👉 ዐውደ ቀመር 532 ዘመን ነው፤ በዚኽ ዕለት፣ ወንጌላዊ፣ አበቅቴ እሊኽ 3ቱ ይገናኙበታል፤ ዕለቱ ሠሉስ፣ ወንጌላዊዉ ማቴዎስ ነው፤ ሠሉስ ማቴዎስ እንዲል አበቅቴው አልቦ ነው “ጥንቱ ለቀመር ዕለተ ሠሉስ ወንጌላዊ ማቴዎስ ወፍጻሜሁ ዕለተ ሰኑይ ወንጌላዊ ዮሐንስ” እንዲል፤ በዐውደ ፀሓይ ቦታ ዐውደ ማኅተም፤ በዐውደ ማኅተም ቦታ ዐውደ ፀሓይ የሚል ይገኛል፤ ከኹለቱ አንዱ ቢታጣ አንዱ ከቀመር ገብቶ ይቈጠራል፤ ቀመርን ለሦስቱ ስም በሰጡ ጊዜ ዐውደ ቀመር ዐቢይ ቀመር፤ ዐውደ ማኅተም ማዕከላዊ ቀመር፤ ዐውደ አበቅቴ ንዑስ ቀመር ይባላል፤ ዐቢይ ቀመር መደቡ 14 ቊጥሩ 532፣532፤ ማዕከላዊ ቀመር መደቡ 6 ቊጥሩ 76፣76፤ ንዑስ ቀመር መደቡ 3 ቊጥሩ 19፣19 ነው፡፡
👉 ከዚኽም ዓመተ አበቅቴን (ወንበር) ለማግኘት 7518 ዘመን በዐቢይ ቀመር ቢቀምሩ 532፤ 532 የተፈጸመለት 14 ዐቢይ ቀመር፤ 19፤ 19 የተፈጸመለት 3 ንዑስ ቀመር ኾኖ 13 ዓመት ይተርፋል።
👉 መላውንም በማእከላዊ ቀመርም ቢቀምሩ 76፤ 76 የተፈጸመለት 98 ማእከላዊ ቀመር 19፤ 19 የተፈጸመለት 3 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል፡፡
👉 በዐውደ ፀሓይም ቢቀምሩ 28፤ ኻያ ስምንት የተፈጸመለት 266 ዐውደ ፀሓይ፤ 19፤ 19 የተፈጸመለት 3 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል፡፡
👉 መላውንም በንዑስ ቀመር ቢቀምሩ 19፤ 19 የተፈጸመለት 395 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል፡፡
👉 7518ቱን ዘመን በቀመረ ዐረብም ቢቀምሩ 228፤ 228 የተፈጸመለት 32 ቀመረ ዐረብ፤ 19፤ 19 የተፈጸመለት 11 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል።
👉 ስመ አቅማር ብዙ ነው አይቶ መተው ነው፤ አሐደ አዕትት ለዘመን እንዲል ስለተጀመረ ተቈጠረ ስላልተፈጸመ ታተተ ብሎ ከ13ቱ አንዱን ቢያትቱ 12 ይተርፋል፤ 12 ዓመተ አበቅቴ ወጣ ገጠር ወንበር ይላል፡፡
👉 አበቅቴን ለማግኘት ከ12ቱ ዓመተ አበቅቴ 11፤ 11 ዕለት ቢነሡ 132 ይኾናል፤ ከ120ውን 30ውን በ4፤ ፴ ቢገድፉት 1 ይተርፋል፤ 12 አበቅቴ ወጣ በዘመነ ማርቆስ፡፡
👉 መጥቅዕንም ለማግኘት ከ12 ዓመተ አበቅቴ 19 ዕለት ቢነሡ 228 ይኾናል፤ 228ቱን በ7፤ ፴ ቢገድፉት 18 ይቀራል፤ 18 መጥቅዕ ወጣ በዘመነ ማርቆስ፤ 18 መጥቅዕና 12 አበቅቴ ፴ ይኾናሉ እንጂ ከ፴ አይወጡም ከ፴ አይወርዱም፤ “ዓዲ መጥቅዕ ወአበቅቴ ክልኤሆሙ እመ ይበዝኁ ወእመ ይውኅዱ ኢየዐርጉ እም፴ ወኢይወርዱ እም፴ ወባሕቱ ወትረ ይከውኑ ፴” እንዲል።
(ከዚኽ በኋላ አበቅቴ ከመጠነ ሠርቀ መዓልትና ከሚለው ዠምሮ…ኢየዐርግ ኢይወርድ ኹሉ እንደ ታሪኩ አስገባ)
❤ መጥቅዕ 18 መጥቅዕ ቢበዛ በመስከረም ይውላልና መስከረም ኀሙስ ይብታል፤ ኀሙስ እስከ ኀሙስ 8 / 15/ ዓርብ 16/ ቅዳሜ 17/ እሑድ 18 በዓለ መጥቅዕ መስከረም 18 እሑድ።
የእሑድ ተውሳክ 7/ 18 ና 7 = 25 ጥር 25 መባጃ ሐመር
በመስከረም ሳኒታ ጥር ዐርብ ይብታል፡፡ ዐርብ - ዐርብ 8/15/22/ ቅዳሜ 23/ እሑድ 24/ ሰኞ 25 ጥር 25 ነነዌ
♦ የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14፤ 14 + 25 = 39 ሠላሳ ቢገድፉ 9 ይተርፋል።
እሑድ እስከ እሑድ 8 ሰኞ 9
የካቲት 9 ዐቢይ ጾም
♦ የደብረ ዘይት ተውሳክ 11፤ 11 እና 25= 36 ሠላሳ ቢገድፉ 6 ይተርፋል መጋቢት ማግሰኞ ይብታል። ማግሰኞ 1/ ረቡዕ 2/ ኃሙስ 3/ ዓርብ 4/ ቅዳሜ 5/ እሑድ 6 መጋቢት 6 ደብረ ዘይት
♦ የሆሣዕና ተውሳክ 2፤ 2 እና 25 = 27፤ ማግሰኞ - ማግሰኞ 8/15/22/ ረቡዕ 23/ ኃሙስ 24/ ዓርብ 25/ ቅዳሜ 26 እሑድ 27 መጋቢት 27 ሆሣዕና።
♦ ከዚኽም በዓለ ፍሥሕን (የአይሁድ ፋሲካን) ይናገሯል፤ ፍሥሕን 4 ነገር ይጠብቃታል፤ ገቦ መጥቅዕ፤ ሰሙነ ሕማማት፤ 190 ዕለት፤ 14 ሌሊት፤ ፍሥሕ የዕለት ተውሳክ አትሻም በደረቅ መጥቅዕ ነው የምትወጣው መጥቅዑ 18 የፍሥሕ ተውሳክ 10= 28፤ መጋቢት 28 ፍሥሕ
በዓሉን አናከብረውም ስለምን እናወጣዋለን ቢሉ ሐዋርያት ፍሥሕን ከትንሣኤ ጋራ አንድ አድርጎ ያዋለ ካህን ቢኾን ከክህነቱ ይሻር፤ ምእመን ቢኾን ከምእመናን ይለይ ብለው አውግዘዋልና ስለዚኽ ለይተን እናወጣዋለን፡፡
♦ የስቅለት ተውሳክ 7፤ 7 እና 25 = 32፤ ሠላሳ ቢገድፉ 2 ይተርፋል። ሚያዝያ ኃሙስ ይብታል። ኀሙስ 1 ዐርብ 2
ሚያዝያ 2 ስቅለት
♦ የትንሣኤ ተውሳክ 9፤ 9 እና 25 =34፤ ሠላሳ ቢገድፉ 4 ይተርፋል። ኀሙስ 1 ዐርብ 2 ቅዳሜ 3 እሑድ 4 ሚያዝያ 4 ትንሣኤ
♦ የርክብ ተውሳክ 3፤ 3 እና 25 = 28፤ ኀሙስ - ኃሙስ 8/15/22/ ረቡዕ 28
ሚያዝያ 28 ረቡዕ
♦ የዕርገት ተውሳክ 18፤ 18 እና 25= 43፤ ሠላሳ ቢገድፉ 13
ግንቦት ቅዳሜ ይብታል። ቅዳሜ - ቅዳሜ 8 እሑድ 9 ሰኞ 10 ማግሰኞ 11 ረቡዕ 12 ኃሙስ 13 ግንቦት 13 ዕርገት
♦ የጰራቅሊጦስ ተውሳክ 28፤ 28 እና 25 = 53፤ ፴ውን ገድፎ 23 ይቀራል፤ ቅዳሜ - ቅዳሜ 8/15/22/ እሑድ 23
ግንቦት 23 ጰራቅሊጦስ
♦ የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ 29፤ 29 እና 25= 54፤ ፴ውን ገድፎ 24 ይቀራል፤ ቅዳሜ - ቅዳሜ 8/15/22/ እሑድ 23/ ሰኞ 24 ግንቦት 24 ጾመ ሐዋርያት
♦ የምሕላ ድኅነት ተውሳክ 1፤ 1 እና 25= 26፤ እሑድ 23 ሰኞ 24 ማግሰኞ 25 ረቡዕ 26 ግንቦት 26 ምሕላ ድኅነት።
👉 ዓመተ ወንጌላዊን ከዚኽ ይናገሯል፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዓመተ ወንጌላዊ ትከፍሎ ለዘመን ኀበ አርባዕቱ እድ ለእመ ተርፈ አሐዱ ማቴዎስ ወክልኤቱ ማርቆስ ወሠለስቱ ሉቃስ ወለእመ ዐረየ ክፍል ዮሐንስ እንዲል፤ ዓመተ ወንጌላዊን ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከአራት ከፍሎ አንድ ቢተርፍ ወንጌላዊዉ ማቴዎስ መኾኑ፤ ኹለት ቢተርፍ ማርቆስ፤ ሦስት ቢተርፍ ሉቃስ ቢተካከል ዮሐንስ መኾኑን በዚኽ ይታወቃል፤ 7518 ዘመን ለአራቱ ወንጌላውያን ቢያካፍሉ 1879 ደርሷቸው 2 ይተርፋል። 2 ቢተርፍ ማርቆስ ያለው ይኽ ነው፤ ዛሬ ወንጌላዊዉ ማርቆስ መኾኑ በዚኽ ታውቋል፡፡
👉 ጥንተ ዮንንም ከዚኽ ይናገሯል፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ጥንተ ዮን ትከፍሎ ለዘመን ኀበ አርባዕቱ እድ ወትዌስክ ቦቱ መጠነ ራብዒት ወትገድፎ በበሱባኤ ወዘተርፈከ እምሱባኤ ተአትት እምኔሁ አሐደ ዓመተ ወእምዝ ይከውን ጥንተ ዮን እንዲል፤ ጥንተ ዮንንም ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከአራት ከፍሎ 5ኛ መጠነ ራብዒት 6ኛ ጳጉሜንን አክሎ፤ በሱባዔ ገድፎ ከሱባዔ የተረፈውን አንዱን አትቶ 1 ቢተርፍ ጥንተ ዮን ረቡዕ መኾኑን መስከረም ረቡዕ መባቱን፤ 2ት ቢተርፍ ኀሙስ፤ 3 ቢተርፍ ዐርብ፤ 4 ቢተርፍ ቀዳሚት፤ 5 ቢተርፍ እሑድ፤ 6 ቢተርፍ ሰኞ፤ 7 ቢተርፍ ማግሰኞ መኾኑ በዚኽ ይታወቃል፡፡
አከፋፈል እንዳለፈው 7518 ዘመን ለአራቱ ወንጌላውያን ቢያካፍሉ 1879 ደርሷቸው 2 ይተርፋል፤ ይኽን በሱባዔ ይገድፏል፤ ከሺው 300 ነሥቶ 700 ግዱፍ፤ ከ800ው አንዱን መቶ ነሥቶ 700 ግዱፍ፤ 400 ይተርል፤ ከ100ው 2፤ ከ400ው 8፤ ከ8ቱ አንድ፤ ከዚያም 1 እና 79 = 80 ይኾናል፤ ከ80ው 77ቱን በ11 ሱባዔ ቢገድፉ 3 ይተርፋል፡፡
👉 ከዚኽም ዓመተ አበቅቴን (ወንበር) ለማግኘት 7518 ዘመን በዐቢይ ቀመር ቢቀምሩ 532፤ 532 የተፈጸመለት 14 ዐቢይ ቀመር፤ 19፤ 19 የተፈጸመለት 3 ንዑስ ቀመር ኾኖ 13 ዓመት ይተርፋል።
👉 መላውንም በማእከላዊ ቀመርም ቢቀምሩ 76፤ 76 የተፈጸመለት 98 ማእከላዊ ቀመር 19፤ 19 የተፈጸመለት 3 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል፡፡
👉 በዐውደ ፀሓይም ቢቀምሩ 28፤ ኻያ ስምንት የተፈጸመለት 266 ዐውደ ፀሓይ፤ 19፤ 19 የተፈጸመለት 3 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል፡፡
👉 መላውንም በንዑስ ቀመር ቢቀምሩ 19፤ 19 የተፈጸመለት 395 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል፡፡
👉 7518ቱን ዘመን በቀመረ ዐረብም ቢቀምሩ 228፤ 228 የተፈጸመለት 32 ቀመረ ዐረብ፤ 19፤ 19 የተፈጸመለት 11 ንዑስ ቀመር ኹኖ 13 ዓመት ይተርፋል።
👉 ስመ አቅማር ብዙ ነው አይቶ መተው ነው፤ አሐደ አዕትት ለዘመን እንዲል ስለተጀመረ ተቈጠረ ስላልተፈጸመ ታተተ ብሎ ከ13ቱ አንዱን ቢያትቱ 12 ይተርፋል፤ 12 ዓመተ አበቅቴ ወጣ ገጠር ወንበር ይላል፡፡
👉 አበቅቴን ለማግኘት ከ12ቱ ዓመተ አበቅቴ 11፤ 11 ዕለት ቢነሡ 132 ይኾናል፤ ከ120ውን 30ውን በ4፤ ፴ ቢገድፉት 1 ይተርፋል፤ 12 አበቅቴ ወጣ በዘመነ ማርቆስ፡፡
👉 መጥቅዕንም ለማግኘት ከ12 ዓመተ አበቅቴ 19 ዕለት ቢነሡ 228 ይኾናል፤ 228ቱን በ7፤ ፴ ቢገድፉት 18 ይቀራል፤ 18 መጥቅዕ ወጣ በዘመነ ማርቆስ፤ 18 መጥቅዕና 12 አበቅቴ ፴ ይኾናሉ እንጂ ከ፴ አይወጡም ከ፴ አይወርዱም፤ “ዓዲ መጥቅዕ ወአበቅቴ ክልኤሆሙ እመ ይበዝኁ ወእመ ይውኅዱ ኢየዐርጉ እም፴ ወኢይወርዱ እም፴ ወባሕቱ ወትረ ይከውኑ ፴” እንዲል።
(ከዚኽ በኋላ አበቅቴ ከመጠነ ሠርቀ መዓልትና ከሚለው ዠምሮ…ኢየዐርግ ኢይወርድ ኹሉ እንደ ታሪኩ አስገባ)
❤ መጥቅዕ 18 መጥቅዕ ቢበዛ በመስከረም ይውላልና መስከረም ኀሙስ ይብታል፤ ኀሙስ እስከ ኀሙስ 8 / 15/ ዓርብ 16/ ቅዳሜ 17/ እሑድ 18 በዓለ መጥቅዕ መስከረም 18 እሑድ።
የእሑድ ተውሳክ 7/ 18 ና 7 = 25 ጥር 25 መባጃ ሐመር
በመስከረም ሳኒታ ጥር ዐርብ ይብታል፡፡ ዐርብ - ዐርብ 8/15/22/ ቅዳሜ 23/ እሑድ 24/ ሰኞ 25 ጥር 25 ነነዌ
♦ የዐቢይ ጾም ተውሳክ 14፤ 14 + 25 = 39 ሠላሳ ቢገድፉ 9 ይተርፋል።
እሑድ እስከ እሑድ 8 ሰኞ 9
የካቲት 9 ዐቢይ ጾም
♦ የደብረ ዘይት ተውሳክ 11፤ 11 እና 25= 36 ሠላሳ ቢገድፉ 6 ይተርፋል መጋቢት ማግሰኞ ይብታል። ማግሰኞ 1/ ረቡዕ 2/ ኃሙስ 3/ ዓርብ 4/ ቅዳሜ 5/ እሑድ 6 መጋቢት 6 ደብረ ዘይት
♦ የሆሣዕና ተውሳክ 2፤ 2 እና 25 = 27፤ ማግሰኞ - ማግሰኞ 8/15/22/ ረቡዕ 23/ ኃሙስ 24/ ዓርብ 25/ ቅዳሜ 26 እሑድ 27 መጋቢት 27 ሆሣዕና።
♦ ከዚኽም በዓለ ፍሥሕን (የአይሁድ ፋሲካን) ይናገሯል፤ ፍሥሕን 4 ነገር ይጠብቃታል፤ ገቦ መጥቅዕ፤ ሰሙነ ሕማማት፤ 190 ዕለት፤ 14 ሌሊት፤ ፍሥሕ የዕለት ተውሳክ አትሻም በደረቅ መጥቅዕ ነው የምትወጣው መጥቅዑ 18 የፍሥሕ ተውሳክ 10= 28፤ መጋቢት 28 ፍሥሕ
