ነጠብጣብ...
1.08K subscribers
45 photos
3 videos
9 links
Brick by brick rebuild yourself!
Download Telegram
✒️#ሎሬት_ፀጋዬ_ገብረመድህን

አህያ ሁን አለኝ፡ አህያ ሆንኩለት
አሰሱን ገሰሱን፡ እንድሸከምለት።
መጓዣ ሁን ብሎ፡ ፈረሱ አደረገኝ
በየዳገቱ ላይ፡ ወስዶ ሚጋልበኝ።
እንጃ ግን ሰሞኑን፡ በግ ነህ ተብያለው
ሊያርደኝ ነው መሰለኝ፡ አሁን ፈርቻለው። 
1👍1
#እኔ_ምን_ልበላት ?💔

አትሆንም ሲሉኝ ትሆናለች ብዬ
እንዳለችኝ ሁኘ ራሴን ገድዬ
ተው ስትለኝ ትቸ ስትልከኝ ተልኬ
ለታላቁ ፍቅር ብኖር ተንበርክኬ😊
ልቧ እየሸፈተ ውጭ ውጭ ሲላት
#ከሌላ ሰው ሳያት ምነው ውዴ ብላት
ውሻ ነህ አለችኝ እኔ ምን ልበላት😡

ላመስግናት እንጅ ከፊቷ አቀርቅሬ
ስጠብቅ በኖርኩኝ በቃላ ታስሬ
ማነው እንደ ውሻ #ታማኝ በዚች አለም
ዘብ ሁኖ ያደረ ሰው ተኝቶ ሲያልም
#ከሰጡት ተሸንጋይ ካጣ #ፆም አዳሪ
ካልነኩት የማይነካ ወዳጁን #አክባሪ
ይኸ አይደለም ወይ ውሻ ስሙ የተሰጠኝ ስድቧን አልጠላውም ግን ለሷ ስም ጠፋኝ

ድመት እንዳልላት!
ድመት የባለቤት ቤት ሸም ሸምሞት ያድራል
የወደደ መስሎ #ለሆዱ ይኖራል

አህያ እንዳልላት
አህያም #የዋህ ነች ከያዝዋት በመላ
አምነው የጫኗትን #ዞራ የማትበላ‼️

እሷ ግን?
እሷ በላች አሉኝ ሙልጭልጭ ሳሙና
ብቻየን ቁጭ ብየ ስም ስመርጥ አዩና
እኔ ልሙት ባለ ሳሰቶ በተጎዳ
ገመናን ደብቆ ቆሻሻን #ባፀዳ
ሳሙና አልላትም ለሰው ሙታ #አታውቅም☹️
ስትበር ያያት ሁሉ አሞራ ይበላት
የሳቀላት ሁሉ ወዳጅ ከመሰላት
ጅቡ ይብላት እንጅ እኔ ምን ልበላት!🤷‍♂
👍5
አንዳንድ ሰዎች የሌሎችን ድክመት በመናገር ራሳቸውን ጠንካራ ያስመስላሉ። ሰው ጉብዝናህን በሹክሹክታ ድከመትህን በኡኡታ ያወራልና አትጨነቅ! አስተዋይ ሰው ሁን። እንዲሁም ብትችል ዝም በል። ያለበለዚያ ግን ያንተን ማንነት ከጀርባህ ሸሽገህ ስለ ሰው አታውራ!❞


   ❝በስንዴው ማሳ ላይ እራሳቸውን ከፍ ከፍ ያደረጉ ሁሉ እንክርዳዶች ናቸውና ራስክን አታቀርቅር!። ምንም ቢሉህ ደካማ አስተሳሰብ ያለውን ሰው እዘንለት እንጂ አትዘንበት። ምክንያቱም የሚያስበው የሚያውቀውን ያህል ነው። እሱን በመጥላት የምታባክነውን ጊዜ ራስህን ውደድበት!❞

