የኢንግሊዝ #ፖሊስ ድምጽ ሳያሰሙ መጸለይን ከለከለ።
በርሚንግሃም #ከተማ #ውስጥ #አንዲት #ሴት በውርጃ ክሊኒክ አቅራቢያ ድምጽ ሳታሰማ መጸለዩአን ተከትሎ ፖሊስ አካባቢውን እንድትለቅ አስገድዷታል።
ፖሊስ የምትጸልየውን ሴት በአካባቢው መገኘቷ፡ ለትንኮሳ #እና ጫና ያሳድራል በማለት ከስፍራው አባረዋታል። ኢሳቤል ቫግሃን ስፕሩስ የተባለች ክርስቲያን፡ ከዚህ ቀደምም ቢሆን ጸረ ውርጃ አቋም በማራመድ የምትታወቅ ናት።
ኢሳቤል ቫግሃን ሁኔታውን ስታስረዳ "ምንም እያደረግሽ እንዳልሆነ አውቃለው፡ ነገር ግን ከውርጃ ክሊኒኮች 150 ሜትር መራቅ አለብሽ" አለኝ ትላለች። በእምነቴ ምክንያት ተገፋሁ ስትል ለዎርዚ ኒውስ ሁኔታውን አስረድታለች።
የበርሚንግሃም ፖሊስ ይህቺኑ ሴት ከዚህ ቀደም #ሁለት #ጊዜ አስሯት ነበረ። #እኔ የጸረ ውርጃ አቋም ስላለኝ ብቻ ወንጀለኛ ተደርጌ መታይቴ ልክ አይደለም ትላለች።
በአሁኑ ወቅት በኢንግሊዝ የሃገር ውስጥ ሚኒስቴር ባወጣው #መረጃ መሰረት በእነዚህ የውርጃ ማዕከላት አካባቢ መገኘት ብቻ ወንጀል ነው ይላል። የኢሳቤል ጠበቃ ጉዳዩ አስጊ ነው ይላል።
እንደ ኢሳቤል #ሁሉ እዚህ መቆም አይቻልም የምንባል ከሆነ በቅርቡ በኢንግሊዝ #መጽሃፍ ቅዱሳዊ አቋም ይዞ መገኘት ወንጀል ሊሆን ይችላል ማለት ነው ሲል ጠበቃዋ ስጋቱን ገልጿል። ኢንግሊዝ "1984" የሚለው መጽሃፍ ላይ እንደተገለጸው አይደለችም ሲል ጨምሮበታል።
ፎቶዎቹ ፋይል ናቸው።
በርሚንግሃም #ከተማ #ውስጥ #አንዲት #ሴት በውርጃ ክሊኒክ አቅራቢያ ድምጽ ሳታሰማ መጸለዩአን ተከትሎ ፖሊስ አካባቢውን እንድትለቅ አስገድዷታል።
ፖሊስ የምትጸልየውን ሴት በአካባቢው መገኘቷ፡ ለትንኮሳ #እና ጫና ያሳድራል በማለት ከስፍራው አባረዋታል። ኢሳቤል ቫግሃን ስፕሩስ የተባለች ክርስቲያን፡ ከዚህ ቀደምም ቢሆን ጸረ ውርጃ አቋም በማራመድ የምትታወቅ ናት።
ኢሳቤል ቫግሃን ሁኔታውን ስታስረዳ "ምንም እያደረግሽ እንዳልሆነ አውቃለው፡ ነገር ግን ከውርጃ ክሊኒኮች 150 ሜትር መራቅ አለብሽ" አለኝ ትላለች። በእምነቴ ምክንያት ተገፋሁ ስትል ለዎርዚ ኒውስ ሁኔታውን አስረድታለች።
የበርሚንግሃም ፖሊስ ይህቺኑ ሴት ከዚህ ቀደም #ሁለት #ጊዜ አስሯት ነበረ። #እኔ የጸረ ውርጃ አቋም ስላለኝ ብቻ ወንጀለኛ ተደርጌ መታይቴ ልክ አይደለም ትላለች።
በአሁኑ ወቅት በኢንግሊዝ የሃገር ውስጥ ሚኒስቴር ባወጣው #መረጃ መሰረት በእነዚህ የውርጃ ማዕከላት አካባቢ መገኘት ብቻ ወንጀል ነው ይላል። የኢሳቤል ጠበቃ ጉዳዩ አስጊ ነው ይላል።
እንደ ኢሳቤል #ሁሉ እዚህ መቆም አይቻልም የምንባል ከሆነ በቅርቡ በኢንግሊዝ #መጽሃፍ ቅዱሳዊ አቋም ይዞ መገኘት ወንጀል ሊሆን ይችላል ማለት ነው ሲል ጠበቃዋ ስጋቱን ገልጿል። ኢንግሊዝ "1984" የሚለው መጽሃፍ ላይ እንደተገለጸው አይደለችም ሲል ጨምሮበታል።
ፎቶዎቹ ፋይል ናቸው።
❤3👍3🔥1
#ታላቅ የወንጌል ኮንፍራስ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን በወላይታ ቀጠና ጠረቤዛ ጊቢ የተካደው ሲሆን #ይህ መርሃ ግብር በ2 አመት አንዴ የሚከናወን ነው።
የወንጌል ኮንፍራሱ በታላቅ ድምቀት የተደረገ #ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ #የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት #ቤተክርስቲያን ም/ክ #ፕሬዝደንት ዶ/ር ስሞዖን ሔሊሶ፤ #የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት #ቤተክርስቲያን #ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላቱ እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የእግዚአብሄረን ቃል የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስሞዖን ሙላቱ ፤ መጋቢና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ፤ መጋቢና ዘማሪ ታምራት ሃይሌ ፤ ጋሽ ዮሃንስ ባሰና እንዲሁም የቀጠናው ጸሃፊ መጋቢ አብርሃም ቦታ ያገለገሉ ሲሆን ዘማሪ አስፋው መሸሻ እና የጊዶ ዃየር በዝማሬ አልግለዋል።
በነበረው መርሃ ግብር ላይ #የእግዚአብሄር መገኘት በኃይል የታየ ሲሆን ከ1001 በላይ ነፍሳት ክርስቶስ እየሱስን እንደግል አዳኛቸው አድረገው ተቀብለዋል።
የቀጠናው መሪዎች የተዘጋጀ #ልዩ #የፍቅር #ስጦታ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ፤ ለመጋቢያን እንዲሁም የወላይታ ቤተ ክርስቲያን በወንጌል እንድትሰፋ ብርቱ #ዋጋ ለከፈሉ አባቶች ተበርክቷል።
