💫ቅምሻ 💫
መጣን ብለው ላኩ ድግሱ ቢያምራቸው፤
እኛም አልቀረንም ሔደን አየናቸው፤
አሉላ አባ ነጋ አስተናገዳቸው፤
አገር ብለው መጡ አገር ሰጠናቸው፤
የደከሙበትን አፈር አጋጥናቸው፤
ግብፆች ፀጋ ወጡ ጣይ ቢያቃጥላቸው፤
እሳት ሆኖ አሉላ አንድዶ ፈጃቸው።
ልብሳቸው በስብሶ ጣሊያኖች ከባሕር፤
የፀሐይዋን ሙቀት ፈልገውት ነበር፤
አሰጣው አሉላ ዘርሮ ከአፈር።
📖 አሉላ አባነጋ በማሞ ውድነህ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
መጣን ብለው ላኩ ድግሱ ቢያምራቸው፤
እኛም አልቀረንም ሔደን አየናቸው፤
አሉላ አባ ነጋ አስተናገዳቸው፤
አገር ብለው መጡ አገር ሰጠናቸው፤
የደከሙበትን አፈር አጋጥናቸው፤
ግብፆች ፀጋ ወጡ ጣይ ቢያቃጥላቸው፤
እሳት ሆኖ አሉላ አንድዶ ፈጃቸው።
ልብሳቸው በስብሶ ጣሊያኖች ከባሕር፤
የፀሐይዋን ሙቀት ፈልገውት ነበር፤
አሰጣው አሉላ ዘርሮ ከአፈር።
📖 አሉላ አባነጋ በማሞ ውድነህ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ💫
አህያ ሁን አለኝ አህያ ሆንኩለት፤
አሰሱን ገሰሱን እንድሸከምለት።
መጋዣ ሁን ብሎ ፈረሱ አደረገኝ፤
በየዳገቱ ላይ ወስዶ ሚጋልበኝ፤
እንጃ ግን ሰሞኑን በግ ነህ ተብያለሁ፤
ሊያርደኝ ነው መሰለኝ አሁን ፈርቻለሁ።
ሎሬት ፀጋዬ ገብረ-መድህን
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
አህያ ሁን አለኝ አህያ ሆንኩለት፤
አሰሱን ገሰሱን እንድሸከምለት።
መጋዣ ሁን ብሎ ፈረሱ አደረገኝ፤
በየዳገቱ ላይ ወስዶ ሚጋልበኝ፤
እንጃ ግን ሰሞኑን በግ ነህ ተብያለሁ፤
ሊያርደኝ ነው መሰለኝ አሁን ፈርቻለሁ።
ሎሬት ፀጋዬ ገብረ-መድህን
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ከታሪክ ማህደር 💫
የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭ የቀይ መስቀል መስራች ደራሲ ገጣሚ አርበኛ
ወይዘሮ ስንዱ ገብሩ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭ የቀይ መስቀል መስራች ደራሲ ገጣሚ አርበኛ
ወይዘሮ ስንዱ ገብሩ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ💫
ክፍል አንድ
" አሁን የሰው ምንነት ግልጽ ብሎ ታየኝ። ሰው ማለት የተፈጠረ መፍጠር የማይችል የሚመግበውና የሚጠብቀው ያለው ነፍስና ሥጋ ያለው ከነፍስ ከሥጋ አንድ የሆነ በነፍስ አካልነት የቆመ የሚያስተውል ፣ የሚያስብ ፣ የሚናገር ፣ የሚንቀሳቀስ ፣ ሥጋ ብቻ ያልሆነ ፣ ነፍስም ብቻ ያልሆነ ፣ ፍፁመ ሥጋ ወነፍስ ፣ ፍፁመ ጸጋ ፣ ምሉዐ ጸጋ ፣ መንግል ያለው ፍጥረት ነው። "
ገፅ 94
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል አንድ
" አሁን የሰው ምንነት ግልጽ ብሎ ታየኝ። ሰው ማለት የተፈጠረ መፍጠር የማይችል የሚመግበውና የሚጠብቀው ያለው ነፍስና ሥጋ ያለው ከነፍስ ከሥጋ አንድ የሆነ በነፍስ አካልነት የቆመ የሚያስተውል ፣ የሚያስብ ፣ የሚናገር ፣ የሚንቀሳቀስ ፣ ሥጋ ብቻ ያልሆነ ፣ ነፍስም ብቻ ያልሆነ ፣ ፍፁመ ሥጋ ወነፍስ ፣ ፍፁመ ጸጋ ፣ ምሉዐ ጸጋ ፣ መንግል ያለው ፍጥረት ነው። "
