Natnael Mekonnen
173K subscribers
28.8K photos
2.9K videos
27 files
6.42K links
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአንድ ቀን የስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲትን ዛሬ ረፋድ ላይ ተቀብለዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በተካሄደው ስብሰባ ወቅት መሪዎቹ በሁለትዮሽ ጉዳዮች በንግድ፣ በመሰረተ ልማት ዝርጋታ እንዲሁም በቀጠናው ሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
“ተግዳሮቶች ያልበገረው ለውጥ” ብለን የጀመርነውን የ2015 በጀት ዓመት አፈፃፀም ግምገማችንን ዛሬ አጠናቅቀናል።

በ2015 በጀት ዓመት ውጤት ያገኘንባቸው ስራዎቻችን የምንረካባቸው ሳይሆኑ የጀመርናቸውን በማስፋት የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል፣ ለኑሮ ምቹ፣ ተወዳዳሪና የኢትዮጵያ ብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ከተማ ለመገንባት ይበልጥ ተነሳሽነት የፈጠርንባቸው ነበሩ።
የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓታችንን ቀልጣፋና ፍትሃዊ ለማድረግ የጀመርናቸው የሪፎርም ስራዎችን በማጠናከር፣ ፍትሐዊ አገልግሎት ለህዝባችን ለማድረስ፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራርን በማስተካከልና አገልግሎት አሰጣጣችንን በቴክኖሎጂ በማስደገፍ ረገድ መሻሻል ቢኖርም በቀጣይ ትኩረት ሰጥተን የምንሰራው ስራ ይሆናል።

ለውጡ ህዝብ ፈልጎ ያመጣውና የሚደግፈው በመሆኑ ተግዳሮት የሚያደናቅፈው አልሆነም።
እኛም ይህን የህዝባችንን እምነት ጉልበት በማድረግ፣ የአመራራችንን አቅም በማጎልበት እና ለህዝብ የሚወግኑ ተቋማትን እየገነባን የነዋሪዎች የዘመናት ጥያቄ የሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እና የኑሮ ጫናን የሚያቀሉ ፕሮጀክቶች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥተን መስራታችንን እንቀጥላለን።
የከተማችንን ሰላም ለማስከብር ከሰላም ወዳዱ ህዝባችን ጋር በመሆን ነዋሪዎቻችን በሰላም ወጥተው በሰላም የሚገቡባት ከተማ መሆኗ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ ለፀረ ሰላም ኃይሎች በእብሪት የሚመጣ ስልጣን እንደሌለ አሁንም ከተማችን ጥሩ ማሳያ ትሆናለች።

ጽንፈኝነትና አክራሪነት በተግባር በህብረ ብሄራዊ ወንድማማችነት የተሸነፈባት፣ ሰላምዋ በዘላቂነት በህዝብ ተሳትፎ የተረጋገጠላትና ለሁሉም የምትመች፣ እንደስምዋ የተዋበች አዲስ አበባን እውን ለማድረግ በትጋት ማገልገላችንን እንቀጥላለን።
በመሀል ከተማ ካሳንችስ ላይ የሚገኝ ቅንጡ አፓርታማ ከኮፊ ፕላዛ

📌 በወንዝዳር ፕሮጀክቶች ፣ በባለ ኮከብ ሆቴሎች ፣ አለም አቀፍ ድርጅቶች እና ተቋማት የተከበበ
     
የመኝታ ቤት አማራጮች

ባለ 1 መኝታ፡ 66 ካሬ ሜ
(ጥቂት ቤቶች ብቻ ነው የቀሩን)

ባለ 3 መኝታ፡ 176 ካሬ ሜ

ባለ 3 መኝታ፡ 204 ካሬ


📌 በወለል (በፍሎር) ከ3 ቤቶች ብቻ 

📌 ቢገዟቸው በዶላር የሚያከራዩዋቸው ለውጭ ሀገር ዜጎች ለኪራይ ተመራጭ እንዲሆኑ ታስበው የተገነቡ

📌 ለኤሌክትሪክ መኪናዎች ቻርጂንግ ስቴሽን ያለው

📌 ደረጃቸውን የጠበቁ ሰፋፊ ሊፍቶች


📌 ቅድመ ክፍያ 30% ብቻ ከፍለው ቀሪውን 70% በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ዘና ብለው የሚከፍሉት፤


 ለበለጠ መረጃ በ 0947743496 ይደውሉ በቴሌግራም @Realtorhenookk በዋትሳፕ ይደውሉ
ለተጨማሪ ቤት ፍላጎቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@Realtorhenook
አየር መንገዱ ስምንት አዳዲስ የመንገደኛ አውሮፕላኖችን በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚረከብ ተገለጸ!!

