The Christian News
5.08K subscribers
3.66K photos
52 videos
911 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#አስደሳች #ዜና
ታፍነው የተወሰዱት ፓስተር ተለቀቁ

በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ስብከት ላይ እያሉ በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱት አሜሪካዊው ፓስተር በደቡብ አፍሪካ ፖሊሶች ድጋፍ መለቀቃቸውን ፎክስ ዜና አስነብቧል።

ባሳለፍነው ሃሙስ በደቡብ አፍሪካ ፌሎሺፕ ባፕቲስት ቸርች ኢን ማዘርዌል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየሰበኩ የነበሩ ጆሽ ሱሌቫን የተባሉ አሜሪካዊ ፓስተር "አራት የታጠቁ እና ጭምብል ያጠለቁ ወንዶች ናቸው ፓስተሩን አፍነው የወሰዷቸው" ሲሉ የፖሊስ ቃል አቀባይ ካፕቴን አንድሬ ቤቴጅ ለቢቢሲ መግለጻቸው ይታወሳል።

ፎክስ ኒውስ ከሰዓት በፊት ይዞት በወጣው ዘገባ የደቡብ አፍሪካ የምስራቅ ኬፕ ግዛት ባለስልጣናት ማክሰኞ እለት በተከፈተ የተኩስ እሩምታ ታፍኖ የነበረውን አሜሪካዊ ፓስተር ማዳን መቻላቸው ገልጸዋል ሲል ዘግቧል።

የ34 ዓመቱ ፓስተር ወደ ደቡብ አፍሪካ ከቤተሰባቸው ጋር ያቀኑት በፈረንጆቹ 2018 ሲሆን፣ አላማቸውም በዦሳ ቋንቋ አገልግሎት የሚሰጥ ቤተ ክርስቲያን መመሥረት እንደነበር ዘገባው አክሏል።
👍137🔥1🙏1💔1
የበዓል ስጦታ ከWSG ሚኒስትሪ

WSG የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤን ምክኒያት በማድረግ ለ1ሺህ አባወራዎች የምግብ ድጋፍ አደረገ።

WSG ድጋፉን ብራይት ስታር ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው ከ1ሺህ ለሚበልጡ አባወራዎች የምግብ እና ሌሎች ቁሳቁሶች ድጋፍ ያደረገው።

ድጋፉ የተደረገው የብራይት ስታር ፍሪደም ት/ቤት ተማሪ ወላጆችና የመንግስት ት/ቤት ለሚገኙ ተማሪ ወላጆች ነው ያደረገው።

የWSG ሚኒስትሪ አስተባባሪ ወ/ሮ ሃዊ በዳሳ ስጦታው ሁሉም በየቤቱ ፋሲካን በደስታ እንዲያስተላልፍ የታሰበ ነው፡ ስለዚህ እንኳን ደስ አደረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

WSG የከፋ ድህነት ውስጥ ለሚገኙ ቤተሰቦች፡ ለጥፋት የተጋለጡና ማደሪያቸውን ጎዳና ላደረጉ ወጣቶች የመንፈሳዊና ቁሳዊ ድጋፍ ያደርጋል።

ከዚህ በተጨማሪ WSG (Win Souls for God Evangelical Ministry) በአውሮፓ በተለይም በስዊድን ለሚገኙ ወገኖች (Mission back to Europe) በሚል ስያሜ የታረደውን በግ ኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል መስበነክ ላይ ይገኛል።
መረጃውን ጋዜጠኛ ጸጋይብጻህ ኢሳይያስ አደረሰን።
👏73👍1🔥1
ሲቃዩ ሊብራራ አይችልም። የመጨረሻውን ስቃይ ተሰቃየ #ሰሙነ #ሕማማት ከሆሳዕና #እስከ ትንሳኤ #እና ፕሮግራም

ከኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን ጋር በመተባበር የተዘጋጀ #እና ለተከታታይ 8 ቀናት እየተላለፈ የሚገኝ በየቀኑ በኢቫንጀሊካል ቴሌቪዥን ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ .. የተለያዩ አገልጋዮች ሰሙነ ሕማማቱን እየተረኩር #ዛሬ ደርሰናል። በሚያገኙት አማራጭ ይከታተሉ።

በማሕበራዊ #ሚዲያ በThe Christian News YouTube channel ላይ ይመልከቱ። https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A?sub_confirmation=1
👍7😭32🔥2🙏1
የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በገረሴ ከተማ አደባባይ በወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በድምቀት ተከበረ።

