ነሐሴ 10 የ10ኛ ቀን ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
https://www.youtube.com/watch?v=i36w-730gOk
https://www.youtube.com/watch?v=i36w-730gOk
YouTube
ነሐሴ 10 የ10ኛ ቀን ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤119👏6
💥 ጳጉሜን 2 የደም ጨረቃ በኢትዮጵያ ሊታይ ነው
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መነበብ የሚገባው ወቅታዊ)
💥 ታላቅ ክብር ባላት በ13ኛ ወራችን በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. እሑድ ማታ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ በዐይናቸው ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃን ያያሉ፡፡
💥 ከ6 ዓመታት በፊት በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ በተዘጋጀው አንድሮሜዳ መጽሐፍ ገጽ 193 ላይ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. ላይ በኢትዮጵያ በላስታ ላሊበላ ስለሚከሰተው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ እና ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በሙሉ ስለሚታየው የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ (የጨረቃ ደም መስሎ መታየት) ላይ አስቀድሞ እንደተገለጸ ይታወቃል፡፡
💥 በዓመት ውስጥ 13 ሙሉ ጨረቃዎች ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ሀገራት 13ኛ ወራቸውን በማጥፋታቸው በ12 ወራት ውስጥ 13ኛ ሙሉ ጨረቃ ይከሰትባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ግን ትክክለኛዋን የጳጉሜን 13ኛ ወራትን በመያዙ 13 የዓመቱ ሙሉ ጨረቃዎችን በአንድ ዓመት ውስጥ እናያለን፡፡
💥 ታላቅ የዘመን ቀመርን፣ አስደናቂ ፊደላትን፣ የራሳችን ዜማ፣ ድንቆች ባህሎችን፣ ድንቅ መልክአ ምድርን አስተባብራ የያዘችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ለመውረርና በራሳቸው ማንነት ለመቀየር ሮማውያን አህጉር አቋርጠው ቢመጡም በብዙ መሥዋዕትነት በ1888 ዓ.ም. በዐድዋ ላይ አባቶቻችን እናቶቻችን ዋጋ ከፍለው ድል በመንሣት ሙሉ ክብራችንን አስጠብቀውልን ታሪክን በወርቅ ቀለም ጽፈው ለመላው ጥቁር ሕዝቦች አብሪ ብርሃን ኾነው የዘመን ቀመራችን ወደ ሮማ ሳያፈልሱ በክብር ዐልፈዋል፡፡
💥 አኹንም በዚኽች ድንቅ የጳጒሜን ወር አፍሪካውያን፣ አውስትራሊያ፣ በእስያ ያሉ የጨረቃ ግርዶሽን በማየት ምሽታቸውን ያሳልፋሉ፡፡
💥 በመኾንም ውድ ኢትጵያውያን ጳጉሜን 2 ምሽታችኹን ከጨረቃ ግርዶሽ ጋር በማድረግ በሕይወታችኍ የማትረሱትን የደም ጨረቃን በዐይናችኍ በማየት ድንቅ ምሽት እንድታደርጉ መልእክቴን በማስተላለፍ በተለይ ደመና በአካባቢያችኍ ከሌለ በግልጽ የሚታይ ሲኾን በዚኽ 13ኛ የሙሉ ጨረቃ ዕለት የሚከሰተውን የሰማይ መርሐ ግብር ለመከታተል እንድትችሉ ሰዓቱን ከዚኽ በታች አስቀምጬላችኋለኊ፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡21 (6:21 PM) - ደማቋ ሙሉዋ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ መውጣት ትጀምራለች፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትዠምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ዠምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
👉 በመጨረሻዋ 13 ወራችን በርኅወተ ሰማይ በጳጉሜን 2 የዚኽ የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ መታየቱ እና የጨረቃ ደም መምሰል ያለው ሳይንሳዊ፣ ኢትጵያዊ ዕውቀት፣ ሃይማኖታዊ፣ ምልክትና መጻኢ ጉዳይ ዙሪያ በዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ፣ በመምህር መስፍን ሰሎሞን የቀረበውን ሰፊና ጥልቅ ትንተና ለማየትና ለማድመጥ በዚኽ ሊንክ ከፍተው ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=nIaFrhIfSIcfc6H9
👉 በመኾኑም ይኽነን ቪዲዮና ጽሑፍ ለኹሉም ሼር በማድረግ በዕለቱ ያለውን ክስተት በመላ ኢትዮጵያ ስለሚታይ ኹሉም ኢትዮጵያውን ከቤታቸው ወጥተው በሰዓቱ ክስተቱን እንዲመለከቱና ጨረቃ ደም መስላ ስትታይ እንዳይደናገጡ መልእክቴን አስተላልፋለኍ፡፡
💥 እኔ ከሥራ ባልደረቦቼ እና ከጓደኞቼ ጋር የማይረሳ በዕለቱ ታላቅ የምሽት መርሐ ግብር የምናደርግ ሲኾን እናንተም ከቤተሰቦቻችኊ፣ ከጓደኞቻችኍ ጋር ክስተቱን በማየት እንድታሳልፉ ምክሬን በማቅረብ የደም ጨረቃን (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽን) በዐይን ማየት ምንም የሚያስከትለው የጤንነት ችግር ስለሌለው ምንም አሳሳቢ ነገር ስለሌለ በተጠቀሰው ሰዓት ባላችኹበት አካባቢ ደመና ከሌለ በሚገባ ማየት ትችላላችኍ፡፡
💥 በዕለቱም ካላችኹበት ቦታ የማስታወሻ ፎቶዎችን በመነሣት በሶሻል ሚዲያዎች እንድታጋሩን በማሳሰብ መጪው 2018 ዓ.ም. ለኹላችኹም የበረከት፣ የምሕረት፣ የከፍታ እንዲኾንላችኍ ከአኹኑ እመኛለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም.)
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መነበብ የሚገባው ወቅታዊ)
💥 ታላቅ ክብር ባላት በ13ኛ ወራችን በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. እሑድ ማታ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ በዐይናቸው ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃን ያያሉ፡፡
💥 ከ6 ዓመታት በፊት በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ በተዘጋጀው አንድሮሜዳ መጽሐፍ ገጽ 193 ላይ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. ላይ በኢትዮጵያ በላስታ ላሊበላ ስለሚከሰተው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ እና ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በሙሉ ስለሚታየው የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ (የጨረቃ ደም መስሎ መታየት) ላይ አስቀድሞ እንደተገለጸ ይታወቃል፡፡
💥 በዓመት ውስጥ 13 ሙሉ ጨረቃዎች ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ሀገራት 13ኛ ወራቸውን በማጥፋታቸው በ12 ወራት ውስጥ 13ኛ ሙሉ ጨረቃ ይከሰትባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ግን ትክክለኛዋን የጳጉሜን 13ኛ ወራትን በመያዙ 13 የዓመቱ ሙሉ ጨረቃዎችን በአንድ ዓመት ውስጥ እናያለን፡፡
💥 ታላቅ የዘመን ቀመርን፣ አስደናቂ ፊደላትን፣ የራሳችን ዜማ፣ ድንቆች ባህሎችን፣ ድንቅ መልክአ ምድርን አስተባብራ የያዘችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ለመውረርና በራሳቸው ማንነት ለመቀየር ሮማውያን አህጉር አቋርጠው ቢመጡም በብዙ መሥዋዕትነት በ1888 ዓ.ም. በዐድዋ ላይ አባቶቻችን እናቶቻችን ዋጋ ከፍለው ድል በመንሣት ሙሉ ክብራችንን አስጠብቀውልን ታሪክን በወርቅ ቀለም ጽፈው ለመላው ጥቁር ሕዝቦች አብሪ ብርሃን ኾነው የዘመን ቀመራችን ወደ ሮማ ሳያፈልሱ በክብር ዐልፈዋል፡፡
💥 አኹንም በዚኽች ድንቅ የጳጒሜን ወር አፍሪካውያን፣ አውስትራሊያ፣ በእስያ ያሉ የጨረቃ ግርዶሽን በማየት ምሽታቸውን ያሳልፋሉ፡፡
💥 በመኾንም ውድ ኢትጵያውያን ጳጉሜን 2 ምሽታችኹን ከጨረቃ ግርዶሽ ጋር በማድረግ በሕይወታችኍ የማትረሱትን የደም ጨረቃን በዐይናችኍ በማየት ድንቅ ምሽት እንድታደርጉ መልእክቴን በማስተላለፍ በተለይ ደመና በአካባቢያችኍ ከሌለ በግልጽ የሚታይ ሲኾን በዚኽ 13ኛ የሙሉ ጨረቃ ዕለት የሚከሰተውን የሰማይ መርሐ ግብር ለመከታተል እንድትችሉ ሰዓቱን ከዚኽ በታች አስቀምጬላችኋለኊ፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡21 (6:21 PM) - ደማቋ ሙሉዋ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ መውጣት ትጀምራለች፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትዠምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ዠምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
👉 በመጨረሻዋ 13 ወራችን በርኅወተ ሰማይ በጳጉሜን 2 የዚኽ የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ መታየቱ እና የጨረቃ ደም መምሰል ያለው ሳይንሳዊ፣ ኢትጵያዊ ዕውቀት፣ ሃይማኖታዊ፣ ምልክትና መጻኢ ጉዳይ ዙሪያ በዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ፣ በመምህር መስፍን ሰሎሞን የቀረበውን ሰፊና ጥልቅ ትንተና ለማየትና ለማድመጥ በዚኽ ሊንክ ከፍተው ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=nIaFrhIfSIcfc6H9
👉 በመኾኑም ይኽነን ቪዲዮና ጽሑፍ ለኹሉም ሼር በማድረግ በዕለቱ ያለውን ክስተት በመላ ኢትዮጵያ ስለሚታይ ኹሉም ኢትዮጵያውን ከቤታቸው ወጥተው በሰዓቱ ክስተቱን እንዲመለከቱና ጨረቃ ደም መስላ ስትታይ እንዳይደናገጡ መልእክቴን አስተላልፋለኍ፡፡
💥 እኔ ከሥራ ባልደረቦቼ እና ከጓደኞቼ ጋር የማይረሳ በዕለቱ ታላቅ የምሽት መርሐ ግብር የምናደርግ ሲኾን እናንተም ከቤተሰቦቻችኊ፣ ከጓደኞቻችኍ ጋር ክስተቱን በማየት እንድታሳልፉ ምክሬን በማቅረብ የደም ጨረቃን (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽን) በዐይን ማየት ምንም የሚያስከትለው የጤንነት ችግር ስለሌለው ምንም አሳሳቢ ነገር ስለሌለ በተጠቀሰው ሰዓት ባላችኹበት አካባቢ ደመና ከሌለ በሚገባ ማየት ትችላላችኍ፡፡
💥 በዕለቱም ካላችኹበት ቦታ የማስታወሻ ፎቶዎችን በመነሣት በሶሻል ሚዲያዎች እንድታጋሩን በማሳሰብ መጪው 2018 ዓ.ም. ለኹላችኹም የበረከት፣ የምሕረት፣ የከፍታ እንዲኾንላችኍ ከአኹኑ እመኛለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም.)
