ቀጥታ ስርጭት የቅዳሜ ውዳሴ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ Megabe Haddis Dr Rodas (መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ)
https://www.youtube.com/watch?v=DoSIJPWZLmM
https://www.youtube.com/watch?v=DoSIJPWZLmM
YouTube
ቀጥታ ስርጭት የቅዳሜ ውዳሴ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ Megabe Haddis Dr Rodas (መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ)
with CameraFi Live
❤152🥰10👏2
ጾመ ፍልሰታ 6ኛ ቀን ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ
https://www.youtube.com/watch?v=SfG60qsbDjs
https://www.youtube.com/watch?v=SfG60qsbDjs
YouTube
ጾመ ፍልሰታ 6ኛ ቀን ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤134🥰10👏5
ነሐሴ 10 የ10ኛ ቀን ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
https://www.youtube.com/watch?v=i36w-730gOk
https://www.youtube.com/watch?v=i36w-730gOk
YouTube
ነሐሴ 10 የ10ኛ ቀን ውዳሴና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤119👏6
💥 ጳጉሜን 2 የደም ጨረቃ በኢትዮጵያ ሊታይ ነው
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መነበብ የሚገባው ወቅታዊ)
💥 ታላቅ ክብር ባላት በ13ኛ ወራችን በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. እሑድ ማታ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ በዐይናቸው ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃን ያያሉ፡፡
💥 ከ6 ዓመታት በፊት በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ በተዘጋጀው አንድሮሜዳ መጽሐፍ ገጽ 193 ላይ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. ላይ በኢትዮጵያ በላስታ ላሊበላ ስለሚከሰተው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ እና ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በሙሉ ስለሚታየው የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ (የጨረቃ ደም መስሎ መታየት) ላይ አስቀድሞ እንደተገለጸ ይታወቃል፡፡
💥 በዓመት ውስጥ 13 ሙሉ ጨረቃዎች ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ሀገራት 13ኛ ወራቸውን በማጥፋታቸው በ12 ወራት ውስጥ 13ኛ ሙሉ ጨረቃ ይከሰትባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ግን ትክክለኛዋን የጳጉሜን 13ኛ ወራትን በመያዙ 13 የዓመቱ ሙሉ ጨረቃዎችን በአንድ ዓመት ውስጥ እናያለን፡፡
💥 ታላቅ የዘመን ቀመርን፣ አስደናቂ ፊደላትን፣ የራሳችን ዜማ፣ ድንቆች ባህሎችን፣ ድንቅ መልክአ ምድርን አስተባብራ የያዘችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ለመውረርና በራሳቸው ማንነት ለመቀየር ሮማውያን አህጉር አቋርጠው ቢመጡም በብዙ መሥዋዕትነት በ1888 ዓ.ም. በዐድዋ ላይ አባቶቻችን እናቶቻችን ዋጋ ከፍለው ድል በመንሣት ሙሉ ክብራችንን አስጠብቀውልን ታሪክን በወርቅ ቀለም ጽፈው ለመላው ጥቁር ሕዝቦች አብሪ ብርሃን ኾነው የዘመን ቀመራችን ወደ ሮማ ሳያፈልሱ በክብር ዐልፈዋል፡፡
💥 አኹንም በዚኽች ድንቅ የጳጒሜን ወር አፍሪካውያን፣ አውስትራሊያ፣ በእስያ ያሉ የጨረቃ ግርዶሽን በማየት ምሽታቸውን ያሳልፋሉ፡፡