ገፅ 94
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ💫
ክፍል ሁለት
" ኤርሚያስ ሲመራመር እግዚአብሔር አንድ ትዕዛዝ ሰጠው። ኤርምያስ ተመልከት አለው ኤርሚያስም እሺ ብሎ ሳለ አንድ ፈጣን ፈረሰኛ በፊቱ በታላቅ ፍጥነት እየጋለበ አለፈ። ፈጣሪም ኤርሚያስን 'ኤርምያስ ይህን ፈረሰኛ ተከተል' ብሎ ባዘዘው ጊዜ ኤርምያስ እንደነገረኝ ለመከተል ሞክሬ ነበር አለኝ። ከዚያስ ብለው አልቻልኩም አለኝ። ሌላ የሚገርም ነገር ልንገርህ፥ ፈጣሪዬም አዘዘኝ። አሁን ደግሞ ሌላ ፈረሰኛ መጣና ተከተለው አለኝ። ያሁኑ ፈረሰኛ ደግሞ ነፋስ ነበር። በሰንጋ ፈረሱ ተቀምጦ ለማየት በማይቻል ፍጥነት አለፈ። አሁንም ፈጣሪዬ ኤርምያስ ተከተለው አለኝ። እኔም አምላኬ ሆይ እንኳን የነፋስ ጋላቢውን የመጀመርያውን የሰው ጋላቢ መከተል አልቻልኩም ብዬ ብመልስ ፈጣሪዬም መለሰልኝ የሰው አቅምንም አስታወቀኝ።
🤔 እንቅልፍ ሲወስደው ራሱን ስለማያቅ የሰውነት ማንነት አቅምን ተረዳሁ። ፈጣሪዬም አየህ ኤርምያስ የመጀመሪያው ፈረሰኛ ያንተ ሐሳብ ነው። ሁለተኛው እኔ ነኝ። አንተም ለመከተል ሞክረህ የነበረው ደግሞ ያቃተህ እንኳን የኔን ነገር የራስህን ሐሳብ እንኳ ልትመረምርና ልታውቀው እንደማይችል ነው ፤ ብሎ አምላክ ገለጸልኝ ያለውን ካወጋኝ በኋላ ተለየኝ። "
ገፅ 119
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል ሁለት
" ኤርሚያስ ሲመራመር እግዚአብሔር አንድ ትዕዛዝ ሰጠው። ኤርምያስ ተመልከት አለው ኤርሚያስም እሺ ብሎ ሳለ አንድ ፈጣን ፈረሰኛ በፊቱ በታላቅ ፍጥነት እየጋለበ አለፈ። ፈጣሪም ኤርሚያስን 'ኤርምያስ ይህን ፈረሰኛ ተከተል' ብሎ ባዘዘው ጊዜ ኤርምያስ እንደነገረኝ ለመከተል ሞክሬ ነበር አለኝ። ከዚያስ ብለው አልቻልኩም አለኝ። ሌላ የሚገርም ነገር ልንገርህ፥ ፈጣሪዬም አዘዘኝ። አሁን ደግሞ ሌላ ፈረሰኛ መጣና ተከተለው አለኝ። ያሁኑ ፈረሰኛ ደግሞ ነፋስ ነበር። በሰንጋ ፈረሱ ተቀምጦ ለማየት በማይቻል ፍጥነት አለፈ። አሁንም ፈጣሪዬ ኤርምያስ ተከተለው አለኝ። እኔም አምላኬ ሆይ እንኳን የነፋስ ጋላቢውን የመጀመርያውን የሰው ጋላቢ መከተል አልቻልኩም ብዬ ብመልስ ፈጣሪዬም መለሰልኝ የሰው አቅምንም አስታወቀኝ።
🤔 እንቅልፍ ሲወስደው ራሱን ስለማያቅ የሰውነት ማንነት አቅምን ተረዳሁ። ፈጣሪዬም አየህ ኤርምያስ የመጀመሪያው ፈረሰኛ ያንተ ሐሳብ ነው። ሁለተኛው እኔ ነኝ። አንተም ለመከተል ሞክረህ የነበረው ደግሞ ያቃተህ እንኳን የኔን ነገር የራስህን ሐሳብ እንኳ ልትመረምርና ልታውቀው እንደማይችል ነው ፤ ብሎ አምላክ ገለጸልኝ ያለውን ካወጋኝ በኋላ ተለየኝ። "
ገፅ 119
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ከላይ የምናያቸው
ሰው ምንድን ነው? (ምንትኑ ውእቱ ሰብእ?)
የማንነትን ትርጉም ፍለጋ ከሚለው የዶክተር ዘበነ ለማ መጽሐፍ የተወሰዱ ናቸው።
© 2011
ዋጋ 99.99 ብር
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ከላይ የምናያቸው
ሰው ምንድን ነው? (ምንትኑ ውእቱ ሰብእ?)