              
👌21
አንዲት ወይዘሮ በባቡር ጉዞ ላይ ሳሉ አጠገባቸው ባለው ወንበር ላይ የተቀመጠ ሻንጣ ስለነበር አንድ ሠራተኛ መጥቶ ይህ ወንበር ለሰው መቀመጫ እንጂ ለዕቃ ማኖሪያ አይደለም የተሰራው እባክዎ ያንሱ ሲላቸው ‹‹አላነሳም›› አሉት፡፡

‹‹ቢያነሱ ይሻላል እምቢ ካሉ ለአለቃዬ እነግራለሁ›› ቢላቸውም ‹‹ሂድ ንገረው›› በማለት በአቋማቸው ፀኑ፡፡ ሂዶ ሲነግረው አለቅየው መጥቶ "ያንሱ እንጂ ለምን አላነሳም ይላሉ?" ብሎ ቢነግራቸውም ‹‹አላነሳም›› በሚለው ሀሳባቸው የማይበገሩ ሆኑበት፡፡

በመጨረሻም ለዋናው ሃላፊ ተነግሮት ይመጣና ‹‹ይህን ሻንጣ ያንሱ›› ሲላቸው ‹‹አላነሳም›› አሉት፡፡ ዋና ኃላፊውም ‹‹ለምን?›› ሲላቸው ‹‹ገና አሁን አዋቂ ሰው መጣ፡፡ እኔ የቸገረኝ እኮ እስካሁን ድረስ ‹‹ለምን›› ብሎ የጠየቀኝ ባለመኖሩ ነበር፡፡ አንተ ‹‹
#ለምን ?›› ስላልከኝ አመሰግናለሁ፡፡ በመሠረቱ ግን ሻንጣው የእኔ አይደለም ሲሉት በመደነቅ ይቅርታ ጠየቃቸው፡፡

አብዛኞቻችን በሰዎች ላይ በደፈናው እንፈርዳለን፡፡ ነገር ግን ሁሌም በደፈናው ከመፍረዳችን በፊት "ለምን?" ብሎ መጠየቅም እውቀት ነው።
         
                 
👍6
ግማሹ ኩራተኛ ነው ይልሃል፡፡ ሌላው እንደርሱ ያለ ትሁት ሰው ገጥሞኝ አያውቅም ይላል፡፡ አንዳንዱ ገና ስምህ ሲነሳ በርግጎ ይጠፋል፤ ሌላው ስላንተ አውርቶ አይጠግብም፡፡ ከፊሉ ያንተን መገኛ ሲያስስ ይውላል፤ ሌላው አንተ ያለህበት ምቾት አይሠጠዉም ይሸሻል፡፡

በአንድ አቋምህ ብቻ አንቅረው የተፉህ እንዳሉ ሁሉ፤ በአንድ አቋምህ የተነሳ ከልባቸው ሊያወጡህ የተቸገሩ አሉ፡፡ አንዳንዱ ለትችትህ ሲሽቀዳደም ሌላው ሲያድንቅህ ዉሎ ቢያድር አይደክመዉም፡፡ አንዱ እሱ ጥሩ ሰው ነው ሲልህ፤ ሌላው በጣም መጥፎ ነው ብሎ ይሞግታል፡፡ አውቀዋለሁ መልካም ሰው ነው የሚል እንዳለ ሁሉ አታውቁትም መሰሪ ሰው ነው ብሎ የሚከራከርም አለ፡፡ ያለምክንያት እንደሚጠሉህ ያሉ ሁሉ ያለምክንያት የሚወዱህም ብዙ ናቸው፡፡

ይህ ሁሉ አንድ እንግዲህ አንተው ብቻ ነህ። አንተ አንድ ነህ፤ ሰዎች ላንተ ያላቸው እይታ ግን ብዙ ነው። የተለያየ መልክን ስብእና ይዘህ በሰዎች ልብ ዉስጥ ትኖራለህ፡፡ ሁላችንም እንደዚያው ነን፡፡

አይግረመን፡፡ ብቻ ትክክል ለመሆን እንጣር፣ እውነትን ይዘን እንኑር፣ ከአላህ አንጻር እንሥራ፡፡ ለአላህ ስንሠራ የሰዎችን ጉዳይ የሚያስተካክልልን እሱ ነው፡፡ ይገርማል የአላህ ሥራ፡፡

©Muhammed Seid Abx
1👍1
ከጥሩ ጋር ዋል ጥሩ ትሆናለህ..!

