ኢትዮጵያዊ ወጎች #Ethiopian
1.4K subscribers
314 photos
3 videos
18 files
50 links
Download Telegram
በኢትዮጵያ በመጪው ሰኔ ወር አጋማሽ የፀሃይ ግርዶሽ ይከሰታል!

በኢትዮጵያ በመጪው ሰኔ ወር አጋማሽ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ እንደሚከሰት የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

ግርዶሹ ከምዕራብ እስከ ሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ የሚታይ ሲሆን ክስተቱም ወለጋ፣ ከፊል ጎጃምና ጎንደር፣ በወሎ በተለይ ላሊበላ አካባቢ ቀኑ #የሚጨልም ይሆናል ተብሏል።

በተቀረው የአገሪቱ ክፍል ደግሞ በዕለቱ በከፊል ጨለማ ሊሆን እንደሚችል የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሰሎሞን በላይ ተናግረዋል።

ግርዶሹ ስድስት ሰዓታት የሚፈጅ ሲሆን እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር የፊታችን ሰኔ 14 እሁድ ቀን ከጠዋቱ 12፡45 እስከ ቀኑ 6፡33 የሚቆይ ይሆናል።

#ENA
©TIKVAH-ETH
#DrLiaTadesse

በኢትዮጵያ አሁን ያለው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት የአኗኗር ሁኔታችንን እንድንቀይር ያስገዳል ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገልፀዋል።

ዶ/ር ሊያ ዛሬ በሱጡት መግለጫ እንዳሉት ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የጉዞ ታሪክ የሌላቸው #በርካታ ግለሰቦች የኮሮና ቫይረስ እየተገኘባቸው ነው።

ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ ሳይኖራቸው ቫይረሱ የሚገኝባቸውም ሰዎች ቁጥር ጨምሯል ሲሉ ተናግረዋል።

የኮቪድ-19 ስርጭት ጎረቤት አገራት ጋር በማይዋሰኑ አካባቢዎችም ጭምር እየሰፋ መጥቷል ያሉት ዶክተር ሊያ 'ይህም አደጋው ወደ እያንዳንዳችን ቤት እየመጣ መሆኑን ያሳያል' ብለዋል።

'የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ሲከሰት በቀላሉ እየጨመረ የሚሄድ የስርጭት ባህሪ እንዳለው ጠቁመው ፤ ስርጭቱ ምን ያህል ይጨምራል የሚለው ጥያቄ ግን በእያንዳንዳችን ጥንቃቄ ይወሰናል ብለዋል።

በኢትዮጵያ ያለፈው ሳምንት የቫይረሱ ስርጭት ሁኔታ ይህን በግልጽ ያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም ከመደናገጥ ወጥተን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በሚጠይቀው ልክ የአኗኗር ባህሪያችንን መቀየር አለብን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

'መራራቅ ፣ መታጠብ ፣ መቆየት ፣ መሸፈን' የሚሉ አራቱ የኮቪድ-19 “መ” ህጎችን መተግበር ደግሞ ከእያንዳንዱ ዜጋ የሚጠበቅ የጥንቃቄ አማራጭ መሆኑ ዶ/ር ሊያ ገልፀዋል - #ENA