የማንነትን ትርጉም ፍለጋ ከሚለው የዶክተር ዘበነ ለማ መጽሐፍ የተወሰዱ ናቸው።
© 2011
ዋጋ 99.99 ብር
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ይህን መጽሐፍ የፃፉት
ዶክተር ዘበነ ለማ በነገረ መለኮት ትምህርት ከቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪ በማስተርስ ዲግሪ ስለአለም እምነቶች ጥናትና ፍልስፍና በሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በዶክትሬት ዲግሪ በሥነ አመራር እና አንትሮፖሎጂ ጥናት ከሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ ተምረው ፈጽመዋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ዶክተር ዘበነ ለማ በነገረ መለኮት ትምህርት ከቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪ በማስተርስ ዲግሪ ስለአለም እምነቶች ጥናትና ፍልስፍና በሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በዶክትሬት ዲግሪ በሥነ አመራር እና አንትሮፖሎጂ ጥናት ከሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ ተምረው ፈጽመዋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
😂😂😂ለፈገግታ 😂😂😂
ወንዱ :- ይሄንን ቀን በጉጉት ስጠብቅ ነበር
ሴቷ :- ትቼህ እንድሄድ ትፈቅድልኛለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም
ሴቷ :- ትወደኛለህ ?
ወንዱ :- አዎን
ሴቷ :- በላዬ ላይ ከሌላ ሴት ጋር
ታመነዝራለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም አላደረገውም
ሴቷ :- ትስመኛለህ ?
ወንዱ :- ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ
ሴቷ :- ትመታኛለህ ?
ወንዱ :- ምን በወጣኝ
ሴቷ :- ልመንህ ?
ወንዱ :- Yes
ሴቷ :- የኔ ፍቅር
” ከጋብቻ በኋላ ከታች ወደ ላይ አንብቡት ”
ምንጭ:-http://www.yasekal.com
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ወንዱ :- ይሄንን ቀን በጉጉት ስጠብቅ ነበር
ሴቷ :- ትቼህ እንድሄድ ትፈቅድልኛለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም
ሴቷ :- ትወደኛለህ ?
ወንዱ :- አዎን
ሴቷ :- በላዬ ላይ ከሌላ ሴት ጋር
ታመነዝራለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም አላደረገውም
ሴቷ :- ትስመኛለህ ?
ወንዱ :- ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ
ሴቷ :- ትመታኛለህ ?
ወንዱ :- ምን በወጣኝ
ሴቷ :- ልመንህ ?
ወንዱ :- Yes
ሴቷ :- የኔ ፍቅር
” ከጋብቻ በኋላ ከታች ወደ ላይ አንብቡት ”
ምንጭ:-http://www.yasekal.com
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫የእለቱ ጥቆማ💫
👉የ ወንድ ልጅ ምጥ
፩.አይነት፡የግጥም መድብል
፪.ደራሲ:ይስምዕከ ወርቁ
፫.የ መጀመርያ እትም:ሀምሌ 1999 ዓ.ም
፬.ገፅ ብዛት:80
