ኤፌሶን ከምዕራፍ 1-3 ማብራሪያ.pdf
258.9 KB
📢 የትምህርት ምዘና ማስታወቂያ
እግዚአብሔር ረድቶን የኤፌሶን እና የቆላስይስ መጻሕፍት ጥናታችንን በሰላም አጠናቅቀናል። አሁን ደግሞ ካጠናነው ትምህርት ምን ያህል ግንዛቤ እንዳገኘን የምንመዝንበት የፈተና ወቅት ላይ እንገኛለን።
ስለ መጀመሪያው ምዘና ዝርዝር መረጃ፦
የፈተናው ይዘት፦ የኤፌሶን መልእክት ማብራሪያ (ከምዕራፍ 1 እስከ 3)
የጥናት ምንጭ፦ በቴሌግራም ቻናላችን t.me/Stpoulos ላይ የሚገኘው የፒዲኤፍ (PDF) ሰነድ።
ጠቅላላ ነጥብ፦ 35%
የጥያቄዎች አይነትና ስርጭት፦
1)
2)
3)
4)
ማሳሰቢያ፦ የፈተናውን ቀን በቅርቡ የምናሳውቅ በመሆኑ ሰነዱን በጥልቀት በማንበብ በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ጠንክራችሁ አንብቡ መልካም የጥናት ጊዜ!
እግዚአብሔር ረድቶን የኤፌሶን እና የቆላስይስ መጻሕፍት ጥናታችንን በሰላም አጠናቅቀናል። አሁን ደግሞ ካጠናነው ትምህርት ምን ያህል ግንዛቤ እንዳገኘን የምንመዝንበት የፈተና ወቅት ላይ እንገኛለን።
ስለ መጀመሪያው ምዘና ዝርዝር መረጃ፦
የፈተናው ይዘት፦ የኤፌሶን መልእክት ማብራሪያ (ከምዕራፍ 1 እስከ 3)
የጥናት ምንጭ፦ በቴሌግራም ቻናላችን t.me/Stpoulos ላይ የሚገኘው የፒዲኤፍ (PDF) ሰነድ።
ጠቅላላ ነጥብ፦ 35%
የጥያቄዎች አይነትና ስርጭት፦
1)
ምርጫ (10 ጥያቄዎች)፦ እያንዳንዳቸው 1 ነጥብ (10%)2)
እውነት ወይም ሐሰት (10 ጥያቄዎች)፦ እያንዳንዳቸው 1 ነጥብ (10%)3)
ባዶ ቦታ መሙላት (5 ጥያቄዎች)፦ እያንዳንዳቸው 2 ነጥብ (10%)4)
ማብራሪያ (2 ጥያቄዎች)፦ እያንዳንዳቸው 2.5 ነጥብ (5%)ማሳሰቢያ፦ የፈተናውን ቀን በቅርቡ የምናሳውቅ በመሆኑ ሰነዱን በጥልቀት በማንበብ በቂ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ጠንክራችሁ አንብቡ መልካም የጥናት ጊዜ!
❤11
ይችን ሳምንት እግዚአብሔር በሰላም በብርታት በጾም በጸሎት እና በስግደት አስፈጽሞ በሰላም ለብርሃነ ትንሣኤው ያድርሰን። አሜን
🙏18❤5
"በሰሙነ ሕማማት ማማተብ አይቻልም" የሚለው ወሬ ፍጹም ስህተት ነው። አንዳንድ ሰዎች ባለማወቅ ቤተ ክርስቲያን ሲገቡም ሆነ ለግል ጸሎት ሲቆሙ ማማተብ ስህተት እንደሆነ ያስባሉ። ነገር ግን መስቀሉን ከግል ክርስቲያናዊ ሕይወታችሁ ልትለዩት አይገባም። መስቀልን በማማተብ የግል ጸሎት መጀመር በሰሙነ ሕማማት የሚሻር ነገር አይደለም። እናስተውል
🙏13❤3
Audio
ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም
ተነስቷል በዚህ የለም
ተነስቷል በዚህ የለም
መድኃኔዓለም
ሞት የማይችለው የበረታ
ኃያል ነው የማይረታ
ማህተሙን የፈታ
የትንሳኤው ጌታ
ተነስቷል በዚህ የለም
ተነስቷል በዚህ የለም
መድኃኔዓለም
ሞት የማይችለው የበረታ
ኃያል ነው የማይረታ
ማህተሙን የፈታ
የትንሳኤው ጌታ
❤13
እመቤታችን የተወለደችበት መታሰቢያ ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ ከሞቀው ቤታችን ወጥተን ድንኳን በመጣል ወደ ውጭ እንወጣለን የሚያሳዝነው ነገር ግን ድንኳኖቻችን በዝማሬ መድመቅ ሲገባቸው እኛ ግን የልደቷን ባለቤት በማይመጥን መልኩ የዘፈን ዳንኪራ ቦታ እናደርጋቸዋለን። አካባቢያችሁን ቃኝታችሁ እስቲ ንገሩኝ ተወዳጆች ተሳስቻለሁ ?
