#ሕብረት ያወጀው የንስሃና ምልጃ ጽሎት ዛሬ ተጀምሯል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ከየካቲት 9-12/2015 ዓ.ም እንዲቆይ ያወጀው የንስሃና ምልጃ ጽሎት በትላንትናው እለት በሕብረቱ ጽ/ቤት ያስጀመረ ሲሆን በመላው ሀገሪቱ እና ከሀገር ውጪ ደግሞ ከዛሬ የሚጀምር ይሆናል።
"እግዚአብሔር ሆይ ተስፋ ባደረግንህ በእኛ ላይ ምህረትህ ትሁን"
በሚል መዝ 33:22 መሪ ቃል በማድረግ የተጀመረው የንስሃና ምልጃ ጽሎት
1. ስለ ፈሰሰው የንጹሃን ደም የእግዚአብሔርን ምህረትን መለመን
2. በጭንቀት ላይ ላሉ አረጋውያን፣ ወላጅ አጥ የሆኑ ህጻናትን፣ በችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች በሙሉ እግዚአብሔር በቃችሁ ብሎ እንዲያሳርፋቸው ምህረትን መለመን።
3. ለሃይማኖት እና ለሃገር መሪዎች ጥበብና ማስተዋል እንዲሰጣቸውና ፣ለሚመሩት ህዝባቸው የተሻለውን ፈጥነው የሚወስኑበትን ማስተዋል እንዲበዛላቸው መለመን።
ከላይ የተዘረዘሩት ነጥቦች ላይ የሚያተኩር ይሆናል።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ከየካቲት 9-12/2015 ዓ.ም እንዲቆይ ያወጀው የንስሃና ምልጃ ጽሎት በትላንትናው እለት በሕብረቱ ጽ/ቤት ያስጀመረ ሲሆን በመላው ሀገሪቱ እና ከሀገር ውጪ ደግሞ ከዛሬ የሚጀምር ይሆናል።
"እግዚአብሔር ሆይ ተስፋ ባደረግንህ በእኛ ላይ ምህረትህ ትሁን"
በሚል መዝ 33:22 መሪ ቃል በማድረግ የተጀመረው የንስሃና ምልጃ ጽሎት
1. ስለ ፈሰሰው የንጹሃን ደም የእግዚአብሔርን ምህረትን መለመን
2. በጭንቀት ላይ ላሉ አረጋውያን፣ ወላጅ አጥ የሆኑ ህጻናትን፣ በችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች በሙሉ እግዚአብሔር በቃችሁ ብሎ እንዲያሳርፋቸው ምህረትን መለመን።
3. ለሃይማኖት እና ለሃገር መሪዎች ጥበብና ማስተዋል እንዲሰጣቸውና ፣ለሚመሩት ህዝባቸው የተሻለውን ፈጥነው የሚወስኑበትን ማስተዋል እንዲበዛላቸው መለመን።
ከላይ የተዘረዘሩት ነጥቦች ላይ የሚያተኩር ይሆናል።
❤1
#ድንቅ ተዓምር ነው።
#አስደሳች አለቀ በተባለ ነገር ላይ ህይወት ይቀጥላል።
ምንም እንኳን የቱርክ ርዕደ መሬት (የመሬት መንቀጥቀጥ) ከ20,000 በላይ የሚሆን የሰዎን ህይወት ቢቀጥፍም ዛሬም ድረስ በተዓምር ስለተረፉ ሰዎች መስማት ብዙዎችን ከሃዘናቸው እያጽናናቸው ነው።
ዛሬ የተሰማው ዜና ደግሞ እናትና ልጅን ጨምሮ 5 ሰዎች በፍርስራሽ ውስጥ ከ9 ቀናት በኋላ በህይወት መገኘታቸውን የሚገልጽ ነው።
ከዘጠኝ ቀናት በፊት ከተከሰተው ርዕደ መሬት በኋላ ከተማዋን በማጽዳት ላይ የነበሩ የነፍስ አድን ሰራተኞች የ42 እና የ74 ዓመት አዛውንቶችን ጨምሮ 5 ሰዎችን ከፍርስራሽ ውስጥ በህይወት አግኝተዋቸዋል።
የዳርካ ከተማ ከንቲባ ሙዛፈር ቢያክ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ያጋሩት ቪዲዮ የነፍስ አድን ሰራተኞች የ74 ዓመቷ ሴሚሊክ ኬኪትስን እያበረታቱ ወደ አምቡላንስ ሲጭኗቸው አሳይቷል።
በሌላ በኩል የ42 ዓመቷ ሜሊክ ኢማንጉሉን ነፍስ አድን ሰራተኞች በህይወት ሲያገኟቸው አድናቆታቸውን እንደገለጹላቸው የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
በርዕደ መሬቱ ክፉኛ በተጎዳችው ሌላኛዋና አንታይካ በተባለችው ከተማ አንዲት እናት ከፍርስራሽ ውስጥ ከሁለት ልጆቿ ጋር በህይወት ተገኝታለች።
አለቀ በተባለ ነገር ላይ የአንዳንዶች ታሪክ ዛሬም ቀጥሏል።
#አስደሳች አለቀ በተባለ ነገር ላይ ህይወት ይቀጥላል።
ምንም እንኳን የቱርክ ርዕደ መሬት (የመሬት መንቀጥቀጥ) ከ20,000 በላይ የሚሆን የሰዎን ህይወት ቢቀጥፍም ዛሬም ድረስ በተዓምር ስለተረፉ ሰዎች መስማት ብዙዎችን ከሃዘናቸው እያጽናናቸው ነው።
ዛሬ የተሰማው ዜና ደግሞ እናትና ልጅን ጨምሮ 5 ሰዎች በፍርስራሽ ውስጥ ከ9 ቀናት በኋላ በህይወት መገኘታቸውን የሚገልጽ ነው።
ከዘጠኝ ቀናት በፊት ከተከሰተው ርዕደ መሬት በኋላ ከተማዋን በማጽዳት ላይ የነበሩ የነፍስ አድን ሰራተኞች የ42 እና የ74 ዓመት አዛውንቶችን ጨምሮ 5 ሰዎችን ከፍርስራሽ ውስጥ በህይወት አግኝተዋቸዋል።
የዳርካ ከተማ ከንቲባ ሙዛፈር ቢያክ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ያጋሩት ቪዲዮ የነፍስ አድን ሰራተኞች የ74 ዓመቷ ሴሚሊክ ኬኪትስን እያበረታቱ ወደ አምቡላንስ ሲጭኗቸው አሳይቷል።