የወንጌል ኮንፍራሱ በታላቅ ድምቀት የተደረገ #ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ #የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት #ቤተክርስቲያን ም/ክ #ፕሬዝደንት ዶ/ር ስሞዖን ሔሊሶ፤ #የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት #ቤተክርስቲያን #ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላቱ እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የእግዚአብሄረን ቃል የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስሞዖን ሙላቱ ፤ መጋቢና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ፤ መጋቢና ዘማሪ ታምራት ሃይሌ ፤ ጋሽ ዮሃንስ ባሰና እንዲሁም የቀጠናው ጸሃፊ መጋቢ አብርሃም ቦታ ያገለገሉ ሲሆን ዘማሪ አስፋው መሸሻ እና የጊዶ ዃየር በዝማሬ አልግለዋል።
በነበረው መርሃ ግብር ላይ #የእግዚአብሄር መገኘት በኃይል የታየ ሲሆን ከ1001 በላይ ነፍሳት ክርስቶስ እየሱስን እንደግል አዳኛቸው አድረገው ተቀብለዋል።
የቀጠናው መሪዎች የተዘጋጀ #ልዩ #የፍቅር #ስጦታ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ፤ ለመጋቢያን እንዲሁም የወላይታ ቤተ ክርስቲያን በወንጌል እንድትሰፋ ብርቱ #ዋጋ ለከፈሉ አባቶች ተበርክቷል።
👍17❤2🔥1🙏1
#የናይጄሪያ ሉተርና ቤ/ክ 100ኛ አመቷን አከበረች።
ከተመሰረተች 100ኛ አመቷን በማክበር ላይ የምትገኘው የናይጄሪያዋ ሉተራን ቸርች ኦፍ ክራይስ ቤ/ክ የ100 ዓመት ክ/በዓሏን በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብራለች።
ቤተ ክርስቲያኗ በአሁኑ ወቅት ከ2.5 ሚሊዮን አባላት ያላት ሲሆን፣ በመላው ሃገሪቱ ከ2400 በላይ አጥቢያዎች አሏት።
ቤተ ክርስቲያኗ አገልግሎቷን የጀመረችው ከሱዳን ዩናይትድ ሚሽን ጋር በመሆን በ1913 ሲሆን፣ በ1925 የናይጄሪያ ሉተራን ቸርች ኦፍ ክራይስ በመባል፣ ኑማን በምትባል ከተማ አገልግሎት ጀምራለች።
የመጀመሪያዎቹ ኢንግሊዛዊያን ሚሽነሪዎች ጡብ በመስራት እና ግብርና ተሰማርተው ወንጌል ይሰብኩ እንደነበር ታሪካቸው ይናገራል።
በማህበራዊ ስራዎች፣ በጤና፣ ትምህርት፣ የወጣቶችና ሴቶች አገልግሎት፣ የልጆች አገልግሎት እና የስነ መለኮት ትምህርትን የመሳሰሉትን ስትሰራ ቆይታለች። ቤተ ክርስቲያኗ የአለም አቀፉ ሉተራን ፌደሬሽን አባል ናት።
ከተመሰረተች 100ኛ አመቷን በማክበር ላይ የምትገኘው የናይጄሪያዋ ሉተራን ቸርች ኦፍ ክራይስ ቤ/ክ የ100 ዓመት ክ/በዓሏን በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብራለች።
ቤተ ክርስቲያኗ በአሁኑ ወቅት ከ2.5 ሚሊዮን አባላት ያላት ሲሆን፣ በመላው ሃገሪቱ ከ2400 በላይ አጥቢያዎች አሏት።
ቤተ ክርስቲያኗ አገልግሎቷን የጀመረችው ከሱዳን ዩናይትድ ሚሽን ጋር በመሆን በ1913 ሲሆን፣ በ1925 የናይጄሪያ ሉተራን ቸርች ኦፍ ክራይስ በመባል፣ ኑማን በምትባል ከተማ አገልግሎት ጀምራለች።
የመጀመሪያዎቹ ኢንግሊዛዊያን ሚሽነሪዎች ጡብ በመስራት እና ግብርና ተሰማርተው ወንጌል ይሰብኩ እንደነበር ታሪካቸው ይናገራል።
በማህበራዊ ስራዎች፣ በጤና፣ ትምህርት፣ የወጣቶችና ሴቶች አገልግሎት፣ የልጆች አገልግሎት እና የስነ መለኮት ትምህርትን የመሳሰሉትን ስትሰራ ቆይታለች። ቤተ ክርስቲያኗ የአለም አቀፉ ሉተራን ፌደሬሽን አባል ናት።
👍4❤2🔥1
#የአጋር_መልዕክት
መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዯጵያ
🙏🙏🙏🙏🙏
የ#ቢሊ ግራሃም ልጅ ሬቭረንድ #ፍራንክሊን ግራሃም በአባታቸው እግር ተተክተው ያገለግላሉ። በመስቀል አደባባይ አሸናፊው ወንጌል ይሰበካል፡ ታሪክ ይደገማል።
🔥🔥🔥
⏰ የካቲት 29 & 30
📍መስቀል አደባባይ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዯጵያ
🙏🙏🙏🙏🙏
የ#ቢሊ ግራሃም ልጅ ሬቭረንድ #ፍራንክሊን ግራሃም በአባታቸው እግር ተተክተው ያገለግላሉ። በመስቀል አደባባይ አሸናፊው ወንጌል ይሰበካል፡ ታሪክ ይደገማል።
🔥🔥🔥
⏰ የካቲት 29 & 30
📍መስቀል አደባባይ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
