The Christian News
5.08K subscribers
3.65K photos
50 videos
908 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#አሳዛኝ #ዜና

መቼም ይሄንን ዜና ስንሰማ ልንደነግጥ እንደሚገባ ግልፅ ነዉ። ምክንያትም በሰዉ እና በእግዚአብሔር ፊት ቃልኪዳን ተገባብተዉ መልሰዉ ሲለያዩ የሚፈጠረዉ ... የአደባባይ ሚስጥር ነዉ።

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት 1ሺህ342 ፍቺዎች እና 14ሺህ 136 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታወቀ።

ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ የተመዘገበው የፍቺ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ተቀራራቢ ሲሆን፤ በ2014 በጀት ዓመት 1 ሺህ 623 የፍቺ ምዝገባዎች መደረጋቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።

በአዲስ አበባ ከ2012 እስከ 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ 16 ሺህ 35 ፍቺዎች እንደተካሄዱ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ መረጃ ያሳያል።

ትዳር በበርካታ ምክንያቶች ሊፈርስ እንደሚችል ጥናቶች የሚያመለክቱ ሲሆን ለአብነትም የኢኮኖሚ ድቀት፣ ቅናት እና አለመተማመን ወዘተ ይጠቀሳሉ።

እንግዲህ #የቤተክርስቲያን እና የመሪዎች የቤት ስራ ጨምሯል።
#ፍትህ
#የሀላባዋ_ታዳጊ_ሊዲያ_ጉዳይ
#ኢየሱስ

በቀን 22/06/2015 እንደማንኛውም ጊዜ ሊዲያ ት/ቤት ለመማር ክፍሏ ተገኝታለች።አንዲት ሙስሊም ተማሪ በክፍሏ ትወድቃለች። ወድቃም ኢየሱስ ጌታ ነው ትላለች።

ይኼኔ ነው ተማሪዋን ከነለበሰችው ዩኒፎርም ያለ ፖሊስ እና ፍርድ ቤት መጥሪያ አፋፍሶ ወደ ሀላባ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ይወስዷታል፤''ልጄን'' እያለ ሊጠይቃት የሄደውን አባቷንም ያስሩታል።ከዛ አባቷን ይፈቱታል።

ከተያዘችበት 5 ቀን በኋላ በ5ኛው ቀን 27/06/2015 ፍ/ቤት ያቀርቧታል፣"ድግምት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ በመስራት ወንጀል ጠርጥረናታል የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ይሰጠን" በማለታቸው 11 ቀን ተፈቅዶላቸው የ14 ዓመት ታዳጊዋን ከፖሊስ ጣቢያ ወደ ሃላባ ማረሚያ ተቋም ውስዷት እየማቀቀች ትገኛለች።

በምርመራ ወቅት በንቅሳት ድግምት አሰርተሻል በሚል እርቃኗን አስቀርቶ እንደፈተሿት እና ሊነገር የማይችል የመብት እና የስነልቦና ጥቃት እንደደረሰባት ሊዲያ ትናግራለች።

#ወንጌል ወንጀል አይደለም!!!
#ፍትህ_ለሊዲያ

በታዳጊዋ ዙሪያ Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ እና ሌሎች ማሕበራዊ ሚዲያዎች ለምታደርጉት ጥረት ምስጋናችን ከፍ ያለ ነዉ።

#share #ShareThisPost
🔥122👍1
#ወደ_ጌታ_እቅፍ_ተሰበሰበ

ተወዳጁ #ዘማሪ ወደ ቤተ ክርስቲያን ዝግጅት ሲያመራ በድንገተኛ አደጋ #ህይወቱ አለፈ።

ዘማሪ ፊሌ ኤልያስ ለአገልግሎት ተጋብዞ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት ዛሬ ማለዳ ከማርሳቢት-ሞያሌ አውራ ጎዳና ላይ ከጠዋቱ 4 ሰአት በደረሰበት የመኪና አደጋ ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።

የተወዳጁ ዘማሪ ቤተሰቦች እና ወጃጆቹ ሞቱን መቀበል ቢያቅታቸዉም "በአምልኮህ እና በምስጋና መዝሙሮችህ በሰዎች ህይወት ላይ ተፅእኖ በመፍጠር እንደዚህ አይነት መልካም ህይወት ኖረክ ትልቅ ውርስ ትተሃል። በማለት ገልፀዉታል።

ኢየሱስም። ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል፤
የዮሐንስ ወንጌል 11 : 25