YouTube
ጳጉሜ 2 የደም ጨረቃን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሊመለከቱ ነው። ግርዶሹና የጳጉሜ ምልክት/ በዕለቱ ምን እናድርግ?
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤212👍50👎4🔥1
🌝 የፀሐይና የጨረቃ መጨለም በኢትዮጵያ ሰነዶች🌚
🌓 የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሊቃውንት ስለ ግርዶሽ በመርሐ ዕውር፣ በአቡሻህር ይልቁኑ በትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ ጋር ከመራቀቅ ባለፈ
በኢትዮጵያ የተከሠቱ ግርዶሾችን የመመዝገብ ልምድ ነበራቸው።
🌒 ለምሳሌ ያህል ስመ መንግሥታቸው መሲሕ ሰገድ በተባሉት በዐጼ በካፋ ዘመነ መንግሥት ስለተደረገው ግርዶሽ በታሪከ ነገሥት የብራናው ጽሑፍ ላይ፡-
🌛 “ወበስድስቱ ዓመተ መንግሥቱ አመ ሰብዑ ለመስከረም በዕለተ ሰኑይ በጊዜ ሠለስቱ ሰዓት ፀልመ ፀሓይ ወተርእዩ ከዋክብት ወተሐውኩ ኲሉ ሰብእ ወተማሕለሉ ወኮነት ከመ ቀዳሚሃ ብርህት”
(ዐጼ በካፋ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት በመስከረም ሰባት በዕለተ ሰኞ ሦስት ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች ከዋክብት ታዩ ሰው ሁሉ ታወከ፤ ለመኑ፤ ፀሓይም እንደ ቀደመው በራች) በማለት የፀሓይ ግርዶች በተገለጠ ጊዜ በተከሰተው ክስተት የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደደነገጠ ጭምር አስፍረዋል፡፡
🌒 ከደርቡሽ ጋር በተደረገው ፍልሚያ በዐጼ ዮሐንስ ዕረፍት ጊዜ ግርዶሽ እንደነበረ ታሪከ ነገሥት ሲያስረዳ፡-
☄️ “አመ አሚሩ ለመጋቢት በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት አሜሃ ኮነ ድልቅልቅ ሌሊተ ኮነ ቀትር ወጸልመ ፀሓይ ወኲሉ ዓለም ሠለስተ መዓልተ ወንጉሥ ዮሐንስ አዕረፈ ውስተ ሐይመቱ”
(መጋቢት 1 በቀዳሚት ሰንበት ዕለት ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ በቀትር ጊዜ ፀሓይ በመላው ዓለም ጨልሞ እንደ ሌሊት ሆነ፤ ንጉሥ ዮሐንስም በድንኳኑ ውስጥ ዐረፈ) ይላል፡፡
🌞 ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በባሕረ ሐሳብ መጽሐፋቸው ላይ በኢትዮጵያ በየዘመናቱ የተደረጉ ታሪኮችን ታሪከ ነገሥትንና በኢትዮጵያ ያሉ የነገሥታት ዜና መዋዕሎችን አመሳክረው በዳሰሰቡት ክፍል ላይ በኢትዮጵያ የተደረጉትን የፀሓይና የጨረቃ ግርዶሾችና የሥነ ፈለክ ክስተቶችን በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር እንዲህ አስፍረውታል፡-
🌖 ➢ በዐጼ ገላውዴዎስ (አጽናፍ ሰገድ ዘመነ መንግሥት) በ1545 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑 ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1661 ዓ.ም. ኅዳር 5 (ጥቅምት 28 የሚልም አለ) በ9 ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች፤ በዚህ ምክንያት ንጉሡ በዕለቱ ሞት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወንጀሎቹ እንዳይነኩ አዘዘ፡፡፡ ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በድጋሚ በ1672 መጋቢት 24 ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑☄️ ➢ በዐጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ዘመነ መንግሥት በ1682 ዓ.ም. ኅዳር 1 ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
🌟 ➢ በዐጼ በካፋ (ዳግማዊ እስክንድር) ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1720 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመ፡፡
🌒☄️ በዐጼ ኢያሱ (ብርሃን ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1735 ዓ.ም. ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
⛅️ ➢ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ በ1792 ዓ.ም. ተክለ ጊዮርጊስ ለስድስተኛ ጊዜ ከዙፋኑ ላይ በወጣበት ዓመት በ1792 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ጨረቃ ጨለመች፡፡
💥 ➢ በዐጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1902 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ለጥቂት ቀናት ጅራታም ኮከብ ታየ በማለት አስቀምጠውታል፡፡
🌞 በዘመናችን ደግሞ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. የቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ እንደተመዘገበ፤ የጳጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም የሙሉ ጨረቃ መጨለም (የደም ጨለማ) በክብር ይመዘገባል።
☄️ ስለ ጳጉሜን 2 ምሽት የጨረቃ ግርዶሽ ለመረዳት በዚህ YouTube ሊንክ ይመልከቱ https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=-5ZvCjFBptZTSKiP
አንድሮሜዳን ያንብቡ።
🌒 መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌓 የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሊቃውንት ስለ ግርዶሽ በመርሐ ዕውር፣ በአቡሻህር ይልቁኑ በትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ ጋር ከመራቀቅ ባለፈ
በኢትዮጵያ የተከሠቱ ግርዶሾችን የመመዝገብ ልምድ ነበራቸው።
🌒 ለምሳሌ ያህል ስመ መንግሥታቸው መሲሕ ሰገድ በተባሉት በዐጼ በካፋ ዘመነ መንግሥት ስለተደረገው ግርዶሽ በታሪከ ነገሥት የብራናው ጽሑፍ ላይ፡-
🌛 “ወበስድስቱ ዓመተ መንግሥቱ አመ ሰብዑ ለመስከረም በዕለተ ሰኑይ በጊዜ ሠለስቱ ሰዓት ፀልመ ፀሓይ ወተርእዩ ከዋክብት ወተሐውኩ ኲሉ ሰብእ ወተማሕለሉ ወኮነት ከመ ቀዳሚሃ ብርህት”
(ዐጼ በካፋ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት በመስከረም ሰባት በዕለተ ሰኞ ሦስት ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች ከዋክብት ታዩ ሰው ሁሉ ታወከ፤ ለመኑ፤ ፀሓይም እንደ ቀደመው በራች) በማለት የፀሓይ ግርዶች በተገለጠ ጊዜ በተከሰተው ክስተት የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደደነገጠ ጭምር አስፍረዋል፡፡
🌒 ከደርቡሽ ጋር በተደረገው ፍልሚያ በዐጼ ዮሐንስ ዕረፍት ጊዜ ግርዶሽ እንደነበረ ታሪከ ነገሥት ሲያስረዳ፡-
☄️ “አመ አሚሩ ለመጋቢት በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት አሜሃ ኮነ ድልቅልቅ ሌሊተ ኮነ ቀትር ወጸልመ ፀሓይ ወኲሉ ዓለም ሠለስተ መዓልተ ወንጉሥ ዮሐንስ አዕረፈ ውስተ ሐይመቱ”
(መጋቢት 1 በቀዳሚት ሰንበት ዕለት ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ በቀትር ጊዜ ፀሓይ በመላው ዓለም ጨልሞ እንደ ሌሊት ሆነ፤ ንጉሥ ዮሐንስም በድንኳኑ ውስጥ ዐረፈ) ይላል፡፡
🌞 ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በባሕረ ሐሳብ መጽሐፋቸው ላይ በኢትዮጵያ በየዘመናቱ የተደረጉ ታሪኮችን ታሪከ ነገሥትንና በኢትዮጵያ ያሉ የነገሥታት ዜና መዋዕሎችን አመሳክረው በዳሰሰቡት ክፍል ላይ በኢትዮጵያ የተደረጉትን የፀሓይና የጨረቃ ግርዶሾችና የሥነ ፈለክ ክስተቶችን በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር እንዲህ አስፍረውታል፡-
🌖 ➢ በዐጼ ገላውዴዎስ (አጽናፍ ሰገድ ዘመነ መንግሥት) በ1545 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑 ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1661 ዓ.ም. ኅዳር 5 (ጥቅምት 28 የሚልም አለ) በ9 ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች፤ በዚህ ምክንያት ንጉሡ በዕለቱ ሞት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወንጀሎቹ እንዳይነኩ አዘዘ፡፡፡ ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በድጋሚ በ1672 መጋቢት 24 ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑☄️ ➢ በዐጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ዘመነ መንግሥት በ1682 ዓ.ም. ኅዳር 1 ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
🌟 ➢ በዐጼ በካፋ (ዳግማዊ እስክንድር) ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1720 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመ፡፡
🌒☄️ በዐጼ ኢያሱ (ብርሃን ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1735 ዓ.ም. ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
⛅️ ➢ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ በ1792 ዓ.ም. ተክለ ጊዮርጊስ ለስድስተኛ ጊዜ ከዙፋኑ ላይ በወጣበት ዓመት በ1792 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ጨረቃ ጨለመች፡፡
💥 ➢ በዐጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1902 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ለጥቂት ቀናት ጅራታም ኮከብ ታየ በማለት አስቀምጠውታል፡፡
🌞 በዘመናችን ደግሞ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. የቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ እንደተመዘገበ፤ የጳጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም የሙሉ ጨረቃ መጨለም (የደም ጨለማ) በክብር ይመዘገባል።
☄️ ስለ ጳጉሜን 2 ምሽት የጨረቃ ግርዶሽ ለመረዳት በዚህ YouTube ሊንክ ይመልከቱ https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=-5ZvCjFBptZTSKiP
አንድሮሜዳን ያንብቡ።
🌒 መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
YouTube
ጳጉሜ 2 የደም ጨረቃን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሊመለከቱ ነው። ግርዶሹና የጳጉሜ ምልክት/ በዕለቱ ምን እናድርግ?