በየመንደሩ በዚህ የተነሳ ድኅነት የሚገኝባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እና ክብሯ ይጎድፋል። በዓላቶቻችን ሁሉ የጌታን ክብር የመግለጥ አባቶቻችን እስከ ሙሉ መንፈሳዊ ሞገሳቸው ቢሰጡንም እኛ ግን የኃጢአት እና የዓለማዊነት ፍላጎታችን መፈጸሚያ የርኩሰት ሜዳ እያደረግናቸው መሆኑ ሲታይ ያሳዝናል።
በየመንደሩ በዚህ የተነሳ ድኅነት የሚገኝባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እና ክብሯ ይጎድፋል። በዓላቶቻችን ሁሉ የጌታን ክብር የመግለጥ አባቶቻችን እስከ ሙሉ መንፈሳዊ ሞገሳቸው ቢሰጡንም እኛ ግን የኃጢአት እና የዓለማዊነት ፍላጎታችን መፈጸሚያ የርኩሰት ሜዳ እያደረግናቸው መሆኑ ሲታይ ያሳዝናል።
👍7❤5🤔1
⚽️ አርሴናል ዋንጫ እንዲያገኝ ብጸልይ ኃጢአት ነውን?
ይህ ጥያቄ በተለይ በወጣቱ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ ዘንድ በተደጋጋሚ የሚነሳ ለአንዳንዶች ቀላል ወይም አስቂኝ ሊመስል የሚችል ነገር ግን በጥልቀት ስንመረምረው የእምነት ሕይወታችንን ሥር የሚነካ ትልቅ አጀንዳ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በግልጽ መወያየታችንና ትክክለኛውን መንፈሳዊ ምላሽ መፈለጋችን የሚጠቅመን በዘመናዊው ዓለም መዝናኛዎችና ስሜቶች ተገፍተን ሳናውቀው ከመንፈሳዊው መስመር እንዳንወጣ በዕለት ተዕለት ምርጫዎቻችን ውስጥም የእግዚአብሔርን ስፍራ በትክክል እንድንረዳ ስለምንማርበት ነው።
ስለምንወደው ክለብ መጨነቅ ማሸነፉን መመኘትና ከልብ መውደድ በራሱ ኃጢአት ባይሆንም ትኩረት የመሳትና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች የማዘበራረቅ ምልክት መሆኑን ግን መካድ አይገባንም። ከዚህም ባለፈ እንደ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ወደ ጸሎት ስንመጣ ነገሩን በሚገባ ልናስተውለው ይገባል።
በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር የምናደርገው ሰማያዊና መንፈሳዊ ውይይት በመሆኑ የምንጸልየው ለነፍሳችን ድኅነት ለኃጢአታችን ሥርየት ለዓለም ሰላም ነው። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል "አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል" (ማቴ. 6፥33) እንዳለን፣ የሰማዩን አምላክ ለምድራዊ፣ ጊዜያዊና መዝናኛ ለሆነ ጨዋታ ውጤት ብለን በጸሎት በፊቱ ስንቆም የጸሎትን ከፍ ያለ ክብርና ሰማያዊ ዓላማ ማሳነስ ይሆንብናል።
