አስተርዮ ማርያም
በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡
የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ ፷፬ ዓመታትን ከኖረች በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባስገነዘባት መሠረት በክብር ዐርፋለች፡፡ የዚህን ዓለም መከራና ሥቃይ ለሰዎች ድኅነት የተቀበለችው ክብርት እናታችን በሥጋ ብትሞትም እንደ ልጇ ደግሞ በትንሣኤዋ ተነሥታለች፤ ይህም የሆነው በተቀደሰች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ነው፡፡
እመ ብርሃን ከእናትና ከአባቷ ጋር ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት፣ ከተወዳጁ ልጅዋ ጋር ፴፫ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመት፣ በድምሩ ፷፬ ዓመት በዚህ በኃላፊው ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓመተ ምሕረት በክብር ዐርፋለች፡፡
ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን በዓል ልናከብር ይገባልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትን ሠርታልናለች፡፡ “አስተርዮ ማርያም” በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ የሚከበር በዓል በመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ማኅበረሰብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉን የምናከብረውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ በማዘከር ብቻ ሳይሆን አማላጅነቷና ተረዳኢነቷን በማሰብና ተስፋ በማድረግ ነው፡፡
ስለዚህም እመ ብዙኃን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዐሥራት ሀገሯን ኢትዮጵያን እንድታስባት፣ ለእኛም ለሕዝቦቿ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን ታሰጠን እንዲሁም ለነፍሳችን ድኅነትን ትለምልን ዘንድ ዕረፍቷን መዘከር ይገባል፡፡
የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!!
#ማህበረ_ጳውሎስ https://t.me/Stpoulos
በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡
የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ ፷፬ ዓመታትን ከኖረች በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባስገነዘባት መሠረት በክብር ዐርፋለች፡፡ የዚህን ዓለም መከራና ሥቃይ ለሰዎች ድኅነት የተቀበለችው ክብርት እናታችን በሥጋ ብትሞትም እንደ ልጇ ደግሞ በትንሣኤዋ ተነሥታለች፤ ይህም የሆነው በተቀደሰች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ነው፡፡
እመ ብርሃን ከእናትና ከአባቷ ጋር ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት፣ ከተወዳጁ ልጅዋ ጋር ፴፫ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመት፣ በድምሩ ፷፬ ዓመት በዚህ በኃላፊው ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓመተ ምሕረት በክብር ዐርፋለች፡፡
ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን በዓል ልናከብር ይገባልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትን ሠርታልናለች፡፡ “አስተርዮ ማርያም” በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ የሚከበር በዓል በመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ማኅበረሰብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉን የምናከብረውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ በማዘከር ብቻ ሳይሆን አማላጅነቷና ተረዳኢነቷን በማሰብና ተስፋ በማድረግ ነው፡፡
ስለዚህም እመ ብዙኃን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዐሥራት ሀገሯን ኢትዮጵያን እንድታስባት፣ ለእኛም ለሕዝቦቿ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን ታሰጠን እንዲሁም ለነፍሳችን ድኅነትን ትለምልን ዘንድ ዕረፍቷን መዘከር ይገባል፡፡
የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!!
#ማህበረ_ጳውሎስ https://t.me/Stpoulos
👍6😁1
የተከበራችሁ ወንድሞችና እህቶች እንደምን አላችሁ? የካቲት 23/2017 ዓ.ም በዕለተ እሁድ ከቀኑ 8:30 አዳጎ ፀደይ ባንክ ላይ ካለው አዳራሽ ለብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ የጽዋ መርሐ ግብር እንድትገኙ ተጠርታችኋል እያንዳንዳችሁ ቢያንስ ሁለት ሁለት ሰዎችን በመጋበዝ ክርስቲያናዊ አደራችሁን እንድትወጡ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን።
🙏6
ተወዳጆች በእግዚአብሔር ሰላም እንደምን አላችሁ? ነገ ማለትም የካቲት 29 በ እለተ ቅዳሜ የዕብራውያን ጥናት ምዕራፍ አንድ የቤት ስራ የምንወያይ ስለሆነ 10:45 በኪዳነ ምህረት ትምህርት ቤት እድትገኙ:: በተቻለ መጠን ላለመዘግየት ሞክሩ!!
