😂 ለፈገግታ 😂
A. አንተ እስካሁን እንዴት አላገባህም
ቆይ!
B. ምን ባክህ ሚሆን ሰው አጥቼ ነው።
እንደው እስኪ አንተ ፈልግልኝ ?
A. እኔ በምን አውቄ ፤ ምን አይነት
ትመችሀለች?
B. ያው ቤተክርስቲያን የምትወድ፣ ሰው
አክባሪ፣ ትሁት፣ሀሜት የማትወድ፣
አፍቃሪ፣ ልጃገረድ ብትሆን ደስ
ይለኛል።
A. 😳😳😳 እንዴ ወንድሜ በዚህ
መስፈርት መነኩሴ ራሱ ሚገኝ
አይመስለኝም።
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
A. አንተ እስካሁን እንዴት አላገባህም
ቆይ!
B. ምን ባክህ ሚሆን ሰው አጥቼ ነው።
እንደው እስኪ አንተ ፈልግልኝ ?
A. እኔ በምን አውቄ ፤ ምን አይነት
ትመችሀለች?
B. ያው ቤተክርስቲያን የምትወድ፣ ሰው
አክባሪ፣ ትሁት፣ሀሜት የማትወድ፣
አፍቃሪ፣ ልጃገረድ ብትሆን ደስ
ይለኛል።
A. 😳😳😳 እንዴ ወንድሜ በዚህ
መስፈርት መነኩሴ ራሱ ሚገኝ
አይመስለኝም።
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔑 ቅምሻ 🔑
🦅 ክፍል ሁለት 🦅
.........አቶ ኦላናም " እህ ..ህ ..ህ " ብለው ጉሮሮአቸውን ጠረግ አረጉና "እንግዲህ ከየት እንጀምር ለሚለው መቼም ካለንበት ነው። ወደየት እንሂድ ለሚለው ደግሞ ወደፊትና መድረስ ወደሚገባን ነው። ይህ ግልጽ ቢሆንም ሁሌም ቀላል አይደለም። ለምሳሌ ካለንበት ለመጀመር ያለንበትን ማወቅና መቀበል ኀላፊነትንም መውሰድን ይጠይቃል። ይህም ከባዶ ኩራትና ያልሆነውን ነን ብሎ ከማሰብ መላቀቅን የግድ ይላል። በተጨማሪም አሁን ለሆነውና መሆን ላቃተን ነገር ያለፈውን ትውልድ ወይም አሁን የሚመሩንን ሰዎች ከመወንጀልና ራስን ከኃላፊነት ለማሸሽ ከሚደረግ ስውር ሽሽት ነጻ መሆንን ያጠቃልላል። ታሪክን ለመመጻደቂያና ለመደበቂያ ሳይሆን፣ እንደ አንድ የትምህርት መድረክ ለመጠቀም ጠንቅቆ ማወቅም ትልቅ ፋይዳ አለው። ወደፊት መሔድ ነው ስል ሁሌም የብዙሀኑ የጅምላ ጉዞ አንድም ባለህበት ርገጥ ነው፤ ወይም እንደ ግመል ሽንት የኋልዮሽ ስለሆነ ነው። ይህም በባህል፤ በሀይማኖትና በአኗኗር ልማድ ውስጥ ጎልቶ ይታያል። " በማለት አባቷ ነገሩን ለሰሎሜ ማስረዳታቸውን ቀጠሉ።
" በየትኛውም ሥልጣኔ ውስጥ ፈር ቀዳጅና ፋና ወጊ ተብለው ለውጥ ያመጡ ሰዎች መጀመሪያ ወንጀለኛ፣ ከዚያም አሳሳች ተብለው መፈረጃቸው የተለመደ ነው። በእርግጥም እነዚህ ጥቂት ብርቅዬ ከዋክብት ከሕብረተሰቡ በሠላሳና በአርባ አመት ቀድመው ወደፊት የሄዱ ስለሆነ ከሰው አይገጥሙም። ሰው አንድም ባለበት ስለሚረግጥ አንድም የኋልዮሽ እንሽርት ጨዋታ ላይ ስለሚባትል እነሱን ይፈራቸዋል ፤ ስለዚህም ይጠላቸዋል። ምንም እንኳ እንደ እውነት ፀርና አሳች መሲሕ ቢታዩም ፣ በሚቀጥለው ትውልድ ግን ሁሌም ብሩህ ከዋክብት ተብለው ይሞገሳሉ ፤ የመታሰቢያ ሐውልትም ይሠራላቸዋል ።" አሉ አይናቸውን ከሰሎሜ ላይ ሳይነቅሉ ።
" የሚቀጥለው ትውልድ ደግሞ በነሱ ሐውልትና ትምሕርት ዙርያ ሲርመሰመስ ፣ ሳያስበው ወደ ኋላ ተንሸራቶ በራሱ ጨለማ ውስጥ ይገባና የራሱን ዘመን ፋና ወጊዎችና እውነት ገላጮች እያሳደደ ዕድሜውን ያቃጥላል። የእኛም ሕዝብ ከዚህ የተለየ አይደለም። እኔ እንደሚመስለኝ ለእኛም አገር አቅጣጫ ጠቋሚና ፈር ቀዳጅ መሪዎች በዋናነት ያስፈልጋሉ። እነዚህ በአስተሳሰባቸው ብዙሀኑን ከእንቅልፍ ቀስቃሾች ፣ የሥልጣኔ አድማስ አመልካቾች ከወጡልን ፣ ሀብት ብቻ አይደለም ፤ ሥልጣኔም በምድራችን እንደ ኃይለኛ ጅረት እንደገና የማይፈስበት ምክንያት የለም። ስለዚህ የት እንጀምር? ካለንበት ፤ መቼ እንጀምር? አሁን ፤ ማን ይጀመር? እኔ አንቺ እኛ ..... የት ለመድረስ? ሰው የደረሰበት ደግሞም ያልደረሰበት ፤ ትልቁና ከባዱ እንዴት እንጀምር? ነው። "ብለው ትንሽ ዝም አሉ።........