በሌላ በኩል ደግሞ ጨዋታው በችሎታ በስልጠናና በዕድል ላይ የተመሰረተ ምድራዊ ውድድር ከመሆኑ የተነሳ የአርሴናል ደጋፊዎች ስንጸልይ የማንችስተር ሲቲ ወይም የሌላ ክለብ ደጋፊ የሆኑ ኦርቶዶክሳውያን ወንድሞቻችንም የነሱ ክለብ እንዲያሸንፍ መጸለያቸው አይቀሬ ነው። እግዚአብሔር የሁላችንም አባት በመሆኑ በአንዱ ደስታ የሌላውን ማዘን ስለማይመርጥ የእግዚአብሔርን ጣልቃ ገብነት ለእንዲህ ዓይነቱ ውድድር መመኘት ክብሩን መጋፋት ሰለሆነ ለክቡርነቱ አይስማማም።
ከሁሉ በላይ ግን ልንጠነቀቅበት የሚገባው ትልቁ መንፈሳዊ አደጋ የእግር ኳስ ፍቅራችን ከፈጣሪ ፍቅር በልጦ ወደ ጣዖት አምልኮ እንዳይቀየር ነው። ክለባችን ሲሸነፍ የምናዝነውንና የምናለቅሰውን ያህል ለኃጢአታችን የማናልቅስ ከሆነ ለጨዋታው የምንሰጠው ትኩረትና ጉልበት ከቅዳሴና ከጸሎት ጊዜያችን በላይ ከበለጠ እንዲሁም የእግር ኳስ ተጫዋቾችን ከቅዱሳን በላይ የምናከብር ከሆነ ጨዋታው በሕይወታችን ላይ ጣዖት እየሆነ መምጣቱን ያሳያል።
ስለዚህ ወንድሜ ሆይ! አርሴናልን መውደድህ ጨዋታ መመልከትህና እንዲያሸንፍ መመኘትህ በራሱ ኃጢአት ባይሆንም በጸሎትህ ጊዜ ለእግር ኳስ ዋንጫ ከመጨነቅ ይልቅ ለሀገርህ ሰላም ለቤተሰብህ ጤና ለነፍስህ ድኅነት እና ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚያስገባህን ዘላለማዊ የጽድቅ ዋንጫ እንድታገኝ ብትጸልይ ይበልጥ ክርስቲያናዊና ኦርቶዶክሳዊ ይሆናል። እግዚአብሔር በምድራዊው መዝናኛችን ውስጥ መንፈሳዊ ማንነታችንን የምንጠብቅበትን ማስተዋል ይስጠን! አሜን
አቤል ተፈራ በላይ
https://t.me/Stpoulos
ይህ ጥያቄ በተለይ በወጣቱ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ ዘንድ በተደጋጋሚ የሚነሳ ለአንዳንዶች ቀላል ወይም አስቂኝ ሊመስል የሚችል ነገር ግን በጥልቀት ስንመረምረው የእምነት ሕይወታችንን ሥር የሚነካ ትልቅ አጀንዳ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ በግልጽ መወያየታችንና ትክክለኛውን መንፈሳዊ ምላሽ መፈለጋችን የሚጠቅመን በዘመናዊው ዓለም መዝናኛዎችና ስሜቶች ተገፍተን ሳናውቀው ከመንፈሳዊው መስመር እንዳንወጣ በዕለት ተዕለት ምርጫዎቻችን ውስጥም የእግዚአብሔርን ስፍራ በትክክል እንድንረዳ ስለምንማርበት ነው።
ስለምንወደው ክለብ መጨነቅ ማሸነፉን መመኘትና ከልብ መውደድ በራሱ ኃጢአት ባይሆንም ትኩረት የመሳትና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች የማዘበራረቅ ምልክት መሆኑን ግን መካድ አይገባንም። ከዚህም ባለፈ እንደ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ወደ ጸሎት ስንመጣ ነገሩን በሚገባ ልናስተውለው ይገባል።
በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር የምናደርገው ሰማያዊና መንፈሳዊ ውይይት በመሆኑ የምንጸልየው ለነፍሳችን ድኅነት ለኃጢአታችን ሥርየት ለዓለም ሰላም ነው። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል "አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል" (ማቴ. 6፥33) እንዳለን፣ የሰማዩን አምላክ ለምድራዊ፣ ጊዜያዊና መዝናኛ ለሆነ ጨዋታ ውጤት ብለን በጸሎት በፊቱ ስንቆም የጸሎትን ከፍ ያለ ክብርና ሰማያዊ ዓላማ ማሳነስ ይሆንብናል።
በሌላ በኩል ደግሞ ጨዋታው በችሎታ በስልጠናና በዕድል ላይ የተመሰረተ ምድራዊ ውድድር ከመሆኑ የተነሳ የአርሴናል ደጋፊዎች ስንጸልይ የማንችስተር ሲቲ ወይም የሌላ ክለብ ደጋፊ የሆኑ ኦርቶዶክሳውያን ወንድሞቻችንም የነሱ ክለብ እንዲያሸንፍ መጸለያቸው አይቀሬ ነው። እግዚአብሔር የሁላችንም አባት በመሆኑ በአንዱ ደስታ የሌላውን ማዘን ስለማይመርጥ የእግዚአብሔርን ጣልቃ ገብነት ለእንዲህ ዓይነቱ ውድድር መመኘት ክብሩን መጋፋት ሰለሆነ ለክቡርነቱ አይስማማም።
ከሁሉ በላይ ግን ልንጠነቀቅበት የሚገባው ትልቁ መንፈሳዊ አደጋ የእግር ኳስ ፍቅራችን ከፈጣሪ ፍቅር በልጦ ወደ ጣዖት አምልኮ እንዳይቀየር ነው። ክለባችን ሲሸነፍ የምናዝነውንና የምናለቅሰውን ያህል ለኃጢአታችን የማናልቅስ ከሆነ ለጨዋታው የምንሰጠው ትኩረትና ጉልበት ከቅዳሴና ከጸሎት ጊዜያችን በላይ ከበለጠ እንዲሁም የእግር ኳስ ተጫዋቾችን ከቅዱሳን በላይ የምናከብር ከሆነ ጨዋታው በሕይወታችን ላይ ጣዖት እየሆነ መምጣቱን ያሳያል።
ስለዚህ ወንድሜ ሆይ! አርሴናልን መውደድህ ጨዋታ መመልከትህና እንዲያሸንፍ መመኘትህ በራሱ ኃጢአት ባይሆንም በጸሎትህ ጊዜ ለእግር ኳስ ዋንጫ ከመጨነቅ ይልቅ ለሀገርህ ሰላም ለቤተሰብህ ጤና ለነፍስህ ድኅነት እና ወደ መንግሥተ ሰማያት የሚያስገባህን ዘላለማዊ የጽድቅ ዋንጫ እንድታገኝ ብትጸልይ ይበልጥ ክርስቲያናዊና ኦርቶዶክሳዊ ይሆናል። እግዚአብሔር በምድራዊው መዝናኛችን ውስጥ መንፈሳዊ ማንነታችንን የምንጠብቅበትን ማስተዋል ይስጠን! አሜን
አቤል ተፈራ በላይ
https://t.me/Stpoulos
❤13🙏2
የእመቤታችን_መገለጥ_ከደብረ_ምጥማቅ_እስከ_ዘይቱን.pdf
2.3 MB
ውድ ኦርቶዶክሳዊያን እንኳን ለእመቤታችን የመገለጥ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ተገለጠች ሲባል ተረት ለሚመስለው ለዚህ ዓለም ሕዝብ ሕያው ማስረጃ ነው።
ፎቶ ማስቀረት በሚችልበት በዚህ ዘመን ከ60,000 ሺህ ህዝብ እየታየች የተገለጠችበት ሁኔታ የሚያሳይ ይህ PDF በአንድ ወንድማችን የተዘጋጀ ድንቅ ማስረጃ ነው ተጠቀሙበት።
ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ ተገለጠች ሲባል ተረት ለሚመስለው ለዚህ ዓለም ሕዝብ ሕያው ማስረጃ ነው።
ፎቶ ማስቀረት በሚችልበት በዚህ ዘመን ከ60,000 ሺህ ህዝብ እየታየች የተገለጠችበት ሁኔታ የሚያሳይ ይህ PDF በአንድ ወንድማችን የተዘጋጀ ድንቅ ማስረጃ ነው ተጠቀሙበት።
👍5
📢 ታላቅ የበረከት ጥሪ ለወልድያ ኦርቶዶክሳውያን በሙሉ!