በሌላ በኩል የ42 ዓመቷ ሜሊክ ኢማንጉሉን ነፍስ አድን ሰራተኞች በህይወት ሲያገኟቸው አድናቆታቸውን እንደገለጹላቸው የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
በርዕደ መሬቱ ክፉኛ በተጎዳችው ሌላኛዋና አንታይካ በተባለችው ከተማ አንዲት እናት ከፍርስራሽ ውስጥ ከሁለት ልጆቿ ጋር በህይወት ተገኝታለች።
አለቀ በተባለ ነገር ላይ የአንዳንዶች ታሪክ ዛሬም ቀጥሏል።
እንደ #ኢየሱስ 40 ቀን እጾማለው ያለው #ፓስተር ሞተ
እንደ #ኢየሱስ ክርስቶስ 40 ቀናት ለመጾም የሞከረው ሞዛምቢካዊ #ፓስተር ሕይወቱ አለፈ።
ፍራንሲስ ባራጃህ የተባለው ፓስተር ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ለ40 ቀናት በመጾም ያደረገውን ምሳሌ ለመድገም ባደረገው ሙከራ ነው ለሕልፈት የተዳረገው።
ፓስተሩ በሞዛምቢክ ማዕከላዊ ግዛት ማኒሺያ ውስጥ የምትገኘው ሳንታ ትሪንዳድ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መሥራች ሲሆን ከጾሙ ጋር በተያያዘ ሕይወቱ ማለፉ ረቡዕ ዕለት ተረጋግጧል።
ፓስተር ፍራንሲስ ባራጃህ በጾሙ ምክንያት ክፉኛ በተዳከመበት ጊዜ ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ቢሆንም ሕይወቱን ለማትረፍ ሳይቻል መቅረቱ ተዘግቧል።
ፓስተሩ ጾሙን ለ40 ቀናት ለማድረግ አቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ከ25 ቀናት ጾም በኋላ ግን በከፍተኛ ሁኔታ ክብደቱ ቀንሶ ለመቆምም ሆነ ለመራመድ ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር።
ይህም ሆኖ ግለሰቡ በጾሙ የቀጠለ ሲሆን፣ ከቀናት በኋላ ግን በዘመዶቹ እና በቤተክርስቲያኗ አባላት ውትወታ ወደ ሆስፒታል ተወስዷል።
ነገር ግን በጾሙ ምክንያት ክፉኛ በመጎዳቱ የተነሳ ሐኪሞች ጤናውን ለመመለስ ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ለህልፈት ተዳርጓል።
ፓስተር ፍራንሲስ ባራጃህ ጾሙን ከጀመረ በኋላ በታየበት ከፍተኛ አካላዊ ለውጥ የተነሳ የቤተክርስቲያኗ አባላት እና በዙሪያው ያሉ ሰዎች ሕልፈቱ ብዙም አላስደነቃቸውም።
ፍራንሲስ ባራጃህ በጾሙ ወቅት ከፍተኛ የክብደት መቀነስ እና የሰውነት አቋሙም ተቀይሮ እንደነበር ተነግሯል።
BBC News Amharic
እንደ #ኢየሱስ ክርስቶስ 40 ቀናት ለመጾም የሞከረው ሞዛምቢካዊ #ፓስተር ሕይወቱ አለፈ።
ፍራንሲስ ባራጃህ የተባለው ፓስተር ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ለ40 ቀናት በመጾም ያደረገውን ምሳሌ ለመድገም ባደረገው ሙከራ ነው ለሕልፈት የተዳረገው።
ፓስተሩ በሞዛምቢክ ማዕከላዊ ግዛት ማኒሺያ ውስጥ የምትገኘው ሳንታ ትሪንዳድ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መሥራች ሲሆን ከጾሙ ጋር በተያያዘ ሕይወቱ ማለፉ ረቡዕ ዕለት ተረጋግጧል።
ፓስተር ፍራንሲስ ባራጃህ በጾሙ ምክንያት ክፉኛ በተዳከመበት ጊዜ ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ቢሆንም ሕይወቱን ለማትረፍ ሳይቻል መቅረቱ ተዘግቧል።
ፓስተሩ ጾሙን ለ40 ቀናት ለማድረግ አቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ከ25 ቀናት ጾም በኋላ ግን በከፍተኛ ሁኔታ ክብደቱ ቀንሶ ለመቆምም ሆነ ለመራመድ ከማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሶ ነበር።
ይህም ሆኖ ግለሰቡ በጾሙ የቀጠለ ሲሆን፣ ከቀናት በኋላ ግን በዘመዶቹ እና በቤተክርስቲያኗ አባላት ውትወታ ወደ ሆስፒታል ተወስዷል።
ነገር ግን በጾሙ ምክንያት ክፉኛ በመጎዳቱ የተነሳ ሐኪሞች ጤናውን ለመመለስ ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ለህልፈት ተዳርጓል።
ፓስተር ፍራንሲስ ባራጃህ ጾሙን ከጀመረ በኋላ በታየበት ከፍተኛ አካላዊ ለውጥ የተነሳ የቤተክርስቲያኗ አባላት እና በዙሪያው ያሉ ሰዎች ሕልፈቱ ብዙም አላስደነቃቸውም።
ፍራንሲስ ባራጃህ በጾሙ ወቅት ከፍተኛ የክብደት መቀነስ እና የሰውነት አቋሙም ተቀይሮ እንደነበር ተነግሯል።
BBC News Amharic
👍1
#ምንድነው እየሆነ ያለው?
