ልክ እንደ #ዳዊት፣ እንደ #ሳሙኤል፣ እንደ #ኤርሚያስ፣ እንደ #ጤሞቴዎስ ሁሉ ልጆቻችን ዛሬ ላይ አገልጋይ እና ሚሽነሪ መሆናቸው እንዳይረሳ።
ልጆች ዛሬም አገልጋይ ናቸው በሚል ሃሳብ፣ ስልጠና ለወላጆችና የልጆች መምህራን ተሰጠ።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ከናቪጌተርስ ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ ጋር ነው ስልጠናውን የሰጠው።
በስልጠናው ልጆቻችንን ጥሩ ክርስቲያን ማድረግ እና ደቀ መዝሙር ማድረግ ይገባል የሚል ነው።
ልጆች ነገ ሳይሆን ዛሬ የወንጌል መልዕክተኛ ስለሆኑ ልክ እንደ ሳሙኤል፣ እንደ ዳዊት፣ ጢሞቴዎስ፣ ኤርሚያስ ያሉ በትንሽነታቸውን እግዚአብሔርን የሚያገለግሉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል።
ይሄንንም እንዲረዱ ያግዝ ዘንድ የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ለተወጣጡ አገልጋዮች ስልጠና የሰጠው።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ሚኒስትሪ መሪ ወ/ሮ ሳሮን ውድነህ፣ ይሄንን ሃሳብ ሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ይዞ መሄድ አለበት፣ በተጨማሪም ስለ ቤተሰብ አገልግሎት በስፋት ሊሰራበት ይገባል ስትል ሃሳቧን አጋርታለች።
የስልጠናው ተሳታፊዎች ቆይታው አይን ከፋች ነው የሆነልን ሲሉ አስተያየታቸውን ለክርስቲያን ዜና አጋርተዋል።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ በቤተሰብ ላይ የሚሰራ ሚኒስትሪ ሲሆን፣ ናቪጌተርስ ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ ደግሞ ደቀ መዝሙር ማፍራት ላይ የሚሰራ የወንጌል አገልግሎት ሚኒስትሪ ነው።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራዉ በመገኘት ፕሮግራሙን በመከታተል ዘገባዉን አሰናዳንላችሁ።
ልጆች ዛሬም አገልጋይ ናቸው በሚል ሃሳብ፣ ስልጠና ለወላጆችና የልጆች መምህራን ተሰጠ።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ከናቪጌተርስ ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ ጋር ነው ስልጠናውን የሰጠው።
በስልጠናው ልጆቻችንን ጥሩ ክርስቲያን ማድረግ እና ደቀ መዝሙር ማድረግ ይገባል የሚል ነው።
ልጆች ነገ ሳይሆን ዛሬ የወንጌል መልዕክተኛ ስለሆኑ ልክ እንደ ሳሙኤል፣ እንደ ዳዊት፣ ጢሞቴዎስ፣ ኤርሚያስ ያሉ በትንሽነታቸውን እግዚአብሔርን የሚያገለግሉ መሆን ይገባቸዋል ብለዋል።
ይሄንንም እንዲረዱ ያግዝ ዘንድ የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ለተወጣጡ አገልጋዮች ስልጠና የሰጠው።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ሚኒስትሪ መሪ ወ/ሮ ሳሮን ውድነህ፣ ይሄንን ሃሳብ ሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያን ይዞ መሄድ አለበት፣ በተጨማሪም ስለ ቤተሰብ አገልግሎት በስፋት ሊሰራበት ይገባል ስትል ሃሳቧን አጋርታለች።
የስልጠናው ተሳታፊዎች ቆይታው አይን ከፋች ነው የሆነልን ሲሉ አስተያየታቸውን ለክርስቲያን ዜና አጋርተዋል።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ በቤተሰብ ላይ የሚሰራ ሚኒስትሪ ሲሆን፣ ናቪጌተርስ ኢትዮጵያ ሚኒስትሪ ደግሞ ደቀ መዝሙር ማፍራት ላይ የሚሰራ የወንጌል አገልግሎት ሚኒስትሪ ነው።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራዉ በመገኘት ፕሮግራሙን በመከታተል ዘገባዉን አሰናዳንላችሁ።
👍6❤2👏2🙏2❤🔥1
#በአፋር ክልል በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ተደረገ።
የመሠረተ ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን ከቲዲ ኤም ኤም ጋር በመተባበር በአፋር ክልል በመሬት መቀጥቀጥ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖቻችን 2,000,000 ብር ወጪ በማድረግ ለ500 አባወራዎች የምግብ ድጋፍ አደረገች።
ቤተክርስቲያኒቱ በአፋር ክልል አዋሽ አርባ አካባቢ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሁለት መጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ዜጎች ድጋፉን ስታደርግ በስፍራው የተገኙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ለተጎጂዎች እርዳታውን በሰጡበት ወቅት #እዚህ_የተገኘውን_ለእናንተ_ያለንን_ፍቅር_ለመግለጽና_በምን_ሁኔታ_ውስጥ_እንዳላችሁ_ለማየት_እንዲሁም_ይህ_ጊዜ_ያልፋል_አይዟችሁ_ለማለት_ነው_ሲሉ በጸሎታችን ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነን ብለዋል።
ተጎጂዎችም ቤተክርስቲያን ስላደረገችላቸው ድጋፍ በማመስገን ደስታቸውን ሲገልጹ ታይቷል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢዎች ለሚገኙ ወገኖቿ ተመሳሳይ ድጋፎችን ስታደርግ መቆየቷ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ዜና የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በአፋር ክልል በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የጸሎት ቤታቸው የፈረሰባቸውን የከሰም ቀበና መሪዎች በስፍራው በመገኘት አበረታተዋል።
ፕሬዚዳንቱ በዛሬው ዕለት በክልሉ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የተጎዱ አካባቢዎችን ተዟዙረው በተመለከቱበት ወቅት በስፍራው ከሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች ጋር ሲወያዩ በውይይታቸውም በአካባቢው ቤተክርስቲያንን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተነጋግረዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በአከባቢው የእግዚአብሔር መንግስት እንዲሰፋ የምትሰጠውን የወንጌል አገልግሎት አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን ከቲዲ ኤም ኤም ጋር በመተባበር በአፋር ክልል በመሬት መቀጥቀጥ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖቻችን 2,000,000 ብር ወጪ በማድረግ ለ500 አባወራዎች የምግብ ድጋፍ አደረገች።