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤161👍28👏11
EOTC TV | ዕቅበተ እምነት | ጳጉሜን 2 ምን ይከሰታል || በመጋቤ ሐዲስ ሮዳ ታደሰ (ዶ/ር) #eotctv
https://youtube.com/watch?v=Y4Hiuanq4Ms&si=eYLNqdPQL7Pn9NP5
https://youtube.com/watch?v=Y4Hiuanq4Ms&si=eYLNqdPQL7Pn9NP5
YouTube
EOTC TV | ዕቅበተ እምነት | ጳጉሜን 2 ምን ይከሰታል || በመጋቤ ሐዲስ ሮዳ ታደሰ (ዶ/ር) #eotctv
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹
ተቋሙን በገንዘብ ለማገዝ፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 👉1000165122406
ዓባይ ባንክ 👉 1462319237132015
📡 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
…
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo
🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹
ተቋሙን በገንዘብ ለማገዝ፡- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 👉1000165122406
ዓባይ ባንክ 👉 1462319237132015
📡 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
…
❤74👏19👍4🔥3🥰3
የ13 ወራትና የ13 ሙሉ ጨረቃዎች ጸጋ ባለቤቶች
☄️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቀመር 13 መቼም አስገራሚ ናት፤ ብዙዎች ስለዚኽ ቊጥር ሲሰሙ ይሸበራሉ፡፡ በተለይ በምዕራቡ ዓለም ቊጥር 13 በእጅጉ ይፈራል፡፡ triskaidekaphobia (ትሪስ ካይ ዴካ ፎቢያ) ይባላል፡፡ ከተመዘገቡት የፍርሃት ዓይነቶች አንዱ ይኽ ነው፡፡
☄️ በግሪክ ቋንቋ τρεισκαίδεκα “ትሪስ” ማለት “3” “ካይ” ማለት “እና” “ዴካ” (ዐሥር) “ፎቢያ” (ፍርሃት) በአጠቃላይ የ13 ቊጥር ፍርሃት ማለት ነው፡፡
በተለይ ዐርብ እና 13 ሲገጥሙ ፍርሃቱ የሚጨምር ሲኾን የፍርሃቱ መጠሪያውም paraskevidekatriaphobia ይባላል፡፡
☄️ በምዕራቡ ዓለማት ያሉት ሀገራት እጅግ ብዙዎቹ 13ኛ ፎቅ የላቸውም፡፡ በሊፍት ሲወጣ 13ኛ ቊጥርን በመዝለል 14 ቊጥር ሲል ማየት የተለመደ ነው፡፡
☄️ ሪልስቴቶች 13ኛ ፎቅ ገዢ ስለሌላቸው 12 ኤ፤ 12 ኤም … እያሉ መሸጥ የተለመደ ነው፡፡
💥 ታላላቆች አየር መንገዶች ለምሳሌ እንደ ዩናይትድ፣ አላስካ፣ ራያኔር፣ ሉፍታንዛ፣ ፓሲፊክ፣ ሲንጋፓር ያሉ 13ኛ መቀመጫ በመዝለል 12 ብለው 14 እንደሚሉ በነዚኽ አየር መንገዶች የሚበሩ መንገደኞች ኹሉ ያውቁታል፡፡
💥 13 ቊጥር ግን ማያውያንን ጨምሮ በጥንት ሥልጡን ሕዝቦች ግን ተወዳጅ ቀመር ናት፡፡ ለምሳሌ በእስራኤል ቀመረ ፊደለ ዕብራይስጥ ፍቅር ማለት “አሀባህ” (אהבה) ሲባል በ22ቱ አሌፋት ሲቀመር (1 + 5 + 2 + 5 = 13) ይሰጣል፡፡ ☄️ በእኛም በግእዝ አልፍ ቤት ቀመረ ግእዝ “ጥበብ፣ ኤል” ይኽንኑ ቀመር ይሰጣሉ፡፡
🌓 ሴቶች በዓመት ውስጥ የሚያዩት የወርኅ አበባ የጨረቃን ዑደት ማእከል ያደረገ በመኾኑ 13 ነው - 28 ቀናት (365/28 = 13) ነው።
☄️ በግእዝ ወር የሚለው ቃል “ወርኅ” (ጨረቃ) ከሚለው ቃል የመጣ ነው፡፡ በእንግሊዝኛም menstruation መባሉ በላቲኒ ሜኔ - ሙን “ጨረቃ” ማለት ነውና ይኽነን ዑደት ማእከል ያደረገ ነው፡፡
☄️ በአፍሮ አይገባ መስቀል ላይ እንደምናየው ከጐን 6 ከጐን 6 ከላይ 1 በድምሩ 13 በማሳየት 12ቱ ሐዋርያትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመወከል፤ 13ቱን ሕማማተ መስቀል በማሳየት አስደናቂ ምሳሌን ያስነብባል፡፡
☄️ የ2017 ዓ.ም. ደግሞ በእጅጉ ልዩ የሚያደርገው ከታላቅነቷ የተነሣ ብዙ ፈተና የተነሣባት 13ኛዋ ወር ጳጒሜን 13ኛው ሙሉ ጨረቃ በዚኽች በ13ኛ ወር ላይ ማረፉ ነው፡፡
🌓 ይኸውም የ2017 ዓ.ም. 13ቱ ሙሉ ጨረቃዎች እነሆ፡-
1ኛ) መስከረም 8 🌞
2ኛ) ጥቅምት 7 🌚
3ኛ) ኅዳር 7 🌞
4ኛ) ታኅሣሥ 6 🌚
5ኛ) ጥር 5 🌞
6ኛ) የካቲት 5 🌚
7ኛ) መጋቢት 5 🌞
8ኛ ሚያዝያ 5 🌑
9ኛ) ግንቦት 4 🌞
10ኛ) ሠኔ 4 🌑
11ኛ) ሐምሌ 3 🌞
12ኛ) ነሐሴ 3 🌑
13ኛ) ጳጉሜን 2 🌓☄️☄️☄️☄️
☄️ በመፈጸም የጨረቃ መጨለም (ግርዶሽ) በምልአተ ወርኅ (በሙሉ ጨረቃ) ጊዜ ብቻ ነውና የሚኾነው ጳጕሜን 2 ተጠባቂዋ የሙሉ ጨለማ ግርዶሽን ቢሊየኖች ያዩታል፡፡ ከምሽቱ 2፡30 ጀምሮ (82 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ22 ደቂቃዎች) ሙሉ ግርዶሽ የደም ጨረቃ በርኅወተ ሰማይ ምሽት እንደነቅባታለን፡፡
☄️ በነገው የጳጉሜን 2 ምሽት ሰብሰብ ብላችኊ ይኽነን የተፈጥሮ ክስተት በማድነቅ ፎቶዎች እያነሣችኊ ለዐዲሱ ዓመት በጎ እየተመኛችኊ እንድትደሰቱበት መልእክቴን በመግለጽ የተባረከ ምሽት ለኹላችኹም እመኛለኍ፡፡
☄️ 13 ወር የፀሓይ ጸጋ ተብላ ብትደነቀው ውቧ ሀገራችንም በዚኽ ዓመት 13ኛ ሙሉ ጨረቃ በ13ኛዋ የጳጒሜን ወር ላይ በመግጠም 13 ወር የጨረቃ ጸጋ እንድንላት አስችሎናል፡፡
ጳጒሜን 2 የዓመቷን ሙሉ ጨረቃ ከግርሽዋ ጋር ካየን በኋላ የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት ሙሉ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 27 ደምቃ በምሥራቅ አድማስ ትወጣለችና ለዐዲሱ ዓመት የመስከረም 27 ሙሉ ጨረቃ በሰላም ደምቀን ያገናኘን፡፡
🌓 የነገው ሰዓት ለማወቅ
🌓 ከምሽቱ 12:21 ላይ 13ኛዋ ሙሉ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ ደምቃ ትወጣለች
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ጀምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
💥 አልፋ እግዚአብሔር ሆይ ቀጣዩ ዘመናችን ኹሉ አንተን በመውደድ፤ ሰውን ኹሉ በእውነት በመውደድ፤ ከአንተ የሚገኘው ሰላም በረከት ጸጋ ኹሉ በቅናት ሳይኾን በቅንነት ነውና ሥጋዊ ቅናትን ከልባችን አስወግደኽ፤ በጠብ ሳይኾን በአንተ ጥበብ፤ በምስጋና በምድራዊ ሰማያዊ በረከቶችኽ እየተደሰትን እንድንጓዝ ፈቃድኽ ይኹንልን። መልካም የጳጉሜን ወር።
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
