የአጥቢያ #ቤተክርስቲያን የቤተሰብ አገልግሎት ምን ምን መካተት ሊኖርበት ይገባል?
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ሚኒስትሪ ከ20 በላይ አብያተ ክርስቲያናት ለተወጣጡ አገልጋዮች ቤተሰብ ተኮር ስልጠና ሰጠ።
ስልጠናው ለሁለት ቀናት በቀነኒሳ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ተወካዮች ከስልጠናው መልስ በሚሄዱባቸ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ቤተሰብ ተኮር ስራዎችን መስራት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተነግሯል።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ሚኒስትሪ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሳሮን ውድነህ፣ ስልጠናው አንዲት ጠንካራ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እንዴት የቤተሰብ አገልግሎት ይኖራታል፣ ምን ምን መካተት ይኖርበታል፣ አለመኖሩ ምንም ምን ችግሮችን ያመጣል በሚሉ ወሳኝ ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ውይይት መካሄዱን
ለክርስቲያን ዜና ገልጸዋል።
ዘ ክርስቲያን ኒውስ ያናገራቸው የስልጠናው ተካፋዮች እንደ አገልጋይም እንደ ባለትዳርም ብዙ የተጠቀምንበት ስልጠና ነው ብለውታል።
እዚህ የተገኘው ልምድ ወደ ቤት ተወስዶ የሚኖር ነው ሲሉ ገልጸውታል።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ፣ ጠንካራቤተሰብ፣ ለቤተ ክርስቲያን ህልውና እና ለታላቁ ተልዕኮ ወሳኝ ነው ብሎ ያምናል። በመሆኑም ይላሉ ወ/ሮ ሳሮን አብያተ ክርስቲያናት ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራዉ ተገኝተን ዝርዝሩን አቀረብንላችሁ።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ሚኒስትሪ ከ20 በላይ አብያተ ክርስቲያናት ለተወጣጡ አገልጋዮች ቤተሰብ ተኮር ስልጠና ሰጠ።
ስልጠናው ለሁለት ቀናት በቀነኒሳ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ተወካዮች ከስልጠናው መልስ በሚሄዱባቸ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ቤተሰብ ተኮር ስራዎችን መስራት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተነግሯል።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ ሚኒስትሪ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሳሮን ውድነህ፣ ስልጠናው አንዲት ጠንካራ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እንዴት የቤተሰብ አገልግሎት ይኖራታል፣ ምን ምን መካተት ይኖርበታል፣ አለመኖሩ ምንም ምን ችግሮችን ያመጣል በሚሉ ወሳኝ ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ውይይት መካሄዱን
ለክርስቲያን ዜና ገልጸዋል።
ዘ ክርስቲያን ኒውስ ያናገራቸው የስልጠናው ተካፋዮች እንደ አገልጋይም እንደ ባለትዳርም ብዙ የተጠቀምንበት ስልጠና ነው ብለውታል።
እዚህ የተገኘው ልምድ ወደ ቤት ተወስዶ የሚኖር ነው ሲሉ ገልጸውታል።
የቤተሰብ ቅጥር አዳሽ፣ ጠንካራቤተሰብ፣ ለቤተ ክርስቲያን ህልውና እና ለታላቁ ተልዕኮ ወሳኝ ነው ብሎ ያምናል። በመሆኑም ይላሉ ወ/ሮ ሳሮን አብያተ ክርስቲያናት ለቤተሰብ አገልግሎት ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል።
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራዉ ተገኝተን ዝርዝሩን አቀረብንላችሁ።
👍9❤2🔥1
#እሁድ የት ናቹ ? #ምክንያቴ #ብዙ ነው።
#እግዚአብሔር ሰውን ለአላማው ከፈለገው ከምን አንስቶ እንደሚጠቀምበት ፓስተር ተከስተ ጌትነት ህያው ማሳያ ነው።
የትናንቱ ቆሎ ተማሪ የዛሬው ፓስተር ተከስተ ላለፉት ሀያ አምስት አመታት በላይ በዘለቀው አገልግሎቱ ተሰምተው የማይጠገቡ፣ ተደምጠው የማይሰለቹ የዝማሬ አልበሞችን አውጥቶ ለሚሊዮኖች የመባረክ ምክንያት ሲያደርገው የተመለከተ እግዚአብሔር ይችላል እንጅ ሌላ ምን ሊል ይችላል?
የመጋቢ ተከስተ ጌትነት ዝማሬዎች የዜማ ምጥቀት፣ የግጥም ጥልቀት የብዙሀንን ልብ ለወንጌሉ ወለል አድርገው ያስከፈቱ ሚሊዮኖችን ለጌታ ፍቅር ያንበረኩኩ ሀያል የወንጌል መሳሪያዎች ሆነው ለአመታት እየተደመጡ ዘልቀዋል።
ተኬ በ80ዎቹ መጨረሻ በኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን አሀዱ ተብሎ የተጀመረው የዝማሬ ጉዞው በብዙ ድልና በብዙ መውደቅ መነሳት ዛሬ እዚህ ደርሶ ምክንያቴ ብዙ ነው ብለን አብረነው ጌታን ልናመልክ እንሆ ቀኑ ተቆርጧል።
መጋቢት 14 ከሰዓት በጊዮን ሆቴል እንገናኝ።
ለማመስገን ምክንያታችን ብዙ ነው።
#እግዚአብሔር ሰውን ለአላማው ከፈለገው ከምን አንስቶ እንደሚጠቀምበት ፓስተር ተከስተ ጌትነት ህያው ማሳያ ነው።
የትናንቱ ቆሎ ተማሪ የዛሬው ፓስተር ተከስተ ላለፉት ሀያ አምስት አመታት በላይ በዘለቀው አገልግሎቱ ተሰምተው የማይጠገቡ፣ ተደምጠው የማይሰለቹ የዝማሬ አልበሞችን አውጥቶ ለሚሊዮኖች የመባረክ ምክንያት ሲያደርገው የተመለከተ እግዚአብሔር ይችላል እንጅ ሌላ ምን ሊል ይችላል?
የመጋቢ ተከስተ ጌትነት ዝማሬዎች የዜማ ምጥቀት፣ የግጥም ጥልቀት የብዙሀንን ልብ ለወንጌሉ ወለል አድርገው ያስከፈቱ ሚሊዮኖችን ለጌታ ፍቅር ያንበረኩኩ ሀያል የወንጌል መሳሪያዎች ሆነው ለአመታት እየተደመጡ ዘልቀዋል።
ተኬ በ80ዎቹ መጨረሻ በኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን አሀዱ ተብሎ የተጀመረው የዝማሬ ጉዞው በብዙ ድልና በብዙ መውደቅ መነሳት ዛሬ እዚህ ደርሶ ምክንያቴ ብዙ ነው ብለን አብረነው ጌታን ልናመልክ እንሆ ቀኑ ተቆርጧል።
መጋቢት 14 ከሰዓት በጊዮን ሆቴል እንገናኝ።
ለማመስገን ምክንያታችን ብዙ ነው።
👍28❤16🔥1🙏1
#የመሠረተ #ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን #አዲስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሾመች።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ መጋቢት 12 እና 13፤ 2017 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛው መደበኛ ስብሰባ ለቀጣይ አራት አመታት ቤተክርስቲያኒቱን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ መጋቢ ሰብረላ ከድርን ሾሟል።
መጋቢ ሰብረላ ከደር በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ላለፋት 33 አመታት ከአጥቢያ ጀምሮ ያገለገሉ ሲሆን በተለይ ባለፈው ስድስት አመት በዋናው ቢሮ የእረኝነት አገልግሎት መምሪያ ከፍተኛ ለውጥ ማስመዝገባቸው ይታወሳል።
የሹመት ስነስርዓቱን ያስፈጸሙት የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ለቤተክርስቲያን ሰውን የሚሰጠው #እግዚአብሔር እንደሆነ በመግለፅ አዲሱ ምክትል ፕሬዚዳንትም ከእግዚአብሔርና ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን አደራ በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል።
#መሠረተ_ክርሰቶስ_ቤተክርስቲያን!