፭.የግጥም ብዛት:60
፮.ልዩ ጥቆማ:
1.ፈሶሎጂ(ገፅ 35)
2.የወንድ ልጅ ምጥ(ገፅ75)
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
👉የ ወንድ ልጅ ምጥ
፩.አይነት፡የግጥም መድብል
፪.ደራሲ:ይስምዕከ ወርቁ
፫.የ መጀመርያ እትም:ሀምሌ 1999 ዓ.ም
፬.ገፅ ብዛት:80
፭.የግጥም ብዛት:60
፮.ልዩ ጥቆማ:
1.ፈሶሎጂ(ገፅ 35)
2.የወንድ ልጅ ምጥ(ገፅ75)
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
📺👉ከታሪክ ማህደር 👈📺
ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም በስልጣን ዘመናቸው ከተናገሯቸው በቴሌቪዥን መስኮት ከቀረቡት ውስጥ በጥቂቱ
📺 "እያንዳንዱ ደቂቃና ሴኮንድ በእያንዳንዱ ወገናችን ህይወት ላይ ይወስናል።እና ቅድም እንዳልኳቹ እነሱ ከእረኛ እስከ ምሁር ተነስተው ለእኩይ አላማቸው ተሰልፈው ሲያበቁ ይህን ያደርጋሉ።ንቀውናል ደፍረውናል ብታምኑም ባታምኑም በቁም ሞተናል። ውይይት ነው ሰላማዊ ሰልፍ ነው ወይስ እንደወያኔ ወጣቶች ታጥቃቹ ትሰለፋላቹ።"
📺 "አብዮታዊ ሰራዊታችን ከሕዝብ እንዳልተወለደ እና የሕዝብ ወገን እንዳልሆነ ሁሉ ፤ ይህንን ገበሬ እየሞተ ባለመሬት እንዳላደረገ ሁሉ ፤ እየለመነ ብስኩትና ዱቄት እንደማያድል ሁሉ ፤ ዛሬ በአክሱም በአደዋ በሽሬ ወዘተርፈ እንደ ጠላት ጦር ይሀው እርሱ ገበሬው እንደ አንበጣ ተሰባስበው እየተከተከው ነው። ......... ኋላቀሮች ረሀብተኞች ችጋራም የምንባለው ከዚሁ ክልል በሚመነጭ ችግር ነው።"
📺 "እንግዲ ሁሉም ለከትና መቼም ወሰን አለው። እኔ ግራህን ሲመቱህ ቀኙን ስጥ የሚባል እምነት የለኝም። በተለይ እንደንደዚህ አይነት የአካባቢያችን እብሪተኞች ደግሞ የሚገባቸው ቋንቋ ዲፕሎማሲ ሳይሆን አፍንጫቸውን ማለት ነው።"
📺 "ሁሉም አኩራፊ፤ ሁሉም ነፃ አውጪ ነኝ ባይ ፤ ሁሉም ተሳዳቢ እና ተቺ ፤ ወርቅ ቢያነጥፉለት ፋንዲያ ነው የሚል ፤ ምን አደረጋችሁልኝ እንጂ እኔ ምን አደረኩ የማይል ቁጥር ጥቂት ባልሆነበት ሁኔታ ውስጥ ምን ተዓምር እንድንሰራ ይጠበቅብናል።"
📺 "እኔ በበኩሌ እኔ ብሎ መናገር ልምዴ እንዳልሆነና እንደማልወደውም ታውቃላችሁ። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና ፈቃድ በተሰጠኝ ሀላፊነት እና በተጣለብኝ እምነትና አደራ ለእናት ሀገሬና ወገኔ ካለኝ ጥልቅ ፍቅር ምን አስተዋፅኦ አደርጋለሁ በሚል እንጂ ከዚህ በተረፈ ቅንጣት ታህል እደግመዋለሁ ቅንጣት ታህል የሥልጣን ጥማትና ምኞት የለኝም።"
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም በስልጣን ዘመናቸው ከተናገሯቸው በቴሌቪዥን መስኮት ከቀረቡት ውስጥ በጥቂቱ
📺 "እያንዳንዱ ደቂቃና ሴኮንድ በእያንዳንዱ ወገናችን ህይወት ላይ ይወስናል።እና ቅድም እንዳልኳቹ እነሱ ከእረኛ እስከ ምሁር ተነስተው ለእኩይ አላማቸው ተሰልፈው ሲያበቁ ይህን ያደርጋሉ።ንቀውናል ደፍረውናል ብታምኑም ባታምኑም በቁም ሞተናል። ውይይት ነው ሰላማዊ ሰልፍ ነው ወይስ እንደወያኔ ወጣቶች ታጥቃቹ ትሰለፋላቹ።"
📺 "አብዮታዊ ሰራዊታችን ከሕዝብ እንዳልተወለደ እና የሕዝብ ወገን እንዳልሆነ ሁሉ ፤ ይህንን ገበሬ እየሞተ ባለመሬት እንዳላደረገ ሁሉ ፤ እየለመነ ብስኩትና ዱቄት እንደማያድል ሁሉ ፤ ዛሬ በአክሱም በአደዋ በሽሬ ወዘተርፈ እንደ ጠላት ጦር ይሀው እርሱ ገበሬው እንደ አንበጣ ተሰባስበው እየተከተከው ነው። ......... ኋላቀሮች ረሀብተኞች ችጋራም የምንባለው ከዚሁ ክልል በሚመነጭ ችግር ነው።"