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ካዘዛቸው 26 አውሮፕላኖች ውስጥ ስምንቱን በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚረከብ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ገልጸዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አየር መንገዱ ተጨማሪ 26 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግና ከኤርባስ ከተሰኙ ግዙፍ የአውሮፕላን አምራች ኩባንያዎች ድርድር በማድረግ ላይ እንደሆነ ጠቁመዋል። ከተገዙት አውሮፕላኖች መካከል አየር መንገዱ ስምንት የመንገደኛ አውሮፕላኖች በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚረከብም ነው የገለጹት።

ቀሪዎቹ የመንገደኞች አውሮፕላኖች በቀጣይ ጊዜያት እንደሚገቡ ገልጸው፤ አየር መንገዱ ሌሎች ተጨማሪ አውሮፕላኖችን ለማስገባት እቅድ እንዳለው ተናግረዋል።

በሌላ በኩል አየር መንገዱ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ የመዳረሻ ሥፍራዎችን ከማስፋት አኳያ በቀጣይ ጥቅምትና ሕዳር ስድስት የበረራ መዳረሻዎች እንደሚጨምር ተናግረዋል። እነዚህ የበረራ መዳረሻዎች በአብዛኛው የአውሮፓ አገራትን እንዲሁም አንድ አፍሪካ አገርን ትኩረት እያደረገ መሆኑን በመጠቆም፤ ስፔን ማድሪድ፣ እንግሊዝ ለንደን-ጋትዊክ፣ ኔዘርላንስ አምስተርዳም፣ ቬትናም ሃኖይና ማዕከላዊ አፍሪካ ባንጓይ የአየር መንገዱ አዳዲስ መዳረሻዎች እንደሚሆኑም ገልጸዋል።

አየር መንገዱ በተያዘው በጀት ዓመት ገቢውን በ22 በመቶ ለማሳደግ እቅድ ይዞ እየሰራ መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ለዚህም ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩን ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአሁኑ ወቅት 145 አውሮፕላኖች ያሉት ሲሆን፤ 134 ዓለም አቀፍና 22 የአገር ውስጥ መዳረሻዎች አሉት።
በሽብር ቡድኖች፣ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርና በሙስና ተሳትፈዋል የተባሉ ከ3 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

ዓመታዊ አፈፃፀሙን በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

ሀገራዊ፣ አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን የተመለከቱ መረጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን የደኅንነት ሥጋቶችን አስቀድሞ የሚያከሽፍ፤ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆነ ፕሮፌሽናል ተቋም ለመገንባት የሚያስችሉ የሪፎርም ሥራዎች መከናወናቸው ተገልጿል፡፡

ከእነዚህ ስኬታማ ተግባራት ጎን ለጎንም ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የጸጥታ ችግሮች በመፍታት ፈተናዎችን እንድትሻገር ያስቻሉ የተልዕኮ ሥራዎች በበጀት ዓመቱ መከናወናቸው ተገምገሟል።

የአገልግሎቱ ሙሉ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም

በሽብር ቡድኖች፣ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርና በሙስና ተሳትፎ የነበራቸው ከ3 ሺ በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዓመታዊ አፈፃፀሙን መገምገሙንና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ማስቀመጡን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ ሀገራዊ፣ አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን የተመለከቱ መረጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን የደኅንነት ሥጋቶችን አስቀድሞ የሚያከሽፍ፤ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆነ እንዲሁም ፕሮፌሽናል ተቋም ለመገንባት የሚያስችሉ ተከታታይ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡

ከእነዚህ ስኬታማ ተግባራት ጎን ለጎንም ኢትዮጵያ ያጋጠሟትን የጸጥታ ችግሮች በመፍታት ፈተናዎችን እንድትሻገር ያስቻሉ የተልዕኮ ሥራዎች በበጀት ዓመቱ መከናወናቸው ተገምገሟል።

የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አፈጻጸም በተገመገመበት መድረክ በበጀት ዓመቱ ከ9 ሺ በላይ መረጃዎች ተቀምረው እንደ አስፈላጊነታቸው ጥቅም ላይ እንዲውሉ መደረጋቸው ተገልጿል፡፡

በአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ተሰብስበውና ተተንትነው ጥቅም ላይ ከዋሉት ከእነዚህ መረጃዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ የተለያዩ የሽብር ቡድኖች እና ኢመደበኛ አደረጃጀቶች እዚህም እዚያም ለመፍጠር እየሞከሯቸው ያሉ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት የዋሉ መሆናቸው በተቋሙ ዓመታዊ ዕቅድ አፈፃፀም ላይ ተጠቁሟል፡፡

በዚህም በሽብር ቡድኖች፣ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሙስናና በሌሎችም ሕገወጥ እንቅስቃሴዎች ተሳትፎ የነበራቸው ከ3 ሺ በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ተቋሙ በሸኔ የሽብር ቡድን እንቅስቃሴ ላይ ባደረገው መረጃ የማሰባሰብ ሥራ ሁለት ሺ 327 የቡድኑ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውንና አንድ ሺ 849 ታጣቂዎች ላይም ክትትሉ ተጠናክሮ መቀጠሉን እንዲሁም በበርካታ የሽብር ቡድኑ አባላት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ መደረጉ በግምገማው ተመልክቷል፡፡ በቤህነን፣ ጉምዝ፣ ቅማንትና ሎሌች የታጠቁ ቡድኖች ላይም አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ተመሳሳይ የመረጃ ስምሪት ማከናወኑ በግምግማው ተገልጿል፡፡

በተያያዘ ሽብርተኝነትን ለመከላከል ተቋሙ ከውጭ አቻ የመረጃና ደኅንነት ተቋማት ጋር የመረጃ ልውውጥ በማድረግ በንፁሃን ዜጎች ላይ ሊፈፁሙ የነበሩ የሽብር አደጋዎችን በመቀልበስ በዚሁ ሴራ እጃቸው ያለበትን 165 የአልሸባብ አባላት እንዲሁም 121 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉ በግምገማ መድረኩ ተነስቷል፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በተለያዩ ተቋማት ላይ ከተፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች ጋር በተያያዘ መረጃዎችን አጠናቅሮ በማቅረብ 225 ተጠርጣሪዎች እንዲያዙ ሲደረግ፤ በ691 ተጠርጣሪ ግለሰቦች ላይ ደግሞ መረጃ መሰብሰቡንም በተቋሙ የበጀት አመቱ ዕቅድ አመጻጸም ተጠቁሟል፡፡

በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርና የውጭ ምንዛሪ ዙሪያ በተደረገ ክትትልና እርምጃ ከ61 ሚልዮን 781 ሺ በላይ የኢትዮጵያ ብር፤ ከ1 ሚሊዮን 769 ሺ በላይ የአሜሪካ ዶላር፤ ከ509 ሺ በላይ ዩሮና ከፍተኛ መጠን ያላቸው የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡

ከሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ጋር በተያየዘም 295 ግለሰቦች፤ ከሕገወጥ የገንዘብ ምንዛሪ ጋር በተያያዘ ደግሞ 117 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውንም የተቋሙን ዓመታዊ እቅድ አፈፃፀም ግምግማ ዋቢ በማድረግ መግለጫው ይፋ አድርጓል፡፡