በመዝሙርና በቃል፣ በድምቀት ተከብሯል።

ገረሴ-ውልአ

በያላችሁበት አከባቢ እንዴት እየተከበረ ነዉ ? ፎቶዎች ላኩልን 🙏🙏
👍41🔥1
የወለንጭቲ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት የትንሳኤ በዓል በጋራ አከበሩ።

ዛሬ ሚያዝያ 12/08/2017 ከማለዳው 11ሰዓት ጀምሮ በፕሮግራሙ ላይ የቦሰት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ጉተማ ቢፍቱ በመገኘት #እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ስላስተላለፉልን በህብረቱ ስም አመስግነዋል።

አጠቃላይ ፕሮግራሙ ላይ በዝማሬ በቃል በወረብ አምልኮ ለሀገር በመጸለይ የተከናወነ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ የምስራቅ ሸዋ ዞን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ሰብሳቢ ፖስተር ሰለሞን ሽፈራዉ እና የቦሰት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በመገኘት እንኳን አደረሳችሁ አስተላልፈዋል::

መሪዎች ከስፍራው ላደረሳችሁን መረጃ ከልብ እናመሰግናለን 🙏🙏
🔥41👍1
ፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸዉን ታዉቋል።

ሊቀ ጳጳሱ ባደረባቸው ከፍተኛ የሳንባ ሕመም የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ቆይተው በዛሬው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ቫቲካን አስታውቃለች፡፡

The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለኢትዮጵያውያን የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ምዕመናን መፅናናትን እንመኛለን።
👍16😭3🤔1🕊1💔1
የ2017 ፓስተርስ ኮንፈራንስ ተጀመረ

ከሚያዝያ 15-17 የሚቆየው አመታዊው ፓስተርስ ኮንፈራንስ በአድዋ 00 መሰብሰቢያ አዳራሽ በይፋ ተጀምሯል።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት አዘጋጅነት የሚካሄደው ኮንፈራንሱ ከመላ ሃገሪ የተወጣጡ ወደ 5ሺህ የሚጠጉ አገልጋዮች እና መሪዎች ለ3 ቀናት በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠናዎችን ይወስዳሉ።

የዘንድሮው አመት ኮንፈራንስ "ክርስቲያናዊ እሴቶችን በማጎልበት የክርስቶስን መልክ የምታንጸባርቅ ቤተ፡ክርስቲያን ማነጽ በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል።"

በስልጠናው
• ክርስቲያናዊ አመራር
• የወንጌል ተልዕኮ
• ሰላምና እርቅ
• የልጆች አገልግሎት
• ወጣት መሪዎች ማፍራት እና
• ግለ ሁለንተናን መንከባከብ

የሚሉ ጉዳዮች በስፋት ይነሳሉ።

በመድረኩ "99 አድቬንቸርስ በመጽሃፍ ቅዱስ ትልቅ ታሪክ ውስጥ" ህብረቱ ለልጆች ማስተማሪያ ያዘጋጀው መጽሃፍ በጸሎት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

የፓስተርስ ኮንፈራንሱ ህብረቱ ለሚያከብረው የ50 ዓመት እዮቤልዩ የመጀመሪያ ምዕራፍ ነው።
👍14👏96🔥1
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት የ50ኛ የወርቅ እዮቤልዩ ክብረ በዓል በድምቀት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም እየተከበረ ነዉ።

ባለፉት 2 ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ አመታዊው ፓስተርስ ኮንፈራንስ በዛሬዉ እለት የተጠናቀቀ ሲሆን ሕብረቱ በአሁኑ ሰዓት የምስረታ 50ኛዉን የወርቅ ኢዮቤልዩ መክፈቻ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች በተገኙበት በድምቀት ማክበር ጀምሯል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራዉ የምንገኝ ሲሆን ተጨማሪ ዝርዝር ይዘን እንመለሳለን።
👍206🔥1🙏1💯1
እኔ የኢየሱስ ነኝ
I BELONG TO JESUS

#Ethiopia | የሊቨርፑሉ አጥቂ ኮዲ ጋክፖ ትላንት ምሽት ክለቡ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ዋንጫ ማንሳቱን ባረጋገጠበት ጨዋታ ጎል በማስቆጠር እኔ የኢየሱስ ነኝ" የሚል ጽሑፍ የያዘ ቲሸርት በማሳየት ወንጌልን ለዓለም ሰብኳል።

ከዚህ ቀደም ብራዚላዊው ካካ በተመሳሳይ ወንጌልን በዚህ መልክ በመስበክ የሚታወቅ ተጫዋች ነው።
33👍8👏3🔥2🙏2👌1