ገፅ 79-80
~~~ይቀጥላል ~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ።
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
#share #comment #participate
አስተያየቶ ለኛ ያስፈልጋልና ቅር ያላቹን እንዲሁም ይቀጥል የምትሉትን አጋሩን። በተጨማሪም ስለ ቻናሉ አስተያየት ካላችሁ 👇
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል ሁለት 🦅
.........አቶ ኦላናም " እህ ..ህ ..ህ " ብለው ጉሮሮአቸውን ጠረግ አረጉና "እንግዲህ ከየት እንጀምር ለሚለው መቼም ካለንበት ነው። ወደየት እንሂድ ለሚለው ደግሞ ወደፊትና መድረስ ወደሚገባን ነው። ይህ ግልጽ ቢሆንም ሁሌም ቀላል አይደለም። ለምሳሌ ካለንበት ለመጀመር ያለንበትን ማወቅና መቀበል ኀላፊነትንም መውሰድን ይጠይቃል። ይህም ከባዶ ኩራትና ያልሆነውን ነን ብሎ ከማሰብ መላቀቅን የግድ ይላል። በተጨማሪም አሁን ለሆነውና መሆን ላቃተን ነገር ያለፈውን ትውልድ ወይም አሁን የሚመሩንን ሰዎች ከመወንጀልና ራስን ከኃላፊነት ለማሸሽ ከሚደረግ ስውር ሽሽት ነጻ መሆንን ያጠቃልላል። ታሪክን ለመመጻደቂያና ለመደበቂያ ሳይሆን፣ እንደ አንድ የትምህርት መድረክ ለመጠቀም ጠንቅቆ ማወቅም ትልቅ ፋይዳ አለው። ወደፊት መሔድ ነው ስል ሁሌም የብዙሀኑ የጅምላ ጉዞ አንድም ባለህበት ርገጥ ነው፤ ወይም እንደ ግመል ሽንት የኋልዮሽ ስለሆነ ነው። ይህም በባህል፤ በሀይማኖትና በአኗኗር ልማድ ውስጥ ጎልቶ ይታያል። " በማለት አባቷ ነገሩን ለሰሎሜ ማስረዳታቸውን ቀጠሉ።
" በየትኛውም ሥልጣኔ ውስጥ ፈር ቀዳጅና ፋና ወጊ ተብለው ለውጥ ያመጡ ሰዎች መጀመሪያ ወንጀለኛ፣ ከዚያም አሳሳች ተብለው መፈረጃቸው የተለመደ ነው። በእርግጥም እነዚህ ጥቂት ብርቅዬ ከዋክብት ከሕብረተሰቡ በሠላሳና በአርባ አመት ቀድመው ወደፊት የሄዱ ስለሆነ ከሰው አይገጥሙም። ሰው አንድም ባለበት ስለሚረግጥ አንድም የኋልዮሽ እንሽርት ጨዋታ ላይ ስለሚባትል እነሱን ይፈራቸዋል ፤ ስለዚህም ይጠላቸዋል። ምንም እንኳ እንደ እውነት ፀርና አሳች መሲሕ ቢታዩም ፣ በሚቀጥለው ትውልድ ግን ሁሌም ብሩህ ከዋክብት ተብለው ይሞገሳሉ ፤ የመታሰቢያ ሐውልትም ይሠራላቸዋል ።" አሉ አይናቸውን ከሰሎሜ ላይ ሳይነቅሉ ።
" የሚቀጥለው ትውልድ ደግሞ በነሱ ሐውልትና ትምሕርት ዙርያ ሲርመሰመስ ፣ ሳያስበው ወደ ኋላ ተንሸራቶ በራሱ ጨለማ ውስጥ ይገባና የራሱን ዘመን ፋና ወጊዎችና እውነት ገላጮች እያሳደደ ዕድሜውን ያቃጥላል። የእኛም ሕዝብ ከዚህ የተለየ አይደለም። እኔ እንደሚመስለኝ ለእኛም አገር አቅጣጫ ጠቋሚና ፈር ቀዳጅ መሪዎች በዋናነት ያስፈልጋሉ። እነዚህ በአስተሳሰባቸው ብዙሀኑን ከእንቅልፍ ቀስቃሾች ፣ የሥልጣኔ አድማስ አመልካቾች ከወጡልን ፣ ሀብት ብቻ አይደለም ፤ ሥልጣኔም በምድራችን እንደ ኃይለኛ ጅረት እንደገና የማይፈስበት ምክንያት የለም። ስለዚህ የት እንጀምር? ካለንበት ፤ መቼ እንጀምር? አሁን ፤ ማን ይጀመር? እኔ አንቺ እኛ ..... የት ለመድረስ? ሰው የደረሰበት ደግሞም ያልደረሰበት ፤ ትልቁና ከባዱ እንዴት እንጀምር? ነው። "ብለው ትንሽ ዝም አሉ።........
ገፅ 79-80
~~~ይቀጥላል ~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ።
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
#share #comment #participate
አስተያየቶ ለኛ ያስፈልጋልና ቅር ያላቹን እንዲሁም ይቀጥል የምትሉትን አጋሩን። በተጨማሪም ስለ ቻናሉ አስተያየት ካላችሁ 👇
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔑 ቅምሻ 🔑
🦅 ክፍል ሶስት 🦅
........... ከልጅ ጋር መሆን እንዴት ሕይወት ያድሳል። ሁሉንም ነገር እነሱ የሚያዩበት እይታ ተስፋ ያዘለና እምቅ ኀይልን የሚለቅ ነው። ደስታም ሩቅ አይሆንም ። ጉጉትና ደግነት ፣ ፍቅርና ወዳጅነት በልጆች ዓለም ሳይበረዝና ሳይለዝዝ ይኖራል ። .............
