Sadat_Text_Posts
10K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
👆🏻ማን የማን ቅጥረኛ ነው?
ኢኽዋኖች ከኢሀዲግ እስከ ግንቦት 7?
አቡበክር አሕመድ፣ ሀሰን ታጁ …..
የኢትዮጵያ ሙስሊም ሐቁን ለመገንዘብ ማዳመጥ ያለበት እውነታ፡፡
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
አልሐምዱሊላህ ወንድሜ ኢብኑ ሙነወር በአላህ ፈቃድ እና ምህረት ከደረሰበት አደጋጋ በማገገም ላይ ነው፡፡ በአላህ ፍቃድ ወደ አዲስ አበባ መኖሪያ ቤቱ በቀጣይ ቀናቶች ውስጥ ይመለሳል፡፡ አላህ ሆይ! በሁለት አገር አፊያ አድርገን፡፡ ወንድሜን ከከባድ አደጋ ስላተረፍከውም አመሰግንሃለሁ፡፡ ብቸኛው ተለማኝ ህያው ጌታችን ሆይ! መቼም ማናችንም ከሞት አናመልጥምና፣ ስንኖርም ስንሞትም በተውሒድ መንገድ ላይ አኑረህ ግደለን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አልሐምዱሊላህ አላህ ወንድማችን ኢብኑ ሙነወርን ከልጆቹ ጋር በሰላም አገናኝቶታል፣ ለቤቱም አብቅቶታል፡፡ የሱን ደህንነት ካላችሁበት ሆናችሁ ስትጠይቁና ዱዓ ላደረጋችሁለት ወንድም እና እህቶች በጠቅላላ አላህ አትርፎት ለቤቱ በመብቃቱ አላህ ምንዳችሁን እጥፍ ድርብ አድርጎ ይክፈላችሁ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የሐበሻ ሙስሊሞች ሆይ! ማንም ከማንም ዘር አይበልጥም፡፡
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
የሐበሻ ሙስሊሞች ሆይ! አላህን እንፍራ ጥምቡን ዘረኝነት ከላያችን ላይ ጨርሰን አራግፈን እንጣል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሰሃባዎቻቸው ላይ ከባድ በደል፣ ስቃይ እና እንግልት ሲደርስባቸው “ሂዱ ወደ ሀበሻ” ነበር ያሉት፡፡ እኛ ሙስሊሞች ነን፡፡ የሀበሻ ሙስሊሞች የሚለው ከበቂ በላይ መታወቂያችን ነው፡፡ ዘራችንን ከኢስላም አስቀድመን እርስ በርስ እየተናናቅን መከፋፈሉ ለከባድ አደጋ ነው የሚዳርገን፡፡
አንድ ሰው በእስልምናው እንጂ በዘሩ ጀነት አይገባም፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ስራው ወደ ኋላ ያስቀረውን ሰው ዘሩ (ወደፊት) አያስቀድመውም” ብለዋል፡፡
አንድ ሰው ጀነት ለመግባት ብቸኛው መንገዱ
- ተውሒድን አሳምሮ መያዙ ከሺርክ እና ከባለቤቶቹ ሙሉ ለሙሉ መፅዳቱ፣
- የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን ሱና አጥብቆ መያዙ ቢድኣ የተባለን በጠቅላላ መራቁ፣
- የሰሃባዎችን አረዳድ መከተሉ የጥመት መንገዶችን ሁሉ መራቁ፣
- የአላህንና የመልክተኛውን ትእዛዝ መፈፀሙ እነሱንም አለማመፁ ……
- …..
