The Christian News
5.09K subscribers
3.65K photos
50 videos
908 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
እዋዳን ልራመታ ኢየሱስ አቴቴ
እዎሮር ቆጡኮክ ኬሴኔ ሀንጨቴቴ (2X)

ገለተ ኡዋሙላ ልራንችኔ እሱም ፎቃ
ፎቃ ገትስት ብክናጋለታ ቡቃ ዮኮ ዮኮ

ዮኮ ዮኮ ዮኮ ኢየሱስና
እገለታ ኤጣ እሆና (2X)

ገለታ ዮሞ
ዘማሪ ደግነት አስፈው

https://www.youtube.com/watch?v=xQp0tvY3bOc
🔥1
#ቤተክርስቲያን ተዘረፈች

በፓስተር አማረ ሀጎስ የምትመራው "ግሬስ ላይፍ ኮሚዩኒቱ ቤተክርስቲያን" ተዘረፈች።

ቤተክርስቲያኒቱ ትጠቀምባቸው የነበሩ ከ40 በላይ የመገልገያ ቁሳቁሶች የተዘረፉ ሲሆን በዚህ ዝርፊያ ቀዳሚ ተጠርጣሪ እና የድርጊቱ አስተባባሪ በጥበቃ ስራ ላይ የነበረው ሰው እንደሆነ ተገልጿል።
በዚህ ዘፊያ ለሚዲያ የሚያገለግሉ ካሜራዎችን ጨምሮ የሙዚቃ መሳሪያዎች ኪቦርድ ፤ ማይክ ፤ ሚክሰር ፤ ጀነሬተር ፤ እስፒከሮች እና ድራም ይገኙበታል።

6.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ንብረት መዘረፉን የቤተክርስቲያኒቱን መሪዎች ዋቢ አድርጎ Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ ዘግቧል።

በዘገባው እንደተመለከትነው ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ ጥበቃ በተቀናጀ ሁኔታ እቃዎቹን ዘርፎ መሰወሩ ተገልጿል።

ዘገባውን በምስል ለመመልከት ሊንኩን ይጠቀሙ። https://www.youtube.com/watch?v=EQLwcb3pwWc

ምንጭ Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ
👍4
#አስደሳች #ዜና
#ቤተክርስቲያን #ሚሲዮናዊ ላከች።
ከታቦር ተራራ - ጋና አክራ

ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ ከእናት መካነ ኢየሱስ ወጥታ ማኅበረ ምእመን ከሆነች ገና ሁለት አስርትን እያስቆጠረች ብትሆንም እየሰራችው ያለችው ሥራ ግን የ200 ዓመታት ታሪክ ያላት ነው የሚመስለው።

ወንጌል ለዓለም ሁሉ ለማድረስ በታላቅ ግለትና ቅናት በመንቀሳቀስ በመላው ኢትዮጵያ በሰሜን፣ በደቡብ፣ በምዕራብና በምስራቅ ከ70 በላይ የወንጌል መልእክተኞችን በማሰማራት አርአያ የሆነች ማኅበረ ምእመን ናት።

የአገር ውስጡን እንዲህ እየስራችም ወንጌልን በዓለም ለማድረስ ሃላፊነቱ የኔ ነው በማለት በጥር 7 ቀን 2015 ዓ.ም በጉባኤ ፊት በጸሎት የሸኘችው ሚስዮናዊ ሳሙኤል ሐይሶ ዛሬ ማለዳ ወደ ጋና አክራ አቅንቷል።
👍4🔥3
#አስደሳች #ዜና
ታዳጊ ሊዲያ_እንድትፈታ ተወሰነ

ከሰሞኑ በሃላባ በእስር ላይ የነበረችው ታዳጊ ሊዲያ አበራ ከደቂቃዎች በፊት በዋለው ችሎት በ30ሺህ ብር ዋስ እንድትፈታ ተወስኗል።

ችሎቱ በትላንትና እለት ወደ ዛሬ የዞረ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ዛሬ ማለዳ ፍርድ ቤቱ ጠበቆች ሳይገኙ አላነብም በማለት ወደ ከሰዓት 9:00 ሰዓት ዞሮ የነበረ ሲሆን ምንም እንኳን ጠበቆቹ በስፍራው ባይገኙም ፍርድ ቤቱ ታዳጊዋ በ30ሺህ ብር ዋስ እንድትፈታ ውሳኔ አሳልፏል ሲል Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ ዘግቧል።

