ኢትዮጵያዊ ወጎች #Ethiopian
1.4K subscribers
314 photos
3 videos
18 files
50 links
Download Telegram
ቀስ የምትችለው የይለፍ ወረቀት ይዘህ ስትገኝ ነው፡፡ ደረጃ ስድስት... የይለፍ ወረቀቱ፣ ከመንግስት የሚሰጥ ሲሆን፤ ስምህን፣ ከየት እንደመጣህ፣ ወደየት እንደምትሄድና ጉዳይህ ምን እንደሆነ ይገልጻል፡፡ ቅርብ ለቅርብ የተሰደሩ የፖሊስ ኬላዎች አሁንም አሁንም ይፈትሹሃል፡፡ ያለ ፍቃድ ከተያዝክ 206ዩሮ ( 8000ብር አካባቢ) ትቀጣለህ፡፡ ያለፍቃድ የተያዝክ ህመምተኛ ከሆንህ ደሞ፣ ነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተከስሰህ ከ1-12 አመት የእስር ግዜ ይጠብቅሃል፡፡
ዛሬ ሀገሬ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሳለች፡፡
.
ወሬኣችንን ስንደመድም
ሀገራት በቸልተኝነት በግዴለሽነት ዜጎቻቸውን ከመጠበቅ ሲፎርሹ ማየት ያማል፡፡ የሚችሉትን ሁሉ ያላረጉ እንደሚቀጡበት ግልጽ ነው፡፡
ይህንን እያነበብክ ከሆነ ተለመነኝ፣ ለጤናህ ስትል የተነገረህን የጥንቃቄ እርምጃ ሁሉ ውሰድ፡፡ ስለጉዳዩ አላወራህም፣ ረስተኸዋል ማለት እሱ ረስቶሃል፣ በራሱ ግዜ ብን ብሎ ይጠፋል ማለት አይደለም፡፡ ማመን ያለብኝ አንድ ነገር፣ የጣልያን መንግስት-መንግስቴ- ይህንን በሽታ ለመቆጣጠር እጅግ የሚያስመሰግነው ስራ መስራቱን ነው፡፡ የተወሰዱት እርምጃዎች፣ ከልክ ያለፉና፣ ያልተመጣጠኑ ቢሆኑም፣ እጅግ አስፈላጊ ነበሩ፡፡ ስርጭቱን ለመቀነስ ያለው ብቸኛ መንገድ ይኸው ብቻ ነው፡፡ ቻይናን ጠቅሟታል፡፡ ለእኛም ይጠቅመናል ብለን እናስባለን፡፡ መጀመሪያ ወደ ማግለያ በገቡት የእኛም ክልሎች ላይ ውጤት እየተገኘ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በመቆሙ ምክንያት፣ መንግስት ድጎማ እያደረገ
ይገኛል፡፡ የቤት ተከራይ ዜጎቹን፣ ሱቃቸውን በኪራይ የያዙ ነጋዴዎችን ወጪ እየሸፈነ ይገኛል፡፡ ይሄንን በሌሎች ሀገራት ማስፈጸም ከባድ እና የማይታሰብ ሊመስል ይችላል፡፡ ሁኔታውን ከሀገሬ ድንበር አሳልፌ ሳየው ግን እጅግ እሰጋለሁ፡፡ ውስጥ እጅ የሚያልብ ድንጋጤ ይወርሰኛል፡፡ የማህበረሰባችንን አኗኗር ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ የሚቀይር መዓት መጣብን ይሆንን? እላለሁ፡፡ ይሄንን ብቻ ስማኝ
ባለህበት አካባቢ በበሽታው የተያዘ ሰው ከተገኘ፣ ቫይረሱ እየተስፋፋ ነው ማለት
ነው፡፡ አሁን የእኔ ሀገር ያለችበት ለመድረስ ሁለት ሳምንት ይበቃሃል፡፡ ዞሮ ዞሮ የእኛ እጣ እጣህ ነው፡፡
የምትችለውን ሁሉ ተጠንቀቅ፡፡
ከሁሉ በላይ ደግሞ እኔን አይነካኝም ብለህ አትበጥ፡፡ ከቻልህ ቤትህን ዘግተህ ተከርቸም፡፡

©ወግ ብቻ
#biniam teshome