📺 "እንግዲ ሁሉም ለከትና መቼም ወሰን አለው። እኔ ግራህን ሲመቱህ ቀኙን ስጥ የሚባል እምነት የለኝም። በተለይ እንደንደዚህ አይነት የአካባቢያችን እብሪተኞች ደግሞ የሚገባቸው ቋንቋ ዲፕሎማሲ ሳይሆን አፍንጫቸውን ማለት ነው።"
📺 "ሁሉም አኩራፊ፤ ሁሉም ነፃ አውጪ ነኝ ባይ ፤ ሁሉም ተሳዳቢ እና ተቺ ፤ ወርቅ ቢያነጥፉለት ፋንዲያ ነው የሚል ፤ ምን አደረጋችሁልኝ እንጂ እኔ ምን አደረኩ የማይል ቁጥር ጥቂት ባልሆነበት ሁኔታ ውስጥ ምን ተዓምር እንድንሰራ ይጠበቅብናል።"
📺 "እኔ በበኩሌ እኔ ብሎ መናገር ልምዴ እንዳልሆነና እንደማልወደውም ታውቃላችሁ። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና ፈቃድ በተሰጠኝ ሀላፊነት እና በተጣለብኝ እምነትና አደራ ለእናት ሀገሬና ወገኔ ካለኝ ጥልቅ ፍቅር ምን አስተዋፅኦ አደርጋለሁ በሚል እንጂ ከዚህ በተረፈ ቅንጣት ታህል እደግመዋለሁ ቅንጣት ታህል የሥልጣን ጥማትና ምኞት የለኝም።"
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ከዚም ከዛም💫
#1. ሉሲ (ድንቅነሽ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘችው በታዋቂዎቹ ሳይንቲስቶች ዶናልድ ጆሀንሰን እና ይቬስ ካኘንስ ነበር።
#2. አሜሪካ ስያሜዋን ያገኘችው አሜሪጎ ቬስፑቺ ከተሰኘውና በ1499 ሀገሪቱን ካገኘው ኢጣሊያዊ የባሕር አሳሽ ነው።
#3. የመጀመሪያዋ የሴት መንኮራኩር አብራሪ የ26 አመቷ ቫለንቲና ተሬሽኮቫ ትባላለች።
#4. ከኢትዮጵያ አንደኛ ከአፍሪካ አራተኛ የሆነው ራስዳሽን 4620m ከባሕር ጠለል በላይ እርዝማኔ አለው።
#5. ንብ አንድ ፓዎንድ የሚመዝንን ማር ለመስራት 55,000 ማይል እና 2,000,000 አበባዎችን መቅሰም አለባት።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
#1. ሉሲ (ድንቅነሽ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘችው በታዋቂዎቹ ሳይንቲስቶች ዶናልድ ጆሀንሰን እና ይቬስ ካኘንስ ነበር።
#2. አሜሪካ ስያሜዋን ያገኘችው አሜሪጎ ቬስፑቺ ከተሰኘውና በ1499 ሀገሪቱን ካገኘው ኢጣሊያዊ የባሕር አሳሽ ነው።
#3. የመጀመሪያዋ የሴት መንኮራኩር አብራሪ የ26 አመቷ ቫለንቲና ተሬሽኮቫ ትባላለች።
#4. ከኢትዮጵያ አንደኛ ከአፍሪካ አራተኛ የሆነው ራስዳሽን 4620m ከባሕር ጠለል በላይ እርዝማኔ አለው።
#5. ንብ አንድ ፓዎንድ የሚመዝንን ማር ለመስራት 55,000 ማይል እና 2,000,000 አበባዎችን መቅሰም አለባት።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ጥቆማ 💫
ሮሜዎና ዡልዬት
ቴአትር
ከከበደ ሚካኤል
ይህ መጽሐፍ አርተር ብሩክ የሚባል አንድ የእንግሊዝ ባለቅኔ መዠመሪያ በግጥም ጻፈው።ቀጥሎ ሼክስፒር ይህን ቅኔ መሠረት አድርጎ በመከተል ቴአትር አድርጎ አቀረበው።ከበደ ሚካኤልም በዚህ መጽሐፉ በግጥም ዘውግ ወደ አማርኛ ለመግለጥ እንዲመቸው አድርጎ አቅርቦታል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ሮሜዎና ዡልዬት
ቴአትር
ከከበደ ሚካኤል