ቤተክርስቲያኒቱ በአፋር ክልል አዋሽ አርባ አካባቢ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሁለት መጠለያ ጣቢያዎች ለሚገኙ ዜጎች ድጋፉን ስታደርግ በስፍራው የተገኙት የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ለተጎጂዎች እርዳታውን በሰጡበት ወቅት #እዚህ_የተገኘውን_ለእናንተ_ያለንን_ፍቅር_ለመግለጽና_በምን_ሁኔታ_ውስጥ_እንዳላችሁ_ለማየት_እንዲሁም_ይህ_ጊዜ_ያልፋል_አይዟችሁ_ለማለት_ነው_ሲሉ በጸሎታችን ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነን ብለዋል።
ተጎጂዎችም ቤተክርስቲያን ስላደረገችላቸው ድጋፍ በማመስገን ደስታቸውን ሲገልጹ ታይቷል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅለው በመጠለያ ጣቢዎች ለሚገኙ ወገኖቿ ተመሳሳይ ድጋፎችን ስታደርግ መቆየቷ ይታወሳል።
በተመሳሳይ ዜና የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ በአፋር ክልል በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የጸሎት ቤታቸው የፈረሰባቸውን የከሰም ቀበና መሪዎች በስፍራው በመገኘት አበረታተዋል።
ፕሬዚዳንቱ በዛሬው ዕለት በክልሉ በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የተጎዱ አካባቢዎችን ተዟዙረው በተመለከቱበት ወቅት በስፍራው ከሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች ጋር ሲወያዩ በውይይታቸውም በአካባቢው ቤተክርስቲያንን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተነጋግረዋል።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በአከባቢው የእግዚአብሔር መንግስት እንዲሰፋ የምትሰጠውን የወንጌል አገልግሎት አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
👍10❤3🔥1👏1
በደቡብ #አፍሪካ የመሪዎች የአንድነት ጊዜ ተካሄደ።
በፈረንጆቹ ሜይ 6 እና 7 በኬፕ ታውን የነበረው የ2ተኛ ዙር የደቡብ አፍሪካ የመሪዎች የአንድነት ጊዜ በጥሩ መንፈስ እና በወንድማማችነት ስሜት መካሄዱን ከስፍራዉ የተላከልን ዝርዝር ያመለክታል።
መድረኩን የካውንስሉ ፕሬዝዳንት ፓስተር ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ በ“እንኳን ደህና መጣችሁ” ንግግር ያስጀመሩት ሲሆን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ፓስተር ገነነ “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ጠብቁ” በሚል መልዕክት አቅርበዋል።
የሴሚናሩ የመጀመሪያ ቀን ማለዳ "የወንድማማች ኅብረት" በሚል ርዕስ በፓስተር ዶ/ር ዴቪድ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በከሰዓቱ ፕሮግራም ዓላማና ግብ ላይ ያጠነጠነ በካውንስሉ ፕሬዝዳንት በፓስተር ዶ/ር ብርሃኑ ትምህርት ቀርቧል።
ዕረቡ ማለዳ ደግሞ መሪነትን በተመለከተ በፓስተር ኤልያስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከሰዓት ደግሞ የፓናል ውይይት በፓስተር ገነነ አወያይነት ሐዋርያው ሳሙኤል፣ ፓስተር በየነ፣ ፓስተር ዴቪድ እና ፓስተር ጡሚሳ አማኞችን የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት በማድረግ ዙሪያ እና በወቅታዊ ክርስቲያናዊ ምልልስ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በሌላም በኩል በተሻለ መንገድ ለመሥራት አብዛኛውን ፕሮቪንሶች አካታች ባደረገ መልኩ 30 የሚሆኑ የቦርድ አባላትን ያካተተ 9 የሥራ አስፈጻሚ ቡድን ሰይሟል። በመሆኑም:-
1. ፓስተር ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ … ፕሬዚደንት
2. ፓስተር ገነነ ማስረሻ … ምክትል ፕሬዚደንት
3. ፓስተር ዴቪድ ሐለንጎ … ዋና ጸሐፊ
4. ፓስተር ብርሃኑ በቀለ … ገንዘብ ያዥ
5. ፓስተር በየነ ሎሳሶ … ሂሳብ ሹም
6. ሐዋርያው ሳሙኤል ሽራንጎ … አባል
7. ፓስተር ኤልያስ ግርማ … አባል
8. ፓስተር አባተ አበራ … አባል
9. ፓስተር ደመቀ ኃይሌ … አባል
ሆነው ተመርጠዋል።
በፈረንጆቹ ሜይ 6 እና 7 በኬፕ ታውን የነበረው የ2ተኛ ዙር የደቡብ አፍሪካ የመሪዎች የአንድነት ጊዜ በጥሩ መንፈስ እና በወንድማማችነት ስሜት መካሄዱን ከስፍራዉ የተላከልን ዝርዝር ያመለክታል።
መድረኩን የካውንስሉ ፕሬዝዳንት ፓስተር ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ በ“እንኳን ደህና መጣችሁ” ንግግር ያስጀመሩት ሲሆን ምክትል ፕሬዝዳንቱ ፓስተር ገነነ “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ጠብቁ” በሚል መልዕክት አቅርበዋል።
የሴሚናሩ የመጀመሪያ ቀን ማለዳ "የወንድማማች ኅብረት" በሚል ርዕስ በፓስተር ዶ/ር ዴቪድ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን በከሰዓቱ ፕሮግራም ዓላማና ግብ ላይ ያጠነጠነ በካውንስሉ ፕሬዝዳንት በፓስተር ዶ/ር ብርሃኑ ትምህርት ቀርቧል።
ዕረቡ ማለዳ ደግሞ መሪነትን በተመለከተ በፓስተር ኤልያስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከሰዓት ደግሞ የፓናል ውይይት በፓስተር ገነነ አወያይነት ሐዋርያው ሳሙኤል፣ ፓስተር በየነ፣ ፓስተር ዴቪድ እና ፓስተር ጡሚሳ አማኞችን የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት በማድረግ ዙሪያ እና በወቅታዊ ክርስቲያናዊ ምልልስ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