👍13❤7👏2🙏2🔥1👌1🕊1
በዴሞክራቲክ ኮንጎዋ #ጎማ ከተማ አብያተ ክርስቲያናት በጦርነት መካከል ማገልገላቸውን ቀጥለዋል።
በቅርቡ M23 አማጺ ቡድን ከሃገሪቱ መንግስት ጋር ሲያደርግ የነበረው ጦርነት፣ 2 ሚሊዮን ዜጎች የሚኖሩባትን የጎማ ከተማ መቆጣጥሩ ይታወሳል። በተጋሄደው አውዳሚ ጦርነት እስከ 3ሺህ የሚጠጉ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
በጦርነቱ ምክኒያት ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆች፣ በየጎዳናው የወዳደቁ አስክሬኖችን መመልከት፣ የአካባቢን ደህንነት የሚያስጠብቅ ፖሊስ አለመኖር፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች መቋረጥ፣ የጎማ ከተማን በቀናት ውስጥ ሲኦል አድርጓታል።
በዚህ ሁሉ ሰቆቃ የጎማ ክርስቲያኖች እሁድን በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ከማመስገን አላገዳቸውም። ከተማዋ ላይ በአመጽ ፈንታ ተስፋ ይታይባታል ተብሏል። አሁንም ቢሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰብዓዊ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች በከተማዋና አቅራቢያዋ አሉ።
በከተማዋ ከሚደረግ የሰብዓዊ እርዳታ ይልቅ፣ ወንጌል ትልቅ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ የአካባቢዋ አገልጋዮች ተናግረዋል። በተለይ ታዳጊ ሴቶች ተደጋጋሚ በሚደፈሩበት በዚህ ክፉ፣ ቀናት ውስጥ “Bwana Asifiwe” (እግዚዓብሔር ይመስገን) የሚሉ መዝሙሮች ይዘመራሉ። ለተጎጂዎች የአካባቢው ክርስቲያኖች አስፈላጊውን ሁሉ ቁሳዊ፣ አካላዊ እና መንፈሳዊ እገዛ እያደረጉ ይገኛሉ።
በጦርነት በምትናወጠው ዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ ጎማ ከተማ፣ ወንጌል ለህዝቡ ተስፋ ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያን አመጽን ስትቋቋም፣ በዚህ ምስቅልቅል ወቅት ክርስቲያኖች ክርስቶስን እያሳዩ ነው ሲል የዘገበው CDI ነው።
በቅርቡ M23 አማጺ ቡድን ከሃገሪቱ መንግስት ጋር ሲያደርግ የነበረው ጦርነት፣ 2 ሚሊዮን ዜጎች የሚኖሩባትን የጎማ ከተማ መቆጣጥሩ ይታወሳል። በተጋሄደው አውዳሚ ጦርነት እስከ 3ሺህ የሚጠጉ ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
በጦርነቱ ምክኒያት ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆች፣ በየጎዳናው የወዳደቁ አስክሬኖችን መመልከት፣ የአካባቢን ደህንነት የሚያስጠብቅ ፖሊስ አለመኖር፣ መሰረታዊ አገልግሎቶች መቋረጥ፣ የጎማ ከተማን በቀናት ውስጥ ሲኦል አድርጓታል።
በዚህ ሁሉ ሰቆቃ የጎማ ክርስቲያኖች እሁድን በቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ከማመስገን አላገዳቸውም። ከተማዋ ላይ በአመጽ ፈንታ ተስፋ ይታይባታል ተብሏል። አሁንም ቢሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰብዓዊ እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች በከተማዋና አቅራቢያዋ አሉ።
በከተማዋ ከሚደረግ የሰብዓዊ እርዳታ ይልቅ፣ ወንጌል ትልቅ ለውጥ እያመጣ እንደሚገኝ የአካባቢዋ አገልጋዮች ተናግረዋል። በተለይ ታዳጊ ሴቶች ተደጋጋሚ በሚደፈሩበት በዚህ ክፉ፣ ቀናት ውስጥ “Bwana Asifiwe” (እግዚዓብሔር ይመስገን) የሚሉ መዝሙሮች ይዘመራሉ። ለተጎጂዎች የአካባቢው ክርስቲያኖች አስፈላጊውን ሁሉ ቁሳዊ፣ አካላዊ እና መንፈሳዊ እገዛ እያደረጉ ይገኛሉ።
በጦርነት በምትናወጠው ዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ ጎማ ከተማ፣ ወንጌል ለህዝቡ ተስፋ ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያን አመጽን ስትቋቋም፣ በዚህ ምስቅልቅል ወቅት ክርስቲያኖች ክርስቶስን እያሳዩ ነው ሲል የዘገበው CDI ነው።
👍13❤7🔥2👏1😭1
#የአጋር_መልዕክት
#መለኮታዊ_ጉብኝት_ለኢትዮጵያ
የአምልኮ፡ ጸሎትና ወንጌል ስርጭት ታላቅ ድግስ የካቲት 29 & 30 በመስቀል አደባባይ ከሬቭረንድ ፍራንክሊን ግራሃም ጋር።
#ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!