.............. ልጅ ለማወቅ የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች አዋቂዎችን ለምን ይሆን የሚያውኳቸው። በተደጋጋሚ መልስ ያጣች ልጅ ደግሞ ቀስ በቀስ ያላዋቂ አዋቂ ወደ መሆን ትቀየርና እሷም መጠየቅ ታቆማለች ።ደርሳ የራሷ ልጅ ሲኖራት እሷም ሌላ ያላዋቂ ልጅ ታፈራለች ።በዚህ መሠረት በትምህርት ቤትም ሆነ በቤት ዕውቀትን የተራቡ ልጆችኝ ተቀብለን ዕውቀት ብለን በምንሰጣቸው የተዛባ መረጃ ተብትበናቸው ያላዋቂ አዋቂዎችን እናፈራለን ። እነሱንም እንደኛ ።
ያላዋቂ አዋቂነትም ተብትቦ ማኅበረሰብ በሚኮራበት ባህል በተባለ ባቡር ሁላችንንም ፍፃሜ ወደሌለው እንጦሮጦስ ይዞን ይወርዳል ። ጥቂት ደፋርና እምቢ ባይ በጥያቄ አስጨናቂ ከዚህ ወረርሽኝ የተረፉ ነፍሶች እስኪገኙ ። ማኅበረሰብን ካላዋቂ አዋቂነቱ የሚያባንኑ ። ነገርግን ልጆች አላዋቂዎች ስለሆኑ ማን ይሰማቸዋል ? አላዋቂ የሚባለው ጠያቂ ፣ አዋቂው ደግሞ የማይጠይቅ መሆኑ አንዱ የህይወት አሳዛኝ ገጽታ ሳይሆን አይቀርም። በርግጥም ድንቅ ነው !! ጥያቄ አቁመው በቁመት ስላደጉ ብቻ አዋቂ የሚል የክብር ስም በዕድሜያቸው ብቻ ለገፉ ህፃናት እንደ ካባ ሲደረብ።..............
ገፅ 100
~~~ይቀጥላል ~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ።
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል ሶስት 🦅
........... ከልጅ ጋር መሆን እንዴት ሕይወት ያድሳል። ሁሉንም ነገር እነሱ የሚያዩበት እይታ ተስፋ ያዘለና እምቅ ኀይልን የሚለቅ ነው። ደስታም ሩቅ አይሆንም ። ጉጉትና ደግነት ፣ ፍቅርና ወዳጅነት በልጆች ዓለም ሳይበረዝና ሳይለዝዝ ይኖራል ። .............
.............. ልጅ ለማወቅ የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች አዋቂዎችን ለምን ይሆን የሚያውኳቸው። በተደጋጋሚ መልስ ያጣች ልጅ ደግሞ ቀስ በቀስ ያላዋቂ አዋቂ ወደ መሆን ትቀየርና እሷም መጠየቅ ታቆማለች ።ደርሳ የራሷ ልጅ ሲኖራት እሷም ሌላ ያላዋቂ ልጅ ታፈራለች ።በዚህ መሠረት በትምህርት ቤትም ሆነ በቤት ዕውቀትን የተራቡ ልጆችኝ ተቀብለን ዕውቀት ብለን በምንሰጣቸው የተዛባ መረጃ ተብትበናቸው ያላዋቂ አዋቂዎችን እናፈራለን ። እነሱንም እንደኛ ።
ያላዋቂ አዋቂነትም ተብትቦ ማኅበረሰብ በሚኮራበት ባህል በተባለ ባቡር ሁላችንንም ፍፃሜ ወደሌለው እንጦሮጦስ ይዞን ይወርዳል ። ጥቂት ደፋርና እምቢ ባይ በጥያቄ አስጨናቂ ከዚህ ወረርሽኝ የተረፉ ነፍሶች እስኪገኙ ። ማኅበረሰብን ካላዋቂ አዋቂነቱ የሚያባንኑ ። ነገርግን ልጆች አላዋቂዎች ስለሆኑ ማን ይሰማቸዋል ? አላዋቂ የሚባለው ጠያቂ ፣ አዋቂው ደግሞ የማይጠይቅ መሆኑ አንዱ የህይወት አሳዛኝ ገጽታ ሳይሆን አይቀርም። በርግጥም ድንቅ ነው !! ጥያቄ አቁመው በቁመት ስላደጉ ብቻ አዋቂ የሚል የክብር ስም በዕድሜያቸው ብቻ ለገፉ ህፃናት እንደ ካባ ሲደረብ።..............
ገፅ 100
~~~ይቀጥላል ~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ።
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ሰላም የዚህ ቻናል ቤተሰቦች በዚህ ጷግሜን ወር ጥያቄና መልስ አዘጋጅተንላችኋል። የጠየቅናቸውን ጥያቄዎች በተደጋጋሚ መመለስ የቻሉትን መዝግበን ጷግሜን 6 ለሁለት ሰዎች ስጦታ አዘጋጅተናል። ጥያቄው ከተለቀቀ በኋላ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ድረስ ጥያቄዎቹን መመለስ ይቻላል። ከ 4:00 በኋላ መልሱ ዋጋ የለውም።
አንድ የመለሰ እንደ አንድ ሶስት የመለሰ እንደ ሶስት በጥያቄው ብዛትና በመለሰው መልስ ብዛት ነጥቡ ይያዛል።
ጥያቄውን ለመመለስ
ይህን👉 @R_e_a_d_e_rs ይጠቀሙ👍 and don't delete your answer since it helps us to count
መልካም እድል!!
መልዕክቱ ላልደረሳቸው አካፍሉ 👍
From
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
አንድ የመለሰ እንደ አንድ ሶስት የመለሰ እንደ ሶስት በጥያቄው ብዛትና በመለሰው መልስ ብዛት ነጥቡ ይያዛል።
ጥያቄውን ለመመለስ
ይህን👉 @R_e_a_d_e_rs ይጠቀሙ👍 and don't delete your answer since it helps us to count
መልካም እድል!!