አንድ አባት ከስራ ቦታው ሲመለስ ልጁን ከቦዘኔ ልጆች ጋር ሲጫወት ያየዋል ልጁን ጠራውና ልጄ ተው ከነሱ ጋር አትዋል ያበላሹሀል አለው።  ''ኧረ አባቴ  እኔ ከነሱ ጋር ጨዋታ ብቻ ነው ምጫወተው እነሱ ሚሰሩትን መጥፎ ስራ አልሰራም'' ሲል መለሰለት እና በተደጋጋሚ ቢመክረውም እንቢታውን ቀጠለበት። አባት ከቀናት ቡሀላ ከስራ ሲመለስ በካኪ ወረቀት የሆነ ነገር ይዞ መጣ እና እንካ ሳጥን ላይ አስቀምጠው ብሎ ሰጠው።

ልጁም አባቱ ያመጣውን ለማየት ጓጓና ከፍቷ አየው ልጁ ተደሰተ ያለበሰለ ፖም ነበር በዛ ላይ አንዷ ፍሬ ተበላሽታለች አና ላውጣት ተበላሽታለች ሲል አባቱን ጠየቀው አይ ተወው ዝም ብለህ አስቀምጠው አለው። እናም ከሳምንት በኋላ እስቲ ያንን ያስቀመጥከውን ነገር አምጣው አለው እናም ልጁ በጉጉት ይጠብቅ ስለነበር ደስ አለው ፖም እንደሚወድም ስለሚያቅ ልጁም ተስፈንጥሮ ተነስቷ አመጣና በጉጉት እና በተስፋ ካኪውን ከፈተው።

ነገር ግን ሁሉም የፖም ፍሬዎች ተበላሽተው ነበር ልጁ በጣም ተናደደና አየሀ አባዬ ያኔ የተበላሸውን የፖም ፍሬ ላውጣው ስለህ እሺ ብትለኝ ኖሮ ሁሉም አይበላሽም አለው አባትም ሌላ ካኪ ወረቀት አመጣና ሰጠው አሁንም ደስ ብሎት ከፍቶ ሲያይ ፖም ነበር ነገር ግን አባቱ አሁንም ያመጣው አልበሰለም እና ልጅ አልበሰለም እኳ ሲል ጠየቀው  አባትም አዎ  ሂድ ሳጥኑ ላይ አስቀምጠው አለው ልጅም እሺ ብሎ ከማስቀመጡ በፊት የተበላሸ እንደሌለው አረጋግጦ አስቀመጠው።

አሁንም ከሳምንት ቡሀላ አባት እስቲ ያንን ነገር አምጣው አለው ልጅም በደስታ እና በፍርሀት ስሜት ውስጥ ሆኖ ካኪውን አመጣው የፈራው እንደበፊቱ እንዳይበላሽ በመስጋቱ ሲሆን ደስ ያለው ደሞ ፖም ስለሚወድ ነበር እና ልጅ ካኪውን ከፈተው ማሻአላህ ሁሉም ሳይበላሽ በስለው ነበር ልጅም በጣም ደስ ተሰኘ እና  አባት ያኔ ፖም ለምን የተበላሸ ይመስልሀል? ሲል ጠየቀው ልጅም "አንዱ ተበላሽቶ ስለነበር ሁሉንም አበላሻቸው እኔ ላውጣው ስልህ ባወጣው ኖሮ ሁሉም አይበላሽም ነበር" አለው።