44 ኪሎግራም ወርቅን ጨምሮ በርከት ያለ መጠን ያላቸው ልዩ ልዩ ማዕድናት በአየር መንገድ በኩል ወደ ውጭ ሊወጡ ሲሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውም ነው የገለፀው፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በሀገር ውስጥ ከሚገኙ አጋር ተቋማት ጋር በትብብር በመሥራት እንዲሁም ከውጭ ሀገራት አቻ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ሀገራዊ፣ቀጣናዊና ዓለምአቀፋዊ ሥጋቶች እንዲወገዱ ያላሰለሰ ጥረት ማድረጉ በዓመታዊ አፈጻጸሙ እንደተመለከተ የጠቀሰው መግለጫው፤ ተቋሙ የሀገርን ጥቅምና ደኅንነት ለማስጠበቅ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁንም ከድርድርና ውይይት ይልቅ መንግሥታዊ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ የሚጥሩ እንዲሁም አጋጣሚዎችን በማቀነባበር ዝርፊያ ለመፈጸም የሚፈልጉ የታጠቁ ቡድኖች፣ ፅንፈኛና አክራሪ ኃይሎች ከውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ሀገራዊ የጸጥታ ሥጋት ለመደቀን ሙከራ እያደረጉ መሆኑ ተገምግሟል፡፡ ሰሞኑን በአማራ ክልል እየታየ ያለው ሁኔታም ለዚህ አብነት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ቀደም ሲል ከኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል የተከሰቱ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከሚመለከታቸው መንግሥታዊ ተቋማት፣ከሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ጋር ተከታታይ ጥረቶች ቢደረጉም ችግሩ በሚፈለገው መንገድ አልተፈታም ያለው የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ፤ ለዘረፋ የተደራጁ ጥቂት ኃይሎች አሁን ላይ መንግሥታዊ መዋቅሮች እንዲፈርሱ፤የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት እንዲቋርጡ፤ አንዳንድ ከፌዴራል መንግሥት ጋር የሚያገናኙ የመንገድ መሠረት ልማቶች እንዲዘጉ በማድረግ፤ ሕዝቡ ላይ ማኅበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ።

በክልሉ ያጋጠመው የጸጥታ መደፍረስ በመደበኛው የሕግ ሥርዓት ሊታረም የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተከትሎ የአማራ ክልል መንግሥት ባደረገው ጥሪ መሠረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ችግሩን ለመፍታት የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መደንገጉን ያስታወሰው መግለጫው፤ የብሔራዊ መረጃና ደኀንነት አገልግሎትም ዐዋጁን የሚያስፈፅመው የጠቅላይ መምሪያ ዕዝን በማስተባበር የክልሉን ሰላምና ደኅንነትን በአጭር ጊዜ ለማረጋገጥ የሚያግዝ ስምሪት ወስዶ እየሠራ መሆኑን አመልክቷል፡፡

በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በዚህ ሕገወጥ እንቅስቃሴ ውስጥ እየተሳተፉ ያሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ያሳሰበው የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መግለጫ፤ አሁንም ችግሩ በውይይትና በድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ ባለመሆኑ ተከታታይ ጥረቶች እንደሚደረጉ ጠቁሟል፡፡

ከዚህ መንገድ በማፈንገጥ ለዝርፊያ ከተደራጁ ቡድኖች ጋር የሚንቀሳቀሱ አካላት ካሉ በሚጠናቀሩ መረጃዎችና ማስረጃዎች አማካኝነት አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድባቸውና ሕግ የማስከበር ሂደቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡

በክልሉ የሚንቀሳቀሱ እነዚህ ለዘረፋ የተደራጁ ኃይሎች ከሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር ለሀገር ሉዓላዊነት፣ የግዛት አንድነትና ለብሔራዊ ጥቅም መከበር ጉልህ አስተዋጽዖ ሲያበረክት የኖረውን የአማራን ሕዝብ ታሪክ ለማጠልሸት ሞክረዋል፡፡
መላው የክልሉ ነዋሪዎች ግን መንግሥት እያደረገ ያለውን ሕግ የማስከበር እንቅስቃሴ በመደገፍ ሰላማቸውን ለማረጋገጥ እየጣሩ ነው ያለው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መግለጫ፤ ይህንንም አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ለኢፌዴሪ አየር ሃይል እንደተጻፈ ተደርጎ እና በቅንብር ተሰርቶ ማህበራዊ ሚድያ ላይ ስለተሰራጨው ደብዳቤ…
#EthiopiaCheck Fact Check
************
“በአስቸኳይ ሽፋን እንድትሰጡን” በሚል ርዕስ ለኢፌዴሪ አየር ሃይል እንደተጻፈ የሚገልጽ ደብዳቤ ባለፉት ሁለት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያ በስፋት ሲሰራጭ ተመልክተናል። በርከት ያሉ ሰዎችም የደብዳቤውን ትክክለኛነት በተመለከተ አስተያየታቸውን ሲሰጡ አስተውለናል።