መልዕክቱ ላልደረሳቸው አካፍሉ 👍
From
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🌼 ስነ-ግጥም 🌼
የሞላ ማድጋ ከጀርባ ካዘሉ ፤
ጎደሎ እንስራ ያዘሉት ተሻሉ ፤
ሙሉ ያዘሉቱ ከላይ ያፈሳሉ ፤
ጀርባቸውን ከታች ያበሰብሳሉ ፤
ጎደሎ ያዘሉ ምን ቢንገላጀጁ፣ ምን
ቢንገዋለሉ ፣
መሙላትን ይሻሉ ።
ምሉዕ ነን የሚሉ፣
እያደር ሲጎሉ፣ ይንቦጫቦጫሉ ።
ምንጭ:- የቀንድ አውጣ ኑሮ፣ 2002፣ የተሻሻለ
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
የሞላ ማድጋ ከጀርባ ካዘሉ ፤
ጎደሎ እንስራ ያዘሉት ተሻሉ ፤
ሙሉ ያዘሉቱ ከላይ ያፈሳሉ ፤
ጀርባቸውን ከታች ያበሰብሳሉ ፤
ጎደሎ ያዘሉ ምን ቢንገላጀጁ፣ ምን
ቢንገዋለሉ ፣
መሙላትን ይሻሉ ።
ምሉዕ ነን የሚሉ፣
እያደር ሲጎሉ፣ ይንቦጫቦጫሉ ።
ምንጭ:- የቀንድ አውጣ ኑሮ፣ 2002፣ የተሻሻለ
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 pinned «ሰላም የዚህ ቻናል ቤተሰቦች በዚህ ጷግሜን ወር ጥያቄና መልስ አዘጋጅተንላችኋል። የጠየቅናቸውን ጥያቄዎች በተደጋጋሚ መመለስ የቻሉትን መዝግበን ጷግሜን 6 ለሁለት ሰዎች ስጦታ አዘጋጅተናል። ጥያቄው ከተለቀቀ በኋላ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ድረስ ጥያቄዎቹን መመለስ ይቻላል። ከ 4:00 በኋላ መልሱ ዋጋ የለውም። አንድ የመለሰ እንደ አንድ ሶስት የመለሰ እንደ ሶስት በጥያቄው ብዛትና በመለሰው መልስ ብዛት ነጥቡ…»
📆 ጷግሜን 📆
🦅 ክፍል አንድ 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
📚 ጳጒሜን የተባለችው 13ኛዋ ወር በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ስትባል ሊቃውንት ተረፍ ይሏታል፡፡ የ5 ቀናትን የጳጉሜንን አመጣጥ ቀደምት የኢትዮጵያ ሊቃውንት ጠንቅቀው ቀምረው በባሕረ ሐሳብ ብራናቸው ላይ ጽፈውልናል፡፡
📚 ይኸውም ከመስከረም 1 እስከ ነሐሴ 30 ያሉት 12ቱ ወራት ያላቸው ዕለታት በአጠቃላይ 360 ናቸው፡፡ በቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ጥልቅ ትንተና 1 ዕለት የሚባለው 24 ሰዓት ከ52 ካልዒት ከ31 ሳልሲት ነው፡፡
📚 1 ካልዒት ማለት 24 ሰከንድ ሲኾን 52 ካልዒት ማለት 1248 ሰከንድ ነው፤ 31 ሣልሲት ማለት 12.4 ሰከንድ (ቅጽበት) ይኾናል፡፡ በመኾኑም በአንድ ቀን ውስጥ 1 ደቂቃ ከ0.4 ሰከንድ ትርፍ መኖሩን ያስረዳል፡፡
📚 በመኾኑም ከመስከረም 1 እስከ ነሐሴ 30 ባሉት 360 ቀናት ያሉትን 52 ካልዒት ወይም 1248 ሰከንድ እንዲኽ እናባዛቸዋለን፤ 52 ካልዒት X 360 ዕለታት= 18720 ካልዒት ወይም (449, 280 ሰከንድ) ይኾናል፤ ወደ ደቂቃ ስንለውጠው 7488 ደቂቃ ወይም 5 ዕለት ይኾናልና የጳጒሜን አመጣጥ ይቺ ናት፡፡
~~~ይቀጥላል~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል አንድ 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
📚 ጳጒሜን የተባለችው 13ኛዋ ወር በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ስትባል ሊቃውንት ተረፍ ይሏታል፡፡ የ5 ቀናትን የጳጉሜንን አመጣጥ ቀደምት የኢትዮጵያ ሊቃውንት ጠንቅቀው ቀምረው በባሕረ ሐሳብ ብራናቸው ላይ ጽፈውልናል፡፡
📚 ይኸውም ከመስከረም 1 እስከ ነሐሴ 30 ያሉት 12ቱ ወራት ያላቸው ዕለታት በአጠቃላይ 360 ናቸው፡፡ በቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ጥልቅ ትንተና 1 ዕለት የሚባለው 24 ሰዓት ከ52 ካልዒት ከ31 ሳልሲት ነው፡፡
📚 1 ካልዒት ማለት 24 ሰከንድ ሲኾን 52 ካልዒት ማለት 1248 ሰከንድ ነው፤ 31 ሣልሲት ማለት 12.4 ሰከንድ (ቅጽበት) ይኾናል፡፡ በመኾኑም በአንድ ቀን ውስጥ 1 ደቂቃ ከ0.4 ሰከንድ ትርፍ መኖሩን ያስረዳል፡፡
📚 በመኾኑም ከመስከረም 1 እስከ ነሐሴ 30 ባሉት 360 ቀናት ያሉትን 52 ካልዒት ወይም 1248 ሰከንድ እንዲኽ እናባዛቸዋለን፤ 52 ካልዒት X 360 ዕለታት= 18720 ካልዒት ወይም (449, 280 ሰከንድ) ይኾናል፤ ወደ ደቂቃ ስንለውጠው 7488 ደቂቃ ወይም 5 ዕለት ይኾናልና የጳጒሜን አመጣጥ ይቺ ናት፡፡