👇👇👇
በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የተዘጋጀ
#መለኮታዊ_ጉብኝት_ለኢትዮጵያ
የአምልኮ፡ ጸሎትና ወንጌል ስርጭት ታላቅ ድግስ የካቲት 29 & 30 በመስቀል አደባባይ ከሬቭረንድ ፍራንክሊን ግራሃም ጋር።
#ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!
👇👇👇
በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የተዘጋጀ
👍10❤3🔥1🕊1
#አስደሳች #ዜና
#የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት #ካዉንስል የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል ሆነ።
በዛሬው እለት #የኢትዮጵያ የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተቋማዊ አደረጃጀቱንና ዉስጣዊ አሰራሩን እንዲሁም የአባል ቤተዕምነቶች የእርስ በእርስ ግንኙነትና በተቋሙ ላይ ያላቸዉ እይታና እርካታ አስመልክቶ የተሰራ የዳሰሳ ጥናት ያጸደቀ ሲሆን በዳሰሳ ጥናቱ መሰረት የጉባኤውን አዲስ መተዳደሪያ ደንብ አጽድቋል።
ጉባኤዉ ከዚህ ቀደም በ7 አባል ቤተዕምነት አባልነት የነበረ ቢሆንም በአዲሱ ደንብ መሰረት 5 አባላት ብቻ እንደሚኖረዉ የተጠቀሰ ሲሆን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስልም አንዱ አባል ሆኗል።
በዛሬዉ እለት በፀደቀዉ ደንብ መሰረት
. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዬች ጠቅላይ ምክር ቤት
. የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን
. የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል
. የ7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን
በአባልነት እንደሚይዝ ደንቡ የሚጠቅስ ሲሆን ከዚህ ቀደም የጉባኤው አባል የነበሩ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፣ የኢትዮጵያ ቃለሕይወት ቤተክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ በካዉንስሉ እንደሚወከሉ ተጠቅሷል።
#ዛሬ ሲካሄድ በነበረው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መድረክ #የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ጉባኤውን በጠቅላይ ጸሐፊነት ለ2ኛ ዙር እንዲመሩ በጠቅላላ ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ተመርጠዋል።
#የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት #ካዉንስል የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል ሆነ።
በዛሬው እለት #የኢትዮጵያ የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ተቋማዊ አደረጃጀቱንና ዉስጣዊ አሰራሩን እንዲሁም የአባል ቤተዕምነቶች የእርስ በእርስ ግንኙነትና በተቋሙ ላይ ያላቸዉ እይታና እርካታ አስመልክቶ የተሰራ የዳሰሳ ጥናት ያጸደቀ ሲሆን በዳሰሳ ጥናቱ መሰረት የጉባኤውን አዲስ መተዳደሪያ ደንብ አጽድቋል።
ጉባኤዉ ከዚህ ቀደም በ7 አባል ቤተዕምነት አባልነት የነበረ ቢሆንም በአዲሱ ደንብ መሰረት 5 አባላት ብቻ እንደሚኖረዉ የተጠቀሰ ሲሆን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስልም አንዱ አባል ሆኗል።
በዛሬዉ እለት በፀደቀዉ ደንብ መሰረት
. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዬች ጠቅላይ ምክር ቤት
. የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን
. የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል
. የ7ኛ ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን
በአባልነት እንደሚይዝ ደንቡ የሚጠቅስ ሲሆን ከዚህ ቀደም የጉባኤው አባል የነበሩ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፣ የኢትዮጵያ ቃለሕይወት ቤተክርስቲያን እና የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ በካዉንስሉ እንደሚወከሉ ተጠቅሷል።
#ዛሬ ሲካሄድ በነበረው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መድረክ #የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ጉባኤውን በጠቅላይ ጸሐፊነት ለ2ኛ ዙር እንዲመሩ በጠቅላላ ጉባኤው በሙሉ ድምጽ ተመርጠዋል።
👍12🔥2❤1👏1🕊1
#20_የበረከት_ዓመታት