በዓሉን አናከብረውም ስለምን እናወጣዋለን ቢሉ ሐዋርያት ፍሥሕን ከትንሣኤ ጋራ አንድ አድርጎ ያዋለ ካህን ቢኾን ከክህነቱ ይሻር፤ ምእመን ቢኾን ከምእመናን ይለይ ብለው አውግዘዋልና ስለዚኽ ለይተን እናወጣዋለን፡፡
♦ የስቅለት ተውሳክ 7፤ 7 እና 25 = 32፤ ሠላሳ ቢገድፉ 2 ይተርፋል። ሚያዝያ ኃሙስ ይብታል። ኀሙስ 1 ዐርብ 2
ሚያዝያ 2 ስቅለት
♦ የትንሣኤ ተውሳክ 9፤ 9 እና 25 =34፤ ሠላሳ ቢገድፉ 4 ይተርፋል። ኀሙስ 1 ዐርብ 2 ቅዳሜ 3 እሑድ 4 ሚያዝያ 4 ትንሣኤ
♦ የርክብ ተውሳክ 3፤ 3 እና 25 = 28፤ ኀሙስ - ኃሙስ 8/15/22/ ረቡዕ 28
ሚያዝያ 28 ረቡዕ
♦ የዕርገት ተውሳክ 18፤ 18 እና 25= 43፤ ሠላሳ ቢገድፉ 13
ግንቦት ቅዳሜ ይብታል። ቅዳሜ - ቅዳሜ 8 እሑድ 9 ሰኞ 10 ማግሰኞ 11 ረቡዕ 12 ኃሙስ 13 ግንቦት 13 ዕርገት
♦ የጰራቅሊጦስ ተውሳክ 28፤ 28 እና 25 = 53፤ ፴ውን ገድፎ 23 ይቀራል፤ ቅዳሜ - ቅዳሜ 8/15/22/ እሑድ 23
ግንቦት 23 ጰራቅሊጦስ
♦ የጾመ ሐዋርያት ተውሳክ 29፤ 29 እና 25= 54፤ ፴ውን ገድፎ 24 ይቀራል፤ ቅዳሜ - ቅዳሜ 8/15/22/ እሑድ 23/ ሰኞ 24 ግንቦት 24 ጾመ ሐዋርያት
♦ የምሕላ ድኅነት ተውሳክ 1፤ 1 እና 25= 26፤ እሑድ 23 ሰኞ 24 ማግሰኞ 25 ረቡዕ 26 ግንቦት 26 ምሕላ ድኅነት።
👉 ዓመተ ወንጌላዊን ከዚኽ ይናገሯል፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዓመተ ወንጌላዊ ትከፍሎ ለዘመን ኀበ አርባዕቱ እድ ለእመ ተርፈ አሐዱ ማቴዎስ ወክልኤቱ ማርቆስ ወሠለስቱ ሉቃስ ወለእመ ዐረየ ክፍል ዮሐንስ እንዲል፤ ዓመተ ወንጌላዊን ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከአራት ከፍሎ አንድ ቢተርፍ ወንጌላዊዉ ማቴዎስ መኾኑ፤ ኹለት ቢተርፍ ማርቆስ፤ ሦስት ቢተርፍ ሉቃስ ቢተካከል ዮሐንስ መኾኑን በዚኽ ይታወቃል፤ 7518 ዘመን ለአራቱ ወንጌላውያን ቢያካፍሉ 1879 ደርሷቸው 2 ይተርፋል። 2 ቢተርፍ ማርቆስ ያለው ይኽ ነው፤ ዛሬ ወንጌላዊዉ ማርቆስ መኾኑ በዚኽ ታውቋል፡፡
👉 ጥንተ ዮንንም ከዚኽ ይናገሯል፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ጥንተ ዮን ትከፍሎ ለዘመን ኀበ አርባዕቱ እድ ወትዌስክ ቦቱ መጠነ ራብዒት ወትገድፎ በበሱባኤ ወዘተርፈከ እምሱባኤ ተአትት እምኔሁ አሐደ ዓመተ ወእምዝ ይከውን ጥንተ ዮን እንዲል፤ ጥንተ ዮንንም ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከአራት ከፍሎ 5ኛ መጠነ ራብዒት 6ኛ ጳጉሜንን አክሎ፤ በሱባዔ ገድፎ ከሱባዔ የተረፈውን አንዱን አትቶ 1 ቢተርፍ ጥንተ ዮን ረቡዕ መኾኑን መስከረም ረቡዕ መባቱን፤ 2ት ቢተርፍ ኀሙስ፤ 3 ቢተርፍ ዐርብ፤ 4 ቢተርፍ ቀዳሚት፤ 5 ቢተርፍ እሑድ፤ 6 ቢተርፍ ሰኞ፤ 7 ቢተርፍ ማግሰኞ መኾኑ በዚኽ ይታወቃል፡፡
አከፋፈል እንዳለፈው 7518 ዘመን ለአራቱ ወንጌላውያን ቢያካፍሉ 1879 ደርሷቸው 2 ይተርፋል፤ ይኽን በሱባዔ ይገድፏል፤ ከሺው 300 ነሥቶ 700 ግዱፍ፤ ከ800ው አንዱን መቶ ነሥቶ 700 ግዱፍ፤ 400 ይተርል፤ ከ100ው 2፤ ከ400ው 8፤ ከ8ቱ አንድ፤ ከዚያም 1 እና 79 = 80 ይኾናል፤ ከ80ው 77ቱን በ11 ሱባዔ ቢገድፉ 3 ይተርፋል፡፡
❤69👍2
ከአንዱ ወንጌላዊ 3 ከ4ቱ ወንጌላውያን 12፤ መጠነ ራብዒት፤ 6ኛ ጳጉሜን 1879 ዕለት ትኾናለች፤ ርሷ በዕለት፤ ወንጌላዊ በዓመት ይተካከላሉና ግድፈት እንዳለፈው፤ መጠነ ራብዒት 3= 15፤ ከዓመተ ወንጌላዊ የተረፈ 2=17፤ ከ17ቱ 14ቱን በ2 ሱባዔ ቢገድፉ 3 ይተርፋል፤ አሐደ አዕትት ለዘመን እንዲል ስለተዠመረ ተቈጠረ ስላልተፈጸመ ታተተ ብሎ ከ3ቱ አንዱን ቢያትቱ 2 ይተርፋል፤ 1 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው፤ የኃሙስ ጥንተ ዮን 2 ነውና፡፡ ጥንተ ዮንም ማለት ጥንተ ፀሓይ፤ ጥንተ ጨረቃ፤ ጥንተ ከዋክብት ማለት ነው፤ ጥንተ ዮን ብሂል ጥንተ ተፈጥሮቶሙ ለፀሓይ፤ ወወርኅ ወከዋክብት እንዲል፡፡
👉 ዕለተ ቀመርንም ለማወቅ ለጥንተ ዮን ከወጣው አንዱን ሳያትቱ በሱባዔ ገድፎ 1 ቢተርፍ ማግሰኞ መኾኑ፤ 2 ቢተርፍ ረቡዕ፤ 3 ቢተርፍ ኀሙስ፤ 4 ቢተርፍ ዐርብ፤ 5 ቢተርፍ ቀዳሚት፤ 6 ቢተርፍ እሑድ፤ 7 ቢተርፍ ሰኞ መኾኑ በዚኽ ይታወቃል፤ ለጥንተ ዮን የወጣው 3 ነው፤ 3 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው። ዕለተ ቀመርም ማለት ቀመር የተዠመረበት ዕለት ማለት ነው፤ ቀመር የተዠመረው ማግሰኞ ነውና፡፡
👉 ዕለተ ዮሐንስንም ከዚኽ ይናገሩታል፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዕለተ ዮሐንስ ትከፍሎ ለዘመን ኀበ አርባዕቱ እድ፤ ወትዌስክ ቦቱ መጠነ ራብዒት፤ ወክልዔተ ዕለተ ጠቢባን ወትገድፎ በበሱባዔ ወዘተርፈከ እምሱባዔ ኢተአትት አሐደ ዓመተ፤ ወእምዝ ይከውን ዕለተ ዮሐንስ እንዲል ዕለተ ዮሐንስን ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከአራት ከፍሎ፤ 5ኛ መጠነ ራብዒት፤ 6ኛ ጳጉሜንን አክሎ፤ 7ኛ 2ት ዕለተ ጠቢባንን ጨምሮ በሱባዔ ገድፎ ከሱባዔ የተረፈውን አንዱን ሳያትቱ አንድ ቢተርፍ ዕለተ ዮሐንስ እሑድ መኾኑ፤ 2 ቢተርፍ ሰኞ፤ 3 ቢተርፍ ማግሰኞ፤ 4 ቢተርፍ ረቡዕ፤ 5 ቢተርፍ ኀሙስ፤ 6 ቢተርፍ ዐርብ፤ 7 ቢተርፍ ቀዳሚት መኾኑ በዚኽ ይታወቃል፡፡
👉 ለጥንተ ዮን የወጣ 3 እና 2 ዕለተ ጠቢባን= 5። 5 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው፤ ዕለተ ዮሐንስም ማለት አሻቅቦ ወደ ላይ እስከ ፍጥረተ ዓለም፤ አቈልቊሎ ወደ ታች እስከ ምጽአተ ክርስቶስ ቢቈጥሩ ለወንጌላዊዉ ዮሐንስ የሚደርሰው ቀን ማለት ነው፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዘኀለፈ ይመርሐከ ዝንቱ እስከ ፍጥረተ ዓለም ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዘይመጽእ ያበጽሐከ ዝንቱ እስከ ምጽአተ ክርስቶስ እንዲል፤ አንድም ሠርቀ ቲቶን ዕለተ ዮሐንስ ይለዋል፤ ቲቶ የተባለው መስከረም ነው፤ የመጥምቁ ዮሐንስ በዓል የሚውልበት ቀን ማለት ነው፤ ርዕሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ እንዲል፡፡
👉 ዕለተ በዓል ዘኀለፈ ዕለተ በዓል ዘይመጽእ የእሑድ አሚሩ ሰንበተ ክርስቲያንን ለማወቅ በዘመኑ የወጣውን ጥንተ ዮን፤ ሠርቀ መዓልት፤ 2 ዕለተ ጠቢባን በየወሩ የሚገኘውን አጽፈ ወርኅ እሊኽን 4ቱን አንድ አድርጎ ቈጥሮ በሱባዔ ገድፎ 1 ቢተርፍ እሑድ አሚሩ፤ 2 ቢተርፍ ሰኞ ሰኑዩ፤ 3 ቢተርፍ ማግሰኞ ሠሉሱ፤ 4 ቢተርፍ ረቡዕ ረቡዑ፤ 5 ቢተርፍ ኀሙስ ኀሙሱ፤ 6 ቢተርፍ ዐርብ ሰዱሱ፤ 7 ቢተርፍ ቀዳሚት ሰቡዑ፤ 8 ቢተርፍ በሱባዔ ገድፎ እሑድ አሚሩ የሚያሰኘው ይኽ ነው፡፡
👉 አጽፈ ወርኅም ማለት የወርኁ ከወርኅ የሚደረብ ማለት ነው፤ ይኽስ ከምን ይገኛል ቢሉ? ወሩን በሱባዔ ቢገድፉ 4 ሱባዔ ኾኖ 2 ይተርፋል፤ የወርኁ 2 የዓመቱ 24፤ እንዲኽ ግን ስለኾነ ለመስከረም አጽፈ ወርኅ የለውም በጥንተ ዮን፤ በሠርቀ መዐልት በኹለት ዕለተ ጠቢባን ይቈጠራል፤ በእሊኽ በ3ቱ ይቈጠራል፤ ጥንተ ዮን 2፤ ሠርቀ መዐልት 1 = 3፤ ኹለት ዕለተ ጠቢባን፤ 5 ይኾናል፤ 5 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው።
👉 ዕለተ ጠቢባንም ማለት ጠቢባን ሥላሴ ይኽነን ዓለም የፈጠሩበት፤ ጠቢባን መላእክት ሥላሴን የሚያመሰግኑበት ቀን ማለት ነው፤ (ዬ) ጠቢባን ሥላሴ ይኽነን ዓለም ከእሑድ እስከ ዐርብ ፈጥረዋል፤ ጠቢባን መላእክት ሥላሴን ዘወትር ያመሰግናሉ ብሎ የቊጥር መጽሐፍን የተማሩ መምህራን ዕለተ ሰንበትን፤ 6ቱ ዕለታትን፤ ያለፉትን የሚመጡትን በዓላት የሚያውቁባቸው የሚያሳውቁባቸው ማለት ነው፤ ዕለተ ጠቢባንም የተባሉ እሑድና ሰኞ ናቸው፤ ከቀመር ገብተው አልተቈጠሩም፡፡
👉 ዕለተ ምርያ አዕዋዲትንም ለማወቅ የፀሓይ ዐውደ ዓመት 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ነው፤ ይኽነን በሱባዔ ቢገድፉት 52 ሱባዔ ኾኖ 1 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ይተርፋል፤ ይኽቺውም አንድ ዕለት የተባለችው ዐምስተኛዪቱ ጳጒሜን ናት፤ ዕለተ ምርያ አዕዋዲት ይላታል፤ ዕለተ ምርያ ማለት ዕለተ መድኀኒት ማለት ነው፤ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበትን ቀን የምታሳውቅ ማለት ነው፤ ርሷ በዋለች ልደት ይውላልና፤ አዕዋዲትም አላት ዘመኑን የምታዘዋውር የምታለዋውጥ ማለት ነው፤ እሑድ የዋለውን ሰኞ፤ ሰኞ የዋለውን ማግሰኞ እንዲውል የምታደርግ ርሷ ናትና፡፡
👉 መጠነ ራብዒት 6ኛ ጳጉሜንም ለማወቅ የአንዱ ዓመት ኬክሮስ 15፤ የ2 ዓመቱ 30፤ የ4 ዓመቱ 60 ኬክሮስ ነው፤ 60ው ኬክሮስ 1 ዕለት ይኾናል፤ ይኽቺውም በሉቃስ መጨረሻ ዮሐንስን ተጠግታ የምትውል ስድስተኛዪቱ ጳጉሜን ናት፤ መጠነ ራብዒት፣ ሠግረ ዮሐንስ ይላታል፤ መጠነ ራብዒት አላት ርሷ በዕለት ወንጌላዊ በዓመት ይተካከላሉና፤ ሠግረ ዮሐንስም አላት ዮሐንስ ተራምዶ የሚውልባት ስለኾነ፡፡
👉 ዕሪና መዓልትና ዕሪና ሌሊትንም ለማወቅ የአንዱ ዓመት ካልዒት 6፤ የ5ቱ ዓመት 30፤ የ10ሩ ዓመት 60 ይኾናል፤ 60ው ካልዒት 1 ኬክሮስ ይኾናል፤ የ100ው ዓመት 10 ኬክሮስ፤ የ600 ዓመት 60 ኬክሮስ፤ 60ው ኬክሮስ አንድ ዕለት ይኾናል፤ ይኽቺውም ሰባተኛዪቱ ጳጉሜን ናት፤ ዓለም በተፈጠረ በ600 ዘመን ዕሪና መዓልት ዕሪና ሌሊት ኾኗል፤ ዓለም ከተፈጠረ ዠምሮ እስከ ዛሬ ድረስ 12 ዕሪና መዓልት 12 ዕሪና ሌሊት ኾኖ 13ኛው ከተዠመረ 318 ኾኖ በዘመነ ማርቆስ ይኸውም ሊመላ 282 ይቀራል፡፡
(ከዚኽ በኋላ እንዲኽ ብሎ ባሕረ ሐሳብ አውጪው እንዲኽ ብሎ አሥርቆት ያውጣ፡፡)
በዘንዜከር ሐሳባተ ሕጉ ወትእዛዙ ለእግዚእነ ወአምላክነ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዘ ሀሎነ በዘመነ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ዘመነ ሉቃስ ዜናዊ፤ ወንጌላዊ አለው ማርቆስን ባለዘመን ነውና፤ ዜናዊ አለው ሉቃስን የሚመጣ ነውና ወረኛ ንጉሥ እንዲሉ፡፡