💥 በመኾንም ውድ ኢትጵያውያን ጳጉሜን 2 ምሽታችኹን ከጨረቃ ግርዶሽ ጋር በማድረግ በሕይወታችኍ የማትረሱትን የደም ጨረቃን በዐይናችኍ በማየት ድንቅ ምሽት እንድታደርጉ መልእክቴን በማስተላለፍ በተለይ ደመና በአካባቢያችኍ ከሌለ በግልጽ የሚታይ ሲኾን በዚኽ 13ኛ የሙሉ ጨረቃ ዕለት የሚከሰተውን የሰማይ መርሐ ግብር ለመከታተል እንድትችሉ ሰዓቱን ከዚኽ በታች አስቀምጬላችኋለኊ፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡21 (6:21 PM) - ደማቋ ሙሉዋ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ መውጣት ትጀምራለች፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትዠምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ዠምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
👉 በመጨረሻዋ 13 ወራችን በርኅወተ ሰማይ በጳጉሜን 2 የዚኽ የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ መታየቱ እና የጨረቃ ደም መምሰል ያለው ሳይንሳዊ፣ ኢትጵያዊ ዕውቀት፣ ሃይማኖታዊ፣ ምልክትና መጻኢ ጉዳይ ዙሪያ በዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ፣ በመምህር መስፍን ሰሎሞን የቀረበውን ሰፊና ጥልቅ ትንተና ለማየትና ለማድመጥ በዚኽ ሊንክ ከፍተው ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=nIaFrhIfSIcfc6H9
👉 በመኾኑም ይኽነን ቪዲዮና ጽሑፍ ለኹሉም ሼር በማድረግ በዕለቱ ያለውን ክስተት በመላ ኢትዮጵያ ስለሚታይ ኹሉም ኢትዮጵያውን ከቤታቸው ወጥተው በሰዓቱ ክስተቱን እንዲመለከቱና ጨረቃ ደም መስላ ስትታይ እንዳይደናገጡ መልእክቴን አስተላልፋለኍ፡፡
💥 እኔ ከሥራ ባልደረቦቼ እና ከጓደኞቼ ጋር የማይረሳ በዕለቱ ታላቅ የምሽት መርሐ ግብር የምናደርግ ሲኾን እናንተም ከቤተሰቦቻችኊ፣ ከጓደኞቻችኍ ጋር ክስተቱን በማየት እንድታሳልፉ ምክሬን በማቅረብ የደም ጨረቃን (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽን) በዐይን ማየት ምንም የሚያስከትለው የጤንነት ችግር ስለሌለው ምንም አሳሳቢ ነገር ስለሌለ በተጠቀሰው ሰዓት ባላችኹበት አካባቢ ደመና ከሌለ በሚገባ ማየት ትችላላችኍ፡፡
💥 በዕለቱም ካላችኹበት ቦታ የማስታወሻ ፎቶዎችን በመነሣት በሶሻል ሚዲያዎች እንድታጋሩን በማሳሰብ መጪው 2018 ዓ.ም. ለኹላችኹም የበረከት፣ የምሕረት፣ የከፍታ እንዲኾንላችኍ ከአኹኑ እመኛለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም.)
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መነበብ የሚገባው ወቅታዊ)
💥 ታላቅ ክብር ባላት በ13ኛ ወራችን በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. እሑድ ማታ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ በዐይናቸው ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃን ያያሉ፡፡
💥 ከ6 ዓመታት በፊት በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ በተዘጋጀው አንድሮሜዳ መጽሐፍ ገጽ 193 ላይ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. ላይ በኢትዮጵያ በላስታ ላሊበላ ስለሚከሰተው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ እና ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በሙሉ ስለሚታየው የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ (የጨረቃ ደም መስሎ መታየት) ላይ አስቀድሞ እንደተገለጸ ይታወቃል፡፡
💥 በዓመት ውስጥ 13 ሙሉ ጨረቃዎች ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ሀገራት 13ኛ ወራቸውን በማጥፋታቸው በ12 ወራት ውስጥ 13ኛ ሙሉ ጨረቃ ይከሰትባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ግን ትክክለኛዋን የጳጉሜን 13ኛ ወራትን በመያዙ 13 የዓመቱ ሙሉ ጨረቃዎችን በአንድ ዓመት ውስጥ እናያለን፡፡
💥 ታላቅ የዘመን ቀመርን፣ አስደናቂ ፊደላትን፣ የራሳችን ዜማ፣ ድንቆች ባህሎችን፣ ድንቅ መልክአ ምድርን አስተባብራ የያዘችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ለመውረርና በራሳቸው ማንነት ለመቀየር ሮማውያን አህጉር አቋርጠው ቢመጡም በብዙ መሥዋዕትነት በ1888 ዓ.ም. በዐድዋ ላይ አባቶቻችን እናቶቻችን ዋጋ ከፍለው ድል በመንሣት ሙሉ ክብራችንን አስጠብቀውልን ታሪክን በወርቅ ቀለም ጽፈው ለመላው ጥቁር ሕዝቦች አብሪ ብርሃን ኾነው የዘመን ቀመራችን ወደ ሮማ ሳያፈልሱ በክብር ዐልፈዋል፡፡
