በካዉንስሉ ፕሬዝደንት የተፃፈዉ "የመሪ ባሕሪያት መሰረታዉያን" የተሰኘዉ መፅሐፍ ተመረቀ።
በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ፕሬዝደንት በዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ የተፃፈዉ እና በ2 ክፍሎች እና በ4 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ200 ገፆች የተዋቀረዉ መፅሐፍ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፣ የፀሐፊዉ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላዉ እንግዶች በተገኙበት በዘፀዓት አፖስቶሊክ ሪፎርሜሽን ቤተክርስቲያን በድምቀት ተመርቋል።
በመድረኩ ዶ/ር ወርቁ የመፅሐፉን ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን በንግግራቸው ዶ/ር ጣሰው መሪነት በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን መጠቀሱን አንስተዉ ባለአደራነት ፤ ጥበብ እና የእግዚአብሔር ቃል የጎደለዉ መሪ ለተቋማት መውደቅ ለአመራት ክፍተት እንደሚፈጠር በመጥቀስ ይሞግታሉ ሲል አንስቷል።
ፖስተር ፃዲቁ አብዱ በበኩላቸው በመሪነት ደረጃ ላሉት ብቻ ሳይሆን ወደ መሪነት ለማደግ ለሚሄዱትም ጠቃሚ የሆነ መጽሀፍ በመሆኑ ሁሉም ሊያነቡት እንደሚገባ መክርዋል።
የመጽሀፊ አዘጋጅ ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ መፅሐፍ ቅዱሳችን እራሱ መሪነትን በየአዉዱ በመከፋፈል የሚያስቀምጥ መሆኑን በመጥቀስ ለአንድ መሪ ባሕሪ መሰራት እና የመሪዎች የበሃሪ ተግዳሮት መስተዋሉ ይህንንም ችግር ለመቀነስ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ለማበርከት መጽሀፉን እንዳዘጋጁት ተናግረዋል።
ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ ይህ 3ኛ መፅሐፋቸዉ ሲሆን ከዚህ ቀደም "የመሪ ፈተናዎች ፤ስህተቶች እና መፍትሄዎቹ" እንዲሁም "ክዋኔ የትግበራ ክህሎት" የተሰኙ ሁለት መፅሐፍትን በ2013 ዓ.ም ለንባብ ማብቃታቸዉ ይታወሳል።
በመድረኩ ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አቤኔዘር ለገሰ በበኩል ዝማሬ በማቅረብ አገልግለዋል።
የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን መረሃ ግብሩን ተከታትለን ዝርዝሩን ወደ እናንተ አቀረብንላችሁ።
በዮሐንስ ግርማ
በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ፕሬዝደንት በዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ የተፃፈዉ እና በ2 ክፍሎች እና በ4 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ200 ገፆች የተዋቀረዉ መፅሐፍ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፣ የፀሐፊዉ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላዉ እንግዶች በተገኙበት በዘፀዓት አፖስቶሊክ ሪፎርሜሽን ቤተክርስቲያን በድምቀት ተመርቋል።
በመድረኩ ዶ/ር ወርቁ የመፅሐፉን ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን በንግግራቸው ዶ/ር ጣሰው መሪነት በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን መጠቀሱን አንስተዉ ባለአደራነት ፤ ጥበብ እና የእግዚአብሔር ቃል የጎደለዉ መሪ ለተቋማት መውደቅ ለአመራት ክፍተት እንደሚፈጠር በመጥቀስ ይሞግታሉ ሲል አንስቷል።
ፖስተር ፃዲቁ አብዱ በበኩላቸው በመሪነት ደረጃ ላሉት ብቻ ሳይሆን ወደ መሪነት ለማደግ ለሚሄዱትም ጠቃሚ የሆነ መጽሀፍ በመሆኑ ሁሉም ሊያነቡት እንደሚገባ መክርዋል።
የመጽሀፊ አዘጋጅ ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ መፅሐፍ ቅዱሳችን እራሱ መሪነትን በየአዉዱ በመከፋፈል የሚያስቀምጥ መሆኑን በመጥቀስ ለአንድ መሪ ባሕሪ መሰራት እና የመሪዎች የበሃሪ ተግዳሮት መስተዋሉ ይህንንም ችግር ለመቀነስ የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ለማበርከት መጽሀፉን እንዳዘጋጁት ተናግረዋል።
ዶ/ር ጣሰዉ ገብሬ ይህ 3ኛ መፅሐፋቸዉ ሲሆን ከዚህ ቀደም "የመሪ ፈተናዎች ፤ስህተቶች እና መፍትሄዎቹ" እንዲሁም "ክዋኔ የትግበራ ክህሎት" የተሰኙ ሁለት መፅሐፍትን በ2013 ዓ.ም ለንባብ ማብቃታቸዉ ይታወሳል።
በመድረኩ ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤል የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አቤኔዘር ለገሰ በበኩል ዝማሬ በማቅረብ አገልግለዋል።
የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን መረሃ ግብሩን ተከታትለን ዝርዝሩን ወደ እናንተ አቀረብንላችሁ።
በዮሐንስ ግርማ
❤5👍1👏1
19 ነብሳት #ወደ #ጌታ መንግስት ተጨምረዋል።
#በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ምዕራብ ደቡብ ቀጣና ቦንጋ ዙሪያ ሕብረት በቦባ ገጫ ቃ/ሕ/ቤ/ያን #እና ከሁለቱ ተከላ ጣቢያ በጌታ አምኖ የደህንነት ትምህርት እየተማሩ የቆዩ የውሃ ጥምቀት ወስዷል።
#በክርስቶስ #ኢየሱስ አምኖ በቤተክርስቲያን የሚሰጠውን የደህንነት ትምህርት በመማር #በቁጥር 19 የሚሆኑ ሰዎች የውሃ ጥምቀት ስነ-ስርዓት ወስዷል።
መረጃውን ከስፍራው The Christian News - የክርስቲያን ዜና አደረሱን!!!
#በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ምዕራብ ደቡብ ቀጣና ቦንጋ ዙሪያ ሕብረት በቦባ ገጫ ቃ/ሕ/ቤ/ያን #እና ከሁለቱ ተከላ ጣቢያ በጌታ አምኖ የደህንነት ትምህርት እየተማሩ የቆዩ የውሃ ጥምቀት ወስዷል።
#በክርስቶስ #ኢየሱስ አምኖ በቤተክርስቲያን የሚሰጠውን የደህንነት ትምህርት በመማር #በቁጥር 19 የሚሆኑ ሰዎች የውሃ ጥምቀት ስነ-ስርዓት ወስዷል።
መረጃውን ከስፍራው The Christian News - የክርስቲያን ዜና አደረሱን!!!
❤13👍1👏1
#አሳዛኝ #ዜና 😭😭 #ወደ #ጌታ ሄደች።
ዘማሪት የምስራች ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወደ ጌታ ሄዳለች።
እህታችን የምስራች ጨጓራዋ አከባቢ ከነበረው 4ኛ ደረጃ ካንሰር በተዓምራት ተፈውሳ እግዚአብሔርን እያመሰገንን መቆየታችን ይታወሳል ከጊዜያት በኋላ ቼካፕ ስታደርግ ጀርባዋ አከባቢ ሶስተኛው አጥንት ላይ እና ሳንባዋ ላይ ካንሰር ከባድ ሳል ታክሎበት በፍጥነት ፅኑ ሕሙማን ክፍል እንድትገባ የተደረገች ቢሆንም ከደቂቃዎች በፊት ወደ ጌታ መሄዷ ታዉቋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና እግዚአብሔር ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ መፅናናትን እንዲያደርግ እንመኛለን።
ዘማሪት የምስራች ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወደ ጌታ ሄዳለች።
እህታችን የምስራች ጨጓራዋ አከባቢ ከነበረው 4ኛ ደረጃ ካንሰር በተዓምራት ተፈውሳ እግዚአብሔርን እያመሰገንን መቆየታችን ይታወሳል ከጊዜያት በኋላ ቼካፕ ስታደርግ ጀርባዋ አከባቢ ሶስተኛው አጥንት ላይ እና ሳንባዋ ላይ ካንሰር ከባድ ሳል ታክሎበት በፍጥነት ፅኑ ሕሙማን ክፍል እንድትገባ የተደረገች ቢሆንም ከደቂቃዎች በፊት ወደ ጌታ መሄዷ ታዉቋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና እግዚአብሔር ለቤተሰቦቿ፣ ለወዳጅ ዘመዶቿ መፅናናትን እንዲያደርግ እንመኛለን።
😭38💔12🕊1
ለመጋቢ እና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ እውቅና ተሰጣቸው።
እውቅና የሰጣቸው ተቋም የኢቫንጄሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ ሲሆን "አዎን ይሆናል" በሚል በሁለት ቋንቋዎች የተዘጋጀው የመዝሙር ስንዱቅ መጽሐፍ በተመረቀበት ወቅት ነው።
በቀድሞ የወንጌላውያን ቴዎሎጂ ኮሌጅ ተማሪ በሆነው አቶ ጥበበ አክሊል የተዘጋጀው የፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶ ቁጥር 8 የመዝሙር ስንዱቅ መጽሀፍ በትላንትናው እለት በETC ተመርቋል።
በመድረኩ ይህንን መጽሐፉ ማዘጋጀት ያስፈለገበት አላማ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት አገልጋዮች ዘንድ ያለውን መንፈሳዊ ምልከታ፣ አስተምህሮና አቋም ማጥናት ለሚፈልጉ የውጪ ዜግነት ያላቸው የስነ መለኮት ተመራማሪዎች ጥቅም ላይ እንዲወል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በትርጉም ስራው ላይም ፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶን ጨምሮ 4 የተለያዩ ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን አቶ ጥበበ አክሊሉ በስንዱቅ 8 የተዘመሩ 13 መዝሙሮችን በእንግሊዘኛ እና ፈረንሳይኛ በመተርጎም ለአንባብያን አቅርበዋል።
ወንድም ጥበበ አክለዉ ላለፉት 35 ዓመታት በመዝሙሮቹ ብዙ ሰለተባረኩባቸው የሌላ ሀገር ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑ ሰዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በፈረንሳይኛና በእንግሊዝኛ ለመተርጎም ጥረት ማድረጋቸዉን አንስተዉ የተተረጎሙት መዝሙሮች በሌላ ቋንቋ መዘመር ሊያሰቸግር ይቻላል ግን የመዝሙሮቹን መልዕክቶች በማጥናት አትራፊ መሆን እንደሚችል ገልጸዋል።
መጋቢ ተስፋዬ በበኩላችው መንፈሳዊ ዝማሬ ፣በአምልኮ ፣በወንጌል ሥርጭት አማኞችን በማስተማር ረገድ የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው በሀገራችን የተዘመሩ መዝሙሮች መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሥነ-መለኮታዊ ይዘት ካሰተዋሉ በኋላ በዜማ እንኳን ቢቀር ቃላቱ በወጪ ሀገር ቋንቋ ቢተረጎም ለአንባቢያን እንዳች መልዕክት ሊያስተላልፋ ይችላል ብለዋል።
መፅሐፍ ለETC ሙሉ በሙሉ ተሰጥቷል።
በቤተልሔም ደረጀ