ኢትዮጵያ ቼክ የደብዳቤውን ትክክለኛነት ለማወቅ በደብዳቤው ላይ ምርመራ አድርጓል፣ የፎቶፎረንሲክ ፍተሻ አካሂዷል እንዲሁም የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊትን አነጋግሯል።

በደብዳቤው ላይ ባደረግነው ምርመራም በርከት ያሉ ግድፈቶች መኖራቸውን አስተውለናል።

በደብዳቤው ላይ ሌ/ጄነራል ጌታቸው በቀለ የሰ/ምዕ እዝ አዛዥ መሆናቸው ተገልጿል። ነገር ግን የሰ/ምዕ እዝ አዛዥ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ እንጂ ሌ/ጄነራል ጌታቸው በቀለ አይደሉም።

በተጨማሪም በደብዳቤው ላይ “የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ” የሚል ማህተም ያረፈ ሲሆን ይህም ደብዳቤውን ጻፈው ከተባለው የሰ/ምዕ እዝ ጋር የሚጣረስ ነው።

ጉዳዩን በተመለከተ ኢትዮጵያ ቼክ ያነጋገራቸው የኢፌድሪ መከላከያ ሠራዊት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ኮሎኔል ጌትነት አዳነ የተሰራጨው ደብዳቤ “ውሸት ነው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

"ውሸት መሆኑን በአንድ ነገር ብቻ ላረጋግጥ! ጠየቁ የተባሉት ሌ/ጀነራል ብርሃኑ በቀለ ዕዝ አዛዥ ናቸው፡፡ ማህተሙ ግን የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የሚል ነው፡፡ ኮንስትራክሽን ድሮን አይጠይቅም የግንባታ ዕቃ እንጂ! ደግሞም እንኳን ጥያቄ የሌለውን ቢኖር በወታደራዊ የመገናኛ ሬዲዮ ተመስጥሮ እንጅ በእንደዚህ አይነት ዘፈቀደ ደብዳቤ አይደለም" በማለት ሃላፊው አብራርተዋል።

ይህን ደብዳቤ በተመለከተ ኢትዮጵያ ቼክ ስሙ በማህተሙ ላይ የሚታየው የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝን ምላሽም የጠየቀ ሲሆን ደብዳቤው የድርጅቱ እንዳልሆነ የሚገልጽ ምላሽ አግኝቷል።

በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ከፍተኛ የኮሙኒኬሽን ባለሙያ የሆኑት ማርታ ተፈሪ ደብዳቤው “የኛ አይደለም፤ እንደዚህ አይነት ደብዳቤ ከድርጅታችን አልወጣም” ሲሉ ለኢትዮጵያ ቼክ ነግረዋል።

“ደብዳቤው የተደራጀ የደብዳቤ ፎርማት የለውም፤ ፕሮቶኮልም የለውም” ሲሉም ነግረውናል።

ኢትዮጵያ ቼክ ይህንኑ ደብዳቤ በፎቶፎረንሲክ መገልገያ የመረመረ ሲሆን የተነካካ ወይም በቅንብር የተሰራ መሆኑን መመልከት ችሏል።
በመሀል ከተማ ካሳንችስ ላይ የሚገኝ ቅንጡ አፓርታማ ከኮፊ ፕላዛ

📌 በወንዝዳር ፕሮጀክቶች ፣ በባለ ኮከብ ሆቴሎች ፣ አለም አቀፍ ድርጅቶች እና ተቋማት የተከበበ
     
የመኝታ ቤት አማራጮች

ባለ 1 መኝታ፡ 66 ካሬ ሜ
(ጥቂት ቤቶች ብቻ ነው የቀሩን)

