The Christian News
5.07K subscribers
3.66K photos
53 videos
912 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#ሰምተዋል?

👉 በአንድነት እግዚአብሔርን የምናመልክበት
👉 በፊቱ በጸሎትና ምልጃ የምንቀርብበት
👉 ታላቅ የወንጌል ስርጭት የምናካሂድበት

የካቲት 29 & 30 በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን በተዘጋጀው የመስቀል አደባባዩ ድግስ፡ አይቀርም።

መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ታላቁ ድግስ ላይ እርሶም በጌታ ፍቅር ተጋብዘዋል።
15👍3🔥1👏1
#36 ወጣቶች ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተቀላቅለው፡ ተጠምቀዋል!

ከአዲስ አበባ 600 ኪ.ሜ ርቃ በምትገኘው የደቡብ ኢትዮጵያዋ አሪ ዞን ጂንካ ከተማ MKC፡ 36 ወጣቶችን በአካባቢው ባለ ወንዝ #አጥምቀናል

ወንጌል ነብሳትን እየለወጠ እየቀጠለ ነው፡ እጅግ ደስ ብሎናል አብራችሁን ደስ ይበላችሁ ብለዋል መጋቢ ደሳለኝ አበበ።
13🙏3❤‍🔥2👍2🔥1
#የታሪክ_ማስታወሻ

እውቁ የወንጌል አገልጋይ ወንጌላዊ ቢሊ ግራሃም ከ65 አመታት በፊት የምስራቹን #ወንጌል በኢትዮጵያ ምድር ሰብከው፡ ከንጉሰ ነገስት አጼ ሃይለስላሴ ዘንድ ምስጋና ተችሯቸው ነበር።

ዛሬ ደግሞ ልጃቸው ሬቭረንድ ፍራንክሊን ግራሃም  የሳቸውን #ሌጋሲ በመከተል፡ መለኮታዊ ጉባኝት ለኢትዮጵያ በሚል ታላቅ የወንጌል ስብከት ያካሂዳሉ።

የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
👍142🔥1🙏1
#እንኳን #ደስ አላችሁ!!

#የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት #ህብረት #አዲስ ያስገነባውን ህንጻ አስመረቀ።

የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ጽ/ቤት ያስገነባውን ህንጻ በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ህንጻውን መርቀው የከፈቱት የከተማዋ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁዋር #እና #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የቦርድ ሰብሳቢና የመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ናቸው።

የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ከተመሰረተ ከ30 አመታት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም የራሱ የሆነ የጽ/ቤት ህንጻ ያልነበረው ሲሆን #አሁን #ግን ከከተማ አስተዳደሩ በተረከበው #ቦታ ላይ ከትራንስፎርሜሽናል ዲሳይፕል ሜኪንግ ሚኒስትሪ (TDMM) ጋር በመተባበር አስገንብቶ ያጠናቀቀውን ህንጻ #ለእግዚአብሔር #መንግስት ክብር ለህዝቡ በረከት እንዲሆን መርቆ #ሥራ አስጀምሯል።

#ክብር#እግዚአብሔር ይሁን!!

የድሬደዋ #ከተማ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁዋር በከተማው ዉስጥ ላሉ የሃይማኖት ተቋማት ለሚሰጡት #መልካም መስተንግዶ እና የሚሰጡት አገልግሎት #እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካቸዉ።
👍21🔥21👏1
#በውኑ #ለእግዚአብሔር #የሚሳነው #ነገር #አለን?

የተከበራችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ቤተሰቦቼ እህታችን መቅደስ መልካሙ ቸሩ ከጠፋች በ9ኛው ቀን ፣ ታግታ ከነበረችበት አዳማ አከባቢ አምልጣ ፣ አርሲ ነጌሌ አከባቢ ከደረሰች በኋላ ፣ በእጇ ይዛ የወጣችው mobile እና የእጅ ቦርሳ እንዲሁም መፅሐፍ ቅዱስ ይዛ ሲሆን ፣

ሁሉንም ቀምተዋት bible ብቻ እጇ ላይ ስለቀረ ፣ በሌላ ሰው ስልክ ወደ ቤተሰቦቿ በመደወል ፣ አርሲ መሆኗን ከነገረቻቸው በኋላ ፣ ሄደው ወደ ሀዋዛ ይዘዋት ተመልሰው ፣ እኛም ተቀብለናት ፣

የክልሉ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ጋር በጋራ በመሆን ባደረገው ምርመራ ፣ ወጣቷ ምንም አይነት የጤና እክል እንዳልደረሰባት ተረጋግጦ ፣ ወላጆቿን ፣ ወዳጅ ዘመዶቿን በሰላም ተቀላቅላለች።

ሁላችሁም ስላደረጋችሁት ርብርብ ፈጣሪ ያክብርልኝ። 🫡🫶🙏

ቅዳሜ 22.06.017 ዓ.ም
ኤደን ለገሠ ተሰማ
👍23👏4🙏2🔥1
#6 ቀን ቀረው

መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ በመስቀል አደባባይ

ቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሳሶሼሽን ከኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ታላቅ ድግስ።

የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!
🔥12👍62👏2🙏2❤‍🔥1🥰1
#Mo'aa TV | ሞአ ቲቪ አየር ሰዓት የሸጥኩላቸው ሰዎች ያለኔ እውቅና በስሜ ገንዘብ ሲሰበስቡ ነበር አለ።

ሞአ ቲቪ በቄስ ዶ/ር ገመቺስ ደስታ በ2009 ዓ.ም የተቋቋመና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ መንፈሳዊ ይዘቶችን የሚያስተላልፍ ክርስቲያን የቲቪ ጣቢያ ነው።

ድርጊቱንም በጣቢያው ስም የተደረገ ዝርፊያ ነው ብሎታል። የተወሰኑ የአየር ሰዓት የገዙ ሰዎች በቤተ ክርስቲያኖች አካባቢ በተለይ በኦሮሚያ ክልል እየተንቀሳቀሱ ገንዘብ ሲሰብሰቡና ለግል ጥቅማቸው ሲያውሉ ነበር ብሏል።

ጉዳዩንም ከህግ አካላት ጋር ክትትል ላይ መሆኑን የጣቢያው ሃላፊ አቶ ኒሞና ኢታና ገልጸዋል። በመላ ሃገሪቱ እንዲሁም በአለም ዙሪያ የሚገኙ ወገኖች ከመሰል ዝርፊያዎች እንዲጠነቀቁ አደራ ብለዋል።
👍6🤔3🔥1🙏1🕊1
#የአጋር_መልዕክት

መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ታላቅ ድግስ 5 ቀን ቀረው

• ፓስተርና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ
• ዘማሪ ዳንኤል አምደሚካኤል
• ዘማሪት ሃና ተክሌ
በዝማሬ ያገለግሉናል

በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የተዘጋጀ የካቲት 29ና 30 በመስቀል አደባባይ።

ሁላችሁም ተግቅብዛችኋል
👍12🔥4🙏1
#4 ቀን ቀረው

መስቀል አደባባይ ላይ እግዚዓብሔር አምላካችንን በዝማሬ፡ በጸሎት፡ በስብከት ከፍ ልናደርገው የካቲት 29 እና 30 ቀጠሮ ይዘናል።

ከሬቨረንድ ፍራንልኪን ግራሃም ጋር ታላቅ የወንጌል ስብከት ይካሄዳል።

• ዘማሪ አገኘው
• ዘማሪ ጳውሎስ
• ዘማሪ አቤኔዘር
• ዘማሪት በረከት
• ዘማሪ ጉቱ
ጋር ጌታን እናመልካለን።

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!
10👏2👍1🔥1👌1
የሀምበሪቾ ተራራ በጸሎት ቱሪዝም መዳረሻ በመሆን በአንድ ቀን ከ50 ሺ በላይ ሰዎች ለጸሎት ወደ ተራራዉ እንደሚወጡ ተነገረ።