የሰላም ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን 20ኛ አመት ክብረ በዓል እና የአዲሱ የአምልኮ ስፍራ ልታስመርቅ ነው።
ቤተክርስቲያኒቱ ቀድሞ በተከራየችበት በጎተራ የእህል ንግድ ድርጅት ግቢ ውስጥ ላለፉት 18 አመታት የክርስቶስን ወንጌል እየሰበከች የቆየች ሲሆን፣ አሁን ደግሞ እግዚአብሔር ባዘጋጀላት ስፍራ የራሷን የማምለኪያ አዳራሽ ገንብታ በቀጣዩ የእግዚአብሔር መንግስት #ወንጌል በሐይል ለመስበክ ዝግጅቷን አጠናክራ ቀጥላለች።
ስለሆኑም የ 20ኛ አመት የምስጋና ኮንፈረንስና የአዳራሸ ምረቃ ፕሮግራም ከመጋቢት 1-7 ታላላቅ አገልጋዮች፣ የቤተክርስቲያን መሪዎችና አባቶች በተገኙበት ይመረቃል።
አሁን የተገነባው የማምለኪያ አዳራሽ በአሁኑ ወቅት ጐተራ ማሳለጫ ሪፍት ቫሊ ዮኒቨርስቲ አጠገብ ሲሆን፣ በእግዚአብሔር እርዳታ ላለፉት አንድ አመት ሲሰራ የቆየነውን አዳራሽ ለእግዚአብሔር ክብርና ለቅዱሳን ጥቅም እንዲሆን ተመርቆ እንደሚከፈት ተገልጿል።
የሰላም ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ላለፋት 20 አመታት ወንጌል የመስበክ እና የማስተማር ተልዕኮ አንግባ የክርስቶስን ወንጌል እየሰበከች፣ የቆየች እና እያገለገለች ያለች ቤተክርስቲያን ነች።
የሰላም ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ኑና የረዳንን እግዚአብሔርን አብረን እናመስግን በማለት ጥሪዋን አቅርባለች።
የሰላም ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን 20ኛ አመት ክብረ በዓል እና የአዲሱ የአምልኮ ስፍራ ልታስመርቅ ነው።
ቤተክርስቲያኒቱ ቀድሞ በተከራየችበት በጎተራ የእህል ንግድ ድርጅት ግቢ ውስጥ ላለፉት 18 አመታት የክርስቶስን ወንጌል እየሰበከች የቆየች ሲሆን፣ አሁን ደግሞ እግዚአብሔር ባዘጋጀላት ስፍራ የራሷን የማምለኪያ አዳራሽ ገንብታ በቀጣዩ የእግዚአብሔር መንግስት #ወንጌል በሐይል ለመስበክ ዝግጅቷን አጠናክራ ቀጥላለች።
ስለሆኑም የ 20ኛ አመት የምስጋና ኮንፈረንስና የአዳራሸ ምረቃ ፕሮግራም ከመጋቢት 1-7 ታላላቅ አገልጋዮች፣ የቤተክርስቲያን መሪዎችና አባቶች በተገኙበት ይመረቃል።
አሁን የተገነባው የማምለኪያ አዳራሽ በአሁኑ ወቅት ጐተራ ማሳለጫ ሪፍት ቫሊ ዮኒቨርስቲ አጠገብ ሲሆን፣ በእግዚአብሔር እርዳታ ላለፉት አንድ አመት ሲሰራ የቆየነውን አዳራሽ ለእግዚአብሔር ክብርና ለቅዱሳን ጥቅም እንዲሆን ተመርቆ እንደሚከፈት ተገልጿል።
የሰላም ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ላለፋት 20 አመታት ወንጌል የመስበክ እና የማስተማር ተልዕኮ አንግባ የክርስቶስን ወንጌል እየሰበከች፣ የቆየች እና እያገለገለች ያለች ቤተክርስቲያን ነች።
የሰላም ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ኑና የረዳንን እግዚአብሔርን አብረን እናመስግን በማለት ጥሪዋን አቅርባለች።
👍11❤4👏3🔥1
20 የበረከት አመታት #የሰላም ወንጌል አማኞች ቤ/ክ የምስጋና ክ/በዓል https://youtu.be/JeRSZlnshsk
YouTube
20 የበረከት አመታት #የሰላም ወንጌል አማኞች ቤ/ክ የምስጋና ክ/በዓል
20 የበረከት አመታት
#gospel
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews #ethiopiantvshow…
#gospel
#thechristiannews #singer #jesus #jesuschrist #መልካም በዓል #marsiltvworldwide #yonatanaklilu #abiye #ebc #fana_tv #ebs #reels
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopia #ethiopiantvshow
#saturdayafternoonshow_ebstv #ethiopianews #ethiopiantvshow…
❤2👍2🔥1
#ሰምተዋል?
👉 በአንድነት እግዚአብሔርን የምናመልክበት
👉 በፊቱ በጸሎትና ምልጃ የምንቀርብበት
👉 ታላቅ የወንጌል ስርጭት የምናካሂድበት
የካቲት 29 & 30 በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን በተዘጋጀው የመስቀል አደባባዩ ድግስ፡ አይቀርም።
መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ታላቁ ድግስ ላይ እርሶም በጌታ ፍቅር ተጋብዘዋል።
👉 በአንድነት እግዚአብሔርን የምናመልክበት
👉 በፊቱ በጸሎትና ምልጃ የምንቀርብበት
👉 ታላቅ የወንጌል ስርጭት የምናካሂድበት
የካቲት 29 & 30 በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን በተዘጋጀው የመስቀል አደባባዩ ድግስ፡ አይቀርም።
መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ታላቁ ድግስ ላይ እርሶም በጌታ ፍቅር ተጋብዘዋል።
❤15👍3🔥1👏1
#36 ወጣቶች ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተቀላቅለው፡ ተጠምቀዋል!