እውቅና የሰጣቸው ተቋም የኢቫንጄሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ ሲሆን "አዎን ይሆናል" በሚል በሁለት ቋንቋዎች የተዘጋጀው የመዝሙር ስንዱቅ መጽሐፍ በተመረቀበት ወቅት ነው።
በቀድሞ የወንጌላውያን ቴዎሎጂ ኮሌጅ ተማሪ በሆነው አቶ ጥበበ አክሊል የተዘጋጀው የፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶ ቁጥር 8 የመዝሙር ስንዱቅ መጽሀፍ በትላንትናው እለት በETC ተመርቋል።
በመድረኩ ይህንን መጽሐፉ ማዘጋጀት ያስፈለገበት አላማ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት አገልጋዮች ዘንድ ያለውን መንፈሳዊ ምልከታ፣ አስተምህሮና አቋም ማጥናት ለሚፈልጉ የውጪ ዜግነት ያላቸው የስነ መለኮት ተመራማሪዎች ጥቅም ላይ እንዲወል ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በትርጉም ስራው ላይም ፓስተር ተስፋዬ ጋቢሶን ጨምሮ 4 የተለያዩ ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን አቶ ጥበበ አክሊሉ በስንዱቅ 8 የተዘመሩ 13 መዝሙሮችን በእንግሊዘኛ እና ፈረንሳይኛ በመተርጎም ለአንባብያን አቅርበዋል።
ወንድም ጥበበ አክለዉ ላለፉት 35 ዓመታት በመዝሙሮቹ ብዙ ሰለተባረኩባቸው የሌላ ሀገር ቋንቋ ተናጋሪ የሆኑ ሰዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በፈረንሳይኛና በእንግሊዝኛ ለመተርጎም ጥረት ማድረጋቸዉን አንስተዉ የተተረጎሙት መዝሙሮች በሌላ ቋንቋ መዘመር ሊያሰቸግር ይቻላል ግን የመዝሙሮቹን መልዕክቶች በማጥናት አትራፊ መሆን እንደሚችል ገልጸዋል።
መጋቢ ተስፋዬ በበኩላችው መንፈሳዊ ዝማሬ ፣በአምልኮ ፣በወንጌል ሥርጭት አማኞችን በማስተማር ረገድ የራሱ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው በሀገራችን የተዘመሩ መዝሙሮች መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሥነ-መለኮታዊ ይዘት ካሰተዋሉ በኋላ በዜማ እንኳን ቢቀር ቃላቱ በወጪ ሀገር ቋንቋ ቢተረጎም ለአንባቢያን እንዳች መልዕክት ሊያስተላልፋ ይችላል ብለዋል።
መፅሐፍ ለETC ሙሉ በሙሉ ተሰጥቷል።
በቤተልሔም ደረጀ
❤24👍8🥰2🔥1👏1
💍✨ የመጨረሻው ዝግጅት : የአጮኝነት ስልጠና✨💍
🔹ውስን ስፍራ፦ ለ20 ጥንዶች ብቻ!
ለምዝገባ የቀረን 3 #ቀን ብቻ ነው
ፈጥናችሁ ተመዝገቡ!
በቃልኪዳን የጋብቻን ጉዞ ከመጀመራችሁ ፊት በቂ ቅድመ-ዝግጅት ማድረግ ብልህነት ነው። "የመጨረሻውን ዝግጅት " ለማድረግ በዚህ የእጮኛሞች ስልጠና ተሳተፉ እና ለዘላቂና ጣፋጭ ትዳር መሰረት ለመጣል የሚረዷችሁን ግብዓቶች ሸምቱ።
📅 ቀን፦ግንቦት 30/June 7
📍 ቦታ፦ አለም ጋለሪ ገርጂ ታክሲ ተራ
💰 መመዝገቢያ Fee፦ለጥንዶች 1200፣ ለአንድ ሰዉ 650ብር ብቻ!
በነገ ህይወታችሁ ላይ ዛሬ ለመዝራት ቦታ ሳያልቅባችሁ ተመዝገቡ!
ወዳጅ ቤተሰብ! ስፖንሰር በማድረግ ለሠርጋቸው ስጦታ በመስጠት ለነገ ህይወታቸው የየድርሻችሁን ተወጡ።
አገልጋዮች ፦
👉ጌቱና ማህደር፦ የሰማይ ፋሚሊ አዘጋጆች
https://www.youtube.com/watch?v=Y6CushnHTrg
👉ሳሮን ውድነህ፦ የጋብቻ አስተማሪ እና አማካሪ
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
ለመመዝገብ፦https://forms.gle/EKtmd52XMHF1612CA
ለበለጠ መረጃ፦ 0911136520/0911642595
🔹ውስን ስፍራ፦ ለ20 ጥንዶች ብቻ!
ለምዝገባ የቀረን 3 #ቀን ብቻ ነው
ፈጥናችሁ ተመዝገቡ!
በቃልኪዳን የጋብቻን ጉዞ ከመጀመራችሁ ፊት በቂ ቅድመ-ዝግጅት ማድረግ ብልህነት ነው። "የመጨረሻውን ዝግጅት " ለማድረግ በዚህ የእጮኛሞች ስልጠና ተሳተፉ እና ለዘላቂና ጣፋጭ ትዳር መሰረት ለመጣል የሚረዷችሁን ግብዓቶች ሸምቱ።
📅 ቀን፦ግንቦት 30/June 7
📍 ቦታ፦ አለም ጋለሪ ገርጂ ታክሲ ተራ
💰 መመዝገቢያ Fee፦ለጥንዶች 1200፣ ለአንድ ሰዉ 650ብር ብቻ!
በነገ ህይወታችሁ ላይ ዛሬ ለመዝራት ቦታ ሳያልቅባችሁ ተመዝገቡ!
ወዳጅ ቤተሰብ! ስፖንሰር በማድረግ ለሠርጋቸው ስጦታ በመስጠት ለነገ ህይወታቸው የየድርሻችሁን ተወጡ።
አገልጋዮች ፦
👉ጌቱና ማህደር፦ የሰማይ ፋሚሊ አዘጋጆች
https://www.youtube.com/watch?v=Y6CushnHTrg
👉ሳሮን ውድነህ፦ የጋብቻ አስተማሪ እና አማካሪ
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
ለመመዝገብ፦https://forms.gle/EKtmd52XMHF1612CA
ለበለጠ መረጃ፦ 0911136520/0911642595
❤6👏1
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በበርሊን ለተሰበሰቡ ወንጌላዊያን መሪዎች ያስተላለፉት መልዕክት ምንድነው?