ሀምበሪቾ ተራራ ከዛሬ ሁለት አመት በፊት በደቡብ ክልል ምክር ቤት ቀርቦ በአዋጅ ህገ ደንብ በመፅደቅ የሀምበሪቾ ኢኮ ቱሪዝም ስፍራ ፅህፈት ቤት በመባል ከባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዉጪ እራሱን ችሎ በቦርድ እንደሚመራ ተገልጿል። የ6 ወር የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሪፖርት እንደሚያሳየዉ 2 መቶ 75 ሺህ ቱሪስቶች ማዕከላዊ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸውን ያመላክታል።
ከዚህ ዉስጥም ከ77 ሺህ በላይ የሚሆኑ ቱሪስቶች የሀምበሪቾ ተራራን የጎበኙ ሲሆን በዓመት ወደ 500,000 የሚጠጉ ቱሪስቶች ተራራዉን ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የዱራሜ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ኃላፊና የቪዝት ከምባታ አስጎብኚ ድርጅት ባለቤት አቶ ሳምሶን ቶማስ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።

የሀምበሪቾ ተራራን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በከፍተኛ ፕሮጀክት ተራራውን የሚያቋርጡ 777 ደረጃዎችን መገንባቱ ተገልጿል።

ተራራው በቅርብ ጊዜ ለቱሪዝም ክፍት መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከ4 ና 5 አመት በፊት ትልቅ የፀሎት መዳረሻ ነበር። ከሀይኪንግ ጎን ለጎን በዓመት አንድ ጊዜ ጥር 11 ላይ ወደ 60 ሺህ የሚጠጉ የወንጌል አማኞች በስፍራ ፀሎት እንደሚያደርጉ አቶ ሳምሶን ቶማስ ጨምረዉ ገልፀዋል።

ስፍራውን ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ የከምባታ ዞን መንገዶች ፅህፈት ቤት በየዓመቱ መንገዶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

መንገዱን አስፋልት ለማድረግና በተራራዉ ላይ ሎጆችንና ሆቴሎች በመገንባት ምቹ ለማድረግ ፅህፈት ቤቱ እንደሚሰራ ተገልጿል። ስፍራዉን በዘላቂነት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ስራዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየተሰሩ ስለመሆናቸዉም ተገልጿል።
👍125🙏1
1.2 #ቢሊዮን ብር ለልማት ስራ የምታውለው ቤ/ክ

የመሰረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ልማት ኮሚሽን ለ2025 ዓ.ም 1.2 ሚሊዮን ብር ለልማት ስራዎች ለማዋል የኮሚሽኑ ስራ አመራር ቦርድ ወስኗል። በቀጣይ በጀቱ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርቦ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል።

ቤተ ክርስቲያኗ ወንጌልን ከመስበክ ቀጥላ ዘርፈ ብዙ የማህበረሰብ አገዝ ስራዎችን ትሰራለች።
👍81🔥1👏1
በቤተ ክርስቲያን የዘረፋ ወንጀል ሲፈፅም የተያዘው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ተከሳሽ አብዱራህማን ነጋ የተባለ ነዋሪነቱ ቸሃ ወረዳ አዶሼ ቀበሌ ሲሆን ተከሳሽ የማይገባውን ጥቅም ለራሱ ለማስገኘት በማሰብ ከሌላ ካልተያዘ ግብረ አበሩ ጋር በመሆን በወልቂጤ ከተማ በጉብሬ ክ/ከተማ ጋሶሬ ቀበሌ ልዩ ቦታው ሪፈራል ሆስፒታል ጀርባ የዝርፊያ ወንጀል ፈጽሟል፡፡

የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመዉ ህዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም በግምት ከሌሊቱ 6፡30 በሚሆንበት ጊዜ የፎከስ ፌሎሺፕ ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት የሚገለገሉበትን ቅጥር አጥር ዘሎ በመግባት ንብረትነታቸው የቤተክርስቲያኑ የሆኑ ጠቅላላ ግምታቸው በድምሩ 33,050 ብር የሆኑ እቃዎች ከንብረት ክፍል ከፍቶ በማውጣት ከቤተክርስቲያኑ አጥር ግቢ ወደ ውጪ በመወርወር ከግብረ አበሩ ጋር ሊውሰድ ሲል የአካባቢው ሰዎች ድምጽ ሰምተው መጥተው ሊይዙት ሲሉ እገድላችኋለሁ እንዳትጠጉኝ እተኩሳለሁ ብሎ ያስፈራራቸው ሲሆን በጩኸት በመጡ ሰዎች ርብርብ ተከሳሹ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

በዚህም አስቦ በፈጸመው በተራ የስርቆት ወንጀል ክስ መመስረቱን የጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ኤልያስ ሰብለጋ ለብስራት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ገልጸዋል፡፡

ክሱ የቀረበለት የጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ማስረጃዎች ከመረመረ በኋላ ተከሳሽ የተከሰሰበት ድንጋጌ በመቀየር በወንጀል ህጉ አንቀፅ 669 ንዑፅ አንቀፅ 3 መሰረት ጥፋተኛ በማለት የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ5 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ መተላለፉን ኤልያስ ሰብለጋ ጨምረው ለብስራት ራድዮ እና ቴሌቭዥን ተናግረዋል፡ ሲል ያስነበበው ዳጉ_ጆርናል ነው።
👍93🔥1
የካቲት 29 እና 30 ቅዳሜ እና እሁድ በመስቀል አደባባይ በሚካሄደው ታላቅ ድግስ አስመልክቶ ካውንስሉ መግለጫ ሰጠ።

መግለጫውን የካውንስሉ ጠ/ጸሃፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ በካውንስሉ ጽ/ቤት ሰጥተዋል።

መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ፡ ከዓመት በላይ ዝግጅት ሲደረግበት የቆየ ሲሆን፡ ስለ ኢትዮጵያ ሰላም፡ እድገት፡ ልማት የምንጸልይበት ይሆናል። እግዚአብሔርን በዝማሬ፡ በአምልኮ፡ በቃል የምናመልክበት ትልቅ ቀን ነው ብለዋል።

በመግለጫው አውቶብሶች በሚቆሙበት ስፍራዎች በጊዜ በመገኘት ወደ መስቀል አደባባይ እንድትመጡ ይሁን። በአካባቢው ከሚኖሩ የጸጥታ አካላት ጋር ትብብር በማድረግ በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄድ አደራ።

በነዚህ ቀናት እንቅስቃሴዎቻችን ሁሉ በጾም ላይ ከሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና የእስልምና እምነት ተከታዮች ጋር በፍቅር እንዲሆን አደራ ብለዋል።

ፕሮግራሙን ቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን ከ ኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በመሆን የተዘጋጀ ነው።
👍73🔥1
#2 ቀን ቀረው

መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ

ከእውቁ ወንጌላዊ ቢሊ ግራሃም ልጅ ሬቨረንድ ፍራንልኪን ግራሃም ጋር በምድራችን የእግዚአብሔርን ስም እንጠራለን።

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!
👍74🔥2👏1🙏1
#ተጠንቀቁ

"ብሩክ እና ወርቁ ከተባሉ አጭበርባሪዎች እንድትጠነቀቁ" ካውንስሉ

ስማቸው ከላይ የተጠቀሱ ግለሰቦች ለአብያተ ክርስቲያናት መሬት ስላገኛቹ ቅድመ ክፍያ አስገቡ በማለት ገንዘብ ሲሰበስቡ ደርሼበታለው ብለዋል።