“የእግዚአብሔር ቃል እንዲሮጥና እንዲከበር...” (2ኛ ተሰ. 3፡1)
የማኅበራችን ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ የክረምት ኮርስ ምዝገባ መጀመሩን በማስመልከት ኮርሱን ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ተደራሽ ለማድረግ እና የተለያዩ መንፈሳዊ ሐሳቦችን ትምህርቶችንና መረጃዎችን ለማጋራት አዲስ የቲክቶክ አካውንት ከፍተናል።
ይህ የወንድሞችና የእህቶች ስብስብ ይበልጥ እንዲሰፋና የክረምቱን ኮርስ ተማሪዎች ቁጥር ከፍ ለማድረግ የእናንተ የሁላችሁም ትብብርና ክርስቲያናዊ አደራ ይፈለጋል።
📌 ከእናንተ ምን ይጠበቃል?
1. አካውንቱን መከተል (Follow): ከታች ያለውን የቲክቶክ ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
2. ማጋራት (Share): ይህንን ማስታወቂያ ፎቶ/ስክሪንሾት በማድረግ (Screenshot) በየግል ማኅበራዊ ሚዲያዎ ላይ ለወልድያ ኦርቶዶክሳውያን እንዲደርስ ያድርጉ።
3. ግብዣ (Invite): ለጓደኞቻችሁ ለቤተሰቦቻችሁና ለወዳጆቻችሁ በማጋራት የክረምቱን ኮርስ እንዲማሩ ይጋብዙ።
🔗 የቲክቶክ አካውንታችን ሊንክ፦
👉 tiktok.com/@saintpoul21
👉 @saintpoul21
ኑ ይሄንን መንፈሳዊ ጥሪ ለሁሉም በማድረስ የበረከቱ ተሳታፊ እንሁን! የማኅበራችን ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ
“የእግዚአብሔር ቃል እንዲሮጥና እንዲከበር...” (2ኛ ተሰ. 3፡1)
የማኅበራችን ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ የክረምት ኮርስ ምዝገባ መጀመሩን በማስመልከት ኮርሱን ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ተደራሽ ለማድረግ እና የተለያዩ መንፈሳዊ ሐሳቦችን ትምህርቶችንና መረጃዎችን ለማጋራት አዲስ የቲክቶክ አካውንት ከፍተናል።
ይህ የወንድሞችና የእህቶች ስብስብ ይበልጥ እንዲሰፋና የክረምቱን ኮርስ ተማሪዎች ቁጥር ከፍ ለማድረግ የእናንተ የሁላችሁም ትብብርና ክርስቲያናዊ አደራ ይፈለጋል።
📌 ከእናንተ ምን ይጠበቃል?