አባትም  "አየህ እኔም ከመጥፎ ጓደኞች ጋር አትዋል ምልህ ለዚ ነው ልክ እንደ ፖሙ ሁሉ አንተንም በጊዜ ሂደት  እንዳያበላሹህ ነው የተበላሸውን ፖም ላውጣው ስትለኝ አውጣው ብልህ ኖሮ ሁሉም አይበላሽም ነበር አንተም ከመጥፎ ጓደኞች ጋር አትዋል ስልህ ካልዋልክ አትበላሽም ነገር ግን የኔን ምክር ችላ ብለህ ከነሱ ጋር ከዋልክ በጊዜ ሂደት እንደነሱ መሆንህ አይቀርም : በሌላ ቀን የመጣሁት ፖም ደግሞ ያልተበላሸው በአጠገቡ የተበላሸ ነገር ሰለሌለ ነው ከጥሩ ነገር ጋር ስላለ ነው ሰለዚህ አንተም ከጥሩ ጋር ከዋልክ ጥሩ ትሆናለህ"።  "ከጥሩ ከዋልክ ጥሩ ትሆናለህ: ከመጥፎ ጋር ከዋልክ መጥፎ ትሆናለህ
።" ©Niha
👍7
"በህይወትህ ውስጥ የሚመጡ ነገሮች በሙሉ የራሳቸው ምክንያት አላቸውና አምነህ ተቀበል፡፡ ሀዘን ባታይ የደስታን ትርጉም አታውቅም እና ሁሉም ነገሮች በግዜና በቦታቸው አስፈላጊ ናቸው፡፡"
👍3
ድሆች  ከቆሻሻ ስፍራ አንስተው መብላት የሚያቆሙት አንዳንድ ቆሻሻ ሃብታሞች የድሆችን ምግብ መብላት ሲያቆሙ ነው።
ይሄ ደግሞ ለናንተ ነው። ሰውን በቀላሉ ለምትንቁት። ስትፈልጉኝ ስለተገኘሁላችሁ፣ስትደውሉ ቶሎ ስላነሳሁ፣ስትፅፉልኝ በሰዓቱ ስለመለስኩላችሁ ብቻ ዋጋዬ ለወረደባችሁ። ድሮም ጀበናን መታቀፍ ትርፉ ማደፍ ነው። ቦታ ስሰጣችሁ መራገጥን ተለማመዳችሁብኝ። እያወቅኩ እንዳላወቅኩ ሆኜ በኖርኩ፤ስለኔ ዕፀፅ ብቻ ስትነዙ ታዝቤ ባለፍኩ ዋጋዬ ቀነሰባችሁ...? አደፋችሁብኝ!
👍3😢1💔1
Selfishness ( ራስ ወዳድነት )

ራስን መወደድ ማለት ሲሆን ፤ ራስን ብቻ ማገልገል ፣ ለራስ ጥቅም ብቻ መኖር ፤ ራስን ብቻ አሸናፊ ማድረግ ማለት ነው። ራስ ወዳድ ሰው ጥቅመኛ ስለሆነ ፤ ምንም ነገር ሲያደርግ የሚያገኘውን ጥቅም ያሰላል። አልፋና ኦሜጋው ጥቅምና ጥቅም ብቻ ነው። ራስ ወዳድነት ድንበር ሲያልፍ Narcissistic ያደርጋል። ናርሲስቲክ ማለት ራስን ማምለክ ነው።

Ego ( ግለ -ግነት )

ለራስ ከፍተኛ እና የገዘፈ አመለካከት መላበስ ማለት ነው። ሁሉንም ነገር ለእኔ ብቻ የሚል ፣ ሁሉንም ነገር ማግኘት አለብኝ ብቻ ሳይሆን ይገባኛል ብሎ የሚያስብ ፤ እኔ የተሻልኩ ነኝ ፣ እኔ እችላለሁ በማለት ራሱን በማስተዋወቅ (Self promotion) የሚደክም ማለት ነው። ኢጎ ድንበር ሲያልፍ ደንታ ቢስ (Careless) ያደርጋል። የኢጎ ህይወት ፤ የውሸት ትወና ( Pseudo action ) ይበዛበታል። ያልሆንኩት ነኝ በማለት ፣ በእያንዳንዱ ተግባሩ ግነትን ማስከተል ይወዳል። ከሌላው የተሻለ ለመምሰል ሁሉንም አይነት ውሸት ይጠቀማል። አንዳንዴ የውሸት ትወናው ሰዎች እስኪቀኑበት ይደርሳል። እራስህን ፈትሽ!
👍1
በዚህ ዓለም ስትኖር አስመሳይ ከሆንክ አንተ ለሰዎች ሀቀኛ (ትክክለኛ) ሰው ነህ ። ሁሌ እውነትን ብቻ ይዘህ ብትጓዝ አንተ ለሰዎች ውሸታም ነህ። ካስመሰልክ ከሰዎች ጋር በሰላም ትኖራለህ ። እምቢ ካልክ ትገለላለህ።