~~~ይቀጥላል~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 pinned «ሰላም የዚህ ቻናል ቤተሰቦች በዚህ ጷግሜን ወር ጥያቄና መልስ አዘጋጅተንላችኋል። የጠየቅናቸውን ጥያቄዎች በተደጋጋሚ መመለስ የቻሉትን መዝግበን ጷግሜን 6 ለሁለት ሰዎች ስጦታ አዘጋጅተናል። ጥያቄው ከተለቀቀ በኋላ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ድረስ ጥያቄዎቹን መመለስ ይቻላል። ከ 4:00 በኋላ መልሱ ዋጋ የለውም። አንድ የመለሰ እንደ አንድ ሶስት የመለሰ እንደ ሶስት በጥያቄው ብዛትና በመለሰው መልስ ብዛት ነጥቡ…»
📆 ጷግሜን 📆
🦅 ክፍል ሁለት 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
☞☞ የጳጉሜን 5 ምስጢር
📚 አራቱ የዓመት ወቅቶች ማለትም መፀው፣ ሐጋይ፣ ጸደይና ክረምት 91, 91 ቀናት የሚኾኑት ከጳጒሜን 1 አንድ ዕለት እየተሰጣቸው ሲኾን በአጠቃላይ 364 ዕለታት ወይም 52 ሳምንት ኾኖ አንዲት ዕለት ትተርፋለች፤ ይቺም ጳጒሜን 5 ስትኾን በኢትዮጵያ ቀደምት የዘመን ቀመር ሊቃውንት “ዕለተ ምርያ፣ አዕዋዲት” ትባላለች፡፡
📚 ዕለተ ምርያ ማለት ዕለተ መድኀኒት ማለት ነው፤ ምክንያቱም ጳጒሜን 5 የመድኀኒታችን ክርስቶስ ልደትን የምናውቅባት ስለኾነች ነው፤ ይኸውም ጳጒሜን 5 በዋለችበት ዕለት የክርስቶስ ልደት ዕለት በተመሳሳይ መልኩ ይውላል፡፡
📚 ለምሳሌ የዚኽ ዘመን ጳጉሜን 5 ዕለት ማግስተ ሰኞ ናት፤ በተመሳሳይ መልኩ የ2012 የጌታችን የልደት በዓል ታኅሣሥ 29 ማግስተ ሰኞ ይውላል፡፡ በዚህ ምክንያት ዕለተ ምርያ የሚል ሥያሜ ሊሰጣት ችሏል፡፡
📚 በተጨማሪም ጳጒሜን 5 የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የዐዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደኾነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመኾኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ መዋሉ በእጅጉ ይደንቃል፡፡
~~~ይቀጥላል~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል ሁለት 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
☞☞ የጳጉሜን 5 ምስጢር
📚 አራቱ የዓመት ወቅቶች ማለትም መፀው፣ ሐጋይ፣ ጸደይና ክረምት 91, 91 ቀናት የሚኾኑት ከጳጒሜን 1 አንድ ዕለት እየተሰጣቸው ሲኾን በአጠቃላይ 364 ዕለታት ወይም 52 ሳምንት ኾኖ አንዲት ዕለት ትተርፋለች፤ ይቺም ጳጒሜን 5 ስትኾን በኢትዮጵያ ቀደምት የዘመን ቀመር ሊቃውንት “ዕለተ ምርያ፣ አዕዋዲት” ትባላለች፡፡
📚 ዕለተ ምርያ ማለት ዕለተ መድኀኒት ማለት ነው፤ ምክንያቱም ጳጒሜን 5 የመድኀኒታችን ክርስቶስ ልደትን የምናውቅባት ስለኾነች ነው፤ ይኸውም ጳጒሜን 5 በዋለችበት ዕለት የክርስቶስ ልደት ዕለት በተመሳሳይ መልኩ ይውላል፡፡
📚 ለምሳሌ የዚኽ ዘመን ጳጉሜን 5 ዕለት ማግስተ ሰኞ ናት፤ በተመሳሳይ መልኩ የ2012 የጌታችን የልደት በዓል ታኅሣሥ 29 ማግስተ ሰኞ ይውላል፡፡ በዚህ ምክንያት ዕለተ ምርያ የሚል ሥያሜ ሊሰጣት ችሏል፡፡
📚 በተጨማሪም ጳጒሜን 5 የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የዐዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደኾነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመኾኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ መዋሉ በእጅጉ ይደንቃል፡፡
~~~ይቀጥላል~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
📆 ጷግሜን 📆
🦅 ክፍል ሶስት 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
☞☞ ጳጉሜን 6 እና አመጣጧ
📚 የ6ተኛዋ ጳጒሜን አመጣጥን ስናይ፡- በኢትዮጵያ የዘመን ቀመር ስሌት 1 ዓመት የምንለው 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ወይም 365 ዕለት ከ6 ሰዓት ከ2 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ ነው፡፡ ይህን የየዓመቱን 6 ሰዓት ስንቈጥር የኹለት ዓመት 12 ሰዓት፤ የሦስት ዓመት 18 ሰዓት፤ የአራተኛው ዓመት 24 ሰዓት ወይም አንድ ዕለት ሲሆን ይኸውም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ መጀመሪያ ሲኾን ይኸውም በቀደምት የአቡሻክር ሊቃውንት “መጠነ ራብዒት፣ ሠግረ ዮሐንስ” ትባላለች። ዘመነ ዮሐንስ ተራምዶ የሚያልፍባት ለማለት ነው፡፡
📚 እኛ ጳጒሜን 6 ስናደርግ ምዕራባውያኑ ግን የጳጒሜን ወራትን በማጥፋታቸው ኹሌ ለእነርሱ 28 የኾነችው የካቲትን በአራት ዓመት አንዴ 29 ያደርጋሉ፤ Leap Year ብለው ይጠሯታል፡፡