“አዲስ አለም አቀፍ ተልዕኮ” ያስፈልጋል ሲሉ ነው በበርሊን በተካሄደው የ2025 ወንጌላዊያን ኮንግረስ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላልፉት።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ወንጌል ከግል ጉዳይ ይበልጣል፣ ማህበረሰብን የመቀየር አቅም አለው” ብለዋል።
ጥልቅ የመንፈሳዊ መታደስ ላይ ትኩረት ባደረገው አዲስ ተልዕኮ ባሉት እቅድ መሰረት “ዘላቂ ለውጥ ከውስጥ ይጀምራል” ብለዋል።
“ከዘር፣ ከሃይማኖት ትምህርት እና ሌሎች መከፋፈሎች ባለፈ በፍቅር፣ በመተሳሰብ እና በመመለስ” ፍቅርን እንቀበል ሲሉ ለአውሮፓዊያኑ ወንጌላዊያን መሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሙሉውን ፌስቡክ ላይ ያንብቡት
👇👇👇
https://www.facebook.com/100063892396728/posts/pfbid0V4hHKCAwLMPQ5on67caZwTLUgTBN6MQbWm17PVdSZPcKFoy4rKriYnKwwLUASb3El/?app=fbl
“አዲስ አለም አቀፍ ተልዕኮ” ያስፈልጋል ሲሉ ነው በበርሊን በተካሄደው የ2025 ወንጌላዊያን ኮንግረስ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላልፉት።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ወንጌል ከግል ጉዳይ ይበልጣል፣ ማህበረሰብን የመቀየር አቅም አለው” ብለዋል።
ጥልቅ የመንፈሳዊ መታደስ ላይ ትኩረት ባደረገው አዲስ ተልዕኮ ባሉት እቅድ መሰረት “ዘላቂ ለውጥ ከውስጥ ይጀምራል” ብለዋል።
“ከዘር፣ ከሃይማኖት ትምህርት እና ሌሎች መከፋፈሎች ባለፈ በፍቅር፣ በመተሳሰብ እና በመመለስ” ፍቅርን እንቀበል ሲሉ ለአውሮፓዊያኑ ወንጌላዊያን መሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።
ሙሉውን ፌስቡክ ላይ ያንብቡት
👇👇👇
https://www.facebook.com/100063892396728/posts/pfbid0V4hHKCAwLMPQ5on67caZwTLUgTBN6MQbWm17PVdSZPcKFoy4rKriYnKwwLUASb3El/?app=fbl
👍11🔥6🤷♂4❤4🥰2🙏1
💍✨ የመጨረሻው ዝግጅት : የአጮኝነት ስልጠና✨💍
🔹ቀድመው ለደውሉልን 5 ጥንዶች በነፃ ስፖንሰር እናደርጋለን!
ለምዝገባ የቀረን 1 ቀን ብቻ ነው
ፈጥናችሁ ተመዝገቡ!
በቃልኪዳን የጋብቻን ጉዞ ከመጀመራችሁ ፊት በቂ ቅድመ-ዝግጅት ማድረግ ብልህነት ነው። "የመጨረሻውን ዝግጅት " ለማድረግ በዚህ የእጮኛሞች ስልጠና ተሳተፉ እና ለዘላቂና ጣፋጭ ትዳር መሰረት ለመጣል የሚረዷችሁን ግብዓቶች ሸምቱ።
📅 ቀን፦ግንቦት 30/June 7
📍 ቦታ፦ አለም ጋለሪ ገርጂ ታክሲ ተራ
💰 መመዝገቢያ Fee፦ለጥንዶች 1200፣ ለአንድ ሰዉ 650ብር ብቻ!
በነገ ህይወታችሁ ላይ ዛሬ ለመዝራት ቦታ ሳያልቅባችሁ ተመዝገቡ!
ወዳጅ ቤተሰብ! ስፖንሰር በማድረግ ለሠርጋቸው ስጦታ በመስጠት ለነገ ህይወታቸው የየድርሻችሁን ተወጡ።
አገልጋዮች ፦
👉ጌቱና ማህደር፦ የሰማይ ፋሚሊ አዘጋጆች
https://www.youtube.com/watch?v=Y6CushnHTrg
👉ሳሮን ውድነህ፦ የጋብቻ አስተማሪ እና አማካሪ
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
ለመመዝገብ፦https://forms.gle/EKtmd52XMHF1612CA
ለበለጠ መረጃ፦ 0911136520/0911642595
🔹ቀድመው ለደውሉልን 5 ጥንዶች በነፃ ስፖንሰር እናደርጋለን!
ለምዝገባ የቀረን 1 ቀን ብቻ ነው
ፈጥናችሁ ተመዝገቡ!
በቃልኪዳን የጋብቻን ጉዞ ከመጀመራችሁ ፊት በቂ ቅድመ-ዝግጅት ማድረግ ብልህነት ነው። "የመጨረሻውን ዝግጅት " ለማድረግ በዚህ የእጮኛሞች ስልጠና ተሳተፉ እና ለዘላቂና ጣፋጭ ትዳር መሰረት ለመጣል የሚረዷችሁን ግብዓቶች ሸምቱ።
📅 ቀን፦ግንቦት 30/June 7
📍 ቦታ፦ አለም ጋለሪ ገርጂ ታክሲ ተራ
💰 መመዝገቢያ Fee፦ለጥንዶች 1200፣ ለአንድ ሰዉ 650ብር ብቻ!
በነገ ህይወታችሁ ላይ ዛሬ ለመዝራት ቦታ ሳያልቅባችሁ ተመዝገቡ!