👉 በሰብዐ ወኀምስቱ ምእት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ዓለም፡፡ በኀምሳ ወኀምስቱ ምዕት ዓመተ ዓለም፤ በዕሥራ ምዕት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ምሕረት፤ ሠረቀ ለነ ወርኀ መስከረም ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ወርኀ ጥቅምት በሰላመ እግዚአብሔር አሜን።
👉 አበቅቴ 12፤ ሠርቀ መዓልት 1፤ ሕጸጽ 1= 14፤ ዐሡሩ ወረቡዑ ሠርቀ ሌሊት፤ ዐሡሩ ወሰሙኑ ሠርቀ ወርኅ፤ አሚሩ ሠርቀ መዓልት፤ ኃሙሱ ሠርቀ ዕለት፤ ዮም በዛቲ ዕለት ዘአቅረብነ ለከ አምኀ ስብሐት ያዐርጉ ለነ መላእክት ተወከፍ ለነ እግዚአ ስብሐት፤ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡።
ከዚያም ዘመነ ማቴዎስ ዐለፈ ዘመነ ማርቆስ መሾሙን 3 ጊዜ ዐውጆ። ይጠናቀቃል
አዘጋጅ፡- መጋቤ ሐዲስ ዶከተር ሮዳስ ታደሰ
የቴሌግራም ቻናሌ https://t.me/Rodas9
👉 ዕለተ ቀመርንም ለማወቅ ለጥንተ ዮን ከወጣው አንዱን ሳያትቱ በሱባዔ ገድፎ 1 ቢተርፍ ማግሰኞ መኾኑ፤ 2 ቢተርፍ ረቡዕ፤ 3 ቢተርፍ ኀሙስ፤ 4 ቢተርፍ ዐርብ፤ 5 ቢተርፍ ቀዳሚት፤ 6 ቢተርፍ እሑድ፤ 7 ቢተርፍ ሰኞ መኾኑ በዚኽ ይታወቃል፤ ለጥንተ ዮን የወጣው 3 ነው፤ 3 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው። ዕለተ ቀመርም ማለት ቀመር የተዠመረበት ዕለት ማለት ነው፤ ቀመር የተዠመረው ማግሰኞ ነውና፡፡
👉 ዕለተ ዮሐንስንም ከዚኽ ይናገሩታል፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዕለተ ዮሐንስ ትከፍሎ ለዘመን ኀበ አርባዕቱ እድ፤ ወትዌስክ ቦቱ መጠነ ራብዒት፤ ወክልዔተ ዕለተ ጠቢባን ወትገድፎ በበሱባዔ ወዘተርፈከ እምሱባዔ ኢተአትት አሐደ ዓመተ፤ ወእምዝ ይከውን ዕለተ ዮሐንስ እንዲል ዕለተ ዮሐንስን ለማወቅ ዓመተ ዓለምን ከአራት ከፍሎ፤ 5ኛ መጠነ ራብዒት፤ 6ኛ ጳጉሜንን አክሎ፤ 7ኛ 2ት ዕለተ ጠቢባንን ጨምሮ በሱባዔ ገድፎ ከሱባዔ የተረፈውን አንዱን ሳያትቱ አንድ ቢተርፍ ዕለተ ዮሐንስ እሑድ መኾኑ፤ 2 ቢተርፍ ሰኞ፤ 3 ቢተርፍ ማግሰኞ፤ 4 ቢተርፍ ረቡዕ፤ 5 ቢተርፍ ኀሙስ፤ 6 ቢተርፍ ዐርብ፤ 7 ቢተርፍ ቀዳሚት መኾኑ በዚኽ ይታወቃል፡፡
👉 ለጥንተ ዮን የወጣ 3 እና 2 ዕለተ ጠቢባን= 5። 5 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው፤ ዕለተ ዮሐንስም ማለት አሻቅቦ ወደ ላይ እስከ ፍጥረተ ዓለም፤ አቈልቊሎ ወደ ታች እስከ ምጽአተ ክርስቶስ ቢቈጥሩ ለወንጌላዊዉ ዮሐንስ የሚደርሰው ቀን ማለት ነው፤ ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዘኀለፈ ይመርሐከ ዝንቱ እስከ ፍጥረተ ዓለም ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ዘይመጽእ ያበጽሐከ ዝንቱ እስከ ምጽአተ ክርስቶስ እንዲል፤ አንድም ሠርቀ ቲቶን ዕለተ ዮሐንስ ይለዋል፤ ቲቶ የተባለው መስከረም ነው፤ የመጥምቁ ዮሐንስ በዓል የሚውልበት ቀን ማለት ነው፤ ርዕሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ወላዴ መጥቅዕ ወአበቅቴ እንዲል፡፡
👉 ዕለተ በዓል ዘኀለፈ ዕለተ በዓል ዘይመጽእ የእሑድ አሚሩ ሰንበተ ክርስቲያንን ለማወቅ በዘመኑ የወጣውን ጥንተ ዮን፤ ሠርቀ መዓልት፤ 2 ዕለተ ጠቢባን በየወሩ የሚገኘውን አጽፈ ወርኅ እሊኽን 4ቱን አንድ አድርጎ ቈጥሮ በሱባዔ ገድፎ 1 ቢተርፍ እሑድ አሚሩ፤ 2 ቢተርፍ ሰኞ ሰኑዩ፤ 3 ቢተርፍ ማግሰኞ ሠሉሱ፤ 4 ቢተርፍ ረቡዕ ረቡዑ፤ 5 ቢተርፍ ኀሙስ ኀሙሱ፤ 6 ቢተርፍ ዐርብ ሰዱሱ፤ 7 ቢተርፍ ቀዳሚት ሰቡዑ፤ 8 ቢተርፍ በሱባዔ ገድፎ እሑድ አሚሩ የሚያሰኘው ይኽ ነው፡፡
👉 አጽፈ ወርኅም ማለት የወርኁ ከወርኅ የሚደረብ ማለት ነው፤ ይኽስ ከምን ይገኛል ቢሉ? ወሩን በሱባዔ ቢገድፉ 4 ሱባዔ ኾኖ 2 ይተርፋል፤ የወርኁ 2 የዓመቱ 24፤ እንዲኽ ግን ስለኾነ ለመስከረም አጽፈ ወርኅ የለውም በጥንተ ዮን፤ በሠርቀ መዐልት በኹለት ዕለተ ጠቢባን ይቈጠራል፤ በእሊኽ በ3ቱ ይቈጠራል፤ ጥንተ ዮን 2፤ ሠርቀ መዐልት 1 = 3፤ ኹለት ዕለተ ጠቢባን፤ 5 ይኾናል፤ 5 ቢተርፍ ኃሙስ ያለው ይኽ ነው።
👉 ዕለተ ጠቢባንም ማለት ጠቢባን ሥላሴ ይኽነን ዓለም የፈጠሩበት፤ ጠቢባን መላእክት ሥላሴን የሚያመሰግኑበት ቀን ማለት ነው፤ (ዬ) ጠቢባን ሥላሴ ይኽነን ዓለም ከእሑድ እስከ ዐርብ ፈጥረዋል፤ ጠቢባን መላእክት ሥላሴን ዘወትር ያመሰግናሉ ብሎ የቊጥር መጽሐፍን የተማሩ መምህራን ዕለተ ሰንበትን፤ 6ቱ ዕለታትን፤ ያለፉትን የሚመጡትን በዓላት የሚያውቁባቸው የሚያሳውቁባቸው ማለት ነው፤ ዕለተ ጠቢባንም የተባሉ እሑድና ሰኞ ናቸው፤ ከቀመር ገብተው አልተቈጠሩም፡፡
👉 ዕለተ ምርያ አዕዋዲትንም ለማወቅ የፀሓይ ዐውደ ዓመት 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ነው፤ ይኽነን በሱባዔ ቢገድፉት 52 ሱባዔ ኾኖ 1 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ይተርፋል፤ ይኽቺውም አንድ ዕለት የተባለችው ዐምስተኛዪቱ ጳጒሜን ናት፤ ዕለተ ምርያ አዕዋዲት ይላታል፤ ዕለተ ምርያ ማለት ዕለተ መድኀኒት ማለት ነው፤ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበትን ቀን የምታሳውቅ ማለት ነው፤ ርሷ በዋለች ልደት ይውላልና፤ አዕዋዲትም አላት ዘመኑን የምታዘዋውር የምታለዋውጥ ማለት ነው፤ እሑድ የዋለውን ሰኞ፤ ሰኞ የዋለውን ማግሰኞ እንዲውል የምታደርግ ርሷ ናትና፡፡
👉 መጠነ ራብዒት 6ኛ ጳጉሜንም ለማወቅ የአንዱ ዓመት ኬክሮስ 15፤ የ2 ዓመቱ 30፤ የ4 ዓመቱ 60 ኬክሮስ ነው፤ 60ው ኬክሮስ 1 ዕለት ይኾናል፤ ይኽቺውም በሉቃስ መጨረሻ ዮሐንስን ተጠግታ የምትውል ስድስተኛዪቱ ጳጉሜን ናት፤ መጠነ ራብዒት፣ ሠግረ ዮሐንስ ይላታል፤ መጠነ ራብዒት አላት ርሷ በዕለት ወንጌላዊ በዓመት ይተካከላሉና፤ ሠግረ ዮሐንስም አላት ዮሐንስ ተራምዶ የሚውልባት ስለኾነ፡፡
👉 ዕሪና መዓልትና ዕሪና ሌሊትንም ለማወቅ የአንዱ ዓመት ካልዒት 6፤ የ5ቱ ዓመት 30፤ የ10ሩ ዓመት 60 ይኾናል፤ 60ው ካልዒት 1 ኬክሮስ ይኾናል፤ የ100ው ዓመት 10 ኬክሮስ፤ የ600 ዓመት 60 ኬክሮስ፤ 60ው ኬክሮስ አንድ ዕለት ይኾናል፤ ይኽቺውም ሰባተኛዪቱ ጳጉሜን ናት፤ ዓለም በተፈጠረ በ600 ዘመን ዕሪና መዓልት ዕሪና ሌሊት ኾኗል፤ ዓለም ከተፈጠረ ዠምሮ እስከ ዛሬ ድረስ 12 ዕሪና መዓልት 12 ዕሪና ሌሊት ኾኖ 13ኛው ከተዠመረ 318 ኾኖ በዘመነ ማርቆስ ይኸውም ሊመላ 282 ይቀራል፡፡
(ከዚኽ በኋላ እንዲኽ ብሎ ባሕረ ሐሳብ አውጪው እንዲኽ ብሎ አሥርቆት ያውጣ፡፡)
በዘንዜከር ሐሳባተ ሕጉ ወትእዛዙ ለእግዚእነ ወአምላክነ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዘ ሀሎነ በዘመነ ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ዘመነ ሉቃስ ዜናዊ፤ ወንጌላዊ አለው ማርቆስን ባለዘመን ነውና፤ ዜናዊ አለው ሉቃስን የሚመጣ ነውና ወረኛ ንጉሥ እንዲሉ፡፡
👉 በሰብዐ ወኀምስቱ ምእት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ዓለም፡፡ በኀምሳ ወኀምስቱ ምዕት ዓመተ ዓለም፤ በዕሥራ ምዕት ዐሠርቱ ወሰመንቱ ዓመተ ምሕረት፤ ሠረቀ ለነ ወርኀ መስከረም ቡሩክ ያብጽሐነ እስከ ወርኀ ጥቅምት በሰላመ እግዚአብሔር አሜን።
👉 አበቅቴ 12፤ ሠርቀ መዓልት 1፤ ሕጸጽ 1= 14፤ ዐሡሩ ወረቡዑ ሠርቀ ሌሊት፤ ዐሡሩ ወሰሙኑ ሠርቀ ወርኅ፤ አሚሩ ሠርቀ መዓልት፤ ኃሙሱ ሠርቀ ዕለት፤ ዮም በዛቲ ዕለት ዘአቅረብነ ለከ አምኀ ስብሐት ያዐርጉ ለነ መላእክት ተወከፍ ለነ እግዚአ ስብሐት፤ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡።
ከዚያም ዘመነ ማቴዎስ ዐለፈ ዘመነ ማርቆስ መሾሙን 3 ጊዜ ዐውጆ። ይጠናቀቃል
አዘጋጅ፡- መጋቤ ሐዲስ ዶከተር ሮዳስ ታደሰ
የቴሌግራም ቻናሌ https://t.me/Rodas9
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
❤217👍41🥰12👏12
የ2018 ዓ.ም. የአጽዋማትና የበዓላት አወጣጣ (ባሕረ ሐሳብ)በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
https://www.youtube.com/watch?v=4Jk_uyi_YGQ
https://www.youtube.com/watch?v=4Jk_uyi_YGQ
YouTube
የ2018 ዓ.ም. የአጽዋማትና የበዓላት አወጣጣ (ባሕረ ሐሳብ)በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤114🥰42👍23👏8😁2
🌓አራቱ ተከታታይ የሰማይ ክስተቶች መንፈሳዊ አምሳል🌒
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌟 በሉቃስ 21፡25 -28 ላይ ✍️ “በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል ...ይኽም ሊኾን ሲጀምር ቤዛችኹ ቀርቦአልና አሻቅባችኹ ራሳችሁን አንሡ።”
በማለት ጌታችን እንዳስተማረ እነዚኽ ሰማያዊ አካላት በየጊዜው የሚያሳዩት ታላላቅ መንፈሳዊ ምልክት አለና በሰማይ ላይ በተከታታይ ስለታዩት አራት ታላላቅ መንፈሳዊ የጊዜያችን ምልክቶች በስሱ ለማለት ወደድኊ፡፡
💥 በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. “ርኅወተ ሰማይ” (የሰማይ መከፈት) በሚደረግበት በዕለተ እሑድ ምሽት በሑት (ዓሣዎች) (ፓይሲስ) መናዝል ውስጥ የ2017 ዓ.ም. የዓመቱ የመጨረሻዋ የሙሉ ጨረቃ ዕለት ታላቅ የደም ጨረቃ (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ) ተከናውኖ ኹላችንም በዐይናችን ያየንበት ድንቅ ዕለት ነበረ፡፡
💥 ፀሓይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብትን እግዚአብሔር ከተፈጠረበት ዋና ዓላማ የመዠመሪያው ለምልክት ነውና “በርኅወተ ሰማይ” (በሰማይ መከፈት) ዕለት መከናወኑ ግጥጥሞሽ ሳይኾን ሥርዓት ነው።
☄️ በማጠናቀቂያ የጳጉሜን ወር ዳግመኛም በመናዝል ማጠቃለያ በፓይሲስ (ሑት - ዓሣዎች) ውስጥ የተከናወነ የደም ጨረቃ በፍጻሜው ጊዜ ለዓሣዎች (የሰው) ልጆች ሕይወት የፈሰሰውን የክርስቶስን የመሥዋዕት ደምና በዕለቱ የጨረቃን ደም መምሰል እንድናስታውስ በሚገባ ያደርገናል።
☄️ በዓሉም የቅዱስ ሩፋኤል ከመኾኑ ጋር ተያይዞ "ሩፋ" ማለት "ፈውስ" ኤል "እግዚአብሔር" ነውና አቅንተው ለተማፀኑ ፈውሰ እግዚአብሔር ለተማፀኑ ኹሉ የተሰጠበት ዕለት ነው።
💥 ሑት (ዓሣ - ፓይሲስ) ብዙ ምስጢር በመያዙ በመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ኹሉ ዋና መግባቢያ ነበረ፡፡