በአሜሪካ ኬንታኪ ግዛት ውስጥ በሚገኝ #asbury ዮንቨርስቲ ምን እየሆነ እንዳለ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል።
በከተማዋ ከሚገኙት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በዚህ ድንቅ ሪቫይቫል ውስጥ እየተካፈሉ ነው። ለ40 ደቂቃ ወደ ጸሎት የገቡት ወጣቶች ዛሬ ቀናትን ተሻግረዋል።
#አምልኮ ለአፍታ ሳይቋረጥ ሳምንት ተሻግሯል። ብዙዎች ከተለያዩ ከተሞች ወደስፍራው እየጎረፉ ነው። እውነት ነው በአሜሪካ ኬንታኪ ግዛት አስበሪ ዮንቨርስቲ ታላቅ #ሪቫይቫል ተነስቷል።
እንደሚል በኬንታኪ ስቴት በሚገኘው ዩኒቨርሲት ተማሪዎች በየሴሚስቴሩ በግቢው ውስጥ በሚገኘው የማመለኪያ አዳራሽ ለጸሎት የተወሰኑ ቀናት መገኘት ይኖርባቸዋል።
ባሳለፍነው ረቡዕ ላይ ለአምልኮ በተሰበሰቡበት ኳየሮች አምልኮ መምራት ይጀምራሉ። ይሁንና ጥቂት ደቂቃዎች እንደሚፈጅ የተጠበቀው አምልኮ ሳይቋረጥ ለሰዓታት ይቀጥላል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ይህንን የሰሙ ወገኖች ከየስቴቱ በስፍራው ይሰበሰባሉ ዛሬ ሳምንቱን ተሻግሯል።
በአንድ ወቅት ወንድማችን ተስፋዬ ሮበሌ ሪቫይቫል ምንድን ነው? ሲል ካሰፈራቸው ነጥቦች ሶስቱን እናስነብባችሁ።
1. "የሪቫይቫል" ቀዳማይ ግብ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት እንጂ፣ ልሳንና ተኣምር አይደለም!
2. የጸጋ ስጦታዎችም ቀዳማይ ግብ፣ እውነተኛ የሕይወት ተሐድሶና የሰዎች ድነት (ሰዎች ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸውና ጌታቸው መቀበላቸው) ነው!
3. "ሪቫይቫል" ነገን እውን ይሆናል ብለን የምንጠብቀው ክሥተት ሳይሆን፣ ዛሬን የምንተገብረውና የምንኖረው ክርስቲያናዊ ሕይወት ነው! እውነተኛ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት ባለበት ቦታ ሁሉ "ሪቫይቫል" አለ:: ይህ በሌለበትም ቦታ "ሪቫይቫል" የለም!
ሲል አስፍሮ ነበር። ሪቫይቫል ምንድነው በቀጣይ ይዘን እንመለሳለን።
በአሜሪካ ኬንታኪ ግዛት ውስጥ በሚገኝ #asbury ዮንቨርስቲ ምን እየሆነ እንዳለ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል።
በከተማዋ ከሚገኙት ከግማሽ በላይ የሚሆኑት በዚህ ድንቅ ሪቫይቫል ውስጥ እየተካፈሉ ነው። ለ40 ደቂቃ ወደ ጸሎት የገቡት ወጣቶች ዛሬ ቀናትን ተሻግረዋል።
#አምልኮ ለአፍታ ሳይቋረጥ ሳምንት ተሻግሯል። ብዙዎች ከተለያዩ ከተሞች ወደስፍራው እየጎረፉ ነው። እውነት ነው በአሜሪካ ኬንታኪ ግዛት አስበሪ ዮንቨርስቲ ታላቅ #ሪቫይቫል ተነስቷል።
እንደሚል በኬንታኪ ስቴት በሚገኘው ዩኒቨርሲት ተማሪዎች በየሴሚስቴሩ በግቢው ውስጥ በሚገኘው የማመለኪያ አዳራሽ ለጸሎት የተወሰኑ ቀናት መገኘት ይኖርባቸዋል።
ባሳለፍነው ረቡዕ ላይ ለአምልኮ በተሰበሰቡበት ኳየሮች አምልኮ መምራት ይጀምራሉ። ይሁንና ጥቂት ደቂቃዎች እንደሚፈጅ የተጠበቀው አምልኮ ሳይቋረጥ ለሰዓታት ይቀጥላል።
በሺዎች የሚቆጠሩ ይህንን የሰሙ ወገኖች ከየስቴቱ በስፍራው ይሰበሰባሉ ዛሬ ሳምንቱን ተሻግሯል።
በአንድ ወቅት ወንድማችን ተስፋዬ ሮበሌ ሪቫይቫል ምንድን ነው? ሲል ካሰፈራቸው ነጥቦች ሶስቱን እናስነብባችሁ።
1. "የሪቫይቫል" ቀዳማይ ግብ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት እንጂ፣ ልሳንና ተኣምር አይደለም!