እንጂ ዘሩ አይደለም፡፡
ዘር ለመተዋወቅ ብቻ እንጅ ለሌላ አይደለም፡፡ እውነቱን ለፈለጉ ሰዎች አላህ እንዲህ ይላል
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አላህ በግልፅ እውነታውን ነግሮናል፡፡
ዘረኞች፣ ዘራቸውን ከኢስላም የሚያስቀድሙ ጥምብ አንሳዎች ናቸው፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ዘረኝነት ጥምብ ናት፡፡ ተዋት፡፡” እያሉን የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትእዛዝ ትተው እሳቸው የከለከሉትን የሚያነሱ ጥምብ አንሳዎች ናቸው፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “….ተዋት” ብለው ጥንቡን ዘረኝነት እንድንተው ሲነግሩን አይ አልተውም ብሎ ከእስልምና ዘሩን አስቀድሞ ሙስሊም የሆነ ከእሱ ዘር ያልሆነው ላይ አደጋ ሊያደርስ፣ ንብረቱን ሊቀማ የሚያስብ ሰው ምንኛ ከሰረ፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሁለት ሙስሊሞች ሰይፍ አይማዘዙም ገዳይም ተገዳይም የእሳት ናቸው” ሲሉ
ሰሃባዎች “ገዳይስ ገድሎ ነው” ተገዳይስ ሲሉ ጠየቁ
የአላህ መልክተኛም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “እሱም ንያ ነበረው” ሲሉ እነዚህ ሰዎች የሚሰሩትን ስራ የእሳት መንገድ እንደሆነ ገለፁ፡፡
ኢስላም ለሁሉም ነገር ዝርዝር የሆነ መተዳደሪያ ያለው፣ ለሁሉም ዘመን፣ ለሁሉም ቦታ፣ ለሁሉም ትውልድ ሙሉና ከበቂ በላይ የሆነ አላህ የሚቀበለው ብቸኛ ሃይማኖት ነው፡፡
ውቡ ኢስላም እርስ በእርስ መጋደላችንን. መበዳደላችንን አጥብቆ ኮንኖታል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አንድ ሙስሊም ለአንድ ሙስሊም ወንድሙ ነው፡፡ አይበድለው….” ብለዋል፡፡ ታድያ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አይበድለው” እያሉ ዘሩ ስላልሆነ ብቻ ሌሎች ሙስሊሞችን ሊገድል የተነሳው ምን ሊባል ነው?
አላህ ይድረስልን፡፡ ከዚህ ቆሻሻ ተግባርም ይጠብቀን፡፡
የሀበሻ ሙስሊሞች ሆይ! ሙስሊም የሆነ ሰው እኛ ዘንድ እንደራሳችን አድርገን ልንወደው ይገባል፡፡ ሙስሊም ደሙም፣ ገንዘቡም፣ ክብሩም የተጠበቀ ነው፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡
የሀበሻ ሙስሊሞች ሆይ! አላህን እንፍራ ዘረኝነትን ከላያችን ላይ እናራግፍ፡፡ ማንም ማንንም በዘሩ አይበልጥም፡፡ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘሮች የሆኑት አረቦች እንኳን አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ አጀሞችን (ከአረብ ውጭ) ያሉትን አይበልጡም፡፡ ለዚህም የሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አረብ በአጀም (ከአረብ ውጭ ባሉ ሰዎች) ላይ ብልጫ የለውም” ብለዋል፡፡
አላህ እንደነገረን
إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ
አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ዘረኝነት ከሺርክና ቢድኣ ቀጥሎ ነቀርሳ ሆኖ እየወጋን ይገኛል፡፡ ይህን መልእክት በየቋንቋችሁ እየተረጎማችሁ ለሁሉም በማድረስ ተባበሩኝ፡፡
አላህ ሆይ! ዘረኝነትን ከመካከላችን አስወግድልም፡፡ ኢስላምን ከዘራቸው የሚያስቀድሙ ምርጥ ትውልዶች አድርገን፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም ዘረኝነትን አጥፍተው እርስ በእርስ ሲጋደሉ የነበሩትን ሰሃባዎች በሱና አንድ ባደረጉት የአላህ ውድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸውና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በኢስላም ሸይኽም ይሁን ነብይ ሞተ ተብሎ የሙት አመት አይከበርለትም፡፡ ማንም ይስራው ማን፣ ለማንም ይሰራ ለማን
“የሙት አመት”
የሚባል ነገር የለም፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የኢስላም አስተማሪዎች፣ የመስጂድ ኸጢቦች፣ ሽማግሌዎች ሃላፍትናችሁን ተወጡ፡፡
“የኛሰው”፣ “ነመኬኛ”፣ “የባድ ወልድ” …. ብለን የምንጠራው ማንን ነው?