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አስተዳደር መሪዎች ጉባኤ መጋቢት 12 እና 13፤ 2017 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛው መደበኛ ስብሰባ ለቀጣይ አራት አመታት ቤተክርስቲያኒቱን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ መጋቢ ሰብረላ ከድርን ሾሟል።
መጋቢ ሰብረላ ከደር በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ላለፋት 33 አመታት ከአጥቢያ ጀምሮ ያገለገሉ ሲሆን በተለይ ባለፈው ስድስት አመት በዋናው ቢሮ የእረኝነት አገልግሎት መምሪያ ከፍተኛ ለውጥ ማስመዝገባቸው ይታወሳል።
የሹመት ስነስርዓቱን ያስፈጸሙት የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ለቤተክርስቲያን ሰውን የሚሰጠው #እግዚአብሔር እንደሆነ በመግለፅ አዲሱ ምክትል ፕሬዚዳንትም ከእግዚአብሔርና ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን አደራ በትጋት እንዲወጡ አሳስበዋል።
#መሠረተ_ክርሰቶስ_ቤተክርስቲያን!
👍11❤5🔥2🙏1👌1
7 #አገልጋዮች ታስረዋል። #ቤተክርስቲያን አሁንም ስደት እየደረሰባት ነው። ካውንስሉ
#የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎች በወንጌል አማኞች ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት እና እስር በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።
ከደቂቃዎች በፊት በተሰጠው መግለጫ በጅማ ፤ በከሰም ቀበና ፤ በጅግጅጋ እና በቦምባስ ከተማዎች በወንጌላውያን ላይ እየረሰው ያለው እስር እና እንግልት እንዲሁም ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥፋት እንዲቆም ጠይቋል።
#ካውንስሉ በመግለጫው ይህ መግለጫ እስኪሰጥበት ደቂቃ ድረስ በጅግጅጋ እና በቦምባስ ከተማ 7 ምዕመናን በእምነታችው ምክንያት እንደታሰሩ ገለጿል።
#በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ የምትገኘው ማሕበረ ምዕመናን ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ድብደባ እና የጸሎት ቤት መቃጠልን ያስታወሰው መግለጫው ምዕመናን የጸሎት ቤቱ ፈርሶባቸው አሁንም በሜዳ ላይ እያመለኩ እንደሚገኙ ጠቅሷል።
በተመሳሳይ #በአፋር ክልል በዱለቻ ወረዳ ውስጥ ባሉ የከሰም ቀበና እና በድሆ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ላይ ዝርፊያ እና ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየተደረገ እንደሆነ በመግለጫው ተጠቅሷል።
#በሱማሌ ክልል ደግሞ በጅግጅጋ እና በቦምባስ ከተማ ውስጥ በድምሩ 7 ምዕመናን በእርስ ላይ እንደሚገኙ በመጥቀስ የሚመለከተው አካላት በእምነታቸው ምክንያት ለእስር የተዳረጉ ምዕመናን እንዲፈቱ ካውንስሉ ጠይቋል።
ካውንስሉ በመግለጫው የእኔ ሃይማኖት የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ባዮች በአከባቢያችን ሌላ እምነት በነጻነት ሊንቀሳቀስ አይገባም በማለት ከሃይማኖት አልፈው ሰላም እና ሁከት በሚፈጥሩ አካላይ ሕጋዊ የእርምት እርምጃ በመውሰድ ከጊዜ ወደ ጊዜ የተባባሰውን ሃይማኖታዊ ጥላቻ እንዲቆም የሚመለከተውን አካላት ጠይቋል።
#የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎች በወንጌል አማኞች ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት እና እስር በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።
ከደቂቃዎች በፊት በተሰጠው መግለጫ በጅማ ፤ በከሰም ቀበና ፤ በጅግጅጋ እና በቦምባስ ከተማዎች በወንጌላውያን ላይ እየረሰው ያለው እስር እና እንግልት እንዲሁም ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥፋት እንዲቆም ጠይቋል።
#ካውንስሉ በመግለጫው ይህ መግለጫ እስኪሰጥበት ደቂቃ ድረስ በጅግጅጋ እና በቦምባስ ከተማ 7 ምዕመናን በእምነታችው ምክንያት እንደታሰሩ ገለጿል።
#በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ ጋትራ ከተማ የምትገኘው ማሕበረ ምዕመናን ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ድብደባ እና የጸሎት ቤት መቃጠልን ያስታወሰው መግለጫው ምዕመናን የጸሎት ቤቱ ፈርሶባቸው አሁንም በሜዳ ላይ እያመለኩ እንደሚገኙ ጠቅሷል።
በተመሳሳይ #በአፋር ክልል በዱለቻ ወረዳ ውስጥ ባሉ የከሰም ቀበና እና በድሆ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ላይ ዝርፊያ እና ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየተደረገ እንደሆነ በመግለጫው ተጠቅሷል።
#በሱማሌ ክልል ደግሞ በጅግጅጋ እና በቦምባስ ከተማ ውስጥ በድምሩ 7 ምዕመናን በእርስ ላይ እንደሚገኙ በመጥቀስ የሚመለከተው አካላት በእምነታቸው ምክንያት ለእስር የተዳረጉ ምዕመናን እንዲፈቱ ካውንስሉ ጠይቋል።
ካውንስሉ በመግለጫው የእኔ ሃይማኖት የበላይነት ሊረጋገጥ ይገባል ባዮች በአከባቢያችን ሌላ እምነት በነጻነት ሊንቀሳቀስ አይገባም በማለት ከሃይማኖት አልፈው ሰላም እና ሁከት በሚፈጥሩ አካላይ ሕጋዊ የእርምት እርምጃ በመውሰድ ከጊዜ ወደ ጊዜ የተባባሰውን ሃይማኖታዊ ጥላቻ እንዲቆም የሚመለከተውን አካላት ጠይቋል።
👍18❤4🙏3🕊1😭1
#በካፋ ዴቻ የክርስቶስ #ኢየሱስ ደቀመዛሙርት የሆኑት መጽሐፍ ቅዱስን በመማር ለመድረክ አገልግሎት የበቁ በሰርተፍኬት ተመረቁ።
#በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት በምዕራብ ደቡብ ቀጣና ቦንጋ ዙሪያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያናት ሕብረት በቦባ ገጫ ቃ/ሕ/ቤያን ላለፉት 7 ወራትን የደቀመዛሙርት ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ በክብር በድል ለመድረክ አገልግሎት የመብቃት ሰርተፍኬት በምረቃ ተቀብለዋል።
#የደቀመዛሙርትን ምረቃ ስነ-ስርዓት በማስፈጸም ከቦንጋ ዙሪያ ቃ/ሕ/ቤያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት የሕብረቱ መንፈሳዊ ዘረፉ ፦ወንጌላዊ መለሰ መሮ እንዲሁም የተጠሩ የአብያተክርስቲያናት ሕብረትም ተገኝቷል።
#ወንጌልን ወደ ውጭ መስበክ ወደ ውስጥ ደቀመዛሙርት በማድረግ መስራት የተሰጠን የተልዕኮአችን ዋነኛውና ቀዳሚ አደራነት ያለው አገልግሎት ነውና በያለንበት ቦታ ሁሉ ወንጌልን ላልዳኑት እየሰበክን የዳኑትን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት በማድረግ ወንጌልን ከቀድሞም ይልቅ መስራት አለብን እግዚአብሔር እንድንሰራ በጸጋው እንዲረዳን መልዕክት አስተላልፈዋል።
መረጃውን ሚሽነሪ አክሊሉ ከካፋ ዞን አደረሰን።
#በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት በምዕራብ ደቡብ ቀጣና ቦንጋ ዙሪያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያናት ሕብረት በቦባ ገጫ ቃ/ሕ/ቤያን ላለፉት 7 ወራትን የደቀመዛሙርት ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ በክብር በድል ለመድረክ አገልግሎት የመብቃት ሰርተፍኬት በምረቃ ተቀብለዋል።
#የደቀመዛሙርትን ምረቃ ስነ-ስርዓት በማስፈጸም ከቦንጋ ዙሪያ ቃ/ሕ/ቤያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት የሕብረቱ መንፈሳዊ ዘረፉ ፦ወንጌላዊ መለሰ መሮ እንዲሁም የተጠሩ የአብያተክርስቲያናት ሕብረትም ተገኝቷል።
#ወንጌልን ወደ ውጭ መስበክ ወደ ውስጥ ደቀመዛሙርት በማድረግ መስራት የተሰጠን የተልዕኮአችን ዋነኛውና ቀዳሚ አደራነት ያለው አገልግሎት ነውና በያለንበት ቦታ ሁሉ ወንጌልን ላልዳኑት እየሰበክን የዳኑትን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት በማድረግ ወንጌልን ከቀድሞም ይልቅ መስራት አለብን እግዚአብሔር እንድንሰራ በጸጋው እንዲረዳን መልዕክት አስተላልፈዋል።
መረጃውን ሚሽነሪ አክሊሉ ከካፋ ዞን አደረሰን።
👍11🔥2❤1🙏1
ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚረዱ የመጽሐፍት ድጋፍ ከራፊኪ ፋውንዴሽን ለኢት/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ተደርጓል፡፡