ወዳጅ ቤተሰብ! ስፖንሰር በማድረግ ለሠርጋቸው ስጦታ በመስጠት ለነገ ህይወታቸው የየድርሻችሁን ተወጡ።
አገልጋዮች ፦
👉ጌቱና ማህደር፦ የሰማይ ፋሚሊ አዘጋጆች
https://www.youtube.com/watch?v=Y6CushnHTrg
👉ሳሮን ውድነህ፦ የጋብቻ አስተማሪ እና አማካሪ
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk
ለመመዝገብ፦https://forms.gle/EKtmd52XMHF1612CA
ለበለጠ መረጃ፦ 0911136520/0911642595
❤3👍1
በቀል በቀለኛውን ያጠፋል።
የኤዶም የበቀል ታሪክ አሁን እንደ ሀገር እና እንደ ማህበረሰብ እንዲሁም እንደቤተክርስቲያን ለገባንበት ቀውስ መውጫ አቅጣጫ የሚያመለክት ነው።
ትንቢተ አብድዩ ላይ ትኩረት ያደረገ ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ላለፊት 17 ዓመታት ያስተማሩት እና የሰበኩትም ታሪክ በመጽሐፍ መልክ ተሰንዶ መጣ።
"በቀል በቀለኛዉን ያጠፋዋል" ድንቅ መጽሀፍ በአድዋ መታሰቢያ ሙዝየም እንደሚመረቅ ታውቋል። ዛሬ 8:00 ሰዓት ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ሲሆን ዝርዝር መረጃውን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
የኤዶም የበቀል ታሪክ አሁን እንደ ሀገር እና እንደ ማህበረሰብ እንዲሁም እንደቤተክርስቲያን ለገባንበት ቀውስ መውጫ አቅጣጫ የሚያመለክት ነው።
ትንቢተ አብድዩ ላይ ትኩረት ያደረገ ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ላለፊት 17 ዓመታት ያስተማሩት እና የሰበኩትም ታሪክ በመጽሐፍ መልክ ተሰንዶ መጣ።
"በቀል በቀለኛዉን ያጠፋዋል" ድንቅ መጽሀፍ በአድዋ መታሰቢያ ሙዝየም እንደሚመረቅ ታውቋል። ዛሬ 8:00 ሰዓት ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ሲሆን ዝርዝር መረጃውን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
👍6❤3🔥1
#የእግዚአብሔር ክብር የኪዳኑ ታቦት" የሚል መጠሪያ ያለው እና በሐዋሪያው ዳንኤል መኮንን የተጻፈው መጽሐፍ ሊመረቅ ነው።
ሰኔ 2 2017ዓ.ም በአድዋ ሙዚየም የሚመረቀውን መጽሐፍ አስመልክቶ በዛሬው እለት ለክርስቲያን ሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል።
በመግለጫው በ10 ምዕራፍ እና በ310 ገጾች የተዋቀረው #ይህ መጽሐፍ ሰኔ 2 ሰኞ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በ11:00 ሰዓት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች እና ጥሪ የሚደረግላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።
ሐዋሪያው ዳንኤል #በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ባለፉት 55 የአገልግሎት አመታት በኦሎምፒያ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጨምሮ ፤ በጅማ ፤ በአሜሪካ እና አውሮፓ የአገልግሎት ዘመናቸው ያሳለፉት በመጽሃፉ ውስጥ በማካተት የህይወት ተሞክሮ እና ምስክርነትን በማጣመር የተዘጋጀ እንደሆነ በመግለጫው ተጠቅሷል።
#ክርስቲያን ከክብር ጋር እንዲገናኝ፤ በእግዚአብሔር ክብር ውስጥ እንዲገኝ እና ናፍቆት እንዲኖረው የተጻፈ እንደሆነም የተገለጸ ሲሆን አዲሱ ትውልድ የእግዚአብሔርን ክብር ናፍቆት መሙላት ላይ የተፈለገው ተጽዕኖ እንዲያሳርፍ የተዘጋጀ እንደሆነ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ #ሙሉ በሙሉ የሽያጩ ገቢው ለአዋሬ ወንጌል ብርሃን አ/አቀፍ ቤ/ክ ግንባታ እንደሚውልም ተገልጿል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን አቀረብንላቹ ተጨማሪ የቪዲዬ ዘገባ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
ግንቦት 28/2017 ዓ.ም
በኦቦሌሳ አዶላ
ሰኔ 2 2017ዓ.ም በአድዋ ሙዚየም የሚመረቀውን መጽሐፍ አስመልክቶ በዛሬው እለት ለክርስቲያን ሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል።
በመግለጫው በ10 ምዕራፍ እና በ310 ገጾች የተዋቀረው #ይህ መጽሐፍ ሰኔ 2 ሰኞ አድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በ11:00 ሰዓት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች እና ጥሪ የሚደረግላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።
ሐዋሪያው ዳንኤል #በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ባለፉት 55 የአገልግሎት አመታት በኦሎምፒያ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጨምሮ ፤ በጅማ ፤ በአሜሪካ እና አውሮፓ የአገልግሎት ዘመናቸው ያሳለፉት በመጽሃፉ ውስጥ በማካተት የህይወት ተሞክሮ እና ምስክርነትን በማጣመር የተዘጋጀ እንደሆነ በመግለጫው ተጠቅሷል።