ከሰዎች ጋር በሰላም ትኖራለህ ማለት ግን ከራስህም ጋር በሰላም ትኖራለህ ማለት አይደለም። ለራስህ ባዕድ ነህ። ከሰው መሃል ሆነህ ከራስህ ተገልለሃል። እያንዳንዱ ድርጊትህ ከራስህ ወይም ከሌላው ይለይሀል። ልዩነትን ክደህ ለመመሳሰል ማሰብ ማቆም አለብህ። ማሰብ ማቆም ደግሞ ስቃይ ነው ። ይኸው ነው!


@Horizonhope
🔥3
ይቺም ሕይወት ሆና ትዝታ በዛባት።
ለእነርሱ ብለን ሌሎችን እንዳልተውን፤እነርሱም ለሌሎች ብለው እኛን ተውን💔...ይመቻቻው!
አትግፉኝ እንጂ እናንተ ከጀመራችሁትማ በኔ ይብሳል ግፍተራው!።
☑️ ልባችሁ ክፉ የማያስብ ከሆነ፣
☑️ ለሰው ስኬት ደስተኛ ከሆናችሁ፣
☑️ ባላችሁ ነገር አመስጋኝ ከሆናችሁ፣
☑️ ሀዘን ጭንቀቱ እንደሚያልፍ የፀና እምነት ካላችሁ፣

እናንተ የስኬት ሰዎች ናችሁ በርቱ!
👍5
እኛን እንዲመርጡ ማስገደድ አንችልም።
☑️ የሳቀህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም።

☑️ አብሮህ የዋለ ሁሉ ወዶህ አይደለም፤ስለ ቸገረውም ሊሆን ይችላል።

☑️ ደስታ ዘላቂ አይደለም። ሀዘንም እንደዛው። ታገስ!

☑️ ልብህን የሰጠሀው በምላሹ ልቡን ላይሰጥህ ይችላል። ብዙ አትጠብቅ!

☑️ ያቀፈህ ሁሉ ወዶህ አይደለም፤በርዶት ይሆናል። በራስህ ተመካ!

☑️ የናፈቅከውን ሁሉ አታገኝም። እውነታውን አምነህ ተቀበል!
👍2
አንዳንዴ አብዝተን የምንፈልጋቸው ነገራቶች አያስፈልጉንም!። ከነሱ የተሻለ ነው የሚገባን።
👍41
የሚሆን ስለ መሰለን ነበር የለፋ ነው። የሚሳካ ስለ መሰለን ነው ግዜና ጉልበታችንን የገበርንበት። እንጂማ በማይሆን ነገር ማን መድከም ይፈልጋል!።
👍3
ብዙዎቻችን ደጋግመን የሰራነው ስህተት ቢኖር፤ለሰዎች ከሚገባቸው በላይ ቦታ መስጠታችን ነው። እራሳችንን እንድናጣ አድርጎናል። ሳናስበው ከከፍታችን ላይ ወርደን ተገኝተናል። አሁን ግን በቃ የምንልበት ግዜው ነው። ጉዞ ወደ እራስን ፍለጋ...

       
ከፍታ ላይ ስሆን መደወል አቁሙ!። በዝቅታዬ ግዜም 'ኮ ስልኬ ነበራችሁ። በሁለት እግሬ ከቆምኩ በኋላ የናንተ እጀባ አያሻኝም!።