አንድን ሰው የእኛ ዘርም ባይሆን ሙስሊም እስከሆነ ድረስ አማራው “የኛሰው”፣ ኦሮሞው “ነመኬኛ”፣ ስልጤው “የባድ ወልድ” …… ብለን መጥራት እስካልቻልን ድረስ አደጋ ውስጥ ነን፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሙስሊም የሙስሊም ወንድሙ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ዛሬ ሰይጣን እና ሰራዊቶቹ ባጠመዱላቸው ወጥመድ ውስጥ ገብተው ለዘራቸው ሲሉ ላኢላሃኢለላህ ብለው ሲያበቁ እርስ በእርስ የሚጋደሉ፣ በመጥፎ የሚፈላለጉ፣ ሰው ሲሞት ሁሉ የእድር እቃ አንሰጥም የሚሉ አውሬዎች አሉ፡፡ አላህ ሁላችንንም ልብ ይስጠን፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሁለት ሙስሊሞች ሰይፍ አይማዘዙም ሁለትሙ የእሳት ናቸው” ብለው ነግረውን ሲያበቁ፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይህን ጥንብ ዘረኝነት “ተዉቱ” እያሉ፣ እሳቸው የከለከሉት ዘረኝነት አንተውም ብለው ታላቋን የምስክረት ቃል “ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፡፡ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን እንዲሁ እመሰክራለሁ” ያሉ ሰዎች እርስ በእርስ ሲጋደሉ እንደማየት አስለቃሽና ልብ የሚያደማ ነገር የለም፡፡
ከማንም በላይ ሃላፍትና ያለባቸው የሃይማኖቱ አስተማሪዎች፣ ኢማሞች፣ ዱአቶች፣ ሽማግሌዎች፣ ኢስላማዊ ቻናሎችና ሬድዬኖች ናቸው፡፡ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ኡመተል ኢስላም እርስ በእርስ እንዲህ እየተገዳደለ አላህ ካዘነላቸው በጣም ጥቂቶች ውጭ አብዛኛዎቹ አዋቂ ተብየዎች ዝምታን መርጠዋል፡፡ አላህን ብትፈሩ አይሻልም ወይ? አላህ አያያዙ የበረታ ነው፡፡ ኡለማዎች ሐቅን ማብራራትና አለመደበቅ ነው ያለባቸው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
ኡመቱ እርስ በእርስ ሲባላ እያዩ ተው አለማለት ምን የሚሉት ነው?
ዘረኝነት ውስጥ ገብታችሁ የተነሱ እሳቶች ላይ ቢንዚል የምታርከፈክፉ ሰዎች የጥፋታችሁን ልክ ላትገነዘቡት ትችላላችሁ፡፡ ግን ልብ በሉ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አንድ አማኝ ያለ አግባብ ከሚሞት ካእባ ቢወገድ ይሻላል” ሁሉ ብለዋል፡፡ መቼ ይሆን የምንመከረው? አላህና መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል እየተባልን ልባችን ከድንጋይ በላይ ደርቆ የነሱን ቃል አልቀበልም ብለን ስሜታችንን ጋልበን መጨረሻን ምን ይሆናል ብለን እንገምታለን?
አረ አላህን እንፍራ፡፡ ከባድ የሆነ አዘቅት ውስጥ እንዳንገባ፡፡ ተወደደም ተጠላም ማንኛውም አይነት ችግር ይበልጥ ጎጂነቱ ለሙስሊሙ ነው፡፡ አእምሮ ያለው ልብ ይበል፡፡
አላህ ሆይ! ከሺርክ፣ ቢድኣ፣ ዘረኝነት የፀዳ እውነተኛ አንድነት ስጠን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ስለ ሰሞኑን ከባድ ብርድ እስልምና ምን ይላል፡፡
የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ
ኢስላም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት ነው፡፡ እንደሚታወቀው በሀይለኛ ሙቀት እና በሀይለኛ ብርድ ሰው ተቸግሯል፡፡ ይህም ከመሆኑ ጋር ለአላህ ካጠፋነው ጥፋቶች ንሰሀ ከመግባት ይልቅ በየዜና አውታሩ “የአለም በረዶ ስለቀለጠ ነው፣ ዛፎች በመቆረጣቸው ነው፣ ኦዞን በመሳሳቱ ነው…..” እና የመሳሰሉትን ምክንያቶች ናቸው እየተባለ ይለፈፋል፡፡
እስቲ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምን እንደሚሉ እንይ
አቡ ሁረይራ (ረድየላሁ አንሁ) ባስተላለፉት፣ ኡማሙ አል-ቡኻሪ በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ላይ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