መጽሐፍቶቹን የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሣ ፋውንዴሽኑ ከሚገኝበት ሞጆ ከተማ በመገኘት ከራፊኪ ፋውንዴሽን አለምአቀፍ ዳይሬክተር ካሬን ኤሊዬት እና ሌሎች የተቋሙ አህጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ አመራር ተረክበዋል፡፡
ራፊኪ ፋውንዴሽን በተለያዩ 10 የአፍሪካ ሀገራት መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፤ በትምህርት፤ በመምህራን ስልጠና፤ በወላጅ አልባ ህጻናት እና ባልቴቶች ድጋፍ የሚሰራ አህጉር አቀፍ ተቋም ሲሆን ከኢት/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ጋር በመተባበር በተጠቀሱት የትኩረት አቅጣጫዎች ዙርያ እየሰራ ይገኛል፡፡
መጽሐፍቶቹ ልጆች እና ወጣቶችን በእግዚአብሔር ቃል ቀርጾ ለማሳደግ የሚረዱ፤ ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የሚረዱ እና በልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ተቀርጾ እየተሰራ ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ፤ ሁለንተናዊ ቤተመጻህፍትን በየማህበረምዕመናኑ ማደራጀት ለሚለው የትኩረት አቅጣጫ ጠቃሚ መሆናቸውን የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሣ ገልጸው፤ ለአገልግሎቱ ለተደረገው ድጋፍ ራፊኪ ፋውንዴሽንን አመስግነዋል፡፡
የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ መጽሀፎቹን በአይራ ከተማ ለሚገኘው የቤተክርስቲያኒቱ ኦነስሞስ ነሲብ ሴሚናሪዮም እና በግምቢ ጆርጎ ሲኖዶስ ግምቢ ከተማ ለሚገኘው ለግምቢ ሁለንተናዊ ሴሚናሪ የመጽሐፍት ድጋፍ አድርጓል።
መጽፍቶቹንም ወንድማገኝ ኡዴሳ በምዕራብ ወለጋ አይራ ከተማ በመገኘት ለሴሚናሪው ፕሪንሲፓል ቄስ አለሙ ብርሃኑ እና በግምቢ ከተማ በመገኘት ለሴሚናሪው ዲን ቄስ ተስፋ ኡጁሉ በማስረከብ በሴሚናሪዎቹም ጉብኝት አድርገዋል።
መጽሐፍቶቹን የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሣ ፋውንዴሽኑ ከሚገኝበት ሞጆ ከተማ በመገኘት ከራፊኪ ፋውንዴሽን አለምአቀፍ ዳይሬክተር ካሬን ኤሊዬት እና ሌሎች የተቋሙ አህጉር አቀፍ እና ሀገር አቀፍ አመራር ተረክበዋል፡፡
ራፊኪ ፋውንዴሽን በተለያዩ 10 የአፍሪካ ሀገራት መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፤ በትምህርት፤ በመምህራን ስልጠና፤ በወላጅ አልባ ህጻናት እና ባልቴቶች ድጋፍ የሚሰራ አህጉር አቀፍ ተቋም ሲሆን ከኢት/ወ/ቤ/ክ/መካነ ኢየሱስ ጋር በመተባበር በተጠቀሱት የትኩረት አቅጣጫዎች ዙርያ እየሰራ ይገኛል፡፡
መጽሐፍቶቹ ልጆች እና ወጣቶችን በእግዚአብሔር ቃል ቀርጾ ለማሳደግ የሚረዱ፤ ለመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የሚረዱ እና በልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ተቀርጾ እየተሰራ ባለው ሁለንተናዊ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት ፓኬጅ፤ ሁለንተናዊ ቤተመጻህፍትን በየማህበረምዕመናኑ ማደራጀት ለሚለው የትኩረት አቅጣጫ ጠቃሚ መሆናቸውን የመምሪያው ዳይሬክተር ወንድማገኝ ኡዴሣ ገልጸው፤ ለአገልግሎቱ ለተደረገው ድጋፍ ራፊኪ ፋውንዴሽንን አመስግነዋል፡፡
የኢ/ወ/ቤ/መ/ኢ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ መጽሀፎቹን በአይራ ከተማ ለሚገኘው የቤተክርስቲያኒቱ ኦነስሞስ ነሲብ ሴሚናሪዮም እና በግምቢ ጆርጎ ሲኖዶስ ግምቢ ከተማ ለሚገኘው ለግምቢ ሁለንተናዊ ሴሚናሪ የመጽሐፍት ድጋፍ አድርጓል።
መጽፍቶቹንም ወንድማገኝ ኡዴሳ በምዕራብ ወለጋ አይራ ከተማ በመገኘት ለሴሚናሪው ፕሪንሲፓል ቄስ አለሙ ብርሃኑ እና በግምቢ ከተማ በመገኘት ለሴሚናሪው ዲን ቄስ ተስፋ ኡጁሉ በማስረከብ በሴሚናሪዎቹም ጉብኝት አድርገዋል።
❤5👍3👏3🔥1
ክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቸርች ታገደ።
ክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቸርች በካውንስሉ በምዝገባ ቁጥር 03111 የተመዘገበች የሃይማኖት ተቋም መሆኗ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ ቤተክርስቲያኒቱ የካውንስሉ አባል ስትሆን ልታከናውናቸው ከሚገቡ መመሪያዎችና ደንቦች መካከል አንዱ የካውንስሉ አባላት ስነ ምግባር መመሪያ ሲሆን በስነ ምግባር መመሪያው አንቀጽ 9.3 ላይ የስነ ምግባር ግድፈቶች ተብለው በዝርዝር የተገለጹትን ተግባራት በቤተክርስቲያኒቱ መሪ መፈጸሙን አረጋግጠናል።
በመሆኑም ጉዳዩ በካውንስሉ ሥነ መለኮት ኮሚሽን እና የሕግ ኮሚሽን ታይቶ በሚመለከታቸው አካላት የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ የቤተክርስቲያኒቱ ፈቃድ ታግዶ የሚቆይ ሲሆን ሁሉም የካውንስሉ አስተዳደራዊ መዋቅሮችና የሚመለከታችሁ የመንግስት አካላት ይህንንና ከዚህ በኋላ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን እንድታስፈጽሙ በግልባጭ ተመዝግቦላችኋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል
ክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቸርች በካውንስሉ በምዝገባ ቁጥር 03111 የተመዘገበች የሃይማኖት ተቋም መሆኗ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ ቤተክርስቲያኒቱ የካውንስሉ አባል ስትሆን ልታከናውናቸው ከሚገቡ መመሪያዎችና ደንቦች መካከል አንዱ የካውንስሉ አባላት ስነ ምግባር መመሪያ ሲሆን በስነ ምግባር መመሪያው አንቀጽ 9.3 ላይ የስነ ምግባር ግድፈቶች ተብለው በዝርዝር የተገለጹትን ተግባራት በቤተክርስቲያኒቱ መሪ መፈጸሙን አረጋግጠናል።
በመሆኑም ጉዳዩ በካውንስሉ ሥነ መለኮት ኮሚሽን እና የሕግ ኮሚሽን ታይቶ በሚመለከታቸው አካላት የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ የቤተክርስቲያኒቱ ፈቃድ ታግዶ የሚቆይ ሲሆን ሁሉም የካውንስሉ አስተዳደራዊ መዋቅሮችና የሚመለከታችሁ የመንግስት አካላት ይህንንና ከዚህ በኋላ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን እንድታስፈጽሙ በግልባጭ ተመዝግቦላችኋል፡፡
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል
👍31👏5❤3🔥1😭1
#ቢሾፍቱ #ስለ #ወንጌል ትጣራለች።
ላለፉት 34 ዓመታት በቢሾፍቱ ከተማ ወንጌልን የማድረስ ስራን ሲከውን የቆየው የቢሾፍቱ ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ህብረት "ቢሾፍቱ ስለ ወንጌል ትጣራለች" በሚል ሃሳብ በዛሬው እለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።
በሰጡት መግለጫ ከ100 በላይ አባላት እና አጋር አባላትን ይዞ የሚያገለግል ሕብረት መሆኑን ጠቅሰው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአመት 2 ጊዜ የጀማ ስብከት እና የወንጌል ስርጭት በማድረግ ወደ ጌታ መንግስት የሚጨመሩትን አዳዲስ ነብሳት ላይ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዋል።
ሕብረቱ በአሁኑ ሰዓት የሰልጠና ማዕከላትን እና ደቀመዝሙራትን እና ተተኪ ትውልዶችን ለማፍራት የበለጠ ስራዎችን ለመስራት የራሱ የሆነ ሕንጻ ለመገንባት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ በመግለጫው በመጥቀስ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ ያሉ ምዕመናን በሙሉ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ሕብረቱን በመደገፍ ሂደት ውስጥ የማሕበራዊ ሚዲያ ባለሞያዎች እና ተጠቃሚዎች ንቅናቄውን በመሳተፍ አብረው እንዲያገለግሉ የክርስቲያን ሚዲያ ባለሞያዎች ማህበር ፕሬዝደንት ወንድም ዘሪሁን ግርማ በመግለጫው በመገኘት አሳስበዋል።
ፓስተር ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው ከፍተኛ የመንፈሳዊ ስራዎች ከሚሰራባቸው ሕብረቶ መካከል አንዱ የቢሾፍቱ ሕብረት መሆኑን በመጥቀስ በሕብረቱ የተገለገሉትን ጨምሮ በመላው አለም የሚገኙ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ስራ በጋራ እንድንሰራ እና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ነገር ለማስረከብ በጋራ እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አቀርበዋል።
https://gofund.me/6378ba81
ከ ወንጌል አማኙ ጎን አብሬ በተግባር እቆማለሁ እርሶስ???