ይህ መጽሐፍ አርተር ብሩክ የሚባል አንድ የእንግሊዝ ባለቅኔ መዠመሪያ በግጥም ጻፈው።ቀጥሎ ሼክስፒር ይህን ቅኔ መሠረት አድርጎ በመከተል ቴአትር አድርጎ አቀረበው።ከበደ ሚካኤልም በዚህ መጽሐፉ በግጥም ዘውግ ወደ አማርኛ ለመግለጥ እንዲመቸው አድርጎ አቅርቦታል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ከታሪክ ማህደር 💫
ከበደ ሚካኤል በኢትየጵያ ስነጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ገናና ከሆኑት ደራስያን አንዱ ናቸው። ጥቅምት 23፣ 1909 የተወለዱት ባለቅኔ የቤተክህነትን ትምህርት ካገባደዱ በኋላ በአሊያንስ ፍራንሴዝና በላዛሪስት ሚስዮን ዘመናዊ ትምህርትን ተከታትለዋል።
የግሪክ፣ የሮማውያን፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የሩስያና የጣልያንን በርካታ መፃህፍት ከመረመሩም በኋላ 26 መፃህፍትን ለወገኖቻቸው አበርክተዋል።
የአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ለዚሁ አስተዋፅኦዋቸው የክብር ዶክተርነት ዲግሪን በ1990 ሰጥቷቸዋል።
በሜጋ አሳታሚ ድርጅት ታትመው ለአንባብያን ከቀረቡት መሀከል
1. ታሪክና ምሳሌ (፩ኛ መጽሐፍ)
2. ታሪክና ምሳሌ (፪ኛ መጽሐፍ)
3. የቅኔ ውበት
4. ሮሜዎና ዡልዬት
5. የዕውቀት ብልጭታ
6. ጃፓን እንደምን ሠለጠነች
7. ታላላቅ ሰዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ከበደ ሚካኤል በኢትየጵያ ስነጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ገናና ከሆኑት ደራስያን አንዱ ናቸው። ጥቅምት 23፣ 1909 የተወለዱት ባለቅኔ የቤተክህነትን ትምህርት ካገባደዱ በኋላ በአሊያንስ ፍራንሴዝና በላዛሪስት ሚስዮን ዘመናዊ ትምህርትን ተከታትለዋል።
የግሪክ፣ የሮማውያን፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የሩስያና የጣልያንን በርካታ መፃህፍት ከመረመሩም በኋላ 26 መፃህፍትን ለወገኖቻቸው አበርክተዋል።
የአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ለዚሁ አስተዋፅኦዋቸው የክብር ዶክተርነት ዲግሪን በ1990 ሰጥቷቸዋል።
በሜጋ አሳታሚ ድርጅት ታትመው ለአንባብያን ከቀረቡት መሀከል
1. ታሪክና ምሳሌ (፩ኛ መጽሐፍ)
2. ታሪክና ምሳሌ (፪ኛ መጽሐፍ)
3. የቅኔ ውበት
4. ሮሜዎና ዡልዬት
5. የዕውቀት ብልጭታ
6. ጃፓን እንደምን ሠለጠነች
7. ታላላቅ ሰዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ቅምሻ 💫
ወንዙን ከላይ ገደብነው፣
ምንጩንም ወትፈን አቆምነው፣
ዝናቡን በድግምት ሰማይ አስቀረነው፤
የሴቱ ነገር ነው እኛን እንቢ ያለነ፣
ተስማምተው ቢሸኑ አጥለቀለቀነ።
...... አዳም ረታ፡ ግራጫ ቃጭሎች ገጽ 29
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ወንዙን ከላይ ገደብነው፣
ምንጩንም ወትፈን አቆምነው፣
ዝናቡን በድግምት ሰማይ አስቀረነው፤
የሴቱ ነገር ነው እኛን እንቢ ያለነ፣
ተስማምተው ቢሸኑ አጥለቀለቀነ።
...... አዳም ረታ፡ ግራጫ ቃጭሎች ገጽ 29
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫 ከታሪክ ማህደር 💫