“ጀሀነም (እሳት) ወደ ጌታዋ ስሞታ አቀረበች፡፡ ከፊሌ ከፊሌን በላው አለች፡፡ አላህ ሁለት ጊዜ እስትንፋስን ፈቀደላት፡፡ አንደኛው በቀዝቃዜ ወራት ሌላኛው ጊዜ በሙቀት ወራት፡፡ በሙቀት ጊዜ የምታገኙት ከባድ ሙቀት እና በቅዝቃዜ ጊዜ የምታገኙት ከባድ ውርጭ (ቅዝቃዜ፣ ቀቅ) (ናቸው)፡፡”
حَدَّثَنَا أَبُو الْيَمَانِ، أَخْبَرَنَا شُعَيْبٌ، عَنِ الزُّهْرِيِّ، قَالَ حَدَّثَنِي أَبُو سَلَمَةَ بْنُ عَبْدِ الرَّحْمَنِ، أَنَّهُ سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ اشْتَكَتِ النَّارُ إِلَى رَبِّهَا، فَقَالَتْ رَبِّ أَكَلَ بَعْضِي بَعْضًا، فَأَذِنَ لَهَا بِنَفَسَيْنِ نَفَسٍ فِي الشِّتَاءِ وَنَفَسٍ فِي الصَّيْفِ، فَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ فِي الْحَرِّ، وَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ مِنَ الزَّمْهَرِيرِ ‏"‌‏.‏
ልብ እንበል ከባዱም ሙቀት እና ከባዱም ብርድ የአዋቂዎች ሁሉ አዋቂ፣ የአላህን ፈሪዎች ሁሉ ፈሪ፣ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ እንደነገሩን የጀሃነም እሳት የምትተነፍሰው ሁለት ትንፋሽ ምክንያት ነው፡፡
ሌላው መገንዘብ ያለብን ነገር እስልምና ሙሉ መሆኑን ለማንኛውም አለም ላይ ላለ ክስተት በል እንዲያውም ለሚቀጥለው አለም ጉዳዩች፣ የሚቀጥለው አለም ላይ ምን እንደሚከሰት በዝርዝር እና በጥቅል የተናገር ዉድ፣ ልዩ፣ የማይበረዝ፣ የማይሰረዝ፣ የማይደለዝ፣ ዘመን የማያልፍበት ሀይማኖት ነውና አጥብቀን እንያዘው፡፡ ይሀው ተመልከቱ አከም “Econmic Crisese” ኢኮኖሚክ ክራይስስ ብለው ሲያወሩ አላህ ጥንትም የወለድ መጨረሻው ይህ መሆኑን ነግሮን ነበር፡፡
ትዳር እንዲመሰረት እና ከዝሙት እንድንታቀብ ከጥንትም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት መክሮ ነበር፡፡ ግን ይህን አልሰማ ብለው አሁን አለም ላለችበት ከባባድ በሽታዎች ተዳርገዋል፡፡
በሁሉም የህይወት ዘርፍ ላይ የጥንት የጠዋቱ ኢስላም (ሰለፍያ) በሄደበት መንገድ መሄድ ብቻና ብቻ ነው ዋስትናው፡፡ ሁለት ሃቅ የለም፡፡ ሁሉም ሙስሊም ከጥመት ቡድኖች እርቆ ወደ ብቸኛዋ አማራጭ እና ሁለተኛ ወደሌላት ሃቅ ጎዳና፣ ሰለፉነ ሷሊሂን የተጓዙባት ጎዳና መመለስ ግድ ይለዋል፡፡ አለበለዚያ በሙስሊሙ አለም ላይ እንዳየነው አሁንም ከባድ ኪሳራ ይከሰታል፡፡
ታድያ ምን ይበጀን?
አማኞች ወደ ጌታቸው በንሰሃ ሊመለሱ፣ ያችን “ጭማሪ አለን?” ብላ የምትጠይቀውን ጀሀነም ከሷ ጌታችን እንዲጠብቀን እሱን ዘውትር መለመን ግድ ይለናል፡፡ የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ፡፡ አላህ እነዚህን ሁሉ ተዓምራት የሚያሳየን በሰጠን አእምሮ የሱን ጌትነት፣ በቸኛ ተመላኪነት አውቀን ወደሱ እንድንመለስ ነው፡፡
አላህ ሆይ! ሁሌ ወዳንተ በጸጸት ከሚመለሱት አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የት በደረሱ ነበር?
አላህ ካዘነላቸው ጥቂቶች ውጭ ስለ ግል ጉዳያቸው፣ ስለ ዘራቸው፣ ስለ መብታቸው ደም ስራቸው እስኪገተር ድረስ የሚቆጡ፣ የሚከራከሩ፣ የሚያብራሩ ሰዎችን ታያለህ፡፡ ነገር ግን ሺርክ (በአላህ ላይ ሲጋራ)፣ ቢድኣ (የነብዩ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ላይ ሲጨመር ሲቀነስ) እያ ዝም ሲሉ ትመለከታቸዋለህ፡፡ ለራሳቸው የተቆጡትን ቁጣ ሺርክና ቢድኣን ሲያዩ ያንን ቁጣ አታይባቸውም፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ ከዚህ የበለጠ ዝቅጠት ምን አለ? የአላህ መብት ሲነካ ሌሎች ጉዳዬች ላይ እንደሚያንዘረዝረን ቢያንዘፈዝፈን፣ ቢዘገንነን፣ ብንቆጣ የት በደረስን ነበር?