2. የጸጋ ስጦታዎችም ቀዳማይ ግብ፣ እውነተኛ የሕይወት ተሐድሶና የሰዎች ድነት (ሰዎች ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸውና ጌታቸው መቀበላቸው) ነው!
3. "ሪቫይቫል" ነገን እውን ይሆናል ብለን የምንጠብቀው ክሥተት ሳይሆን፣ ዛሬን የምንተገብረውና የምንኖረው ክርስቲያናዊ ሕይወት ነው! እውነተኛ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት ባለበት ቦታ ሁሉ "ሪቫይቫል" አለ:: ይህ በሌለበትም ቦታ "ሪቫይቫል" የለም!
ሲል አስፍሮ ነበር። ሪቫይቫል ምንድነው በቀጣይ ይዘን እንመለሳለን።
❤1
#በሊቢያ ስድስት የግብፅ #ክርስቲያኖች ታፍነው ተወሰዱ።
ስድስቱ ሰዎች ለስራ ወደ ሊቢያ ዋና ከተማ ትሪፖሊ ተጉዘዋል እንደነበር ምንጮች ተናግረዋል። ነገር ግን ከኤርፖርት ወደ ስራ ቦታቸው ሲጓዙ በህገ ወጥ ኬላ ላይ መቆማቸው ታውቋል። ሊቢያዊው ሾፌራቸው ወዲያው የተፈታ ሲሆን ነገር ግን ክርስቲያኖቹ ወዳልታወቀ ቦታ ተዛውረዋል ሲሉ ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጮች ተናግረዋል።
ድርጊቱን በቅርበት የተከታተለው ግብፃዊው ጋዜጠኛ ናደር ሹክሪ፣ ታጋቾቹ በአንድ ምርኮ 15,000 የሊቢያ ዲናር (3,100 ዶላር) ክፍያ እንደሚፈልጉ ሰምቻለው ሲል ጽፏል።
ናድር ሹክሪ ቤተሰቦቻቸው ቤታቸውን ሳይሸጡ እነዚህን ክፍያዎች መክፈል እንደማይችሉ ተናግራለች። የግብፅ ፕሬዝዳንት እና መንግስት ጣልቃ እንዲገቡ አሳስበዋል።
አክሎም በየቀኑ ድብደባ እንደሚደርስባቸው እና በጣም ትንሽ ምግብ እንደሚያገኙም ተናግሯል።
ስድስቱ ሰዎች ለስራ ወደ ሊቢያ ዋና ከተማ ትሪፖሊ ተጉዘዋል እንደነበር ምንጮች ተናግረዋል። ነገር ግን ከኤርፖርት ወደ ስራ ቦታቸው ሲጓዙ በህገ ወጥ ኬላ ላይ መቆማቸው ታውቋል። ሊቢያዊው ሾፌራቸው ወዲያው የተፈታ ሲሆን ነገር ግን ክርስቲያኖቹ ወዳልታወቀ ቦታ ተዛውረዋል ሲሉ ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጮች ተናግረዋል።
ድርጊቱን በቅርበት የተከታተለው ግብፃዊው ጋዜጠኛ ናደር ሹክሪ፣ ታጋቾቹ በአንድ ምርኮ 15,000 የሊቢያ ዲናር (3,100 ዶላር) ክፍያ እንደሚፈልጉ ሰምቻለው ሲል ጽፏል።
ናድር ሹክሪ ቤተሰቦቻቸው ቤታቸውን ሳይሸጡ እነዚህን ክፍያዎች መክፈል እንደማይችሉ ተናግራለች። የግብፅ ፕሬዝዳንት እና መንግስት ጣልቃ እንዲገቡ አሳስበዋል።
አክሎም በየቀኑ ድብደባ እንደሚደርስባቸው እና በጣም ትንሽ ምግብ እንደሚያገኙም ተናግሯል።
ለተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ጸሎት ከተፈቀደ በኋላ የእንግሊዝ ቤተ-ክርስቲያን መሪ ተወገዙ።
የእንግሊዝ ቤተክርስቲያን ለተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ጸሎት እንዲደረግ ድጋፍ ከሰጠች በኋላ ከመላው ዓለም የተሰባሰቡ የአንግሊካን መሪዎች የቤተ ክርስቲያኗ መሪ ጀስቲን ዌልቢ መሪያችን አይደሉም አሉ።
በመላው ዓለም የሚገኙት እና 42 አባላት ካሉት የአንግሊካን ኅብረት አባላት መካከል አሥሩን የሚወክሉት ሊቀ ጳጳሳት፤ ጀስቲን ዌልቢ ከአሁን በኋላ “የዓለም አቀፉ ኅብረት መሪ” አድርገን አንመለከታቸውም ብለዋል።
ሊቀ ጳጳሳቱ ጨምረውም የእንግሊዝ ቤተ-ክርስቲያን “እናት ቤተ-ክርስቲያን” ከመሆን “ውድቅ” ተደርጋለች ብለዋል።
42 አንግሊካን አብያተ ክርስቲያናትን ያቀፈው ዓለም አቀፉ የአንግሊካን ኅብረት እአአ 1867 በእንግሊዝ አገር ከተመሠረተ ጀምሮ የካንተበሪ ሊቀ ጳጳሳት የኅብረቱ መንፈሳዊ መሪ ኃላፊነትን ሲወስዱ ቆይተዋል።
ይህንን ሃሳብ የተቃወሙት 10 ሊቃነ ጳጳሳት እና በአሜሪካ እና ብራዚል የሚገኙ ሁለት ተገንጣይ አብያተ ክርስቲያናት የደቡብ ሱዳን፣ የቺሊ፣ የኢንዲያን ኦሽን፣ የኮንጎ፣ የሚያንማር፣ የባንግላዴሽ፣ የኡጋንዳ፣ የሱዳን፣ የአሌክሳንደሪያ እና የሜላኔሲያ ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት በተለይ በእሲያ እና በአፍሪካ ብዙ ተከታዮች ያሏቸው ናቸው።