#ክርስቲያን ከክብር ጋር እንዲገናኝ፤ በእግዚአብሔር ክብር ውስጥ እንዲገኝ እና ናፍቆት እንዲኖረው የተጻፈ እንደሆነም የተገለጸ ሲሆን አዲሱ ትውልድ የእግዚአብሔርን ክብር ናፍቆት መሙላት ላይ የተፈለገው ተጽዕኖ እንዲያሳርፍ የተዘጋጀ እንደሆነ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ #ሙሉ በሙሉ የሽያጩ ገቢው ለአዋሬ ወንጌል ብርሃን አ/አቀፍ ቤ/ክ ግንባታ እንደሚውልም ተገልጿል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን አቀረብንላቹ ተጨማሪ የቪዲዬ ዘገባ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
ግንቦት 28/2017 ዓ.ም
በኦቦሌሳ አዶላ
❤5👍2🔥2🙏1
የኢትዮጵያ ወጣት ክርስቲያን ማህበር አርቲስት ሸዋፈራው ደሳለኝን የክብር አምባሳደር አድርጎ መረጠ።
አርቲስት ሽዋፈራሁ ደሳለኝ እንዲህ አይነት ወጣቶች ላይ የሚሰራ እና ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ከፍተኛ ፍሬ በማምጣት በጎ ተፅእኖ በመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ካለ ተቋም ጋር በመስራቴ እኔም እድለኛ ነኝ ብሏል።
የአምባሳደርነት ስምምነቱ ለ2 አመት ይቆያል።
የኢትዬጲያ ወጣት ክርስቲያ ማህበር /E.Y.C.A 21ኛ ዓመት የወጣቶች ምስጋና በዓል ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ" በሚል መሪ ቃል ሃምሌ 5 ቀን 2017 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት መሆኑን በመግለጫዉ ተጠቅሷል።
ከ450 ተማሪዎች በላይ የሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ኮሌጆችና የሞያ ተቋማት እንዲያገኙ መደረጉ የተጠቀሰ ሲሆን በተለያዩ ማረሚያ ቤቶችና ዩኒቨርስቲዎች በመንቀሳቀስ ማህበራዊ ግዴታውን ሲወጣ ቆይቷል።
በመግለጫዉ በሃምሌ 5 በሚሊኒየም አዳራሽ፡ 2025 ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ'' በሚል መሪ ቃል ታላቅ የምስጋና በዓል እና የወንጌል መልዕክት ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተነግሯል።
አርቲስት ሸዋፈራሁ ይህ ጉዳይ የሁሉም ሰው በመሆኑ በከፍተኛ ችግር ያለውን ህዝባችንን መርዳት እና ትውልዳችንን በወንጌል መታደግ ስራ ላይ ነፃ አገልግሎት በመስጠት ሁሉም ባለው ነገርና አቅም ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት እንደሆነ ተነስቷል።
አርቲስት ሽዋፈራሁ ደሳለኝ እንዲህ አይነት ወጣቶች ላይ የሚሰራ እና ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ከፍተኛ ፍሬ በማምጣት በጎ ተፅእኖ በመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ካለ ተቋም ጋር በመስራቴ እኔም እድለኛ ነኝ ብሏል።
የአምባሳደርነት ስምምነቱ ለ2 አመት ይቆያል።
የኢትዬጲያ ወጣት ክርስቲያ ማህበር /E.Y.C.A 21ኛ ዓመት የወጣቶች ምስጋና በዓል ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ" በሚል መሪ ቃል ሃምሌ 5 ቀን 2017 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት መሆኑን በመግለጫዉ ተጠቅሷል።
ከ450 ተማሪዎች በላይ የሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ኮሌጆችና የሞያ ተቋማት እንዲያገኙ መደረጉ የተጠቀሰ ሲሆን በተለያዩ ማረሚያ ቤቶችና ዩኒቨርስቲዎች በመንቀሳቀስ ማህበራዊ ግዴታውን ሲወጣ ቆይቷል።
በመግለጫዉ በሃምሌ 5 በሚሊኒየም አዳራሽ፡ 2025 ''ታሪክ ሰሪ ትውልድ'' በሚል መሪ ቃል ታላቅ የምስጋና በዓል እና የወንጌል መልዕክት ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተነግሯል።
አርቲስት ሸዋፈራሁ ይህ ጉዳይ የሁሉም ሰው በመሆኑ በከፍተኛ ችግር ያለውን ህዝባችንን መርዳት እና ትውልዳችንን በወንጌል መታደግ ስራ ላይ ነፃ አገልግሎት በመስጠት ሁሉም ባለው ነገርና አቅም ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
ማህበሩ ያለፉትን 20 ዓመታት ወጣቱን ማዕከል ያደረገ ከፍተኛ መንፈሳዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ለብዙ ነፍሳቶች በክርስቶስ አምነው መዳን ምክንያት እንደሆነ ተነስቷል።
❤5👍1
"በቀል በቀለኛውን ያጠፋዋል" - ፓስተር ጻድቁ አብዶ
መጽሃፉ፡ የበኩር መጽሃፋቸው ሲሆን፡ መነሻ ያደረገው በመድረክ ላይ ያስተምሩ ከነበረው የትንቢተ አብድዩ መጽሃፍ የተወሰደ ነው። በቅርብ ወዳጆች ጥያቄ መሰረት በመጽሃፍነት እንዲቀመጥ ተጠይቀው እነሆ ለህትመት በቅቷል።
"መንታ ወንድማማች ስር በሰደደ ጸብ ምክኒያት አንዱ ሞተ፡ አንዱ ተሰደደ። በትውልዳቸው ጥላቻ ስር ሰደደ። ኤዶማዊያን እና እስራኤላዊያን፡ ኤሳው እና ያዕቆብ። በቂም ምክኒያት ኤዶማዊያን ዛሬ የሉም፡ እስራኤላዊያን ስር ሰደዋል።
ከዚህ ታሪክ፡ ይቅርታ እና ምህረትን እንድናደርግ መጽሃፉ ይሞግታል። የቂም እና ክፋት መንገድ ወደ ጥፋት ያደርሰናል። መጽሃፉ በእግዜብሔር ቃል ከክፋት ወደ ቀናነት እንድንመለስ የሚያስተምር ነው።
