የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia
22.8K subscribers
2.2K photos
53 videos
234 links
NEBE
Download Telegram
The National Election Board of Ethiopia (NEBE) held a workshop with the United Nations Development Program (UNDP) on the annual work plan of the (SEEDS2) project.

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) conducted a workshop in collaboration with the United Nations Development Program (UNDP) to develop the annual work plan for the SEEDS2 project. The workshop, held over three days, brought together department heads from NEBE to strategize on activities for the 2025 G.C. under the UNDP-supported SEEDS2 initiative.

The primary goal of the workshop was to enhance NEBE’s institutional capacity in planning and implementing activities effectively. The sessions aimed to ensure that NEBES’ departmental work plans align with the support provided by the SEEDS2 project while fostering a result-oriented approach.

For more https://nebe.org.et/en/node/1097
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፆታዊ ትንኮሳን የተመለከተ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት (procedure) ለሠራተኞቹ አስተዋወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቴክኒክ ቡድን አዋቅሮ አንድ ዓመት በወሰደ ጊዜ ያስጠናውን የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት (procedure) በፌደራል እና በክልል ለሚሰሩ የቦርዱ ጏላፊዎችና ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ጥናት አስተዋወቀ።

በአውደ ጥናቱ በዋንኛነት የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት አስፈላጊነት፣ የፆታዊ ትንኮሳ ባህሪያት እና መገለጫዎች፣ የፆታዊ ትንኮሳ ክስ የሚቀርብበት ሥነ-ሥርዓት፣ የፓሊሲው የተፈፃሚነት ወሰን እና ፆታዊ ትንኮሳ በሚያስከትለው ችግሮች ላይ ገለፃ ተሰጥቶ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

በአውደ ጥናቱ የመክፈቻ ንግግራቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሙያዊ ሥነ-ምግባራቸውን ጠብቀው የሚሰሩ ባለሙያዎች እና ጏላፊዎች ያሉበት ጠንካራ የዲሞክራሲ ተቋም ነው ያሉት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ጏይሉ ይህ የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እንዲወጣ የወሰንበት ዋንኛ ምክንያት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሊፈጠሩ የሚችሉ የፆታዊ ትንኮሳዎችን ለመከላከል ብሎም ደህንነቱ የተጠበቀ የስራ ከባቢን በአስተማማኝ መደላድል ላይ ለመፍጠር ያለመ ነው ብለዋል።

ተጨማሪ ይመልከቱ https://shorturl.at/fYPzr