💥 አኹንም በዚኽች ድንቅ የጳጒሜን ወር አፍሪካውያን፣ አውስትራሊያ፣ በእስያ ያሉ የጨረቃ ግርዶሽን በማየት ምሽታቸውን ያሳልፋሉ፡፡
💥 በመኾንም ውድ ኢትጵያውያን ጳጉሜን 2 ምሽታችኹን ከጨረቃ ግርዶሽ ጋር በማድረግ በሕይወታችኍ የማትረሱትን የደም ጨረቃን በዐይናችኍ በማየት ድንቅ ምሽት እንድታደርጉ መልእክቴን በማስተላለፍ በተለይ ደመና በአካባቢያችኍ ከሌለ በግልጽ የሚታይ ሲኾን በዚኽ 13ኛ የሙሉ ጨረቃ ዕለት የሚከሰተውን የሰማይ መርሐ ግብር ለመከታተል እንድትችሉ ሰዓቱን ከዚኽ በታች አስቀምጬላችኋለኊ፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡21 (6:21 PM) - ደማቋ ሙሉዋ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ መውጣት ትጀምራለች፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትዠምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ዠምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
👉 በመጨረሻዋ 13 ወራችን በርኅወተ ሰማይ በጳጉሜን 2 የዚኽ የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ መታየቱ እና የጨረቃ ደም መምሰል ያለው ሳይንሳዊ፣ ኢትጵያዊ ዕውቀት፣ ሃይማኖታዊ፣ ምልክትና መጻኢ ጉዳይ ዙሪያ በዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ፣ በመምህር መስፍን ሰሎሞን የቀረበውን ሰፊና ጥልቅ ትንተና ለማየትና ለማድመጥ በዚኽ ሊንክ ከፍተው ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=nIaFrhIfSIcfc6H9
👉 በመኾኑም ይኽነን ቪዲዮና ጽሑፍ ለኹሉም ሼር በማድረግ በዕለቱ ያለውን ክስተት በመላ ኢትዮጵያ ስለሚታይ ኹሉም ኢትዮጵያውን ከቤታቸው ወጥተው በሰዓቱ ክስተቱን እንዲመለከቱና ጨረቃ ደም መስላ ስትታይ እንዳይደናገጡ መልእክቴን አስተላልፋለኍ፡፡
💥 እኔ ከሥራ ባልደረቦቼ እና ከጓደኞቼ ጋር የማይረሳ በዕለቱ ታላቅ የምሽት መርሐ ግብር የምናደርግ ሲኾን እናንተም ከቤተሰቦቻችኊ፣ ከጓደኞቻችኍ ጋር ክስተቱን በማየት እንድታሳልፉ ምክሬን በማቅረብ የደም ጨረቃን (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽን) በዐይን ማየት ምንም የሚያስከትለው የጤንነት ችግር ስለሌለው ምንም አሳሳቢ ነገር ስለሌለ በተጠቀሰው ሰዓት ባላችኹበት አካባቢ ደመና ከሌለ በሚገባ ማየት ትችላላችኍ፡፡
💥 በዕለቱም ካላችኹበት ቦታ የማስታወሻ ፎቶዎችን በመነሣት በሶሻል ሚዲያዎች እንድታጋሩን በማሳሰብ መጪው 2018 ዓ.ም. ለኹላችኹም የበረከት፣ የምሕረት፣ የከፍታ እንዲኾንላችኍ ከአኹኑ እመኛለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም.)
YouTube
ጳጉሜ 2 የደም ጨረቃን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሊመለከቱ ነው። ግርዶሹና የጳጉሜ ምልክት/ በዕለቱ ምን እናድርግ?
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤212👍50👎4🔥1
🌝 የፀሐይና የጨረቃ መጨለም በኢትዮጵያ ሰነዶች🌚
🌓 የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሊቃውንት ስለ ግርዶሽ በመርሐ ዕውር፣ በአቡሻህር ይልቁኑ በትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ ጋር ከመራቀቅ ባለፈ
በኢትዮጵያ የተከሠቱ ግርዶሾችን የመመዝገብ ልምድ ነበራቸው።
🌒 ለምሳሌ ያህል ስመ መንግሥታቸው መሲሕ ሰገድ በተባሉት በዐጼ በካፋ ዘመነ መንግሥት ስለተደረገው ግርዶሽ በታሪከ ነገሥት የብራናው ጽሑፍ ላይ፡-
🌛 “ወበስድስቱ ዓመተ መንግሥቱ አመ ሰብዑ ለመስከረም በዕለተ ሰኑይ በጊዜ ሠለስቱ ሰዓት ፀልመ ፀሓይ ወተርእዩ ከዋክብት ወተሐውኩ ኲሉ ሰብእ ወተማሕለሉ ወኮነት ከመ ቀዳሚሃ ብርህት”
(ዐጼ በካፋ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት በመስከረም ሰባት በዕለተ ሰኞ ሦስት ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች ከዋክብት ታዩ ሰው ሁሉ ታወከ፤ ለመኑ፤ ፀሓይም እንደ ቀደመው በራች) በማለት የፀሓይ ግርዶች በተገለጠ ጊዜ በተከሰተው ክስተት የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደደነገጠ ጭምር አስፍረዋል፡፡