መጽሃፉ ለአብያተ ክራቲያናት፡ በቀል ይቅር የተባለ ሰው ባህሪ አይደለም። አማኞች በምህረት ያለን ነን። ስለዚህ በቀል ከክርስቲያናዊ አኗኗር ትውቃራኒ ያለ ነው። ይቅር አለማለት እራስን መውደድ እና ጨካኛነት ነው። ከአዙሪት እንዴት እንውጣ፡ የሚል መልስ ይዟል።
መጽሃፉ ሃገራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮቻችንን እንድንቃኝ ያበረታታል። በ150 ገጾች የተዋቀረ ነው።
እሁድ ሰኔ 8፡ 2017 ዓ.ም አድዋ መታሰቢያ አዳራሽ ይመረቃል። በእለቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፡ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት ይመረቃል። ክርስቲያኖች በስፍራው ተገኝተው አብረው እንዲመርቁ ጥሪ ቀርቧል።
በመግለጫው ስለ ርዕሱ ያብራሩት ጸሃፊው "በነብዩ አሞጽ እንደተነገረ፡ በባቢሎን ግዞት ዘመን እስራኤላዊያን በኤዶማዊያን ለመጥፋት ተቃርበው የነበረ ቢሆንም፡ በነብዩ አብድዩ አፍ ደግሞ እንዴት እንደጠፉ ያሳያል።" ብለዋል።
የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን ወደ እናንተ አደረስንላችሁ።
ግንቦት 28/2017ዓ.ም
በኦቦሌሳ አዶላ
መጽሃፉ፡ የበኩር መጽሃፋቸው ሲሆን፡ መነሻ ያደረገው በመድረክ ላይ ያስተምሩ ከነበረው የትንቢተ አብድዩ መጽሃፍ የተወሰደ ነው። በቅርብ ወዳጆች ጥያቄ መሰረት በመጽሃፍነት እንዲቀመጥ ተጠይቀው እነሆ ለህትመት በቅቷል።
"መንታ ወንድማማች ስር በሰደደ ጸብ ምክኒያት አንዱ ሞተ፡ አንዱ ተሰደደ። በትውልዳቸው ጥላቻ ስር ሰደደ። ኤዶማዊያን እና እስራኤላዊያን፡ ኤሳው እና ያዕቆብ። በቂም ምክኒያት ኤዶማዊያን ዛሬ የሉም፡ እስራኤላዊያን ስር ሰደዋል።
ከዚህ ታሪክ፡ ይቅርታ እና ምህረትን እንድናደርግ መጽሃፉ ይሞግታል። የቂም እና ክፋት መንገድ ወደ ጥፋት ያደርሰናል። መጽሃፉ በእግዜብሔር ቃል ከክፋት ወደ ቀናነት እንድንመለስ የሚያስተምር ነው።
መጽሃፉ ለአብያተ ክራቲያናት፡ በቀል ይቅር የተባለ ሰው ባህሪ አይደለም። አማኞች በምህረት ያለን ነን። ስለዚህ በቀል ከክርስቲያናዊ አኗኗር ትውቃራኒ ያለ ነው። ይቅር አለማለት እራስን መውደድ እና ጨካኛነት ነው። ከአዙሪት እንዴት እንውጣ፡ የሚል መልስ ይዟል።
መጽሃፉ ሃገራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮቻችንን እንድንቃኝ ያበረታታል። በ150 ገጾች የተዋቀረ ነው።
እሁድ ሰኔ 8፡ 2017 ዓ.ም አድዋ መታሰቢያ አዳራሽ ይመረቃል። በእለቱ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፡ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች በተገኙበት ይመረቃል። ክርስቲያኖች በስፍራው ተገኝተው አብረው እንዲመርቁ ጥሪ ቀርቧል።
በመግለጫው ስለ ርዕሱ ያብራሩት ጸሃፊው "በነብዩ አሞጽ እንደተነገረ፡ በባቢሎን ግዞት ዘመን እስራኤላዊያን በኤዶማዊያን ለመጥፋት ተቃርበው የነበረ ቢሆንም፡ በነብዩ አብድዩ አፍ ደግሞ እንዴት እንደጠፉ ያሳያል።" ብለዋል።
የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን ወደ እናንተ አደረስንላችሁ።
ግንቦት 28/2017ዓ.ም
በኦቦሌሳ አዶላ
❤9👍1🔥1
ቤተክርስቲያን ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥታ መስራት አለባት ተባለ።
ይህ የተባለዉ የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የባለ ትዳሮች ቃል ኪዳን ማደስ ፕሮግራም ባደረገችበት ወቅት ነዉ።
መርሃ ግብሩ ላይ የአጥቢያ ቤተክርሲያኒቱ መስራች አባላት፣ አገልጋዮችና መሪዎች የነበሩት አቶ ማሞ ገ/መስቀል ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል፣ ወንጌላዊት ቀለሟ ሃይሌ፣ የወቅቱ የአጥቢያ መሪዎች፣ አገልጋዮች እና ባለትዳሮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር ተገኝተዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ የጋብቻ ማማከር አገልግሎት ለባለትዳሮችና ላልተጋቡ ወጣቶች ሥልጠናዎችን በመስጠት ተግታ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየ እንደሆነ የገለጹት የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና የመርሃ ግብሩ ታዳሚያን ቤተክርስቲያን ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥታ መስራት እንዳለባት አሳስበዋል።
የቃል ኪዳን ማደስ ሥነ-ሥርዓቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና መጋቢ የሆኑት መጋቢ ተስፋዬ ገመቹ “እግዚአብሄር ሁል ጊዜ ኪዳኑን ያስባል፤ ከሕዝቡ ጋር ያለውም ትስስርም ከኪዳኑ ግንኙነት የሚመነጭ ነው” በማለት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ መዓዛ መኩሪያ ጋር በመሆን ስርዓቱን መርተዋል።
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ከ65 አመታት በላይ በትዳር የቆዩ ጥንዶች እና በቅርቡ የተጋቡ አዳዲስ ሙሽሮች ኬክ ቆረሳ ያደረጉ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የአንድነት ጌዜ እንደነበራቸው ታውቋል፡፡