ተቃውሟቸውን ያሰሙት ሊቃነ ጳጳሳት ባወጡት መግለጫ ላይ የእንግሊዝ ቤተ-ክርስቲያን በጥንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ጸንተው ከሚገኙት የኅብረቱ አባላት ለመለየት ወስናለች ብለዋል።
ይሁን እንጂ አሁንም ቤተ-ክርስቲያኗ በተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ላይ ያላት አቋም አልተቀየረም እንዲሁም የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ ማድረግ አልተፈቀደም።
የእንግሊዝ ቤተክርስቲያን ለተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ጸሎት እንዲደረግ ድጋፍ ከሰጠች በኋላ ከመላው ዓለም የተሰባሰቡ የአንግሊካን መሪዎች የቤተ ክርስቲያኗ መሪ ጀስቲን ዌልቢ መሪያችን አይደሉም አሉ።
በመላው ዓለም የሚገኙት እና 42 አባላት ካሉት የአንግሊካን ኅብረት አባላት መካከል አሥሩን የሚወክሉት ሊቀ ጳጳሳት፤ ጀስቲን ዌልቢ ከአሁን በኋላ “የዓለም አቀፉ ኅብረት መሪ” አድርገን አንመለከታቸውም ብለዋል።
ሊቀ ጳጳሳቱ ጨምረውም የእንግሊዝ ቤተ-ክርስቲያን “እናት ቤተ-ክርስቲያን” ከመሆን “ውድቅ” ተደርጋለች ብለዋል።
42 አንግሊካን አብያተ ክርስቲያናትን ያቀፈው ዓለም አቀፉ የአንግሊካን ኅብረት እአአ 1867 በእንግሊዝ አገር ከተመሠረተ ጀምሮ የካንተበሪ ሊቀ ጳጳሳት የኅብረቱ መንፈሳዊ መሪ ኃላፊነትን ሲወስዱ ቆይተዋል።
ይህንን ሃሳብ የተቃወሙት 10 ሊቃነ ጳጳሳት እና በአሜሪካ እና ብራዚል የሚገኙ ሁለት ተገንጣይ አብያተ ክርስቲያናት የደቡብ ሱዳን፣ የቺሊ፣ የኢንዲያን ኦሽን፣ የኮንጎ፣ የሚያንማር፣ የባንግላዴሽ፣ የኡጋንዳ፣ የሱዳን፣ የአሌክሳንደሪያ እና የሜላኔሲያ ሊቃነ ጳጳሳት ናቸው። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት በተለይ በእሲያ እና በአፍሪካ ብዙ ተከታዮች ያሏቸው ናቸው።
ተቃውሟቸውን ያሰሙት ሊቃነ ጳጳሳት ባወጡት መግለጫ ላይ የእንግሊዝ ቤተ-ክርስቲያን በጥንታዊ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ጸንተው ከሚገኙት የኅብረቱ አባላት ለመለየት ወስናለች ብለዋል።
ይሁን እንጂ አሁንም ቤተ-ክርስቲያኗ በተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ላይ ያላት አቋም አልተቀየረም እንዲሁም የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በቤተ-ክርስቲያን ውስጥ ማድረግ አልተፈቀደም።
👍3
#መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን አስቸኳይ መግለጫ ሰጠች #በቦረና በአካል አይተናል የብዙዎች ሁኔታ አሳ ነዉ # ኦሮሚያ ክልል ያቀረበውን እርቅ እንደግፋለን
https://youtu.be/3sD2948LTc4
https://youtu.be/3sD2948LTc4
YouTube
#መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን አስቸኳይ መግለጫ ሰጠች #በቦረና በአካል አይተናል የብዙዎች ሁኔታ አሳሳቢ ነዉ # ኦሮሚያ ክልል ያቀረበውን እርቅ እንደግፋለን
#መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን አስቸኳይ መግለጫ ሰጠች #በቦረና በአካል አይተናል የብዙዎች ሁኔታ አሳሳቢ ነዉ # ኦሮሚያ ክልል ያቀረበውን እርቅ እንደግፋለን
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome…
ወዳችሁ እና ፈቅዳችሁ ስለምትመለከቱን ከልብ እናመሰግናለን!!! Like, Share ማድረጎን አይርሱ!!