☄️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ቀመር 13 መቼም አስገራሚ ናት፤ ብዙዎች ስለዚኽ ቊጥር ሲሰሙ ይሸበራሉ፡፡ በተለይ በምዕራቡ ዓለም ቊጥር 13 በእጅጉ ይፈራል፡፡ triskaidekaphobia (ትሪስ ካይ ዴካ ፎቢያ) ይባላል፡፡ ከተመዘገቡት የፍርሃት ዓይነቶች አንዱ ይኽ ነው፡፡
☄️ በግሪክ ቋንቋ τρεισκαίδεκα “ትሪስ” ማለት “3” “ካይ” ማለት “እና” “ዴካ” (ዐሥር) “ፎቢያ” (ፍርሃት) በአጠቃላይ የ13 ቊጥር ፍርሃት ማለት ነው፡፡
በተለይ ዐርብ እና 13 ሲገጥሙ ፍርሃቱ የሚጨምር ሲኾን የፍርሃቱ መጠሪያውም paraskevidekatriaphobia ይባላል፡፡
☄️ በምዕራቡ ዓለማት ያሉት ሀገራት እጅግ ብዙዎቹ 13ኛ ፎቅ የላቸውም፡፡ በሊፍት ሲወጣ 13ኛ ቊጥርን በመዝለል 14 ቊጥር ሲል ማየት የተለመደ ነው፡፡
☄️ ሪልስቴቶች 13ኛ ፎቅ ገዢ ስለሌላቸው 12 ኤ፤ 12 ኤም … እያሉ መሸጥ የተለመደ ነው፡፡
💥 ታላላቆች አየር መንገዶች ለምሳሌ እንደ ዩናይትድ፣ አላስካ፣ ራያኔር፣ ሉፍታንዛ፣ ፓሲፊክ፣ ሲንጋፓር ያሉ 13ኛ መቀመጫ በመዝለል 12 ብለው 14 እንደሚሉ በነዚኽ አየር መንገዶች የሚበሩ መንገደኞች ኹሉ ያውቁታል፡፡
💥 13 ቊጥር ግን ማያውያንን ጨምሮ በጥንት ሥልጡን ሕዝቦች ግን ተወዳጅ ቀመር ናት፡፡ ለምሳሌ በእስራኤል ቀመረ ፊደለ ዕብራይስጥ ፍቅር ማለት “አሀባህ” (אהבה) ሲባል በ22ቱ አሌፋት ሲቀመር (1 + 5 + 2 + 5 = 13) ይሰጣል፡፡ ☄️ በእኛም በግእዝ አልፍ ቤት ቀመረ ግእዝ “ጥበብ፣ ኤል” ይኽንኑ ቀመር ይሰጣሉ፡፡
🌓 ሴቶች በዓመት ውስጥ የሚያዩት የወርኅ አበባ የጨረቃን ዑደት ማእከል ያደረገ በመኾኑ 13 ነው - 28 ቀናት (365/28 = 13) ነው።
☄️ በግእዝ ወር የሚለው ቃል “ወርኅ” (ጨረቃ) ከሚለው ቃል የመጣ ነው፡፡ በእንግሊዝኛም menstruation መባሉ በላቲኒ ሜኔ - ሙን “ጨረቃ” ማለት ነውና ይኽነን ዑደት ማእከል ያደረገ ነው፡፡
☄️ በአፍሮ አይገባ መስቀል ላይ እንደምናየው ከጐን 6 ከጐን 6 ከላይ 1 በድምሩ 13 በማሳየት 12ቱ ሐዋርያትን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በመወከል፤ 13ቱን ሕማማተ መስቀል በማሳየት አስደናቂ ምሳሌን ያስነብባል፡፡
☄️ የ2017 ዓ.ም. ደግሞ በእጅጉ ልዩ የሚያደርገው ከታላቅነቷ የተነሣ ብዙ ፈተና የተነሣባት 13ኛዋ ወር ጳጒሜን 13ኛው ሙሉ ጨረቃ በዚኽች በ13ኛ ወር ላይ ማረፉ ነው፡፡
🌓 ይኸውም የ2017 ዓ.ም. 13ቱ ሙሉ ጨረቃዎች እነሆ፡-
1ኛ) መስከረም 8 🌞
2ኛ) ጥቅምት 7 🌚
3ኛ) ኅዳር 7 🌞
4ኛ) ታኅሣሥ 6 🌚
5ኛ) ጥር 5 🌞
6ኛ) የካቲት 5 🌚
7ኛ) መጋቢት 5 🌞
8ኛ ሚያዝያ 5 🌑
9ኛ) ግንቦት 4 🌞
10ኛ) ሠኔ 4 🌑
11ኛ) ሐምሌ 3 🌞
12ኛ) ነሐሴ 3 🌑
13ኛ) ጳጉሜን 2 🌓☄️☄️☄️☄️
☄️ በመፈጸም የጨረቃ መጨለም (ግርዶሽ) በምልአተ ወርኅ (በሙሉ ጨረቃ) ጊዜ ብቻ ነውና የሚኾነው ጳጕሜን 2 ተጠባቂዋ የሙሉ ጨለማ ግርዶሽን ቢሊየኖች ያዩታል፡፡ ከምሽቱ 2፡30 ጀምሮ (82 ደቂቃዎች (1 ሰዓት ከ22 ደቂቃዎች) ሙሉ ግርዶሽ የደም ጨረቃ በርኅወተ ሰማይ ምሽት እንደነቅባታለን፡፡
☄️ በነገው የጳጉሜን 2 ምሽት ሰብሰብ ብላችኊ ይኽነን የተፈጥሮ ክስተት በማድነቅ ፎቶዎች እያነሣችኊ ለዐዲሱ ዓመት በጎ እየተመኛችኊ እንድትደሰቱበት መልእክቴን በመግለጽ የተባረከ ምሽት ለኹላችኹም እመኛለኍ፡፡
☄️ 13 ወር የፀሓይ ጸጋ ተብላ ብትደነቀው ውቧ ሀገራችንም በዚኽ ዓመት 13ኛ ሙሉ ጨረቃ በ13ኛዋ የጳጒሜን ወር ላይ በመግጠም 13 ወር የጨረቃ ጸጋ እንድንላት አስችሎናል፡፡
ጳጒሜን 2 የዓመቷን ሙሉ ጨረቃ ከግርሽዋ ጋር ካየን በኋላ የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት ሙሉ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 27 ደምቃ በምሥራቅ አድማስ ትወጣለችና ለዐዲሱ ዓመት የመስከረም 27 ሙሉ ጨረቃ በሰላም ደምቀን ያገናኘን፡፡
🌓 የነገው ሰዓት ለማወቅ
🌓 ከምሽቱ 12:21 ላይ 13ኛዋ ሙሉ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ ደምቃ ትወጣለች
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ጀምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
💥 አልፋ እግዚአብሔር ሆይ ቀጣዩ ዘመናችን ኹሉ አንተን በመውደድ፤ ሰውን ኹሉ በእውነት በመውደድ፤ ከአንተ የሚገኘው ሰላም በረከት ጸጋ ኹሉ በቅናት ሳይኾን በቅንነት ነውና ሥጋዊ ቅናትን ከልባችን አስወግደኽ፤ በጠብ ሳይኾን በአንተ ጥበብ፤ በምስጋና በምድራዊ ሰማያዊ በረከቶችኽ እየተደሰትን እንድንጓዝ ፈቃድኽ ይኹንልን። መልካም የጳጉሜን ወር።
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
❤497👍77👏38🔥15😁6👎4
☄️ ሀገራቸውን ላከበሩ ምስጋና ለጉጉል አድናቂዎች ተግሣጽ🌓
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌓 ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. ላይ የተከሰተውን የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ በጣም በታላቅ መደነቅ ኹላችንም ተመልክተናል፡፡ በግርዶሹ ዙሪያ ሳይንሳዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ትውፊታዊ፣ ምልክታዊ ፍቺውን፤ ቀድመው የረቀቁ የኢትዮጵያ ሊቃውንት የተራቀቁበትን፣ ዛሬ ዓለም ከደረሰበት ጋር እያመሰጠርን በተለያዩ ሚዲያዎች ስናስተላልፍ ቆይተናል፡፡
🌓 ግርዶሹ ከተናወነ በኋላ ሀገራቸውን የሀገራቸውን ዕውቀት ያከበሩ ኹሉ ደስታቸውን ሲገልጹ እንደ ጎርጎርዮሳዊ አቆጣጠር መስከረም 4/ 1998 ዓ.ም. የተመሠረተውን 27 ዓመት ላስቆጠረውን ለጉጉል እና ሐምሌ 29/ 1958 ዓ.ም. ላይ ከተመሠረተ ገና 67 ዓመት ብቻ ላስቆጠረው ለናሳ ጠበቃ ኾነው ሲሟገቱ ሲታዩ የ4000 ዓመት የከዋክብት ዕውቀት ያላት የሀገራቸውን ዕውቀትና ጥበብ ምን ያኽል አለማወቃቸው በእጅጉ አስገራሚ ነው፡፡
🌓 እኔም የብዙ ሺ ዘመን ሥልጣኔ የብዙ ሺዎች የብራና መጻሕፍት ባለቤት የራሷ ፊደል፣ የራሷ የዘመን ቀመር፣ የራሷ ዜማ ለሺዎች ዓመታት ጠብቃ የዘመንን ዑደት ስትሰፍር ስትቆጥር የነበረችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ከ67 ዓመት ተቋም ጋር ጥቂቶች እያነጻጸሩ የሀገራቸውን ዕውቀት ሲያብጠለጥሉ ባይ ራስን ያለማወቅና ያለማክበር ውጤት ምን ያህል ጨለማ እንደኾነ ስለተሰማኝ ትንሽ ልጽፍ ወደድኹ፡፡