ግለሰቦቹ የአዲስ አበባ ከተማ መሬት አስተዳደር ሰራተኞች ነን እያሉ ገንዘብ እንደሚሰበስቡ ካውንስሉ ገልጾ፡ ቤተ እምነቶች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አደራ ብሏል።
👍2
የወንጌላዊ ልጅ የሆኑት ሬቨረንድ ፍራንክሊን የካቲት 29 እና 30 ለሚካሄደው "መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ"ን አስመልክቶ ለሀገር ውስጥ የመንግስት እና የሃይማኖት ተቋማት ሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃማ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ #ኢትዮጵያ በመጣሁበት #ወቅት ሃገሪቱ ጦርነት #ላይ የነበረች ቢሆንም ውብ ሃገር ውብ ህዝብ እንዳላችሁ አየሁ እኔም ዛሬ ወንጌል ለማገልገል እዚህ ተገኝቻለሁ ብለዋል።

የዛሬ 65 ዓመት አባቴ በኢትዮጵያ ሰብኳል። ከዛ በኋላ ብዙ ነገር ተለዋውጧል። ነገር ግን መልዕክቱም አልተቀየረም። ዛሬም ኢየሱስ ያድናል የሚል ህያው የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል በኢትዮጵያ ምድር ይሰበካል ብለዋል።

የዛሬ 65 አመት አባቴ እንደሰበከው እኔም ዛሬ አገለግላለሁ፡ ልጄ ኤድዋርድ እዚህ አለ፡ እሱም የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ለቀጣይ 65 ዓመታት ማገልገል ይቀጥላል። 1980 ለመጀመሪያ ጊዜ ከመጣሁ ጀምሮ ሃገራችሁ ኢትዮጵያ ላይ ብዙ ለውጦችን አይቻለው ሲሉም ተናግረዋል።

ምናልባት ፕሬዝደንት ትራምፕ በUSAID በኩል የሚገባን ድጋፍ ዋሽንግተን ላይ ባለ ሙስና ምክኒያት አስቁመውታል። ለአጭር ጊዜ ችግር ሊገጥም እንደሚችል አምናለው። ስጋት አይግባቹ ሰማሪታን ፐርስ አገልግሎቱን ይቀጥላል። ድጋፋችን ከአሜሪካ መንግስት ሳይሆን ከእግዚአብሄር ነው ሲሉም ከሰሞኑ የአሜሪካ መንግስት በUSAID በኩል የወሰደው እርምጃንም በተመለከተ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ቢሊ ግርሃም የዛሬ 65 አመት በንጉሰ ነገስት ቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ ተጋብዘው ማገልገላቸውን አስታውሰው ልጃቸው በአሁኑ ሰዓት ለማገልገል በመምጣታቸው እንዲሁም የሚመሩት ሳማሪታን ፐርስ ለሃገራችን ያበረከቱት ትልቅ ነገር ስለሆነ እናመሰግናለን ያሉት ደግሞ የካውንስሉ ጠ/ጸሃፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ ናቸው።
👍1810🔥1
#የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊካል አሶሴሽን ፕሬዚዳንት ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃም ጋር ተወያይተዋል።

ከንቲባ #አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃምን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው #እንኳን ደህና መጡ ማለታቸውን ገልጸዋል፡፡

ፍራንክሊን ግራሃም እንደ አባታቸው ሁሉ ለኢትዮጵያ ጥልቅ ፍቅር ያላቸው መሆኑን፣ ሁሌ እንደሚፀልዩና ላለፉት 40 ዓመታት ኢትዮጵያን በተደጋጋሚ እንደጎበኙ መግለጻቸውን ጠቅሰዋል።

ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃም በአዲስ አበባ ከተማ ባዩት ፈጣን ለውጥ መደነቃቸውን አመልክተዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች ሬቨረንድ ፍራንክሊን ግራሃም ለኢትዮጵያ እና ህዝቦቿ ላሳዩት #ፍቅር እና #መልካም ምኞት አመስግነዋል።
👍1311🔥1👏1