🌒 ከደርቡሽ ጋር በተደረገው ፍልሚያ በዐጼ ዮሐንስ ዕረፍት ጊዜ ግርዶሽ እንደነበረ ታሪከ ነገሥት ሲያስረዳ፡-
☄️ “አመ አሚሩ ለመጋቢት በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት አሜሃ ኮነ ድልቅልቅ ሌሊተ ኮነ ቀትር ወጸልመ ፀሓይ ወኲሉ ዓለም ሠለስተ መዓልተ ወንጉሥ ዮሐንስ አዕረፈ ውስተ ሐይመቱ”
(መጋቢት 1 በቀዳሚት ሰንበት ዕለት ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ በቀትር ጊዜ ፀሓይ በመላው ዓለም ጨልሞ እንደ ሌሊት ሆነ፤ ንጉሥ ዮሐንስም በድንኳኑ ውስጥ ዐረፈ) ይላል፡፡
🌞 ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በባሕረ ሐሳብ መጽሐፋቸው ላይ በኢትዮጵያ በየዘመናቱ የተደረጉ ታሪኮችን ታሪከ ነገሥትንና በኢትዮጵያ ያሉ የነገሥታት ዜና መዋዕሎችን አመሳክረው በዳሰሰቡት ክፍል ላይ በኢትዮጵያ የተደረጉትን የፀሓይና የጨረቃ ግርዶሾችና የሥነ ፈለክ ክስተቶችን በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር እንዲህ አስፍረውታል፡-
🌖 ➢ በዐጼ ገላውዴዎስ (አጽናፍ ሰገድ ዘመነ መንግሥት) በ1545 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑 ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1661 ዓ.ም. ኅዳር 5 (ጥቅምት 28 የሚልም አለ) በ9 ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች፤ በዚህ ምክንያት ንጉሡ በዕለቱ ሞት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወንጀሎቹ እንዳይነኩ አዘዘ፡፡፡ ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በድጋሚ በ1672 መጋቢት 24 ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑☄️ ➢ በዐጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ዘመነ መንግሥት በ1682 ዓ.ም. ኅዳር 1 ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
🌟 ➢ በዐጼ በካፋ (ዳግማዊ እስክንድር) ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1720 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመ፡፡
🌒☄️ በዐጼ ኢያሱ (ብርሃን ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1735 ዓ.ም. ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
⛅️ ➢ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ በ1792 ዓ.ም. ተክለ ጊዮርጊስ ለስድስተኛ ጊዜ ከዙፋኑ ላይ በወጣበት ዓመት በ1792 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ጨረቃ ጨለመች፡፡
💥 ➢ በዐጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1902 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ለጥቂት ቀናት ጅራታም ኮከብ ታየ በማለት አስቀምጠውታል፡፡
🌞 በዘመናችን ደግሞ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. የቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ እንደተመዘገበ፤ የጳጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም የሙሉ ጨረቃ መጨለም (የደም ጨለማ) በክብር ይመዘገባል።
☄️ ስለ ጳጉሜን 2 ምሽት የጨረቃ ግርዶሽ ለመረዳት በዚህ YouTube ሊንክ ይመልከቱ https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=-5ZvCjFBptZTSKiP
አንድሮሜዳን ያንብቡ።
🌒 መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌓 የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ሊቃውንት ስለ ግርዶሽ በመርሐ ዕውር፣ በአቡሻህር ይልቁኑ በትርጓሜ ሚጠተ ብርሃናት ዘሔኖክ ጋር ከመራቀቅ ባለፈ
በኢትዮጵያ የተከሠቱ ግርዶሾችን የመመዝገብ ልምድ ነበራቸው።