~~~ይቀጥላል~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል ሶስት 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
☞☞ ጳጉሜን 6 እና አመጣጧ
📚 የ6ተኛዋ ጳጒሜን አመጣጥን ስናይ፡- በኢትዮጵያ የዘመን ቀመር ስሌት 1 ዓመት የምንለው 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ወይም 365 ዕለት ከ6 ሰዓት ከ2 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ ነው፡፡ ይህን የየዓመቱን 6 ሰዓት ስንቈጥር የኹለት ዓመት 12 ሰዓት፤ የሦስት ዓመት 18 ሰዓት፤ የአራተኛው ዓመት 24 ሰዓት ወይም አንድ ዕለት ሲሆን ይኸውም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ መጀመሪያ ሲኾን ይኸውም በቀደምት የአቡሻክር ሊቃውንት “መጠነ ራብዒት፣ ሠግረ ዮሐንስ” ትባላለች። ዘመነ ዮሐንስ ተራምዶ የሚያልፍባት ለማለት ነው፡፡
📚 እኛ ጳጒሜን 6 ስናደርግ ምዕራባውያኑ ግን የጳጒሜን ወራትን በማጥፋታቸው ኹሌ ለእነርሱ 28 የኾነችው የካቲትን በአራት ዓመት አንዴ 29 ያደርጋሉ፤ Leap Year ብለው ይጠሯታል፡፡
~~~ይቀጥላል~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 pinned «ሰላም የዚህ ቻናል ቤተሰቦች በዚህ ጷግሜን ወር ጥያቄና መልስ አዘጋጅተንላችኋል። የጠየቅናቸውን ጥያቄዎች በተደጋጋሚ መመለስ የቻሉትን መዝግበን ጷግሜን 6 ለሁለት ሰዎች ስጦታ አዘጋጅተናል። ጥያቄው ከተለቀቀ በኋላ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት ድረስ ጥያቄዎቹን መመለስ ይቻላል። ከ 4:00 በኋላ መልሱ ዋጋ የለውም። አንድ የመለሰ እንደ አንድ ሶስት የመለሰ እንደ ሶስት በጥያቄው ብዛትና በመለሰው መልስ ብዛት ነጥቡ…»
📆 ጷግሜን 📆
🦅 ክፍል አራት 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
☞☞ ጳጒሜን 7 እና አመጣጧ
📚 የኢትዮጵያን ቀደምት ሊቃውንትን በእጅጉ እንድናደንቅ ከሚያደርገን አንዱ የጳጒሜን 7ትን ስሌት ጠንቅቀው አስልተው በብራና የአቡሻክር መጽሐፍ ላይ ጽፈውልን ስሌቱን አስልተው ማለፋቸው ሲኾን፤ የስሌቱም መጠሪያ “ዕሪና መዓልት ዕሪና ሌሊት” በመባል ይታወቃል፡፡
📚 ይኸውም 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ወይም 365 ዕለት ከ6 ሰዓት ከ2 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ የኾነው የፀሓይ ዐውደ ዓመት የ6 ካልዒት ወይም የ 2 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ ጥርቅም ወይም ከላይ ያየናት የአንዷ ዕለት 0.4 ሰከንድ ጥርቅም ነው፡፡
📚 ስናሰላውም የ5 ዓመቱ 30 ካልዒት፤ የ10ሩ ዓመት 60 ካልዒት (1 ኬክሮስ ወይም 24 ደቂቃ) ይሆናል፡፡ የ100 ዓመት (10 ኬክሮስ) ወይም 240 ደቂቃ (4 ሰዓት) ይኾናል፡፡ የ200 ዓመት 20፤ የ300 ዓመት 30፤ የ400 ዓመት 40 ኬክሮስ፤ የ500 ዓመት 50 ኬክሮስ፤ የ600 ዓመት 60 ኬክሮስ ሲሆን 60 ኬክሮስ ማለት 1440 ደቂቃ ወይም 24 ሰዓት ወይም 7 ተኛዪቱ ጳጉሜን ናት፡፡
📚 ሆኖም ግን የአቡሻሕርና የባሕረ ሐሳብ መምህራን ጳጕሜን 7 የተገኘችው ከጥቃቅን መስፈርት ወገን ከሆነችው ከካልዒት በመሆኑ ሒሳቧ ብቻ ታስባ ድቁቅ ደቃይቅ ተብላ ብቻ እንድትተው በማዘዝ ዕለቷ ግን በኅሊና ብቻ እንድትታሰብ እንጂ ተቆጥራ እንዳትከበር አዘዋል፡፡ በመሆኑም በማሰብ ብቻ እንጂ በዕለትነት ተቆጥራ አትውልም፡፡
📚 በአቡሻሕሩ ስሌት መሠረት እስከ ዛሬ ድረስ 12 ዕሪና መዓልት 12 ዕሪና ሌሊት (ጳጉሜን 7) ተመላልሶ በ1700 ዓ.ም. ወይም በ7800 ዓመተ ዓለም ኾኖ 13ኛው ከተጀመረ 311 ሆኖ በዘመነ ሉቃስ ይኸው ሊፈጸም በ2011 ዓ.ም ካሰላነው 289 ዓመት ይቀራል ወይም በ2300 ዓ.ም. ላይ ይሆናል ማለት ነው፡፡
📚 ይህ በሚሆን ጊዜ ዐቀድ የሚባል ኮከብ አለ፤ ሰሌዳው በፀሓይ ልክ፤ ባሕርዩ ጽሉም ነው፤ ርሱ በ600 ዓመት መጥቶ ፀሓይን ይጋርዳታል፤ ያን ጊዜ ሌሊቱና መዓልቱ ጨለማ ኹኖ ይውላል ያድራል፤ ይኸውም የመከራ ፊት አውራሪ አጫሪ ነው፤ ይኸውም በዐጤ ኢያሱ ወይም ፀሓይ ሰገድ በተባለ በዐጤ ዮስጦስ ጊዜ ተደርጓል ብለው መዝገብውልናል፡፡ ይህን ስናይ የቀደምት ኢትዮጵያውያንን ዕውቀት ሁሌም እንድናደንቅ ያደርገናል፤ መልካም የጳጉሜን 13ኛ ወራት ይሁንልን፡፡
🌼
ለመጪው ዘመን ከቁጥር ሳንጎድል በሰላም በፍቅር ያድርሰን!