በሌላም በኩል በተሻለ መንገድ ለመሥራት አብዛኛውን ፕሮቪንሶች አካታች ባደረገ መልኩ 30 የሚሆኑ የቦርድ አባላትን ያካተተ 9 የሥራ አስፈጻሚ ቡድን ሰይሟል። በመሆኑም:-
1. ፓስተር ዶ/ር ብርሃኑ ታምሬ … ፕሬዚደንት
2. ፓስተር ገነነ ማስረሻ … ምክትል ፕሬዚደንት
3. ፓስተር ዴቪድ ሐለንጎ … ዋና ጸሐፊ
4. ፓስተር ብርሃኑ በቀለ … ገንዘብ ያዥ
5. ፓስተር በየነ ሎሳሶ … ሂሳብ ሹም
6. ሐዋርያው ሳሙኤል ሽራንጎ … አባል
7. ፓስተር ኤልያስ ግርማ … አባል
8. ፓስተር አባተ አበራ … አባል
9. ፓስተር ደመቀ ኃይሌ … አባል
ሆነው ተመርጠዋል።
👍7❤1🔥1
የባይተዋር ወዳጅ - ሶፊያ ሽባባዉ አዲስ መዝሙር ተባረኩበት ከረጅም ጊዜ በኋላ በድጋሜ ስላየናት ደስ ብሎናል። https://www.youtube.com/watch?v=Rp_Mls0nKgg
YouTube
የባይተዋር ወዳጅ - ሶፊያ ሽባባዉ // yebaytewar wedaj - sofia shibabaw // new song //አዲስ መዝሙር
new song አዲስ መዝሙር የባይተዋር ወዳጅ ሶፊያ ሽባባ new pro // Official Sofia Shibabaw 2023 //
subscribe and like our video for more interesting contents•
ይህን ቪዲዮ ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ማድረግ አይርሱ።
ሰብስክራይብ ያላደረጋችሁ አዳዲስ ቪዲዮ እንዲደርሳችሁ ሰብስክራይብ በማድረግ የደውል ምልክቱን መጫን አትርሱ።
This…
subscribe and like our video for more interesting contents•
ይህን ቪዲዮ ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ማድረግ አይርሱ።
ሰብስክራይብ ያላደረጋችሁ አዳዲስ ቪዲዮ እንዲደርሳችሁ ሰብስክራይብ በማድረግ የደውል ምልክቱን መጫን አትርሱ።
This…
❤9🙏2🔥1👏1
የፊንፊኔ ኦሮሞ መካነ ኢየሱስ የአምልኮ ህንጻ በድምቀት ተመረቀ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ የሱስ የፊንፊኔ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን ማምለኪያ ህንፃ ተመረቀ፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ የሱስ የፊንፊ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን በጉለሌ ዊንጌት አከባቢ ኢቢሲ ፊት ለፊት ያስገነባችውን የአምልኮ አዳራሽ እና ሁለ ገብ ህንፃ እሁድ እለት አስመርቃለች፡፡
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች ፣ከውጭ እና ሀገር ውስጥ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ቤተ ክርስቲኑ ባለፉት 33 ዓመታት ለራሷ ድንኳን ውስጥ ተቀምጣ የስብከት ጣቢያዎችን በማስፋፋት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የወንጌል ስርጭት ስራ በመስራት ላይምል ትገኛለች፡፡
በዚሁ መሰረት 14 ስብከት ጣቢዎችን ወደ ቤተክርስቲን በማሳደግ፣ 29 ስብከት ጣቢዎችን በመትከል ወንጌል እዲስፋፋ ትልቅ ስራ ሰርታለች፡፡
ዛሬ ላይ ቤተክርስቲያኗ በእግዚአብሔር እርዳታ ባገኘችው የራሷ ሰፊ ቦታ ላይ ያስገነባችውን የአምልኮ አዳራሽ እና ሁለ ገብ ህንፃ በማስመረቅ የወንጌል ስርጭት ስራ ይበልጥ ለማስፋፋት ተዘጋጅታለች፡፡
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች አገኘነው
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ የሱስ የፊንፊኔ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን ማምለኪያ ህንፃ ተመረቀ፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ የሱስ የፊንፊ ኦሮሞ ማህበረ ምዕመናን በጉለሌ ዊንጌት አከባቢ ኢቢሲ ፊት ለፊት ያስገነባችውን የአምልኮ አዳራሽ እና ሁለ ገብ ህንፃ እሁድ እለት አስመርቃለች፡፡
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቢሮ ከፍተኛ አመራሮች ፣ከውጭ እና ሀገር ውስጥ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
ቤተ ክርስቲኑ ባለፉት 33 ዓመታት ለራሷ ድንኳን ውስጥ ተቀምጣ የስብከት ጣቢያዎችን በማስፋፋት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የወንጌል ስርጭት ስራ በመስራት ላይምል ትገኛለች፡፡
በዚሁ መሰረት 14 ስብከት ጣቢዎችን ወደ ቤተክርስቲን በማሳደግ፣ 29 ስብከት ጣቢዎችን በመትከል ወንጌል እዲስፋፋ ትልቅ ስራ ሰርታለች፡፡
ዛሬ ላይ ቤተክርስቲያኗ በእግዚአብሔር እርዳታ ባገኘችው የራሷ ሰፊ ቦታ ላይ ያስገነባችውን የአምልኮ አዳራሽ እና ሁለ ገብ ህንፃ በማስመረቅ የወንጌል ስርጭት ስራ ይበልጥ ለማስፋፋት ተዘጋጅታለች፡፡
መረጃውን ከቤተ ክርስቲያኗ መሪዎች አገኘነው
❤10👍7💔4🔥1
የወንጌል አርበኛዋ እማማ ዛናቄ በክብር ተሸኙ 🥺
በጨንቻና አካባቢዋ የመጀመሪያዋ ሴት የወንጌል አማኝ እና የወንገል አርበኛ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑት ወ/ሮ ዛናቄ ዛሜ በትላንትናው ቀን ግንቦት 5/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸዉ ይታወሳል።
የወንጌል አርበኛዋ ከዘማሪ እስራኤል ኩማ እና ከሌሎች ዘማሪያን ጋር ሆነው ሃሹ ጊዶኮና ጦሳ ና'' በሚለው የጋሞኛ ዝማሬ የቪዲዮ ክሊፕ ላይ በዝማሬ ከታዩ በኋላ በበርካቶች ዘንድ አክብሮት እና አድናቆት ተችሯቸዋል።
ወ/ሮ ዛናቀ ዛሜ በምድር ቆይታቸው በወንጌል ምክንያት መከራን ተቀብለው ለትውልድ ምሳሌ በመሆን ሲመላለሱ የነበሩ ብርቱ እናት እንደነበሩ በቅርበት የሚያውቋቸው ይመሰክራሉ።በጋሞ ዞን ጨንቻና አካባቢው ወንጌልን ለትውልድ በማድረስ አንቱታን ያተረፉት እማማ ዛናቄ ዛሜ ዛሬ በቀን 6/09/2017 ዓ.ም በተወለዱበት በዶኮ መሾ ዮይራ ያጭኔ ሁለገብ ስታዲየም በመንፈሳዊ ስነስርዓት ሽኝት በድምቀት ተካሄደዋል።
ለቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን!
