SOA COMMUNITY POLICE 2 CAMPUS
606 subscribers
784 photos
39 videos
81 files
34 links
ይህ ድህረ ገፅ የተለያዩ የትምህርት አይነቶች አጠቃሎ የያዘ ሲሆን የሚለቀቁት ጥያቄዎችም ሆኑ ማስታወሻዎች በቀላሉ ታገኛላችሁ። በ👉👉👉SOAPO2
Download Telegram
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በዓለም ዐቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት በፈረቃ ሲሰጥ የቆየው ትምህርት በ2014 የትምህርት ዘመን ወደ መደበኛው እንደሚመለስ አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ለ "አዲስ ማለዳ ጋዜጣ" ነው።

የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል እንዲረዳ በማሰብ በ2013 የትምህርት ዘመን ትምህርት በፈረቃ ሲሰጥ ነበር።

በተጨማሪ ተማሪዎች ሲማሩበት የነበረው የቀናት ቁጥር በሳምንት ወደ 3 ቀን ተቀንሶ ተማሪዎች በቀናት ፈረቃ ተምረው አሳልፈዋል።

ከሚቀጥለው ትምህርት ዘመን (2014 ዓ.ም) ጀምሮ የትምህርት ስርዓቱ ከዚህ ቀደም ወደ ነበረበት ማለትም ከሰኞ - አርብ የትምህርት ጊዜውን ለመመለስ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

Credit - Addis Maleda Newspaper

@tikvahethiopia