👍5
ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ መጋቢት 7.jpg
2.6 MB
ይህንን ፎቶ አውረዳችሁ My Story በማድረግ ቅስቀሳው ላይ እንድትሳተፉ በእግዚአብሔር ስም አደራ ችላ እንዳትሉ።
👍13❤2
ይቅርታ ለእናተ ቴክስት ከላኩኝ በኋላ ያልተመቸ ሁኔታ ሰለተፈጠረ ጉባኤያችን ዛሬ አይኖርም ። ነገ የቅዱስ ጳውሎስ ዝክር እንገናኝ። በሰላም ዋሉ። አደራ ላልሰሙት መልእኩትን አድርሱልኝ
👍7
ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ
ወደ ራማ ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና አረቋቴ ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም ሲሆን
የጉዞው መነሻ መጋቢት 19 አርብ ከቀኑ 8:00
የጉዞው መመለሻ መጋቢት 21 እሁድ
የትኬቱ ዋጋ 1000 ብር
ትኬቱ የሚገኝበት ቦታ አዳጎ ሳምራዊት ጫማ መሸጫ +251913920421
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ 👉 0921047323
ወደ ራማ ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና አረቋቴ ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም ሲሆን
የጉዞው መነሻ መጋቢት 19 አርብ ከቀኑ 8:00
የጉዞው መመለሻ መጋቢት 21 እሁድ
የትኬቱ ዋጋ 1000 ብር
ትኬቱ የሚገኝበት ቦታ አዳጎ ሳምራዊት ጫማ መሸጫ +251913920421
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ 👉 0921047323
የኤፌሶን መልእክት ከሳምንቱ ንባባችን ላይ ከምዕራፍ 1 እስከ 3 የመመዘኛ ፈተና ነገ 10:50 በአዳጎ ቤተ ክህነት ሕንጻ ላይ ይኖረናል። የነገ ሰው ይበለን
👍5😁1
ዛሬ ኮርሳችን እንደተጠበቀ ነው። አዳጎ ቤተ ክህነት ሕንጻ ላይ 8፡30 ይጀመራል። እንዳትቀሩ በእግዚአብሔር ፍቅር ጋብዘናችኋል። “እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ አሁን በየቦታቸው ንስሐ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል”
ሐዋርያት 17፥30
ሐዋርያት 17፥30
❤3
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣 ጋይስ ብቻዬን ከምስቅ ብዬ ነው ለምን እናተስ ይቀርባችኋል። 🤣
🤣19😁2👍1
Picsart_25-04-09_14-20-02-655.jpg
2.7 MB
ይህንን ፎቶ አውረዳችሁ My Story በማድረግ ቅስቀሳው ላይ እንድትሳተፉ በእግዚአብሔር ስም አደራ ችላ እንዳትሉ።
👍9
ጥያቄው
የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት በተጻፉበት ዓመተ ምሕረት ቅደም ተከተል መሠረት አንደኛው የተጻፈው መልእክት እስከ አምስተኛው መልእክት ከተጻፋበት ዓመተ ምሕረት ጋር በቅደም ተከተል ዘርዝራችሁ አስቀምጡ ?
መልሱን በዚሁ ላይ 👇 አስቀምጡልኝ መልካም እድል
የቅዱስ ጳውሎስ መልእክታት በተጻፉበት ዓመተ ምሕረት ቅደም ተከተል መሠረት አንደኛው የተጻፈው መልእክት እስከ አምስተኛው መልእክት ከተጻፋበት ዓመተ ምሕረት ጋር በቅደም ተከተል ዘርዝራችሁ አስቀምጡ ?