🌟 “ዓሣ” ኢክተስ ΙΧΘΥΣ (Ichthys) ሲባል ፍቺውም በምሕጻረ ቃል “ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ፣ አዳኝ” ማለት ነበረ።
☄️ በተመሳሳይ የውሃ ጠባይዕ በኾነው በዓሣዎቹ መናዝል ቀይ የደም ጨረቃ በዚኽ ዕለት ሲታይ ለመጀመሪያ ጊዜም በግብጽ በዐባይ ውሃ ላይ በሙሴ በትር የተደረገው ተአምር የውሃው ደም መኾንና የዓሣዎቹ መሞት ነበረ። ተመሳሳይ ምልክት በሰማይ በታየ በኹለተኛው ቀን ጳጉሜን 4 የዐባይ ግድብ በመጠናቀቅ የኢትዮጵያ ታላቅ ዑደት ጀምሯል።
💥💥💥
🌒 እሑድ መስከረም 11/ 2018 ዓ.ም. በዐዲሱ ዓመታችን የመዠመሪያዋ ጠፍ ጨረቃ በምትውልበት ዕለት ደግሞ በደቡብ ፓሲፊክ፣ ኒውዝላንድ፣ ምሥራቅና ደቡብ አውስትራሊያ፣ አንታርክቲካ ያሉ ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ ይታያል፡፡
🌟 ፀሓይ በዚኽ ግርዶሽ ጊዜ በሰንቡላ (ድንግል - ቪርጎ) መናዝል ውስጥ በመኾን በእሳት ቀለበት 🌚 ተሞሽራ ትታያለች፡፡
☄️ በመንፈሳዊ ትርጓሜ ሰንቡላ (ቪርጎ) በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቤተልሔም የምትመሰል ናት፡፡
🌟 በእኛ “ሰንቡላ” በዕብራይስጥ “ቤቱላህ” ትባላላች፤ ፍቺውም “ድንግል” ማለት ነው፡፡ በግሪክም “ሴሬስና ፓርቴኖስ” ስትባል ፍቺውም “ንጽሕት ብላቴና ድንግል” ማለት ነው፡፡
☄️ በዐረቢክም “አዳራህ” ሲሏት ፍቺዋም “ንጽሕት ድንግል” ማለት ነው፡፡ ይኽችን መናዝል አምላክ በሰማይ ማኖሩ የመሲሑን ከድንግል መወለድ የሚያመለክት ሕያው ምልክት ነበረ፡፡
🌟 ፀሓይ በመስከረም 10 በመስከረም 11 ዕለት በዚኽ ግርዶሽ ወቅት በዚኽች ሰንቡላ ውስጥ እንደምታበራ በዮሐንስ ራእ 12፡1 ✍️“ወአስተርአየ ተአምር ዐቢይ በውስተ ሰማይ ብእሲት እንተ ትለብስ ፀሓየ” (“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”
— ራእይ 12፥1
ያለውን ምልክቱ ያሳያል፡፡
☄️ መስከረም 10 ሲነሣ ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያም ልደትን ጳጒሜን 3 (September 8th) አብዛኞቹ የዓለማት ሀገራትና አብያተ ክርስቲያናት ያስባሉ፡፡ ሌላው መስከረም 10 ሲኾን፤ መጨረሻው ግንቦት 1 ይከበራል፡፡
🌟 በተአምሯ መቅድም ላይ “ቦ እለ ይቤሉ አመ ዐሡሩ ለመስከረም ልደታ ወንሕነሰ ንብል ጥዩቀ በከመ መሀሩነ አበዊነ ሊቃውንት አመ አሚሩ ለግንቦት ልደታ” (መስከረም ዐሥር ቀን ልደቷ ነው የሚሉም አሉ፤ እኛ ግን በተረዳ ነገር አባቶቻችን ሊቃውንት እንዳስተማሩን ልደቷን ግንቦት 1 ቀን ነው እንላለን) ይላል፡፡
💥💥💥
✍️ ሰኞ መስከረም 12/ 2018 ዓ.ም. ፀሐይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና በመላው ዓለም “ዕሪና መዓልት ወሌሊት” (ቀኑና ሌሊቱ እኩል የሚኾንበት) ቀን ሲኾን እኩሌ” (Autumn Equinox) ይባላል፡፡ ይህ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አቅጣጫ የምትሄድበት ጊዜ ሲሆን ፀሐይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ሆና ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚሆንበት ጊዜ ነው፡፡
✍️ ዲድስቅልያ የወቅቶችን መለወጫ ሲያይ “እስመ ይዔሪ መዓልት ወሌሊት አመ ዕሥራ ወኀሙሱ” (ቀንና ሌሊት በ25 ይተካከላልና) ይላል እንጂ መስከረም 12 – 14 ውስጥ ይመላለሳል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በግእዝ መዝገበ ቃላት ገጽ 577 ላይ በደቃይቅ ቊጥር አራት ቀን ወደ ታች ወርዶ “አመ ዕሥራ ወአሚሩ” (በ21) ኹኗል፡፡ በኛም ብተት “አመ ዐሡሩ ወሠሉሱ” (በ13ኛው ዕለት) ወይም “ወረቡዑ” (በ14ኛው ዕለት) ኹኗል በማለት የቀመሩን ስልት ጽፈዋል፡፡ ይኽ መተካከል በየ182 ቀን የሚከናወን ሲኾን ይኸውም በግእዝ ፊደላት ቊጥር ስደራ ልክ ነው (26 ፊደላት x 7 = 182)፡፡
💥💥💥
✍️ ሰኞ መስከረም 12 - ረቡዕ 14/ 2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡ በዕብራውያን ትውፊትና በቤዛንታይን ባሉት ኹሉ ትውፊት “ልደተ ዓለም” (ዓለም የተፈጠረበት ወር) ተብሎ ይታሰባል፡፡
🌟 እንደ አለቃ ኪዳነ ወልድ ትንታኔ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ቀዳማዊ ወር ኤታኒም ነበር በኋላ ግን ከግብጽ የወጡበት ኔሣን (ሚያዝያ) ስለነበር “ዝንቱ ወርኅ ይኩንክሙ ቀዳማየ አውራኅ” (ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችኊ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችኊ) ተብለው በእነርሱ የጥቅምትን ቅድምና ለሚያዝያ የሚያዝያን 7ተኛነት ለጥቅምት (በእኛ ለመስከረም) እንዲሰጡ ታዘው ነበር ይላሉ (ዘፀ 12፡2)።
☄️ እስራኤላውያን ከግብጽ የወጡበትን ሚያዝያን ዐዲስ ዓመታቸውን እንዲያከብሩ ቢታዘዙም ግን ዓለም የተፈጠረበትን የኤታኒም 7ተኛ ወርን እንዲያከብሩ “አመ ርእሰ ሳብዕ ሠርቀ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ” (በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችኊ) ተብለው ታዘው ነበርና ቀንደ መለከት እየነፉ ዓለም የተፈጠረበት ወር ያከብሩ ነበር፡፡ (ዘሌዋ 23፡24)፡፡
💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ
✍️ “ንፍሑ ቀርነ በጽዮን ወስብኩ በደብረ መቅደስየ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር እስመ ይቤ ዛቱ በዓለ እግዚአሔር” (በጽዮን ቀንደ መለከትን ንፉ፤ በመቅደሴ ተራራ ስበኩ፤ ይኸቺ ዕለት የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሏልና) በማለት የገለጻት ይኽቺ በዓል በብሉይ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት አንደኛዋ ስትኾን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ክርስቶስ ለፍርድ ሲመጣ የሚነፋውን ቀንደ መለከት ጠቋሚ ናት፡፡
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌟 በሉቃስ 21፡25 -28 ላይ ✍️ “በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል ...ይኽም ሊኾን ሲጀምር ቤዛችኹ ቀርቦአልና አሻቅባችኹ ራሳችሁን አንሡ።”
በማለት ጌታችን እንዳስተማረ እነዚኽ ሰማያዊ አካላት በየጊዜው የሚያሳዩት ታላላቅ መንፈሳዊ ምልክት አለና በሰማይ ላይ በተከታታይ ስለታዩት አራት ታላላቅ መንፈሳዊ የጊዜያችን ምልክቶች በስሱ ለማለት ወደድኊ፡፡
💥 በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. “ርኅወተ ሰማይ” (የሰማይ መከፈት) በሚደረግበት በዕለተ እሑድ ምሽት በሑት (ዓሣዎች) (ፓይሲስ) መናዝል ውስጥ የ2017 ዓ.ም. የዓመቱ የመጨረሻዋ የሙሉ ጨረቃ ዕለት ታላቅ የደም ጨረቃ (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ) ተከናውኖ ኹላችንም በዐይናችን ያየንበት ድንቅ ዕለት ነበረ፡፡
💥 ፀሓይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብትን እግዚአብሔር ከተፈጠረበት ዋና ዓላማ የመዠመሪያው ለምልክት ነውና “በርኅወተ ሰማይ” (በሰማይ መከፈት) ዕለት መከናወኑ ግጥጥሞሽ ሳይኾን ሥርዓት ነው።
☄️ በማጠናቀቂያ የጳጉሜን ወር ዳግመኛም በመናዝል ማጠቃለያ በፓይሲስ (ሑት - ዓሣዎች) ውስጥ የተከናወነ የደም ጨረቃ በፍጻሜው ጊዜ ለዓሣዎች (የሰው) ልጆች ሕይወት የፈሰሰውን የክርስቶስን የመሥዋዕት ደምና በዕለቱ የጨረቃን ደም መምሰል እንድናስታውስ በሚገባ ያደርገናል።
☄️ በዓሉም የቅዱስ ሩፋኤል ከመኾኑ ጋር ተያይዞ "ሩፋ" ማለት "ፈውስ" ኤል "እግዚአብሔር" ነውና አቅንተው ለተማፀኑ ፈውሰ እግዚአብሔር ለተማፀኑ ኹሉ የተሰጠበት ዕለት ነው።
💥 ሑት (ዓሣ - ፓይሲስ) ብዙ ምስጢር በመያዙ በመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ኹሉ ዋና መግባቢያ ነበረ፡፡
🌟 “ዓሣ” ኢክተስ ΙΧΘΥΣ (Ichthys) ሲባል ፍቺውም በምሕጻረ ቃል “ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ፣ አዳኝ” ማለት ነበረ።
☄️ በተመሳሳይ የውሃ ጠባይዕ በኾነው በዓሣዎቹ መናዝል ቀይ የደም ጨረቃ በዚኽ ዕለት ሲታይ ለመጀመሪያ ጊዜም በግብጽ በዐባይ ውሃ ላይ በሙሴ በትር የተደረገው ተአምር የውሃው ደም መኾንና የዓሣዎቹ መሞት ነበረ። ተመሳሳይ ምልክት በሰማይ በታየ በኹለተኛው ቀን ጳጉሜን 4 የዐባይ ግድብ በመጠናቀቅ የኢትዮጵያ ታላቅ ዑደት ጀምሯል።
💥💥💥
🌒 እሑድ መስከረም 11/ 2018 ዓ.ም. በዐዲሱ ዓመታችን የመዠመሪያዋ ጠፍ ጨረቃ በምትውልበት ዕለት ደግሞ በደቡብ ፓሲፊክ፣ ኒውዝላንድ፣ ምሥራቅና ደቡብ አውስትራሊያ፣ አንታርክቲካ ያሉ ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ ይታያል፡፡
🌟 ፀሓይ በዚኽ ግርዶሽ ጊዜ በሰንቡላ (ድንግል - ቪርጎ) መናዝል ውስጥ በመኾን በእሳት ቀለበት 🌚 ተሞሽራ ትታያለች፡፡
☄️ በመንፈሳዊ ትርጓሜ ሰንቡላ (ቪርጎ) በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቤተልሔም የምትመሰል ናት፡፡
🌟 በእኛ “ሰንቡላ” በዕብራይስጥ “ቤቱላህ” ትባላላች፤ ፍቺውም “ድንግል” ማለት ነው፡፡ በግሪክም “ሴሬስና ፓርቴኖስ” ስትባል ፍቺውም “ንጽሕት ብላቴና ድንግል” ማለት ነው፡፡
☄️ በዐረቢክም “አዳራህ” ሲሏት ፍቺዋም “ንጽሕት ድንግል” ማለት ነው፡፡ ይኽችን መናዝል አምላክ በሰማይ ማኖሩ የመሲሑን ከድንግል መወለድ የሚያመለክት ሕያው ምልክት ነበረ፡፡
🌟 ፀሓይ በመስከረም 10 በመስከረም 11 ዕለት በዚኽ ግርዶሽ ወቅት በዚኽች ሰንቡላ ውስጥ እንደምታበራ በዮሐንስ ራእ 12፡1 ✍️“ወአስተርአየ ተአምር ዐቢይ በውስተ ሰማይ ብእሲት እንተ ትለብስ ፀሓየ” (“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”
— ራእይ 12፥1
ያለውን ምልክቱ ያሳያል፡፡
☄️ መስከረም 10 ሲነሣ ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያም ልደትን ጳጒሜን 3 (September 8th) አብዛኞቹ የዓለማት ሀገራትና አብያተ ክርስቲያናት ያስባሉ፡፡ ሌላው መስከረም 10 ሲኾን፤ መጨረሻው ግንቦት 1 ይከበራል፡፡