ምንም እንኳን ታዳጊዋ በዋስ እንድትፈታ ውሳኔ ቢተላለፍም አሁንም በአከባቢው በክርስቲያኖች ላይ ስጋት እንዳለ አክሎ ዘገባው አስታውሷል።
9👍2
" ምዕራባውያን እንግዳ የሆነ ባህል (የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት) እንድንፈቅድ #ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " - ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ

የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች በአፍሪካ አገራት ላይ በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።

ሙሴቬኒ ይህን ያሉት አገራቸው የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በተመለከተ አዲስ ሕግ እያረቀቀች ባለችበት ወቅት ነው።

የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ወንጀል በሆነባት ኡጋንዳ እየተረቀቀ ያለው ሕግ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ላይ የበለጠ ጠንካራ ቅጣት የሚጥል ነው።

ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ ትናንት ሐሙስ መጋቢት 07/2015 ዓ.ም. በአገሪቱ ፓርላማ ቀርበው ይህን ብለዋል ፦

" ምዕራባውያን እንግዳ የሆነ ባህል (የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት) እንድንፈቅድ #ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ።

ምዕራባውያን የራሳቸውን አሰራር በሌሎች ላይ ለመጫን የሚያባክኑትን ጊዜ ማቆም አለባቸው።

አውሮፓውያኑ የአጎት እና የአክስት ልጅ ጋር ትዳር ይመሰርታሉ እዚህ [ኡጋንዳ] የአንድ ጎሳ አባልን ማግባት ነውር ነው።

እነሱ የቅርብ ዘመድ እንዳያገቡ ማዕቀብ እንጣል ? ይህ የእኛ ሥራ አይደለም። "

ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪያንን አፈንጋጭ ብለው የገለጿቸው ሲሆን በጉዳዩ ላይ ብዙ ምክክር መደረግ አለበት ብለዋል።

ኡጋንዳ አሁን ላይ እያረቀቀች ባለችው ሕግ መሠረት በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ውስጥ ያለ ወይም እራሱን የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አፍቃሪ ብሎ የሚገልጽ ሰው እስከ 10 ዓመታት የእስር ጊዜን እንዲያሳልፍ ያዛል።

የኡጋንዳ መንግሥት በአገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የውጭ አገራት መንግሥታት ተቋማት እና ምዕራባውያን ኤጀንሲዎች የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን እያስተዋወቁ ነው በማለት ይከሳል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
9🔥2👍1
#ካውንስሉ
#ሃላባ

በተማሪ ሊዲያ ጉዳይ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያን ካውንስል ያወጣዉን መግለጫ የሀላባ ዞን አስተዳደር አጣጣለ

👉🏼 አስተዳድሩ ፤ ቤተክርቲያኒቷ በምዕመናን ላይ ይደርሳል ያለችዉ ጫና የተጋነነ ነዉ ቢልም ምዕመናን ጫና አንደማይደርስባቸዉ ግን ማረጋገጫ መስጠት አልቻለም

በትናንትናዉ እለት የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያን ካውንስል የሀላባ ዞንን በተመለከተ ያወጠው መግለጫ ፍጹም ዞኑን የማይገልጽና ለዘመናት ተቻችለው የኖሩ ማህበረሰቦችን ወደ ግጭት የሚያመራ ነው ሲል የሀላባ ዞን አስተዳደር አጣጥሎታል።

በመግለጫው የተጠቀሱት የምዕመናን እንግልቶች የሌሉና እጅግ የተጋነኑ ናቸዉ ሲል አስተዳድሩ የተናገረ ሲሆን ምዕመናን ጫና እንደማይደርስባቸዉ ግን ማረጋገጫ መስጠት አልቻለም።

በተጨማሪም እንግልቶቹ ከቤተ እምነቶች ቦታ ጋር በተያየዘ የሀገራችን ህግ በማይፈቅድ መልኩ ቤተ ዕምነቶችን ለመምራት በሚፈልጉ እና የህዝብን ሰላምና ደህንነት ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ ቡድኖች እየተራገበ ያለ ሐሰተኛ ድርጊት የመጣ ነው ብሏል።

ከሰሞኑም ከሊዲያ አበራ ጋር በተያየዘ ያለ ዕድሜዋ ታሰረች የሚባለው ግለሰቧ በህክምና በተረጋገጠው መሠረት ከ17 - 19 የዕድሜ ክልል የምትገኝ ስሆን በወቅቱ አምስት ግለሰቦች በከሰሱት ክስ መሠረት ጉዳዮዋ በህግ ሂደት ላይ መሆኑን ብስራት ራዲዮ ከመግለጫው ተመልክቷል።