መልሱን በዚሁ ላይ 👇 አስቀምጡልኝ መልካም እድል
👍13
ለሴቶች
ሴቶች በክርስቶስ መዐዛ ምዑዛት ይሁኑ እንጂ በቆዳ ቅባትና በሽቱ አይደለም፡፡ እውነትን ከመስማት የበለጡ ጆሮዎች ጌጣጌጥ የላቸውምና ለሴቶች ለምድርዊ ጌጣጌጦች ጆሮችውን #አይበሱ፡፡ እውነትን ለመስማት የተበሱ ጆሮዎች ቅዱስ ነገርን መለኮታዊ ቃልን ያደምጣሉና
ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ
ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።
ቅዱስ ጴጥሮስ 1ኛ 3:3-4
ሴቶች በክርስቶስ መዐዛ ምዑዛት ይሁኑ እንጂ በቆዳ ቅባትና በሽቱ አይደለም፡፡ እውነትን ከመስማት የበለጡ ጆሮዎች ጌጣጌጥ የላቸውምና ለሴቶች ለምድርዊ ጌጣጌጦች ጆሮችውን #አይበሱ፡፡ እውነትን ለመስማት የተበሱ ጆሮዎች ቅዱስ ነገርን መለኮታዊ ቃልን ያደምጣሉና
ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ
ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።
ቅዱስ ጴጥሮስ 1ኛ 3:3-4
👍9🙏6
IMG_20250612_091437_454.jpg
2.9 MB
ይህንን ፎቶ አውረዳችሁ My Story በማድረግ ቅስቀሳው ላይ እንድትሳተፉ በእግዚአብሔር ስም አደራ ችላ እንዳትሉ።
👍5
ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ሰሜን ሸዋ ገዳማትና አድባራት
በማኅበረ ጳውሎስ በአይነቱ ልዩ የሆነ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ተዘጋጅቷል። የጉዟችን መነሻ ነሐሴ 18 / 2017 ዓመተ ምሕረት ወልድያ ከተማ ሲሆን በዛው ዕለት ወደ ጻድቃኔ ማርያም 400 ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ ማደሪያውን በገዳሙ ያደርጋል። በጠዋት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በመነሳት በጻድቃኔ ማርያም ዙሪያ ላይ የሚገኙትን የበረከት ቦታዎች ምስካበ ቅዱሳን መድኃኒዓለም እና አጃና ሚካኤል በመሳለም የሁለተኛ ቀኑን ማደሪያ ወደ ሚሆነው ወደ ዘብር ገብርኤል ጉዞውን ይቀጥላል።
በዘብር ገብርኤል አዳሩን ካሳለፈ በኋላ በዚህ ታላቅ ገዳም ዙሪያ የሚገኙትን የበረከት ቦታዎች ሰቅላየ ማርያም እና አርባራ መድኃኒዓለም በመሳለም ጉዞውን ወደ ደብረ ብርሃን በማድረግ ኩክየለሽ ማርያም ቀራኒዎ መድኃኒዓለም ዋሻ ቤተ ክርስቲያን እና ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት በመሳለም የሦስተኛ ቀን አዳሩን ደብረ ብርሃን ያደርጋል።
ከደብረ ብርሃን በጠዋት በመነሳ ሁለት ቀን ወደ ምንቆይባት ስዉሯ ማርያም በማድረግ ታላቅ ተአምር ወደሚፈጸምባት ወደዚች የተቀደሰች ቦታ ጉዞውን ያቀናል። በስዉሯ ማርያም ካደርን በኋላ ፀበል ተጸብለን ከስዉሯ ማርያም ወደ እጨጌ ዮሐንስ የተወሰነ የእግር ጉዞ በማድረግ ይህንን የበረከት ቦታ ተሳልመን ወደ ስዉሯ ማርያም ተመልሰን አዳረችንን በዛው እናደርጋለን።
በማለዳ በመነሳት የቀኑ የጉዞ እቅዳችን ውስጥ ወደ ተካተተችው ሰገነት ማርያምን በመሳለም ዕለቱን ለማደሪያ ወደ አሰብነው የተቀደሰ ወደ ሆነው አቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም እናደርጋለን። እረፋዱን በአቡነ ዜና ማርቆስ ጸሎት እና ጉብኝታችንን እንደጨረስን የጉዟችን መዳረሻ ወደሆነው ታላቁ ገዳም ወደ ደብረ ሊባኖስ ጉዟችንን እናደርጋለን። የምንደርስበትን ሰዓት ታሳቢ በማድረግ ወደ አቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም በመሄድ ከተሳለምን በኋላ ነሐሴ 24 በታላቅ ድምቀት ወደ ሚከበረው የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ንግሥ በደብረ ሊባኖስ ለማክበር ከአቡነ ሀብተ ማርያም ወደ ገዳሙ እንመለሳለን። በዓሉን ካከበርን በኋላ ወደ ከተማችን ወልድያ እንመለሳለን።