🌟 በተአምሯ መቅድም ላይ “ቦ እለ ይቤሉ አመ ዐሡሩ ለመስከረም ልደታ ወንሕነሰ ንብል ጥዩቀ በከመ መሀሩነ አበዊነ ሊቃውንት አመ አሚሩ ለግንቦት ልደታ” (መስከረም ዐሥር ቀን ልደቷ ነው የሚሉም አሉ፤ እኛ ግን በተረዳ ነገር አባቶቻችን ሊቃውንት እንዳስተማሩን ልደቷን ግንቦት 1 ቀን ነው እንላለን) ይላል፡፡
💥💥💥
✍️ ሰኞ መስከረም 12/ 2018 ዓ.ም. ፀሐይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና በመላው ዓለም “ዕሪና መዓልት ወሌሊት” (ቀኑና ሌሊቱ እኩል የሚኾንበት) ቀን ሲኾን እኩሌ” (Autumn Equinox) ይባላል፡፡ ይህ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አቅጣጫ የምትሄድበት ጊዜ ሲሆን ፀሐይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ሆና ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚሆንበት ጊዜ ነው፡፡
✍️ ዲድስቅልያ የወቅቶችን መለወጫ ሲያይ “እስመ ይዔሪ መዓልት ወሌሊት አመ ዕሥራ ወኀሙሱ” (ቀንና ሌሊት በ25 ይተካከላልና) ይላል እንጂ መስከረም 12 – 14 ውስጥ ይመላለሳል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በግእዝ መዝገበ ቃላት ገጽ 577 ላይ በደቃይቅ ቊጥር አራት ቀን ወደ ታች ወርዶ “አመ ዕሥራ ወአሚሩ” (በ21) ኹኗል፡፡ በኛም ብተት “አመ ዐሡሩ ወሠሉሱ” (በ13ኛው ዕለት) ወይም “ወረቡዑ” (በ14ኛው ዕለት) ኹኗል በማለት የቀመሩን ስልት ጽፈዋል፡፡ ይኽ መተካከል በየ182 ቀን የሚከናወን ሲኾን ይኸውም በግእዝ ፊደላት ቊጥር ስደራ ልክ ነው (26 ፊደላት x 7 = 182)፡፡
💥💥💥
✍️ ሰኞ መስከረም 12 - ረቡዕ 14/ 2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡ በዕብራውያን ትውፊትና በቤዛንታይን ባሉት ኹሉ ትውፊት “ልደተ ዓለም” (ዓለም የተፈጠረበት ወር) ተብሎ ይታሰባል፡፡
🌟 እንደ አለቃ ኪዳነ ወልድ ትንታኔ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ቀዳማዊ ወር ኤታኒም ነበር በኋላ ግን ከግብጽ የወጡበት ኔሣን (ሚያዝያ) ስለነበር “ዝንቱ ወርኅ ይኩንክሙ ቀዳማየ አውራኅ” (ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችኊ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችኊ) ተብለው በእነርሱ የጥቅምትን ቅድምና ለሚያዝያ የሚያዝያን 7ተኛነት ለጥቅምት (በእኛ ለመስከረም) እንዲሰጡ ታዘው ነበር ይላሉ (ዘፀ 12፡2)።
☄️ እስራኤላውያን ከግብጽ የወጡበትን ሚያዝያን ዐዲስ ዓመታቸውን እንዲያከብሩ ቢታዘዙም ግን ዓለም የተፈጠረበትን የኤታኒም 7ተኛ ወርን እንዲያከብሩ “አመ ርእሰ ሳብዕ ሠርቀ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ” (በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችኊ) ተብለው ታዘው ነበርና ቀንደ መለከት እየነፉ ዓለም የተፈጠረበት ወር ያከብሩ ነበር፡፡ (ዘሌዋ 23፡24)፡፡
💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ
✍️ “ንፍሑ ቀርነ በጽዮን ወስብኩ በደብረ መቅደስየ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር እስመ ይቤ ዛቱ በዓለ እግዚአሔር” (በጽዮን ቀንደ መለከትን ንፉ፤ በመቅደሴ ተራራ ስበኩ፤ ይኸቺ ዕለት የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሏልና) በማለት የገለጻት ይኽቺ በዓል በብሉይ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት አንደኛዋ ስትኾን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ክርስቶስ ለፍርድ ሲመጣ የሚነፋውን ቀንደ መለከት ጠቋሚ ናት፡፡
❤78👍3👎2🥰1
☄️ ይኸውም 7 ፍጹም ነው = ፍጻሜ ዓለምን
☄️ 7 የዕረፍት ቀን ነው = ዕረፍት መምጣቱን፤
☄️ የቀንደ መለከት መነፋት - በሊቃነ መላእክት የሚነፋውን ቀንደ መለከት ይገልጻል፡-
✍️ “መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ።”
— ማቴዎስ 24፥31
✍️“አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥51-52
✍️ “ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥16
☄️ በመኾኑም በሰማይ መከፈት የተደረገው የጨረቃ ግርዶሽ - የአሮጌ ዑደት መጠናቀቅ
☄️ የቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ - የዐዲስ ዑደት ዥማሮን
☄️ በሚዛን ወቅት ያለ የቐንና የሌሊት መተካከል - የፍርድ ሚዛንን
☄️ የቀንደ መለከት ድምፅ - ንቃተ ኅሊና በመላው ዓለም መታወጅን ይወክላል
💥 በመጨረሻም የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያዋ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 28/ 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 12፡26 ላይ ደምቃ በመውጣት እስከ ሌሊቱ 12፡!2 ድረስ ሰማዩን አድምቃው ትውላለችና ለዚያ ዕከት በሰላም ያድርሰን፡፡
ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ መስከረም 10 ተጻፈ።
☄️ 7 የዕረፍት ቀን ነው = ዕረፍት መምጣቱን፤
☄️ የቀንደ መለከት መነፋት - በሊቃነ መላእክት የሚነፋውን ቀንደ መለከት ይገልጻል፡-
✍️ “መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ።”
— ማቴዎስ 24፥31
✍️“አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥51-52
✍️ “ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥16
☄️ በመኾኑም በሰማይ መከፈት የተደረገው የጨረቃ ግርዶሽ - የአሮጌ ዑደት መጠናቀቅ
☄️ የቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ - የዐዲስ ዑደት ዥማሮን
☄️ በሚዛን ወቅት ያለ የቐንና የሌሊት መተካከል - የፍርድ ሚዛንን
☄️ የቀንደ መለከት ድምፅ - ንቃተ ኅሊና በመላው ዓለም መታወጅን ይወክላል
💥 በመጨረሻም የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያዋ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 28/ 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 12፡26 ላይ ደምቃ በመውጣት እስከ ሌሊቱ 12፡!2 ድረስ ሰማዩን አድምቃው ትውላለችና ለዚያ ዕከት በሰላም ያድርሰን፡፡
ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ መስከረም 10 ተጻፈ።
❤127👍22👏7👎2🔥2
🌟 መስከረም 12 ኢትዮጵያ የጠበቀችው ድንቅ ዕለት🌟
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 መስከረም 12 ለፕላኔታችን መሬት በሙላ ታላቅ ዕለት ናት፤ ይኽነን ጥበብ በዘመን ቀመሯና በፊደሏ የያዘችውና የምትምሰክረው ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፤ በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር መስከረም 12 በሌላው ዓለም አቈጣጠር ደግሞ እንደ ኹኔታው መስከረም (September) 21 ወይም 21 አንዳንዴም 22 ይኾናል።
🌟 በዚኽ ቀን ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀኑና ሌሊቱ በመላው ዓለም እኩል የሚኾንበት ወቅት “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው" (የመፀው እኩሌ (Autumnal /fall equinox) ይባላል፡፡
🌟 ይኽ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ መፀው የሚዠምርበት ዕለት ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡
🌟 የኢትዮጵያ ዐዲሱ ዓመት መግቢያ “መስከረም” ከኾነባቸው በርካታ ምክንያት ውስጥም አንደኛው በ182 ቀን አንዴ “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው” (የመፀው የቀንና የሌሊት መተካከል) (Autumnal /fall equinox) የሚኾንበት ወርም ጭምር በመኾኑ ነው፡፡
🌟 መጽሐፍ ስንክሳርም የዓመቱ መዠመሪያ ስለኾነው የመስከረም ወር እንዲኽ ይተነትነዋል፡-
✍️ “ወርኃ መስከረም ቡሩክ ርእሰ አውራኅ ዓመታት ዘግብጽ ወኢትዮጵያ ሰዓተ መዓልቱ ፲ወ፪ቱ ዕሩይ ምስለ ሌሊቱ ወእምዝ የሐጽጽ”
(የተባረከ የመስከረም ወር የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመታት ወሮች ራስ ነው፤ የቀኑ ሰዓትም ከሌሊቱ ሰዓት የተስተካከለ ዐሥራ ኹለት ነው፤ ከዚኽ በኋላ እያነሰ ይኼዳል) በማለት የመፀው እኩሌ የሚደረግበት ወር እንደኾነ አስቀምጧል፡፡
💥 91 ዕለት ከ15 ኬክሮስ የአራቱ ወቅታት የዘመን ቀመር ላለን በዲድስቅልያ 30 ላይ ✍️ “እስመ ይዔሪ መዓልት ወሌሊት አመ ዕሥራ ወኀሙሱ” (መዓልትና ሌሊት በመጋቢት 25 ይተካከላል) ይላል፡፡
🌟 አለቃ ኪዳነ ወልድ በመዝገበ ቃላታቸው ገጽ 577 ላይ ሲያብራሩ በ25 ያለው የድሮውን ነው፤ ዛሬ ግን በደቃይቅ ቊጥር 4 ቀን ወደ ታች ወርዶ “አመ ዕሥራ ወአሚሩ” (በ21) ኹኗል፡፡ በእኛ ብተት ደግሞ “አመ ዐሡሩ ወሠሉሱ ወይም ወረቡዑ” (በ12 ወይም በ13) ይኾናል ብለዋል፡፡
ኹለተኛው በ182 ቀን የሚኾነው የቀንና ሌሊት መተካከል
🌟 በኢትዮጵያ አቈጣጠር መጋቢት 12 በፈረንጆች ደግሞ መጋቢት (ማርች 20 ወይም 21) ላይ የሚውለው እና ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚኾንበት ጊዜ (ወቅት) “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘጸደይ” (የጸደይ የቀንና ሌሊት መተካከል) (Vernal/spring equinox) ይባላል፡፡
🌟 ይኽ ዕለት ፀሓይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ሰሜን አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን ለሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ ላሉ ጸደይ የሚዠምሩበት ቀን ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡ በየ182 ቀናቱ የሚኾነውን የዕሪና መዓልት ወሌሊት (ኢኪውኖክስ) ሳይንስን በሚገባ በመረዳታቸው ነበር ይኽነን መተካከል የሚደረግበት ሌላኛውን ወር “መጋቢት” ብለው ሠይመውታል፡፡