በጨንቻና አካባቢዋ የመጀመሪያዋ ሴት የወንጌል አማኝ እና የወንገል አርበኛ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የዕድሜ ባለፀጋ የሆኑት ወ/ሮ ዛናቄ ዛሜ በትላንትናው ቀን ግንቦት 5/2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸዉ ይታወሳል።
የወንጌል አርበኛዋ ከዘማሪ እስራኤል ኩማ እና ከሌሎች ዘማሪያን ጋር ሆነው ሃሹ ጊዶኮና ጦሳ ና'' በሚለው የጋሞኛ ዝማሬ የቪዲዮ ክሊፕ ላይ በዝማሬ ከታዩ በኋላ በበርካቶች ዘንድ አክብሮት እና አድናቆት ተችሯቸዋል።
ወ/ሮ ዛናቀ ዛሜ በምድር ቆይታቸው በወንጌል ምክንያት መከራን ተቀብለው ለትውልድ ምሳሌ በመሆን ሲመላለሱ የነበሩ ብርቱ እናት እንደነበሩ በቅርበት የሚያውቋቸው ይመሰክራሉ።በጋሞ ዞን ጨንቻና አካባቢው ወንጌልን ለትውልድ በማድረስ አንቱታን ያተረፉት እማማ ዛናቄ ዛሜ ዛሬ በቀን 6/09/2017 ዓ.ም በተወለዱበት በዶኮ መሾ ዮይራ ያጭኔ ሁለገብ ስታዲየም በመንፈሳዊ ስነስርዓት ሽኝት በድምቀት ተካሄደዋል።
ለቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን!
👍15😭11🥰4❤2🔥1👏1
በግሬስ #ክርስቲያን #ሚዲያ የተዘጋጀውን "ግሬስ ቶርናመንት" የእግር ኳስ ውድድር አስመልክቶ ጋዜጣዊ #መግለጫ በዛሬው እለት ተሰጥቷል።
'ግሬስ ቶርናመንት' ማህበረሰባችን ለስፖርት ለማንቃት #እና እርስ በእርስ ተቀራርቦ ስፖርታዊ ባህልን እንዲያዳብር ለማስለመድ የተዘጋጀ የእግር ኳስ ውድድር እንደሆነ ተገልጿል። በእግር ኳስ ጨዋታ #ውስጥ ለመያያዝና ማህበረባችን ለመጥቀም ለበጎ አላማ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህ የእግር #ኳስ ውድድር 16 ቡድኖች የሚሳተፉ ሲሆን፣ በሰላምና በፍቅር ለወንጌል ምሳሌነት በሚሆን መልኩ፣ እርስ በእርስ ውድድራችን እናደርጋለን ተብሏል። እግር ኳስ ዘርፈ #ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት እናምናለን በማለት ተናግረዋል።
#ይህ ቶሮናመንት የፊታችን #ቅዳሜ የክብር እንግዶች የቤተክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች በተገኙበት ግንቦት 9/2017 ከ 9:00 ጀምሮ በቡልቡላ #ሜዳ #ላይ የሚከናወን ሲሆን፣ የመክፈቻ ጨዋታው በናዝራውያን ቡድንና፣ በዘጸአት ቤተ ክርስቲያን ቡድኖች መሐል በሚደረገው ጨዋታ እንደሚጀመር ተገልጿል።
'ግሬስ ቶርናመንት' ማህበረሰባችን ለስፖርት ለማንቃት #እና እርስ በእርስ ተቀራርቦ ስፖርታዊ ባህልን እንዲያዳብር ለማስለመድ የተዘጋጀ የእግር ኳስ ውድድር እንደሆነ ተገልጿል። በእግር ኳስ ጨዋታ #ውስጥ ለመያያዝና ማህበረባችን ለመጥቀም ለበጎ አላማ የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህ የእግር #ኳስ ውድድር 16 ቡድኖች የሚሳተፉ ሲሆን፣ በሰላምና በፍቅር ለወንጌል ምሳሌነት በሚሆን መልኩ፣ እርስ በእርስ ውድድራችን እናደርጋለን ተብሏል። እግር ኳስ ዘርፈ #ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት እናምናለን በማለት ተናግረዋል።
#ይህ ቶሮናመንት የፊታችን #ቅዳሜ የክብር እንግዶች የቤተክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች በተገኙበት ግንቦት 9/2017 ከ 9:00 ጀምሮ በቡልቡላ #ሜዳ #ላይ የሚከናወን ሲሆን፣ የመክፈቻ ጨዋታው በናዝራውያን ቡድንና፣ በዘጸአት ቤተ ክርስቲያን ቡድኖች መሐል በሚደረገው ጨዋታ እንደሚጀመር ተገልጿል።
👍6❤3🔥1🥰1
“LetAfrica Go” 2025” ኮንፈራንስ ተካሄደ።
በኮንፈራንሱከ20 የአፍሪካ ሃገራት የተወጣጡ መሪዎች እና አገልጋዮች ተካፋይ ሆነዋል።
ከግንቦት1-3 አዲስ በተከፈተው የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር የተካሄደው ኮንፈራንሱ “መለኮታዊ ግንኙነት - የእስራኤል
ትንቢታዊ ሃላፊነት በአፍሪካ መነቃቃትና ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል።
ወንጌላዊያንመሪዎቹ ሰላም በኢየሩሳሌም እንዲሰፍን፣ በሃማስ የታገቱ እስራኤላዊያን እንዲለቀቁ እና በአፍሪካ እና እስራኤል መካከል ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖር ጸሎት አድርገዋል።
በመድረኩበኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ዶ/ር አቭራሃም ንጉሴ፣ ኢትዮጵያ እና እስራኤል ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት አስታውሰው፣
ሃገራቱ በልማት፣ ግብርና፣ መድሃኒት፣ የምግብ ደህንነት፣ ፈጠራ እና ሌሎችም ዘርፎች ላይ ይበልጥ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
የ”LetAfrica Go” ንቅናቄ መስራች ዶ/ር ፓስተር አበራ ሃብቴ በአህጉሪቱ እና በውጪ ያሉ አፍሪካዊያን በሙሉ ከእስራኤል ጎን
መቆም አለባቸው ሲሉ ተናገረዋል።
LetAfrica Go ንቅናቄ የአፍሪካ ለውጥ ከፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ በላይ መንፈሳዊ መሆን አለበት ብሎ ያምናል። በተጨማሪ ከእስራኤል ጋር አብሮ መቆም ዋና መርሁ ነው። አመታዊ ኮንፈራንሱ በኤልሻዳይ ቲቪ ኔትወርክ መስራች ዶ/ር አበራ ሃብቴ በ2023 የተጀመረ ነው።
በኮንፈራንሱከ20 የአፍሪካ ሃገራት የተወጣጡ መሪዎች እና አገልጋዮች ተካፋይ ሆነዋል።
ከግንቦት1-3 አዲስ በተከፈተው የአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር የተካሄደው ኮንፈራንሱ “መለኮታዊ ግንኙነት - የእስራኤል
ትንቢታዊ ሃላፊነት በአፍሪካ መነቃቃትና ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል።
ወንጌላዊያንመሪዎቹ ሰላም በኢየሩሳሌም እንዲሰፍን፣ በሃማስ የታገቱ እስራኤላዊያን እንዲለቀቁ እና በአፍሪካ እና እስራኤል መካከል ጠንካራ ግንኙነት እንዲኖር ጸሎት አድርገዋል።
በመድረኩበኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር ዶ/ር አቭራሃም ንጉሴ፣ ኢትዮጵያ እና እስራኤል ያላቸውን ታሪካዊ ግንኙነት አስታውሰው፣