አላህ ሆይ! ያንተን መብት ከሚያከብሩና ከሚያስከብሩ ትውልዶች አድርገን፡፡ ውስጥ እላያችንንም አሳምርልን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህን መብቶች ያሟላን ጊዜ የእኛም መብቶች ይሟላሉ፡፡
የፈጣሪን መብት ሳናሟላ ፍጡራን መብቶቻችንን አያሟሉልንም፡፡
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
https://t.me/SadatTextPosts
ታላቁ በደል ለምን ያህል ዘመን?
በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እጅግ በጣም ሩህሩህ፡፡ የአላህ ሰላትና ሰላም በመልክተኞች ሁሉ መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸውና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
የዛሬው አርእስት ልብ የሚያደማ ነው፡፡ አላህ መቼም ከናታችን ሆድ ስንወጣ ምንም የማናውቅ የነበርን ብንሆንም፣ መስሚያን፣ መመልከቻን ልቦናንን አድርጎልናል፡፡ የመልክተኞች ሁሉ ኢማም የሆኑትን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ላከልን፡፡ ቁርኣንን አወረደልን፡፡ ምስጋና ሁሉ ጥራት ለተገባው አላህ ይሁን፡፡ መቼም ይህን ሁሉ አድርጎልን ሀቁን ከባጢሉ ታላቁን በደል ከታላቁ በደል በታች ካሉት ለይተን ማወቂያ አእምሮን ሰጥቶናል፡፡
እኛ ሀበሾች ከማንም በፊት የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጥርት ያለች ጥሪ እንደደረሰን ይታወቃል፡፡ ታድያ የበደሎች ሁሉ በደል ምን እንደሆነ ኢስላም ነግሮናል አልነገረንም? ነግሮናል እንጂ
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ قَالَ لُقْمَٰنُ لِٱبْنِهِۦ وَهُوَ يَعِظُهُۥ يَٰبُنَىَّ لَا تُشْرِكْ بِٱللَّهِ ۖ إِنَّ ٱلشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ
ሉቅማንም ለልጁ እርሱ የሚገሥጸው ሲኾን «ልጄ ሆይ! በአላህ (ጣዖትን) አታጋራ፡፡ ማጋራት ታላቅ በደል ነውና» ያለውን (አስታውስ)፡፡
አላህ ይሀው በግልፅ እንደነገረን ታላቁ በደል በእሱ ላይ ማንንም ይሁን ምንንም ማጋራት ነው፡፡ ሀገራችንንም ላይ ይሁን አለም ላይ በአላህ ላይ ሺርክን በመፈፀም ታላቁ በደል ይሰራል፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
ታላቁ በደል (ሺርክ) ሁለት አገር ያጨልማል፡፡ የታላቁ በደል ተቃራኒ አላህን በብቸኝነት ማምለክ ነው፡፡ አላህን በብቸኝነት ማምለክ (ተውሒድ) የፍትሆች ሁሉ ፍትህ ነው፡፡ ሁለት ሀገር ለስኬት ያበቃል፡፡
የአላህን መብት እናሟላ የእኛም መብቶች እንዲሟሉልን፡፡ በሁለት ሀገር ስኬታማ እንድንሆን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሐቅን መደበቅ ከባድ አደጋ ነው፡፡
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
https://t.me/SadatTextPosts
እውር አሞራ ቀላቢውን አላህ የካዱ፡፡
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ አሳዛኙ የአገራችን እውነታ፡፡
ጥርት ያለችው የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጥሪ ከማንም በፊት ለሀበሾች ደርሶ ሲያበቃ፣ እዚሁ አገር ላይ ብቸኛውን ቀላቢ ትተው ፍጡር የሆኑትን ተቀላቢዎች እንደሚከተለው ከአላህ ውጭ ቀላቢ ናቸው ሲሉ የአላህን ስልጣን አሳልፈው ይሰጣሉ
1) አባድር ፆም አያሳድር፣
2) አላሁመ ሰሊ አላ ሙሐመዲ፣ መገን ነቢ የሁሉ ቀላቢ፣
3) ላክም አንቱ ነው ያ ነቢ፣ ለመላውም ኸልቅ ቀላቢ
አላህ ግን በግልፅ ቀላቢነቱን እንዲህ እያለ ሱረቱል ሁድ ላይ ነግሮን ሲያበቃ