🌓 ለማንኛውም ጥቂት ስለ ኢትዮጵያ የሥነ ፈለክ ዕውቀት
በዓለም ታሪክ የዛሬ 4000 ዘመን ከአክናሁስ ሳባ እና ከነክህቲ ካልንሶ በመቀጠል ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1890-1871 ለ19 ዓመት ኢትዮጵያን በመራችው በንግሥት ካሲዮፕያ ጊዜ ሕብራተ ከዋክብት (Constellations) በማወቅና በመሰየም በቀደምትነት ያላችና ዛሬም በ88ቱ ሕብራተ ከዋክብት ካርታ ላይ እንደ ሀገር በብቸችኝነት የተጻፈች ኢትዮጵያ ብቻ መኾኗን ዕወቁ፤ ዐውቃችኹም አክብሯት።
☄️ ከጉጉል ውጪ ስለ ሀገራችሁ ዕውቀት የሌላችኹ ደግሞ የዛሬ 27 ዓመት የተመሠረተውን ጉጉል ተጠቅማችኹ እንድታዩ እነሆ ሊንኩ
https://starchild.gsfc.nasa.gov/docs/StarChild/questions/88constellations.html
ከፈለጋችሁ ጉጉል አድርጉ፡፡
🌓 ቀደምት አባቶቻችን ለሺዎች ዓመታት ተፈጥሮን በመመርመር በፀሓይ፣ በጨረቃ፣ በከዋክብት፣ በፈለከ ፈለካት፣ በአየረ አየራት፣ በመባርቅት፣ በነጐድጓድ፣ በ12ቱ ነፋሳት ላይ በመራቀቅ ብራና ፍቀው፣ ቀለም በጥብጠው፣ ብርዕ ቀርጸው እጅግ ድንቅ የኾኑ ዓለም የሚደመምባቸው መጻሕፍትን የጻፉ ድንቆች ናቸው፡፡
🌓 ካላቸው ታላቅ ዕውቀት የተነሣ በዘረፋ በስርቆት እየወጡ በዶክትሬት ደረጃ የሚጠኑ በሺዎች የሚቆጠሩ የውጪ ሀገራት ቤተ መጻሕፍትን ያጣበቡ የግእዝ መጻሕፍት ምስክር ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ እናታችን ዓለም የበተነውን ጳጉሜንን የጠበቀች፣ ዲዮናስዮስ በስሌት ስሕተት የጨመረውን 7 ዓመት የጠበቀች፤ ፓፕ ጎርጎርጎስ 1582 ዓ.ም. የጨመረውን 11 ዕለት ሳትጨምር ጠብቃ የያዘች፣ እስከ ሳድሲት ድረስ ተራቅቃ የዘመን ቀመሯን ለሺዎች ዘመናት አስከብራ የኖረች ስንዱ እመቤት ናት፡፡
🌓 ዓለም ለብዙ ሺሕ ዘመን አጥቶት ዕንቆቅልሽ የኾነውን የሔኖክን መጽሐፍ ጠብቃ ይዛ ዓለም ድጋሚ እንዲያገኘው ያደረገች ብቸኛ ሀገር ናት፡፡ ለማንኛውም ስለ ግርዶሽ ዕውቀት ኢትዮጵያውያኑ ተራቅቀው በመርሐ ዕውር (ባሕረ ሐሳብ)፣ አቡሻህር ላይ የሚውቁት ዕውቀት ሲኾን በመጽሐፈ ሔኖክ ላይ በእጅጉ በመራቀቅ ያያቸውን ብርሃናት እያራቀቁ በተረጎሙበት “ትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ” ላይ ለሺዎች ዓመታት ሲራቀቁበት ሲያመሰጥሩት ሲመዘግቡት ኖረዋል፤ እንጂ 67 ዓመት ያስቆጠረ ተቋም መረጃቸው አላደረጉም፡፡
🌓 ናሳ እንኳን የኒውተን የስበት ሕግና የኬፕለር ኦሪቢታል ሜካኒክስን ከመጨመር ባለፈ የጥንቱን ዕውቀት ተጠቅሞ ግርዶሽን ያሰላል እንጂ የጥንቱን ዕውቀት ገሸሽ አያደርግም፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሊቃውንት በዐውደ ፀሓይ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒትና በዐውደ ወርኅ (ጨረቃ) 354 ዕለት ከ22 ኤክሮስ፣ ከ1 ካልዒት፣ ከ37 ሣልሲት፣ ከ52 ራብዒት ያለውን 11 ዕለትና ፀሓይና ጨረቃ መንገዳቸውን ፈጽፈው በተፈጠሩበት ኆኅት እንደሚገኛኙ ስለ ግርዶሽ የኢትዮጵያ ሊቃውንት የሚያመሰጥሩትን ስለተጀመረ ተቆጠረ ስላልተፈጸመ ታተተ የሚሉት የ19 ዓመት ዑደትን 1 በመቀነስ የኢትዮጵያ ሊቃውንት 19 – 1 = 18 ዓመት ከ11 ቀናት ዑደትን ጭምር በመጠቀም በብዙ ሒሳቦች ስለ ግርዶሽ ሲያሰሉ ይኽም የሳሮስ ዑደት (Saros Cycle) በመባል ይታወቃል፡፡
🌓 ይኽነን የዐውደ አበቅቴ ዑደት በመጠቀም ለማስላት ከፈለጋችኹ ለምሳሌ ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ አይተናል፡፡ መስከረም 6/ 2036 ዓ.ም. የኀሙሱን የ128ኛ ዑደትን ማወቅ ይቻላል፡፡
☄️ ይኽ ዑደት ከ1,200 - 1,500 ዓመታት ሲገሠግሥ በውስጡ በአማካይ ከ70–80 ግርዶሾችን ያካተተ ነው፡፡ ለማንኛውም ሀገራችኹን የማታከብሩ ዓለም ኢትዮጵያን በዚህ ዕውቀቷ እንዴት እንዳከበራት ለማወቅ ጥንታዊውን ዕውቀታችንን ዓለም ከደረሰበት የሥነ ፈለክ ዕውቀት ጋር እያዋሐደ የሚተነትነውን አንድሮሜዳ ቊጥር 1 እና ቊጥር 2 አንብቡ፡፡
🌓 መጪው 2018 ዓ.ም. ጳጉሜን 2 ቀና ብለን ሰማይን እየተመለከትን እንደጀመርነው ከመሬት ወደ ሰማይ ከፍ ብለን ዓለም የሚመረምራቸው የሺዎች ዓመታት የኢትዮጵያ መጻሕፍት እኛው እየመረመርን፣ ዓለም አኹን የደረሰበትን የሳይንስ ዕውቀት ጋር እያዋሐድን ታላላቅ ሥራዎችን ለእናታችን ኢትዮጵያ በመሥራት እንድናሳልፍ ምኞቴ ነው፡፡
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌓 ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. ላይ የተከሰተውን የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ በጣም በታላቅ መደነቅ ኹላችንም ተመልክተናል፡፡ በግርዶሹ ዙሪያ ሳይንሳዊ፣ ሃይማኖታዊ፣ ትውፊታዊ፣ ምልክታዊ ፍቺውን፤ ቀድመው የረቀቁ የኢትዮጵያ ሊቃውንት የተራቀቁበትን፣ ዛሬ ዓለም ከደረሰበት ጋር እያመሰጠርን በተለያዩ ሚዲያዎች ስናስተላልፍ ቆይተናል፡፡
🌓 ግርዶሹ ከተናወነ በኋላ ሀገራቸውን የሀገራቸውን ዕውቀት ያከበሩ ኹሉ ደስታቸውን ሲገልጹ እንደ ጎርጎርዮሳዊ አቆጣጠር መስከረም 4/ 1998 ዓ.ም. የተመሠረተውን 27 ዓመት ላስቆጠረውን ለጉጉል እና ሐምሌ 29/ 1958 ዓ.ም. ላይ ከተመሠረተ ገና 67 ዓመት ብቻ ላስቆጠረው ለናሳ ጠበቃ ኾነው ሲሟገቱ ሲታዩ የ4000 ዓመት የከዋክብት ዕውቀት ያላት የሀገራቸውን ዕውቀትና ጥበብ ምን ያኽል አለማወቃቸው በእጅጉ አስገራሚ ነው፡፡
🌓 እኔም የብዙ ሺ ዘመን ሥልጣኔ የብዙ ሺዎች የብራና መጻሕፍት ባለቤት የራሷ ፊደል፣ የራሷ የዘመን ቀመር፣ የራሷ ዜማ ለሺዎች ዓመታት ጠብቃ የዘመንን ዑደት ስትሰፍር ስትቆጥር የነበረችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ከ67 ዓመት ተቋም ጋር ጥቂቶች እያነጻጸሩ የሀገራቸውን ዕውቀት ሲያብጠለጥሉ ባይ ራስን ያለማወቅና ያለማክበር ውጤት ምን ያህል ጨለማ እንደኾነ ስለተሰማኝ ትንሽ ልጽፍ ወደድኹ፡፡
🌓 ለማንኛውም ጥቂት ስለ ኢትዮጵያ የሥነ ፈለክ ዕውቀት
በዓለም ታሪክ የዛሬ 4000 ዘመን ከአክናሁስ ሳባ እና ከነክህቲ ካልንሶ በመቀጠል ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1890-1871 ለ19 ዓመት ኢትዮጵያን በመራችው በንግሥት ካሲዮፕያ ጊዜ ሕብራተ ከዋክብት (Constellations) በማወቅና በመሰየም በቀደምትነት ያላችና ዛሬም በ88ቱ ሕብራተ ከዋክብት ካርታ ላይ እንደ ሀገር በብቸችኝነት የተጻፈች ኢትዮጵያ ብቻ መኾኗን ዕወቁ፤ ዐውቃችኹም አክብሯት።