ከአዲስ አበባ 600 ኪ.ሜ ርቃ በምትገኘው የደቡብ ኢትዮጵያዋ አሪ ዞን ጂንካ ከተማ MKC፡ 36 ወጣቶችን በአካባቢው ባለ ወንዝ #አጥምቀናል።
ወንጌል ነብሳትን እየለወጠ እየቀጠለ ነው፡ እጅግ ደስ ብሎናል አብራችሁን ደስ ይበላችሁ ብለዋል መጋቢ ደሳለኝ አበበ።
ከአዲስ አበባ 600 ኪ.ሜ ርቃ በምትገኘው የደቡብ ኢትዮጵያዋ አሪ ዞን ጂንካ ከተማ MKC፡ 36 ወጣቶችን በአካባቢው ባለ ወንዝ #አጥምቀናል።
ወንጌል ነብሳትን እየለወጠ እየቀጠለ ነው፡ እጅግ ደስ ብሎናል አብራችሁን ደስ ይበላችሁ ብለዋል መጋቢ ደሳለኝ አበበ።
❤13🙏3❤🔥2👍2🔥1
#የታሪክ_ማስታወሻ
እውቁ የወንጌል አገልጋይ ወንጌላዊ ቢሊ ግራሃም ከ65 አመታት በፊት የምስራቹን #ወንጌል በኢትዮጵያ ምድር ሰብከው፡ ከንጉሰ ነገስት አጼ ሃይለስላሴ ዘንድ ምስጋና ተችሯቸው ነበር።
ዛሬ ደግሞ ልጃቸው ሬቭረንድ ፍራንክሊን ግራሃም የሳቸውን #ሌጋሲ በመከተል፡ መለኮታዊ ጉባኝት ለኢትዮጵያ በሚል ታላቅ የወንጌል ስብከት ያካሂዳሉ።
የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
እውቁ የወንጌል አገልጋይ ወንጌላዊ ቢሊ ግራሃም ከ65 አመታት በፊት የምስራቹን #ወንጌል በኢትዮጵያ ምድር ሰብከው፡ ከንጉሰ ነገስት አጼ ሃይለስላሴ ዘንድ ምስጋና ተችሯቸው ነበር።
ዛሬ ደግሞ ልጃቸው ሬቭረንድ ፍራንክሊን ግራሃም የሳቸውን #ሌጋሲ በመከተል፡ መለኮታዊ ጉባኝት ለኢትዮጵያ በሚል ታላቅ የወንጌል ስብከት ያካሂዳሉ።
የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
👍14❤2🔥1🙏1
#እንኳን #ደስ አላችሁ!!
#የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት #ህብረት #አዲስ ያስገነባውን ህንጻ አስመረቀ።
የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ጽ/ቤት ያስገነባውን ህንጻ በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
ህንጻውን መርቀው የከፈቱት የከተማዋ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁዋር #እና #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የቦርድ ሰብሳቢና የመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ናቸው።
የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ከተመሰረተ ከ30 አመታት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም የራሱ የሆነ የጽ/ቤት ህንጻ ያልነበረው ሲሆን #አሁን #ግን ከከተማ አስተዳደሩ በተረከበው #ቦታ ላይ ከትራንስፎርሜሽናል ዲሳይፕል ሜኪንግ ሚኒስትሪ (TDMM) ጋር በመተባበር አስገንብቶ ያጠናቀቀውን ህንጻ #ለእግዚአብሔር #መንግስት ክብር ለህዝቡ በረከት እንዲሆን መርቆ #ሥራ አስጀምሯል።
#ክብር ለ #እግዚአብሔር ይሁን!!
የድሬደዋ #ከተማ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁዋር በከተማው ዉስጥ ላሉ የሃይማኖት ተቋማት ለሚሰጡት #መልካም መስተንግዶ እና የሚሰጡት አገልግሎት #እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካቸዉ።
#የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት #ህብረት #አዲስ ያስገነባውን ህንጻ አስመረቀ።
የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ጽ/ቤት ያስገነባውን ህንጻ በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
ህንጻውን መርቀው የከፈቱት የከተማዋ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁዋር #እና #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የቦርድ ሰብሳቢና የመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሳለኝ አበበ ናቸው።
የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት ከተመሰረተ ከ30 አመታት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም የራሱ የሆነ የጽ/ቤት ህንጻ ያልነበረው ሲሆን #አሁን #ግን ከከተማ አስተዳደሩ በተረከበው #ቦታ ላይ ከትራንስፎርሜሽናል ዲሳይፕል ሜኪንግ ሚኒስትሪ (TDMM) ጋር በመተባበር አስገንብቶ ያጠናቀቀውን ህንጻ #ለእግዚአብሔር #መንግስት ክብር ለህዝቡ በረከት እንዲሆን መርቆ #ሥራ አስጀምሯል።
#ክብር ለ #እግዚአብሔር ይሁን!!
የድሬደዋ #ከተማ ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከድር ጁዋር በከተማው ዉስጥ ላሉ የሃይማኖት ተቋማት ለሚሰጡት #መልካም መስተንግዶ እና የሚሰጡት አገልግሎት #እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካቸዉ።
👍21🔥2❤1👏1
#በውኑ #ለእግዚአብሔር #የሚሳነው #ነገር #አለን?
የተከበራችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ቤተሰቦቼ እህታችን መቅደስ መልካሙ ቸሩ ከጠፋች በ9ኛው ቀን ፣ ታግታ ከነበረችበት አዳማ አከባቢ አምልጣ ፣ አርሲ ነጌሌ አከባቢ ከደረሰች በኋላ ፣ በእጇ ይዛ የወጣችው mobile እና የእጅ ቦርሳ እንዲሁም መፅሐፍ ቅዱስ ይዛ ሲሆን ፣
ሁሉንም ቀምተዋት bible ብቻ እጇ ላይ ስለቀረ ፣ በሌላ ሰው ስልክ ወደ ቤተሰቦቿ በመደወል ፣ አርሲ መሆኗን ከነገረቻቸው በኋላ ፣ ሄደው ወደ ሀዋዛ ይዘዋት ተመልሰው ፣ እኛም ተቀብለናት ፣
የክልሉ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ጋር በጋራ በመሆን ባደረገው ምርመራ ፣ ወጣቷ ምንም አይነት የጤና እክል እንዳልደረሰባት ተረጋግጦ ፣ ወላጆቿን ፣ ወዳጅ ዘመዶቿን በሰላም ተቀላቅላለች።
ሁላችሁም ስላደረጋችሁት ርብርብ ፈጣሪ ያክብርልኝ። 🫡🫶🙏
ቅዳሜ 22.06.017 ዓ.ም
ኤደን ለገሠ ተሰማ
የተከበራችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ቤተሰቦቼ እህታችን መቅደስ መልካሙ ቸሩ ከጠፋች በ9ኛው ቀን ፣ ታግታ ከነበረችበት አዳማ አከባቢ አምልጣ ፣ አርሲ ነጌሌ አከባቢ ከደረሰች በኋላ ፣ በእጇ ይዛ የወጣችው mobile እና የእጅ ቦርሳ እንዲሁም መፅሐፍ ቅዱስ ይዛ ሲሆን ፣
ሁሉንም ቀምተዋት bible ብቻ እጇ ላይ ስለቀረ ፣ በሌላ ሰው ስልክ ወደ ቤተሰቦቿ በመደወል ፣ አርሲ መሆኗን ከነገረቻቸው በኋላ ፣ ሄደው ወደ ሀዋዛ ይዘዋት ተመልሰው ፣ እኛም ተቀብለናት ፣
የክልሉ እንዲሁም የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ጋር በጋራ በመሆን ባደረገው ምርመራ ፣ ወጣቷ ምንም አይነት የጤና እክል እንዳልደረሰባት ተረጋግጦ ፣ ወላጆቿን ፣ ወዳጅ ዘመዶቿን በሰላም ተቀላቅላለች።
ሁላችሁም ስላደረጋችሁት ርብርብ ፈጣሪ ያክብርልኝ። 🫡🫶🙏
ቅዳሜ 22.06.017 ዓ.ም
ኤደን ለገሠ ተሰማ
👍23👏4🙏2🔥1
#Mo'aa TV | ሞአ ቲቪ አየር ሰዓት የሸጥኩላቸው ሰዎች ያለኔ እውቅና በስሜ ገንዘብ ሲሰበስቡ ነበር አለ።
ሞአ ቲቪ በቄስ ዶ/ር ገመቺስ ደስታ በ2009 ዓ.ም የተቋቋመና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ መንፈሳዊ ይዘቶችን የሚያስተላልፍ ክርስቲያን የቲቪ ጣቢያ ነው።
ድርጊቱንም በጣቢያው ስም የተደረገ ዝርፊያ ነው ብሎታል። የተወሰኑ የአየር ሰዓት የገዙ ሰዎች በቤተ ክርስቲያኖች አካባቢ በተለይ በኦሮሚያ ክልል እየተንቀሳቀሱ ገንዘብ ሲሰብሰቡና ለግል ጥቅማቸው ሲያውሉ ነበር ብሏል።
ጉዳዩንም ከህግ አካላት ጋር ክትትል ላይ መሆኑን የጣቢያው ሃላፊ አቶ ኒሞና ኢታና ገልጸዋል። በመላ ሃገሪቱ እንዲሁም በአለም ዙሪያ የሚገኙ ወገኖች ከመሰል ዝርፊያዎች እንዲጠነቀቁ አደራ ብለዋል።
ሞአ ቲቪ በቄስ ዶ/ር ገመቺስ ደስታ በ2009 ዓ.ም የተቋቋመና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ መንፈሳዊ ይዘቶችን የሚያስተላልፍ ክርስቲያን የቲቪ ጣቢያ ነው።
ድርጊቱንም በጣቢያው ስም የተደረገ ዝርፊያ ነው ብሎታል። የተወሰኑ የአየር ሰዓት የገዙ ሰዎች በቤተ ክርስቲያኖች አካባቢ በተለይ በኦሮሚያ ክልል እየተንቀሳቀሱ ገንዘብ ሲሰብሰቡና ለግል ጥቅማቸው ሲያውሉ ነበር ብሏል።
ጉዳዩንም ከህግ አካላት ጋር ክትትል ላይ መሆኑን የጣቢያው ሃላፊ አቶ ኒሞና ኢታና ገልጸዋል። በመላ ሃገሪቱ እንዲሁም በአለም ዙሪያ የሚገኙ ወገኖች ከመሰል ዝርፊያዎች እንዲጠነቀቁ አደራ ብለዋል።
👍6🤔3🔥1🙏1🕊1
#የአጋር_መልዕክት
መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ታላቅ ድግስ 5 ቀን ቀረው
• ፓስተርና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ
• ዘማሪ ዳንኤል አምደሚካኤል
• ዘማሪት ሃና ተክሌ
በዝማሬ ያገለግሉናል
በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የተዘጋጀ የካቲት 29ና 30 በመስቀል አደባባይ።
ሁላችሁም ተግቅብዛችኋል
መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ታላቅ ድግስ 5 ቀን ቀረው
• ፓስተርና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ
• ዘማሪ ዳንኤል አምደሚካኤል
• ዘማሪት ሃና ተክሌ
በዝማሬ ያገለግሉናል
በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ አሶሴሽን የተዘጋጀ የካቲት 29ና 30 በመስቀል አደባባይ።
ሁላችሁም ተግቅብዛችኋል
👍12🔥4🙏1