🌟 መጋቢት የሚለው ቃል “መግቦ መግቦት” ከሚለው የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የወጣ ቃል ሲኾን ትርጒሙም የመዓልትና የሌሊት ምግብና እንደ መስከረም ትክክል የሚኾንበት ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚመጋገብበት ወርኀ ዕሪና (የመተካከል ወር) ማለት ነው፡፡
💥 በኢትዮጵያ የሥነ ከዋክብት ትምህርት በ12ቱ ወራት የስፍረ ሰዓት የሠንጠረዥ ትምህርት ላይ የመስረምና የመጋቢት ወር ሠንጠረዥ አንድ ሲኾን ቀኑና ሌሊቱ 12 ዐሥራ ኹለት ነው፡፡በምድር ወገብ በየትኛውም ወቅት ቢኾን የሰዓተ መዓልቱ ጊዜ በዚኽ ዕለት 12 ሰዓታት ያኽል ነው፡፡
🌟 ከመጋቢት እኩሌ (March equinox) እስከ መስከረም እኩሌ (September equinox)፤ ፀሓይ በ23.5° ዲግሪ በሰሜን ምሥራቅ በኩል በመውጣት በ23.5° ዲግሪ በሰሜን ምዕራብ በኩል ትጠልቃለች፡፡
🌟 ከመስከረም እኩሌ እስከ መጋቢት እኩሌ፤ ፀሓይ በ23.5° ዲግሪ በደቡብ ምሥራቅ በኩል በመውጣት፤ በ23.5° ዲግሪ በደቡብ ምዕራብ በኩል ትጠልቃለች፡፡
🌟 በመጋቢት እና በመስከረም (ኹለቱ እኩሌዎች) የመዓልቱ ርዝማኔ 12 ሰዓታት ያኽል ነው፡፡ይኽነን ጥበብ በታላቁ የፊደል ቀመራችን ውስጥ በጥበብ ተሠናሥሎ ተዋሕዶና ተጋምዶ የተቀመጠባት ብቸኛዋ የምድራችን ሀገር ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፡፡
💥 ከፊደል [አ] እስከ ፊደል [ፐ] ከላይ ወደ ታች የተደረደሩት 26ት የግእዝ ፊደላት ናቸው፡፡
☄️ወደ ጐን ያሉት [አ] [ቡ] [ጊ] [ዳ] [ሄ] [ው] [ዞ] ደግሞ 7 ናቸው፡፡
☄️ በአጠቃላይ ለማወቅ 26 × 7 =182 ይኾናሉ፡፡
☄️ ይኸውም 365 የዓመት ቀናት ÷ 2 = 182.5 በመምጣት የዓመቱን የግማሽ ዕለት ቀመርን ፊደላቱ ይዘዋል፡፡ በምንኖርባት ምድር ላይ በግእዝ ፊደላችን ቊጥር ልክ በየ182ት ቀናት የሚከሰቱትን፡-
💥 ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው
💥 ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘጸደይ
ናቸው፡፡
🌟 በዚኽች ቀንና ሌሊቷ እኩል በሚኾንበት ሰኞ መስከረም 12 በ2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ רֹאשׁ הַשָּׁנָה የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡
☄️ በዕብራውያን ትውፊትና በቤዛንታይን ባሉት ኹሉ ትውፊት “ልደተ ዓለም” (ዓለም የተፈጠረበት ወር) Έτη Γενέσεως Κόσμου κατά 'Ρωμαίους ተብሎ ይታሰባል፡፡
https://orthochristian.com/97046.html
💥 እንደ አለቃ ኪዳነ ወልድ ትንታኔ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ቀዳማዊ ወር ኤታኒም ነበር በኋላ ግን ከግብጽ የወጡበት ኔሣን (ሚያዝያ) ስለነበር “ዝንቱ ወርኅ ይኩንክሙ ቀዳማየ አውራኅ” (ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችኊ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችኊ) ተብለው በእነርሱ የጥቅምትን ቅድምና ለሚያዝያ የሚያዝያን 7ተኛነት ለጥቅምት (በእኛ ለመስከረም) እንዲሰጡ ታዘው ነበር ይላሉ (ዘፀ 12፡2)።
💥 እስራኤላውያን ከግብጽ የወጡበትን ሚያዝያን ዐዲስ ዓመታቸውን እንዲያከብሩ ቢታዘዙም ግን ዓለም የተፈጠረበትን የኤታኒም 7ተኛ ወርን እንዲያከብሩ፡-
✍️ “አመ ርእሰ ሳብዕ ሠርቀ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ” (በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችኊ) ተብለው ታዘው ነበርና ቀንደ መለከት እየነፉ ዓለም የተፈጠረበት ወር ያከብሩ ነበር፡፡ (ዘሌዋ 23፡24)፡፡
💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ
✍️ “ንፍሑ ቀርነ በጽዮን ወስብኩ በደብረ መቅደስየ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር እስመ ይቤ ዛቱ በዓለ እግዚአሔር” (በጽዮን ቀንደ መለከትን ንፉ፤ በመቅደሴ ተራራ ስበኩ፤ ይኸቺ ዕለት የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሏልና) በማለት የገለጻት ይኽቺ በዓል በብሉይ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት አንደኛዋ ስትኾን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ክርስቶስ ለፍርድ ሲመጣ በሊቃነ መላእክት የሚነፋውን የቀንደ መለከት ጠቋሚ ናት፡፡
💥 በተለይ ቢሊየኖች ከተመለከቱት በርኅወት ሰማይ (በሰማይ መከፈት) ከጳጉሜን 2 እሑድ ምሽት በዓሣዎች (ሑት፣ ፓይሲስ) ከተከናወነው የደም ጨረቃ ግርዶሽ ተከናወነ።
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 መስከረም 12 ለፕላኔታችን መሬት በሙላ ታላቅ ዕለት ናት፤ ይኽነን ጥበብ በዘመን ቀመሯና በፊደሏ የያዘችውና የምትምሰክረው ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፤ በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር መስከረም 12 በሌላው ዓለም አቈጣጠር ደግሞ እንደ ኹኔታው መስከረም (September) 21 ወይም 21 አንዳንዴም 22 ይኾናል።
🌟 በዚኽ ቀን ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀኑና ሌሊቱ በመላው ዓለም እኩል የሚኾንበት ወቅት “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው" (የመፀው እኩሌ (Autumnal /fall equinox) ይባላል፡፡
🌟 ይኽ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ መፀው የሚዠምርበት ዕለት ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡
🌟 የኢትዮጵያ ዐዲሱ ዓመት መግቢያ “መስከረም” ከኾነባቸው በርካታ ምክንያት ውስጥም አንደኛው በ182 ቀን አንዴ “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው” (የመፀው የቀንና የሌሊት መተካከል) (Autumnal /fall equinox) የሚኾንበት ወርም ጭምር በመኾኑ ነው፡፡
🌟 መጽሐፍ ስንክሳርም የዓመቱ መዠመሪያ ስለኾነው የመስከረም ወር እንዲኽ ይተነትነዋል፡-
✍️ “ወርኃ መስከረም ቡሩክ ርእሰ አውራኅ ዓመታት ዘግብጽ ወኢትዮጵያ ሰዓተ መዓልቱ ፲ወ፪ቱ ዕሩይ ምስለ ሌሊቱ ወእምዝ የሐጽጽ”
(የተባረከ የመስከረም ወር የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመታት ወሮች ራስ ነው፤ የቀኑ ሰዓትም ከሌሊቱ ሰዓት የተስተካከለ ዐሥራ ኹለት ነው፤ ከዚኽ በኋላ እያነሰ ይኼዳል) በማለት የመፀው እኩሌ የሚደረግበት ወር እንደኾነ አስቀምጧል፡፡
💥 91 ዕለት ከ15 ኬክሮስ የአራቱ ወቅታት የዘመን ቀመር ላለን በዲድስቅልያ 30 ላይ ✍️ “እስመ ይዔሪ መዓልት ወሌሊት አመ ዕሥራ ወኀሙሱ” (መዓልትና ሌሊት በመጋቢት 25 ይተካከላል) ይላል፡፡
🌟 አለቃ ኪዳነ ወልድ በመዝገበ ቃላታቸው ገጽ 577 ላይ ሲያብራሩ በ25 ያለው የድሮውን ነው፤ ዛሬ ግን በደቃይቅ ቊጥር 4 ቀን ወደ ታች ወርዶ “አመ ዕሥራ ወአሚሩ” (በ21) ኹኗል፡፡ በእኛ ብተት ደግሞ “አመ ዐሡሩ ወሠሉሱ ወይም ወረቡዑ” (በ12 ወይም በ13) ይኾናል ብለዋል፡፡
ኹለተኛው በ182 ቀን የሚኾነው የቀንና ሌሊት መተካከል
🌟 በኢትዮጵያ አቈጣጠር መጋቢት 12 በፈረንጆች ደግሞ መጋቢት (ማርች 20 ወይም 21) ላይ የሚውለው እና ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚኾንበት ጊዜ (ወቅት) “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘጸደይ” (የጸደይ የቀንና ሌሊት መተካከል) (Vernal/spring equinox) ይባላል፡፡
🌟 ይኽ ዕለት ፀሓይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ሰሜን አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን ለሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ ላሉ ጸደይ የሚዠምሩበት ቀን ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡ በየ182 ቀናቱ የሚኾነውን የዕሪና መዓልት ወሌሊት (ኢኪውኖክስ) ሳይንስን በሚገባ በመረዳታቸው ነበር ይኽነን መተካከል የሚደረግበት ሌላኛውን ወር “መጋቢት” ብለው ሠይመውታል፡፡
🌟 መጋቢት የሚለው ቃል “መግቦ መግቦት” ከሚለው የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የወጣ ቃል ሲኾን ትርጒሙም የመዓልትና የሌሊት ምግብና እንደ መስከረም ትክክል የሚኾንበት ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚመጋገብበት ወርኀ ዕሪና (የመተካከል ወር) ማለት ነው፡፡
💥 በኢትዮጵያ የሥነ ከዋክብት ትምህርት በ12ቱ ወራት የስፍረ ሰዓት የሠንጠረዥ ትምህርት ላይ የመስረምና የመጋቢት ወር ሠንጠረዥ አንድ ሲኾን ቀኑና ሌሊቱ 12 ዐሥራ ኹለት ነው፡፡በምድር ወገብ በየትኛውም ወቅት ቢኾን የሰዓተ መዓልቱ ጊዜ በዚኽ ዕለት 12 ሰዓታት ያኽል ነው፡፡
🌟 ከመጋቢት እኩሌ (March equinox) እስከ መስከረም እኩሌ (September equinox)፤ ፀሓይ በ23.5° ዲግሪ በሰሜን ምሥራቅ በኩል በመውጣት በ23.5° ዲግሪ በሰሜን ምዕራብ በኩል ትጠልቃለች፡፡
🌟 ከመስከረም እኩሌ እስከ መጋቢት እኩሌ፤ ፀሓይ በ23.5° ዲግሪ በደቡብ ምሥራቅ በኩል በመውጣት፤ በ23.5° ዲግሪ በደቡብ ምዕራብ በኩል ትጠልቃለች፡፡
🌟 በመጋቢት እና በመስከረም (ኹለቱ እኩሌዎች) የመዓልቱ ርዝማኔ 12 ሰዓታት ያኽል ነው፡፡ይኽነን ጥበብ በታላቁ የፊደል ቀመራችን ውስጥ በጥበብ ተሠናሥሎ ተዋሕዶና ተጋምዶ የተቀመጠባት ብቸኛዋ የምድራችን ሀገር ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፡፡
💥 ከፊደል [አ] እስከ ፊደል [ፐ] ከላይ ወደ ታች የተደረደሩት 26ት የግእዝ ፊደላት ናቸው፡፡
☄️ወደ ጐን ያሉት [አ] [ቡ] [ጊ] [ዳ] [ሄ] [ው] [ዞ] ደግሞ 7 ናቸው፡፡