አሌክሳንደር ፑሽኪን (1799-1837)
በ1977 ተወለደ። በጊዜው ተራማጅ አስተሳሰብ የነበረው ፑሽኪን: ሕይወቱን ለሩሲያ ስነ-ፅሁፍ ዕድገት ያዋለ በመሆኑ: የሀገሪቱ የመጀመሪያው የፈጠራ ፅሁፍ ጠቢብ ለመባል በቅቷል። የፑሽኪን የስነ-ፅሁፍ ውጤቶች የምዕራባውያን ባለ ቅኔዎች እና የብእር ሰዎች ተፅዕኖ የዳሰሳቸው ቢሆንም አርአያና ምሳሌ ለመሆን በበቁት በቅኔው፡ በተውኔቱ፡ በልብወለድ እና አጫጭር ድርሰቶቹ ጥልቀት እና ምጥቀት ብሔራዊ ባለቅኔነቱን ለማስመስከር ችሏል። ፑሽኪን በሰፊ የስነ-ፅሁፍ እና የስድ ፅሁፍ አዝመራው አማካኝነት ዘመናዊውን ስነ-ፅሁፋዊ ቋንቋ ለሩሲያ ያበረከተ ታላቅ የፈጠራ ሰው በመሆኑ፡ 'የሩሲያ ስነ-ፅሁፍ ታላቁ ጴጥሮስ' እያሉ የሚጠሩትም አልታጡም። የዛሬዋ ሶቪዬት ኅብረት ደራሲያንም፡ 'የሕዝባችን ነፍስ' የሚል ስያሜ የሰጡት ያለ ምክንያት አይደለም። የአርበኝነትን ባሕርይ፡ ጠንካራ ብሔራዊ ኩራትንና ለሩሲያ አፈር ያለውን ጥልቅ ፍቅር ከአብዮታዊ ስሜት ጋር በማዋሀድ በቅኔዎቹ ይገልጥ ስለነበር ነው። ይህም ስለ ስራው እና ስለ ህይወቱ በሚተርኩ ገድሎች ውስጥ ተመዝግቧል። በተለይም በከፍተኛ ስሜት ይደግፈው በነበረው፡ "የታኅሣሣዊያን ንቅናቄ" እየተባለ በሚጠራው፡ የ1825 እንቅስቃሴ ውስጥ ታላቅ ተጋድሎ ላደረጉት አርበኞች ጓደኞቹ መታሰቢያነት የፃፋቸው ቅኔዎች ለዚህ ቋሚ ምስክር ናቸዉና ሊጠቀሱ ይገባል።
ፑሽኪን ኢትዮጵያዊ ደም ነበረው። በሀገራችን በይበልጥ የሚታወቀውም በኢትዮጵያዊው ቅድመ አያቱ በአብርሃም ሃኒባል ታሪክ እንጂ፥ እምብዛም በኪነታዊ ስራዎቹ አይደለም። ወደ አማሪኛ ከተመለሱት ጥቂት አጫጭር ታሪኮቹ በስተቀር ዋነኛዎቹ የፑሽኪን የጥበብ ውጤቶች፡ በተለይም ድንቅ ቅኔዎቹ እስከ ዛሬ በሀገራችን ልሳናት አልተተረጎሙም።
የፑሽኪን መጨረሻ ድንገተዊ እና የሚያሳዝንም ነበር። በአንዳንድ ምክንያቶች የተነሳ፡ ዳንቴስ ከሚባል ሰው ጋር የከረረ አለመግባባት ይፈጠርና ሁለቱ ጠበኞች በተኩስ ለመፋለም ይወስናሉ። እኒሁ ግለሰቦች የካቲት 8 ቀን 1837 ባደረጉት የተኩስ ፍልሚያ የ38 ዓመቱ ጎልማሳ ደራሲ በለጋነቱ ተቀጨ።
[ካፖርቱ እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች (ትርጉም) በመስፍን አለማየሁ፡ገጽ 7 እና 8፡ 1978 ዓ.ም ]
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
አሌክሳንደር ፑሽኪን (1799-1837)
በ1977 ተወለደ። በጊዜው ተራማጅ አስተሳሰብ የነበረው ፑሽኪን: ሕይወቱን ለሩሲያ ስነ-ፅሁፍ ዕድገት ያዋለ በመሆኑ: የሀገሪቱ የመጀመሪያው የፈጠራ ፅሁፍ ጠቢብ ለመባል በቅቷል። የፑሽኪን የስነ-ፅሁፍ ውጤቶች የምዕራባውያን ባለ ቅኔዎች እና የብእር ሰዎች ተፅዕኖ የዳሰሳቸው ቢሆንም አርአያና ምሳሌ ለመሆን በበቁት በቅኔው፡ በተውኔቱ፡ በልብወለድ እና አጫጭር ድርሰቶቹ ጥልቀት እና ምጥቀት ብሔራዊ ባለቅኔነቱን ለማስመስከር ችሏል። ፑሽኪን በሰፊ የስነ-ፅሁፍ እና የስድ ፅሁፍ አዝመራው አማካኝነት ዘመናዊውን ስነ-ፅሁፋዊ ቋንቋ ለሩሲያ ያበረከተ ታላቅ የፈጠራ ሰው በመሆኑ፡ 'የሩሲያ ስነ-ፅሁፍ ታላቁ ጴጥሮስ' እያሉ የሚጠሩትም አልታጡም። የዛሬዋ ሶቪዬት ኅብረት ደራሲያንም፡ 'የሕዝባችን ነፍስ' የሚል ስያሜ የሰጡት ያለ ምክንያት አይደለም። የአርበኝነትን ባሕርይ፡ ጠንካራ ብሔራዊ ኩራትንና ለሩሲያ አፈር ያለውን ጥልቅ ፍቅር ከአብዮታዊ ስሜት ጋር በማዋሀድ በቅኔዎቹ ይገልጥ ስለነበር ነው። ይህም ስለ ስራው እና ስለ ህይወቱ በሚተርኩ ገድሎች ውስጥ ተመዝግቧል። በተለይም በከፍተኛ ስሜት ይደግፈው በነበረው፡ "የታኅሣሣዊያን ንቅናቄ" እየተባለ በሚጠራው፡ የ1825 እንቅስቃሴ ውስጥ ታላቅ ተጋድሎ ላደረጉት አርበኞች ጓደኞቹ መታሰቢያነት የፃፋቸው ቅኔዎች ለዚህ ቋሚ ምስክር ናቸዉና ሊጠቀሱ ይገባል።