ሃገራቱ በልማት፣ ግብርና፣ መድሃኒት፣ የምግብ ደህንነት፣ ፈጠራ እና ሌሎችም ዘርፎች ላይ ይበልጥ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
የ”LetAfrica Go” ንቅናቄ መስራች ዶ/ር ፓስተር አበራ ሃብቴ በአህጉሪቱ እና በውጪ ያሉ አፍሪካዊያን በሙሉ ከእስራኤል ጎን
መቆም አለባቸው ሲሉ ተናገረዋል።
LetAfrica Go ንቅናቄ የአፍሪካ ለውጥ ከፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ በላይ መንፈሳዊ መሆን አለበት ብሎ ያምናል። በተጨማሪ ከእስራኤል ጋር አብሮ መቆም ዋና መርሁ ነው። አመታዊ ኮንፈራንሱ በኤልሻዳይ ቲቪ ኔትወርክ መስራች ዶ/ር አበራ ሃብቴ በ2023 የተጀመረ ነው።
🔥6👍3👏2❤1
አዲሱ የካቶሊክ ቤ/ክ ሊቀ ጳጳስ ቤተሰብ የሚመሰረተው በአንድ ወንድ እና አንድ ሴት ጥምረት ነው አሉ።
ሊቀ ጳጳሱ ሊዮ 14ኛ አክለውም ከማህጸን ያልወጣ እና ያረጀ ሰው በእግዚአብሔር ፊት እኩል ክብር ያላቸው ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።
ይሄ ንግግራቸው ቤተ ክርስቲያኗ ለምትታማበት የግብረሰዶም
እና ውርጃ ጉዳዮች መጽሃፍ ቅዱሳዊ ቱምቢ ያስቀመጠ ንግግር ነው ተብሏል።
የመጀመሪያው አሜሪካዊ ጳጳስ የሆኑ ሊቀ ጳጳስ ሊዮ 14ኛ በቫቲካን ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በሃይማኖቶች መካከል ንግግሮችን ማዳበር ያስፈልጋል ብለዋል።
ትላንት አርብ ከዲፕሎማቲክ
ማህበረሰብ ጋር ከእሁዱ የመጀሪያዉ ሲመታቸው በፊት ባደረጉት የዝግ በር ንግግር ነው።
ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ ሊቀ ጳጵሱ ከ180 ሃገራት ጋር ግንኙነትያላትን ቫቲካን ሃገረ መንግስት መሪ በመሆናቸው የሚደረግ ግንኙነት ነው።
ሊቀ ጳጳሱ ከአውግስጢኖስ ቤተ ስርዓት የወጡ ስለሆነ ግንቦት 1 ወደ አደባባይ ሲወጡ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” ብለው ንግግራቸውን መጀመራቸው ሰላም በጵጵስናቸው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑ አመላካች ነው።
ሰላማዊ ማህበረሰብን በመገንባት ሂደት ውስጥ ለቤተሰብ ቅድሚያ በመስጠት በአንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት ላይ መሰረት ያደረገ ቤተሰብ መገንባትን መንግስታት ማገዝ አለባቸው ብለዋል።
ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ በጵጵስናቸው ወቅት ውርጃን እና በፈቃደኝነት ራስን ማጥፋትን የተቃወሙ ሲሆን፣ የቤተ ክርስቲያንን በሮች ለሰዶማዊያን ከፍተዋል ሲል ያስነበበው አሶሼትድ ፕረስ
ነው።
ሊቀ ጳጳሱ ሊዮ 14ኛ አክለውም ከማህጸን ያልወጣ እና ያረጀ ሰው በእግዚአብሔር ፊት እኩል ክብር ያላቸው ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።
ይሄ ንግግራቸው ቤተ ክርስቲያኗ ለምትታማበት የግብረሰዶም
እና ውርጃ ጉዳዮች መጽሃፍ ቅዱሳዊ ቱምቢ ያስቀመጠ ንግግር ነው ተብሏል።
የመጀመሪያው አሜሪካዊ ጳጳስ የሆኑ ሊቀ ጳጳስ ሊዮ 14ኛ በቫቲካን ከዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በሃይማኖቶች መካከል ንግግሮችን ማዳበር ያስፈልጋል ብለዋል።
ትላንት አርብ ከዲፕሎማቲክ
ማህበረሰብ ጋር ከእሁዱ የመጀሪያዉ ሲመታቸው በፊት ባደረጉት የዝግ በር ንግግር ነው።
ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ ሊቀ ጳጵሱ ከ180 ሃገራት ጋር ግንኙነትያላትን ቫቲካን ሃገረ መንግስት መሪ በመሆናቸው የሚደረግ ግንኙነት ነው።
ሊቀ ጳጳሱ ከአውግስጢኖስ ቤተ ስርዓት የወጡ ስለሆነ ግንቦት 1 ወደ አደባባይ ሲወጡ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” ብለው ንግግራቸውን መጀመራቸው ሰላም በጵጵስናቸው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑ አመላካች ነው።
ሰላማዊ ማህበረሰብን በመገንባት ሂደት ውስጥ ለቤተሰብ ቅድሚያ በመስጠት በአንድ ወንድ እና በአንዲት ሴት ላይ መሰረት ያደረገ ቤተሰብ መገንባትን መንግስታት ማገዝ አለባቸው ብለዋል።
ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ በጵጵስናቸው ወቅት ውርጃን እና በፈቃደኝነት ራስን ማጥፋትን የተቃወሙ ሲሆን፣ የቤተ ክርስቲያንን በሮች ለሰዶማዊያን ከፍተዋል ሲል ያስነበበው አሶሼትድ ፕረስ
ነው።
👍18👏5❤1🔥1
የአምቦ መካነ ኢየሱስ የአምልኮ ህንጻ ተመረቀ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አምቦ ማህረ ምዕመናን አዲስ የአምልኮ ህንፃ ተመረቀ።
ከተተከለች 50 ዓመታትን ያስቆጠረችው የአምቦ መካነ ኢየሱስ ቤ/ክ፡ የቤተ ክርስቲያኗ ፕሬዝደንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በተገኙበት ተመርቃለች።
ቤ/ክኗ ለወንጌላዊያን የስደት ዘመን በነበረበት 1975 ዓ.ም ጀመራ የምስራቹን ወንጌል ስታገለግል የቆየች ናት። በነዚህ ጊዜያት በርካታ ማህበረ ምዕመናንን እና የስብከት ጣቢያዎችን በመትከል ወንጌል ስታዳርስ ቆይታለች።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አምቦ ማህረ ምዕመናን አዲስ የአምልኮ ህንፃ ተመረቀ።
ከተተከለች 50 ዓመታትን ያስቆጠረችው የአምቦ መካነ ኢየሱስ ቤ/ክ፡ የቤተ ክርስቲያኗ ፕሬዝደንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በተገኙበት ተመርቃለች።
ቤ/ክኗ ለወንጌላዊያን የስደት ዘመን በነበረበት 1975 ዓ.ም ጀመራ የምስራቹን ወንጌል ስታገለግል የቆየች ናት። በነዚህ ጊዜያት በርካታ ማህበረ ምዕመናንን እና የስብከት ጣቢያዎችን በመትከል ወንጌል ስታዳርስ ቆይታለች።
❤12👍4🔥1
#ጥንቃቄ
ከግንቦት 16 እና 17 የሚደረገው ፕሮግራም በቅድሚያ መስቀል አደባባይ ተብሎ ነበር የተሰራው ነገር ግን ቦታው በሌላ ፕሮግራም ስለ ተያዘ ወደ ሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም መቀየሩ ይታወቃል።
ሆኖም ቀደም ተብሎ የተሰራው የምስል ማስታወቂያ በትልልቅ መንፈሳዊ ቴሌቪዥን በEvangelical, GMM እና በሌሎችም ሚዲያዎች አሁንም ቦታው መስቀል አደባባይ ተብሎ እየተነገረ ያለው ስህተት በመሆኑ ትክክለኛው በአብያተ ክርስቲያናት የተዘጋጀው የንስሃና የምልጃ ፕሮግራም በሀዋሳ እስታዲየም መሆኑን እንዲታወቅ ለሁሉም ይነገር እና ሼር ይደረግ።