የጉዞ መነሻ ቀን ነሐሴ 18
የጉዞ መመለሻ ቀን ነሐሴ 25
የአንድ ሰው ጉዞ ትኬት 6000
የተለያዩ ዝማሬ ትምህርት ሥልጠናና መሰረታዊ መንፈሳዊ የውይይትና የምክክር መርሐ ግብሮች የተካተተበት ሲሆን ቲኬቱ ከሰኔ 22/2017 ከማክሰኛ ጀምሮ መሸጥ የተጀመረ ሲሆን እስከ ነሐሴ 5/2017 ድረስ የቲኬት ሽያጩ ይጠናቀቃል!!! ከአሁኑ ቀድማችሁ ቦታ እንድትይዙ በእግዚአብሔር ፍቅር እናሳስባችኋለን
ለበለጠ መረጃ
[Mobile] 091 392 0421
[Mobile] 092 104 7323
በማኅበረ ጳውሎስ በአይነቱ ልዩ የሆነ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ተዘጋጅቷል። የጉዟችን መነሻ ነሐሴ 18 / 2017 ዓመተ ምሕረት ወልድያ ከተማ ሲሆን በዛው ዕለት ወደ ጻድቃኔ ማርያም 400 ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ ማደሪያውን በገዳሙ ያደርጋል። በጠዋት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በመነሳት በጻድቃኔ ማርያም ዙሪያ ላይ የሚገኙትን የበረከት ቦታዎች ምስካበ ቅዱሳን መድኃኒዓለም እና አጃና ሚካኤል በመሳለም የሁለተኛ ቀኑን ማደሪያ ወደ ሚሆነው ወደ ዘብር ገብርኤል ጉዞውን ይቀጥላል።
በዘብር ገብርኤል አዳሩን ካሳለፈ በኋላ በዚህ ታላቅ ገዳም ዙሪያ የሚገኙትን የበረከት ቦታዎች ሰቅላየ ማርያም እና አርባራ መድኃኒዓለም በመሳለም ጉዞውን ወደ ደብረ ብርሃን በማድረግ ኩክየለሽ ማርያም ቀራኒዎ መድኃኒዓለም ዋሻ ቤተ ክርስቲያን እና ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት በመሳለም የሦስተኛ ቀን አዳሩን ደብረ ብርሃን ያደርጋል።
ከደብረ ብርሃን በጠዋት በመነሳ ሁለት ቀን ወደ ምንቆይባት ስዉሯ ማርያም በማድረግ ታላቅ ተአምር ወደሚፈጸምባት ወደዚች የተቀደሰች ቦታ ጉዞውን ያቀናል። በስዉሯ ማርያም ካደርን በኋላ ፀበል ተጸብለን ከስዉሯ ማርያም ወደ እጨጌ ዮሐንስ የተወሰነ የእግር ጉዞ በማድረግ ይህንን የበረከት ቦታ ተሳልመን ወደ ስዉሯ ማርያም ተመልሰን አዳረችንን በዛው እናደርጋለን።
በማለዳ በመነሳት የቀኑ የጉዞ እቅዳችን ውስጥ ወደ ተካተተችው ሰገነት ማርያምን በመሳለም ዕለቱን ለማደሪያ ወደ አሰብነው የተቀደሰ ወደ ሆነው አቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም እናደርጋለን። እረፋዱን በአቡነ ዜና ማርቆስ ጸሎት እና ጉብኝታችንን እንደጨረስን የጉዟችን መዳረሻ ወደሆነው ታላቁ ገዳም ወደ ደብረ ሊባኖስ ጉዟችንን እናደርጋለን። የምንደርስበትን ሰዓት ታሳቢ በማድረግ ወደ አቡነ ሀብተ ማርያም ገዳም በመሄድ ከተሳለምን በኋላ ነሐሴ 24 በታላቅ ድምቀት ወደ ሚከበረው የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን ንግሥ በደብረ ሊባኖስ ለማክበር ከአቡነ ሀብተ ማርያም ወደ ገዳሙ እንመለሳለን። በዓሉን ካከበርን በኋላ ወደ ከተማችን ወልድያ እንመለሳለን።
የጉዞ መነሻ ቀን ነሐሴ 18
የጉዞ መመለሻ ቀን ነሐሴ 25
የአንድ ሰው ጉዞ ትኬት 6000
የተለያዩ ዝማሬ ትምህርት ሥልጠናና መሰረታዊ መንፈሳዊ የውይይትና የምክክር መርሐ ግብሮች የተካተተበት ሲሆን ቲኬቱ ከሰኔ 22/2017 ከማክሰኛ ጀምሮ መሸጥ የተጀመረ ሲሆን እስከ ነሐሴ 5/2017 ድረስ የቲኬት ሽያጩ ይጠናቀቃል!!! ከአሁኑ ቀድማችሁ ቦታ እንድትይዙ በእግዚአብሔር ፍቅር እናሳስባችኋለን
ለበለጠ መረጃ
[Mobile] 091 392 0421
[Mobile] 092 104 7323
❤8