ፑሽኪን ኢትዮጵያዊ ደም ነበረው። በሀገራችን በይበልጥ የሚታወቀውም በኢትዮጵያዊው ቅድመ አያቱ በአብርሃም ሃኒባል ታሪክ እንጂ፥ እምብዛም በኪነታዊ ስራዎቹ አይደለም። ወደ አማሪኛ ከተመለሱት ጥቂት አጫጭር ታሪኮቹ በስተቀር ዋነኛዎቹ የፑሽኪን የጥበብ ውጤቶች፡ በተለይም ድንቅ ቅኔዎቹ እስከ ዛሬ በሀገራችን ልሳናት አልተተረጎሙም።
የፑሽኪን መጨረሻ ድንገተዊ እና የሚያሳዝንም ነበር። በአንዳንድ ምክንያቶች የተነሳ፡ ዳንቴስ ከሚባል ሰው ጋር የከረረ አለመግባባት ይፈጠርና ሁለቱ ጠበኞች በተኩስ ለመፋለም ይወስናሉ። እኒሁ ግለሰቦች የካቲት 8 ቀን 1837 ባደረጉት የተኩስ ፍልሚያ የ38 ዓመቱ ጎልማሳ ደራሲ በለጋነቱ ተቀጨ።
[ካፖርቱ እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች (ትርጉም) በመስፍን አለማየሁ፡ገጽ 7 እና 8፡ 1978 ዓ.ም ]
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫 ከታሪክ ማህደር 💫
ጥቂት ስለ ንግሥተ ሳባ
አባቷ ንጉሥ ተዋስያን ሲሆን እናቷ ደግሞ እቴጌ ኤስሜኒ ይባላሉ
ንግሥተ ሳባ የነገሰችው ከክርስቶስ ልደት በፊት 1013 ዓመት (በ 3,987 ዓመተ ዓለም) ሲሆን በጽሑፍ ከተገኙ መረጃዎች የኢትዮጵያ ነገስታት ተርታ 52ኛዋ በጠቅላላው ከነገሡት ነገሥታት ተረታ ደግሞ 98ኛዋ ነበረች።
ንግሥተ ሳባ ሰሎሞንን የጎበኘችው 'ታምሪን' በተባለ ኢትዮጵያዊ ነጋዴ አማካኝነት ነበር።
ከንጉሥ ሰሎሞን የወለደችው ልጇ ስሙ 'እብነ እልኪምን' ይባል ነበር። ትርጉሙም 'የብልሃተኛ ልጅ' ማለት ነው።
-በኋላም ንግሥተ ሳባ ለ31 ዓመት ስታስተዳድር ቆይታ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ982 ዓመት(በ3,518 ዓ.ም) መንግሥቷን ለልጇ ስታወርስ ስሙ 'ቀዳማዊ ምኒልክ' ወይም 'ዳዊት' ነብሎ ነግሷል
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ጥቂት ስለ ንግሥተ ሳባ
አባቷ ንጉሥ ተዋስያን ሲሆን እናቷ ደግሞ እቴጌ ኤስሜኒ ይባላሉ
ንግሥተ ሳባ የነገሰችው ከክርስቶስ ልደት በፊት 1013 ዓመት (በ 3,987 ዓመተ ዓለም) ሲሆን በጽሑፍ ከተገኙ መረጃዎች የኢትዮጵያ ነገስታት ተርታ 52ኛዋ በጠቅላላው ከነገሡት ነገሥታት ተረታ ደግሞ 98ኛዋ ነበረች።
ንግሥተ ሳባ ሰሎሞንን የጎበኘችው 'ታምሪን' በተባለ ኢትዮጵያዊ ነጋዴ አማካኝነት ነበር።
ከንጉሥ ሰሎሞን የወለደችው ልጇ ስሙ 'እብነ እልኪምን' ይባል ነበር። ትርጉሙም 'የብልሃተኛ ልጅ' ማለት ነው።
-በኋላም ንግሥተ ሳባ ለ31 ዓመት ስታስተዳድር ቆይታ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ982 ዓመት(በ3,518 ዓ.ም) መንግሥቷን ለልጇ ስታወርስ ስሙ 'ቀዳማዊ ምኒልክ' ወይም 'ዳዊት' ነብሎ ነግሷል
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