~~~ ተፈፀመ ~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል አራት 🦅
የጳጒሜን 5፤ 6 እና 7 አመጣጧ
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
☞☞ ጳጒሜን 7 እና አመጣጧ
📚 የኢትዮጵያን ቀደምት ሊቃውንትን በእጅጉ እንድናደንቅ ከሚያደርገን አንዱ የጳጒሜን 7ትን ስሌት ጠንቅቀው አስልተው በብራና የአቡሻክር መጽሐፍ ላይ ጽፈውልን ስሌቱን አስልተው ማለፋቸው ሲኾን፤ የስሌቱም መጠሪያ “ዕሪና መዓልት ዕሪና ሌሊት” በመባል ይታወቃል፡፡
📚 ይኸውም 365 ዕለት ከ15 ኬክሮስ ከ6 ካልዒት ወይም 365 ዕለት ከ6 ሰዓት ከ2 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ የኾነው የፀሓይ ዐውደ ዓመት የ6 ካልዒት ወይም የ 2 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ ጥርቅም ወይም ከላይ ያየናት የአንዷ ዕለት 0.4 ሰከንድ ጥርቅም ነው፡፡
📚 ስናሰላውም የ5 ዓመቱ 30 ካልዒት፤ የ10ሩ ዓመት 60 ካልዒት (1 ኬክሮስ ወይም 24 ደቂቃ) ይሆናል፡፡ የ100 ዓመት (10 ኬክሮስ) ወይም 240 ደቂቃ (4 ሰዓት) ይኾናል፡፡ የ200 ዓመት 20፤ የ300 ዓመት 30፤ የ400 ዓመት 40 ኬክሮስ፤ የ500 ዓመት 50 ኬክሮስ፤ የ600 ዓመት 60 ኬክሮስ ሲሆን 60 ኬክሮስ ማለት 1440 ደቂቃ ወይም 24 ሰዓት ወይም 7 ተኛዪቱ ጳጉሜን ናት፡፡
📚 ሆኖም ግን የአቡሻሕርና የባሕረ ሐሳብ መምህራን ጳጕሜን 7 የተገኘችው ከጥቃቅን መስፈርት ወገን ከሆነችው ከካልዒት በመሆኑ ሒሳቧ ብቻ ታስባ ድቁቅ ደቃይቅ ተብላ ብቻ እንድትተው በማዘዝ ዕለቷ ግን በኅሊና ብቻ እንድትታሰብ እንጂ ተቆጥራ እንዳትከበር አዘዋል፡፡ በመሆኑም በማሰብ ብቻ እንጂ በዕለትነት ተቆጥራ አትውልም፡፡
📚 በአቡሻሕሩ ስሌት መሠረት እስከ ዛሬ ድረስ 12 ዕሪና መዓልት 12 ዕሪና ሌሊት (ጳጉሜን 7) ተመላልሶ በ1700 ዓ.ም. ወይም በ7800 ዓመተ ዓለም ኾኖ 13ኛው ከተጀመረ 311 ሆኖ በዘመነ ሉቃስ ይኸው ሊፈጸም በ2011 ዓ.ም ካሰላነው 289 ዓመት ይቀራል ወይም በ2300 ዓ.ም. ላይ ይሆናል ማለት ነው፡፡
📚 ይህ በሚሆን ጊዜ ዐቀድ የሚባል ኮከብ አለ፤ ሰሌዳው በፀሓይ ልክ፤ ባሕርዩ ጽሉም ነው፤ ርሱ በ600 ዓመት መጥቶ ፀሓይን ይጋርዳታል፤ ያን ጊዜ ሌሊቱና መዓልቱ ጨለማ ኹኖ ይውላል ያድራል፤ ይኸውም የመከራ ፊት አውራሪ አጫሪ ነው፤ ይኸውም በዐጤ ኢያሱ ወይም ፀሓይ ሰገድ በተባለ በዐጤ ዮስጦስ ጊዜ ተደርጓል ብለው መዝገብውልናል፡፡ ይህን ስናይ የቀደምት ኢትዮጵያውያንን ዕውቀት ሁሌም እንድናደንቅ ያደርገናል፤ መልካም የጳጉሜን 13ኛ ወራት ይሁንልን፡፡
🌼
ለመጪው ዘመን ከቁጥር ሳንጎድል በሰላም በፍቅር ያድርሰን!
~~~ ተፈፀመ ~~~
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ጷግሜን 6
የመጨረሻዋ የ2011 ቀንን ከተቀያየማችሁት ሰው ጋር ይቅርታ እንድትጠያየቁ፣ አሮጌውን ወደጎን እንድትጥሉ በቻናላችን ስም እንጠይቃለን!
የነገ ሰው ይበለን!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
@Readers_To_Know
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የመጨረሻዋ የ2011 ቀንን ከተቀያየማችሁት ሰው ጋር ይቅርታ እንድትጠያየቁ፣ አሮጌውን ወደጎን እንድትጥሉ በቻናላችን ስም እንጠይቃለን!
የነገ ሰው ይበለን!