- ንግድ ባንክ- 1000011144873
- ብርሃን ባንክ- 2600180029025
https://gofund.me/6378ba81
ላለፉት 34 ዓመታት በቢሾፍቱ ከተማ ወንጌልን የማድረስ ስራን ሲከውን የቆየው የቢሾፍቱ ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ህብረት "ቢሾፍቱ ስለ ወንጌል ትጣራለች" በሚል ሃሳብ በዛሬው እለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።
በሰጡት መግለጫ ከ100 በላይ አባላት እና አጋር አባላትን ይዞ የሚያገለግል ሕብረት መሆኑን ጠቅሰው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአመት 2 ጊዜ የጀማ ስብከት እና የወንጌል ስርጭት በማድረግ ወደ ጌታ መንግስት የሚጨመሩትን አዳዲስ ነብሳት ላይ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዋል።
ሕብረቱ በአሁኑ ሰዓት የሰልጠና ማዕከላትን እና ደቀመዝሙራትን እና ተተኪ ትውልዶችን ለማፍራት የበለጠ ስራዎችን ለመስራት የራሱ የሆነ ሕንጻ ለመገንባት እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ በመግለጫው በመጥቀስ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ ያሉ ምዕመናን በሙሉ የራሳቸውን አሻራ እንዲያሳርፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ሕብረቱን በመደገፍ ሂደት ውስጥ የማሕበራዊ ሚዲያ ባለሞያዎች እና ተጠቃሚዎች ንቅናቄውን በመሳተፍ አብረው እንዲያገለግሉ የክርስቲያን ሚዲያ ባለሞያዎች ማህበር ፕሬዝደንት ወንድም ዘሪሁን ግርማ በመግለጫው በመገኘት አሳስበዋል።
ፓስተር ጻዲቁ አብዶ በበኩላቸው ከፍተኛ የመንፈሳዊ ስራዎች ከሚሰራባቸው ሕብረቶ መካከል አንዱ የቢሾፍቱ ሕብረት መሆኑን በመጥቀስ በሕብረቱ የተገለገሉትን ጨምሮ በመላው አለም የሚገኙ ቅዱሳን የእግዚአብሔር ስራ በጋራ እንድንሰራ እና ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ነገር ለማስረከብ በጋራ እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አቀርበዋል።
https://gofund.me/6378ba81
ከ ወንጌል አማኙ ጎን አብሬ በተግባር እቆማለሁ እርሶስ???
- ንግድ ባንክ- 1000011144873
- ብርሃን ባንክ- 2600180029025
https://gofund.me/6378ba81
👍8❤4🔥2🙏1
የቤተክርስቲያን ወለል ተደርምሶ አራት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደረሰ።
ትላንት እሁድ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጎሮ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኘዉ ቤተክርስቲያን ዉስጥ አማኞች በአምልኮ ስነ-ስርዓት ላይ እያሉ ወለሉ ተደርምሶ አራት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የአምቡላንስ አገልግሎት ባለሞያዎች በአደጋዉ ቦታ ፈጥነዉ በመድረስ ተጎጂዎችን ከተደረመሰዉ ጉዳጓድ ዉስጥ በማዉጣት ለተጨማሪ ህክምና በአቅራቢዉ ወደሚገኘዉ ጎሮ ጤና ጣቢያ ማድረሳቸውን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴለቪዥን ተናግረዋል።
ለአደጋዉ ምክንያት የሆነዉም የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ክዳኑ በመደርመሱና ቤተክርስቲያኑ በመጸዳጃ ቤት ላይ የተሰራ በመሆኑ ነዉ። ጉዳት ከደረሰባቸዉ አራት ሰዎች መካከል ሶስቱ ሴቶች ናቸዉ።
የአምልኮ ስፍራዎች በርካታ ሰዎች የሚታደሙት ቦታ በመሆኑ ደረጃቸዉን የጠበቁና የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ያሟሉ መሆኑን ማረጋገጥ መሰረታዊ በመሆኑ ለዚህም የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪዎች የዕምነቱ ተከታዮችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ኮሚሽኑ አሳስቧል።
ትላንት እሁድ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ጎሮ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኘዉ ቤተክርስቲያን ዉስጥ አማኞች በአምልኮ ስነ-ስርዓት ላይ እያሉ ወለሉ ተደርምሶ አራት ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችና የአምቡላንስ አገልግሎት ባለሞያዎች በአደጋዉ ቦታ ፈጥነዉ በመድረስ ተጎጂዎችን ከተደረመሰዉ ጉዳጓድ ዉስጥ በማዉጣት ለተጨማሪ ህክምና በአቅራቢዉ ወደሚገኘዉ ጎሮ ጤና ጣቢያ ማድረሳቸውን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ እና ቴለቪዥን ተናግረዋል።
ለአደጋዉ ምክንያት የሆነዉም የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ ማጠራቀሚያ ጉድጓድ ክዳኑ በመደርመሱና ቤተክርስቲያኑ በመጸዳጃ ቤት ላይ የተሰራ በመሆኑ ነዉ። ጉዳት ከደረሰባቸዉ አራት ሰዎች መካከል ሶስቱ ሴቶች ናቸዉ።
የአምልኮ ስፍራዎች በርካታ ሰዎች የሚታደሙት ቦታ በመሆኑ ደረጃቸዉን የጠበቁና የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ያሟሉ መሆኑን ማረጋገጥ መሰረታዊ በመሆኑ ለዚህም የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳዳሪዎች የዕምነቱ ተከታዮችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት ኮሚሽኑ አሳስቧል።
👍9😭3💔2🔥1🙏1
ስጦታ የተበረከተላቸውን መኪና መልሰው ለቤተክርስቲያን የሰጡት የወንጌል አባት።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ምዕራብ ኢትዮጵያ ቀጠና ነቀምት ከተማ በተካሄደ ፕሮግራም ላለፉት 55 አመታት በወለጋ በሚገኙ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አጥቢያዎች፣ ክልሎች፣ ኮሌጅና ቀጠና ላገለገሉት የወንጌል አባት መጋቢ ተፈራ ጎንፋ የምስጋናና ዕውቅና መርሃ ግብር ተከናውኗል።