#በ0930699543_ማንኛውንም_አይነት_የክርስቲያን_መረጃዎችን_ለክርስቲያን_ዜና_ሚዲያ_መጠቆም_ይችላሉ
#The_Christian_News
Welcome…
👍5🔥1
ጕዳዩ፦ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን የተነገረውን የተሳሳተ አገላለጽ እንዲታረም ስለመጠየቅ
የሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ በተለያዩ ግለ ሰቦች የተጻፉና ለሕዝብ ይጠቅማሉ የተባሉ መጽሐፎችን በመገምገም ጸሐፊዎችንና አንባቢዎች በጥሩ አመለካከት እንዲታነጹ በማድረግ የተቀደሰ ስራ የሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል። ለዚህ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ በርቱ ማለት እንፈልጋለን።
በዚሁ የመጽሐፍ ክበብ በጥር ወር ላይ፣ “የተከዳ እውነት” በሚል በቀረበውና በመጋቢ ስሜ ታደሰ የተጻፈ መጽሐፍ ግምገማ ላይ የተገኙት የመጽሐፉ ጸሐፊ “መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካልቪናዊ ቤተክርስቲያን ነች” በማለት በምንም ዓይነት ሁኔታ የማይወክላትን የራሳቸውን እይታ የቤተክርስቲያኗ እምነትና ልምምድ አድርገው ተናግረዋል።
የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አንድም ቀን እኛ ካልቪን ነን ወይም አርሚን ነን ብላ አስተምራ አታውቅም። ከሁለቱም ጎራ ባትሆንም አመጣጧ ከአናባፕቲስት ስትሆን ሰዎች ለመዳን ክርስቶስ ኢየሱስን ማመን እንዳለባቸው/እንደሚጠበቅባቸው/፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ለሁሉም ሰው እንጂ ለተወሰኑ ምርጦች ብቻ እንዳልሆነ፣ ሰው የተሰጠውን በወንጌል የማመን ዕድል ሊጠቀም ወይም ላይጠቀም እንደሚችል፣ ሰው የተዘጋጀለትን የዘላለም ክብር ለማግኘት መጽናት እንደሚገባው የእግዚአብሔርም ጸጋ ለዚህ እንደሚረዳው ታምናለች ታስተምራለች።
ስለዚህ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካልቪናዊት ነች የሚለው የተሳሳተ ፍረጃ በቀረበበት የሕንጸት መድረክ ላይ የተሳሳተ ገለጻ እንደሆነ ታውቆ ማስተካከያ እንዲደረግ እየጠየቅን የትምህርትና ስልጠና መምሪያ በቅርበት እንዲከታተል ግልባጭ ተደርጎለታል።
የሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ በተለያዩ ግለ ሰቦች የተጻፉና ለሕዝብ ይጠቅማሉ የተባሉ መጽሐፎችን በመገምገም ጸሐፊዎችንና አንባቢዎች በጥሩ አመለካከት እንዲታነጹ በማድረግ የተቀደሰ ስራ የሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል። ለዚህ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ በርቱ ማለት እንፈልጋለን።
በዚሁ የመጽሐፍ ክበብ በጥር ወር ላይ፣ “የተከዳ እውነት” በሚል በቀረበውና በመጋቢ ስሜ ታደሰ የተጻፈ መጽሐፍ ግምገማ ላይ የተገኙት የመጽሐፉ ጸሐፊ “መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካልቪናዊ ቤተክርስቲያን ነች” በማለት በምንም ዓይነት ሁኔታ የማይወክላትን የራሳቸውን እይታ የቤተክርስቲያኗ እምነትና ልምምድ አድርገው ተናግረዋል።
የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አንድም ቀን እኛ ካልቪን ነን ወይም አርሚን ነን ብላ አስተምራ አታውቅም። ከሁለቱም ጎራ ባትሆንም አመጣጧ ከአናባፕቲስት ስትሆን ሰዎች ለመዳን ክርስቶስ ኢየሱስን ማመን እንዳለባቸው/እንደሚጠበቅባቸው/፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ለሁሉም ሰው እንጂ ለተወሰኑ ምርጦች ብቻ እንዳልሆነ፣ ሰው የተሰጠውን በወንጌል የማመን ዕድል ሊጠቀም ወይም ላይጠቀም እንደሚችል፣ ሰው የተዘጋጀለትን የዘላለም ክብር ለማግኘት መጽናት እንደሚገባው የእግዚአብሔርም ጸጋ ለዚህ እንደሚረዳው ታምናለች ታስተምራለች።
ስለዚህ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካልቪናዊት ነች የሚለው የተሳሳተ ፍረጃ በቀረበበት የሕንጸት መድረክ ላይ የተሳሳተ ገለጻ እንደሆነ ታውቆ ማስተካከያ እንዲደረግ እየጠየቅን የትምህርትና ስልጠና መምሪያ በቅርበት እንዲከታተል ግልባጭ ተደርጎለታል።
👍4
ኬንያ በትምህርት ቤቶች ውስጥ የፀረ ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ዘመቻ ጀመረች።
ኬንያ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተንሰራፍቷል ያለችው የተመሳሳይ ጾታ አጀንዳ ላይ ዘመቻ ጀመረች።
የኬንያ የትምህርት ሚንስትር ኢዚኬል ማቾጉ በኬንያ ትምህር ቤቶች ውስጥ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች አጀንዳ ሰርጎ ገብቷል ሲሉ ለአገሪቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል።
ሚንስትሩ በትምህር ቤቶች ውስጥ ‘የተመሳሳይ ጾታ አጀንዳን’ ለማስቀረት በኬንያ አንጀሊካን ቤተ-ክርስቲያን የሚመሩ ጉዳዩን የሚከታተሉ ሰዎች ይሾማሉ ብለዋል።
በኬንያ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የተመለከቱ ጉዳዮችን የሚከታተል ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን ኮሚቴው መማሪያ እና አጋዥ መጽሐፍትን መከለሰን ሊያካትት እንደሚችል ትምህርት ሚንስትሩ ገልጸዋል።