۞ وَمَا مِن دَآبَّةٍ فِى ٱلْأَرْضِ إِلَّا عَلَى ٱللَّهِ رِزْقُهَا وَيَعْلَمُ مُسْتَقَرَّهَا وَمُسْتَوْدَعَهَا ۚ كُلٌّ فِى كِتَٰبٍ مُّبِينٍ
በምድርም ላይ ምንም ተንቀሳቃሽ የለችም ምግቧ በአላህ ላይ ያለ ቢኾን እንጂ፡፡ ማረፊያዋንም መርጊያዋንም ያውቃል፡፡ ሁሉም ግልጽ በሆነው መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አላህን እንፍራ፡፡ ኡለማዎችና ዱአቶች አደራችሁን ተወጡ፡፡ ህዝቡን ከምንም በፊት እምነቱን እንዲያስተካክል አስተምሩት፡፡ ይህም ከአላህ የተሰጣችሁት አደራ ነውና፡፡ የአላህን አደራ መብላት ከምንም በላይ ከባድ ወንጀል ነው፡፡ አብዛኛው አስታዋሽ ካጣ የአላህ ቁጣ ሲመጣ አደጋው ሁላችንንም ያገኘናል፡፡ አላህ በፍፁም የማይምረው ሺርክን ነው፡፡ ከሺርክ በታች ያለውን ለሻው ሰው ይምራል፡፡ ያ ከሺርክ በታች ወንጀሎችን የሰራ ሰው አላህ ከቀጣው እንኳን የጥፋቱን ያህል ተቀጥቶ ወደ ጀነት ይመለሳል፡፡ ነገር ግን በሺርክ ላይ የሞተ ሰው ዘላለሙን ከእሳት አይወጣም፡፡ ታድያ ይህን የተገነዘቡ ኡለማዎችና ዱአቶች ለምን ከምንም አርእስት በላይ ይህንን ጉዳይ አበክረው አይመክሩም?
አሳዛኙ እውነታ አላህ ካዘነላቸው ጥቂቶች ውጭ አብዛኛው ይህን አይነት ከባድ ሺርክ የሚሰራባቸው አገሮች ላይ ሌላ አርእስት በማውራት ቢዚ የሆኑ ሰዎችን መመልከት ነው፡፡
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ ለቀላቢው ያልታመነ ለፍጡራን አይታመንም፡፡ ቀላቢውን ያላወቀ ከእንስሳት በታች ነው፡፡
አላህ የተውሒድን ብርሃን አውቀው አጥብቀው ከሚይዙትና ወደሱም ከሚጣሩት ያድርገን፡፡ የሺርክን ጨለማ አውቀው ከሚጠነቀቁት፣ ከሚያስጠነቅቁትና ከሚርቁት ያድርገን፡፡ አሚን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የቱን እንምረጥ የእውነቱን ወይንስ የውሸቱን አንድነት?
አላህ የልብ መመልከቻችንን ያብራልን፡፡
አላህ ሐቁን ይምራን፡፡ የውስጥ መመልከቻ ሲታወር የላይኛው አይን ቢመለከትም አያይም፡፡
እስቲ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አላህ በሰጠን ንጹህ አእምሮ እንየው እንዴት ነው እውነተኛው ብቸኛ አንድ መንገድ አንድ ያደርጋል፣ እሷም ላይ እንሰብሰብ ማለት “ሙቡታተን” በተገላቢጦሹ ደግሞ አላህ ያወገዘውን የሰይጣን መንገዶች መከተል እና ልዩነት “አንድነት” ተብሎ የሚጠራው?
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! እስቲ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ነፍሳችንን እንጠይቅ
1) ሃቅ ስንት ናት?
መልሱም አንድ እና አንድ ብቻ ናት፡፡ ለዚህም ማስረጃው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አብደላህ ኢብን መስኡድ ባስተላለፉት ሀዲስ “መሬት ላይ ቀጥተኛ መስመር አሰመሩ ይህም የአላህ ቀጥተኛው መንገድ ነው አሉ”
“ከዛም በጎን እና በጎን ሌሎች መስመሮች አሰመሩ እነዚህም መንገዶች ናቸው እያንዳንዱ መንገድ ላይ የሰይጣን ተጣሪ አለበት” አሉ፡፡
እስቲ ሀቅ ፈላጊዎች ሆይ! ሰይጣን የሚጣራባቸው የጥመት መንገዶች ብዙ መሆናቸው እና ሃቅ ብቸኛ አንድ መንገድ መሆኗ በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አንደበት ተነገረን ወይንስ አልተነገረንም?
መልሱም ተነገረን ነው፡፡
2) የትኛው ነው የሃቅ መንገድ?
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቁጥር አንድ ላይ ባየነው ነጥብ መሰረት ሃቅ አንድ መሆኗን ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በመቀጠል እቺን ብቸኛ የሀቅ ጎዳና እናውቃት ዘንድ የቷ ናት?