መጋቢ ተፈራ ጎንፋ በወንጌል አገልግሎታቸው ብዙ ያፈሩ የአሁኑ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በቤተክርስቲያኒቱ ከአጥቢያ እስከ ዋናው ቢሮ በተለያዩ ኃላፊነቶች እያገለገሉ የሚገኙ አገልጋዮችን ያሳደጉ እንዲሁም ከሀያ ዘጠኝ አመት በፊት ለተመሰረተው የወለጋ መሠረተ ክርስቶስ ኮሌጅ ምስረታ እና ዕድገት የደከሙ፤ በቤተክርስያኒቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀጠና ሆኖ የተቋቋመውን የምዕራብ ኢትዮጵያ ቀጠናን ከምስረታው ጀምሮ በዋና ጸሐፊነት ያገለገሉ፤ ለመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለአካባቢው አብያተክርስቲያናት የወንጌል እንቅስቃሴ ጉልህ ሚና የተጫወቱ እንዲሁም በአካባቢው ማህበረሰብ እና መንግስት በጎ ተጽዕኖ በማሳደራቸው የሚታወቁ እጅግ የተወደዱ አባት ናቸው።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ፣ የአካባቢው ሐይማኖት አባቶች፣ የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ተወካዮች፣ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ኃላፊዎችና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተካሄደው የእውቅና ፕሮግራም እኚህ የወንጌል አባት ባለቤታቸው በተገኙበት የመኪና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ነገር ግን በስጦታ ያገኙትን ተሽከርካሪ #እኔ አገልግሎቴን ጨርሻለሁ ከዚህ በኋላ መኪና ለእኔ ሳይሆን ለቀጠናው ነው የሚያስፈልገው በማለት በጉባኤው ፊት በምዕራብ ኢትዮጵያ ለሚካሄደው የእግዚአብሔር መንግሥት ስራ አበርክተዋል።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ምዕራብ ኢትዮጵያ ቀጠና ነቀምት ከተማ በተካሄደ ፕሮግራም ላለፉት 55 አመታት በወለጋ በሚገኙ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አጥቢያዎች፣ ክልሎች፣ ኮሌጅና ቀጠና ላገለገሉት የወንጌል አባት መጋቢ ተፈራ ጎንፋ የምስጋናና ዕውቅና መርሃ ግብር ተከናውኗል።
መጋቢ ተፈራ ጎንፋ በወንጌል አገልግሎታቸው ብዙ ያፈሩ የአሁኑ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በቤተክርስቲያኒቱ ከአጥቢያ እስከ ዋናው ቢሮ በተለያዩ ኃላፊነቶች እያገለገሉ የሚገኙ አገልጋዮችን ያሳደጉ እንዲሁም ከሀያ ዘጠኝ አመት በፊት ለተመሰረተው የወለጋ መሠረተ ክርስቶስ ኮሌጅ ምስረታ እና ዕድገት የደከሙ፤ በቤተክርስያኒቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀጠና ሆኖ የተቋቋመውን የምዕራብ ኢትዮጵያ ቀጠናን ከምስረታው ጀምሮ በዋና ጸሐፊነት ያገለገሉ፤ ለመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለአካባቢው አብያተክርስቲያናት የወንጌል እንቅስቃሴ ጉልህ ሚና የተጫወቱ እንዲሁም በአካባቢው ማህበረሰብ እና መንግስት በጎ ተጽዕኖ በማሳደራቸው የሚታወቁ እጅግ የተወደዱ አባት ናቸው።
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ዋናው ቢሮ፣ የአካባቢው ሐይማኖት አባቶች፣ የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ተወካዮች፣ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅት ኃላፊዎችና የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተካሄደው የእውቅና ፕሮግራም እኚህ የወንጌል አባት ባለቤታቸው በተገኙበት የመኪና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
ነገር ግን በስጦታ ያገኙትን ተሽከርካሪ #እኔ አገልግሎቴን ጨርሻለሁ ከዚህ በኋላ መኪና ለእኔ ሳይሆን ለቀጠናው ነው የሚያስፈልገው በማለት በጉባኤው ፊት በምዕራብ ኢትዮጵያ ለሚካሄደው የእግዚአብሔር መንግሥት ስራ አበርክተዋል።
❤38👍8🔥2🙏2💯1
በዶ/ር ሙላቱ በላይነህ የተዘጋጀ “የለውጥ ባለራዕይ” የተሰኘ መጽሐፍ ተመረቀ
ለሰዎች፣ ለተቋማት እንዲሁም ለማህበረሰብ ለእውነተኛ፣ ለሁለንተናዊ ለውጥና እድገት አስፈላጊ ነው የተባለለት ይህ መጽሐፍ፣ የደራሲው ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና የተቋማት መሪዎች በተገኙበት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።
ሰው ሁሉ ለውጥ ፈላጊ በመሆኑ፣ በተለዋዋጭ አለም ውስጥ እውነተኛ ለውጥን አስተናግዶ እንዴት መኖር ይችላል የሚል ምክረ ሃሳብን ይዟል። በተጨማሪም ለውጥ ከውጪ ሳይሆን ከራስ የሚጀምር ሂደት መሆኑንም መጽሃፉ ይሞግታል።
የመጽሃፉ አርታኢ አቶ በርናባስ ስለ መጽሃፉ ዳሰሳ ያቀረበ ሲሆን፣ ከአብያተ ክርስቲያናት፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ ከሚድያ እና የተለያዩ የስራ መስኮች የተወጣጡ ተናጋሪዎች አስተያየታቸውን አጋርተዋል።
የደራሲ ዶ/ር ሙላቱ በላይነህ ቤተሰብ፣ አሳዳጊ መምህራን እና ተጋባዥ እንግዶች መርቀው ለንባብ አብቅተዋታል።
ደራሲው 9ኛ መጽሃፍ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ከተጠናቀቀ 14 ዓመታት በኋላ ነው ለህትመት የበቃው።
ለሰዎች፣ ለተቋማት እንዲሁም ለማህበረሰብ ለእውነተኛ፣ ለሁለንተናዊ ለውጥና እድገት አስፈላጊ ነው የተባለለት ይህ መጽሐፍ፣ የደራሲው ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች እና የተቋማት መሪዎች በተገኙበት ተመርቆ ለንባብ በቅቷል።
ሰው ሁሉ ለውጥ ፈላጊ በመሆኑ፣ በተለዋዋጭ አለም ውስጥ እውነተኛ ለውጥን አስተናግዶ እንዴት መኖር ይችላል የሚል ምክረ ሃሳብን ይዟል። በተጨማሪም ለውጥ ከውጪ ሳይሆን ከራስ የሚጀምር ሂደት መሆኑንም መጽሃፉ ይሞግታል።
የመጽሃፉ አርታኢ አቶ በርናባስ ስለ መጽሃፉ ዳሰሳ ያቀረበ ሲሆን፣ ከአብያተ ክርስቲያናት፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤት፣ ከሚድያ እና የተለያዩ የስራ መስኮች የተወጣጡ ተናጋሪዎች አስተያየታቸውን አጋርተዋል።
የደራሲ ዶ/ር ሙላቱ በላይነህ ቤተሰብ፣ አሳዳጊ መምህራን እና ተጋባዥ እንግዶች መርቀው ለንባብ አብቅተዋታል።
ደራሲው 9ኛ መጽሃፍ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ከተጠናቀቀ 14 ዓመታት በኋላ ነው ለህትመት የበቃው።
👍10❤8🥰1
ህብረቱ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት ኢዮቢልዩ በዓል መክፈቻ እና ዓመታዊ የመሪዎች ጉባዔ ከሚያዚያ 15-17 ያካሄዳል
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት ኢዮቢልዩ በዓል መክፈቻ እና ዓመታዊ የመሪዎች ጉባዔ ከሚያዚያ 15-17 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሄድ ህብረቱ በዛሬው እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል
በዚህ 50ኛ ዓመት ኢዮቢልዩ በዓል የመሪዎችና የመጋቢዎች ኮንፍረንስ እንደሚካሄድ የተገለፀ ሲሆን ከመላው አገሪቱ ከአራት ሺህ በላይ መጋቢያን እና አገልጋዮች በዚህ ኮንፍራንስ ይታደማሉ ተብሏል
እንዲሁም የወንጌል #እና የሰላም ጉዳይ ትልቅ ትኩረት የሚሰጥበት ፣ በመንፈሳዊ ፣ በማኅበራዊ ፣ በባህላዊና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ትምህርቶች የሚሰጡበትና ውይይቶች እንደሚካሄዱበት ተነግሯል