1. አካውንቱን መከተል (Follow): ከታች ያለውን የቲክቶክ ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
2. ማጋራት (Share): ይህንን ማስታወቂያ ፎቶ/ስክሪንሾት በማድረግ (Screenshot) በየግል ማኅበራዊ ሚዲያዎ ላይ ለወልድያ ኦርቶዶክሳውያን እንዲደርስ ያድርጉ።
3. ግብዣ (Invite): ለጓደኞቻችሁ ለቤተሰቦቻችሁና ለወዳጆቻችሁ በማጋራት የክረምቱን ኮርስ እንዲማሩ ይጋብዙ።
🔗 የቲክቶክ አካውንታችን ሊንክ፦
👉 tiktok.com/@saintpoul21
👉 @saintpoul21
ኑ ይሄንን መንፈሳዊ ጥሪ ለሁሉም በማድረስ የበረከቱ ተሳታፊ እንሁን! የማኅበራችን ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ
❤1👍1
የምስገባ አማራጮች
ሀ) በአካል ለመመዝገብ ለሚፈልጉ
አዳጎ -> ማሚ ህንፃ ጌጤ ጫማ ቤት
ፒያሳ -> ፎቶ ግዕዝ
ጎንደር በር -> ቴድሮስ ኤሌክትሮኒክስ
ለ) በስልክ ለምትመሰገቡ ይሄንን ተጠቀሙ
0965106126 ሀብታሙ አገኘሁ
0929077309 ዳዊት ደርቤ
0921975099 ሙሉቀን አከለ
0992304006 ማህሌት አስራት
ሐ) በቴሌግራም ለምትመሰገቡ ይሄንን ተጠቀሙ
t.me/ha21a21
t.me/dev199207
t.me/Fidel19kal
t.me/Maki92
#ሳይሞላባችሁ #ተመዝገቡ
ሀ) በአካል ለመመዝገብ ለሚፈልጉ
አዳጎ -> ማሚ ህንፃ ጌጤ ጫማ ቤት
ፒያሳ -> ፎቶ ግዕዝ
ጎንደር በር -> ቴድሮስ ኤሌክትሮኒክስ
ለ) በስልክ ለምትመሰገቡ ይሄንን ተጠቀሙ
0965106126 ሀብታሙ አገኘሁ
0929077309 ዳዊት ደርቤ
0921975099 ሙሉቀን አከለ
0992304006 ማህሌት አስራት
ሐ) በቴሌግራም ለምትመሰገቡ ይሄንን ተጠቀሙ
t.me/ha21a21
t.me/dev199207
t.me/Fidel19kal
t.me/Maki92
#ሳይሞላባችሁ #ተመዝገቡ
❤6
20260526_095243 (2).jpg
5.7 MB
የማኅበራችን ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ የክረምት ኮርስ ምዝገባ መጀመሩን በማስመልከት ኮርሱን ለሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ተደራሽ ለማድረግ ይሄንን ፎቶ Story ሁላችሁም በቅስቀሳው እንድትሳለፉ በእግዚአብሔር ስም አደራ።
❤7
https://vt.tiktok.com/ZSCYp9H8X/
የማህበራችን መልእክትና አገልግሎት ለብዙሃን እንዲደርስ ይረዳን ዘንድ፤ ሁላችሁም የማህበሩን አካውንት ፎሎው (Follow)፣ ቪዲዮዎቹን ደግሞ ላይክ (Like) እና ሪፖስት (Repost) በማድረግ የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
የማህበራችን መልእክትና አገልግሎት ለብዙሃን እንዲደርስ ይረዳን ዘንድ፤ ሁላችሁም የማህበሩን አካውንት ፎሎው (Follow)፣ ቪዲዮዎቹን ደግሞ ላይክ (Like) እና ሪፖስት (Repost) በማድረግ የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
👍7
ነገረ ድኅነት 1ኛ ሳምንት ትምህርት .pdf
1009 KB
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የ"ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ" ማኅበር አባላትና የትምህርቱ ተካፋዮች በሙሉ፦ የእግዚአብሔር ሰላም ፍቅርና ጥበቃ በያላችሁበት ይብዛላችሁ፡፡ ማኅበራችን "ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ" በዚህ ዓመት የክረምት ወቅት ለወልድያ ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችና ምዕመናን ባዘጋጀው ልዩ የመንፈሳዊ ትምሀርት መርሐ-ግብር መሠረት የመጀመሪያው ሳምንት ትምህርታችን የነበረውን ጥልቅና መሠረታዊ የሆነውን "የነገረ ድኅነት" ትምህርት በሰፊው ተምረናል።
