሞላበት ጥቃት" ሲል የገለፀውን ድርጊት አውግዞ የሶሪያ መንግስት ሁከት ፈጣሪዎችን ሁሉ በህግ እንዲጠየቅ እና የሃይማኖት እና የጎሳ አባላትን ጨምሮ የመላው ሶሪያውያን ደህንነት እንዲያረጋግጥ ጠይቋል።
ከጦርነት በፊት ከነበሩት 22 ሚሊዮን የሶሪያ ህዝብ 10 በመቶ ያህሉ ናቸው ነገር ግን በ 14 ግጭት ዓመታት ቁጥራቸው በስደት ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ሲሆን አሁን በሶሪያ እንደሚኖሩ የሚገመተው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ናቸው።
በሟቾች የቀብር ስነ-ስረዓት ላይ በሶሪያ አዲስ መንግስት ውስጥ ብቸኛዋ ክርስቲያን እና ብቸኛ ሴት የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ሂንድ ካባዋት መገኘታቸውን የዎርዚ ኒውስ በዘገባው አክሎ ገልጿል።
ሶሪያ ለክርስትና አስቸጋሪ ከሆኑ 50 ሀገራት መካከል 18ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
የሶሪያ ከፍተኛ የክርስቲያን መሪ በእሁድ ቀን በርካታ ሰዎችን ለገደለው የቤተክርስቲያን ፍንዳታ የሶሪያውን ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራአን መንግስትን ወቅሰዋል።
ባሳለፍነው እሁድ በደማስቆ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ ከሞቱ 25 ሰዎች በተጨማሪ 59 ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል።
መሪዎቹ በመንግስት ጥበቃ በሚሰጠው ዋስትና ላይ መመካት አለመቻላቸውን እና ያላቸውን ጥርጣቄ አጠናክሯል ተብሏል።
በአንጾኪያ የግሪክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ጆን (ኤክስ) ያዚጊ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ “በፍቅር እና በአክብሮት ክቡር ፕሬዝደንት ሀዘናችሁን ለመግለፅ በስልክ መነጋገራቸውን ገልጸው ለስልክ ጥሪው አመስጋኞች ነን ግን የተፈጠረው ወንጀል ከዚህ ትንሽ ይበልጣል ሲሉ ተናግረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ "ጨካኝ እና ፈሪነት የተሞላበት ጥቃት" ሲል የገለፀውን ድርጊት አውግዞ የሶሪያ መንግስት ሁከት ፈጣሪዎችን ሁሉ በህግ እንዲጠየቅ እና የሃይማኖት እና የጎሳ አባላትን ጨምሮ የመላው ሶሪያውያን ደህንነት እንዲያረጋግጥ ጠይቋል።
ከጦርነት በፊት ከነበሩት 22 ሚሊዮን የሶሪያ ህዝብ 10 በመቶ ያህሉ ናቸው ነገር ግን በ 14 ግጭት ዓመታት ቁጥራቸው በስደት ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ሲሆን አሁን በሶሪያ እንደሚኖሩ የሚገመተው በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ናቸው።
በሟቾች የቀብር ስነ-ስረዓት ላይ በሶሪያ አዲስ መንግስት ውስጥ ብቸኛዋ ክርስቲያን እና ብቸኛ ሴት የማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ሂንድ ካባዋት መገኘታቸውን የዎርዚ ኒውስ በዘገባው አክሎ ገልጿል።
ሶሪያ ለክርስትና አስቸጋሪ ከሆኑ 50 ሀገራት መካከል 18ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
❤7😭4💔3🕊1
"አንተን አልጣ እንጂ" ዘማሪ አስፋው መለሰ
ይሄ 6ኛ አልበም፡ ማቴዎስ 6፥31 ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሲሆን
በ20 ዓመታት የአገልግሎት ጊዜዬ በማግኘትም በማጣትም ጌታን ብቻ ዋናዬ ነበረ። ልደታ አሴምብልስ ኦፍ ጋድ ቤ/ክ ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም ይመረቃል።
መጋቢ አስፋው በ20 ዓመታት አገልግሎቱ በከተማም በገጠርም በትጋት እና በታማኝነት አገልግሏል ከዚህ በፊት የነበሩት መዝሙሮች ለቤተ ክርስቲያን መታነጽ፡ ለትውልድ መባረክ ምክንያት ሆነዋል። ይሄኛውም አልበም ብዙዎችን እንደሚባርክ እርግጠኛ ነን።
ጉባኤ እግዚአብሄር ቤ/ክ ከ20 ዓመታት በላይ አገልግሏል። ቤተ ክርስቲያኗ የምታምንበትን ሰው ጌታን ካለው ምንም ያጣም ብላ ስለምታምን፡ ይሄንን መዝሙር ለክርስቲያኖች በረከት ይሆናል።
በዚህ መዝሙር ግለሰቦች እና ቤ/ክ ብቻ ሳይሆን ሃገር ይጠቀማል። ሐምሌ 6 በሚኖረው የአምልኮ ድግስ ተገናኝተን እናምልክ።
"አንተን አልጣ እንጂ" የሙዚቃ ዝግጅት ስራ ላይ ከ2 ዓመት በላይ ፈጅቷል። ይሁን እንጂ ዘማሪ ስለሆንኩኝ ሁሌም መዝሙር እዘምራለሁ። መዝሙሩን
ሐዋ 4፥4 መሰረት አድርጎ ከባለቤቴ እና ልጆቼ ጋር አንድ ክሊፕ አለው። ሰንዱቁ 11 መዝሙሮችን ይዟል። ሚሊኒየም አዳራሽ ድግስ አትጠብቁ!