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላሉ “የሁዳዎች 71 ቦታ ይከፈላሉ፣ ነሷራዎች 72 ቦታ ይከፈላሉ፣ ይህም ኡመት 73 ቦታ ይከፈላል ሁሉም የእሳት ናቸው አንዷ ስትቀር”
የአላህ መልክተኛ አሁንም የሀቅ መንገድ አንድ ብቻ መሆኗን ጠቀሱ
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አንዷ የሀቅ መንገድ የትኛዋናት ተብለው ሲጠየቁ
“እኔ እና ሰሃባዎቼ ዛሬ ያለንባት መንገድ ናት” አሉ፡፡
በሌላ ሀዲስ ደግሞ
“ከሰዎች ሁሉ በላጭ እኔ ያለሁባቸው (ሰሃባዎች)፣ ከዛም ቀጥሎ ያሉት (ታቢኢን)፣ ከዛም ከጥሎ ያሉት (አትባኡ ታቢኢን)”
ይህ ነው እንግዲህ ብቸኛው የሁለት አገር ደህንነት እና ሰላም ዋስትና፣ የሰለፍያ ጎዳና፣ ብቸኛው ሃቅ፣ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ኹለፋኡ ራሺዲን፣ ሰሃባዎች፣ ታቢኢዬች፣ አትባኡታቢኢን የሄዱበት መንገድ፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ግልጽ ሆነልን ሀቅ አንድ ብቻ መሆኗ?
ባረከላሁ ፊኩም፡፡ ሰይጣን የሚጣራባቸው የእሳት፣ የጥመት እና የጥፋት መንገዶች የትኛዎቹ ናቸው የሚለውን በሚቀጥለው ነጥብ እንመልከት፡፡
3) የትኛዎቹ ናቸውስ የትፋት መንገዶች?
ማንኛውም የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና የሰሃባዎቻቸው፣ የሰለፉነ ሷሊሂንን መንገድ ያልተከተለ እና የተቃረነ እዚህ የጥፋት እና የጥመት መንገድ ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ ተቃርኖ በእምነት ጉዳይም ይሁን በአካሄድ ብቸኛዋን የሃቅ መንገድ የተቃረን ሁሉ እዚህ ሰይጣን የሚጣራበት የጥፋት መንገድ ውስጥ ገብቷል፡፡
በአላህ ፍቃድ እዚህ ጋር የጥመት ቡድኖችን ስም እጠቅሳለሁ፡፡ ልክ የሀቋ ብቸኛ ሰለፊያ ጎዳናን እንደጠቀስኩት ሁሉ፡፡
- ቀደሪያ፣
- ኸዋሪጅ፣ ሀሩሪያ፣ ኡባዲያ፣
- ራፊዳ ሺኣ፣
- ሙእተዚላ፣
- ማትሩድያ፣
- ጀህሚያ፣
- አሽአሪያ፣
- ኩላቢያ፣
- ሱፊያ ቃዲርያ፣
- ሱፍያ ቲጃንያ፣
- ሱፍያ ነቅሸበንዲያ……፣
- ኢኽዋን፣ ቁጥቢያ፣ ሱሩሪያ፣ ተብሊግ፣ አህባሽ፣ …….. እና ሌሎችም
እዚህ የተዘረዘሩት ሁላ ብቸኛዋን የሃቅ ጎዳና ሰለፊያ የተቃረኑ ናቸው፡፡ መንገድ የሳቱ ቡድኖች ለመሆናቸው ይሄ ማስረጃ ነው፡፡
4) ከላይ ቁጥር 3 ላይ የተዘረዘሩት ስንት ናቸው?
እንደሚታወቀው ቁጥር ሶስት ላይ የተዘረዘሩት ከአንድ በላይ ናቸው፡፡ ከዛም አልፎ ከብቸኛው የሰለፎች ጎዳና የተቃረኑ የጥመት ጎዳናዎች ናቸው፡፡
5) የመጀመሪያ ነጥብ ላይ ሃቅ ስንት እንደሆነች ነበር ያየነው?
መልሱም አንድ ብቻ ናት፡፡
6) ታድያ ለምን የውሸት አንድነት አስፈለገ?