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
@Readers_To_Know
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
🗓 የዘመን አቆጣጠር በኢትዮጵያ 🗓
ዘመን የሚለካው የጸሐይንና ጨረቃን እንቅስቃሴ መሰረት አድርጎ ዕለት፣ ወር እና ዓመት በሚል መስፈሪያ ተጠራቅሞ ነው::
ዕለት ፦ አንድ ዕለት ማለት አንድ የብርሃን እና አንድ የጨለማ ክፍለ ጊዜ ያለው ሲሆን ጸሐይ አንድ ግዜ ከወጣች በኋላ ተመልሳ እስክትወጣ ድረስ ያለውን ጊዜ
የያዘ ነው:: በሌላ አባባል ምድር በራሷ ዛቢያ አንድ ጊዜ ያምትሽከረከርበት ጊዜ ነው::
ወር ፦ አንድ ወር ማለት ሙሉ ጨረቃ ከወጣች በኋላ ድጋሚ ሙሉ ሆና እስከምትወጣ ድረስ ያለው ጊዜ ነው:: ይህም ጨረቃ መሬትን አንድ ጊዜ ዞራ ለመጨረስ የሚፈጅባት ጊዜ ሲሆን 29.5 ዕለታት ማለት ነው::
ዓመት፦ አንድ ዓመት ማለት መሬት በጸሐይ ዙሪያ ለመዞር የሚፈጅባት ጊዜ ሲሆን 365 ዕለታት ከሩብ ያህል ነው::
የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠርም እነዚህን መስፈሪያዎች በመጠቀም 30 ዕለታት ያሉዋቸው 12 ወራት (መስከረም፣ ጥቅምት፣ ህዳር፣ ታህሳስ፣ ጥር፣ የካቲት፣ መጋቢት፣ ሚያዚያ፣ ግንቦት፣ ሰኔ፣ ሐምሌ እን ነሐሴ) እና 5 (በየ4 ዓመታት ደግሞ 6) ዕለታት ያሏት 13ኛ ወር (ጷግሜን) ዑደት ይጠቀማል:: ለዚህም ነው ኢትዮጵያ የ13 ወር ባለቤት የምትባለው::
የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሃይማኖታዊ ይዘት ሲኖረው መነሻ የሚያደርገውም የክርስቶስን ልደት ነው:: ዘመናቱም በሐዋርያት ተሰይመው በአራት መደባት ይዞራሉ፤ ዘመነ ማቴዎስ፣ ዘመነ ማርቆስ፣ ዘመነ ሉቃስ(ጷግሜን 6 ዕለታት የሚሆንበት) እና ዘመነ ዮሐንስ ናቸው:: አዲስ ዘመን የሚጀምረውም መስከረም 1 ነው::
ምንጭ – መስከረም 2004 አዲስ ጉዳይ መፅሄት እትም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼 እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ 🌼
🌼ዮሐንስ በሰላም አደረሳችሁ 🌼
🌼 አደረሰን! 🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ዘመን የሚለካው የጸሐይንና ጨረቃን እንቅስቃሴ መሰረት አድርጎ ዕለት፣ ወር እና ዓመት በሚል መስፈሪያ ተጠራቅሞ ነው::
ዕለት ፦ አንድ ዕለት ማለት አንድ የብርሃን እና አንድ የጨለማ ክፍለ ጊዜ ያለው ሲሆን ጸሐይ አንድ ግዜ ከወጣች በኋላ ተመልሳ እስክትወጣ ድረስ ያለውን ጊዜ
የያዘ ነው:: በሌላ አባባል ምድር በራሷ ዛቢያ አንድ ጊዜ ያምትሽከረከርበት ጊዜ ነው::
ወር ፦ አንድ ወር ማለት ሙሉ ጨረቃ ከወጣች በኋላ ድጋሚ ሙሉ ሆና እስከምትወጣ ድረስ ያለው ጊዜ ነው:: ይህም ጨረቃ መሬትን አንድ ጊዜ ዞራ ለመጨረስ የሚፈጅባት ጊዜ ሲሆን 29.5 ዕለታት ማለት ነው::
ዓመት፦ አንድ ዓመት ማለት መሬት በጸሐይ ዙሪያ ለመዞር የሚፈጅባት ጊዜ ሲሆን 365 ዕለታት ከሩብ ያህል ነው::
የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠርም እነዚህን መስፈሪያዎች በመጠቀም 30 ዕለታት ያሉዋቸው 12 ወራት (መስከረም፣ ጥቅምት፣ ህዳር፣ ታህሳስ፣ ጥር፣ የካቲት፣ መጋቢት፣ ሚያዚያ፣ ግንቦት፣ ሰኔ፣ ሐምሌ እን ነሐሴ) እና 5 (በየ4 ዓመታት ደግሞ 6) ዕለታት ያሏት 13ኛ ወር (ጷግሜን) ዑደት ይጠቀማል:: ለዚህም ነው ኢትዮጵያ የ13 ወር ባለቤት የምትባለው::
የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሃይማኖታዊ ይዘት ሲኖረው መነሻ የሚያደርገውም የክርስቶስን ልደት ነው:: ዘመናቱም በሐዋርያት ተሰይመው በአራት መደባት ይዞራሉ፤ ዘመነ ማቴዎስ፣ ዘመነ ማርቆስ፣ ዘመነ ሉቃስ(ጷግሜን 6 ዕለታት የሚሆንበት) እና ዘመነ ዮሐንስ ናቸው:: አዲስ ዘመን የሚጀምረውም መስከረም 1 ነው::
ምንጭ – መስከረም 2004 አዲስ ጉዳይ መፅሄት እትም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼 እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ 🌼
🌼ዮሐንስ በሰላም አደረሳችሁ 🌼
🌼 አደረሰን! 🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#share #comment #participate
@R_e_a_d_e_rs
@Let_us_read_bot
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