#ዛሬ ግንቦት 16 ቅዳሜ ከ9:00 ጀምሮ ሀዋሳ እስታዲየም እንገናኝ።
ከግንቦት 16 እና 17 የሚደረገው ፕሮግራም በቅድሚያ መስቀል አደባባይ ተብሎ ነበር የተሰራው ነገር ግን ቦታው በሌላ ፕሮግራም ስለ ተያዘ ወደ ሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም መቀየሩ ይታወቃል።
ሆኖም ቀደም ተብሎ የተሰራው የምስል ማስታወቂያ በትልልቅ መንፈሳዊ ቴሌቪዥን በEvangelical, GMM እና በሌሎችም ሚዲያዎች አሁንም ቦታው መስቀል አደባባይ ተብሎ እየተነገረ ያለው ስህተት በመሆኑ ትክክለኛው በአብያተ ክርስቲያናት የተዘጋጀው የንስሃና የምልጃ ፕሮግራም በሀዋሳ እስታዲየም መሆኑን እንዲታወቅ ለሁሉም ይነገር እና ሼር ይደረግ።
#ዛሬ ግንቦት 16 ቅዳሜ ከ9:00 ጀምሮ ሀዋሳ እስታዲየም እንገናኝ።
❤6🔥2👍1👏1
#የኢትዮጵያ #ሙሉ #ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን የሁለት አቅመ ደካማ እማወራ ቤቶችን የማደስ ስራ አስጀመረች።
በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን የማደስ የማስጀመር ስራ ላይ የቤተ እምነቷ ፕሬዝዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ፣ ም/ት ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው ተገኝተው ስራውን አስጀምረዋል።
የቤት እደሳው መርሃ ግብር በሁለት ወራት የሚጠናቀቅ መሆኑን በወቅቱ በተሰጠው መግለጫ የታወቀ ሲሆን በቤት ውስጥ የነበሩ ሰዎች ለጊዜው የማረፍያ ቦታ እንዳይቸገሩ የቤት ኪራይ የሚሆን ወጪ በቤተክርስቲያኗ መሸፈኑ ተገልጾአል።
የቤተ እምነቷ ፕሬዝደንት ባደረጉት ንግግር ቤተክርስቲያኗ እንደዚህ አይነት ማህበራዊ ሀላፊነት ማከናወን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መርህ የተከተለና በቀጣይም በማህበራዊ እና በሀገራዊ ልማት ስራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ምስጋና እንጅሉ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ይሄን በጎ ሰናይ ተግባር በማከናወኗ ምስጋናቸውን አቅርበው በዚህ አርያነት መከተሏ ቤተክርስቲያኗ ለሌሎችም ምሳሌ የምትሆን ናት ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ዋና ጽ/ ቤት ከዚህ ቀደም በወረዳው የሚመጡትን ልማታዋና ማህበራዊ ጉዳዮች የያዙ ጥያቄዎችን በመቀበል በንቃት በመሳተፍ ማህበራዊ እና መንፈሳዊ ሀላፊነቷን እየተወጣች መሆኑንን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን የማደስ የማስጀመር ስራ ላይ የቤተ እምነቷ ፕሬዝዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ፣ ም/ት ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው ተገኝተው ስራውን አስጀምረዋል።
የቤት እደሳው መርሃ ግብር በሁለት ወራት የሚጠናቀቅ መሆኑን በወቅቱ በተሰጠው መግለጫ የታወቀ ሲሆን በቤት ውስጥ የነበሩ ሰዎች ለጊዜው የማረፍያ ቦታ እንዳይቸገሩ የቤት ኪራይ የሚሆን ወጪ በቤተክርስቲያኗ መሸፈኑ ተገልጾአል።
የቤተ እምነቷ ፕሬዝደንት ባደረጉት ንግግር ቤተክርስቲያኗ እንደዚህ አይነት ማህበራዊ ሀላፊነት ማከናወን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መርህ የተከተለና በቀጣይም በማህበራዊ እና በሀገራዊ ልማት ስራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ እንደምትቀጥል ገልጸዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ምስጋና እንጅሉ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ይሄን በጎ ሰናይ ተግባር በማከናወኗ ምስጋናቸውን አቅርበው በዚህ አርያነት መከተሏ ቤተክርስቲያኗ ለሌሎችም ምሳሌ የምትሆን ናት ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ዋና ጽ/ ቤት ከዚህ ቀደም በወረዳው የሚመጡትን ልማታዋና ማህበራዊ ጉዳዮች የያዙ ጥያቄዎችን በመቀበል በንቃት በመሳተፍ ማህበራዊ እና መንፈሳዊ ሀላፊነቷን እየተወጣች መሆኑንን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
👍9❤3
#አሁን ከሃዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም #livestreaming
"ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ" የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም
የሃዋሳ ከተማአቀፍ የተሃድሶ ንቅናቄ
በ Facebook እና youtube በቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት ከደቂቃዎች በኋላ ይከታተላሉ። 🙏🙏🙏
"ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ" የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም
የሃዋሳ ከተማአቀፍ የተሃድሶ ንቅናቄ
በ Facebook እና youtube በቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት ከደቂቃዎች በኋላ ይከታተላሉ። 🙏🙏🙏
👍9❤4🔥1
ተጀመረ ተጀመረ አሁኑኑ በቀጥታ ስርጭት አብረውን ይገልገሉ። https://www.youtube.com/watch?v=2LO6vTLJ5Qc
YouTube
Day 1🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 1
Day 1🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 1
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel This…
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel This…
❤8👍1