ይህ እጃችሁ ላይ የደረሰው ጽሑፍ (Handout) በክፍል ውስጥ የተማርነውን ይዘት በቤታችሁ ኾናችሁ በሰፊው እንድታነቡት እንድታጠኑትና ለሕይወታችሁ ስንቅ እንድታደርጉት ይበልጥ በሚያመች መልክተደራጅቶ የተዘጋጀ የመጀመሪያው ሳምንት የፒዲኤፍ (PDF) ሰነድ ነው።
በዚሁ መሠረት፣ በሚቀጥሉት ሳምንታት የምንማራቸውን ተከታታይ ትምሀርቶች በሙሉ እያዘጋጀን በማኅበራችን ይፋዊ የቴሌግራም ግሩፕ እና ቻናል ላይ የምንለቅ መሆኑን እንገልጻለን። እናንተም ይሀንን ሰነድ ከግሩፑ አውርዳችሁ (Download አድርጋችሁ) በስልካችሁ ላይ ዝም ብሎ እንዲቀመጥ ሳይሆን በጸሎት መንፈስ ኾናችሁ በደንብ እንድታነቡትና እንድታጠኑት በቅዱስ እግዚአብሔር ስም አደራ ማለት እወዳለሁ።
የቀደሙት አባቶቻችንና ቅዱሳን ሐዋርያት የተጋደሉለትን ደማቸውን ያፈሰሱለትንና የጻፉልንን እውነተኛውን የመዳን እውቀት (የነገረ ድኅነት ምስጢር) አውቀን በእምነት እንድንጸና እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ይደልውልን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
አቤል ተፈራ በላይ
ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም
ወልድያ ኢትዮጵያ
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የ"ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ" ማኅበር አባላትና የትምህርቱ ተካፋዮች በሙሉ፦ የእግዚአብሔር ሰላም ፍቅርና ጥበቃ በያላችሁበት ይብዛላችሁ፡፡ ማኅበራችን "ዝክረ ቅዱስ ጳውሎስ" በዚህ ዓመት የክረምት ወቅት ለወልድያ ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችና ምዕመናን ባዘጋጀው ልዩ የመንፈሳዊ ትምሀርት መርሐ-ግብር መሠረት የመጀመሪያው ሳምንት ትምህርታችን የነበረውን ጥልቅና መሠረታዊ የሆነውን "የነገረ ድኅነት" ትምህርት በሰፊው ተምረናል።
ይህ እጃችሁ ላይ የደረሰው ጽሑፍ (Handout) በክፍል ውስጥ የተማርነውን ይዘት በቤታችሁ ኾናችሁ በሰፊው እንድታነቡት እንድታጠኑትና ለሕይወታችሁ ስንቅ እንድታደርጉት ይበልጥ በሚያመች መልክተደራጅቶ የተዘጋጀ የመጀመሪያው ሳምንት የፒዲኤፍ (PDF) ሰነድ ነው።
በዚሁ መሠረት፣ በሚቀጥሉት ሳምንታት የምንማራቸውን ተከታታይ ትምሀርቶች በሙሉ እያዘጋጀን በማኅበራችን ይፋዊ የቴሌግራም ግሩፕ እና ቻናል ላይ የምንለቅ መሆኑን እንገልጻለን። እናንተም ይሀንን ሰነድ ከግሩፑ አውርዳችሁ (Download አድርጋችሁ) በስልካችሁ ላይ ዝም ብሎ እንዲቀመጥ ሳይሆን በጸሎት መንፈስ ኾናችሁ በደንብ እንድታነቡትና እንድታጠኑት በቅዱስ እግዚአብሔር ስም አደራ ማለት እወዳለሁ።
የቀደሙት አባቶቻችንና ቅዱሳን ሐዋርያት የተጋደሉለትን ደማቸውን ያፈሰሱለትንና የጻፉልንን እውነተኛውን የመዳን እውቀት (የነገረ ድኅነት ምስጢር) አውቀን በእምነት እንድንጸና እግዚአብሔር አምላክ ማስተዋሉን ይደልውልን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
አቤል ተፈራ በላይ
ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ.ም
ወልድያ ኢትዮጵያ
🙏8❤1