በአመራሮች ጫና ህጻን የሆነች ያለክስና ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ታስራለች የሚባሉ እጅግ ስሜት ቀስቃሽ ውንጀላዎች ህዝቡን በሐይማኖት ለማጋጨት ሆን ተብሎ የተፈበረካ ዕኩይ ሴራ ከመሆኑም በላይ ህግና ስርኣትን ለመናድ ያለመም መሆኑ ሊታወቅ ይገባል ብሏል በመግለጫው።

በአጠቃላይ የካውንስሉ መግለጫ ዞኑን የማይገልጽና የዞኑን መልካም ገጽታ ለማበላሻት ያለመ መሆኑን እያሳወቅን የዞናችን ማህበረሰብ በሰከነ መልኩ ጉዳዩን በመገንዘብ የሴረኞችን ዕኩይ አላማ በጋራ እንድናከሽፍ ጥሪ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል በአዋጅ ቁጥር 2008/2012 በአዋጅ ሕጋዊ ሰውነት ያለው የወንጌል አማኞች ምክር ቤት መሆኑ ይታወቃል።

#ዳጉ_ጆርናል
👍3🔥1
#በሰላም #ተጠናቋል

ከ3000 በላይ የቤተ-እምነት መሪዎች፣ በውጪ አገር የሚኖሩ ዓለም አቀፍ አስተማሪዎች እና የወንጌል ሠራተኞች የታደሙበት "የመጋቢያን ኮንፍራንስ" በሚሊኒየም አዳራሽ ተጠናቀቀ።

“እርቅ፣ መንፈሳዊ ተሃድሶና መነቃቃት ለኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የነበረው የመሪዎች ኮንፍራን የተጠናቀቀ ሲሆን The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን በጉባኤው የነበረውን ድባብ በተመለከተ መሪዎችን አናግረን መረጃዎችን ይዘን ምሽት ላይ የምንመለስ ይሆናል።

ጉባኤዉ የአቋም መግለጫ ያዉጣ ሲሆን መሉ መግለጫዉን በyoutube ቻናላችን ይዘን እንመለሳለን።
👍72👏2
የኬንያ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን አስራት ለቤተክስርቲያን የማይሰጡ ሰራተኞች ላይ ክትትል እንደሚያደርጉ አስታወቁ

በኬንያ የናንዲ ግዛት ገዥ አዲስ የተሾሙ ስራ አስፈፃሚዎች 10 በመቶ ገቢያቸውን ለቤተክርስትያ እንዲሰጥ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸዉን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።የናንዲ ግዛት አስተዳዳሪ እስጢፋኖስ ሳንግ መመሪያው ያስፈለገው አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ከመሪዎች እና ከግዛቲቱ መንግስት ድጋፍ ስለሚያስፈልጋቸው ነው ብለዋል።

በዴይሊ ኔሽን ድህረ ገጽ ዘገባ መሰረት "በመጨረሻ የስራ ዘመኔ የምሾማቸዉ ዋና የስራ ኃላፊዎች በተለየ መንገድ መስራት እና ለህብረተሰቡ ማገልገል አለባቸው" ሲል ተናግረዋል።ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን ያሉት የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች በተገኙበት በተካሄደው የባለሥልጣናቱ ቃለ መሃላ ወቅት ነው።

ገዥው የአስራት ትእዛዙን እንዴት ለማስፈጸም እንዳቀዱ ባይታወቅም አስራት በማይሰጡ  የመንግስት ሰራተኞችን የስም ዝርዝር ከሀይማኖት አባቶች ጋር በመሆን ክትትል እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።አሥራት ለቤተ ክርስቲያን የመስጠት ልማድ የክርስትና የጥንት አካል ቢሆንም የግዴታ መሆን አለበት በሚለው ጉዳይ ላይ እርስ በእርሱ የሚጋጩ አስተያየቶች ተሰንዝረዋል፡፡

በኬንያ ያሉ ገዥዎች እና የስራ አስፈፃሚ ሰራተኞቻቸው ለትምህርት ቤቶች፣ ለመንገዶች እና ለሆስፒታሎች የታሰበ የህዝብ ገንዘብ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር ያደርጋሉ።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
👏63👍1