የሀምበሪቾ ተራራ በጸሎት ቱሪዝም መዳረሻ በመሆን በአንድ ቀን ከ50 ሺ በላይ ሰዎች ለጸሎት ወደ ተራራዉ እንደሚወጡ ተነገረ።
ሀምበሪቾ ተራራ ከዛሬ ሁለት አመት በፊት በደቡብ ክልል ምክር ቤት ቀርቦ በአዋጅ ህገ ደንብ በመፅደቅ የሀምበሪቾ ኢኮ ቱሪዝም ስፍራ ፅህፈት ቤት በመባል ከባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዉጪ እራሱን ችሎ በቦርድ እንደሚመራ ተገልጿል። የ6 ወር የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሪፖርት እንደሚያሳየዉ 2 መቶ 75 ሺህ ቱሪስቶች ማዕከላዊ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸውን ያመላክታል።
ከዚህ ዉስጥም ከ77 ሺህ በላይ የሚሆኑ ቱሪስቶች የሀምበሪቾ ተራራን የጎበኙ ሲሆን በዓመት ወደ 500,000 የሚጠጉ ቱሪስቶች ተራራዉን ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የዱራሜ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ኃላፊና የቪዝት ከምባታ አስጎብኚ ድርጅት ባለቤት አቶ ሳምሶን ቶማስ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
የሀምበሪቾ ተራራን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በከፍተኛ ፕሮጀክት ተራራውን የሚያቋርጡ 777 ደረጃዎችን መገንባቱ ተገልጿል።
ተራራው በቅርብ ጊዜ ለቱሪዝም ክፍት መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከ4 ና 5 አመት በፊት ትልቅ የፀሎት መዳረሻ ነበር። ከሀይኪንግ ጎን ለጎን በዓመት አንድ ጊዜ ጥር 11 ላይ ወደ 60 ሺህ የሚጠጉ የወንጌል አማኞች በስፍራ ፀሎት እንደሚያደርጉ አቶ ሳምሶን ቶማስ ጨምረዉ ገልፀዋል።
ስፍራውን ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ የከምባታ ዞን መንገዶች ፅህፈት ቤት በየዓመቱ መንገዶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
መንገዱን አስፋልት ለማድረግና በተራራዉ ላይ ሎጆችንና ሆቴሎች በመገንባት ምቹ ለማድረግ ፅህፈት ቤቱ እንደሚሰራ ተገልጿል። ስፍራዉን በዘላቂነት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ስራዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየተሰሩ ስለመሆናቸዉም ተገልጿል።
ሀምበሪቾ ተራራ ከዛሬ ሁለት አመት በፊት በደቡብ ክልል ምክር ቤት ቀርቦ በአዋጅ ህገ ደንብ በመፅደቅ የሀምበሪቾ ኢኮ ቱሪዝም ስፍራ ፅህፈት ቤት በመባል ከባህልና ቱሪዝም ቢሮ ዉጪ እራሱን ችሎ በቦርድ እንደሚመራ ተገልጿል። የ6 ወር የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሪፖርት እንደሚያሳየዉ 2 መቶ 75 ሺህ ቱሪስቶች ማዕከላዊ ኢትዮጵያን መጎብኘታቸውን ያመላክታል።
ከዚህ ዉስጥም ከ77 ሺህ በላይ የሚሆኑ ቱሪስቶች የሀምበሪቾ ተራራን የጎበኙ ሲሆን በዓመት ወደ 500,000 የሚጠጉ ቱሪስቶች ተራራዉን ይጎበኙታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የዱራሜ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ኃላፊና የቪዝት ከምባታ አስጎብኚ ድርጅት ባለቤት አቶ ሳምሶን ቶማስ ከብስራት ሬዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
የሀምበሪቾ ተራራን የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በከፍተኛ ፕሮጀክት ተራራውን የሚያቋርጡ 777 ደረጃዎችን መገንባቱ ተገልጿል።
ተራራው በቅርብ ጊዜ ለቱሪዝም ክፍት መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከ4 ና 5 አመት በፊት ትልቅ የፀሎት መዳረሻ ነበር። ከሀይኪንግ ጎን ለጎን በዓመት አንድ ጊዜ ጥር 11 ላይ ወደ 60 ሺህ የሚጠጉ የወንጌል አማኞች በስፍራ ፀሎት እንደሚያደርጉ አቶ ሳምሶን ቶማስ ጨምረዉ ገልፀዋል።
ስፍራውን ለቱሪስቶች ምቹ ለማድረግ የከምባታ ዞን መንገዶች ፅህፈት ቤት በየዓመቱ መንገዶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
መንገዱን አስፋልት ለማድረግና በተራራዉ ላይ ሎጆችንና ሆቴሎች በመገንባት ምቹ ለማድረግ ፅህፈት ቤቱ እንደሚሰራ ተገልጿል። ስፍራዉን በዘላቂነት የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ስራዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየተሰሩ ስለመሆናቸዉም ተገልጿል።
👍12❤5🙏1