☄️ ከጉጉል ውጪ ስለ ሀገራችሁ ዕውቀት የሌላችኹ ደግሞ የዛሬ 27 ዓመት የተመሠረተውን ጉጉል ተጠቅማችኹ እንድታዩ እነሆ ሊንኩ
https://starchild.gsfc.nasa.gov/docs/StarChild/questions/88constellations.html
ከፈለጋችሁ ጉጉል አድርጉ፡፡
🌓 ቀደምት አባቶቻችን ለሺዎች ዓመታት ተፈጥሮን በመመርመር በፀሓይ፣ በጨረቃ፣ በከዋክብት፣ በፈለከ ፈለካት፣ በአየረ አየራት፣ በመባርቅት፣ በነጐድጓድ፣ በ12ቱ ነፋሳት ላይ በመራቀቅ ብራና ፍቀው፣ ቀለም በጥብጠው፣ ብርዕ ቀርጸው እጅግ ድንቅ የኾኑ ዓለም የሚደመምባቸው መጻሕፍትን የጻፉ ድንቆች ናቸው፡፡
🌓 ካላቸው ታላቅ ዕውቀት የተነሣ በዘረፋ በስርቆት እየወጡ በዶክትሬት ደረጃ የሚጠኑ በሺዎች የሚቆጠሩ የውጪ ሀገራት ቤተ መጻሕፍትን ያጣበቡ የግእዝ መጻሕፍት ምስክር ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ እናታችን ዓለም የበተነውን ጳጉሜንን የጠበቀች፣ ዲዮናስዮስ በስሌት ስሕተት የጨመረውን 7 ዓመት የጠበቀች፤ ፓፕ ጎርጎርጎስ 1582 ዓ.ም. የጨመረውን 11 ዕለት ሳትጨምር ጠብቃ የያዘች፣ እስከ ሳድሲት ድረስ ተራቅቃ የዘመን ቀመሯን ለሺዎች ዘመናት አስከብራ የኖረች ስንዱ እመቤት ናት፡፡
🌓 ዓለም ለብዙ ሺሕ ዘመን አጥቶት ዕንቆቅልሽ የኾነውን የሔኖክን መጽሐፍ ጠብቃ ይዛ ዓለም ድጋሚ እንዲያገኘው ያደረገች ብቸኛ ሀገር ናት፡፡ ለማንኛውም ስለ ግርዶሽ ዕውቀት ኢትዮጵያውያኑ ተራቅቀው በመርሐ ዕውር (ባሕረ ሐሳብ)፣ አቡሻህር ላይ የሚውቁት ዕውቀት ሲኾን በመጽሐፈ ሔኖክ ላይ በእጅጉ በመራቀቅ ያያቸውን ብርሃናት እያራቀቁ በተረጎሙበት “ትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ” ላይ ለሺዎች ዓመታት ሲራቀቁበት ሲያመሰጥሩት ሲመዘግቡት ኖረዋል፤ እንጂ 67 ዓመት ያስቆጠረ ተቋም መረጃቸው አላደረጉም፡፡
🌓 ናሳ እንኳን የኒውተን የስበት ሕግና የኬፕለር ኦሪቢታል ሜካኒክስን ከመጨመር ባለፈ የጥንቱን ዕውቀት ተጠቅሞ ግርዶሽን ያሰላል እንጂ የጥንቱን ዕውቀት ገሸሽ አያደርግም፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ሊቃውንት በዐውደ ፀሓይ 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒትና በዐውደ ወርኅ (ጨረቃ) 354 ዕለት ከ22 ኤክሮስ፣ ከ1 ካልዒት፣ ከ37 ሣልሲት፣ ከ52 ራብዒት ያለውን 11 ዕለትና ፀሓይና ጨረቃ መንገዳቸውን ፈጽፈው በተፈጠሩበት ኆኅት እንደሚገኛኙ ስለ ግርዶሽ የኢትዮጵያ ሊቃውንት የሚያመሰጥሩትን ስለተጀመረ ተቆጠረ ስላልተፈጸመ ታተተ የሚሉት የ19 ዓመት ዑደትን 1 በመቀነስ የኢትዮጵያ ሊቃውንት 19 – 1 = 18 ዓመት ከ11 ቀናት ዑደትን ጭምር በመጠቀም በብዙ ሒሳቦች ስለ ግርዶሽ ሲያሰሉ ይኽም የሳሮስ ዑደት (Saros Cycle) በመባል ይታወቃል፡፡
🌓 ይኽነን የዐውደ አበቅቴ ዑደት በመጠቀም ለማስላት ከፈለጋችኹ ለምሳሌ ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ አይተናል፡፡ መስከረም 6/ 2036 ዓ.ም. የኀሙሱን የ128ኛ ዑደትን ማወቅ ይቻላል፡፡
☄️ ይኽ ዑደት ከ1,200 - 1,500 ዓመታት ሲገሠግሥ በውስጡ በአማካይ ከ70–80 ግርዶሾችን ያካተተ ነው፡፡ ለማንኛውም ሀገራችኹን የማታከብሩ ዓለም ኢትዮጵያን በዚህ ዕውቀቷ እንዴት እንዳከበራት ለማወቅ ጥንታዊውን ዕውቀታችንን ዓለም ከደረሰበት የሥነ ፈለክ ዕውቀት ጋር እያዋሐደ የሚተነትነውን አንድሮሜዳ ቊጥር 1 እና ቊጥር 2 አንብቡ፡፡
🌓 መጪው 2018 ዓ.ም. ጳጉሜን 2 ቀና ብለን ሰማይን እየተመለከትን እንደጀመርነው ከመሬት ወደ ሰማይ ከፍ ብለን ዓለም የሚመረምራቸው የሺዎች ዓመታት የኢትዮጵያ መጻሕፍት እኛው እየመረመርን፣ ዓለም አኹን የደረሰበትን የሳይንስ ዕውቀት ጋር እያዋሐድን ታላላቅ ሥራዎችን ለእናታችን ኢትዮጵያ በመሥራት እንድናሳልፍ ምኞቴ ነው፡፡
በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
❤259👏27👍14🥰3😁1
የ2018 ዓ.ም. የአጽዋማትና የበዓላት አወጣጥ
👉 በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(እንደሚታወቀው በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዓመቱ አጽዋማትና በዓላት የሚወጣበት ሲኾን የባሕረ ሐሳብ ሊቅ በቃሉ ማውጣት ካልኾነ በንባብም ቢኾን ወጥቶ መገበሪያው የሚባረክበት ታላቅ ዕለት በመኾኑ በተለይ የባሕረ ሐሳብ መምህር በሌለባቸው እንዲያወጡበት እኔ የተማርኩትን የባሕረ ሐሳብ ዐዋጅ ከዚኽ በመቀጠል ጽፌያለኹ።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ንዌጥን በረድኤተ እግዚአብሔር ጽሒፈ ቀመረ ባሕረ ሐሳብ ዘድሜጥሮስ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ ጸሎቱ ወበረከቱ የሃሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን።
👉 ይኽ መጽሐፍ መርሐ ዕውራን፤ ባሕረ ሐሳብ ይባላል፤ መርሐ ዕውራን አለው አላዋቂዎችን መርቶ ወደ ዕውቀት የሚያደርስ ስለኾነ፤ ሐሳብ ቊጥር ነው ብፁዓን እለ ተኃድገ ሎሙ ኀጢአቶሙ ወእለ ኢኃሰበ ሎሙ ኲሎ ጌጋዮሙ እንዲል።
☄️ ባሕረ ሐሳብ አለው ባሕር እስኪለምዱት ድረስ ያስፈራል ይገርማል፤ ከለመዱት በኋላ በልብ ተኝቶ ይውሏል ይኽም መጽሐፍ እስኪለምዱት ድረስ ያስፈራል ይገርማል ከለመዱት በኋላ ብዙ ምስጢር አስታውቆ ደስ ያሰኛልና።
☄️ አንድም ባሕር ከለመዱት በኋላ ከመሠረቱ ወርዶ አሸዋ ይዞ ይወጧል፤ ይኽም መጽሐፍ ከለመዱት በኋላ ብዙ ምስጢር ያስታውቃል ያስመርምራል።
☄️ አንድም የባሕር አዟሪቱ መንገዱ ብዙ ነው የዚኽም መጽሐፍ መንገዱ ስልቱ ብዙ ነውና።
አንድም "ሐሳበ ባሕር" ይላል ባሕር ዘመን ነው "ሠፈራ ለባሕር በመሥፈርት ወደለዋ ለዓለም በመዳልው መኑ ዘአእመረ ስፍሐ ሰማይ ወዕመቀ ቀላይ" እንዲል በባሕር ውስጥ ያለውን እግዚአብሔር እንጂ ሰው እንዳያውቀው በዘመንም ኹሉ የሚደረገውን እግዚአብሔር እንጂ ሰው አያውቀውምና፤ "ኢኮነ ለክሙ ታእምሩ መዋዕለ ወአዝማነ ዘሠርዐ አብ" እንዲል፡፡