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት በአገር ውስጥ 182 ቤተ እምነቶችን በአባልነት፣ 75 ቤተክርስቲያን አጋዥ ክርስቲያናዊ ድርጅቶችን በተባባሪ አባልነት እንዲሁም ከ450 በላይ የሚሆኑ ቤተ-እምነቶችን በአጋር አባልነት የሚያስተባብር ኅብረት ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል እና የበላይ ጠባቂም ነው፡፡
የመጋቢዎችና የመሪዎች ኮንፈረንስ ላይ ለመመዝገብ ከታች ባለው ስልክ ቁጥሮች መጠቀም እንደሚቻል ማህበሩ አስታውቋል
099595706 / 099595707
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት ኢዮቢልዩ በዓል መክፈቻ እና ዓመታዊ የመሪዎች ጉባዔ ከሚያዚያ 15-17 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሄድ ህብረቱ በዛሬው እለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል
በዚህ 50ኛ ዓመት ኢዮቢልዩ በዓል የመሪዎችና የመጋቢዎች ኮንፍረንስ እንደሚካሄድ የተገለፀ ሲሆን ከመላው አገሪቱ ከአራት ሺህ በላይ መጋቢያን እና አገልጋዮች በዚህ ኮንፍራንስ ይታደማሉ ተብሏል
እንዲሁም የወንጌል #እና የሰላም ጉዳይ ትልቅ ትኩረት የሚሰጥበት ፣ በመንፈሳዊ ፣ በማኅበራዊ ፣ በባህላዊና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ትምህርቶች የሚሰጡበትና ውይይቶች እንደሚካሄዱበት ተነግሯል
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት በአገር ውስጥ 182 ቤተ እምነቶችን በአባልነት፣ 75 ቤተክርስቲያን አጋዥ ክርስቲያናዊ ድርጅቶችን በተባባሪ አባልነት እንዲሁም ከ450 በላይ የሚሆኑ ቤተ-እምነቶችን በአጋር አባልነት የሚያስተባብር ኅብረት ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል እና የበላይ ጠባቂም ነው፡፡
የመጋቢዎችና የመሪዎች ኮንፈረንስ ላይ ለመመዝገብ ከታች ባለው ስልክ ቁጥሮች መጠቀም እንደሚቻል ማህበሩ አስታውቋል
099595706 / 099595707
👍6❤2🔥1
ዋዕ ሁንደም ሞኦሃኔ
እግዚአብሔር ሁሉን ያያል
ስለዚህ ድንቅ ዘማሪ በድሩ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርክህ 🙏🙏
መዝሙሩ የአማረኛ ትርግም (Subtitle) ስላለዉ ሁላችሁም ተባረኩበት https://youtu.be/Q2CPfbOPDeQ?si=bJuMnOh5nTW9rSCL
እግዚአብሔር ሁሉን ያያል
ስለዚህ ድንቅ ዘማሪ በድሩ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርክህ 🙏🙏
መዝሙሩ የአማረኛ ትርግም (Subtitle) ስላለዉ ሁላችሁም ተባረኩበት https://youtu.be/Q2CPfbOPDeQ?si=bJuMnOh5nTW9rSCL
YouTube
ዋእ_ሁንደም_ሞኦሃኔ_የሚል_አዲስ_መዝሙር_ተለቋል_badiru_nuriye_official_
#berekettesfaye
#mogosamanuel
#duet
#abelbirhanuየወይኗ
#29january
#habesha
#daysoftheyear
#tesfayegirma
#gospelmusic
#january
#kasu
#kasahungirma
#yosefsamuel
#tagaschamacho
#mulunashyohans
#abidinagogadisa
#abochedasalagni
#abelabuna
#Lilytilahun…
#mogosamanuel
#duet
#abelbirhanuየወይኗ
#29january
#habesha
#daysoftheyear
#tesfayegirma
#gospelmusic
#january
#kasu
#kasahungirma
#yosefsamuel
#tagaschamacho
#mulunashyohans
#abidinagogadisa
#abochedasalagni
#abelabuna
#Lilytilahun…
👍3❤1🔥1
የህማማቱን ሳምንት በንስሃ እንቆይ ተብላችኋል!
አገራዊች የንስሃ አስተባባሪ ኮሚቴ ለ6 ቀናት የሚቆይ የንስሃ እና መመለስ የጸሎት ጥሪ አቀረበ። ኮሚቴው ቅዳሜ ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በሳሮማርያ ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫው ተደጋጋሚ የንስሃ እና የመመለስ ጥሪ ወደ ምድራችን እየመጣ መሆኑን ታሪካዊ ዳራ በመጥቀስ ያብራራ ሲሆን በተለይም የእውነትና የሕይወት ድምፅ አገልግሎት በኩል በመጋቢ ዘካሪያስ በላይ እግዚአብሔር ወደ ምድራችን ባመጣው ትንቢታዊ መልዕክት ትኩረት በማድረግ ለአገራዊ የንስሃ መርሃ ግብር ሲዘጋጅ መቆየቱን አንስቷል።
በአራት ምዕራፍ የንስሃ መርሃ ግብሩ የሚካሄድ ሲሆን በምዕራፍ 1 በአምስት አቅጣጫዎች ላይ ከፊታችን ሰኞ ሚያዝያ 6 ጀምሮ የህማማቱን ሳምንት ሙሉ ቅዱሳን ባሉበት አካባቢ በየአጥቢያቸው በመሰባሰብ በንስሃ ኑዛዜ እንደሚቆይ ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት፦
– ሰኞ ሚያዝያ 6፦ የፅድቅ ተጠያቂነት፣
– ማክሰኞ ሚያዝያ 7፦ የህይወት ቀደም አገልግሎት ተጠያቂነት፣
– ዕሮብ ሚያዝያ 8፦ የንስሃ አገልግሎት ተጠያቂነት፣
– ሃሙስ ሚያዝያ 9፦ የእግዚአብሔር መንግስት ተጠያቂነት፣
– አርብ ሚያዝያ 10፦ የበጎ ስራ ተጠያቂነት
- ቅዳሜ ሚያዝያ 11፦ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ አገራት መካከል ስላለው ግንኙነት እንዲጸለይ አደራ ብሏል።
የንስሃ መርሃ ግብሩ በምዕራፍ 2 ከሚያዚያ 19 እስከ ግንቦት17 ለ5 ሳምንት የንስሃ ፍሬ እንዲሆን ትምህርት የሚሰጥበት እንደሚሆን ተነግሯል።
በምዕራፍ 3 ደግሞ ከግንቦት 19 እስከ 20 ቅዱሳን በያሉበት የንስሃው መዝጊያ የሚደረግ ሲሆን በምዕራፍ 4 ከግንቦት 25 – 27 በአዲስ አበባ የማጠቃለያ መርሃ ግብር እንዲሆን ታቅዷል።
ስለዚህ ሁላችሁ ቅዱሳን በዚህ አገራዊ የንስሃ መርሃ ግብር ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
አገራዊች የንስሃ አስተባባሪ ኮሚቴ ለ6 ቀናት የሚቆይ የንስሃ እና መመለስ የጸሎት ጥሪ አቀረበ። ኮሚቴው ቅዳሜ ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በሳሮማርያ ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫው ተደጋጋሚ የንስሃ እና የመመለስ ጥሪ ወደ ምድራችን እየመጣ መሆኑን ታሪካዊ ዳራ በመጥቀስ ያብራራ ሲሆን በተለይም የእውነትና የሕይወት ድምፅ አገልግሎት በኩል በመጋቢ ዘካሪያስ በላይ እግዚአብሔር ወደ ምድራችን ባመጣው ትንቢታዊ መልዕክት ትኩረት በማድረግ ለአገራዊ የንስሃ መርሃ ግብር ሲዘጋጅ መቆየቱን አንስቷል።
በአራት ምዕራፍ የንስሃ መርሃ ግብሩ የሚካሄድ ሲሆን በምዕራፍ 1 በአምስት አቅጣጫዎች ላይ ከፊታችን ሰኞ ሚያዝያ 6 ጀምሮ የህማማቱን ሳምንት ሙሉ ቅዱሳን ባሉበት አካባቢ በየአጥቢያቸው በመሰባሰብ በንስሃ ኑዛዜ እንደሚቆይ ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት፦
– ሰኞ ሚያዝያ 6፦ የፅድቅ ተጠያቂነት፣