#አሁን ከሃዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም #livestreaming ከሁሉም አለም አብራችሁን ሁኑ ለሌሎች እንዲደርስ Share አድርጉ !!! https://www.youtube.com/watch?v=tHQFuhBnp5M
YouTube
Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2
Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel This…
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel This…
👍1
#አስደሳች #ዜና
የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲናን ጨምሮ ለ3 መሪዎች እውቅና ሰጠ።
"ኑ ወደ #እግዚአብሔር እንመለስ" በሚል የምልጃ እና የንሰሐ ኮንፍራንስ በሐዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም እየተካሄደ ሲሆን በኮንፍራንሱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር መኩሪያ ማርሻዬ ባደረጉት ንግግር #ዛሬ በአንድነት #እና በጋራ በመስራት ሀገራችንን በላባችን እና በመሰዋዕትነት ልናሳድገት ይገባል ያሉ ሲሆን የሃይማኖት እና የብሔር ብዝሃነት ጸጋችንን በመጠቀም ሰላማችንን ለማምጣት እኛ ክርስቲያኖች #ምሳሌ በመሆን ልንኖር ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ ለሃዋሳ ከተማችን መለወጥ #ወንጌል ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ በመጥቀስ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽዖ የከተማ አስተዳደሩ እና የሲዳማ ክልል ለ4 የወንጌላውያን መሪዎች እውቅና ሰጥቷል።
ኑሮዓቸውን በአሜሪካ ላደረጉት ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና ፤ ለኢትዮያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ለፓስተር ጻዲቁ አብዶ ፤ ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ እና ለሃዋሳ ሕይወት ብረሃን ቤተክርስቲያን ዋና መጋቢ ፓስተር ጌቱ አያሌው እውቅናው እና ሽልማቱ ተሰቷቸዋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከስፍራው በ Facebook እና youtube ቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት እያስተላለፍን ስለሆነ እንድትከታተሉን እንጋብዛለን። https://www.youtube.com/watch?v=tHQFuhBnp5M 🙏🙏🙏
የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲናን ጨምሮ ለ3 መሪዎች እውቅና ሰጠ።
"ኑ ወደ #እግዚአብሔር እንመለስ" በሚል የምልጃ እና የንሰሐ ኮንፍራንስ በሐዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም እየተካሄደ ሲሆን በኮንፍራንሱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር መኩሪያ ማርሻዬ ባደረጉት ንግግር #ዛሬ በአንድነት #እና በጋራ በመስራት ሀገራችንን በላባችን እና በመሰዋዕትነት ልናሳድገት ይገባል ያሉ ሲሆን የሃይማኖት እና የብሔር ብዝሃነት ጸጋችንን በመጠቀም ሰላማችንን ለማምጣት እኛ ክርስቲያኖች #ምሳሌ በመሆን ልንኖር ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ ለሃዋሳ ከተማችን መለወጥ #ወንጌል ትልቁን ድርሻ እንደሚወስድ በመጥቀስ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽዖ የከተማ አስተዳደሩ እና የሲዳማ ክልል ለ4 የወንጌላውያን መሪዎች እውቅና ሰጥቷል።
ኑሮዓቸውን በአሜሪካ ላደረጉት ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና ፤ ለኢትዮያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ለፓስተር ጻዲቁ አብዶ ፤ ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ እና ለሃዋሳ ሕይወት ብረሃን ቤተክርስቲያን ዋና መጋቢ ፓስተር ጌቱ አያሌው እውቅናው እና ሽልማቱ ተሰቷቸዋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከስፍራው በ Facebook እና youtube ቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት እያስተላለፍን ስለሆነ እንድትከታተሉን እንጋብዛለን። https://www.youtube.com/watch?v=tHQFuhBnp5M 🙏🙏🙏
❤9👍3🔥1
#አሁን ከሃዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም #livestreaming ከሁሉም አለም አብራችሁን ሁኑ ለሌሎች እንዲደርስ Share አድርጉ !!! https://www.youtube.com/watch?v=cM6Ep-t62b0
YouTube
Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2 እሁድ ከሰዓት
Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2 እሁድ ከሰዓት
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel…
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel…
❤1👍1🔥1
ያልተቋረጠ ድንቅ አምልኮ በቀጥታ ከሃዋሳ #ድንቅ አምልኮ ከሃዋሳ በቀጥታ ስርጭት Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2 እሁድ https://youtube.com/live/n4Qi9tTG0zY
YouTube
#ድንቅ አምልኮ ከሃዋሳ በቀጥታ ስርጭት Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2 እሁድ
Day 2🔴 #ቀጥታ ስርጭት //ኑ ወደ እግዚአብሔር እንመለስ//የምልጃ እና የንሰሓ ኮንፍራንስ በሐዋሳ//ቀን 2 እሁድ ከሰዓት
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel…
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_በቴሌግራም_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome to Our channel…
🔥4👍2❤1
በድል #ተጠናቀቀ #እግዚአብሔር ይመስገን!!!