☄️ በአጠቃላይ ለማወቅ 26 × 7 =182 ይኾናሉ፡፡
☄️ ይኸውም 365 የዓመት ቀናት ÷ 2 = 182.5 በመምጣት የዓመቱን የግማሽ ዕለት ቀመርን ፊደላቱ ይዘዋል፡፡ በምንኖርባት ምድር ላይ በግእዝ ፊደላችን ቊጥር ልክ በየ182ት ቀናት የሚከሰቱትን፡-
💥 ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው
💥 ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘጸደይ
ናቸው፡፡
🌟 በዚኽች ቀንና ሌሊቷ እኩል በሚኾንበት ሰኞ መስከረም 12 በ2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ רֹאשׁ הַשָּׁנָה የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡
☄️ በዕብራውያን ትውፊትና በቤዛንታይን ባሉት ኹሉ ትውፊት “ልደተ ዓለም” (ዓለም የተፈጠረበት ወር) Έτη Γενέσεως Κόσμου κατά 'Ρωμαίους ተብሎ ይታሰባል፡፡
https://orthochristian.com/97046.html
💥 እንደ አለቃ ኪዳነ ወልድ ትንታኔ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ቀዳማዊ ወር ኤታኒም ነበር በኋላ ግን ከግብጽ የወጡበት ኔሣን (ሚያዝያ) ስለነበር “ዝንቱ ወርኅ ይኩንክሙ ቀዳማየ አውራኅ” (ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችኊ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችኊ) ተብለው በእነርሱ የጥቅምትን ቅድምና ለሚያዝያ የሚያዝያን 7ተኛነት ለጥቅምት (በእኛ ለመስከረም) እንዲሰጡ ታዘው ነበር ይላሉ (ዘፀ 12፡2)።
💥 እስራኤላውያን ከግብጽ የወጡበትን ሚያዝያን ዐዲስ ዓመታቸውን እንዲያከብሩ ቢታዘዙም ግን ዓለም የተፈጠረበትን የኤታኒም 7ተኛ ወርን እንዲያከብሩ፡-
✍️ “አመ ርእሰ ሳብዕ ሠርቀ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ” (በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችኊ) ተብለው ታዘው ነበርና ቀንደ መለከት እየነፉ ዓለም የተፈጠረበት ወር ያከብሩ ነበር፡፡ (ዘሌዋ 23፡24)፡፡
💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ
✍️ “ንፍሑ ቀርነ በጽዮን ወስብኩ በደብረ መቅደስየ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር እስመ ይቤ ዛቱ በዓለ እግዚአሔር” (በጽዮን ቀንደ መለከትን ንፉ፤ በመቅደሴ ተራራ ስበኩ፤ ይኸቺ ዕለት የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሏልና) በማለት የገለጻት ይኽቺ በዓል በብሉይ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት አንደኛዋ ስትኾን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ክርስቶስ ለፍርድ ሲመጣ በሊቃነ መላእክት የሚነፋውን የቀንደ መለከት ጠቋሚ ናት፡፡
💥 በተለይ ቢሊየኖች ከተመለከቱት በርኅወት ሰማይ (በሰማይ መከፈት) ከጳጉሜን 2 እሑድ ምሽት በዓሣዎች (ሑት፣ ፓይሲስ) ከተከናወነው የደም ጨረቃ ግርዶሽ ተከናወነ።
Orthodox Christianity
Byzantine Creation Era Calendar
According to the Church's calendar, developed during the Byzantine period and based on Biblical chronologies, September 1/14 marks the beginning of the ecclesiastical year. Specifically, September 1/14, 2016 marks the beginning of the year 7525 from the creation…
❤93👍9
💥 መስከረም 11/1/2018 (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ቀመር ከተከናወነው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ በሰንቡላ (ቪርጎ) ከታየ በኋላ፤ መላው ዓለም ቀንና ሌሊቱ እኩለ በሚኾንበት መስከረም 12 ዕለት በዋለው በሮሽ ሀሻናህ ዕለት 100 ጥንታዊ የኾኑ ቀንደ መለከት በኢየሩሳሌም ሲነፉ ለመጀመሪያ ጊዜ መላው ዓለም የቀጥታ ሥርጭት እንዲተላለፍ መወሰኑ እንዲኾን መደረጉ እንዲኹ የኾነ አይደለም። በዓለማችን ታላቅ ጉዳይና አንድ ታላቅ የትንቢት ቀጠሮ ጊዜ በጊዜያችን እንደተቃረበ አመላካች ሊኾን ይችላልና በጣም ብዙ ያልተጠበቁ ክንውኖች በዜናም ይኹን በሌላ በሚቀጥሉት ጊዜያቶች ልናይ እንደምንችል በመረዳት ኅሊናችንን ሰብሰብ ማረግ ጥሩ ነው፡፡
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ 11/1/2018 ዓ.ም. (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ተጻፈ
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ 11/1/2018 ዓ.ም. (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ተጻፈ
❤118👍29
💥የመስከረም ወር ሙሉ ጨረቃ እና የሴቶች አበባ
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ዛሬ ማግሰኞ መስከረም 27 የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት የመስከረም ወር የመጀመሪያዋ ሙሉ ጨረቃ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 12፡26 ጀምራ በመውጣት ጠፈሩን አድምቃው አምሽታ ታነጋለች፡፡
🌚 ያለፈው ዓመት የ2017 ዓ.ም. የመጨረሻዋ ሙሉ ጨረቃ በሙሉ የደም ጨረቃ ግርዶሽን ጳጉሜን 2 ሸኝተን የዐዲሱን ዓመት የ2018 ዓ.ም. ደማቅ፣ ውብ፣ ያማረች ጨረቃን በዛሬው ምሽት የምናያት ይኾናል፡፡
💥 እንደሚታወቀው ክረምቱን መስከረም 25 ሸኝተን መስከረም 26 ላይ ዘመነ መፀውን ተቀብለናል፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ የመፀው ወቅት ከመስከረም 26 እስከ ታኅሣሥ 25 ያለው ሲኾን የነፋስ ወቅትም ይባላል፡፡
🌺 መፀው የሚለውን የግእዝ ቃል ወደ ዐማርኛ ሲፈታ “መፀወ” ማለት (ጸገየ፣ ጼነወ፣ መጠወ) “አበበ 🌼 ፣ አበባ ያዘ 🌸 ፣ የአበባ መዐዛ ሸተተ 💐 ” ማለት ነውና ወርኀ ጽጌ፣ ዘመነ ጽጌ (የአበባ ወር፣🌸 የአበባ ዘመን🌻) ማለት ነው፡፡
🌾 ታዲያ በዚኽ የአበባ ወቅትና በመስከረም የዐዲሱ ዓመት የመዠመሪያ ሙሉ ጨረቃን ከሴቶች 🤰ተፈጥሯዊ ኩነት ጋር “ማዛሮት” የሚለው መጽሐፌ ገጽ 312 ላይ ያለውን አጋራችኋለኊ፡፡
💥 ኢትዮጵያን ጨምሮ የጥንት ሥልጡን ሕዝቦች የሴቶች የወርኀዊ ደምና 🌺 ጨረቃ ግንኙነት እንዳላቸው ይገልጹ ነበር፡፡ በእኛም አጠራር “የወር አበባ” ማለት “የጨረቃ አበባ” ማለት ነው፡፡ “ወር” የሚለው የዐማርኛ ቃል “ወርኅ” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲኾን ፍቺውም “ጨረቃ🌛” ማለት ነው፡🌛ምክንያቱም አንድ ወር ማለት ጨረቃ ምድርን የምትዞርበትና የጨረቃ ሰሌዳዎች (phases) የሚቀያየሩበት የ29.5 ቀናት ዑደት ስለኾነ “ዐውደ ወርኅ” ተብሎ በጨረቃ ተሰይሟል፡፡ 🌻 አበባ ማለት ደግሞ አንድ ተክል ካበበ ፍሬ ለመያዝ መድረሱን አመላካች እንደሆነ 🤰ሴቶቹም ፍሬ ጽንስ የሚቋጥሩበት ጊዜ መቃረቡን አመልካች ነው፡፡
🤰በእንግሊዝኛ “ሜኑስትሬሽን (menstruation) እና “ሜንስስ” (menses) የሚለው ቃል ጥንቱኑ የመጣው “ሙን፣ ሜኔ” (moon (mene)) ከሚለው የላቲንና የግሪክ ቃል ሲኾን ፍቺውም “የጨረቃ ወር የያዘ የሴቶች ዑደት” ማለት ነው፡፡
🌓 ጨረቃና የጨረቃ የሴቶች አበባ የሚለው ዑደት የተሳሰረው የቀናቱ የርዝመት አማካይ ቅርርቦች፣ የጨረቃ በየደረጃው ያሉ ሰሌዳዎቿ፣ የዑደታቱ የድርጊት ግጥጥሞሽ መሠናሠል ነው፡፡
🌓 የወር አበባ ስንል ወርኅ ማለት ጨረቃ ማለት ነውና የሴቷ ዑደት የጀመረው በመጀመሪያው ቀን እንደኾነ ብናስብ በአማካይ አብዛኛው የሴቶች ዑደቱ 28 እስከ 29 ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ነገር ግን ዐልፎ ዐልፎ በልዩነት ከ21-35 ዕለት ሊረዝም ይችላል፡፡
🌓 በተመሳሳይ መልኩ ጨረቃ መሬት ለመዞር የሚፈጅባት 27.3 ቀናት (27 ቀናት፤ ከ7 ሰዓት፤ ከ43 ደቂቃ) ሲሆን ወይም ከጠፍ ጨረቃ 🌚 ወደ ሙሉ ጨረቃ 🌝 ከዚያ መልሶ ወደ ጠፍ ጨረቃ 🌑 ለመሆን የሚፈጅባት ዑደት በ29 እና በ30 ማለትም በአማካይ 29.5 ቀናት እንደማለት ነው፡፡ ይኽንን ስናይ በአማካይ ምን ያህል የተቀራረቡ እንደኾነ እንረዳለን፡፡
👩🦱 ሌላው የሴቶች ወር አበባ (የጨረቃ አበባ) ዑደት አራት ዋና ዋና የዑደት ደረጃዎች አሉት፡፡ እነዚኽም፡-
1. ሜንስትሩአል
2. የፎሊኪውላር
3. ኦቪውሌሽን (ኦቪውላቶሪ)
4. ሉቴዬል ይባላሉ፡፡
🌝 ወደ ጨረቃ ስንመጣም አራት ታላላቅ ዋና ገጾች (4 major phases) አሏት፡፡ እነዚህም፡-
1. ጠፍ (በክ) ጨረቃ - የማትታይ ጨረቃ (new moon)
2. መንፈቀ ወርኅ - ግማሽ ጨረቃ (first quarter)
3. ምልአተ ወርኅ - ሙሉ ጨረቃ (full moon)
4. ሕፀፀ ወርኅ - የጎደለች ጨረቃ (last quarter)
🤰 እነዚህም ርስ በርሳቸው ዑደታቱ እንዴት እንደሚነጻጸሩና ተፈጥሮን አምላክ እንዴት ውብ አድርጎ እንዳያያዘው ከዚኽ ቀጥለን እንመለከታለን፡፡
🌑🤰1ኛ) ሜንስትሩአል ዑደትና የጨረቃ ልደት
🤰 በመጀመሪያው “ሜንስትሩአል ፌዝ” ጊዜ በአማካይ ከ3 እስከ 7 ቀናት የሴቶች ወርኀዊ ደም ፍሳሽ መታየት (መውጣት) ይጀምራል፡፡
🌛 ወደ ጨረቃ ስንመጣም ጠፍ ጨረቃ (new moon) ከኾነች ከአንድ አራት ቀን በኋላ ግን የተወሰነ ብርሀን ያረፈበት አካሏን በማጭድ ቅርጽ መልክ እናየዋለን፡፡ እኛም ጨረቃ ተወለደች፣ ወጣች እንላለን፡፡ ይኽንን የኹለቱንም የመታየት የመውጣት ቀንን ማነጻጸር የበለጠ እንድንረዳው ያስችላል፡፡
🤰🌓 2ኛ) ፎሊኪውላር ዑደትና ግማሽ ጨረቃ
🤰ከአንድ ሳምንት በኋላ ባለው በዚኽ የወር አበባ ዑደት ጊዜ በተለይ በሴቶች የመራቢያ ሕዋስ በአንዱ እንቁላል ማደግ የሚጀምርበት እድገቱን የሚያፋጥን ሆርሞን የሚመረትበት ጊዜ ነው፡፡
🌓 ወደ ጨረቃ ስንመጣም በተመሳሳይ መልኩ ከሰባት ቀን ወይም ከአንድ ሳምንት በኋላ ደግሞ የፀሐይ ብርሃን ያገኘው ክፍሏ ይጨምርና ግማሽ አካሏ ብርሀን ያርፍበታል በግእዝ “መንፈቀ ወርኅ” (እኩሌታ ጨረቃ) ትባላለች፡፡
ስለዚኽ ግማሽ ጨረቃ ሆና አድጋ ትታየናለች ማለት ነው፡፡ ይኽ የደረሰችበት የቅርጽ ደረጃ ደግሞ እንደ ሳይንሱ የመጀመሪያ ሩብ (first quarter) ይባላል፡፡