አሁን የሚወጡ መዝሙሮች ገቢ ማግኛ ሳይሆኑ ለእግዚአብሄር የሚቀርቡ መስዋዕቶች ስለሆኑ ገቢ ማግኛ አይደሉም።
"አሁን የሚወጡ መዝሙሮች እና ዘማሪዎች ከወጪ እና ገቢ አንጻር ወዶ ዘማች ናቸው።" ዘማሪ መስፍን ጉቱ
ዘማሪና መጋቢ አስፋው "ብዙ ዘመን ራራህልኝ"፡ "በጅምር አይቀርም የኔ ነገር"፡ "ትላንት ዛሬ አይደለም"፡ "የሩቅ ህልሞቼ"፡ "ይሁን" እና 6ኛ አልበም "አንተን አልጣ እንጂ" የዘመራቸው መዝሙር አልበሞች ናቸው።
ዝማሬዎቹ ሐምሌ 6 በፓስተር አስፋው መለሰ ክራስት ግሎሪ ዩቲዩብ ገጹ ይለቀቃል።
ይሄ 6ኛ አልበም፡ ማቴዎስ 6፥31 ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሲሆን
በ20 ዓመታት የአገልግሎት ጊዜዬ በማግኘትም በማጣትም ጌታን ብቻ ዋናዬ ነበረ። ልደታ አሴምብልስ ኦፍ ጋድ ቤ/ክ ሐምሌ 6/2017 ዓ.ም ይመረቃል።
መጋቢ አስፋው በ20 ዓመታት አገልግሎቱ በከተማም በገጠርም በትጋት እና በታማኝነት አገልግሏል ከዚህ በፊት የነበሩት መዝሙሮች ለቤተ ክርስቲያን መታነጽ፡ ለትውልድ መባረክ ምክንያት ሆነዋል። ይሄኛውም አልበም ብዙዎችን እንደሚባርክ እርግጠኛ ነን።
ጉባኤ እግዚአብሄር ቤ/ክ ከ20 ዓመታት በላይ አገልግሏል። ቤተ ክርስቲያኗ የምታምንበትን ሰው ጌታን ካለው ምንም ያጣም ብላ ስለምታምን፡ ይሄንን መዝሙር ለክርስቲያኖች በረከት ይሆናል።
በዚህ መዝሙር ግለሰቦች እና ቤ/ክ ብቻ ሳይሆን ሃገር ይጠቀማል። ሐምሌ 6 በሚኖረው የአምልኮ ድግስ ተገናኝተን እናምልክ።
"አንተን አልጣ እንጂ" የሙዚቃ ዝግጅት ስራ ላይ ከ2 ዓመት በላይ ፈጅቷል። ይሁን እንጂ ዘማሪ ስለሆንኩኝ ሁሌም መዝሙር እዘምራለሁ። መዝሙሩን
ሐዋ 4፥4 መሰረት አድርጎ ከባለቤቴ እና ልጆቼ ጋር አንድ ክሊፕ አለው። ሰንዱቁ 11 መዝሙሮችን ይዟል። ሚሊኒየም አዳራሽ ድግስ አትጠብቁ!
አሁን የሚወጡ መዝሙሮች ገቢ ማግኛ ሳይሆኑ ለእግዚአብሄር የሚቀርቡ መስዋዕቶች ስለሆኑ ገቢ ማግኛ አይደሉም።
"አሁን የሚወጡ መዝሙሮች እና ዘማሪዎች ከወጪ እና ገቢ አንጻር ወዶ ዘማች ናቸው።" ዘማሪ መስፍን ጉቱ
ዘማሪና መጋቢ አስፋው "ብዙ ዘመን ራራህልኝ"፡ "በጅምር አይቀርም የኔ ነገር"፡ "ትላንት ዛሬ አይደለም"፡ "የሩቅ ህልሞቼ"፡ "ይሁን" እና 6ኛ አልበም "አንተን አልጣ እንጂ" የዘመራቸው መዝሙር አልበሞች ናቸው።
ዝማሬዎቹ ሐምሌ 6 በፓስተር አስፋው መለሰ ክራስት ግሎሪ ዩቲዩብ ገጹ ይለቀቃል።
❤23👍3🔥1👏1
#አስደሳች #ዜና
በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።
ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው
1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)
ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም
ቦታ፡ #አዲስ አበባ #እና ሀዋሳ
(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ሕይወት ብርሃን ቤ/ክ)
አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን
ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822
ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።
https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)
መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።
ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው
1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)
ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም
ቦታ፡ #አዲስ አበባ #እና ሀዋሳ
(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ሕይወት ብርሃን ቤ/ክ)
አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን
ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822
ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።
https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit
❤6👍1