👉 ድሜጥሮስ ማለት መጽሔት ማለት ነው፤ አንድም ፀሓይ ማለት ነው ሰውን በትምህርቱ ብሩህ ያደርጋልና የድሜጥሮስ ትውልዱ ነገዱ ከአዝማደ እስክንድርያ ነው ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው? ቢሉ ያባቱ ወንድም ያጐቱ ሴት ልጅ ነበረችው አባቷ ሲሞት ልጄን ከልጅኽ አትለይብኝ አደራ ብሎት ሞተ፤ አብረው አደጉ አካለ መጠን አደረሱ ዘመኑ ሐሰተኞች የበዙበት ነበርና ርሱንም ከሌላ ብናጋባው ርሷንም ለሌላ ብንድራት ከሃይማኖት ይወጣሉ ከምግባር ያድጻሉ ሕንጻ ሃይማኖት ከሚፈርስ ሕንጻ ሥጋ ይፍረስ ርስ በርሳቸው እናጋባቸው ብለው መከሩ መክረው አልቀረ ሠርግ አደረጉ፤ ሥርዓተ ከብካቡ ሲፈጸም ሥርዓተ መርዓዊና ሥርዓተ መርዓት ያድርሱ ብለው ከጫጉላው ቤት አግብተዋቸው ኼዱ።
👉 ርሷን አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስ አነሣሥቶ ድሜጥሮስ ያንት ወንድምነት ለኔ የኔ እኅትነት ላንተ አልበቃ ብሎ የባዕድ ሥራ እንሥራ አልኽን አለችው፤ እኔስ የናት ያባቴን ፈቃድ ማፍረስ ይኾንብኛል ብዬ ነው እንጂ ፈቃዴም አይደል ፈቃድሽ ካልኾነ አንተወውምን አላት እንተወው አለችው፤ እንኪያስ የተለያየን እንደኾነ አንችን ለሌላ ወንድ እኔንም ለሌላ ሴት ያጋቡናልና መስለን እንኑር አላት እንኑር አለችው፤ በአንድ ቤት በአንድ አልጋ እየተኙ 48 ዘመን ኖሩ፤ ርሱን መልአኩ ቀኝ ክንፉን ርሷን ግራ ክንፉን እያለበሳቸው ያድራል፤ ሲነጋ በመስኮቱ በአምሳለ ርግብ ወጥቶ ሲኼድ ያዩታል ስለምን ቢሉ? በቅተዋልና አንድም በንጽሕናቸው ይትጉበት ብሎ።
👉 በዘመኑ የተሾመው ሊቀ ጳጳስ ሉክዮስ ሉክያኖስ ይባላል አረጀ ደከመ፤ ሕዝቡ ተሰብስበው አባታችን አንተ አረጀኽ ደከምኽ ካንተ ቀጥሎ የሚሾመውን ንገረን አሉት፤ እናንተም ወደ እግዚአብሔር አመልክቱ እኔም ወደ እግዚአብሔር አመለክታለኊ ብሎ ቀን ቀጥሮ ሰደዳቸው ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጣ ስሙ ድሜጥሮስ የሚባል ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ ካንተ ሊባረክ ይመጣል ካንተ ቀጥሎ የሚሾመው ርሱ ነው አለው፤ ሕዝቡም በቀጠራቸው ቀን መጡ አገኛችኹት? አላቸው እኛስ አላገኘንም አሉት እኔ አገኘኹላችኊ አላቸው፤ ስሙ ድሜጥሮስ የሚባል ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ ሊባረክ ይመጣል ከኔ ቀጥሎ የሚሾመው ርሱ ነው ለጊዜው እንቢ ይላችኋል ግድ ብላችኊ ሹሙት አላቸው፡፡
👉 ይኽም ድሜጥሮስ ተክል አጽድቆ ዕርፍ አርቆ የሚኖር ገበሬ ነበር ይላሉ፤ ከዕለታት በአንድ ቀን ተክል ለመጐብኘት ከተክል ቦታ ገብቶ ሳለ ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ አገኘ ይኽንስ ከሊቀ ጳጳሱ ወስዶ ሊባረኩበት ይገባል ብሎ በንጹሕ ዕቃ አድርጎ ይዞ ኺዶ ንገሩልኝ አለ፤ እንዲኽ ያል ይዞ የመጣ ሰው ከደጅ ቁሟል ብለው ነገሩት እንዲኽ ያል ይዞ የመጣውን ከደጅ ያቆሙታልን ያገቡታልን እንጂ ግባ በለው አለው፤ ገብቶ ተባርኳል፤ ከኔ ቀጥሎ የሚሾመው ይኽ ነው ብሏቸው ወዲያው ዐረፈ፤ ቀብረው ሲመለሱ ሕዝቡ ተሾምልን አሉት።
☄️ በማርቆስ ወንበር የሚቀመጥ የተማረ ነው ደግሞም ንጹሕ ድንግል ነው፤ እኔ እንደምታውቁኝ ሕዝባዊ ነኝ ደግሞም ሥጋዊ ነኝ እንደምን አድርጎ ይኾናል አላቸው፤ እኛስ አባታችን ያዘዘንን ትተን ሌላ አንሾምም አሉት፤ ርሱም እንደማይተውት ዐውቆ ሊቀ ጳጳሱ ሲሾም ምን ያደርግላችኊ ነበር አላቸው አንቀጸ አባግዕን አንብቦ ይተረጒምልን ነበር አሉት ወንጌል አምጡልኝ አለ፤ አመጡለት እንኳን ትርጓሜውን ንባቡን አያውቀው የነበረ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ተርጒሞላቸዋል፤ ይኽም ብቻ አይደለም ብሉይና ሐዲስ ተርጒሟል፡፡
👉 ከዚኽ በኋላ ከደጀ ሰላም ቆሞ አንተ በቅተኻል ተቀበል አንተ አልበቃኽም ቆይ እያለ ከልክሏቸዋል፤ ሕዝቡም ቆንጆ ሚስቱን ከቤቱ አስቀምጦ እኛን ይከለክለናል ብለው አምተውታል፤ መልአኩም "ኢትፍቅድ አድኅኖ ርእስከ ወብእሲትከ አላ አላ አድኅኖ ሕዝብከ" አለው፤ ርሱም ዕንጨት እየያዛችኊ ተሰብሰቡ ብሎ ዐዋጅ ነገረ ምእመናኑም ዕንጨት እየያዙ ተሰበሰቡ ደመራ አሠርቶ በእሳት አቃጥሎ ልብሰ ተክህኖውን ለብሶ ሊቀድስ ገባ ጸሎተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ልብሰ ተክህኖውን እንደለበሰ በእሳቱ መኻከል እየተመላለሰ ያጥን ጀመር፤ ሚስቱም ከዚያ ነበረችና "ስፍሒ አጽፈኪ" ልብስሽን ዘርጊ አላት ዘረጋች እሳቱን እየታፈነ ከልብሷ ላይ አደረገላት ልብሷ ሳይቃጠል ቀርቷል ሕዝቡም አባታችን ይኽን ተአምራት ያደረግኸው ስለምን ነው አሉት፤ አምታችኹኝ አላቸው፤ አላበጀንም በድለናል ይቅር በለን አሉት፤ ይፍታሕ ወይኅድግ ያንጽሕ ወይስረይ ብሎ ናዟቸዋል፤ ኑዛዜ ከዚያ ወዲኽ ተጀምሯል፡፡
👉 ድሜጥሮስ በተሸመ በ27 ጌታ ባረገ በ207 ዘመን ይኽን መጽሐፍ ተናግሮታል፤ ስለምን ቢሉ ከሐዋርያት ጀምሮ እስከ ርሱ የነበሩ ምእመናን ዐቢይ ጾምን የጥምቀት ሳኒታ ጀምረው በየካቲት 21 ይፈጽሙ ነበር፤ ሕማማትንም ወአጐንድዮሙ መዋዕለ ይላል በመጋቢት ያደርጉ ነበር እንዲኽ ማድረጋቸው ተጠምቆ ጹሟል ሕማሙም በመጋቢት ነው ሲሉ፤ አጽዋማትን በዓላትን እንዳገኙ ያደርጉ ነበር፤ ርሱ ግን በዘአለበዎ መንፈስ ቅዱስ ይላል ሰኞ የሚኾነውን ከሰኞ ረቡዕ የሚኾነውን ከረቡዕ ኀሙስ የሚኾነውን ከኀሙስ ዐርብ የሚኾነውን ከዐርብ እሑድ የሚኾነውን ከእሑድ እንዳይወጣ ኢየዐርግ ኢይወርድ እየሰጠ ወስኖታል፤ አይወጣም አይናወጥም ቢናወጥስ አጽዋማት በዓላትም እንደቀድሞ በኾኑ ነበር፤ ርሱም በዘአለበዎ መንፈስ ቅዱስ ባልተባለም ነበር፡፡
👉 በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(እንደሚታወቀው በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዓመቱ አጽዋማትና በዓላት የሚወጣበት ሲኾን የባሕረ ሐሳብ ሊቅ በቃሉ ማውጣት ካልኾነ በንባብም ቢኾን ወጥቶ መገበሪያው የሚባረክበት ታላቅ ዕለት በመኾኑ በተለይ የባሕረ ሐሳብ መምህር በሌለባቸው እንዲያወጡበት እኔ የተማርኩትን የባሕረ ሐሳብ ዐዋጅ ከዚኽ በመቀጠል ጽፌያለኹ።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ንዌጥን በረድኤተ እግዚአብሔር ጽሒፈ ቀመረ ባሕረ ሐሳብ ዘድሜጥሮስ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ ጸሎቱ ወበረከቱ የሃሉ ምስሌነ ለዓለመ ዓለም አሜን።
👉 ይኽ መጽሐፍ መርሐ ዕውራን፤ ባሕረ ሐሳብ ይባላል፤ መርሐ ዕውራን አለው አላዋቂዎችን መርቶ ወደ ዕውቀት የሚያደርስ ስለኾነ፤ ሐሳብ ቊጥር ነው ብፁዓን እለ ተኃድገ ሎሙ ኀጢአቶሙ ወእለ ኢኃሰበ ሎሙ ኲሎ ጌጋዮሙ እንዲል።