ይህ የኬንያ ትምህርት ሚንስቴር እቅድ የተሰማው ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አደጋ ፈጥሯል በማለት በመላው ኬንያ ጸሎት እንዲደረግ ካወጁ ከቀናት በኋላ ነው።
የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ባለቤት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ‘ቤተሰብ በሚባለው ተቋም ላይ አደጋ ደቅኗል' ብለዋል።
“አባት፣ እናት እና ልጆች ያሉበትን የቤተሰብ ተቋም ማጠናከር እንፈልጋለን። የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት በመጽሐፍ ቅዱስም ሆነ በአፍሪካውያን ዘንድ ተቀባይነት የለውም። የቤተሰብ እሴቶችን እንጠብቅ” ብለዋል ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ።
አንዳንድ የተመሳሳይ ጾታ ደጋፊዎች ግን ይህ የመንግሥት እርምጃ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስለ ተመሳሳይ ጾታ የተሳሳተ ግንዛቤ አንዲሰርጽ ያደርጋል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት በኬንያ ሕጋዊ አይደለም። የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚቃወሙ አመለካከቶች ባለፉት ቀናት ጠንከር ብለው ታይተዋል።
ኬንያ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተንሰራፍቷል ያለችው የተመሳሳይ ጾታ አጀንዳ ላይ ዘመቻ ጀመረች።
የኬንያ የትምህርት ሚንስትር ኢዚኬል ማቾጉ በኬንያ ትምህር ቤቶች ውስጥ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች አጀንዳ ሰርጎ ገብቷል ሲሉ ለአገሪቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል።
ሚንስትሩ በትምህር ቤቶች ውስጥ ‘የተመሳሳይ ጾታ አጀንዳን’ ለማስቀረት በኬንያ አንጀሊካን ቤተ-ክርስቲያን የሚመሩ ጉዳዩን የሚከታተሉ ሰዎች ይሾማሉ ብለዋል።
በኬንያ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የተመለከቱ ጉዳዮችን የሚከታተል ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን ኮሚቴው መማሪያ እና አጋዥ መጽሐፍትን መከለሰን ሊያካትት እንደሚችል ትምህርት ሚንስትሩ ገልጸዋል።
ይህ የኬንያ ትምህርት ሚንስቴር እቅድ የተሰማው ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አደጋ ፈጥሯል በማለት በመላው ኬንያ ጸሎት እንዲደረግ ካወጁ ከቀናት በኋላ ነው።
የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ባለቤት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ‘ቤተሰብ በሚባለው ተቋም ላይ አደጋ ደቅኗል' ብለዋል።
“አባት፣ እናት እና ልጆች ያሉበትን የቤተሰብ ተቋም ማጠናከር እንፈልጋለን። የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት በመጽሐፍ ቅዱስም ሆነ በአፍሪካውያን ዘንድ ተቀባይነት የለውም። የቤተሰብ እሴቶችን እንጠብቅ” ብለዋል ቀዳማዊት እመቤት ሬቸል ሩቶ።
አንዳንድ የተመሳሳይ ጾታ ደጋፊዎች ግን ይህ የመንግሥት እርምጃ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስለ ተመሳሳይ ጾታ የተሳሳተ ግንዛቤ አንዲሰርጽ ያደርጋል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት በኬንያ ሕጋዊ አይደለም። የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚቃወሙ አመለካከቶች ባለፉት ቀናት ጠንከር ብለው ታይተዋል።
👍7👏1
የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ከኡጋንዳ ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘዋል ስለተባሉት ሰዎች የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መልስ ሰጠ።
የዓለም ፍፃሜ ተቃርቧል በሚል ፍራቻ በኡጋንዳ ምስራቃዊ ክፍል በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከመንደራቸው ወጥተው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን የኡጋንዳ ፖሊስ ከሰሞኑ አስታውቆ ጉዳዩንም እየመረመረ መሆኑን ገልጾ ነበር።ኡጋንዳዊያኑ "የክርስቶስ ሐዋሪያዎች" የተሰኘ እምነት ተከታዮች የዓለም ፍጻሜ በቅርቡ የሚጀምረው ከአካባቢያቸው መሆኑን በማመን ንብረታቸውን በመሸጥ ወደ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ እየገቡ ያሉት ከየካቲት ጀምሮ እንደሆነ የኡጋንዳ ፖሊስ ተናግሯል ተብሏል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባዩ አምባሳደር መለስ አለም በሳምንታዊ መግለጫቸው ከሰሞኑ ከ100 በላይ ኡጋንዳዊያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል ፣መድህን የሚገኘውም በኢትዮጵያ ነው በሚል ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ስለተባሉት የሀይማኖት ሰዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ዜናውን እንደሰሙት የተናገሩት አምባሳደር መለስ "በተባለው ልክ ከኡጋንዳ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የሚያሳይ ነገር የለም፣ ከወትሮው የተለየ ቁጥር ያላቸው ኡጋንዳዊያን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የሚያሳይ ነገር የለም" ብለዋል።