ይህም ምን ያህል በወር አበባና በጨረቃ ሰሌዳዎች ያለውን የዕድገት ጭማሪ ደረጃ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡
🤰💥 3ኛ) ኦቪውሌሽንና ሙሉ ጨረቃ (14ኛ ቀን)
💥 ከ2 ሳምንት በኋላ ወይም በ14ኛው ቀን ጨረቃ ከፀሓይ በተቃራኒ በኩል ትሆንና የፀሐይ ብርሃን ሙሉ ለሙሉ ሲያርፍባት ደምቃ ታበራለች፤ ይኽም ደረጃ ሙሉ ጨረቃ “ምልአተ ወርኅ” (full moon) ይባላል፡፡
🤰 በተመሳሳይ መልኩ በሴቶች የወር አበባ ዑደት 14ኛው ቀን ሴት በተለይ ፅንስ መቋጠር የምትችልበት ሲሆን በዚህ ጊዜ ከመራቢያ ሕዋሳቷ በአንዱ ያደገው እንቁላል (ፅንስ ሊሆን የሚችለው ደም) ወደ ማሕፀን ይወርዳል፡፡
ልክ እንደ ፀሓይ ምሳሌ ከወንድ ዘር ጋር ሲገናኝ ሕይወት ይጀምራል፤ ብርሃን ነፍስ ያለችው ፍሬ ጽንስ በማሕፀኗ ይቋጠራል፡፡ አበባነቱ ወደ ፍሬ ይደርሳል፡፡
🤰🌒 4ኛ) ሉቴዬልና የጨረቃ ጒድለት (ከ17-28)
🤰🌒 ከ17-28 ቀናት ባለው በዚህ የሉቴዬል የወር አበባ ዑደት ጊዜ በማሕፀን ውስጥ የሚመረተውን የሆርሞን መጠን እየቀነሰ የሚሄድበት ነው፡፡
🌛 ወደ ጨረቃ ዑደት ስንመጣ በ14ኛው ወይም በ15ኛው ቀን ሙሉ በመሆን በምሥራቅ ወጥታ ሌሊቱን ሁሉ ደምቃ ታበራለች፤ ከዚያም በተከታታይ እስከ 14 ቀን ድረስ አንድ አንድ እጅ ብርሃን እየተነሣት (እያጣች) እየጐደለች በሌሊት የመውጫዋ ጊዜ እየዘገየ ጠፍ ወደ መሆን ታዘግማለች፡፡ ይህም ሕጸጸ ወርኅ (የጨረቃ ጉድለት) ይባላል፡፡
😍 ከዚኹ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያውያኑ የሥነ ፈለክ ጥበባዊ ትምህርት ፀሓይ ከወንድ ጋር ጨረቃ ከሴት ጋር በስፋት ይነጻጸራሉ፡፡ ሴቶች ሰማይን ቢመረምሩና እንደ ጨረቃ ሳቢ ተፈጥሮን እግዚአብሔር እንደሰጣቸው ቢረዱ ኖሮ ከፍተኛ ኃይል ይኖራቸው ነበረ። ዳሩ ግን ዓለም የምታሸክመው ብዙ የማይጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ኃይላቸውን እንዲያባክኑ በማድረግ ለአንክሮ ለማድነቅ ለተዘክሮ ለማሰብ የተፈጠሩትን ፍጥረታት እንዳያስቡ በማድረግ ሙሉ ጨረቃ ኾነው እንዳይደምቁ ትፈትናቸዋለች።
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ዛሬ ማግሰኞ መስከረም 27 የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት የመስከረም ወር የመጀመሪያዋ ሙሉ ጨረቃ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 12፡26 ጀምራ በመውጣት ጠፈሩን አድምቃው አምሽታ ታነጋለች፡፡
🌚 ያለፈው ዓመት የ2017 ዓ.ም. የመጨረሻዋ ሙሉ ጨረቃ በሙሉ የደም ጨረቃ ግርዶሽን ጳጉሜን 2 ሸኝተን የዐዲሱን ዓመት የ2018 ዓ.ም. ደማቅ፣ ውብ፣ ያማረች ጨረቃን በዛሬው ምሽት የምናያት ይኾናል፡፡
💥 እንደሚታወቀው ክረምቱን መስከረም 25 ሸኝተን መስከረም 26 ላይ ዘመነ መፀውን ተቀብለናል፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ የመፀው ወቅት ከመስከረም 26 እስከ ታኅሣሥ 25 ያለው ሲኾን የነፋስ ወቅትም ይባላል፡፡
🌺 መፀው የሚለውን የግእዝ ቃል ወደ ዐማርኛ ሲፈታ “መፀወ” ማለት (ጸገየ፣ ጼነወ፣ መጠወ) “አበበ 🌼 ፣ አበባ ያዘ 🌸 ፣ የአበባ መዐዛ ሸተተ 💐 ” ማለት ነውና ወርኀ ጽጌ፣ ዘመነ ጽጌ (የአበባ ወር፣🌸 የአበባ ዘመን🌻) ማለት ነው፡፡
🌾 ታዲያ በዚኽ የአበባ ወቅትና በመስከረም የዐዲሱ ዓመት የመዠመሪያ ሙሉ ጨረቃን ከሴቶች 🤰ተፈጥሯዊ ኩነት ጋር “ማዛሮት” የሚለው መጽሐፌ ገጽ 312 ላይ ያለውን አጋራችኋለኊ፡፡
💥 ኢትዮጵያን ጨምሮ የጥንት ሥልጡን ሕዝቦች የሴቶች የወርኀዊ ደምና 🌺 ጨረቃ ግንኙነት እንዳላቸው ይገልጹ ነበር፡፡ በእኛም አጠራር “የወር አበባ” ማለት “የጨረቃ አበባ” ማለት ነው፡፡ “ወር” የሚለው የዐማርኛ ቃል “ወርኅ” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲኾን ፍቺውም “ጨረቃ🌛” ማለት ነው፡🌛ምክንያቱም አንድ ወር ማለት ጨረቃ ምድርን የምትዞርበትና የጨረቃ ሰሌዳዎች (phases) የሚቀያየሩበት የ29.5 ቀናት ዑደት ስለኾነ “ዐውደ ወርኅ” ተብሎ በጨረቃ ተሰይሟል፡፡ 🌻 አበባ ማለት ደግሞ አንድ ተክል ካበበ ፍሬ ለመያዝ መድረሱን አመላካች እንደሆነ 🤰ሴቶቹም ፍሬ ጽንስ የሚቋጥሩበት ጊዜ መቃረቡን አመልካች ነው፡፡
🤰በእንግሊዝኛ “ሜኑስትሬሽን (menstruation) እና “ሜንስስ” (menses) የሚለው ቃል ጥንቱኑ የመጣው “ሙን፣ ሜኔ” (moon (mene)) ከሚለው የላቲንና የግሪክ ቃል ሲኾን ፍቺውም “የጨረቃ ወር የያዘ የሴቶች ዑደት” ማለት ነው፡፡
🌓 ጨረቃና የጨረቃ የሴቶች አበባ የሚለው ዑደት የተሳሰረው የቀናቱ የርዝመት አማካይ ቅርርቦች፣ የጨረቃ በየደረጃው ያሉ ሰሌዳዎቿ፣ የዑደታቱ የድርጊት ግጥጥሞሽ መሠናሠል ነው፡፡
🌓 የወር አበባ ስንል ወርኅ ማለት ጨረቃ ማለት ነውና የሴቷ ዑደት የጀመረው በመጀመሪያው ቀን እንደኾነ ብናስብ በአማካይ አብዛኛው የሴቶች ዑደቱ 28 እስከ 29 ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ነገር ግን ዐልፎ ዐልፎ በልዩነት ከ21-35 ዕለት ሊረዝም ይችላል፡፡
🌓 በተመሳሳይ መልኩ ጨረቃ መሬት ለመዞር የሚፈጅባት 27.3 ቀናት (27 ቀናት፤ ከ7 ሰዓት፤ ከ43 ደቂቃ) ሲሆን ወይም ከጠፍ ጨረቃ 🌚 ወደ ሙሉ ጨረቃ 🌝 ከዚያ መልሶ ወደ ጠፍ ጨረቃ 🌑 ለመሆን የሚፈጅባት ዑደት በ29 እና በ30 ማለትም በአማካይ 29.5 ቀናት እንደማለት ነው፡፡ ይኽንን ስናይ በአማካይ ምን ያህል የተቀራረቡ እንደኾነ እንረዳለን፡፡
👩🦱 ሌላው የሴቶች ወር አበባ (የጨረቃ አበባ) ዑደት አራት ዋና ዋና የዑደት ደረጃዎች አሉት፡፡ እነዚኽም፡-
1. ሜንስትሩአል
2. የፎሊኪውላር
3. ኦቪውሌሽን (ኦቪውላቶሪ)
4. ሉቴዬል ይባላሉ፡፡
🌝 ወደ ጨረቃ ስንመጣም አራት ታላላቅ ዋና ገጾች (4 major phases) አሏት፡፡ እነዚህም፡-
1. ጠፍ (በክ) ጨረቃ - የማትታይ ጨረቃ (new moon)
2. መንፈቀ ወርኅ - ግማሽ ጨረቃ (first quarter)
3. ምልአተ ወርኅ - ሙሉ ጨረቃ (full moon)
4. ሕፀፀ ወርኅ - የጎደለች ጨረቃ (last quarter)
🤰 እነዚህም ርስ በርሳቸው ዑደታቱ እንዴት እንደሚነጻጸሩና ተፈጥሮን አምላክ እንዴት ውብ አድርጎ እንዳያያዘው ከዚኽ ቀጥለን እንመለከታለን፡፡
🌑🤰1ኛ) ሜንስትሩአል ዑደትና የጨረቃ ልደት
🤰 በመጀመሪያው “ሜንስትሩአል ፌዝ” ጊዜ በአማካይ ከ3 እስከ 7 ቀናት የሴቶች ወርኀዊ ደም ፍሳሽ መታየት (መውጣት) ይጀምራል፡፡
🌛 ወደ ጨረቃ ስንመጣም ጠፍ ጨረቃ (new moon) ከኾነች ከአንድ አራት ቀን በኋላ ግን የተወሰነ ብርሀን ያረፈበት አካሏን በማጭድ ቅርጽ መልክ እናየዋለን፡፡ እኛም ጨረቃ ተወለደች፣ ወጣች እንላለን፡፡ ይኽንን የኹለቱንም የመታየት የመውጣት ቀንን ማነጻጸር የበለጠ እንድንረዳው ያስችላል፡፡
🤰🌓 2ኛ) ፎሊኪውላር ዑደትና ግማሽ ጨረቃ
🤰ከአንድ ሳምንት በኋላ ባለው በዚኽ የወር አበባ ዑደት ጊዜ በተለይ በሴቶች የመራቢያ ሕዋስ በአንዱ እንቁላል ማደግ የሚጀምርበት እድገቱን የሚያፋጥን ሆርሞን የሚመረትበት ጊዜ ነው፡፡
🌓 ወደ ጨረቃ ስንመጣም በተመሳሳይ መልኩ ከሰባት ቀን ወይም ከአንድ ሳምንት በኋላ ደግሞ የፀሐይ ብርሃን ያገኘው ክፍሏ ይጨምርና ግማሽ አካሏ ብርሀን ያርፍበታል በግእዝ “መንፈቀ ወርኅ” (እኩሌታ ጨረቃ) ትባላለች፡፡
ስለዚኽ ግማሽ ጨረቃ ሆና አድጋ ትታየናለች ማለት ነው፡፡ ይኽ የደረሰችበት የቅርጽ ደረጃ ደግሞ እንደ ሳይንሱ የመጀመሪያ ሩብ (first quarter) ይባላል፡፡
ይህም ምን ያህል በወር አበባና በጨረቃ ሰሌዳዎች ያለውን የዕድገት ጭማሪ ደረጃ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡
🤰💥 3ኛ) ኦቪውሌሽንና ሙሉ ጨረቃ (14ኛ ቀን)
💥 ከ2 ሳምንት በኋላ ወይም በ14ኛው ቀን ጨረቃ ከፀሓይ በተቃራኒ በኩል ትሆንና የፀሐይ ብርሃን ሙሉ ለሙሉ ሲያርፍባት ደምቃ ታበራለች፤ ይኽም ደረጃ ሙሉ ጨረቃ “ምልአተ ወርኅ” (full moon) ይባላል፡፡
🤰 በተመሳሳይ መልኩ በሴቶች የወር አበባ ዑደት 14ኛው ቀን ሴት በተለይ ፅንስ መቋጠር የምትችልበት ሲሆን በዚህ ጊዜ ከመራቢያ ሕዋሳቷ በአንዱ ያደገው እንቁላል (ፅንስ ሊሆን የሚችለው ደም) ወደ ማሕፀን ይወርዳል፡፡
ልክ እንደ ፀሓይ ምሳሌ ከወንድ ዘር ጋር ሲገናኝ ሕይወት ይጀምራል፤ ብርሃን ነፍስ ያለችው ፍሬ ጽንስ በማሕፀኗ ይቋጠራል፡፡ አበባነቱ ወደ ፍሬ ይደርሳል፡፡
🤰🌒 4ኛ) ሉቴዬልና የጨረቃ ጒድለት (ከ17-28)
🤰🌒 ከ17-28 ቀናት ባለው በዚህ የሉቴዬል የወር አበባ ዑደት ጊዜ በማሕፀን ውስጥ የሚመረተውን የሆርሞን መጠን እየቀነሰ የሚሄድበት ነው፡፡
🌛 ወደ ጨረቃ ዑደት ስንመጣ በ14ኛው ወይም በ15ኛው ቀን ሙሉ በመሆን በምሥራቅ ወጥታ ሌሊቱን ሁሉ ደምቃ ታበራለች፤ ከዚያም በተከታታይ እስከ 14 ቀን ድረስ አንድ አንድ እጅ ብርሃን እየተነሣት (እያጣች) እየጐደለች በሌሊት የመውጫዋ ጊዜ እየዘገየ ጠፍ ወደ መሆን ታዘግማለች፡፡ ይህም ሕጸጸ ወርኅ (የጨረቃ ጉድለት) ይባላል፡፡
😍 ከዚኹ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያውያኑ የሥነ ፈለክ ጥበባዊ ትምህርት ፀሓይ ከወንድ ጋር ጨረቃ ከሴት ጋር በስፋት ይነጻጸራሉ፡፡ ሴቶች ሰማይን ቢመረምሩና እንደ ጨረቃ ሳቢ ተፈጥሮን እግዚአብሔር እንደሰጣቸው ቢረዱ ኖሮ ከፍተኛ ኃይል ይኖራቸው ነበረ። ዳሩ ግን ዓለም የምታሸክመው ብዙ የማይጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ኃይላቸውን እንዲያባክኑ በማድረግ ለአንክሮ ለማድነቅ ለተዘክሮ ለማሰብ የተፈጠሩትን ፍጥረታት እንዳያስቡ በማድረግ ሙሉ ጨረቃ ኾነው እንዳይደምቁ ትፈትናቸዋለች።
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
❤119👍21🔥7
🌒 ይኽነን በስፋት በሌላ ጊዜ የምጽፍላችኍ ሲኾን በዛሬው መስከረም 27 ምሽት ላይ ጨረቃን በማየት ተፈጥሮን በማድነቅ የፍጥረታት ፈጣሪ እግዚአብሔርን በማመስገን ወራችኹ በሙሉ እንደ ሙሉዋ ጨረቃ የበራ፣ የደመቀ እንዲኾን በመማፀን የምታነሡትን ፎቶዎች ደግሞ በቴሌግራም ቻናሌ https://t.me/Rodas9 እና https://t.me/+xN518gdGKvswNzE0
ላይ እንድታጋሩኝ እጠይቃለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
መስከረም 27/ 2018 ዓ.ም.
ላይ እንድታጋሩኝ እጠይቃለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
መስከረም 27/ 2018 ዓ.ም.
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
❤122👍21🔥6👏3👎1