የቤተክርሲቲያኒቱ ሰብሳቢ የሆኑት ፕሮፌስር ብርሃኑ ቆጢሶ ሕዝቡን በፀሎት የባረኩ ሲሆን ዘማሪት ሃና ተክሌና ዘማሪ አድነው ዓለሙ በዝማሬ አገልግለዋል።
ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል በበለጠ ተስፋ፣ በበለጠ እምነትና በአንድነት በመያያዝ እግዚአብሄርን በታመነ ሕይወት ለመኖር ልትበረታቱ ያስፈልጋል በማለት የእግዚአብሄር ቃል መልዕክት አካፍለዋል።
በሮማን ከሊል
ይህ የተባለዉ የጌጃ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የባለ ትዳሮች ቃል ኪዳን ማደስ ፕሮግራም ባደረገችበት ወቅት ነዉ።
መርሃ ግብሩ ላይ የአጥቢያ ቤተክርሲያኒቱ መስራች አባላት፣ አገልጋዮችና መሪዎች የነበሩት አቶ ማሞ ገ/መስቀል ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል፣ ወንጌላዊት ቀለሟ ሃይሌ፣ የወቅቱ የአጥቢያ መሪዎች፣ አገልጋዮች እና ባለትዳሮች ከትዳር አጋሮቻቸው ጋር ተገኝተዋል።
የቤተክርስቲያኒቱ የጋብቻ ማማከር አገልግሎት ለባለትዳሮችና ላልተጋቡ ወጣቶች ሥልጠናዎችን በመስጠት ተግታ እየሰራ እንደሆነ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ ለረጅም ጊዜ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየ እንደሆነ የገለጹት የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና የመርሃ ግብሩ ታዳሚያን ቤተክርስቲያን ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሰጥታ መስራት እንዳለባት አሳስበዋል።
የቃል ኪዳን ማደስ ሥነ-ሥርዓቱን የቤተ ክርስቲያኒቱ ዋና መጋቢ የሆኑት መጋቢ ተስፋዬ ገመቹ “እግዚአብሄር ሁል ጊዜ ኪዳኑን ያስባል፤ ከሕዝቡ ጋር ያለውም ትስስርም ከኪዳኑ ግንኙነት የሚመነጭ ነው” በማለት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ መዓዛ መኩሪያ ጋር በመሆን ስርዓቱን መርተዋል።
በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ ከ65 አመታት በላይ በትዳር የቆዩ ጥንዶች እና በቅርቡ የተጋቡ አዳዲስ ሙሽሮች ኬክ ቆረሳ ያደረጉ ሲሆን ተሳታፊዎቹ የአንድነት ጌዜ እንደነበራቸው ታውቋል፡፡
የቤተክርሲቲያኒቱ ሰብሳቢ የሆኑት ፕሮፌስር ብርሃኑ ቆጢሶ ሕዝቡን በፀሎት የባረኩ ሲሆን ዘማሪት ሃና ተክሌና ዘማሪ አድነው ዓለሙ በዝማሬ አገልግለዋል።
ጋሽ ሽፈራው ወልደ ሚካኤል በበለጠ ተስፋ፣ በበለጠ እምነትና በአንድነት በመያያዝ እግዚአብሄርን በታመነ ሕይወት ለመኖር ልትበረታቱ ያስፈልጋል በማለት የእግዚአብሄር ቃል መልዕክት አካፍለዋል።
በሮማን ከሊል
❤4👏3❤🔥1
#የእግር #ኳስ #ዜና #አይደለም
ሶስት የፈረንሳይ ሊግ ተጨዋቾች #ግብረሰዶማዊነትን #በመቃወማቸዉ ቅጣት ተጣለባቸው
የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ (ኤልኤፍፒ) የዲሲፕሊን ኮሚቴ በሶስት የፈረንሳይ ሊግ 1 ተጫዋቾች ላይ ቅጣት ጥሏል።
የሊዮኑ ተጨዋች ኒማንያ ማቲች ፣ የሌንንሱ ተጨዋች ጆናታን ግራዲት ፣ እና ለሌ ሃቭሬ የሚጫወተዉ አህመድ ሀሰን በጸረ-ግብረ ሰዶም ቀን የግብረሰዶማውያን ባንዲራ ያለበትን አርማ ባለማድረጋቸዉ "ጥላቻ" በተሰኘ ተግባራቸዉ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
ጆናታን ግራዲት አንድ ጨዋታ ኒማንያ ማቲች እና አህመድ ሀሰን ሁለት ጨዋታዎችን እንዲቀጡ ተብሏል።
በፈረንሳይ ሊግ በተጨዋቾች እጅጌ መለያቸዉ ላይ የግብረ ሰዶማውያን መለያ አርማ ቢለጠፍም ኒማንያ ማቲች አርማዉን በፕላስተር ሸፍኖት ታይቶ ነበር። በዚህም ድርጊቱ ለሁለት ጨዋታ እንዲቀ ወስነዉበታል።
በተጨማሪም የፈረንሳይ እግር ኳስ ግብረሰዶማዉያን ላይ ሰራዋለሁ በሚለዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ እንዲሳተፍ ታዝዟል።
ዳጉ ጆርዳል እንዳስነበበው
ሶስት የፈረንሳይ ሊግ ተጨዋቾች #ግብረሰዶማዊነትን #በመቃወማቸዉ ቅጣት ተጣለባቸው
የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ሊግ (ኤልኤፍፒ) የዲሲፕሊን ኮሚቴ በሶስት የፈረንሳይ ሊግ 1 ተጫዋቾች ላይ ቅጣት ጥሏል።
የሊዮኑ ተጨዋች ኒማንያ ማቲች ፣ የሌንንሱ ተጨዋች ጆናታን ግራዲት ፣ እና ለሌ ሃቭሬ የሚጫወተዉ አህመድ ሀሰን በጸረ-ግብረ ሰዶም ቀን የግብረሰዶማውያን ባንዲራ ያለበትን አርማ ባለማድረጋቸዉ "ጥላቻ" በተሰኘ ተግባራቸዉ ቅጣት ተጥሎባቸዋል።
ጆናታን ግራዲት አንድ ጨዋታ ኒማንያ ማቲች እና አህመድ ሀሰን ሁለት ጨዋታዎችን እንዲቀጡ ተብሏል።
በፈረንሳይ ሊግ በተጨዋቾች እጅጌ መለያቸዉ ላይ የግብረ ሰዶማውያን መለያ አርማ ቢለጠፍም ኒማንያ ማቲች አርማዉን በፕላስተር ሸፍኖት ታይቶ ነበር። በዚህም ድርጊቱ ለሁለት ጨዋታ እንዲቀ ወስነዉበታል።
በተጨማሪም የፈረንሳይ እግር ኳስ ግብረሰዶማዉያን ላይ ሰራዋለሁ በሚለዉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ እንዲሳተፍ ታዝዟል።
ዳጉ ጆርዳል እንዳስነበበው
👍10👏3❤2🔥1