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ በዚህ ዘመን ሙስሊሙ በአንድ ሀቅ ላይ እንዳይሰባሰብ “ሁሉም ጀመኣ የራሱ ድክመት አለው”፣ “ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም” እና የመሳሰለውን እያሉ የሚበታትኑት እና ተለያይቶ “አንድ ነን” እያለ እንዲዋሽ የሚያደርጉት የጥመት ቡድን የሆኑት ኢኽዋነል ሙስሊሚን ፍልስፍናን ተከታዬች ናቸው፡፡
ለምሳሌ፡-
ሀሰን አል በና የተባለው የዚህ ጥመት ፖለቲካዊ ቡድን መስራች እንዲህ ይላል
اعلموا أنَّ أهل السنة والشيعة مسلمون تجمعهم كلمة لا إله إلاَّ الله وأنَّ محمداً رسول الله وهذا أصل العقيدة ,والسنة والشيعة فيه سواء وعلى التقاء ,أما الخلاف بينهما فهو في أمور من الممكن التقريب فيها بينهما
(ذكريات لا مذكرات)ط1- دار الاعتصام 1985 يقول الأستاذ عمر التلمساني ص249 و250
“እወቅ አህለሱና እና ሺአ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ ላኢላሃ ኢለላህ ሙሐመዱ ረሱሉላህ የምትለው ቃል አንድ ታደርጋቸዋለች፡፡ ይህችም የአቂዳ መሰረት ናት፡፡ ሱና እና ሺኣ በዚህ ጉዳይ አንድ ናቸው፣ እኩል (የሚገናኙ፣ የሚጣጣሙ) ናቸው፡፡ በመካከላቸው ያለው ልዩነት እማ ሁለቱንም ማቀራረብ የሚቻል ነው (እንደ ልዩነት አይቆጠርም፡፡ ብዙ የሚያስቆጣ አይደለም፡፡)”
እውነታው ግን ሀሰን አል በና እንዳለው ሳይሆን ከሺአ ራፊዳዎች ጋር አንድ መሆን በፍጹም አንችልም፡፡ ልዩነታችንም የእምነት እና የክህደት ጉዳይ ነው፡፡
ምክንያቱን እነሱ ማለት እምነታቸው እና ተግባራቸው እንደሚከተለው በክህደት የተጨማለቀ ነው
- 12ቱ ኢማም ብለው የሚያምኑባቸውን ‹‹ከነብያት በላይ ናቸው፡፡ ከነብያት ይበልጣሉ›› ይላሉ፡፡ ይህ አባባላቸው ክህደት ነው፡፡
- ከአላህ ውጭ ‹‹ያ ሁሴን፣ ያ አልይ፣ ያ ፋጢማ፣ ያ ዘይነብ………›› እያሉ ይጣራሉ፡፡ ይሄም ሽርክ ነው፡፡ ጥሪ የሚገባው ለአላህ ብቻ ነው፡፡
- “ቁርዐን ተቀንሷል፤ ሱረቱል ዊላያ የሚባል ሱራ አለ ያላሉ” ይህ የክህደት እምነት ነው ምክንያቱም አላህ “ቁርዐንን እኛ ነን ያወረድነው እኛው እንጠብቀዋለን” ስለሚል ነው፤
- ሀዲስንም አይቀበሉም ቡኻሪ፤ ሙስሊም፤ አህመድ የመሳሰሉትን፡፡ በሱና የሚክድ ካፊር ነው፡፡
- እንዲህ ብለው ነሺዳ ሲያነሽዱም ተሰምተዋል “አንተ ሁሴን ከአላህ በላይ ትልቅ ነህ” ይሄም ኩፍር ነው፡፡
- የሺዐ መሪ ከነበሩት አንዱ ሃያቶላ ኹመይኒ እንዲህ ይላል “አነዚህ ሙሽሪኮች መዲናን መውረርና እነዛን ሁለት ጣዖቶች (አቡበክር እና ኡመርን) ማስወገድ ፈለጉ” ተመልከት ሱንዬ ወንድሜ ሆይ! ኢኽዋኖች ለማን አሳልፈው እየሰጡህ እንደሆነ? አቡበክርና ኡመርን (ረድየላሁ አንሁማ) ጣኦት ብሎ የሚጠራ ሸይጧን፡፡
- ከሺዐዎች መሪ አንዱም ስለ ምዕመናን እናት አኢሻ እንዲህ አለ “አኢሻ በእርግጥ ካሃዲ(ካፊር) ናት” የአላህ እና የረጋሚዎች እርግማን ሁሉ በርሱ ላይ ይሁን፡፡ ይህም ኩፍር ነው፡፡
- ከሺዐዎች አንዱም ተጠየቀ “ሱንዩ አለም ሙስሊም ይባላል ወይ?” እሱም “አይባሉም፤ ምክንያቱም ሙስሊም የሆነ ሰው አቡበክርን እና ኡመርን አይወድም” በማለት መለሰ፡፡ የአላህ ቁጣ በሱ ላይ ይሁንና፡፡ አቡበክርና ኡመርን በመውደድ ወደ አላህ እንቃረባለን፡፡
- የኡመር ኢብነል ኸጣብን ገዳይ አቡ አላ አልመጁሲን የዲን ጀግና ነው ብለው አላህን ከዚህ የተረገመ ሰው ጋር እንዲቀሰቅሳቸው ዱዐ ያደርጋሉ፤