ባለ 3 መኝታ፡ 176 ካሬ ሜ

ባለ 3 መኝታ፡ 204 ካሬ


📌 በወለል (በፍሎር) ከ3 ቤቶች ብቻ 

📌 ቢገዟቸው በዶላር የሚያከራዩዋቸው ለውጭ ሀገር ዜጎች ለኪራይ ተመራጭ እንዲሆኑ ታስበው የተገነቡ

📌 ለኤሌክትሪክ መኪናዎች ቻርጂንግ ስቴሽን ያለው

📌 ደረጃቸውን የጠበቁ ሰፋፊ ሊፍቶች


📌 ቅድመ ክፍያ 30% ብቻ ከፍለው ቀሪውን 70% በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ ዘና ብለው የሚከፍሉት፤


 ለበለጠ መረጃ በ 0947743496 ይደውሉ በቴሌግራም @Realtorhenookk በዋትሳፕ ይደውሉ
ለተጨማሪ ቤት ፍላጎቶች የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@Realtorhenook
🎁ለ 1 ሳምንት ብቻ የሚቆይ ልዩ ቅናሽ 🎁

የዘመኑን ልዩ ልዩ የስልክ አማራጮች በቅናሽ ከ HABMART

📲 0913849228 📩 @habworld
የያዙት ስልክ ላይ ጨምረው መቀየርም ይቻላል

📍ቦሌ መድሃኒአለም Selam city mall, ground floor G06
  ልደታ AIA የገበያ ማዕከል , ground floor
For more products @habmartofficial
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🎁ዘመናዊ የበር ስር የንፋስ እና ቆሻሻ መከላከያ 🎁

    🎁 Door Bottom seal strip Stopper 🎁

🔷ቀን ቆሻሻ እና ማታ ንፋስ እየገባ አስቸግሮታል እንግዲያውስ አሪፍ ዘመናዊ እና ለአገጣጠም ቀላል የሆነ መፍትሄ አቅርበንሎታል

🔷በቀላሉ በር ስር በመድፈን ምንም አይነት ቆሻሻ ፣ በራሪ ነፍሳት ፣ አይጥ ና ንፋስ ወደ ቤት ወስጥ እንዳይገባ የሚከላከል በአይጥ እንዳይበላ ኬሚካል የተደረገበት ዘመናዊ የበር መድፈኛ

📍800ብር ☎️ 0961276575 📩 @tedsport1

📌አድራሻ-ቦሌ ት/ቤት ፊት ለፊት አለምነሽ ኘላዛ 014

📍ቴሌግራማችንን በመቀላቀል እቃዎችን ይጎብኙ
https://t.me/tedtech  https://t.me/tedtech
እስካሁን 11 ሚሊየን 882 ሺህ 117 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መጓጓዙን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡
ኮርፖሬሽኑ ለ2015/16 የሰብል ዘመን ከውጭ ከገዛው 13 ሚሊየን 975 ሺህ 520 ኩንታል ውስጥ 96 ነጥብ 4 በመቶው ጂቡቲ ወደብ መድረሱን ገልጿል፡፡
ወደብ ከደረሰው 13 ሚሊየን 475 ሺህ 419 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እስካሁን 11 ሚሊየን 882 ሺህ 117 ኩንታል ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ ተጓጉዟል መባሉን ከኮርፖሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ትናንት 524 ሺህ 670 ኩንታል ዩሪያ የጫነች መርከብ ጂቡቲ ወደብ መድረሷ የተገለፀ ሲሆን÷ የመጨረሻዋ መርከብ ተጨማሪ 500 ሺህ ኩንታል ዩሪያ ጭና በቅርቡ ጂቡቲ ወደብ እንደምትደርስ ይጠበቃል።
ለ2015/16 የሰብል ዘመን ከውጭ የተገዛው የአፈር ማዳበሪያ 13 ሚሊየን 975 ሺህ 520 ኩንታል ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 2 ሚሊየን 788 ሺህ 940 ኩንታል ኤን ፒ ኤስ፣ 5 ሚሊየን 686 ሺህ 580 ኩንታል ኤን ፒ ኤስ ቦሮን እና 5 ሚሊየን 500 ሺህ ኩንታል ዩሪያ መሆኑ ታውቋል፡፡
የመከላከያ እና የልዩ ሃይል ልብስን በመልበስ በወንጀል ድርጊት ላይ ሲሳተፉ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር መዋላቸው ተነገረ፡፡

በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ የመከላከያን እና የልዩ ሃይልን የደንብ ልበስ ለብሰው ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሃብታሙ አሰፋ፣ ግለሰቦቹ ከጅማ እና ከዳውሮ ወደ ወላይታ ሶዶ የሚመጡ መኪናዎችን በማስቆም ዝርፊያ ሲፈፅሙ እንደነበር ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።

ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን ሲፈፅሙ የነበሩት መኪናዎችን አስቁመው በስለት መሣሪያ በማስፈራራት መሆኑን የፖሊሲ አዛዡ ገልጸዋል።
ሃምሌ 17 ከለሊቱ 6 ሰዓት ላይ ወንጀሉን ሲፈፅሙ ከነበሩት መካከል መልካሙ መና እና አለማየሁ ሻንጋ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ተናግረዋል።

የተቀረው አንድ ተጠርጣሪ ያመለጠ ሲሆን የወረዳው ፖሊስ ግለሰቡን ለመያዝ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
ይህ ተግባር በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን የመከላከያ ሃይልን ክብር የሚያወርድ ነው ያሉት ምክትል ኮማንደር ሃብታሙ አሰፋ፣ መሰል ድርጊቶች እንዳይደገሙ አስተማሪ እርምጃ እንደሚሻ ገልጸዋል።

የወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት እንደገለፀው ግለሰቦቹ ከዚህ ቀደምም ተመሳሳይ ድርጊቶች ሲፈፅሙ እንደነበር ተረጋግጧል፡፡
#ኢትዮጵያ

" ደም አፋሳሽ ግጭቶች በአስቸኳይ ይቁሙ "

በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚታዩ ደም አፋሳሽ ግጭቶች በአስቸኳይ ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲቆሙ ጥሪ ቀረበ።

ይህን ጥሪ ያቀረበው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ነው።

ኮሚሽኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ፥ ልዩነቶች እና አለመግባባቶች በንግግርና በምክክር መፍታት ሲገባ በተለያዩ አካባቢዎች እና በተለያዩ ወገኖች እየተወሰዱ ያሉ የኃይል እርምጃዎች የሀገራችን ኢትዮጵያን ደህንነትና ህልውና በመፈታተን ላይ መጥተዋል ሲል አሳውቋል።

ኮሚሽኑ " የተቋቋምኩበትን ተግባርና ኃላፊነት ለመወጣት ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረኩ ባለሁበት በዚህ ወቅት በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየታዩ ያሉ ደም አፋሳሽ ግጭቶች ሥራዬን አዳጋች እያደረጉት ይገኛሉ " ብሏል።

የኮሚሽኑ ምክር ቤት ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ/ም ባደረገው ልዩ ስብሰባ በመላው ሀገራችን የሚታዩ ግጭቶች በአስቸኳይ ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ ቆመው የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ አሉን የሚሏቸውን ልዩነቶች ወይም ጥያቄዎች በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው በምክክር እንዲፈቱ አስቸኳይ ሀገራዊ ጥሪ አቅርቧል።

ለዚህም ተግባራዊነት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለድርሻ አካላትን በማቀራረብ፣ የልዩነት አጀንዳዎችን ሰብስቦ ለማወያየትና ለማመካከር አመቺ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ዝግጁ መሆኑን ያ
አሳውቋል።
🏠145ካሬ ዱፕሌክስ(G+1) አፓርትመንት ለመኖርያ ምቹ በሆነው በCMC

☆3መኝታ ቤቶች + 1 የሰራተኛ ክፍል
☆3 መታጠቢያ ክፍሎች
☆በረንዳ ( balcony) ያለው

እንዲሁም በግቢው ውስጥ
☆ሰፊ መናፈሻ ( Green Area)
☆2 ሊፍት በፍሎር የተዘጋጀለት
☆ተጠባባቂ ጀነሬተር
☆የከርሰምድር ውሀ
☆መዋለ ህፃናት (KG) ያለው ነው

  ቅድመክፍያ 15% ብቻ

⏰️  ውስን ቤቶች ብቻ ናቸው የቀሩን ይፍጠኑ

🔷በተጨማሪም ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚሆኑ ሱቆችም አሉን

ለበለጠ መረጃ
በ +251934159546 @ Whatsapp, Viber, Telegram ወይም ቀጥታ ይደውሉ