🌒 ለምሳሌ ያህል ስመ መንግሥታቸው መሲሕ ሰገድ በተባሉት በዐጼ በካፋ ዘመነ መንግሥት ስለተደረገው ግርዶሽ በታሪከ ነገሥት የብራናው ጽሑፍ ላይ፡-
🌛 “ወበስድስቱ ዓመተ መንግሥቱ አመ ሰብዑ ለመስከረም በዕለተ ሰኑይ በጊዜ ሠለስቱ ሰዓት ፀልመ ፀሓይ ወተርእዩ ከዋክብት ወተሐውኩ ኲሉ ሰብእ ወተማሕለሉ ወኮነት ከመ ቀዳሚሃ ብርህት”
(ዐጼ በካፋ በነገሠ በስድስተኛው ዓመት በመስከረም ሰባት በዕለተ ሰኞ ሦስት ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች ከዋክብት ታዩ ሰው ሁሉ ታወከ፤ ለመኑ፤ ፀሓይም እንደ ቀደመው በራች) በማለት የፀሓይ ግርዶች በተገለጠ ጊዜ በተከሰተው ክስተት የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደደነገጠ ጭምር አስፍረዋል፡፡
🌒 ከደርቡሽ ጋር በተደረገው ፍልሚያ በዐጼ ዮሐንስ ዕረፍት ጊዜ ግርዶሽ እንደነበረ ታሪከ ነገሥት ሲያስረዳ፡-
☄️ “አመ አሚሩ ለመጋቢት በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት አሜሃ ኮነ ድልቅልቅ ሌሊተ ኮነ ቀትር ወጸልመ ፀሓይ ወኲሉ ዓለም ሠለስተ መዓልተ ወንጉሥ ዮሐንስ አዕረፈ ውስተ ሐይመቱ”
(መጋቢት 1 በቀዳሚት ሰንበት ዕለት ያን ጊዜ ንውጽውጽታ ሆነ በቀትር ጊዜ ፀሓይ በመላው ዓለም ጨልሞ እንደ ሌሊት ሆነ፤ ንጉሥ ዮሐንስም በድንኳኑ ውስጥ ዐረፈ) ይላል፡፡
🌞 ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በባሕረ ሐሳብ መጽሐፋቸው ላይ በኢትዮጵያ በየዘመናቱ የተደረጉ ታሪኮችን ታሪከ ነገሥትንና በኢትዮጵያ ያሉ የነገሥታት ዜና መዋዕሎችን አመሳክረው በዳሰሰቡት ክፍል ላይ በኢትዮጵያ የተደረጉትን የፀሓይና የጨረቃ ግርዶሾችና የሥነ ፈለክ ክስተቶችን በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር እንዲህ አስፍረውታል፡-
🌖 ➢ በዐጼ ገላውዴዎስ (አጽናፍ ሰገድ ዘመነ መንግሥት) በ1545 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑 ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1661 ዓ.ም. ኅዳር 5 (ጥቅምት 28 የሚልም አለ) በ9 ሰዓት ላይ ፀሓይ ጨለመች፤ በዚህ ምክንያት ንጉሡ በዕለቱ ሞት ተፈርዶባቸው የነበሩት ወንጀሎቹ እንዳይነኩ አዘዘ፡፡፡ ➢ በጻድቁ ዮሐንስ (አእላፍ ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በድጋሚ በ1672 መጋቢት 24 ፀሓይ ጨለመች፡፡
🌑☄️ ➢ በዐጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ዘመነ መንግሥት በ1682 ዓ.ም. ኅዳር 1 ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
🌟 ➢ በዐጼ በካፋ (ዳግማዊ እስክንድር) ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1720 ዓ.ም. ፀሓይ ጨለመ፡፡
🌒☄️ በዐጼ ኢያሱ (ብርሃን ሰገድ) ዘመነ መንግሥት በ1735 ዓ.ም. ጅራታማ ኮከብ ታየ፡፡
⛅️ ➢ በዘመነ መሳፍንት ጊዜ በ1792 ዓ.ም. ተክለ ጊዮርጊስ ለስድስተኛ ጊዜ ከዙፋኑ ላይ በወጣበት ዓመት በ1792 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ጨረቃ ጨለመች፡፡
💥 ➢ በዐጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ጊዜ በ1902 ዓ.ም. በሚያዝያ ወር ለጥቂት ቀናት ጅራታም ኮከብ ታየ በማለት አስቀምጠውታል፡፡
🌞 በዘመናችን ደግሞ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. የቀለበታማ የፀሐይ ግርዶሽ እንደተመዘገበ፤ የጳጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም የሙሉ ጨረቃ መጨለም (የደም ጨለማ) በክብር ይመዘገባል።
☄️ ስለ ጳጉሜን 2 ምሽት የጨረቃ ግርዶሽ ለመረዳት በዚህ YouTube ሊንክ ይመልከቱ https://youtu.be/OoiU6WHxsWM?si=-5ZvCjFBptZTSKiP
አንድሮሜዳን ያንብቡ።
🌒 መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
YouTube
ጳጉሜ 2 የደም ጨረቃን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሊመለከቱ ነው። ግርዶሹና የጳጉሜ ምልክት/ በዕለቱ ምን እናድርግ?
Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.
❤161👍28👏11