የዓለም ፍፃሜ ተቃርቧል በሚል ፍራቻ በኡጋንዳ ምስራቃዊ ክፍል በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከመንደራቸው ወጥተው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን የኡጋንዳ ፖሊስ ከሰሞኑ አስታውቆ ጉዳዩንም እየመረመረ መሆኑን ገልጾ ነበር።ኡጋንዳዊያኑ "የክርስቶስ ሐዋሪያዎች" የተሰኘ እምነት ተከታዮች የዓለም ፍጻሜ በቅርቡ የሚጀምረው ከአካባቢያቸው መሆኑን በማመን ንብረታቸውን በመሸጥ ወደ ኢትዮጵያ በሕገወጥ መንገድ እየገቡ ያሉት ከየካቲት ጀምሮ እንደሆነ የኡጋንዳ ፖሊስ ተናግሯል ተብሏል።የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባዩ አምባሳደር መለስ አለም በሳምንታዊ መግለጫቸው ከሰሞኑ ከ100 በላይ ኡጋንዳዊያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል ፣መድህን የሚገኘውም በኢትዮጵያ ነው በሚል ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ስለተባሉት የሀይማኖት ሰዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
ዜናውን እንደሰሙት የተናገሩት አምባሳደር መለስ "በተባለው ልክ ከኡጋንዳ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የሚያሳይ ነገር የለም፣ ከወትሮው የተለየ ቁጥር ያላቸው ኡጋንዳዊያን ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን የሚያሳይ ነገር የለም" ብለዋል።
👍2🔥1
#የፓስተሮች ኮንፍረንስ ሊካሔድ ነዉ።
በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት አዘጋጅነት ከ3000 በላይ የቤተ ዕምነት መሪዎች የሚሳተፊበት ፓስተርስ ኮንፍረንስ በሚሊኒየም አዳራሽ ሊካሔድ ነዉ።
በዚህ የመጋቢያን ኮንፍራንስ ከ3000 በላይ የቤተ-እምነት መሪዎች፣ በውጪ አገር የሚኖሩ ዓለም አቀፍ አስተማሪዎች እና የወንጌል ሠራተኞች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው በዚህ አገር አቀፍ ኮንፍራንስ፣ “እርቅ፣ መንፈሳዊ ተሃድሶና መነቃቃት ለኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት” በተሰኘ መሪ አሳብ፣
ሁለንተናዊ ክርስቲያናዊ አመራር፤
የወንጌል መልዕክትና መልዕክተኛው፤
ሰላምና እርቅ፤ ከተማ አቀፍ የወንጌል አገልግሎት፤ የባህላዊ እምነት ተግዳሮትን መመከት፤ የተሰኙ ንዑሳን ርዕሶች ትኩረት የሚደረግባቸው እንደሆነም ታዉቋል።
ጉዳዩን አስመልክቶ የሕብረቱ ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
የመሪዎቹ ኮንፍረንስ ከመጋቢት 6-8 ቀን /2015 ዓ.ም የሚካሔድ ሲሆን ከ2:30 - 11:00 የመሪዎች ኮንፍረንስ ከ11:30 - 2:00 ሰዓት ልዩ ኮንፍረንስ ለሁሉም ለወንጌል አማኞች በሙሉ የሚከወን ይሆናል።
ሙሉ መግለጫዉን ለመመልከት ሊንኩን ይጠቀሙ። https://youtu.be/vQ80ZKds3_w
ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለግዎ፣ ከታች 👇 በሚገኙ ስልክ ቁጥሮች በመገልገል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
09-95-99-56-77
09-95-99-56-67
09-95-99-57-06
09-95-99-57-07
09-26-76-82-81
09-11-43-14-43
በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት አዘጋጅነት ከ3000 በላይ የቤተ ዕምነት መሪዎች የሚሳተፊበት ፓስተርስ ኮንፍረንስ በሚሊኒየም አዳራሽ ሊካሔድ ነዉ።
በዚህ የመጋቢያን ኮንፍራንስ ከ3000 በላይ የቤተ-እምነት መሪዎች፣ በውጪ አገር የሚኖሩ ዓለም አቀፍ አስተማሪዎች እና የወንጌል ሠራተኞች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው በዚህ አገር አቀፍ ኮንፍራንስ፣ “እርቅ፣ መንፈሳዊ ተሃድሶና መነቃቃት ለኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት” በተሰኘ መሪ አሳብ፣
ሁለንተናዊ ክርስቲያናዊ አመራር፤
የወንጌል መልዕክትና መልዕክተኛው፤
ሰላምና እርቅ፤ ከተማ አቀፍ የወንጌል አገልግሎት፤ የባህላዊ እምነት ተግዳሮትን መመከት፤ የተሰኙ ንዑሳን ርዕሶች ትኩረት የሚደረግባቸው እንደሆነም ታዉቋል።
ጉዳዩን አስመልክቶ የሕብረቱ ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶ ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
የመሪዎቹ ኮንፍረንስ ከመጋቢት 6-8 ቀን /2015 ዓ.ም የሚካሔድ ሲሆን ከ2:30 - 11:00 የመሪዎች ኮንፍረንስ ከ11:30 - 2:00 ሰዓት ልዩ ኮንፍረንስ ለሁሉም ለወንጌል አማኞች በሙሉ የሚከወን ይሆናል።
ሙሉ መግለጫዉን ለመመልከት ሊንኩን ይጠቀሙ። https://youtu.be/vQ80ZKds3_w
ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለግዎ፣ ከታች 👇 በሚገኙ ስልክ ቁጥሮች በመገልገል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
09-95-99-56-77
09-95-99-56-67
09-95-99-57-06
09-95-99-57-07
09-26-76-82-81
09-11-43-14-43
👍4❤2