– ማክሰኞ ሚያዝያ 7፦ የህይወት ቀደም አገልግሎት ተጠያቂነት፣
– ዕሮብ ሚያዝያ 8፦ የንስሃ አገልግሎት ተጠያቂነት፣
– ሃሙስ ሚያዝያ 9፦ የእግዚአብሔር መንግስት ተጠያቂነት፣
– አርብ ሚያዝያ 10፦ የበጎ ስራ ተጠያቂነት
- ቅዳሜ ሚያዝያ 11፦ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ አገራት መካከል ስላለው ግንኙነት እንዲጸለይ አደራ ብሏል።
የንስሃ መርሃ ግብሩ በምዕራፍ 2 ከሚያዚያ 19 እስከ ግንቦት17 ለ5 ሳምንት የንስሃ ፍሬ እንዲሆን ትምህርት የሚሰጥበት እንደሚሆን ተነግሯል።
በምዕራፍ 3 ደግሞ ከግንቦት 19 እስከ 20 ቅዱሳን በያሉበት የንስሃው መዝጊያ የሚደረግ ሲሆን በምዕራፍ 4 ከግንቦት 25 – 27 በአዲስ አበባ የማጠቃለያ መርሃ ግብር እንዲሆን ታቅዷል።
ስለዚህ ሁላችሁ ቅዱሳን በዚህ አገራዊ የንስሃ መርሃ ግብር ተሳታፊ እንድትሆኑ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
❤16👍7🔥1👏1
"በሆሳዕና አትታመኑ በስቀለውም ተስፋ አትቁረጡ" ፓስተር ጻዲቁ አብዶ Day 01 እሁድ https://www.youtube.com/watch?v=mkQL1I8ULn0&t=1s
YouTube
"በሆሳዕና አትታመኑ በስቀለውም ተስፋ አትቁረጡ" ፓስተር ጻዲቁ አብዶ Day 01 እሁድ
#gospel #billy
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews #ethiopiantvshow…
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews #ethiopiantvshow…
❤4👍1🙏1
የዓመቱ ተሸላሚ #ክርስቲያን ጋዜጠኛ በመባል እውቅና ተሰጠው።
#እንኳን #ደስ አለህ 🙏🙏🙏
ከኤልሻዳይ ቴሌቪዥኝ ለተጠናቀረው ዘገባ ታምራት ሞቲ ነኝ። የሚል ድምፅ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ይሰማ ነበር።
ለክርስቲያን ሚዲያ እድገት #እና እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፆ ያደረገ እና እስካሁንም እየተጋ የሚገኝ እጅግ ተወዳጅ እና ሰዉ አክባሪ ወጣት ነዉ። ጋዜጠኛ እና አገልጋይ ታምራት ሞቲ
ከጋዜጠኝነቱ ባሻገር በስነፅሁፍ ስራዎቹም ይታወቃል። ለኤልሻዳይ፤ ለኢቫንጅሊካል ፤ ለGMM ቲቪ የዜና ምንጭ በመሆን አገልግሏል። እኛን ጨምሮ ዛሬ ላሉት ብዙ ታዳጊ ክርስቲያን ጋዜጠኞች አርዓያ ነው።
#አሁን ደግሞ በGMM TV "ጉብዝናዬ" የሚል ፕሮግራም እየሰራ በአገልግሎት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ አርዓያ ባለታሪኮችን እያቀረበ የጉብዝና ወራታቸውን ጌታን በማገልገል እንዴት እንዳተረፉ በማስታወስ ብዙዎችን እያገለገል ይገኛል።
አገልጋይ ፣ ጋዜጠኛ ፣ ተወናይ እና የመፅሐፍ ከታቢ ታምራት ሞቴ ከሰሞኑ በጋዜጠኞች ዘርፍ የዓመቱ ተሸላሚ በመሆን እውቅና ተቀብሏል።🏅🏆
የሳቤህ ምንጭ ዓለም አቀፍ አገልግሎት በ8 ዘርፎች በየአመቱ በሚያደርጋቸው የእውቅና መርሃ ግብር ላለፉት 12 ዓመታት በመንፈሳዊ ቴሌቪዥን የጋዜጠኝነት አገልግሎቱ እያበረከተ ላለው #መልካም አስተዋፅኦ ይገባሃል ሲል የ2017 በጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ አድርጎታል።
ደስስስስስስስስስስስስስስስስ ብሎናል! The Christian News - የክርስቲያን ዜና የተሰማንን ደስታ እንገልጻለን።
አዘጋጆቹ ስላበረከቱት ሽልማት እና እውቅና ከልብ እያመሰገንን ወዳጃችን የበለጠ እየሰራ እንዲሄድ እናበረታታዋለን። 🙏🙏🙏
በድጋሜ እንኳን ደስ አለህ🙏🙏🙏
#እንኳን #ደስ አለህ 🙏🙏🙏
ከኤልሻዳይ ቴሌቪዥኝ ለተጠናቀረው ዘገባ ታምራት ሞቲ ነኝ። የሚል ድምፅ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ይሰማ ነበር።
ለክርስቲያን ሚዲያ እድገት #እና እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋፆ ያደረገ እና እስካሁንም እየተጋ የሚገኝ እጅግ ተወዳጅ እና ሰዉ አክባሪ ወጣት ነዉ። ጋዜጠኛ እና አገልጋይ ታምራት ሞቲ
ከጋዜጠኝነቱ ባሻገር በስነፅሁፍ ስራዎቹም ይታወቃል። ለኤልሻዳይ፤ ለኢቫንጅሊካል ፤ ለGMM ቲቪ የዜና ምንጭ በመሆን አገልግሏል። እኛን ጨምሮ ዛሬ ላሉት ብዙ ታዳጊ ክርስቲያን ጋዜጠኞች አርዓያ ነው።
#አሁን ደግሞ በGMM TV "ጉብዝናዬ" የሚል ፕሮግራም እየሰራ በአገልግሎት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ አርዓያ ባለታሪኮችን እያቀረበ የጉብዝና ወራታቸውን ጌታን በማገልገል እንዴት እንዳተረፉ በማስታወስ ብዙዎችን እያገለገል ይገኛል።
አገልጋይ ፣ ጋዜጠኛ ፣ ተወናይ እና የመፅሐፍ ከታቢ ታምራት ሞቴ ከሰሞኑ በጋዜጠኞች ዘርፍ የዓመቱ ተሸላሚ በመሆን እውቅና ተቀብሏል።🏅🏆
የሳቤህ ምንጭ ዓለም አቀፍ አገልግሎት በ8 ዘርፎች በየአመቱ በሚያደርጋቸው የእውቅና መርሃ ግብር ላለፉት 12 ዓመታት በመንፈሳዊ ቴሌቪዥን የጋዜጠኝነት አገልግሎቱ እያበረከተ ላለው #መልካም አስተዋፅኦ ይገባሃል ሲል የ2017 በጋዜጠኞች ዘርፍ አሸናፊ አድርጎታል።
ደስስስስስስስስስስስስስስስስ ብሎናል! The Christian News - የክርስቲያን ዜና የተሰማንን ደስታ እንገልጻለን።
አዘጋጆቹ ስላበረከቱት ሽልማት እና እውቅና ከልብ እያመሰገንን ወዳጃችን የበለጠ እየሰራ እንዲሄድ እናበረታታዋለን። 🙏🙏🙏
በድጋሜ እንኳን ደስ አለህ🙏🙏🙏
👍11❤4🔥1
እውቅና ተሰጣቸው።
ለመጋቢ ለገሠ ጸጋዬ የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም በሆሳዕና ከተማ ተዘጋጀ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የሆሳዕና ክልል ላለፉት 29 አመታት በፅናትና ታማኝነት ክልሉን ያገለገሉትን መጋቢ ለገሠ ጸጋዬን በመሀል ሆሣዕና መሠረተ ክርስቶስ አጥቢያ ከ52 በላይ በክልሉ ስር የሚገኙ የአጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች እንዲሁም የተለያዩ ጥሪ የተዳረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
መጋቢ ለገሠ ጸጋዬ በክልሉ አገልግሎት ሲጀምሩ የነበረው አንድ ክልል በአሁን ሰዓት ወደ ስድስት ክልሎች ሲያድግ የአጥቢያዎች ብዛት ደግሞ 112 መድረስ ችሏል።
በአካባቢው ያለው የቤተክርስቲያኒቱ አማኞች ቁጥርም ከ6900 በመነሳት በአሁን ሰዐት ከ70000 መብለጡን በመድረኩ ተገልጿል። በዚህ ሁሉ አመራር በመስጠት ላገለገሉት መጋቢ ለገሠ ጸጋዬ ቤተክርስቲያን እውቅና ሰጥታለች።
በዝግጅቱ ለመጋቢ ለገሠ ጸጋዬና ባለቤታቸው የተለያየ ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን መጋቢ ለገሰም ስለሆነው ሁሉ እግዚአብሔርን በማመስገን በአገልግሎታቸው ከጎናቸው ለቆሙትና አብሮነታቸውን ላሳዪአቸው ሁሉ ምስጋና በማቅረብ ቤተክርስቲያንን ባርከዋል።
ለመጋቢ ለገሠ ጸጋዬ የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም በሆሳዕና ከተማ ተዘጋጀ።
በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የሆሳዕና ክልል ላለፉት 29 አመታት በፅናትና ታማኝነት ክልሉን ያገለገሉትን መጋቢ ለገሠ ጸጋዬን በመሀል ሆሣዕና መሠረተ ክርስቶስ አጥቢያ ከ52 በላይ በክልሉ ስር የሚገኙ የአጥቢያ መሪዎችና አገልጋዮች እንዲሁም የተለያዩ ጥሪ የተዳረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የምስጋናና እውቅና ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።
መጋቢ ለገሠ ጸጋዬ በክልሉ አገልግሎት ሲጀምሩ የነበረው አንድ ክልል በአሁን ሰዓት ወደ ስድስት ክልሎች ሲያድግ የአጥቢያዎች ብዛት ደግሞ 112 መድረስ ችሏል።
በአካባቢው ያለው የቤተክርስቲያኒቱ አማኞች ቁጥርም ከ6900 በመነሳት በአሁን ሰዐት ከ70000 መብለጡን በመድረኩ ተገልጿል። በዚህ ሁሉ አመራር በመስጠት ላገለገሉት መጋቢ ለገሠ ጸጋዬ ቤተክርስቲያን እውቅና ሰጥታለች።
በዝግጅቱ ለመጋቢ ለገሠ ጸጋዬና ባለቤታቸው የተለያየ ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን መጋቢ ለገሰም ስለሆነው ሁሉ እግዚአብሔርን በማመስገን በአገልግሎታቸው ከጎናቸው ለቆሙትና አብሮነታቸውን ላሳዪአቸው ሁሉ ምስጋና በማቅረብ ቤተክርስቲያንን ባርከዋል።
👍11❤3🔥1
ይህንን የምታደርገው በምን ስልጣን ነው? ወንድም ትንሳኤ ከተማ Day 3 ማክሰኞ https://youtu.be/2MvtSduGTK4
YouTube
ይህንን የምታደርገው በምን ስልጣን ነው? ወንድም ትንሳኤ ከተማ Day 3 ማክሰኞ
#gospel #billy
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels #thechristiannews #saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow #saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews…
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels #thechristiannews #saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow #saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews…
❤2👍1
መካነ #ኢየሱስ #አዲስ ኮሚሽነር መረጠች።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማት #እና ማኅበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን 21ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አቶ ሰለሞን ሽፈራው ለቀጣይ አራት አመታት በኮሚሽነርነት እንዲያገሉ በመምረጥ ጉባኤውን አጠናቋል።
ወደ አገልግሎቱ የሚመጡት አቶ ሰለሞን ሽፈራ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ዶ/ር አበያ ዋቅወያን ምትክ ይሆናል።
አቶ ሰለሞን ኮሚሽኑን በተለያዩ ደረጃዎች ላለፉት አስርት አመታት ያገለገሉ ሲሆን በቤተ ክርስቲያኒቱ የልማት አገልግሎት ፍልስፍና ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን ቤተክርስቲያኒቱም ለአቶ ሰለሞን አዲስ የአመራር ምዕራፍ #መልካም ምኞትዋን ገልጻለች።
ኮሚሽኑንም ወደሚቀጥለው ሁለንተናዊ የተጽኖ ምዕራፍ ለማሻገር ቤተ ክርስቲያን በአቶ ሰለሞን አመራር ላይ በፀሎት የሆነ እምነቷን አስቀምጣለች።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የልማት #እና ማኅበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን 21ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አቶ ሰለሞን ሽፈራው ለቀጣይ አራት አመታት በኮሚሽነርነት እንዲያገሉ በመምረጥ ጉባኤውን አጠናቋል።
ወደ አገልግሎቱ የሚመጡት አቶ ሰለሞን ሽፈራ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ባጠናቀቁት ዶ/ር አበያ ዋቅወያን ምትክ ይሆናል።
አቶ ሰለሞን ኮሚሽኑን በተለያዩ ደረጃዎች ላለፉት አስርት አመታት ያገለገሉ ሲሆን በቤተ ክርስቲያኒቱ የልማት አገልግሎት ፍልስፍና ዙሪያ በቂ ግንዛቤ እንዳላቸው የተገለጸ ሲሆን ቤተክርስቲያኒቱም ለአቶ ሰለሞን አዲስ የአመራር ምዕራፍ #መልካም ምኞትዋን ገልጻለች።
ኮሚሽኑንም ወደሚቀጥለው ሁለንተናዊ የተጽኖ ምዕራፍ ለማሻገር ቤተ ክርስቲያን በአቶ ሰለሞን አመራር ላይ በፀሎት የሆነ እምነቷን አስቀምጣለች።
👍7❤1🙏1
#አስደሳች #ዜና
ታፍነው የተወሰዱት ፓስተር ተለቀቁ
በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ስብከት ላይ እያሉ በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱት አሜሪካዊው ፓስተር በደቡብ አፍሪካ ፖሊሶች ድጋፍ መለቀቃቸውን ፎክስ ዜና አስነብቧል።
ባሳለፍነው ሃሙስ በደቡብ አፍሪካ ፌሎሺፕ ባፕቲስት ቸርች ኢን ማዘርዌል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየሰበኩ የነበሩ ጆሽ ሱሌቫን የተባሉ አሜሪካዊ ፓስተር "አራት የታጠቁ እና ጭምብል ያጠለቁ ወንዶች ናቸው ፓስተሩን አፍነው የወሰዷቸው" ሲሉ የፖሊስ ቃል አቀባይ ካፕቴን አንድሬ ቤቴጅ ለቢቢሲ መግለጻቸው ይታወሳል።
ፎክስ ኒውስ ከሰዓት በፊት ይዞት በወጣው ዘገባ የደቡብ አፍሪካ የምስራቅ ኬፕ ግዛት ባለስልጣናት ማክሰኞ እለት በተከፈተ የተኩስ እሩምታ ታፍኖ የነበረውን አሜሪካዊ ፓስተር ማዳን መቻላቸው ገልጸዋል ሲል ዘግቧል።
የ34 ዓመቱ ፓስተር ወደ ደቡብ አፍሪካ ከቤተሰባቸው ጋር ያቀኑት በፈረንጆቹ 2018 ሲሆን፣ አላማቸውም በዦሳ ቋንቋ አገልግሎት የሚሰጥ ቤተ ክርስቲያን መመሥረት እንደነበር ዘገባው አክሏል።
ታፍነው የተወሰዱት ፓስተር ተለቀቁ
በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ስብከት ላይ እያሉ በታጣቂዎች ታፍነው የተወሰዱት አሜሪካዊው ፓስተር በደቡብ አፍሪካ ፖሊሶች ድጋፍ መለቀቃቸውን ፎክስ ዜና አስነብቧል።
ባሳለፍነው ሃሙስ በደቡብ አፍሪካ ፌሎሺፕ ባፕቲስት ቸርች ኢን ማዘርዌል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየሰበኩ የነበሩ ጆሽ ሱሌቫን የተባሉ አሜሪካዊ ፓስተር "አራት የታጠቁ እና ጭምብል ያጠለቁ ወንዶች ናቸው ፓስተሩን አፍነው የወሰዷቸው" ሲሉ የፖሊስ ቃል አቀባይ ካፕቴን አንድሬ ቤቴጅ ለቢቢሲ መግለጻቸው ይታወሳል።
ፎክስ ኒውስ ከሰዓት በፊት ይዞት በወጣው ዘገባ የደቡብ አፍሪካ የምስራቅ ኬፕ ግዛት ባለስልጣናት ማክሰኞ እለት በተከፈተ የተኩስ እሩምታ ታፍኖ የነበረውን አሜሪካዊ ፓስተር ማዳን መቻላቸው ገልጸዋል ሲል ዘግቧል።
የ34 ዓመቱ ፓስተር ወደ ደቡብ አፍሪካ ከቤተሰባቸው ጋር ያቀኑት በፈረንጆቹ 2018 ሲሆን፣ አላማቸውም በዦሳ ቋንቋ አገልግሎት የሚሰጥ ቤተ ክርስቲያን መመሥረት እንደነበር ዘገባው አክሏል።
👍13❤7🔥1🙏1💔1