እንደሚል The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለቤተሰቦቹ እና ለወዳጆቹ መፅናናትን ይመኛል።
1
7🔥2
#እግዚአብሔር ይመስገን ቦረና ዝናብ ጥሎዋል 🙏

በቦረና ዝናብ ያዘነበ እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን። ክብር ለንጉሱ❗️Yeesoon Gooftaa❗️

አሁንም ፀሎቱ እና ድጋፉ ተጠናክሮ ይቀጥል።
🥰5
የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ኪሪል ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ግንኙነት ባላት ቤተክርስቲያን ላይ የምትፈጥረውን ተጽእኖ እንድታቆም ጠየቁ፡፡

የኬቭ መንግስት የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከተመሰረተችበትና ረዥም ዘመናት ካስቆጠረው ገዳም ለቃ እንድትወጣ ያዘዘው አርብ እለት እንደነበር ይታወሳል፡፡

በዚህም ከጥቅምት ወር ጀምሮ የዩክሬን የደህንነት አገልግሎት በዩክሬን አብያተ ክርስቲያናት ላይ በየጊዜው ፍተሻ ሲያደርግ መቆየቱ፣ በጳጳሳቱ እና የገንዘብ ድጋፍ በሚያደርጉ ላይ ማዕቀብ መጣሉ እንዲሁም በደርዘን በሚቆጠሩ ቀሳውስት ላይ የወንጀል ክስ መክፈቱን ነው ሬውተርስ የዘገበው።

የዩክሬን ባህል ሚኒስቴር ፤ የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እስከ መጋቢት 29 ባለው ጊዜ ውስጥ 980 አመታት ካስቆጠረው የኪቭ-ፔቸርስክ ላቭራ ገዳም ግቢ መልቀቅ አለባት ሲል አሳስቧል፡፡

የሩሲያው ፓትሪያርክ የዩክሬን መንግስት ውሳኔን ተቃውሞውታል፡፡

ኪሪል የዩክሬን ምዕመናን መብት እና ነጻነት በገሃድ እየተጣሰ መሆኑ የሚያሳዝን ነው ብለዋል።

ፓትሪያርኩ የተወሰደሰውን እርምጃ በመቃውም የካቶሊኩ አባ ፍራንሲስን እና ሌሎች የሃይማኖት መሪዎች ዩክሬን ከድርጊቷ እንድትቆጠብ እንዲያሳምኑ ሲሉም ጠይቀዋል፡፡

“ገዳሙን በኃይል መዝጋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ የዩክሬን አማኞች መብት መጣስ ነው” ያሉት ፓትሪያርኩ፤ የሃይማኖት መሪዎች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድርጊቱን ለማስቆም የተቻላቸውን እንዲደርጉ ማሳሰባቸውም በቤተክርስቲያኗ ድረ ገፅ ላይ የወጣው መግለጫ አትቷል።

ቤተክርስቲያኗ ከሞስኮ ፓትርያርክ ጋር ያለኝን ግንኙነት አቋርጫለሁ ማለቷም አይዘነጋም።
በፓስተሮቻቸው #ጸሎት ተአምራትን ለማግኘት #ዕዳ ውስጥ የሚዘፈቁ ምዕመናን።

“ከሐሰተኛ #ነብያት ተጠንቀቁ” እንደሚለው መጽሃፉ፣ በኬንያ በርካቶች ፓስተሮች እንዲጸልዩላቸው ለመጠየቅ ዕዳ ውስጥ መዘፈቃቸው ተነግሯል።