☄️ ባሕረ ሐሳብ አለው ባሕር እስኪለምዱት ድረስ ያስፈራል ይገርማል፤ ከለመዱት በኋላ በልብ ተኝቶ ይውሏል ይኽም መጽሐፍ እስኪለምዱት ድረስ ያስፈራል ይገርማል ከለመዱት በኋላ ብዙ ምስጢር አስታውቆ ደስ ያሰኛልና።
☄️ አንድም ባሕር ከለመዱት በኋላ ከመሠረቱ ወርዶ አሸዋ ይዞ ይወጧል፤ ይኽም መጽሐፍ ከለመዱት በኋላ ብዙ ምስጢር ያስታውቃል ያስመርምራል።
☄️ አንድም የባሕር አዟሪቱ መንገዱ ብዙ ነው የዚኽም መጽሐፍ መንገዱ ስልቱ ብዙ ነውና።
አንድም "ሐሳበ ባሕር" ይላል ባሕር ዘመን ነው "ሠፈራ ለባሕር በመሥፈርት ወደለዋ ለዓለም በመዳልው መኑ ዘአእመረ ስፍሐ ሰማይ ወዕመቀ ቀላይ" እንዲል በባሕር ውስጥ ያለውን እግዚአብሔር እንጂ ሰው እንዳያውቀው በዘመንም ኹሉ የሚደረገውን እግዚአብሔር እንጂ ሰው አያውቀውምና፤ "ኢኮነ ለክሙ ታእምሩ መዋዕለ ወአዝማነ ዘሠርዐ አብ" እንዲል፡፡
👉 ድሜጥሮስ ማለት መጽሔት ማለት ነው፤ አንድም ፀሓይ ማለት ነው ሰውን በትምህርቱ ብሩህ ያደርጋልና የድሜጥሮስ ትውልዱ ነገዱ ከአዝማደ እስክንድርያ ነው ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው? ቢሉ ያባቱ ወንድም ያጐቱ ሴት ልጅ ነበረችው አባቷ ሲሞት ልጄን ከልጅኽ አትለይብኝ አደራ ብሎት ሞተ፤ አብረው አደጉ አካለ መጠን አደረሱ ዘመኑ ሐሰተኞች የበዙበት ነበርና ርሱንም ከሌላ ብናጋባው ርሷንም ለሌላ ብንድራት ከሃይማኖት ይወጣሉ ከምግባር ያድጻሉ ሕንጻ ሃይማኖት ከሚፈርስ ሕንጻ ሥጋ ይፍረስ ርስ በርሳቸው እናጋባቸው ብለው መከሩ መክረው አልቀረ ሠርግ አደረጉ፤ ሥርዓተ ከብካቡ ሲፈጸም ሥርዓተ መርዓዊና ሥርዓተ መርዓት ያድርሱ ብለው ከጫጉላው ቤት አግብተዋቸው ኼዱ።
👉 ርሷን አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስ አነሣሥቶ ድሜጥሮስ ያንት ወንድምነት ለኔ የኔ እኅትነት ላንተ አልበቃ ብሎ የባዕድ ሥራ እንሥራ አልኽን አለችው፤ እኔስ የናት ያባቴን ፈቃድ ማፍረስ ይኾንብኛል ብዬ ነው እንጂ ፈቃዴም አይደል ፈቃድሽ ካልኾነ አንተወውምን አላት እንተወው አለችው፤ እንኪያስ የተለያየን እንደኾነ አንችን ለሌላ ወንድ እኔንም ለሌላ ሴት ያጋቡናልና መስለን እንኑር አላት እንኑር አለችው፤ በአንድ ቤት በአንድ አልጋ እየተኙ 48 ዘመን ኖሩ፤ ርሱን መልአኩ ቀኝ ክንፉን ርሷን ግራ ክንፉን እያለበሳቸው ያድራል፤ ሲነጋ በመስኮቱ በአምሳለ ርግብ ወጥቶ ሲኼድ ያዩታል ስለምን ቢሉ? በቅተዋልና አንድም በንጽሕናቸው ይትጉበት ብሎ።
👉 በዘመኑ የተሾመው ሊቀ ጳጳስ ሉክዮስ ሉክያኖስ ይባላል አረጀ ደከመ፤ ሕዝቡ ተሰብስበው አባታችን አንተ አረጀኽ ደከምኽ ካንተ ቀጥሎ የሚሾመውን ንገረን አሉት፤ እናንተም ወደ እግዚአብሔር አመልክቱ እኔም ወደ እግዚአብሔር አመለክታለኊ ብሎ ቀን ቀጥሮ ሰደዳቸው ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጣ ስሙ ድሜጥሮስ የሚባል ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ ካንተ ሊባረክ ይመጣል ካንተ ቀጥሎ የሚሾመው ርሱ ነው አለው፤ ሕዝቡም በቀጠራቸው ቀን መጡ አገኛችኹት? አላቸው እኛስ አላገኘንም አሉት እኔ አገኘኹላችኊ አላቸው፤ ስሙ ድሜጥሮስ የሚባል ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ ይዞ ሊባረክ ይመጣል ከኔ ቀጥሎ የሚሾመው ርሱ ነው ለጊዜው እንቢ ይላችኋል ግድ ብላችኊ ሹሙት አላቸው፡፡
👉 ይኽም ድሜጥሮስ ተክል አጽድቆ ዕርፍ አርቆ የሚኖር ገበሬ ነበር ይላሉ፤ ከዕለታት በአንድ ቀን ተክል ለመጐብኘት ከተክል ቦታ ገብቶ ሳለ ያለጊዜዋ ያፈራች የወይን ዘለላ አገኘ ይኽንስ ከሊቀ ጳጳሱ ወስዶ ሊባረኩበት ይገባል ብሎ በንጹሕ ዕቃ አድርጎ ይዞ ኺዶ ንገሩልኝ አለ፤ እንዲኽ ያል ይዞ የመጣ ሰው ከደጅ ቁሟል ብለው ነገሩት እንዲኽ ያል ይዞ የመጣውን ከደጅ ያቆሙታልን ያገቡታልን እንጂ ግባ በለው አለው፤ ገብቶ ተባርኳል፤ ከኔ ቀጥሎ የሚሾመው ይኽ ነው ብሏቸው ወዲያው ዐረፈ፤ ቀብረው ሲመለሱ ሕዝቡ ተሾምልን አሉት።
☄️ በማርቆስ ወንበር የሚቀመጥ የተማረ ነው ደግሞም ንጹሕ ድንግል ነው፤ እኔ እንደምታውቁኝ ሕዝባዊ ነኝ ደግሞም ሥጋዊ ነኝ እንደምን አድርጎ ይኾናል አላቸው፤ እኛስ አባታችን ያዘዘንን ትተን ሌላ አንሾምም አሉት፤ ርሱም እንደማይተውት ዐውቆ ሊቀ ጳጳሱ ሲሾም ምን ያደርግላችኊ ነበር አላቸው አንቀጸ አባግዕን አንብቦ ይተረጒምልን ነበር አሉት ወንጌል አምጡልኝ አለ፤ አመጡለት እንኳን ትርጓሜውን ንባቡን አያውቀው የነበረ መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት ተርጒሞላቸዋል፤ ይኽም ብቻ አይደለም ብሉይና ሐዲስ ተርጒሟል፡፡
👉 ከዚኽ በኋላ ከደጀ ሰላም ቆሞ አንተ በቅተኻል ተቀበል አንተ አልበቃኽም ቆይ እያለ ከልክሏቸዋል፤ ሕዝቡም ቆንጆ ሚስቱን ከቤቱ አስቀምጦ እኛን ይከለክለናል ብለው አምተውታል፤ መልአኩም "ኢትፍቅድ አድኅኖ ርእስከ ወብእሲትከ አላ አላ አድኅኖ ሕዝብከ" አለው፤ ርሱም ዕንጨት እየያዛችኊ ተሰብሰቡ ብሎ ዐዋጅ ነገረ ምእመናኑም ዕንጨት እየያዙ ተሰበሰቡ ደመራ አሠርቶ በእሳት አቃጥሎ ልብሰ ተክህኖውን ለብሶ ሊቀድስ ገባ ጸሎተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ልብሰ ተክህኖውን እንደለበሰ በእሳቱ መኻከል እየተመላለሰ ያጥን ጀመር፤ ሚስቱም ከዚያ ነበረችና "ስፍሒ አጽፈኪ" ልብስሽን ዘርጊ አላት ዘረጋች እሳቱን እየታፈነ ከልብሷ ላይ አደረገላት ልብሷ ሳይቃጠል ቀርቷል ሕዝቡም አባታችን ይኽን ተአምራት ያደረግኸው ስለምን ነው አሉት፤ አምታችኹኝ አላቸው፤ አላበጀንም በድለናል ይቅር በለን አሉት፤ ይፍታሕ ወይኅድግ ያንጽሕ ወይስረይ ብሎ ናዟቸዋል፤ ኑዛዜ ከዚያ ወዲኽ ተጀምሯል፡፡
👉 ድሜጥሮስ በተሸመ በ27 ጌታ ባረገ በ207 ዘመን ይኽን መጽሐፍ ተናግሮታል፤ ስለምን ቢሉ ከሐዋርያት ጀምሮ እስከ ርሱ የነበሩ ምእመናን ዐቢይ ጾምን የጥምቀት ሳኒታ ጀምረው በየካቲት 21 ይፈጽሙ ነበር፤ ሕማማትንም ወአጐንድዮሙ መዋዕለ ይላል በመጋቢት ያደርጉ ነበር እንዲኽ ማድረጋቸው ተጠምቆ ጹሟል ሕማሙም በመጋቢት ነው ሲሉ፤ አጽዋማትን በዓላትን እንዳገኙ ያደርጉ ነበር፤ ርሱ ግን በዘአለበዎ መንፈስ ቅዱስ ይላል ሰኞ የሚኾነውን ከሰኞ ረቡዕ የሚኾነውን ከረቡዕ ኀሙስ የሚኾነውን ከኀሙስ ዐርብ የሚኾነውን ከዐርብ እሑድ የሚኾነውን ከእሑድ እንዳይወጣ ኢየዐርግ ኢይወርድ እየሰጠ ወስኖታል፤ አይወጣም አይናወጥም ቢናወጥስ አጽዋማት በዓላትም እንደቀድሞ በኾኑ ነበር፤ ርሱም በዘአለበዎ መንፈስ ቅዱስ ባልተባለም ነበር፡፡
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
❤86👏4👍3🥰2😁1