በሀዋሳ #ኢንተርናሽናል ስታዲየም በግንቦት 16 እና 17 ከተማ አቀፍ የንስሃና የተሃድሶ ፕሮግራም በድል በጥሩ ውጤት ተጠናቀቀ።
“የእስራኤል ቅዱስ፥ ጌታ #እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፤ በጸጥታና በመታመን ኃይል ይሆንላችኋል፤ እናንተም እንቢ አላችሁ፥”
ኢሳይያስ 30፥15
የሲዳማ ክልል ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ከየሀዋሳ ከተማ ዞን ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት እና የሲዳማ ክልል ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል በጥምረት የተዘጋጀው "ኑ ወደ #እግዚአብሔር እንመለስ" በሚል የምልጃ እና የንሰሐ ኮንፍራንስ በብዙ ድምቀት ተጠናቋል።
በሐዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም በተካሄደው ኮንፍራንስ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር መኩሪያ ማርሻዬን ጨምሮ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የሃዋሳ ከተማ ቅዱሳን በመረሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከስፍራው በ Facebook እና youtube ቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት ስናስተላልፍ የነበረ ሲሆን በስፍራው የቀጥታ ሆነው ስርጭቱን እንድናስተላልፍ የፈቀዱልን የፕሮግራሙ አስተባባሪ መሪዎች እና Amanuel Audion Video International Asfaw Ashagre ፤ Yididiya Bethelhem እና ወንድም ዳዊት ከልብ እናመሰግናለን!!!
በሀዋሳ #ኢንተርናሽናል ስታዲየም በግንቦት 16 እና 17 ከተማ አቀፍ የንስሃና የተሃድሶ ፕሮግራም በድል በጥሩ ውጤት ተጠናቀቀ።
“የእስራኤል ቅዱስ፥ ጌታ #እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፤ በጸጥታና በመታመን ኃይል ይሆንላችኋል፤ እናንተም እንቢ አላችሁ፥”
ኢሳይያስ 30፥15
የሲዳማ ክልል ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ከየሀዋሳ ከተማ ዞን ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት እና የሲዳማ ክልል ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል በጥምረት የተዘጋጀው "ኑ ወደ #እግዚአብሔር እንመለስ" በሚል የምልጃ እና የንሰሐ ኮንፍራንስ በብዙ ድምቀት ተጠናቋል።
በሐዋሳ አለም አቀፍ እስታድየም በተካሄደው ኮንፍራንስ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር መኩሪያ ማርሻዬን ጨምሮ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የሃዋሳ ከተማ ቅዱሳን በመረሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና ከስፍራው በ Facebook እና youtube ቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት ስናስተላልፍ የነበረ ሲሆን በስፍራው የቀጥታ ሆነው ስርጭቱን እንድናስተላልፍ የፈቀዱልን የፕሮግራሙ አስተባባሪ መሪዎች እና Amanuel Audion Video International Asfaw Ashagre ፤ Yididiya Bethelhem እና ወንድም ዳዊት ከልብ እናመሰግናለን!!!
👍8❤2🙏2🔥1
#እኔ_እያለሁ_ቸርች_አትወረስም...
ልትወረስ 15 ቀን የቀራት ቸርች እናድን
ሁላችንም የ500 ብር ቻሌንጅ በመቀላቀል ቤተክርስቲያንን እንታደግ...
እባክዎ መልዕክቱን ሼር ያድርጉ
ልትወረስ 15 ቀን የቀራት ቸርች እናድን
ሁላችንም የ500 ብር ቻሌንጅ በመቀላቀል ቤተክርስቲያንን እንታደግ...
እባክዎ መልዕክቱን ሼር ያድርጉ
👍14❤1🔥1
#ዛሬ አይቀርም።
#ልትወረስ 15 ቀን ለቀራት ቤተክርስቲያን 😭🥺
ሁላችንም የ500 ብር ቻሌንጅ በመቀላቀል ቤተክርስቲያንን እንታደግ።
የቤተክርስቲያኒቱ የሂሳብ ቁጥር
ርሆቦት የህይወት መንገድ አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን
ንግድ ባንክ ፥ 1000685337391
አቢሲንያ ባንክ ፥ 220 466 655
ብርሃን ባንክ ፥ 1600420110376
አዋሽ ባንክ ፥013521542623700
ኦሮምያ ህብረት ስራ ባንክ ፥ 1008100180768
ቴሌ ብር ፥ 0975836154
#ዛሬ ምሽት ለዚህች ቤተክርስቲያን በክርስቲያን ቲዩብ የፌስቡክና የዩቲዩብ ቻናል የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም እናደርጋለን !
#ልትወረስ 15 ቀን ለቀራት ቤተክርስቲያን 😭🥺
ሁላችንም የ500 ብር ቻሌንጅ በመቀላቀል ቤተክርስቲያንን እንታደግ።
የቤተክርስቲያኒቱ የሂሳብ ቁጥር
ርሆቦት የህይወት መንገድ አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን
ንግድ ባንክ ፥ 1000685337391
አቢሲንያ ባንክ ፥ 220 466 655
ብርሃን ባንክ ፥ 1600420110376
አዋሽ ባንክ ፥013521542623700
ኦሮምያ ህብረት ስራ ባንክ ፥ 1008100180768
ቴሌ ብር ፥ 0975836154
#ዛሬ ምሽት ለዚህች ቤተክርስቲያን በክርስቲያን ቲዩብ የፌስቡክና የዩቲዩብ ቻናል የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም እናደርጋለን !
👍6❤4🔥2