ኤቫርሊን ኦኬሎ አንድ ፓስተር እንዲጸልይላት ለመክፈል ዕዳ ውስጥ ገብታለች።

በመቶዎች የሚቆጠር ዶላር ዕዳ እንዳለባት ስትናገር እያነባች ነው።

ነዋሪነቷ በኬንያዋ መዲና ናይሮቢ፣ ዋነኛው የድሆች መኖሪያ መንደር ኪቤራ ነው።

ኤቫርሊን በአሁኑ ወቅት አራት ልጆቿን መመገብ ተስኗታል።

ለወራት ያህል ምንም ገንዘብ እንደሌላት ለቢቢሲ ተናግራለች።

በአንድ ወቅት ነው ጸሎቱ ሕይወት ስለሚያሻሽለው ፓስተር የሰማችው።

አገኘችው፣ ፓስተሩም 15 ሺህ የኬንያ ሽልንግ (115 ዶላር) እንድታመጣ ጠየቃት።

ይህ የገንዘብ ስጦታ “የዘር መስዋዕት” በመባል ይታወቃል።

ተዓምር ለሚያደርጉ የሃይማኖት መሪዎች የሚበረከት የገንዘብ መዋጮ ነው።

ኤቫርሊን ገንዘቡን ከጓደኛዋ ተበደረች።

ጓደኛዋም ለእሷ ስትል ብድር ወስዳ ነው የሰጠቻት።

የዚህ ፓስተር ጸሎት በጣም ኃይለኛም ስለሆነ በሳምንት ውስጥ ገንዘቧ እንደሚመለስም ተነግሯታል።

የተባለው ተአምር አልደረሰም። እንዲያውም ይባስ ብሎ ጓደኛዋ የተበደረችውን ገንዘብ በጊዜ ባለመክፈሏ ወለዱ ጨመረ።

በአሁኑ ወቅት ኤቫርሊን ከ300 ዶላር በላይ ብድር አለባት። እንዴት እንደምትከፍለው ግን አታውቅም።

ጓደኛዋም አታናግራትም፤ ሥራም የላትም።

“በጣም ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ ስለሆንኩ ሙሉ በሙሉ ተስፋ ቆርጫለሁ” ትላለች።

ለማንኛውም ይህ ዘገባ BBC News Amharic ነው ሙሉውን ገብታችሁ አንብቡት። https://www.bbc.com/amharic/articles/c89e7dv8zvvo
የመሰረተ ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን #ግማሽ_ሚሊዬን ብር ድጋፍ አደረገች።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከየካቲት 30 እስከ መጋቢት 2/2015 ዓም ድረስ በቦረና አካባቢ ያሉትን ወገኖች ጎብኝታለች።

በቦረና ከተከሰተው ድር ቅ የተነሣ ለካፋ ችግር ለተጋለጡ የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች እና ሌሎች ወገኖች ግማሽ ሚልዮን ብር ወጭ በማድረግ በጊዜያዊነት እርዳታ አድርጋለች።

በሌላ በኩል በአከባቢው #የእግዚአብሔር_የእርዳታ_እንዲገለጥ በጋራ ጸሎት ከማድረጋቸውም በተጨማሪ ከተለያዩ የቦረና አከባቢዎች ከተውጣጡ የቤተክርስቲያን መሪዎች ጋር የቤተክርስቲያንቷ ፕሬዚዳንት የወደፊት የትኩረት አቅጣጫ ዙሪያ ላይ ምክክር አድርገዋል።

እግረ መንገዳቸውንም የዲላ አጥቢያን ጨምሮ የተለያዩ አጥቢያ ቤተክርስቲያናትን መጎብኘታቸውን እና ለቦረና አከባቢ ጸሎት እና የምግብ እህል ድጋፍ እንዲደረግ ማሳሰባቸውን የቤተክርስቲያኒቱ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አሳውቋል።
🔥2👍1
#አስደሳች_ዜና

ተማሪ ሊዲያ አበራ የዋስትና መብቷ እንዲከበር ይግባኝ ተጠየቀ

በሀላባ ከተማ በጊዜ ቀጠሮ መዝገብ በስር ላይ የምትገኘው ተማሪ ሊዲያ አበራ  የዋስትና መብቷ እንዲከበር ይግባኝ ተጠየቀ። የይግባኝ ጥያቄዉን የቀረበው ለሃላባ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው።

ይግባኙን ካቀረቡት 4 ጠበቆች መካከል ጠበቃ አበባየሁ  ጌታ አንዱ ሲሆኑ  ''ተማሪ ሊዲያ አበራ የ10 ኛ ክፍል ተማሪና  እድሜዋ 15 አመት እንደሆናት ጠቁመው ከዕድሜዋ አንጻር በስር ቤት ልታሳልፍ እንደማይገባ ገልጸዋል''

በዚህም መነሻ የዋስትና መብቷ ተከብሮ ከስር ተፈታ በውጭ ሆና ጉዳይዋን እንድትከታተል ይግባኝ መጠየቃቸውን አብራርተዋል።

ፍርድ ቤቱም ይግባኙን ለመልክቶ ብይን ለመስጠት ለመጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ/ም ቀጥሯል።

Via ታሪክ አዱኛ
#ዳጉ_ጆርናል
7👍3👏2